fa
Feedback
ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

رفتن به کانال در Telegram

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

کانال ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖 (@bookshelf13) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 18 345 مشترک است و جایگاه 1 930 را در دسته کتب و رتبه 1 892 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 18 345 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 17 سپتامبر, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -115 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -1 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 9.51% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 3.71% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 1 745 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 681 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 18 سپتامبر, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته کتب تبدیل کرده‌اند.

18 345
مشترکین
-124 ساعت
-397 روز
-11530 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
سپتامبر '26
سپتامبر '26
+6
در 0 کانال‌ها
اوت '26
+28
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '26
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '26
+12
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '26
+108
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '26
+31
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مارس '26
+16
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '26
+15
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '26
+21
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '25
+36
در 1 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '25
+42
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '25
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '25
+31
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '25
+60
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '25
+44
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '25
+72
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '25
+451
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '25
+460
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '25
+500
در 4 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '25
+317
در 2 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '25
+421
در 1 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '24
+481
در 1 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '24
+275
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+244
در 1 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '24
+254
در 2 کانال‌ها
Get PRO
اوت '24
+307
در 2 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '24
+388
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+231
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+241
در 1 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+354
در 3 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+325
در 2 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+251
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+96
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+184
در 1 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+141
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+96
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '23
+46
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '23
+119
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '23
+158
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '23
+143
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '23
+79
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '23
+59
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '23
+62
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '23
+182
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '23
+195
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '22
+468
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '22
+92
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '22
+399
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '22
+71
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '22
+91
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '22
+205
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '22
+198
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '22
+317
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '22
+718
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '22
+177
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '22
+356
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '22
+36
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '21
+213
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '21
+243
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '21
+908
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '21
+917
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '21
+873
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '21
+219
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '21
+59
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '21
+125
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '21
+430
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '21
+396
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '21
+304
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '21
+354
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '20
+14 056
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
18 سپتامبر0
17 سپتامبر+1
16 سپتامبر0
15 سپتامبر0
14 سپتامبر0
13 سپتامبر0
12 سپتامبر0
11 سپتامبر0
10 سپتامبر+1
09 سپتامبر0
08 سپتامبر0
07 سپتامبر0
06 سپتامبر0
05 سپتامبر+1
04 سپتامبر+2
03 سپتامبر0
02 سپتامبر0
01 سپتامبر+1
پست‌های کانال
2
© Mes Oud
1 961
3
◉ ከሞት ወዲህ [The Denial of Death] ከሞት ወዲያ ምንም የሚታወቅ ነገር የለም። ካወራንም ከተፈላሰፍንም ከሞት ወዲህ ባለው ነው። በውቄ በሆነ ግጥሙ «የመቃብር ስውር አገር ...የሄዱትን ውጦ ሚያስቀር ፥ዜናው እንዳይነገር » የሚሉ ስንኞች አሉት። ከሞት ወዲያንዲያ ያለው ሀገር ዝም ጭጭ ያለ መሆኑን ለመግለፅ። ግና ቢርቀንም ባናውቀውም ስለሱ ማሰባችን አይቀርም። ኧረ እንዲያውም የዚህን ሀገር ሰዎች በሪሞት የሚያንቀሳቅሰን ይሄ ሞት ይሉት ጉድ ነው። እኔ መች አልኩ። ቤከር ነው ያለው። "The Denial of Death" የተሰኘውን የ Ernest Beckerን መጽሐፍ ከወር ላለፈ ግዜ ከርሜበታለሁ። በምሳሌዎችና በሊቃውንት ሀሳብ የተሞላ ነው። ትንታኔ ይበዛዋል። አንድን ሀሳብ ለማሳመን በሳይኮሎጂ፣ በፍልስፍና ...በስነፅሁፍ ዙሪያ ስለሚሽከረከር ትንሽ አሰልችነት አለው። እኔ ቀድሜ በሀሳቡ ተጠምቄ ሳለ እሱ ውሀውን ያባክናል። ለብዙ ነገሮች ዐይኔን ቢገልጥልኝም፣ የደበዘዙትን ቢያጠራልኝም አዲስ ነገር ሰጠኝ ለማለት ግን አልደፍርም። ጥርጣሬዎቼንና ሀሳቦቼን በመረጃና በትንተና ስላስረገጠልኝ ግን ወድጄዋለሁ። ቤከር መጽሐፉን የሚጀምረው የሞት ፍርሃት እና የሞት ሀሳብ የሰውን ልጅን አእምሮ ሙሉ በሙሉ እንደሚቆጣጠረው በመግለጽ ነው። «የሰው ልጅን ተረክ አድርጎ የሚያንቀሳቅሰው፣ የሚያስጨንቀውና ባህሪውን የሚቀርጸው በውስጡ የመሸገው Terror of Death ነው ይላል። "ይሄ ሰው ምን እያለ ነው? " ብዬ ጠይቄ የገባኝን እነሆ። ➊ ሰው ከንቱ [And on the loftiest throne in the world we me are still sitting only on our own rump.] - Michel de Montaigne የሰው ልጅ paradoxical nature አለው ይላል እነ አድለርን ጠቅሶ። half animal and half symbolic ነው ይሄ የአደም ዘር። በአንድ በኩል አምላክ አከል ፈጣሪ አእምሮ ያለው፣ በሌላ በኩል ደግሞ ለበሽታ፣ ለበስባሽነትና ለሞት የተጋለጠ ደካማ ፍጡር መሆኑ። Montaigne ይህን የሰው ልጅን ከንቱነት ለማሳየት ነው «ሰው በዓለም ካለው ከፍታኛ ዙፋን ላይ እንኳ የሚቀመጠው በፊንጢጣው ላይ ነው» ማለቱ። በአንድ በኩል የሰው ልጅ በማሰብ፣ በመፍጠር ወሰን የሌለው አቅም አለው። በጣም መጥቆ ኢ- መዋቲነትን ያስባል። በሌላ በኩል ደሞ እንደ ማንኛውም እንስሳ የሚታመም በመጨረሻም መሞቱና መበስበሱ የማይቀር አካል አለው። ይህ በምናባችን ዘላለማዊ ኑሮ መኖር መፈለጋችን እና በአካላችን ግን ለሞት መገዛታችን የሚፈጥረው ተቃርኖ Existential Terror ይፈጥርብናል ባይ ነው። ለዚህ ፍርሀት ደሞ Immortality Projects ማምለጫ ቀዳዳዎች ናቸው። ❷ Immortality Projects ሰውን ከሚያንቀሳቅሱት ነገሮች ሁሉ ዋነኛው የሞት ፍርሃቱ ነው ብለን የለ? የሰው ልጅ የሞት ፍርሃቱን በቀጥታ ተጋፍጦ መኖር ስለማይችል ፍርሃቱን ለመሸፈንና ህይወቱ ትርጉም እንዳለው ለማመን Hero Systems ወይም Cultural Immortality Projects ይፈጥራል ይላል። እነዚህ ፕሮጀክቶች ሰዎች ከሞቱ በኋላም ስማቸው ወይም ስራቸው እንዲኖር የሚያደርጉባቸው መንገዶች ናቸው። ጥበብ፣ ፍልስፍና፣ ሀብት፣ ስልጣን፣ ዝና፣ልጆችን መተካት... ለሆነ ዓላማ መስዋዕት መሆን....እነዚህ ሁሉ የሰው ልጅ "እኔ ከሞትኩም በኋላ ትውስታዬ ወይም ስራዬ አይሞትም" ለማለት የሚያደርጋቸው ስነ-ልቦናዊ መከላከያ ስልቶች ናቸው። ሰዎች ለራሳቸው ያላቸውን ዋጋ ከፍ የሚያደርጉበትና ከሞት ጥላ ስር የሚያመልጡባቸው ብልሀቶች ናቸው ይላል። እስማማለሁ። ◉ «ግን የሰው ልጅ ሞትን ያህል ጉድ በአንቀልባው አዝሎ እየሮጠ እንዴት እኒህን ሁሉ ማድረግ ተቻለው?» ብለን መጠየቃችን አይቀርም። እሱም ናርሲስት መሆናችን ነው ይላል። ❸ ናርሲዝም [The lion feels in his heart that God is with him, rather than with the gazelle.] -George Santayana ይህ ሀሳብ ፍሮይድ ካበረከተልን ታላላቅ ሀሳቦች መሀል አንዱ ነው። እያንዳንዳችን የዚያን የግሪክ አፈ-ታሪክ ናርሲሰስን አሳዛኝ ታሪክ እንደግመዋለን ይላል ቤከር። የዚህ ናርሲሲዝም አስቀያሚው ገጽታ ከራሳችን ውጭ ያለው ማንኛውም ሰው ቢጠፋ እንደማይቆጨን የሚሰማን ስሜት ነው። ሰዎች ወደ ጦር ሜዳ እንዲወርዱ የሚያደርጋቸውም ይሄው የናርሲሲዝም ባህሪ አይደለምን? በልቡ ውስጥ እሱ እንደሚሞት አይሰማውም። ከአጠገቡ ላለው ሰው ብቻ ያዝናል። መኪና ስንሳፈር ሌሎች ላይ እንጅ እኛ ላይ አደጋ እንደማይደርስ አናስብም ወይም ማሰብ አንፈልግም። የሰው ልጅ በድብቁ አእምሮው ራሱን immortal አድርጎ ይቆጥራል ይላል ፍሩይድ። ቤከር ደሞ ይህ ስሜት ወደ ንቃተ-ህሊና ተለውጧል ባይ ነው። Santayana እንዳለው «አንበሳ አምላክ ከእሱ ጋር እንደሆነ ከአጋዘን በላይ ይሰማዋል» ጥንካሬና ሀይል ያለው ፍጡር (እንደ አንበሳው) በህይወት የመቀጠል እምነቱ ከፍተኛ ስለሆነ፣ የሞት ፍርሃቱን በቀላሉ የመጫን አቅም እንዳለው ለማሳየት የገባ ምሳሌ ነው። ❹ ሰው- ሞትን የጨቆነ ጀግና «ይሄ የሞት ፍርሃት ካለ ለምን ዘወትር ሳንጨነቅ እንኖራለን?» የሚል ጥያቄ መጠየቅ ተገቢ ነው። ቤከር አእምሮአችን በጥንካሬ ለመኖር ሲል የሞት ፍርሃቱን ከውስጡ ከድኖ ይኖራል ይለናል። የሰው ልጅ ሟችነቱን፣ በስባሽነቱን በየሰከንዱ እያሰበ ቢኖር ኖሮ፣ በአእምሮ ጭንቀትና በፍርሃት ሽባ ሆኖ ከቤት መውጣት ባልቻለ ነበር። ስለዚህ አእምሮአችን ራሱን ለማዳን Repression ይጠቀማል። ይህ ማለት ፍርሃቱን ጨርሶ ማጥፋት ሳይሆን፣ ወደ unconscious mind አውርዶ በትልቅ ክዳን ማፈን ነው። ከዛም የሞት ፍርሃቱን ለመደበቅ ከዓለም ህብስት ላይ በትንሹ እየቆረሰ ይኖራል። በማህበረሰቡ የተደነገጉ ልማዶችን፣ የዕለት ተዕለት ስራዎችን በመከተል እራሱን ያኖራል። ልክ ዛሬ እኛ እንደምንኖረው። ​"To live fully is to live with the awareness of the rumble of terror that lies at the very base of human existence." Ernest Becker ቤከር የሰው ልጅ የሞትን ሀቅ ሳያዛንፍና ሳይሸሽ ሊረዳው ይገባል ይላል። ፍጹም ያልሆንን ፍጡራን መሆናችንን መቀበል ህይወትን በኸይረኛው መንገድ እንድንኖር ይረዳናል ነው የሚለው። ሞት አይቀሬ መሆኑን መቀበል ለአጭሯ ህይወታችን ትርጉም እንድንሰጣትና በትህትና እንድንኖር ያደርገናል ባይ ነው። እውነት አለው። እኔ ደሞ ይሄን እላለሁ «ይቺ ሕይወት ከኋላዋ ሞት ባታስከትል ኖሮ ከሞት የባሰ አስፈሪ በሆነች ነበር።» ጨለማ ባይኖር ኖሮ የከዋክብትን ብርሀንና ውበት እንደማናየው ሁሉ ሞት ባይኖር ደግሞ የሕይወትን ጣዕም አንቀምሰውም ነበር። ሰሞኑን የሆነ overthinker የጠየቀውን ጥያቄ እያሰብኩ ስስቅ ነበር። እንዲህ ይላል "What if oxygen is a slow poison and it takes 80-100 years to kill us?" አንዱ ምን መለሰለት? "Please do not breath and be immortal" 😂 ሞት ባይኖር ኑሮ የምርም oxygen አዘግይቶ የሚገድል መርዝ ይሆንብን ነበር አልኩ እኔማ። ብቻ አዝማሪዋ እንዳለችው ነው። «ሞት ይቅር ይላሉ ሞት ቢቀር አልወድም አፈሩም ድንጋዩም ከሰው ፊት አይከብድም!»
