ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖 的分析概览
频道 ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖 (@bookshelf13) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 18 589 名订阅者,在 书籍 类别中位列第 1 890,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 813 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 18 589 名订阅者。
根据 16 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -163,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 11.37%。内容发布后 24 小时内通常能获得 4.27% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 115 次浏览,首日通常累积 795 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 14。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"”
凭借高频更新(最新数据采集于 17 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 书籍 类别中的关键影响点。
18 589
订阅者
-124 小时
-167 天
-16330 天
数据加载中...
吸引订阅者
七月 '26
七月 '26
+15
在0个频道中
六月 '26
+12
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+108
在1个频道中
Get PRO
四月 '26
+31
在1个频道中
Get PRO
三月 '26
+16
在0个频道中
Get PRO
二月 '26
+15
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+21
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+36
在1个频道中
Get PRO
十一月 '25
+42
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+31
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+31
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+60
在0个频道中
Get PRO
七月 '25
+44
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+72
在0个频道中
Get PRO
五月 '25
+451
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+460
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+500
在4个频道中
Get PRO
二月 '25
+317
在2个频道中
Get PRO
一月 '25
+421
在1个频道中
Get PRO
十二月 '24
+481
在1个频道中
Get PRO
十一月 '24
+275
在1个频道中
Get PRO
十月 '24
+244
在1个频道中
Get PRO
九月 '24
+254
在2个频道中
Get PRO
八月 '24
+307
在2个频道中
Get PRO
七月 '24
+388
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+231
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+241
在1个频道中
Get PRO
四月 '24
+354
在3个频道中
Get PRO
三月 '24
+325
在2个频道中
Get PRO
二月 '24
+251
在0个频道中
Get PRO
一月 '24
+96
在0个频道中
Get PRO
十二月 '23
+184
在1个频道中
Get PRO
十一月 '23
+141
在0个频道中
Get PRO
十月 '23
+96
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+46
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+119
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+158
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+143
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+79
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+59
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+62
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+182
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+195
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+468
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+92
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+399
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+71
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+91
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+205
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+198
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+317
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+718
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+177
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+356
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+36
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+213
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+243
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+908
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+917
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+873
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+219
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+59
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+125
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+430
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+396
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+304
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+354
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+14 056
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 17 七月 | 0 | |||
| 16 七月 | 0 | |||
| 15 七月 | +1 | |||
| 14 七月 | +1 | |||
| 13 七月 | +1 | |||
| 12 七月 | +4 | |||
| 11 七月 | +1 | |||
| 10 七月 | +4 | |||
| 09 七月 | 0 | |||
| 08 七月 | +1 | |||
| 07 七月 | 0 | |||
| 06 七月 | 0 | |||
| 05 七月 | +1 | |||
| 04 七月 | 0 | |||
| 03 七月 | 0 | |||
| 02 七月 | +1 | |||
| 01 七月 | 0 |
频道帖子
ከተምኔት ወደ ሳይንስ የሚለው ያ ሶሻሊስታዊ መፈክር በነገራቼን ላይ ብዙ መሣጭ ነገሮች ነበሩት። ለዛዘመን እመርታዎችም ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ ነበር።
"ኢህቲአኔደር"፣ ወይም "እንደሰው በሜድር፣ እንደዓሣ በባህር" በሚሉ ርዕሶች ከሶቭየቶች ፕሮግረስ (ራዱጋን ነበር የማስታውሰው ሁሌ) የተተረጎመው ይህ መፅሐፍ በውስጤ የማይረሳ ትውስታንና መነሳሳትን ጥሎ ያለፈ፣ ሁሌም ደማቅ (vivid) ምስሎቹ አብረውኝ የሚኖሩ አስገራሚ ሳይንሳዊ ልብወለድ መፅሐፍ ነበር።
የመፅሐፉን ፎቶ ለጥፈው፣ ይህን የቆየ ትውስታ ለመቆስቆስና ለወዳጆቼ ለማጋራት ያነሳሱኝን ሰብለ የመፅሐፍት ማከፋፈያ (የፌስቡክ ገፅ) አመሠግናለሁ።
ትናንት ያነበቡ፣ አሸና ያሰቡ፣ ትናንታቸውን አልፈው ዛሬያችንን አሸጋግረው አይተውት ነበር። እናንብብ፣ እና ጊዜያችንን እንቅደመው! እንሻገረው።
ሠርተንበት፣ ተሳስበን፣ አፍቅረንበት፣ ተደስተንበት፣ አቅማችንን አሟጠን ተጠቅመንበት፣ ረክተን፣ አበርክተን፣ ተካፍለን፣ አንብበን.... እንለፈው ዛሬያችንን።
ቺርስ!