1 819
4
+2
بدون متن...
1 434
5
መልካም አዲስ ዓመት!! ------------------------------------------ © እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.) ሠኞ ጳጉሜ ፪ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.
1 678
6
ከራስህ ጋር ሳትታረቅ አዲሱን ዓመት አትጀምር!! (Be peaceful with you first) (እ.ብ.ይ.) ትናንት የዛሬ መነሻ ነው፡፡ ያለፈ ጊዜ አለፈ የሚባለው ቀኑ እንጂ ታሪኩ አይደለም፡፡ ታሪኩ ቀሪና ቀጣይ ነው፡፡ እሱ ነው እውቀትና ብልሃት የሚሰጠን፤ ታሪኩ ነው ሞራላችንና ሰብዕናችን ላይ እንዲሁም ስሜታችን ላይ ከፍተኛ ሚና የሚጫወተው፡፡ በትናንት የጊዜ ባቡር ባንሳፈር የዛሬ ጉዞ ላይ መድረስ አንችልም፡፡ ለዚህ ነው ዊሊያም ሼክሰፔር ‹‹ያለፈው ነገር ላሁኑ መቅድም ነው (What is past is prologue.)›› የሚለው፡፡ የትኛውም መጨረሻ የሌላ ነገር መጀመሪያ ነው፡፡ ያለቀ ዓመትም የአዲስ ዓመት ብስራት ነው፡፡ እኛ ኢትዮጵያውያኖች አሮጌው ዘመን ሲያልቅ አዲሱ ዓመት ላይ ዘው ብለን አንገባም፤ ባለቀውና አዲስ በሚጀምረው ዓመት መካከል ማረፊያ ጥቂት ቀናቶች አሉን፡፡ እነዚህን ቀናት በጉያዋ ሸጉጣ የያዘችው ወር ደግሞ ጳጉሜ ትባላለች፡፡ ካሮጌው ዓመት እንደተክለበለብን መጥተን እንደተክለበለብን ከአዲሱ ዓመት ጋር አንቀላቀልም፡፡ ፍሬን መያዣ፣ ራሳችንን ማስከኛ፣ የኋሊታችንን መመልከቻ የስክነት ጊዜ አለን፡፡ ባሮጌውና በአዲሱ ወር መካከል የምትገኝ፣ በመጨረሻና በመጀመሪያ አማካይ መንገድ ላይ ያለች ከእምዬ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን የተበረከተችልን ጥቂት ቀናትን የያዘች የመሸጋገሪያ ወር ስጦታ አለችን፡፡ ይህቺ ወር ከሌሎች ወር የተቀነሱ ቀናትን ይዛ የተሰራች ጭማሪ ወር ናት፡፡ ጥበበኞቹ አበው አስራሁለት ወራት እኩል ሰላሳ ሰላሳ ቀናትን ይዘው የተረፉትን ቀናት በ13ኛ ወር ውስጥ ሆነው እንዲጠቃለሉ አድርገዋል፡፡፡ ስሟንም ጳጉሜ ብለዋታል፡፡ ጳጉሜ ማለት በግሪክ ቋንቋ ጭማሪ ማለት ነው፡፡ ጳጉሜ እንደተጨማሪ እድል የተሰጠችን ገፀበረከታችን አድርገን ልንወስዳት እንችላለን፡፡ አሮጌውን ዓመት አገባድደን አዲሱን ዓመት ከመጀመራችን በፊት ያለች ሰከን ብለንና ተረጋግተን ትናንትን እየመዘንን ለነገ የምንዘጋጅባት የማሰቢያ ወራችን ነች፡፡ ይህቺ የጳጉሜ ወር በሐገራችን አብዛኛው አካባቢ በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ አምስቱን ቀናት በሙሉ እየፀለዩና ፀበል እየተፀበሉ ለአዲሱ ዓመት ራሳቸውን የሚያዘጋጁባት፤ በዓመቱ ውስጥ ከሠሯቸው ስህተቶች የሚነፁባት፤ መንፈሳቸውን የሚያድሱባት ትንሽ ጊዜ የምትመስል ነገር ግን ትልቅ ትርጉም የምትሠጥ የትንሽ ትልቅ ወራችን ናት፡፡ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት በአንድ ፅሁፋቸው ‹‹ ……… የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር ለየት ከሚያደርጉት ነገሮች አንዱ ጳጉሜ የምትባል አሥራ ሦስተኛ ወር ስላለችን ነው፡፡ የቤት ኪራይና የወር ደመወዝ የማንከፍልባትና የማንቀበልባት፤ መብራትና ውኃ ግን ከነሐሴ ወር ጋር ጨምረው የሚያስከፍሉባት፤ ሲሻት አምስት፣ ሲያስፈልጋት ስድስት፣ ስትፈልግ ደግሞ ሰባት የምትሆን ወር ናት፡፡ እንዲያውም ከአሥራ ሁለቱ የኢትዮጵያ ወሮች ጳጉሜ በብዙ መንገድ የተለየች ናት፡፡ በአንድ በኩል በጣም ትንሿ ወር ናት፡፡ ሲቀጥልም ወርኃዊ በዓላት የማይውሉባት ወር ናት፡፡ እንዲያም ሲል ደግሞ ከሌሎች ወሮች በተለየ የቀኖቿ መጠን የሚቀያየሩ ብቸኛ ወር ናት፡፡ ከሌሎች የኢትዮጵያ ወሮች በተለየም ስሟ ኢትዮጵያዊ ያልሆነ ወር ናት፡፡ በሁለት ዘመናት መካከልም እንደ መሸጋገሪያ የምትታይ ወርም ናት፡፡…. ›› በማለት ገልፀዋታል፡፡ አሮጌው ዓመት ጉዞው ተገባዷል ታሪኩ ግን አላለቀም፡፡ ሞት ብቻ ነው የሰው ልጅን ታሪክ የሚቋጨው፡፡ እስትንፋሱ ያልተቋረጠ፣ ትንፋሹ ያልቀዘቀዘ ሰው በአዲስ ዓመት ደብተር አዲስ ታሪክ እየፃፈ ኑረቱን ይቀጥላል፡፡ አዲሱ ዓመት ያልተጀመረባት፤ ነገር ግን ምን እንደሚፃፍባት የምንመረምርባት ጊዜ ናት ጳጉሜ፡፡ ያለፈው ዓመት ማብቂያ የአዲሱ ዓመት መጀመሪያ ዋዜማ በመሆኗ ጳጉሜን ለየት ያደርጋታል፡፡ ጳጉሜ ራስን መመልከቻ መስታወት ናት፡፡ አሮጌው መልካችንን ምንም ሳትደብቅ የምታሳይ፤ የወደፊት መልካችንን በዓይነ-ህሊናችን የምትስል ራሳችንን ማያ ናት፡፡ ካለፈው የሕይወት ተሞክሯችን መልካሙን ነገር ወስደን፣ ደካማውን ጎናችንን እንድናሻሽል ህይወታችንን በዓይነ-ህሊና መነፅራችን የምንጎበኝበት የንስሃና የተሃድሶ ዕድል የምናገኝበት ምርጥ ጊዜአችን ናት፡፡ ጳጉሜ አሮጌውን ዓመት ካዲሱ ዓመት የምታገናኝ ድልድይ ናት፤ የትናንት ማንነታችንን ከአዲሱ ማንነታችን ጋር የምታዋህድ ቅመምም ናት፡፡ አሮጌው ዓመት ወደኋላ ቀርቷል፤ አዲሱ ዓመት ደግሞ ከፊትለፊታችን ተገትሯል፡፡ ጳጉሜ አሮጌውን በሰከነ መንፈስ መርምረን ባገኘነው ዕውቀት ከፊታችን ያለውን አዲሱን ዓመት በተሻለ ተሞክሮ፣ ስሜትና ብርታት እንድንመራው ትንሽ የማሰቢያ ጊዜና እረፍት የምትሰጠን አማካይ ጊዜ ናት፡፡ ይህቺ ወር የሕይወታችንን ሩጫ ገታ አድርገን፣ ትንፋሽ ወስደን፣ ቆም ብለን የምናስብባት ተጨማሪ ቀናችን ናት፡፡ ጳጉሜን ላሰበበትና ራሱን ለገመገመባት የውሸት መኖርና የእውነት መኖር (living versus existing) ምን እንደሆነ ግንዛቤ ያገኝባታል፡፡ ወደኋላህ ዞር ብለህ የምታየው ሕይወትን እንድትረዳበት ነው፤ የተረዳኸውን የምትኖርበት ግን ዛሬን በመጀመር የወደፊትህን ጭምር ነው፡፡፡ ከአንድ ዓመት ወደሌላ ዓመት ዝም ብሎ መዘዋወር እሱ እውነተኛ መኖር አይደለም፡፡ አሮጌውን ዓመት አገባድደን ወደአዲሱ ዓመት ስንቀላቀል አዕምሯዊና ስሜታዊ ለውጥ ካላመጣን የእውነት ኖርን አይባልም፡፡ ቢያንስ ካለፈው ዓመት የሚሻል ቅንጣት ለውጥ ሊኖረን ይገባል፡፡ አዲሱን ዓመት ደስ ብሎን የምንቀበለው በቀናት መለዋወጥ፣ በዓመታት መቀያየር ብቻ ሳይሆን በለውጥ መስመር ውስጥ ስናልፍ ነው፡፡ ኢኮኖሚያዊ ችግራችንን በስራና በአዲስ ክህሎት ስንቀርፍ፣ መንፈሳዊ ድህነታችንን ስንገረስስ፣ ክፉ ልማዳችንን ስንተው፣ እውቀት ስንጨምር፣ በስሜት ብስለታችን ላይ ጉልህ ልዩነት ስናመጣ፣ ስህተታችንን ላለመድገም ለራሳችን ቃል ስንገባ፣ ለነፍሳችን ደስታ አንድ እርምጃ ወደፊት ስንራመድ፣ ራሳችንን ሳንሆን ባባከንነው ጊዜ ተፀፅተን ወደራሳችን ስንመለስ፣ ወዘተ መልካም ነገሮችን ማሟላት ስንችል የምንቀበለው አዲስ ዓመት የደሰታና የፍስሃ ይሆንልናል፡፡ ወዳጄ ሆይ… ‹‹በከንቱ የጠፋ ጊዜ መልሶ አይገኝም! (Lost time is never found again)›› እንዲል ቤንጃሚን ፍራንክሊን ዕድሜህን በዋል ፈሰስ አታባክነው፡፡ ጳጉሜን ከተጠቀምክባት የመታደስ፣ የመለወጥ፣ የመሻሻል፣ የማገገም፣ ወደራስህ የመመለስና ከራስህ ጋር እርቅ የምትፈፅምባት ውድ ስጦታህ ናት፡፡ የአዲስ ማንነትህ መብቀያ ዘር ናት፡፡ የሚቀጥለው ዓመት ወይም ሌላ ጊዜ ይደርሳል እያልክ ዛሬህን አታባክን፡፡ አስብና ወስን፤ ወስንና ጀምር፡፡ ጳጉሜን ስለራስህ አስብባት፣ ትናንትህን ገምግምባት፣ ወደፊትህን ወጥንባት፣ አካሄድህን መርምርባት! ከራስሀ ጋር ሳትታረቅ አዲሱን ዓመት አትጀምር!! አዲስ ዓመት ከትናንትህ ጋር የምትዋጋበት አዲስ የጦር ግንባር አይደለም፤ ይልቁንስ እርቅ ፈፅመህ በአዲስ ማንነት የምትጀምርበት ልዩ ቀንህ ነው፡፡ አዲሱ ዓመት የሠላም፣ የፍቅር፣ የእድገትና እና እርስበርስ የምንስማማበት፤ ከግል ጥቅም ይልቅ የሐገር ጥቅም የምናስቀድምበት፤ ፍትህ ላጣው ወገናችን የምንቆምበት፣ ለተቸገረው የምንደርስበት፣ ለተራበው የምናጎርስበት ዓመት እንዲሆን ሁላችንም ከራሳችን የመንደር ሳጥን ወጥተን ሀገራዊ፣ ወገናዊና ኢትዮጲያዊ መንፈስ ተላብሠን ከልጅ እስከ አዋቂ፣ ከሊቅ እስከ ደቂቅ በአንድነት ሆ ብለን የምንነሳበት ዓመት ያድርግልን…!!!!! ቸር ጊዜ!
1 772
7
بدون متن...
1 221
8
የሰው ልጅ ሞትን የሚፈራ ይመስላችኋል? እኔ አይመስለኝም! በርግጥ ሞት የሚያስፈራ ነገር ነው። ግን ሞትን ብቻውን አንፈራውም። ከሞት ወዲያ ያለውን መረሳትን ነው የምንፈራው፡፡ እዚህ ጋር የሄኖክ በቀለ ለማ “ሀገር ያጣ ሞት” መፅሐፍ ውስጥ ያለ ‘ተስፋ’ የተባለ አንድ ሚስኪን ገፀ ባሕርይ ትዝ አለኝ፡፡ ‘ተስፋ’ እንዲህ ይላል… «ሞትን እፈራዋለሁ? አ! አ! ይልቅ መረሳትን ነው የምፈራው፡፡ ነገ ውስጥ ዕድል ፈንታ ማጣትን ነው የምፈራው፡፡ ነገ የማልተነፍሰው አየር ይነፍሳል፤ ነገ አበጀህ የማልለው፤ አጠፋህ የማልለው ንጉሥ ይነግሣል፡፡ ነገ የማልጠለለው ዝናብ ይዘንባል፤ ነገ የማልሰማው ወሬ ሀገሩን ያዳርሳል፡፡ የምፈራው ይህንን ነው፡፡ የምፈራው መብነን ነው፡፡ ነገ ተስፋ ማን እንደሆነ ትርጉም የማይሰጥበት ጊዜ ይመጣል፡፡ የምፈራው እርሱን ነው፡፡» በቃ ይኼው ነው፡፡ በዚች ምድር አንድ ሰው በሠራው ሥራ እንደሚታወስ እርግጠኛ ከሆነ ሞትን ለምን ብሎ ነው የሚፈራው? አሁን ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ ሞትን የሚፈራ ይመስላችኋል? አስቴር አወቀስ? እኔን'ጃ! እኔ አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም ነገ የሚታወሱበትን ሥራ ባላቸው ጊዜ ሠርተዋልና ነው፡፡ አጋፋሪ እንደሻው ሞትን የሚፈሩትና የሚሸሹት ለመታወስ የሚያበቃቸውን ሥራ ስላልሠሩ ይመስለኛል፡፡ አገር እያሳበሩ ምድርን በዱካቸው ከሚያዳርሱ… ምናለ በሰዎች አእምሮ ውስጥ ትውስታቸውን ለማኖር ቢኳትኑ!? ቀላሉ መንገድ ይሄ ነበር፡፡ ምክንያቱም ሞትን ሸሽተን አናመልጠውምና፡፡ ሕይወት አጭር ናት፤ በእጃችን እንዳለ አረፋ አልያም ቀና ብለን ሰማይ ላይ እንደምናየው ጉም፡፡ ሰዎች ካለፉ በኋላ በክፉም በደጉም ይታወሳሉ፡፡ ሁሉም ሰው በተመሳሳይ መንገድ አይታወስም፡፡ እነ ሂትለርን፣ ጆሴፍ ስታሊንን፣ ኤዲ አሚንን ዛሬም እናስታውሳቸዋለን፤ ግን ጥሩ ባልሆነ መልኩ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ማንዴላን፣ ጋንዲን፣ ካትሪን ሀምሊንን፣ ማዘር ትሬዛን…. ወ.ዘ.ተ ምድር ለይ ሠርተዉት በሄዱት መልካም ሥራ እናስታውሳቸዋለን፡፡ Herostratus የተባለ ሰው ‘Madman’ ብለው ይጠሩታል ፈረንጆቹ፤ የታላቁ እስክንድርን መወለድ እና የአማልክቱን መዘገናጋት ተጠቅሞ ከሰባቱ የዓለም ድንቅ ቅርሳ ቅርስ መካከል የሚቆጠረውን ‘Temple of artemesium’ (የአርጤምሲስን ቤተ መቅደስ) ጣርያ በእሳት አያይዞ ያቃጠለው በታሪክ ስሙ እንዲታወስ ስለፈለገ ብቻ እንደሆነ ይነገራል። በዚህም ምክንያት ‘Herastratus’ የሚለው ቃል በመዝገበ ቃላት ውስጥ ራሱን በየትኛውም ዓይነት መንገድ ተጠቅሞ ዝነኛ እና የሚታወስ ሰው ለማድረግ ለሚጥር ሰው የተሰጠ ገላጭ ሆኖ የእንግሊዘኛ ቋንቋ ውስጥ ገብቷል። ይህ ሰው ተሳክቶለት ዘመን አልፎ እኛም በዚህ ሰበብ የምናስታውሰው ሆነናል። አንድ ነገር ግን ልብ በሉ! እንደነ ‘Herostratus’ በክፉ ነገር ከመታወስ መረሳት ይሻላል ባይ ነኝ፡፡ ሰው በመልካም ነገር መታወስ ሲችል ነው ያልባከነ ሕይወት ኖሮ አለፈ የሚባለው፡፡ ◉ ወደ ተነሳሁበት ፊልም ልመልሳችሁ፤ ሄክቶር ‘Remember Me’ የሚለውን ሙዚቃ የፃፈው ለልጁ "coco" ነበር፡፡ ምክንያቱም በ ራቅ ወዳለ ቦታ ሊሄድ ስለነበር፡፡ coco በዛ ሰዓት ህጻን ነበረች፡፡ ዝም ብሎ መሄድ ይችል ነበር፡፡ ግን እንዴት ብሎ? የሰው ልጅ አይደል? የሆነ ነገር ሳይጥል ርቆ መሄድ አይችልም፡፡ እንድታስታወሰው ስለፈለገ ‘Remember Me’ን ደርሶ ዘፈነላት፡፡ ከዛ ግን አልተመለሰም ነበር፡፡ ልጁ coco አባቷን የምታስታውሰው ሌላ በምንም አልነረም፤ በሙዚቃው ነው፤ በሰራው ስራ፡፡ የመጨረሻውን Final death ያመለጠውም በህይወት እያለ መታወሻ እንዲሆነኝ ብሎ በሰራው ስራ ነው፡፡ ይሄው ነው፡፡ ለሰው ልጅ የዛሬ ስራው ለነገ ቤዛው ነው፡፡ ዝም ብሎ እንዲሄድ አልተፈቀደለትም፡፡ እርሱም አይችልም፡፡ እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው? REMEMBER ME. ▭▭ NB: ከመዲና መፅሔት ተሻሽሎና ተመጥኖ የተወሰደና ዳግም የተለጠፈ © Mes Oud
2 260
9
◉ ከመረሳት ወዲያ... [REMEMBER ME] “የሰው ልጅ ለምን የተወለደበትን ቀን ብቻ ያከብራል? የሞተበትስ ለምን አይከበርም?” ብለው ሚክሲኳዊያን “dia de los muertos” የሙታን ቀንን (Day of the dead) ያከብራሉ፡፡ በዓለም ላይ የማጂላንን ዱካ ተከትላችሁ ብታስሱ ከሜክሲኮ ውጭ የሙታንን ቀን የሚያከብር አንድም ሀገር አታገኙም፡፡ ታዲያ ይሄ ገራሚ ባህል ለአንድ ልዩ፣ አስደናቂና አይረሴ አኒሜሽን ፊልም መነሻ ሆኗል፡፡ COCO. የፊልሙን ታሪክ በአጭሩ ላወራበት ካሰብኩት ጉዳይ ጋር አስተሳስሬ ሳቀርበው እንዲህ ነው…ፊልሙ ላይ ሰዎች ከሞቱ በኋላ የሚሄዱበት ዓለም አለ፤ "Land of dead" ይባላል፡፡ ሕያዋን የሚኖሩበት ደግሞ "Land of living" ይሰኛል፡፡ ሟቾች የሚሄዱበት 'Land of dead' የሚባለው ቦታ ድጋሚ ሳይሞቱ፣ አፅማቸው ሳይፈርስ፤ ሉሲን ወይም አርዲን መስለው የሚኖሩበት ቦታ ነው፡፡ ታዲያ እኒህ ሕያዋን አፅሞች የሚኖሩት በምድር ላይ እነርሱን የሚያስታውሳቸው ሰው አስካለ ድረስ ብቻ ነው፡፡ ፊልሙ ላይ አንድ የሚያሳዝን ሄክቶር የሚባል ገጸ ባሕርይ አለ፡፡ 'በጨው ደንደስ በርበሬ ተወደስ' የሚሉት ብሂል ደርሶበት መታወሻ ምግባር ሳያንሰው - ተዘንግቶ… ተረስቶ የመጨረሻውን ሞት ሊሞት ጫፍ የደረሰ … ህላዌው በአንድ ሰው ማስታወስ ብቻ ተንጠልጥላ የቀረች… ላለመረሳትና ለመታወስ ሲባዝን የምናየው ምስኪን ፍጡር፡፡ ምስኪኑ ሄክቶር ስለገጠመው እጣ ፈንታ እንዲህ ይላል... “When there’s no one left in the living world who remembers you , you disappear from this world. we call it the final death.” አዎ! በሕይወት ያለ አንድም ሰው የሚያስታውስህ ካልሆነ የመጨረሻ ሞትን (final death) ጽዋ ትቀምሳለህ፡፡ ሄክቶርም የገጠመው ይሄ ነበር። መረሳት!!! ፊልሙ ላይ ዝነኛ የሆነች አንድ ዘፈን አለች። 