© Assaf Hailu
| 2 | ኢህቲአንደር — እንደ ሰው በምድር፣ እንደ ዓሣ በባህር
________
(ከደርግ ዘመን ምርጥ ሥጦታዎች አንዱ)
ይሄን መፅሐፍ ከሰብለ መጽሐፍት አከፋፋይ የፌስቡክ ገፅ ላይ ሳገኘው ተደንቄያለሁ። የሃይስኩል ትዝታዎቼን ጎልጉሎ አመጣብኝ።
10ኛ ክፍል ላይ ነበር ያነበብኩት። አማን የሚባል የክፍሌ ተማሪና ጓደኛዬ የነበረ (10ኛ ስፔሻል ክላስ) ይህንን የኢህቲአንደርን ታሪክ በፊልም አይቶ ይሁን መፅሐፉን አንብቦ የሚገርም አድርጎ ተረከልኝ። መች አግኝቼ ባየሁት እያልኩ ውስጤ ቀረ።
በኋላ አሁን ማን እንዳዋሰኝ ብረሳውም - ምናልባት ራሱ አማን ይሆናል - አገኘሁት መፅሐፉን። "እንደ ሰው በምድር እንደ ዓሣ በባህር"። ምናልባት ይሄ መፅሐፍ ሁለቴ ሳይተረጎም አይቀርም፣ ሁለቴ ሳላነበውም አልቀረሁም። "ኢህቲአንደር" በሚል ርዕስም ታትሟል።
ደራሲው የሶቭየት ራሺያ ደራሲ አሌክሳንደር ቤላዬቭ ለዚህ መፅሐፉ የሰጠው ርዕስ በእንግሊዝኛ ሲተረጎም "Amphibian Man" የሚል ነበር። የተፃፈውም በ1928 እኤአ ነው። ወደ አማርኛ የተተረጎመበት መንገድ፣ ከርዕሶቹ ጀምሮ፣ ድንቅ ይመስለኛል።
ቤላዬቭ ሳይንሳዊ ልብወለዶችን በመፃፍ በዓለም የታወቀ ቀደምት ደራሲ ነው። ከሌሎች መፅሐፎቹ መሐል "አየር ቸርቻሪው" የሚለውን መፅሐፉንም አግኝቼያለሁ።
በተመሳሳይ ዘውግ በመፃፍ በዓለም ከታወቁት ከፈረንሳዊው ደራሲ ዡልስ ቨርን እና ከእንግሊዛዊው ኸርበርት ዌልስ ጋር ያነፃፅሩታል።
እኔ ደሞ ከእንግሊዛዊቷ ጉደኛ የፍራንከንስታይን ሳይንሳዊ ሆረር ልብወለድ ደራሲ ከሜሪ ሼሊ ጋር አነፃፅረዋለሁ። ሜሪ ሼሊ በአጭር መቀጨቷና ምሥጢራዊ አሟሟቷ (ሰጥማ መገኘቷ) ሁሌ አንጀቴን ይበላዋልና አልረሳትም።
ብዙውን የመፅሐፉን ታሪክ ረስቼዋለሁ። ግን በውስጤ የቀረና ለዘለዓለሙ የማይረሳኝ የሚመስለኝ ገፀባህርይ፣ ከራሱ ከኢህቲአንደር ቀጥሎ፣ አርጀንቲናዊው ቀዶጠጋኝ ሃኪምና ሳይንቲስት የሆነው ዶክተር ሳልቫቶር ነው።
ዶክተር ሳልቫቶር ኢህቲአንደርን ይወልዳል። ልጁ ነው። ግን ህፃኑ ልጅ ህይወቱን ለአደጋ የሚያጋልጥ የመተንፈስ ችግር ያጋጥመዋል።
እና ልጁን ከሞት ለማዳን ሲል በላብሯቶሩ አኔዱን እንስሳ ከሌላው ጋር እያዳቀለ ከሚመራመርባቸው ፍጡራን መካከል እጅግ ጠንካራ የሆነውን የሻርክ ሳንባ መርጦ ይገጥምለታል ለልጁ። Transplantation ሠራለት።
ይሄ ድርሰት በተፃፈበት ጊዜ የሰው አካል ንቅለ-ተከላ ገና እውን አልሆነም ነበር። እና ልክ ከላይ እንደጠቀስኳቸውና እንደሌሎቹም (እንደነ አይዛክ አሲሞቭ)፣ መፅሐፍቱ ወይም የደራሲያኑ የማሰላሰል አቅም፣ የእውነተኛውን ዓለም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቀድሞ የተራመደ ነበር።
ምናልባትም ይሄን የመሠሉ መፃህፍት ለተከታዮቹ የሰውልጅ ሳይንሳዊ እርምጃዎች፣ ጥንስሱን ሃሳብ አቀብለዋል። ኤች ጂ ዌልስ ስለ ኢንቪዚቢሊቲ ሲፅፍ የዛሬ ዘመኖቹ ስቲልዝ ፋይተር ጄቶችናሌሎች እልፍ ቴክኖሎጂዎች አልታሰቡም።
ዡልስ ምድርን በ80 ቀን ውስጥ ሳያቋርጡ ስለመሽከርከር አድቬንቸር ሲፅፍ፣ ገና እነዚያን የደደራሲውን ህልሞች እውን ሊያደርጉ የሚችሉ የአቪዬሽንም ሆነ የሌላ ትራንስፖርት ዘዴዎች ገና እንጭጭ ነበሩ። አልተፈጠሩም ነበር።
ይህም ኢህቲአንደር መፅሐፍ የጀነቲክ ኢንጂነሪንግንና መሰል ባዮቴክ ሳይንሶችንና ግኝቶችን የቀደመ ነው። ማሰብ ከሳይንስ እንደሚቀድም፣ መፅሐፍትም ከጊዜ አፈናጥረው ወደ ወደፊቱ ዘመን የሚያሻግሩ እጅግ ኃይለኛ የአዕምሮ ትጥቆች መሆናቸውን በዚህ መፅሐፍና በሌሎቹም መረዳት ይቻላል።
ኢህቲአንደር እንደ ሰው በምድር ላይ ኖርማል ሰው መስሎ ይኖራል። ግን ደሞ የሻርክ ሳምባ ስለተገጠመለት እና እንደ ዓሦች የመተንፈሻ ስንጥብ ሥርዓተ አካልም ስለተሠራለት፣ ያሰኘውን ያህል ጊዜ በባህር ውስጥ እየዋኘ መቆየት ይችል ነበር። ከሰዎችም ተነጥሎ ወደ ባህር ፍቅሩ ያዘነብል ነበር።
በመሐል አንዲቷን ምድራዊ ጉብል ያይና በፍቅሯ ይነደፋል። እሷም ትወደዋለች። ግን ምሥጢሩን መናገር ይኖርበታል። በዚህ ጭንቅ መሐል አንድ የከበሩ ማዕድናት ስግብግብ ነጋዴ የኢህቲአንደርን የተለየ ችሎታ ይደርስበትና ከባህር ወለል ላይ የከበሩ ኮራሎችን እንዲያወጣለት ሊያግባባውና ሊያስገድደው ይሞክራል።
በዚህ መሐል የዶክተር ሳልቫቶር ምሥጢራዊ ላቦራቶሪ ምሥጢሯ ያፈተልካል። ሀገሩ ሁሉ በእንግዳ ዜናዎች ይታመሳል። በአርጀንቲናው ዶክተር ሳልቫቶር የምርምር ግቢ ውስጥ የእባብ አካልና የድመት ጭንቅላት፣ የወፍ ጭንቅላትና የጅብ አካል፣ የአንበሳ መዳፍና የአህያ ፊት የያዙ፣ የተዳቀሉ እንግዳ ፍጥረታት ይገኛሉ።
ዶክተሩ ለፍርድ ይቀርባል። የሀገሩ ጳጳስ ሊመሠክሩበት ይቀርባሉ በችሎት። እና ፈጣሪ ለሁሉም የሚበጀውን ተፈጥሯዊ አካል ፈጥሮለት፣ መልካም እንደሆነም አይቶ፣ ባርኮ ነው ወደ ምድር ያመጣን፣ እና አንዱን እንስሳ ከሌላው ጋር ማዛነቅ ፈጣሪን ማስቆጣትና ከፈጣሪ ጋር መፎካከር ነው፣ ውጉዝ ከመ አርዮስ ነው ይላሉ!!