'Remember Me' የምትል። የፊልሙን ሃሳብ የተሸከመች ናት፡፡ ሄክቶር ለልጁ የደረሳት የነፍስ ሙዚቃ፡፡ ሄክቶር ቀድሞ ይህ እጣ ፈንታ እንደሚገጥመው ሳይታወቀው አልቀረም፡፡ ➊ መረሳት - እውነትም የመጨረሻ ሞት በሰዎች Memory ውስጥ ቦታ ማጣት እውነትም የሞት ሞት ነው፡፡ ታዲያ ይህንን ሚስጥር ለሰው ልጅ ማን ሹክ ብሎት ነው? ልክ እንደፊልሙ ሁሉ ከሞት በኋላ ያለው ሕይወቱም እዚህ በቀሩት ሕያዋን ትውስታ ላይ ተንጠልጥሎ ይቀራል ብሎ ማነው የነገረው? እንጃ! ድርጊቱን ከታዘባችሁ ግን የሰማው አልያም የደረሰበት ሚስጥር እንዳለ የሚያሳብቅ ነው፡፡ የአደም ዘር እንደመረሳት የሚፈራው ነገር በዚህ ምድር ላይ የለም፡፡ እሩቅ ሳንሄድ ሰውን በተለያዩ አጋጣሚዎች 'አላስታወስኩህም!' ስትሉት እንዴት ነው የሚንጨረጨረው? መረሳትን ፍፁም አይፈልግምና ነው፡፡ የሰው ልጅ በዚች ዓለም የሚከውናት እያንዳንዷ ቅንጣት ተግባር መታወስን ዒላማ ያደረገች ናት፡፡ የዛሬ ልፋቱ ነገ በሰዎች አእምሮ ላይ የራሱን የትውስታ መስክ አጥሮ ይዞ ለመቦረቅ በማለም ነው፡፡ ቢችል በመላው ዓለም ካልሆነ ደግሞ በሚወዳቸው ሰዎች ዘንድ ብቻ ለመታወስ ይፍገመገማል፡፡ ታዲያ እንደመልኩ ሁሉ ለመታወስ የሚጥርበት መንገድም የተለያየ ነው፡፡ አባ ወራው ዛሬ በሚስቱ በኩል ያለውን ዋሻ የሚምሰው ከዘኪዮስ ያጠረችውን ሐሴት ለማጣጣም ብቻ አይደለም! ነገ የእርሱን ስም እንደባቡር ፉርጎ ከኋላቸው አስከትለው በዘመን ሀዲድ ላይ የሚነጉዱ መታወሻዎቹን ለማግኘት ነው፡፡ «ስም ከመቃብር በላይ ይውላል» ማለቱስ ሊዚህ አይደል? አንዴ አምባሰል አንዴ አንቺ ሆዬ እያለ በጉሮሮው ላይ ታች እያለ የሚንከለከለው ዘፋኝ ምን ከጅሎ ነው? ትንፋሹን ጆሯችን ላይ ሁ ብሎ ፈለጉን ሊያኖር… ከዚያም ባለ 3 መኝታ የተንጣለለ የትውስታ ጎጆ ከአእምሯችን ሊገዛ አስቦ ነው፡፡ 🎶 “በቁም ካፈቀርሽኝ ስሞት እንዳትረሽኝ” ብሎ ጨርሶታልኮ ጥሌ፡፡ አንገቱን ቀብሮ ወረቀቱን በእስክርቢቶው እያረሰ ዘሩን የሚዘራው ደራሲም ግቡ የጥበብ ሃራራውን ማስታገስ አልያም ውስጣዊ ሃሴትን መሸመት ብቻ አይመስለኝም፡፡ ስሙን በተነቀሱ የጥበብ ፍሬዎቹ ነገ ሊታወስ ፈልጎ ነው፡፡ ለሌላ አይደለም፡፡ ሰሞኑን አንብቤ የጨረስኩት አንድ መፅሐፍ አለ። በ ኧርነስት ቤከር የተፃፈው «The Denial of Death» ...እና በመፅሐፉ ሰውዬው “Immortality Project” የሚለው ነገር አለ። ቤከር እንደሚያስረዳው ሰው ሞትን ስለሚፈራና ገላው የምስጥ ፍሪዳ ሁኖ እንደሚጠፋ ስለሚያውቅ፣ በማህበረሰቡ ውስጥ፣ በሀገሩ...በኪነ ጥበብ፣ በልጆች ወይም በታላላቅ ሥራዎች ውስጥ ስሙና አሻራው እንዲኖር ይፍገመገማል፡፡ ልጅ ሲወልድ፣ በጎ ሲሰራ፣ ህንፃ ሲያቆም፣ ዝነኛ ሲሆን "የሰራሁት ነገር ከሞት በኋላም ይኖራል" በሚል ነው። ❷ መታወስን የማይፈልግ ይኖር ይሆን? እውን በዚች ምድር መታወስ የማይፈልግ ሰው ይኖር ይሆን? እኔንጃ። በምሳሌነት የሚቀርቡ ሰዎች አሉ በርግጥ። እንደፍራንዝ ካፍካ እና ፈርናንዶ ፔሽዋ ያሉ በሠሩት ሥራ መታወስ የማይፈልጉ ደራሲያን መኖራቸውን አልዘነጋሁም። ሁለቱም በሕይወት ዘመናቸው በስማቸው ያሳተሙት ነገር በብዛት ካለመኖሩም በተጨማሪ ሲሞቱም ጽሑፎቻቸው እንዲቃጠሉ ወይ እንዳይታተሙ ተናዝዘው የሞቱ ናቸው። ምንም እንኳ በኑዛዜ አስፈጻሚዎቹ መልካም ፈቃድ እና አለመታዘዝ ሥራዎቻቸው ለትውልድ ተርፎ ዘመን አልፈው ቢታወሱም። በተለይ ፈርናንዶ ፔሽዋ ለመታወስ ካለመፈለጉ የተነሳ ሲፅፍ ከመቶ በላይ የብዕር ስሞችን እና ማንነቶችን ይጠቀም ነበር። ልጨኛ ሥራውን 'The Book of Disquite'ን ይመለከቷል። ይሄን ታሪክ ስሰማ መጀመሪያ ገረሞኝ ነበር፡፡ “የመታወስን ፍላጎት በአዕምሮው ሸጉጦ ያላኖረ ሰብዕ እውን ይኖራልን?” ብዬ ትንሽ አሰሳ አደረግኩኝ፡፡ እናም ላለመታወስ ብሎ ለቁጥር በሚያታክቱ የብዕር ስሞች ሲፅፍ ኑሮ የሞተው ገጣሚ If, After I Die በተሰኘ ግጥሙ ልክ እንደ ማንኛውም ሰው መታወስን በሩቁ ሲታከክ እንደነበር አስተዋልኩ፡፡ If, after I die, they want to write my biography, There is nothing more simple. There are only two dates – the one of my birth and that of my death. Between the two every day things are mine. I’m pretty easy to define. I saw myself as a fool. I loved things without any sentimentality. I never had a desire that I couldn’t realise, because I never blinded myself. እኒህን ስንኞች ለማስረጃ ባቀርብ በቂ ይመስለኛል፡፡ አንዳንዴ እንዲህ ይሆናል፡፡ መታወስን እሸሻለሁ የሚልን ጀግና፣ ቀረብ ብላችሁ ብታጤኑት በስውር መታወስን ሲያባርር ልትይዙት ትችላላችሁ፡፡ በርካቶችም የዝና ማማ ላይ ተንጠላጥለው መሰቀል የሚፈልጉት ከማማው ላይ ሆነው ንፋስ ሊቀበሉ አስበው አይደለም፡፡ ይልቁንስ በበርካቶች ዘንድ ዘመናትን ተሻግሮ ለመታወስ ነው፡፡ ❸ ከሞት ወዲያ
1 733
10
+1
بدون متن...