ዶክተር ሳልቫቶር በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ አንድ ጥያቄ ያቀርብላቸዋል ለጳጳሱ፦ "እርስዎ ባለፈው ትርፍ አንጀት በሆድዎ ውስጥ ወጥቶብዎት፣ ቆርጬ አውጥቼልዎት ከሞት አትርፌዎታለሁ አይደል?" ብሎ ይጠይቃቸዋል። በአዎንታ ይመልሳሉ።
ከዚያ፣ የእርስዎን ነፍስ ለማትረፍ በእግዜሩ ሥራ ገብቼ አካልዎትን ስቆርጥና ስቀጥል እግዜር አይወደውም ብለው አልተቃወሙኝም ነበር፣ እንዲያውምጰበጣም ተደስተው መረቁኝ አይደለም? — በአዎንታ ይመልሳሉ።
ታዲያ የእርስዎን ትርፍ አንጀት ቆርጦ ማውጣት እግዜር የፈጠረውን የሰው አካል መንካት አይደለም? ለእርስዎ ሲሆን ብቻ የተባረከ፣ ለሌሎች ሲሆን ደሞ የተኮነነ ይሆናል ማለት ነው ተመሳሳይ ድርጊት?
የሰዎችን ህይወት የሚያተርፍ ከሆነስ በእንስሳት ቤንመራመርና አካላቸውን ብንዋስ ምን አለበት? ሁሉ ለሰው አልተሰጠውም? በምድሪቱ ሁሉ ላይ እንዲሰለጥን አልተሰጠውም የአዕምሮ ፀጋ ለሰውልጅ?
ያዥጎደጉድባቸዋል ጥያቄውን። ጳጳሱ ከንፈራቸው ይንቀጠቀጣል። በእፍረት ፊታቸው ይቀላል። ችሎት የተሰበሰበው ሰው ዶክተሩን ይደግፋል።
በመጨረሻም ያሸንፋል መሠለኝ አርጀንቲናዊው ዶክተር ሳልቫቶር። ግን ሳይንሳዊ ላብራቶሪው ይወረስበትና ይዘጋበታል። የተለየ ፍጡራኑም ይጠፋሉ።
የሰውን ልጅ ዘር ከሻርክ ሳንባና ስንጥብ ጋር ብትደቅለውም፣ ከመላዕክት ክንፍ ብትሠራውም፣ ከኔፊሊምስ ጋር ብታራክበውም፣ አሊያም የአህያ ሆድ ብታሸክመውም፣ የሰውልጅ የሰውነቅንጣት እውስጡ እስካለ ድረስ፣ የማፍቀር ፀጋው ከውስጡ አይጠፋም የሚል መልዕክቱን ሊያስተላልፍልን የፈለገ ይመስላል የኢህቲአንደር ደራሲ።
በተጨማሪም በሰዎች ተፈጥሮ ውስጥ ያደረውን የስግብግብነት፣ ትርፍን በማንኛውም ዋጋና መሥዋዕትነት የማሳደድ ሰዋዊ አባዜያችንን ልክ ካላበጀንለት፣ ወደ ምዓይነት ትራጀዲ እንደሚጨምረንም ሊያሳይ ሞክሯል ደራሲው።
ያው በ1928 እኤአ በሶቭየት ራሺያ ሳይኔቲፊክ ሶሻሊዝምን እንገነባለን ተብሎ ሸብ ረብ የሚባልበት የርዕዮተዓለሞች ዘመን ስለነበረ፣ እና ደራሲውም በሶቭየት ያለ ደራሲ ስለሆነ፣ ... ርዕዮተዓለማዊ መልዕክቶችም አይጠፉትም መፅሐፉ።
ወደፊት ለሰውልጅ የጋራ ጥቅም እንዲውል አድርገን፣ ባህላዊና ኃይማኖታዊ ኩነኔዎችን ተሻግረን፣ ሳይንስን ብናዳብር፣ ተፈጥሮን በቁጥጥራችን ሥር ማዋል አይሳነንም፣ ...
ሁሉ በእጃችን ነው፣ ሰውን ሰው ያደረገው ሥራና መተሳሰብ ነው፣ ሶሻሊስታዊ ቁስአካላዊነት ስግብግቡን ካፒታሊዝም ያሸንፋል፣ ወዘተ. የሚሉ መፈክሮችንም በውስጡ አንግቧል። | 730 |
| 3 | 没有文字... | 701 |
| 4 | ወንጌላዊ ኦኔስሞስ ነሲብና ዳግማዊ ምኒልክ፣
(ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ በእንግሊዝኛ እንደጻፉት፣ ሲሣይ ተፈራ መኮንን ወደ አማርኛ እንደተረጎመው)
እንደ ልጅ ልጃቸው አቶ ኢዶሳ ገመቺስ ከሆነ ኦኔስሞስ ነሲብ የተወለዱት በኢሉባቦር ሁርሙ በሚባለው አካባቢ ሲሆን ዘመኑም 1842 ዓ.ም ነው፡፡ የኦኔስሞስ ነሲብ የልጅነት ስማቸው ሂካ ሲሆን ሂካ ማለትም በኦሮምኛ ፈቺው ወይም ተርጓሚው እንደማለት ነው፡፡ ወላጆቻቸው እንደትንቢት ሂቃ ብለው የሰየሟቸው ኦኔስመስ፣ ልክ እንደስማቸው የመጀመሪያውን የመጽሀፍ ቅዱስ የኦሮሚኛ ትርጉም በማዘጋጀታቸው ታረክ ሲያስታውሳቸው ይኖራል፡፡
የሂካ የልጅነት ጊዜ አሳዛኝ ነበር፡፡ አባታቸው በ4 አመት እድሜያቸው እንደሞቱ ሂካ በባሪያ ፈንጋዮች ታፍነው ተወሰዱ፡፡ ጠረፍ እስከሚደርሱ ድረስም በተለያዩ ጌቶች ስር በባርነት አድረዋል፡፡ አንዳንዶች ሂካ ነጻ ከመውጣታቸው በፊት 4 ጊዜ በባርነት እንደተሸጡ ሲጽፉ ሌሎች ደግሞ የተሸጡበትን ጊዜ 8 ያደርሱታል፡፡ በመጨረሻም ምጽዋ ላይ በነበረው የፈረንሳይ ቆንሲል ዌርነር ሙዚንገር አማካኝነት ሂካ ከባርነት ነጻ ወጥተዋል፡፡
ዌርነር ሙዚንገር በጥቅምት ወር 1863 ዓ.ም ከባርነት ነጻ የወጡትን ሂካ ለስዊድናውያን ሚሲዮኖች ያስረከቡ ሲሆን የሂካም ህይወት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በዘላቂነት መለወጥ ጀመረ፡፡ በመጋቢት ወር 1864 ዓ.ም የፋሲካ ቀን ዋና ጠባቂ ሆነው በተመደቡላቸው ሉንድሃል አማካኝነት ሂካ ኦኔስሞስ በሚል አዲስ ስም እንዲጠመቁ ተደረገ፡፡
ኦኔስሞስ ነሲብ በ1868 ዓ.ም ወደ ስዊድን የተላኩ ሲሆን በዛም ለ5 አመት ያህል ሃይማኖታዊ ትምርት ተከታትለዋል፡፡ ከስዊድን እንደተመለሱም የአጼ ቴዎድሮስ የቀድሞ ጸሀፊና የስዊድን ሚሽን ት/ቤት መምህር የነበሩትን የጎጃሙን አለቃ ኃይሉ ልጅ ምህረት ሐይሉን አገቡ፡፡ ከዚህ በኋላም ከንቲባ ገብሩ አቅደው ከፍጻሜ ያላደረሱትን መጽሀፍ ቅዱስን ለኦሮሞ ህዝብ የማስተማር እቅድ በትውልድ አካባቢያቸው ለመፈጸም ሂካ ወደዛው ለመጓዝ ወሰኑ፡፡
ነገር ግን አጼ ዮሀንስ የሚሲዮናውያንን እንቅስቃሴ አግደው ስለነበር፣ ኦኔስሞስ ወደ ወለጋ ለመጓዝ በቅድሚያ በቀይ ባህር ቀዝፈው ሱአኪን ወደምትባለው የሱዳን ወደብ መጓዝ ነበረባቸው፡፡ ከሱዳን ግዛት ወደ በርበር ካቋረጡ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ጠረፍ ወደ ሚያደርሰው አባይ በመጓዝ በታህሳስ ወር 1875 ዓ.ም ፋማካ ተብላ ወደምትጠራው የጠረፍ ከተማ ደረሱ፡፡ ነገር ግን ወደ ኢትዮጵያ ጠረፍ ማቋረጥ ከጀመሩ በኋላ ችግር እንዳለ በመስማታቸው ለመመለስ ተገደዱ፡፡
የመጀመሪያው ሙከራ ከከሸፈ ከ3 አመት በኋላ በ1878 ዓ.ም ኦኔስሞስ በታጁራና ሸዋ አድርገው ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ለመጓዝ ያደረጉት ጥረትም ንጉሥ ምኒልክ አስቀድመው የሰጡትን ተስፋ በሚጻረር መልኩ የሸዋ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ማቴዎስ ባሰሙት ተቃውሞ ምክንያት ውጤት አልባ ሆነ፡፡ በትውልድ አካባቢያቸው በአካል በመገኘት የወንጌልን ት/ት ለማስፋፋት በተደጋጋሚ ያደረጉት ጥረት ባለመሳካቱ ያዘኑት ኦኔስሞስ ነሲብ መጽሀፍ ቅዱስን የትውልድ አካባቢያቸው ህዝብ በሚገባው የኦሮምኛ ቋንቋ ለመተርጎም ወሰኑ፡፡
የ4 አመት ህጻን ሆኖ የትውልድ አካባቢውን ለለቀቀ ሰው መጽሀፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ መተርጎም ቀላል ባይሆንም፣ ኦኔስሞስ አስቴር ጋኖ በተባሉ የሊሙ ኦሮሞ ወዳጃቸው እየታገዙ የትርጉም ስራቸውን ቀጠሉ፡፡ በመጨረሻም ኦኔስሞስ አዲስ ኪዳንን እና ብሉይ ኪዳንን በቅደም ተከተል በ1885 ዓ.ም እና በ1891 ዓ.ም ወደ ኦሮምኛ በመተርጎም የትርጉም ስራቸውን አጠናቀቁ፡፡ የትርጉም ስራቸውን ለማከናወን በዋነኛነት የተጠቀሙት የአማርኛውን መጽሀፍ ቅዱስ ሲሆን በስዊድን ቋንቋ የተዘጋጀውን መጽሀፍ ቅዱስ ደግሞ ለማመሳከሪያነት ተጠቅመዋል፡፡
የመጀመሪያ ሚስታቸው ወ/ሮ ምህረት ከሞቱ ጥቂት አመታት በኋላ ኦኔስሞስ ሊዲያ ዲምቦ የተባሉትን የወለጋ ሲዮ አካባቢ ተወላጅ አገቡ፡፡ በአስመራ ከተማ ይገኙ ለነበሩ ወደ 500 የሚጠጉ የኦሮሞ ኮሚኒቲ አባላትም የወንጌል ትምህርትን ማስተማር ጀመሩ፡፡ ይህም የትውልድ አካባቢያቸውን ህዝብ በአካል በማስተማር ውጤታማ ስራ ከመስራታቸው በፊት በመፈጸሙ በጎ መንደርደሪያ ሆነላቸው፡፡
በ1885 ዓ.ም ኦኔስሞስ ሚስታቸውን፣ 3 ልጆቻቸውንና አዲስ ሰራተኞቻቸውን በመያዝ ከአስመራ ወደ አዲስ አበባ ተጓዙ፡፡ በአዲስ አበባም በከንቲባ ገብሩ አማካኝነት ኦኔስሞስ ከዳግማዊ ምኒልክና ከአቡነ ማታዎስ ጋር ተገናኙ፡፡ ኦኔስሞስም ለዳግማዊ ምኒልክ የተረጎሙትን የኦሮምኛ መጽሀፍ ቅዱስ ኮፒ በስጦታ አበረከቱ፡፡ በመጨረሻም ኦኔስሞስ በሚጓዙበት ሁሉ ድጋፍ እንዲደረግላቸው የሚያዘውን የዳግማዊ ምኒልክ ደብዳቤ ታጥቀው ወደ ወለጋ ተጓዙ፡፡