1 706
11
‹‹ባልሆንከው ከምትወደድ በሆንከው ብትጠላ ይሻላል!›› (Unity without uniformity) (እ.ብ.ይ.) ከሰው ጋር ለመመሳሰል ብሎ ያልሆነውን የሚሆን ብዙ ነው፡፡ በሌሎች ፊት አዲስ ዓመል የሚያሳይ፣ ሰው ሲያይ የሚለወጥ ሞልቷል፡፡ ያልነበረውንና የሌለውን ባህሪ ለሰው ሲል የሚያሳይ እልፍ ነው፡፡ ከሰው ጋር ለመኖር ተብሎ ያልሆንከውን መሆን ልክ አይደለም፡፡ መመሳሰል ማለት ራስን መካድ አይደለም፡፡ የራስህን ይዘህ ከሰው ጋር መቀላቀል ይቻላል፡፡ ሌሎች የሆኑትን መምሰል ግን እነሱን መሆን ነው፡፡ በሚያስማማህ፣ በሚያግባባህ፣ በምታምነውና በምትመራበት ፍልስፍና ውስጥ ሆነህ ከሰው ጋር ተስማምቶ መኖር ይቻላል፡፡ ማህበራዊ ህይወት ላይ ለመሳተፍ፣ የሌሎችን ተቀባይነት አገኛለሁ ብለህ ራስህን መተው የለብህም፡፡ ለሰው ብለህ የምታምነውን ክደህ፣ የምትመራበትን ፍልስፍና ችላ ብለህ፣ መገኘት በሌለብህ ቦታ የምትገኝ ከሆነ አንተ ራስህን ሳይሆን ሌሎችን ለመሆን እየባከንክ ነው፡፡ እስከነአቋምህ፣ እስከነእምነትህ፣ እስከነጉድለትህ፣ እስከነምናምንህ ራስህን ሆነህ ነው ከሰው ፊት መቆም ያለብህ፡፡ የሆንከውን አንተነትህን የማይቀበል ወዳጅም ይሁን ባልንጀራ ካጋጠመህ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ ብለህ ቻው ማለት ነው፡፡ በሌሎች መስፈርትና ፍላጎት ራስህን አታባክን፤ ይሄ ለራስህ የምትውልለት ትልቅ ውለታ ነው፡፡ ይልቁንስ የእኔ የህይወት መንገድና መስፈርት ያዋጣል ወይ፣ ልክ ነው ወይ ብለህ ራስህን እየጠየቅክ አካሄድህን፣ ፍልስፍናህን፣ እምነትህን፣ አቋምህን እየፈተሽክ፤ ራስህን እያረምክና እያሻሻልክ ወፊት መገስገስ ነው፡፡ በመርህ ደረጃ በማትቀበለውና መሆን በማትፈልግበት ቦታ ለሰው ብለህ አትገኝ፡፡ ባልሆንከው ከምትወደድ በሆንከው ብትጠላ ይሻላልና (“It is better to be hated for what you are than to be loved for what you are not.”) አንድን ክፉ ልማድ ብዙ ሰዎች ደጋግመው ስለሚፈፅሙት ልክ ነው ማለት አይደለም፡፡ ምንም ነገር ቢሆን አስበህበት፣ አምነህበትና ፈትሸኸው ተቀበለው እንጂ ሌላ ሰው አይተህ አታድርገው፡፡ መፅሐፈ ሲራክ ምዕራፍ 6 ቁጥር 17 ላይ ‹‹ብዙ ናቸው ብለህ ከሐጢያተኞች ጋር አንድ አትሁን›› የሚለው ብዛት ጥራት አለመሆኑን ሲያስረዳ ነው፡፡ በኦሪት ዘጽአት ምዕራፍ 23 ቁጥር 2 ላይም ‹‹ክፉውን ለማድረግ ብዙ ሰዎችን አትከተል፤ ፍርድንም ለማጥመም ከብዙ ሰዎች ጋር ተስማምተህ አትመስክር (Do not follow the crowd in doing wrong.)›› ይላል፡፡ ንጉስ ዳዊትም በመዝሙሩ የመጀመሪያ ምዕራፍና ቁጥር ላይ ‹‹ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፤ በኃጢያተኞችም መንገድ ያልቆመ፤ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ›› ሲል ራሱን ከመንጋው የሚጠብቅን ሰው ያመሰግናል፡፡ ሰው ስለበዛበት ብቻ ብዙ ሰው የሚያደርገው ነገር ሁሉ ሁልጊዜ ልክ አይሆንም፡፡ ትክክልን ወይም ስህተትን በሰው ብዛት ሳይሆን ነገሩንና ሁኔታውን መርምረህ ለይ፡፡ እንደውም ሰው የበዛበት ነገር በጥርጣሬ የሚታይና ከስር መሠረቱ ሊጠና የሚገባ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ክፉ ስራንና አጉል ልማድን መሸሽ ሰውን መጥላት የሚመስላቸው አሉ፡፡ ከማይመችህ አጉል ልማድ መሸሽ፤ ከማታምንበት አስተሳሰብ መራቅ ራስን መጠበቂያ መንገድ ነው፡፡ ነገር ግን ሐጢያቱን መራቅ ሃጢያተኛውን መጥላት አይሆንም፡፡ ኩነኔውን መቃወም ሰሪውን ማውገዝ አይደለም፡፡ ሰሪው ሃጢያት በሰራበት ህይወቱ የፅድቅ ስራም ሊሰራበት አቅም አለው፡፡ ከሐጢያተኞች ሃጢያት እንጂ ከሰዎቹ አትሽሽ፡፡ በክፉ ስራቸው አትተባበራቸው እንጂ ከሰውነታቸው አትራቅ፡፡ ልትጠላው የሚገባው ክፉ ስራቸውን ነው፡፡ ሰው እንደሰው በደግም በክፉም ሊለዋወጥ ስለሚችል የምናወግዘውም ሆነ የምናደንቀው ስራውን ነው፡፡ ሃጢያተኛውን እንደሰው ውደድ ነገር ግን የሀጢያቱ ተከታይ ወይም ደጋፊ አትሁን፡፡ ዛሬ ሃጢያተኛ የሆነ ሰው ነገ ፃድቅ መሆን የሚችል አቅም እንዳለው ተረዳ፡፡ የዛሬ ፃድቁም የነገ ሃጢያተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ ማንንም በዛሬው ሁኔታው ብቻ ጠቅልለህ እስከወደፊት ማንነቱ አትደምድም፡፡ የወደቀ ይነሳል፤ የተነሳ ይወድቃል፡፡ ከፍ ያለ ዝቅ የሚልበት፤ ዝቅ ያለ ከፍ የሚልበት ዓለም ውስጥ ነን ያለነው፡፡ ትናንት የት ይደርሳል የተባለ “መልካም ሰው” ሰይጥኖ አይተነዋል፡፡ ትናንት አይለወጥም ያልነው “ክፉ ሰው” ተለውጦ መልካም ዜጋ ሲሆን ተመልክተናል፡፡ አይደለም በሌላ ሰው በራስ እንኳን እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይቻልም፡፡ ታዋቂዎች፣ አዋቂዎች፣ ዝነኞች፣ በህብረተሰቡ ዘንድ የተከበሩ ሰዎች የሚያደርጉት ነገር ሁሉ ልክ ላይሆን ይችላል፡፡ ተሞክሮ መውሰድ አሪፍ ነገር ነው፤ ልምድና እውቀት ካላቸው ሰዎች ሃሳብ መጋራት፤ እውቀት መካፈል ያለ ነው፡፡ ነገር ግን ስትከተላቸው መርምረህ ተከተላቸው፡፡ ብትችል ተከታይ አትሁን፤ ራስህን በራስህ ምራ፡፡ አርአያ የሚሆኑህን ሰዎች ፈትሸህ እወቅ፡፡ አዋቂነትም ይሁን ታዋቂነት የመልካም ሞራልና የጥሩ ስነምግባር ማረጋገጫ አይደለም፡፡ ስም ያላቸው፤ መልካም ስራ ግን የሌላቸው መዓት ናቸው፡፡ ብዙ ወረቀት የሰበሰቡ፤ ቅንነት ግን የጎደላቸው አይጠፉም፡፡ ህብረተሰቡ የሚያከብራቸው ነገር ግን በድብቅ ነውር የሚፈፅሙ አስመሳዮች ተቆጥረው አያልቁም፡፡ የማንነታቸው መጋረጃ ቢገለጥ ጉድ የሚሆኑ ብዙ አሉ፡፡ ውስጡን ለቄስ፣ ሰው መሳይ በሸንጎ የሆኑ የትየለሌ ናቸው፡፡ ማንም ንፁህ የለምና ከሰዎች የምትወስደውን ትምህርት አስተውለህ ምረጥ፡፡ ኦስካር ዋይልድ ‹‹የትኛውም ፃድቅ ትናንት አለው፤ የትኛውም ሃጢያተኛ ነገ አለው (“Every saint has a past, and every sinner has a future”)›› የሚለው የትኛውም ሰው ይብዛም ይነስም ደግም ክፉም ስራ እንዳለው ለማሳየት ነው፡፡ ስለሰው አንዲቷን ነገር ብቻ ዓይቶ አፍን ሞልቶ በርግጠኝነት መናገር ከባድ ነው፡፡ ዛሬ ጥሩ የሆነ ሰው ትናንት የወደቀበት ሐጢያት ሊኖረው ይችላል፡፡ ከስህተቱ ተምሮና ሃጢያቱ ዋጋ አስከፍሎት ዛሬ መልካም የሆነ ሰው ብዙ ነውና፡፡ ዛሬ ሐጢያተኛ ሆኖ የተገኘም እሱ ራሱ በራሱ ላይ እስካልፈረደ ድረስ ሃጢያተኛ ሆኖ ዘላለሙን እንዲኖር አልተፈረደበትም፡፡ የመቀየር፣ የመለወጥ፣ ንስሃ የመግባት፣ ራሱን የመግዛት፣ የበደለውን ይቅርታ የመጠየቅና ለራሱም ምህረት የማድረግ፣ እንዲሁም አዲስ ሰው የመሆን እድል አለው፡፡ ወዳጄ ሆይ…. በሰው ለመወደድ ብለህ የማይወደድ ስራ አትስራ፡፡ ትክክለኛ የሰው ፍቅር በታይታና በማስመሰል የሚገኝ አይደለም፡፡ ሰዎች የበዙበት ነገር ሁሉ ልክ ላይሆን ስለሚችል ነገሩን መርምር፡፡ ነውርን አውግዝ፤ ክፉ ስራን ጥላ፡፡ ለተበዳዩ ቁም፤ ፍትህ ላጣው ድምጽ ሁንለት፡፡ ሰውን በሰውነቱ ውደድ፡፡ ማንም ሲጎዳ ስታይ እዘንለት፡፡ ያዘነን ሰው ለማፅናናት፣ የተከፋን ሃዘኑን ለመካፈል ያንተ ወገን እስከሚሆን ብቻ አትጠብቅ፡፡ ሰው ሁሉ የሰው ወገን ነው፡፡ ከሰውነትህ በፊት ጎጥህን፣ ዘመድህን፣ ብሔርህን አታስቀድም፡፡ ጭካኔን ኮንን፣ ክፉ ስራን ተቃወም፤ ጨካኙን ግን እዘንለት፡፡ ሰው መሆንን ልመድ! ራስህን መሆን ተለማመድ፡፡ ሌሎችን በመምሰል ዕድሜህን አታባክን፡፡ ባልሆንከው ከምትወደድ በሆንከው ብትጠላ ይሻላልና! ቸር ጊዜ! ------------------------------------ © እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.) ሠኞ ነሐሴ ፳፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.
2 261
12
بدون متن...