በወለጋ እንደደረሱም በደጃዝማች ገብረ እግዚአብሔር ሞሮዳ/ኩምሳ ሞሮዳ ከፍተኛ አቀባበል ተደረገላቸው፡፡ ኦኔስሞስ ለመጓዝ ያሰቡት ወደ ትውልድ አካባቢቸው ኢሉባቦር የነበረ ቢሆንም በዳግማዊ ምኒልክና በደጃዝማች ኩምሳ ሞረዳ በተደረላቸው የክብር አቀባበል ምክንያት ወንጌላዊ ስራቸውን በወለጋ ጀመሩ፡፡ ነጆ አካባቢ በምትገኘው ቦጂ ለኦኔስሞስ መሬት የተሰጣቸው ሲሆን በዛም የማስተማር ስራቸውን ጀመሩ፡፡
የኦኔስሞስን ሃይማኖታዊ ትምህርት በአደጋነት የተመለከቱ የኦርቶዶክስ አባቶች ባቀረቡት ክስ ምክንያት ኦኔስሞስ ወደ አዲስ አበባ ከተጠሩ በኋላ በአቡነ ማቴዎስ የእስራት ፍርድ ተፈረደባቸው፡፡ ነገር ግን ዳግማዊ ምኒልክ የአቡኑን ፍርድ ባለመቀበል ጉዳዩ በድጋሚ በአፈ ንጉሥ ኢስጢፋኖስ እንዲመረመር አዘዙ፡፡ በዚሁ መሰረት አፈ ንጉሡ ጉዳዩን በድጋሚ መርምረው ኦኔስሞስን ከቀረበባቸው ክስ በነጻ አሰናበቱ፡፡
ዳግማዊ ምኒልክ ከዚህም አልፈው ለኦኔስሞስ በንግድ ሚኒስቴር ስራ እንዲሰጣቸው አዘው የነበረ ቢሆንም፣ በወቅቱ የነበሩት ሹማምንት ኦኔስሞስ በንግድ ጉዳይ ለመስራት የሚያስችል እውቀትና ክህሎት የላቸውም በሚል የምኒልክን ትዕዛዝ ሳይፈጽሙ ቀርተዋል፡፡ ኦኔስሞስ ነሲብ ወደ ወለጋ ተመልሰው በተለይም ከልጅ ኢያሱ ዘመን ጀምሮ በነጻነት ሲያስተምሩ ከቆዩ በኋላ በሰኔ ወር 1923 ዓ.ም በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡ ነፍስ ይማር!
ምንጭ፣ Pioneers of Change in Ethiopia: The Reformist Intellectuals of the Early 20th Century, Prof Bahru Zewde, PP.46-49
ምስል፦ ኦኔስሞስ ነሲብ ከባለቤታቸውና ከልጆቻቸው ጋራ ኤርትራ ውስጥ የተነሱት ፎቶግራፍ ነው፡፡ ፎቶው የመቼ እንደሆነ አልተገለጸም።
© Jemal Abdulaziz | 1 276 |
| 5 | 没有文字... | 1 177 |
| 6 | "ጠያይም መላእክት
የኮምዩኒዝም ርኩስ መንፈስ "
ቤተ ማርያም ተሾመ
*******
© ቤልጅግ ዓሊ
ይህ መፀሐፍ እንደ ሃገራችን አቆጣጠር 2015 ነው የታተመው ። በቅርብ አዲስ አበባ በመጠሁ ጊዜ ከደራሲው ተፈርሞ ተሰጠኝ ። ደራሲው ስለሰጠኝና የደራሲውን ሌሎች ስራዎች ስለማውቅ አነበብኩት እንጂ በሁለት ምክንያቶች ላላነበው እችል ነበር ።
አንደኛው "የኮምዩኒዝም ርኩስ መንፈስ" የሚለው ርዕስ ኮምዩኒዝምን ብዙ ለማይጠላ እንደኔ ላለው ግለሰብ ዘጊ ነው ። በተለይ ባሁኑ ወቅት ማርክሲዝም የሃሳብ አቅጣጫ (school of thouhght ) መሆኑን የማይረዱ ግን ከማያውቁት የካፒታሊስ ስርዓተ ማህበር ፍቅር ያያዛቸውና ማርክሲዝም የሰፈር ፖለቲካ ብቻ የሚመስላቸው (philosophical & scientific views) እንዳለው የማይረዱ የፃፉት ስድብ ቀመስ መፅሐፍ ሊመስል ይችላል ። ግን መፀሐፉን በውጩ ብቻ ( Judging the book by its cover) ያዩና ገብተው የሚያነቡ የተለየ መረዳት ይኖራቸዋል ።
ሁለተኛው ደቃቅ ጽሁፎቹ ዓይናቸው ለደከመ ግለሰቦች የታሰበ እንዳልሆነ ይጠቁማል ። በነገራችን ላይ ይህንን መፀሐፍ ከልብ ልንወደው የምንችለው ግለሰቦች ብዙዎቻችን በአሁኑ ወቅት የዓይን ዕይታ ችግር ሊኖርብን ይችላል ። ስለዚህ ሁለተኛ እትም በሚታተምበት ጊዜ ሊታሰብበት የሚገባ ነው ።
መጽሐፉን የሚያነበው ግለሰብ የደራሲውን ዕድሜ መጠየቁ አይቀሬ ነው ። ለነገሩ ደራሲውን ሳያውቀው መጽሐፉን የሚያነብ ሰው ደራሲው ዕድሜው 63 ≥ ነው ብሎ ሊገምት ይችላል ። መጽሐፉን ልዩ የሚያደርገው ደራሲው ያልኖረበትን ዘመን ከኖሩበት በላይ አሳምሮ መተረኩ (መግለፁ) ነው ። እኔ በበኩሌ ይህንን የመሰለ በእንደዚህ ዓይነት የተፃፈ ድንቅ መጽሐፍ በአማርኛ ለማንበቤ መረጃ የለኝም ። እንዲያውም የስነጽሁፍ ሰዎች ከምን እንደሚመድቡት ለማወቅ እጓጓለሁ። በተለይ አዲስ አበባ ያለው 'አትራኖስ' የሚባል ድንቅ የስነ ፅሁፍ ቡድን አለ። ይህ ቡድን ይህንን መጽሐፍ ከደራሲው ጋር ውይይት አድርገው ለአድማጭ በሚስማማ መልኩ እንዲያቀረቡልን ማሳሰብ እወዳለሁ ።
ይህ መጽሐፍ 'ያ ትውልድ¹' ከሚባለው ጋር የሚያያይዘው ብዙ ጉዳይ ተካትቶበታል። በዚህ 'ያን ትውልድ'ን መስደብ ወይም ማንጓጠጥ አዋቂ በሚያስብልበት ጊዜ ይህንን ዓይነት ዘመኑን ከልብ የተረዳ መጽሐፍ መፃፍ የሚያስመሰግን ነው። ደራሲውን የምናውቀው ሰዎች በእሱ ዕድሜ ያልኖረበትን ዘመን እንዲህ ልቅም አርድጎ መረዳት እንዴት ቻለ? ብለን መጠየቃችን አይቀርም። እኛን መስሎ ፣ እኛን ተረድቶ ፣ እኛን ወቅሶ ፣ እኛን አሞግሶ ይህንን መጽሐፍ ለንባብ ማብቃቱ የደራሲውን ጥልቅ አዋቂነት አጉልቶ የሚያሳይ ነው። ምን አልባትም ግልብ የሆነ እንቶ ፈንቶ ትችት ላይ የራሳቸውን አዋቂነት ለመገንባት የሚጥሩ የደራሲውን ትውልድ የሚጋሩ 'ደራሲያን' ከዛ ወጥተው ወቀሳም ይሁን ሙገሳ በእንደዚህ ዓይነት ሲቀርብ ገንቢነት እንደሚኖረው ሊረዱ ይገባል።
መጽሐፉን ስንጀምረው እንደ መግቢያ የተጻፈውን ስንመለከት :-
"ይህ መፅሐፌ ለተካደው፣ ቅልጥም ላመለጠው ለዐይነ አፋሩ ትውልዴ መታሰቢያ ይሁንልኝ።" ይላል ደራሲው ። የደራሲው ትውልድ በያ ትውልድና ባሁኑ ትውልድ መካከል አለ የሚለው ነው። ቀጥሎም "እኔ - እንደ ዱብዕዳ ተከስቶ አገሬን ተጣብቷት የነበረው ( የተጣባትን ) (በቅንፍ የገባው አሁንም አለ ለማለት ይመስለል ) ያ የኮምዩኒዝም ርኩስ መንፈስ ተከትሎ የተፈጠረው የትውልድ ክፍተት ድምፁም አጥፍቶ የሞላው የዛ ጅግና ትውልድ አባል ነኝ።"
ይላል ገፅ 4 ላይ ።
በደራሲው "ጀግና ትውልድ" የተባለው እውን ጀግና ነው ወይስ የግል ጥቅምን አሳዳጅ ፣ ዐላማ ቢስ ፣ ለሱስ የተጋለጠ ነበር የሚለውን ለታሪክ እንተወውና በደፈናው ጀግና መባሉን ወደ ጎን አድርጌ ልለፈው ።
ከዚህ ተነስተን የደራሲው ዘመን ስንለካ እሱ 'ከኮምዩኒዝም ርኩስ መንፈስና ከዲጂታል አርበኞች' ከሚላቸው ማካከል ያለ ትውልድ አባል እንደሆነ ማወቅ ይቻላል ። ደራሲው በሁለቱ ትውልዶች መሐል የሚገኝ ምስኪን ትውልድ አባል ይሁን እንጂ ፣ ይህ የእሱ ትውልድ ሌሎች ትውልዶች የጫኑበትን መከራ ለመወጣት ምን እንዳደረገ ወደ ፊት ይጽፍልናል የሚል ሃሳብ አለኝ ጠ። ለእኔ ግን ይህ የእሱ 'ጀግና' የሚለው ትውልድ "የድጋፍ ወረቀት ጀሌ" ብዬ በብዙ ቦታ እጠቅሰዋለሁ። አለመስማማት መብታችሁ ነው። ለእኔ ግን በሕዝባዊ ድርጅቶች፣ በኪነት፣ በቀበሌ እና በመሳሰሉት ተሸሽጎ ራሱን ለመደበቅ ይጥር የነበረ ትውልድ ለመሆኑ ብዙ መረጃ አለ።
ወደ መጽሐፉ ስንገባ 106 ገፅ ላይ የሰፈረ ሲሆን በሰባት ንዑስ ርዕሶች የተካተተ ነው። ታሪኩ ተከታታይነው ይኑረው እንጂ በአንድ ግድግዳ ላይ ያጠነጠነ ነው ። ይህንን በሚመለከት :-
"ቀጥላችሁ የምታነቡት ይህ "የጠያይሞች መልአክ" ታሪክ አአንድ ግድግዳ ታሪክ ነው ሊባል ይችላል። " ይለናል ። እውነት ነው ታሪኩ አአንድ ግድግዳ ላይ ያጠነጠ ነው ። ግን ደግሞ ያ ግድግዳ የዘመንን ታሪክ በፅሁፍና በስዕል የያዘ ነው:: የዘመኑ ልጆች ምን ያህል ይወቁት አይወቁት አላውቅም እንጂ በእኛ ዘመን በአሮጌ ጋዜጣ የቤትን ግድግዳ ለጠፎ ማሳመር የተለመደ ነበር ። በተለይ ሰው ቤት እንግድነተ ከተሄደ በእየግድግዳው ላይ የተለጠፈውን ጋዜጣውን ማንበብ የተለመደ ነው ። አንዳንዴ ተከታዩ ገጽ ስለማይኖር አንደጓጉ መቅረትም ይመጣል።
ግድግዳ እንደምን ታሪክ ይሰራል ? ''ግድግዳህን አሳየኝና ማንነትህን ልንገርህ '' የነዚህ አባባሎች ምንነት ለመረዳት መጽሐፉን ማንበብ የሚያስፈልግ ነው። ይህ መጽሐፍ በስሜታዊነት የተጻፈ አይደለም፤ ከወገናዊነት አንጻር የተጻፈ ኣይደለም፤ ተጨባጭ (ኦብጄክቲቭ) በሆነ መንገድ ጥርት ባለ መልክ አንድን ትውልድ የሚገመግም ፣ የሚወቅስ፣ የሚያስተምርና የሚያመሰግን ነው ።
© Think Ethiopia | 1 726 |
| 7 | 没有文字... | 1 462 |
| 8 | «ታስፈሩኛላችሁ!! »
[ አስኮ ጌታሁን እና A Madman's Diary]
➊ "A Madman's Diary"
በታዋቂው ቻይናዊ ጸሐፊ Lu Xun የተጻፈው "A Madman's Diary" የተሰኘውን Short Story አንድ ወዳጄ ጋብዞኝ አነበብኩ። እውነትም ዩኒክ ነገር አለው። ፅሁፏ ስትታይ ቀድረ ቀላል ብትመስልም የምትጥለው ጥላ ግን ግዙፍ ነው።