1 586
13
ስለሆነም በጥበብም ሆነ በሕይወት ውስጥ ውበት ከትርጉም ጋር አብሮ የሚነቃው ፈጽሞ ያልተነካ ...ያልተባለ አዲስ ነገርን ፍለጋ ከመባከን ሳይሆን፤ ያንኑ አሮጌውን የሰው ልጅ ሕይወት በራሳችን ምናብ ዳግም አዲስ አድርጎ ማቅረብ ሲቻል ነው። ​አሮጌው ታሪክ በሌላ ሰው ብዕር ሲቀርብ አዲስ ተአምር ሆኖ ይገለጣል፤ እውነተኛ ጥበበኛም አዲስ ነገር ፈጣሪ ሳይሆን ለጥንቱ ተፈጣሪ አዲስ ሩህ የሚዘራው ነው። ምን ትላላችሁ? © Mes Oud
2 047
14
◉ «አዲስ ነገር የለም ...ዳግም ልደት'ንጂ» ከዓመታት በፊት ተማሪ ሳለሁ ያየሁት አንድ ፊልም ነበር። Upside Down ይሰኛል። ዛሬ ድረስ አስታውሰዋለሁ። "እንዴት ያለ አዲስ ፈጠራ ነው?" ብዬ በወቅቱ ተደምሜበታለሁ። "ደራሲው እንዴት አሰበው? እንዴት እንደዚህ ያለ አዲስ ሀሳብ ሊፈጥር ቻለ?" ብዬ አስብ ነበር ለብዙ ግዜ። ኋላ ላይ ብዙ ነገር ስረዳ ያ የተደመምኩበት ስራ አዲስ የሚባል አልነበረም። እንደውም አሮጌ ነበር። ተደጋግሞ የተነገረን እኔም ደጋግሜ የሰማሁት ታሪክ ነበር። ምግቡ ሳይሆን የቀረበበት ትሪ ነበር አዲሱ። እንደውም ሀዲስ አለማየሁ የተባሉ የሀገሬ ደራሲ ከፃፉት "ፍቅር እስከመቃብር" ከተባለው ድርሰት ነጥዬ ማየት አልቻልኩም ነበር። እንዴት አላችሁ? ​➊ ፍቅር እስከ መቃብር ​ያው እንደምታውቁት በዛብህ የደሃ ገበሬ ልጅ ነው። የተሻለ እውቀት ሊቀስም ወደ ዲማ የተጓዘ፤ በዚያም የፊውዳሉ ባላባት የፊታውራሪ መሸሻ ልጅ የሆነችውን ሰብልወንጌልን አስተማሪነት እቤቷ ድረስ እየሄደ እንዲያስተምራት የተመደበ ሰው ነው። በዚህ አጋጣሚ በሁለቱ መካከል ጠጠር ያለ የፍቅር ስሜት ይፈጠራል። ​ነገር ግን በጊዜው በነበረው የፊውዳል ስርዓት፣ የባላባት ልጅ ከተራ ድሃ ጋር መጋባት ፈጽሞ የማይታሰብ ነበር። በዛብህ ፍቅሩን ማጣት ስላልቻለ ወዲህም የተቃጣበትን አደጋ ለመሸሽ ከአካባቢው ይኮበልላል...ከዛም ተንከራቶ ይሞታል። ሰብልዬም ቢሆን የወላጆቿን ፍላጎት ተቃውማ፣ ፍቅሯን ጠብቃ ለመኖር አለም በቃኝ ብላ ገዳም ትገባለች። ታሪኩ የሰው ልጅ ማህበራዊ መደብ ከእውነተኛ ፍቅር ጋር ሲጋጭ የሚያስከትለውን ስቃይ ያሳያል። ከብዙ በትንሹ። ❷ Upside Down ​የዚህ ፊልም ታሪክ የሚሰግረው ደግሞ Dual Gravity ባላቸው ሁለት ተቃራኒ ፕላኔቶች ላይ ነው። የመጀመሪያው Up Above ወይም የላይኛው ዓለም በመባል ይታወቃል። በሀብት የበለጸገ እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተንበሻበሸ ነው። ሁለተኛው ደሞ Down Below ወይም ታችኛው አለም ይሰኛል። ድሃ፣ የወደመ እና የተበዘበዘ ዓለም ነው። የሁለቱ አለማት ህግ ፈጽሞ እንዳይገናኙ ያዝዛል። የታችኛው አለም ሰው ወደ ላይኛው አለም ቢሄድ በስስበት ሀይል ህግ ምክንያት አካሉ የመቃጠል አደጋ ያጋጥመዋል። ​Adam ከታችኛው ድሃ አለም የተወለደ ወጣት ሲሆን፣ Eden ደግሞ ከላይኛው ሀብታም አለም የወጣች ሴት ናት። ሁለቱ ገና በልጅነታቸው ሁለቱ አለማት በሚገናኙበት ተራራ ጫፍ ላይ ተገናኝተው በምስጢር ይፋቀራሉ። ነገር ግን የድንበር ጥበቃዎች ፍቅራቸውን ደርሰውበት ሲያሳድዷቸው ኤደን ተከስክሳ ትወድቃለች፤ አዳም ደግሞ ኤደን የሞተች ይመስለዋል። ​ከአመታት በኋላ አዳም ኤደን በህይወት መኖሯን እና «TransCorp» በሚባል ሁለቱን አለማት በሚያገናኝ ትልቅ ኩባንያ ውስጥ እንደምትሰራ ያውቃል። አዳም ከታችኛው አለም የተገኘን ልዩ ፈጠራ በመጠቀም የራሱን የሰውነት ስስበት በመቀየርና አደጋውን ተቋቁሞ ወደ ላይኛው አለም በመግባት ኤደንን ፍለጋ ይጓዛል። ታሪኩ የፊዚክስ ህግ በመጣስ አዳም ከኤደን ጋር ለመገናኘት የሚያደርገውን ተጋድሎ የሚያሳይ በሳይንስ-ልብወለድ ዘውግ የቀረበ ፊልም ነው። ◉ ሁለቱም ስራዎች የተገነቡት Forbidden Love ላይ ነው። ሀዲስ አለማየሁ በፍቅር እስከ መቃብር ውስጥ የሰዎችን የመደብ ልዩነት በታሪክ፣ በባህል እና በፊውዳላዊ አስተሳሰብ ገለጹት። የUpside Down ደራሲ ደግሞ አሁንም ድረስ በሰው ልጅ መካከል ያለውን የሀብታም እና የድሃ ወይም የበላይ እና የበታች ክፍፍልን ወስዶ በ Physical Metaphor ወደ ሁለት ተቃራኒ የስስበት ሀይል ወዳላቸው ፕላኔቶች ለወጠው። የማህበራዊ መደብ ልዩነቱን በሳይንስ ማዕድ ላይ ፈትፍቶ ወደ ተፈጥሮ ህግ ቀየረው። ​እዚህ ጋር ነው «በጥበብ ውስጥ አዲስ ነገር የለም፤ ነባሩን እንደ አዲስ መስራት እንጂ» የሚለው ታዋቂ ሀሳብ የሚገዛን። Forbidden Love በስነ-ጽሁፍ እና በፊልም ውስጥ በጣም ከተደጋገሙ ጭብጦች አንዱ ነው። በቅርቡ በ Pixar አኒሜሽን የተሰራውን Elemental ፊልም አይቼ ነበር። በተፈጥሮ ህግ ፈጽሞ የማይገናኙ እና የማይነካኩ ሁለት ንጥረ ነገሮች እሳት እና ውሃ ተፋቅረው ነው። «እሳት እና ውሃ መነካካት አይችሉም» የሚለውን የተፈጥሮ ህግ እና የልማድ አጥር በመጣስ ፍቅራቸውን ለማስቀጠል የሚያደርጉት ጥረትን ያሳያል። ልክ እንደ ሰብለና በዛብህ። የሼክስፒር Romeo and Juliet እና Titanicን የሚለያቸው ምንድነው? የብስና ባህር አይደለምን? ታዲያ አዲሱ ነገር ምንድንነው? ❸ «አዲስ ነገር የለም ...ዳግም ልደት'ንጂ» «በአስማት በትር ከአለመኖር ወደመኖር የሚመጣ ነገር የለም» በሚለው ሀሳብ ተጠምቄያለሁ። በፊት " አዲስ ፈጠራ አያልቅም" የምል ሰው ነበርኩ። «ዓለም ሰርክ አዲስ ሁና ሳለ ያልተባለ አዲስ ነገር ይኖራታልንጂ» ብዬ የማስብ። ኋላ ግን «በዱንያ ላይ ያልተባለ አዲስ ነገር መፍጠር የለም» ወደማለት ተቃረብኩ። ሁሉም አሮጌ ነው። ነገሮችን አዲስ የሚያስመስላቸው የቀረቡበት መንገድና የታዩበት የእይታ መነፅር ብቻ ነው። ጓደኛዬ በቅርቡ Habte Awalom የተባሉ ዘፋኝ በ 1978 የዘፈኑትን "እንደ ቢራቢሮ" የሚል ሸጋ ዘፈን ላከልኝ። ቴዲ በመጀመሪያ አልበሙ እንዳዲስ ዘፍኖታል። (ከመጀመሪያው አንፃር የቴዲ ብሽቅ ነው) እና ምናልኩ? ማንኛውም ጥበበኛ የቀደሙትን ትከሻ ተንተርሶ ነው የሚቆመው። ምናልባት habte awalom "እንደ ቢራቢሮ"ን በተዓምር አልከሰቱትም። የሆነ አዝማሪ ወይም አንድ እረኛ ሲያንጎራጉሩት ሰምተው ሊሆን ይችላል። በጥበብ ውስጥ መኮረጅ እና በተጽዕኖ መውደቅ ያሉ ናቸው። መጥፎው ኩረጃ የሌሎችን ቅርጽ እንዳለ መቅዳት ሲሆን፣ በጎው ተጽዕኖ ግን ነባሩን ሀሳብ ወስዶ የራስን ነፍስ ዘርቶበት እንደ አዲስ ማቅረብ ነው። ​◉ ባጭሩ በጥበብ አለም ጥሬ እቃው ያው አሮጌው የሰው ልጅ ህይወት ነው። አዲሱ ነገር ግን ያንን አሮጌ የምንቀርጽበት የራሳችን ምናብ፣ ፈጠራ እና ስሜት ነው። ግና «አዲስ ፈጠራ የለም» ሲባል የሰውን ልጅ የፈጠራ አቅም ዝቅ ለማድረግ አይደለም። የፈጠራን አኸላለቅ ለመረዳትንጂ። በጥበብ አለም ውስጥ ሙሉ በሙሉ ከምንም ተነስተን የምንፈጥረው አዲስ ነገር አለመኖሩን ለማመልከት ብቻ ነው። እንጂ ፈጠራ አለ። በሌላ ቋንቋ ፈጠራ ማለት ነባር ሀሳቦችን፣ ስሜቶችንና እውነታዎችን በራሳችን አዲስ መነፅር አጣጥሞ እንደገና የማቅረብ ጥበብ ነው። በጥበብ ዓለም የምናነሳቸው ጭብጦች በሙሉ የተደጋገሙ ናቸው። ስላላገኘናቸው፣ ስላልደረሱን ነውንጂ በሆነ ቦታና በሆነ ሰው ተብለዋል። ፍቅር፣ ሞት፣ አገር፣ ክህደት፣ ብቸኝነት... የህይወት ትርጉም ፍለጋ ....ከጥንት እስከ ዛሬ ተስተጋብተዋል። አዲስ ነገር የሚሆነው ጭብጡ ሳይሆን የጥበበኛው እይታ ነው። ​አሜሪካዊው ደራሲ Mark Twain "ፈጠራ ማለት የተበታተኑ ነባር ሀሳቦችን አጣጥሞ አዲስ ቅርጽ መስጠት ነው" ያለው ለዚህ መሰለኝ። ​«There is no such thing as a new idea. It is impossible. We simply take a lot of old ideas and put them into a sort of mental kaleidoscope. We give them a turn and they make new and curious combinations.» ​
2 152
15
+1
بدون متن...