በዙሪያው ያሉ ሰዎች... ጎረቤቶቹ፣ አልፎ ተርፎም የገዛ ወንድሙ ጭምር ሰው በላዎች እንደሆኑና እሱን ለመብላት እንደሚያሴሩ የሚያምን የአንድ ሰው ማስታወሻ ነው። ሐኪም ሊያየው እጁንና እና የልብ ትርታውን ሲዳስስ ምን ያህል እንደሰባና ሥጋው ለምግብነት እንደሚሆን እየፈተሸ የሚመስለው አይነት። የዚህ የእብድ ማስታወሻ የአእምሮ ሕመምተኛ ቅዠት ቢመስልም ከጀርባው ግን philosophical የሆነ ማኅበራዊ ሂስን ያዘለ ነው።
በታሪኩ መቅድም ላይ የዲያሪው አመጣጥ ይተረክበታል። አንድ ሰው፤ በሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እያለ በጣም የቅርብ ጓደኞቹ ወደነበሩ ሁለት ወንድማማቾች ዘንድ ይሄዳል። በቅርቡ አንደኛው በጣም ታሞ እንደነበር ወሬ ሰምቷል። እና ሊያያቸው ወደ ቤታቸው አቀና። ነገር ግን ያገኘው ታናሽ ወንድሙን ብቻ ነበር። እሱም ወንድሙ ከታመመ ቆይቶ አሁን ግን ሙሉ በሙሉ ድኖ ሥራ ፍለጋ ወደ ሌላ ከተማ እንደሄደ ይነግረውና "ወንድሜ አእምሮው በታመመበት ወቅት የጻፈውን ማስታወሻ ላንተ ለድሮ ጓደኛው ብሰጥህ ምንም አይደለም" ብሎ ያቀብለዋል።
ማስታወሻውን ሲያነበው የተዘበራረቁ፣ ትርጉም የሌላቸውና የተቆራረጡ ፅሁፎች ነበሩ። ብዙ የቅዠትና የጭንቀት ንግግሮች ታጭቆበታል። የማስታወሻወቹ ዋና ነጥብ ግን ሰዎች ሊበሉት እንደሚፈልጉ ማመኑ ነበር።
ሂዶ ሂዶ ማስታወሻው ድንገት ሲቋረጥ ሰውዬው መጨረሻ ላይ ምን እንደደረሰበት ግልጽ ሳያደርግ ጥርጣሬ ላይ ይተወናል። የመፅሐፉ መቅድም ላይ እብድ የተባለው ሰውዬ ድኖ ሥራ ፍለጋ ወደ ሌላ ከተማ መሄዱ ይነገረናል። ነገር ግን ሰውዬው የዳነው እንዴት ነው? የሚል ጥያቄ ደሞ ማንሳታችን አይቀርም።
ዳነ ማለት ወደ ፈራው ማኅበረሰብ ተመለሰ? እሱም እንደ ሌሎቹ ሰው በላ ሆነ ማለት ነው? ወይንስ ማኅበረሰቡ አስገዳጅ በሆነ መንገድ ዝም አሰኘው? ይህ ደራሲው ለአንባቢው የተወው ጥያቄ ይመስለኛል።
መፅሐፉን በደንብ ከመረመርነው እብድ የተባለው ሰውዬ ብቻ ነው በዚያ በበሰበሰና በተበላሸ ሥርዓት ውስጥ ብቸኛው ጤነኛ እና ሀቁን የተረዳ ሰው ሆኖ የሚገኘው። ማኅበረሰቡ ሰውዬውን ጨልሏል ይለዋል። እሱ ግን በዙሪያው ያሉ ሰዎች ሁሉ ሰብአዊነት የጎደለውና አንዱ ሌላውን የሚበላበት ሥርዓት ውስጥ መኖሩን የተረዳ ብቸኛው ሰው ነበር።
የማስታወሻው ማብቂያ ላይ «ይህንን ሥርዓት መቀየር አለብን። ሰውን መብላት ማቆም አለብን! ሰውን የማይበላ አዲስ ማኅበረሰብ መፍጠር ይቻላል። ልጆቹን አድኑ...» ይላል እብዱ ሰው። ይህች የመጨረሻዋ ተማጽኖ የተቀላቀለባት ዓረፍተ ነገር ማስታወሻው ብቻ ሳይሆን ሙሉው አጭር ልብ-ወለድ የሚደመደምበት መስመር ናት።
❷ «አስኮ ጌታሁን»
ይህንን Lu Xun ታሪክ ሳነብ ትዝ ያለኝ የጃርሶ ሞትባይኖር ኪሩቤል "አስኮ ጌታሁን" አጭር ልብወለድ ነው። ሀሳባቸው ከሞላ ጎደል ተመሳሳይ ነው።
◉ ጌታሁን ፍቅረየሱስ (አስኮ ጌታሁን) ጎበዝ መምህር ነበር። ግን ደፍረው ሀቅ ሀቋን የሚናገሩ መምህር ስለሆኑ ከብዙ ሰው ጋር መቀያየማቸው አልቀረም። የመምህርነት ሙያ ምግባረ ቀና እና የተማሩና የተገነዘቡ ሰዎችን ማፍራት እንጂ ለደመወዝ ማግኛ ብቻ የሚፈፀም የግብር ይውጣ መሆን እንደሌለበት የሚያምን ነበር። እንዲህ ማሰባቸው ባላንጣ ከማፍራት አልከለላቸውም።
ትምህርት ቤት አይፈርስም ስላለ በሹመኞች ቂም ተቋጥሮበታል። በራስ አነሳሽነት የጀመሩት በየገጠሩ በመሄድ ተማሪዎችን ፊደል ማስቆጠራቸው ከሀገሬው ምስጋና አትርፎላቸው፤ ከሹማምንት ወታደር የመሳሪያ ሰደፍ አሸልሟቸዋል።
ሚስቱን የዘመድ ባላንጣዎች መርዝ አብልተው የገደሉበት ሰው ነው። በሴራ 18 ዓመት ታስሮ ወጥቷል። በደረሰበት መከራና ጭንቅላቱ ላይ በደረሰ ጉዳት ያ አስፈሪው "አስኮ ጌታሁን" ይወለዳል።
አስኮ እየጮኸ ሁሌ የሚናገራት አንዲት ቃል አለች..