1 852
16
እስቲ ዛሬ ስለደበረኝ ላስደብራችሁ። የካርል ማርክስ የትርፍ ዋጋ (Surplus Value) ቲዎሪ በፎቶ ሳገኘው የገባኝን ያህል ላስረዳችሁ ወደድኩ። የካርል ማርክስ የትርፍ ዋጋ «Surplus Value» ቲዎሪ የካፒታሊዝም ትርፍ እንዴት ነው የመጣው የሚለውን ለማብራራት የቀረበ ሀሳብ ነው። ካርል ማርክስ እንዲህ የምትል አባባል አለችው፦«The worker creates the wealth, capital claims the profit» ምን ማለቱ መሰላችሁ ሰራተኛው ከሚከፈለው ደሞዝ በላይ ዋጋ ይፈጥራል፤ ያ ተጨማሪ ዋጋ ግን ለካፒታሊስቱ ነው ትርፍ የሚሆነው። በፎርሙላ ሲቀመጥ፦Surplus Value (s) = Total Value Created (v) − Wages (w) ይመስላል። በአጭሩ ሳስረዳችሁ፦ S= V−W S= የትርፍ ዋጋ (Surplus Value) V= ሰራተኛው የፈጠረው ጠቅላላ ዋጋ W= የተከፈለው ደሞዝ ይወክላል። ለምሳሌ አንድ ዳቦ ጋጋሪ በቀን 1000 ብር የሚያህል ዋጋ ይሰራል እንበል። ደሞዙ ግን 400 ብር ነው። S= 1000 − 400= 600 ብር ይመጣል። እዚህ ጋር ማርክስ ይህ 600 ብር ከየት መጣ አይልም። ይልቅስ ለምንስ ለካፒታሊስቱ ብቻ የሚገባ ዋጋ ሆነ ነው ጥያቄው። ይህን ጭዌ አልሰማችሁም። አንድ የኩባንያ ባለቤት አዲስ መኪና ገዝቶ ወደድርጅቱ ያቀናል። አዲሱን መኪና የተመለከተው ሰራተኛም በጉጉት አለቃውን ይጠይቀዋል፦«በጣም ምርጥ መኪና ነው የገዛኸው የምር አስቀናኸኝ» አለቃውም ፈገግ እንዳለ፦«አንተም አሁን ባለህበት አቋም ጠንከረ የምትሰራ ከሆነ ቀጣይ አመት ሌላ የተሻለ መኪና እቀይራለሁ!» 🤓 ማርክስ የሚለን ይሄንኑ ነው። ሰራተኛው ደሞዙን ለማግኘት ግማሽ ቀን ይሰራል፤ የቀረውን ግማሽ ቀን ደግሞ ለአለቃው ትርፍ ይሰራል። ሰራተኛው ጠንክሮ ይሰራል፤ አለቃው ጠንክሮ ትርፍ ይሰበስባል። ለምሳሌ አንድ ሰራተኛ በቀን 8 ሰዓት ይሰራል። በመጀመሪያው 4 ሰዓታት የቀኑን ደሞዝ 500 ብር ቢሰራ፤ በቀሪው 4 ሰዓት ደግሞ ሌላ 500 ብር ዋጋ መፍጠር ይጠበቅበታል። ነገር ግን የሚከፈለው 500 ብር ብቻ ነው። ያን ተጨማሪ 500 ብር ትርፍ ካላመጣ ቀጥታ ይባረራል። ስለዚህ የፈጠረው ጠቅላላ ዋጋ 1000 ብር ይሆናል። የሚያገኘው ደግሞ 500 ብር ነው። በመጨረሻም የትርፍ ዋጋ 500 ብር ይመጣል። ማርክስ ይህንን ነው «Surplus Value» የሚለው። ነገር ግን ማርክስ የሚያነሳው ጉዳይ የገንዘብ ብቻ አይደለም፤ በሥነ-ልቦናም ጭምር የሚፈተሽ ነው። ሰራተኛው ይህ ሥራ ከሌለው ገቢ እንደማይኖረው ያውቃል። ቤት ኪራይ፣ ምግብ፣ ቤተሰብ እና ዕለታዊ ወጪዎች ይጠብቁታል። ስለዚህ ሥራውን የማጣት ፍርሃት ብዙ ጊዜ የድርድር ኃይሉን ያዳክማል። በሌላ አነጋገር ሰራተኛው ስለደሞዝ ጥያቄ ካነሳ ስራውን የማጣት ስጋት ይጋረጥበታል። ይህን ፍርሃት የካፒታሊዝም ስርዓት እስከዛሬ እንዲቀጥል ካደረጉ ኃይሎች መካከል ነው። ምክንያቱም ሰራተኛው የተሻለ ክፍያ ቢፈልግም ሥራ አጥነትን ስለሚፈራ ያለውን ሁኔታ ለመቀበል ሊገደድ ይችላል። በዚህ ምክንያት ማርክስ የካፒታሊዝም ትርፍ surplus value «ያልተከፈለ የሰራተኛ ላብ» ነው ብሎ ያምናል። እዚህ ጋር ግን ካፒታሊስቶች መልስ አላጡም። መልሳቸውም ይሄ ነው። ባለካፒታሉ ገንዘብ አፍስሷል፣ የኪሳራ ስጋቱንም የሚሸከመውም እሱ ነው፣ ማሽኖችንና ቁሳቁሶችን የሚያቀርበውም እሱ ነው፣ ንግዱ ቢከስርም ኪሳራውን የሚሸከመው ለብቻው ነው፣ ስለዚህ ትርፉም ለካፒታሊስቱ የተገባ ነው። ብቻ የማርክስ «Surplus value» የትርፍ እሴት ቲዎሪ በኢኮኖሚክስ ውስጥ እስከዛሬ ድረስ ክርክር የሚያስነሳ ሃሳብ ሆኖ ቀጥሏል። ማርክስ የሚለው ባጭሩ የካፒታሊዝም ትርፍ የሚመጣው ሰራተኛው ከሚከፈለው በላይ ባፈሰሰው የላብ ዋጋ ነው፤ እና ይህ ሁኔታም በሰራተኛው የሥራ መልቀቅ ወይም የሥራ ማጣት ፍርሃት ላይ ጥገኛ ነው። እኔ ግን የካፒታሊስቶችን አስተሳሰብ ከግማሽ ፐርሰት በላይ እቀበለዋለሁ። በአጭሩ በምሳሌ እንግባባ ዘንድ ላስረዳችሁና ልሰናበት። «የዳቦው ዋጋ ለማን የተገባ ነው?» እስቲ በአይነ ህሊናችን አንድ ዳቦ ቤት እንሳል። የዳቦ ቤቱ ባለቤት ህንፃውን ተከራየ፣ ምድጃውን ገዛ፣ ዱቄቱን አመጣ፣ ንግድ ፈቃድም አወጣ። ይህ ሁሉ ወጪ እና ስጋት የባለቤቱ risky ነው። ከዚያ አንድ ዳቦ ጋጋሪ ቀጠረ። ይህም ሰራተኛ በቀን 100 ዳቦ ይጋግራል። እያንዳንዱ ዳቦ 20 ብር ቢሸጥ የቀኑ ገቢ 2000 ብር ይሆናል። ከ2000 ብሩ ውስጥ የዱቄት፣ የኤሌክትሪክ፣ የቤት ኪራይ እና ሌሎች ወጪዎች 1000 ብር ቢሆኑ 1000 ብር ይቀራል። ከዚያ የሰራተኛው ደሞዝ 400 ብር ቢሆን ቀሪው 600 ብር ለባለቤቱ ይሆናል። እዚህ ላይ ነው የካርል ማርክስ ጥያቄ የሚጀምረው፦«ያ 600 ብር ከየት መጣ?» እሱ ብቻ አይደለም ማርክስ የሚለን፦«ዳቦውን የጋገረው ሰራተኛው ነው። ዋጋውን የፈጠረውም እሱ ነው። የተከፈለው ግን 400 ብር ብቻ ነው፤ ቀሪው 600 ብር ግን የሰራተኛው ያልተከፈለ የላብ ዋጋ ነው።» ካፒታሊስቶች ግን ይህ ሃሳብ ውድቅ በማድረግ እንዲህ ይላሉ፦«ዳቦውን የጋገረው ሰራተኛው ቢሆንም ዳቦ ቤቱን የከፈተው፣ የፋይናንስ ስጋቱን የሚወስደው፣ ኪሳራ ቢመጣ እራሱ ሊሸከም የሚችለው ባለቤቱ ብቻ ነው።» እውነት ለመናገር ግን ከዚህ በላይ ውስብስብ ነው። ምክንያቱም ኢኮኖሚ በቁሳቁስ ብቻ አይገነባም፤ በአዕምሮም የተዋቀረ ሂደትም ጭምር ነው። አንድ ቀን ይህ ዳቦ ጋጋሪ በምሬት እንዲህ አለ፦«ይህን ሁሉ ዳቦ የምጋግረው እኔ ነኝ።» ባለቤቱም ፈገግ ብሎ መለሰለት፦«አዎ ነገር ግን ያለእኔ ምድጃ የት ትጋግረዋለህ?» ሰራተኛው እዚህ ጋር ዝምታ ብቻ ነው መልሱ። ይህ የኢኮኖሚ ጨዋታ ብቻ አይደለም፤ የአዕምሮ ጨዋታ Mind Game ጭምር ነው። ሰራተኛው ለራሱን «እድለኛ ነኝ ምክንያቱም ስራ አግኝቻለሁ» ብሎ ያስባል። ባለቤቱ ደግሞ እንዲህ ይላል፦«እኔ ነኝ እድል የሰጠሁት» እዚህ ጋር ሁለቱም በከፊል ትክክል ናቸው። በመጨረሻም ማርክስ ያነሳውን ጥያቄ ባጭሩ ስንዘጋው ትርፍ የምንለው ከየት መጣ ሳይሆን። ይህ ትርፍ ተገቢ በሆነ መልኩ ክፍፍል አልተደረገለትም ነው። ምክንያቱም ዳቦውን አንድ ሰው ብቻ አልጋገረውም፤ አንድ ሰውም ብቻም አይሸጠውም። ቢሆንም ሁላችንም እንደሕዝብ እራሳችንን ብንፈትሽ ስለ ዳቦው ዋጋ እንጂ ስለ ጋጋሪው ዋጋ አንከራከርም። ስለጋጋሪው ዋጋ ግድ የማይለው ገዢ ደግሞ ዳቦ መወደዱን አስመልክቶ ማማረር አይችልም። በርግጥ ግን የዳቦ ቤቱ ባለቤት ለዳቦ ጋጋሪው ደሞዝ ቢጨምር ኖሮ ካሉበት ሌሎች ወጪዎች ጋር ተደምሮ 20 ብር ይሸጥ የነበረው ዳቦ 25 መግባቱ አይቀሬ ነው። ስለዚህ መልሱ በአጭሩ መንግስት ጋር ተቀምጧል። የቤት ክራይ፣ የስንዴ ዱቄት እና ምድጃ እነዚህ ሁሉ የአንድ ሀገር ግብር መጨመርን ተከትሎ የሚመጣ የዋጋ ንረት ወይም መወደድ ነው!። © ሞገስ ዘአምድ
3 406
17
بدون متن...
2 594
18
------------------------------------ © እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.) ሠኞ ነሐሴ ፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.
3 148
19
‹‹አዲስ ሃሳብ ከፈለግክ የድሮ መፅሐፍትን አንብብ! (Old ideas, new minds) (እ.ብ.ይ.) አዲሱ ትውልድ የድሮን ነገር ሲያጥላላ አያለሁ፤ አሮጌው ትውልድ ደግሞ አዲሱን ዘመን በብዙ መንገድ ሲተች እሰማለሁ፡፡ ሁለቱም የየራሳቸውን ዘመን ብቻ በማደናነቅ ያለበቂ ምክንያት ስለሚተቻቹ ልክ አይሆኑም፡፡ በደምሳሳው የዛሬውን ሙሉ በሙሉ የሚያናንቁ የትናንት ናፋቂዎችም ብዙ ናቸው፡፡ የሆነው ሆኖ ከትናንቱም የሚወሰድ፣ ከዛሬውም የሚጣል አይጠፋም፡፡ ካለፈውም ሆነ ከወትሮው የማይወደድ ሃሳብ ይኖራል፡፡ የማያስፈልገውን ለማወቅ የትናንቱን ዘመን አስተሳሰብ መረዳት ግድ ይላል፡፡ አዲስ ሃሳብ ወይም አዲስ ፈጠራ እንዲሁ ከሰማይ ዱብ የሚል አይደለም፡፡ አዲስ ነገር ከአሮጌው ነው የሚወለደው፡፡ ዛሬ የትናንት ቀጣይ ነው፡፡ ነገም የዛሬ ውላጅ ነው፡፡ አዲስ ሃሳብ በራሱ አይፈጠርም፤ ካለፈው ጊዜ ሃሳብ ጋር በተራክቦ፣ በሙግት፣ በውይይትና በጥልቀት በማሰብ የሚመጣ ነው፡፡ ይሄን ለማወቅ ግን ትናንትን ማጥናት ግድ ይላል፡፡ ሰው አንድም ከተፈጥሮው ይማራል፤ አንድም ከተሞክሮው ይማራል፤ አንድም በማየትና በመስማት ብቻ ነገሮችን ይገነዘባል፤ አንድም ከመደበኛ ትምህርት ቤት አስኳላ ገብቶ አመለካከቱን ይቀርፃል፡፡ የሰው አዕምሮ የሚጎለብበትና የሚነቃበት መንገድ ብዙ ነው፡፡ ከችግሩ የሚማር አለ፤ ወድቆ በመነሳት አዲስ ሃሳብ የሚያገኝ አለ፤ በህይወት ውጣ ውረድ ውስጥ ሆኖ የኑሮ ፊደል የሚቆጥር ሞልቷል፤ በማጣት የሚማር አለ፤ በማግኘት የሚማር አለ፡፡ ከፍቅር የሚማር አለ፤ ከጸብና ከጥላቻም ግንዛቤ የሚያገኝ አለ፡፡ ከሀዘን የሚማር አለ፤ ከደስታው የህይወት ነገር የሚገባው ይኖራል፡፡ ከብቸኝነቱ፣ ከሰፊ ማህበራዊ ግንኙነቱ፣ ከአካባቢው፣ ከባህሉ፣ ከሃይማኖቱ፣ ከፖለቲካው፣ ወዘተ የሚማር አለ፡፡ ተፈጥሮን አንብቦ አመለካከቱን የሚያጎለብትም የትየለሌ ነው፡፡ ከነዚህ ሁሉ መጽሐፍ ማንበብም አንደኛው የዕውቀት መሰብሰቢያ፣ አዕምሮን ማንቂያ፣ አመለካከትን ማስፊያ መንገድ ነው፡፡ ነገር ግን ያነበበ ሁሉ የነቃ ነው ማለት አይቻልም፡፡ መረጃ ያለው ሁሉ ዕውቀት ያለው ነው ብሎ መደምደም ስህተት ነው፡፡ አዋቂ የሆነ ሁሉ ትክክል፤ ቅንና ደግ ሰው ነው አይባልም፡፡ በዕውቀቱ የሚያጭበረብር፣ በመረጃው የሚሰርቅ የተማረ ሌባ እልፍ ነው፡፡ መረጃ ኖሮት ዕውቀት ከሌለው ከመዝገብ-ቤት አይለይም፤ ዕውቀት ኖሮት ቅንነትና ደግነት ከጎደለው ሰብዓዊነት የማይሰማው የሰው ሮቦት ነው የሚሆነው፡፡ በመረጃው ተጠቅሞ፣ ባነበበው አገናዝቦ አዲስ ጠቃሚ ሃሳብ ማመንጨት ሲችል ነው አንባቢው በማንበቡ ተጠቅሞበታል የሚባለው፡፡ ሩሲያዊው የባይሎጂ ተመራማሪ የነበረው ኢቫን ፓቭሎቭ ‹‹አዲስ ሃሳብ ከፈለግክ የድሮ መፅሐፍትን አንብብ!›› ይላል፡፡ እንደኢቫን አገላለፅ የድሮ መፅሐፍት የሚገልጡልህ አዳዲስ አተያዮች አሉ ለማለት ነው፡፡ ትናንትን መረዳት ዛሬን ለማቅናት ጠቃሚ ነው፡፡ ብዙዎቹ የዛሬ ችግሮቻችን ዋና ምንጮች ትናንት ላይ የተፈጠሩ ናቸው፡፡ የትናንትን ሁኔታ ለመገንዘብ ስለትናንት የተፃፉ መፃህፍትን ማንበብ ጥሩ ነው፡፡ አንዳንዶቹ ጠቃሚ ሃሳቦች በዘመናዊነት ስም ተረስተዋል ወይም ዘመን አልፎባቸው እንደኋላ ቀር ታይተዋል፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ትንሽ ለወጥ ተደርገው፣ ስም ተቀይሮላቸው እንደአዲስ ዘመናዊ ሃሳብ ተብለው ይቀርባሉ፡፡ የተረሱ ሃሳቦች ወይም ችላ የተባሉ ችግሮች መፍትሄ እስካልተበጀላቸው ድረስ የዛሬም ሆነ የነገ አደጋዎች እንደሆኑ ይቀጥላሉ፡፡ የቆዩ መፅሐፍትን ማንበብ ታሪክን ማጥናት ብቻ አይደለም፡፡ በጊዜው ያልታዩ ሃሳቦችን ነፃና ገለልተኛ ሆኖ መልሶ በማየት ከዛሬ ጋር ተወራራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ይጠቅማል፡፡ የአዲሱን ዘመን መፅሐፍትን ማንበብ የአዲሱን ትውልድ አስተሳሰብ ለመረዳት ይጠቅማል፤ የቆዩ መፅሐፍትን ማንበብ ግን አመለካከታችንን ሰፊ፣ እይታችንን ሩቅ ተሻጋሪ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ለዚህ ነው አይዛክ ኒውተን ‹‹አርቄ ማየት ከቻልኩኝ ከትላልቆቹ ትከሻ ላይ ቆሜ አያለሁ(“If I have seen further, it is by standing on the shoulders of giants.”)›› የሚለው፡፡ ኒውተን አዲስ ግኝት ወይም ፈጠራ ትናንትን በመተው የሚገኝ አይደለም፤ ያለፈውን በደንብ አንብበህ ስትረዳ ነው አርቀህ መመልከት የምትችለው ማለቱ ነው፡፡ ሬኔ ዴስካርቴም ‹‹አሪፍ መፃህፍትን ስታነብ ከድሮው ዘመን ምርጥ ጭንቅላቶች ጋር እንደመነጋገር ያለ ነው (“The reading of all good books is like a conversation with the finest minds of past centuries.”)›› ይላል፡፡ ሲ.ኤስ. ሊዊስም ‹‹አዲስ መፅሐፍ ካነበብክ በኋላ ሌላ አዲስ መፅሐፍ ከማንበብህ በፊት በመሐል አንድ የድሮ መፅሐፍ አንብብ፡፡ ይሄ አሪፍ ህግ ነው (“It is a good rule, after reading a new book, never to allow yourself another new one till you have read an old one in between.”)›› ሲል ያለፈውን ዘመን ካሁኑ ዘመን ጋር እያሰተያየንና እያነፃፀርን እንድናነብ ይመክረናል፡፡ በሌላ ጎኑ ደግሞ ፍራንስስ ቤከን የድሮ መፅሐፍቶችን ማንበብ ብዙ ጥቅም የለውም ብሎ ያምናል፡፡ ከዛ ይልቅ አዲስ ችግር አዲስ እውቀት፣ አዲስ አተያይና አዲስ መላ ስለሚፈልግ ወደድሮ መፃህፍት መመለስ አያስፈልግም ባይ ነው ቤከን፡፡ ይኸው ሰው በሌላ ሃሳቡ ላይ የድሮ መፃህፍትን አምኖ ከመቀበል ይልቅ መርምሮ መቀበል እንደሚገባ ያስጠነቅቃል፡፡ ቤከን ‹‹የድሮ መፅሐፍት ውርስ ዕውቀቶችን ይሰጡሃል፤ ልምድህ ግን አዲስ ዕውቀት ይሰጥሃል›› ሲል መከራከሪያውን ያቀርባል፡፡ ዴስካርትም እንደጠርጣራነቱ ‹‹ከድሮው የወረስኩት የተሳሳተ ቢሆንስ (What if what I inherited is wrong) ?›› ሲል ይጠይቃል፡፡ ዴስካርቴ ማለት የፈለገው የድሮ መፅሐፍ ስናነብ ቀጥታ ከመውረስ ይልቅ እየሞገትን፣ እየፈተንንና እየጠየቅን ቢሆን አዲስ ሃሳብ ማዋለድ እንችላለን ማለቱ ነው፡፡ ኒቼም በዚህ ጉዳይ ላይ ዝም አላለም፡፡ ኒቼ እንደውም ‹‹አዲስ ሃሳብ ፈጣሪም እንጂ ምሁር ብቻ ከመሆን ተጠበቅ (beware of becoming a scholar instead of a creator)›› ሲል ይመክራል፡፡ ብዙ በማንበብ ያለፈ ዘመን ታሪክ ብቻ በጭንቅላትህ ውስጥ አጭቀህ አዲስ ነገር ለመፍጠር እንዳይሳንህ ማለቱ ነው፡፡ የምታነበው አዲስ ሃሳብ ከመፍጠር ይልቅ አዕምሮህን በመረጃ ለማጨናነቅ ከሆነ ንባብህ ዋጋ የለውም እያለህ ነው፡፡ ወዳጄ ሆይ.. በርግጥ የድሮ መፃህፍት ሁሉ አሪፍ ናቸው ማለት አይደለም፡፡ ደስ የማይሉ፣ ብዙ ትርጉም የማይሰጡ፣ ተሻጋሪ ሃሳብ የሌላቸው መፅሐፍትም ይኖራሉ፡፡ ነገር ግን ይዘታቸውን ለመገምገምም እንኳን የግድ የመፅሐፍቶቹን ገጽ እየገለጥን ማንበብ ይጠበቅብናል፡፡ ሰው ስለነገረን ብቻ አንድን መፅሐፍ ማድነቅም ሆነ ማጥላላት አይቻልም፡፡ ራሳችን አንብበን ነው መፍረድ ያለብን፡፡ ያም ሆነ ይህ ግን አንብበህ በባህሪህ ላይ ለውጥ ካላመጣህ፤ ለሀገርህ ችግር ጠብ የሚል መፍትሄ ካላበጀህ ማንበብህ ትርፉ ምንድነው? ታሪክ መተንተኑ የተሻለ አዲስ ታሪክ ካላሰራ ትርፉ ወሬ ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ ለማንኛውም የድሮውንም የአሁኑንም እየመዘንክ፣ እየሞገትክ፣ የራስህን አዲስ ሃሳብ እየፈጠርክ አንብብ!! ቸር ንባብ! ደግ ምናብ!
3 080
20
بدون متن...
2 144