«ታስፈሩኛላችሁ!! »
◉ ይህች "ታስፈሩኛላችሁ" የምትለው ቃል የሁለቱንም ታሪኮች ማዕከላዊ ስሜት ትገልጻለች። ንጹሕና ሀቀኛ ሰው በክፉዎች፣ በሴረኞችና በሰው በላዎች በተከበበ ማኅበረሰብ ውስጥ ሲኖር የሚሰማው የመጨረሻው የስሜት ጥግ ፍርሃት ነው።
«ታስፈሩኛላችሁ!» ወይም «ሊበሉኝ ነው!» የሚለው ፍርሃት የአእምሮ ሕመም ሳይሆን የአንድን ማኅበረሰብ መበስበስ የተረዳ ንቁ ሕሊና ያለው ሰው የሚያሰማው ዋስትና የማጣት ጩኸት ነው።
የዛሬዋ ዓለም በካፒታሊዝም፣ በፖለቲካዊ ሽኩቻና በራስ ወዳድነት የምትመራ ናት። ጠንካራው ደካማውን የሚበላበት፣ ባለሥልጣኑ ተራውን ሕዝብ የሚጨቁንበት፣ ትልልቅ አገራት ትናንሾቹን የሚያጠፉበት ሥርዓት ነው። Lu Xun እና ጃርሶ ሞትባይኖር ሊነግሩን የፈለጉት ዓለማችን በሕግ ትገዛለች ቢባልም፤ በሥልጣኔ ብትስፈነጠርም፣ በቴክኖሎጂ ብትራቀቅም፤ በሞራልና በሰብአዊነት ግን ወደ አውሬነት እየወረደች መሆኑን ነው።
በሁለቱም ታሪኮች ውስጥ እብደት የተባለው ነገር ከግለሰቦቹ የአእምሮ መታወክ የመጣ ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡና ሥርዓቱ እውነቱን የተናገሩትንና ከጭፍን ልማድ የወጡትን ንጹሐን ሰዎች የሚቀጡበትና ስም የሚሰጡበት መንገድ መሆኑን ነው።
◉ "A Madman's Diary" ውስጥ ታሪኩ የሚደመደመው "ልጆቹን አድኑ..." በሚል የልመና ጥሪ ነው። ተስፋው ገና ባልተበከሉ ሕፃናት ላይ ነው።
በ"አስኮ ጌታሁን" ውስጥም መምህር ጌታሁን ሕይወታቸውን ሙሉ የደከሙት ለታዳጊ ትውልድ ነበር።
ሁለቱም ገጸ-ባህሪያት ለአዲሱ ትውልድ ትልቅ ስፍራ አላቸው። ለዛ ነው ልጆቻችሁን አድኑ ብለው የሚለፍፉት።
እና እኔ ምን እያልኳችሁ ነው?
"ታስፈሩኛላችሁ!"
▭▭
© Mes Oud | 2 222 |
| 9 | 没有文字... | 1 767 |
| 10 | ሰለሞን ደሬሳ ይሄን ሲያይ ነው “በአያትህ በር ማን እንዳለፈ አታውቅም” ያለው። እንዲህ አይነት ደስ የሚያሰኝ ታሪክ ነበረን። ይሄን ሁነት ደራሲው እንዲህ ይገልጸዋል።
“በዚህ አይነት ከተለያዩ አካባቢዎች ተጉዘው በበጌምድር በሰፈሩት የኢትዮጵያ ልዩ ልዩ ብሄረሰብ አባላት ሳቢያ፣ የጎንደርና የምዕራብ ወሎ ሕዝብ ምን ያህል እንደተቀላቀለና በልጅ ልጆቹም እንደተዋለደ መረዳት ይቻላል። ሰፈራው በአገራችን ታሪክ ከጥንት ጀምሮ ከተከናወኑ ማህበራዊ ሰፈራዎች አንዱና በልማት ሳቢያ ‘በወዶ ፈቃድ’ እንደተከናወኑ ከሚነገርላቸው አንዱ ነው። ዛሬ ‘ጎንደር ቤቴ፣ ርስቴና ጉልቴ’ እያለ በጎንደሬነቱ የሚኮራው ብዙ የአካባቢው ህዝብ ደሙ ከምዕራብ፣ ከደቡብ፣ ከምስራቅና ከማዕከላዊ ኢትዮጵያ ልዩ ልዩ አካባቢ ነዋሪዎች የተቀዳመሆኑን ያስገነዝበናል”። ይላል።
እና ሰው ሀረግ ነው። እኛ አሁን ከምናስበውና ከምናውቀው በተለየ መልኩ እንዲህ እርስ በእርስ የተዳቀልን ህዝቦች ነን።
ምናልባት ይሄን አይነቱን ታሪካችንን ስለማናውቀው ነው ወይስ ሆነ ብለን ስለምንክደው እንዲህ እርስ በእርስ የምንናከሰው እያልሁ መብሰልሰሌን ተያያዝሁት።
ንጉሱ ባቡር እየገነቡ፣ የተጎዳ አካባቢንም እንዲህ እያለሙ፣ በዓለም ፊትም ግርማቸውን እንደለበሱ ሞት አይቀሬው ወሰዳቸው። ይሄው እኛም አለን። ባቡሩ አዲስ አበባ ከደረሰ በኋላ እስከ ጅማ የማድረስ ሃሳብ ነበራቸው። ከቪክቶሪያ ሃይቅ ጋር አገናኝተው በመርከብ ንግድ ላይም የመሳተፍ ትልቅ ህልም ነበራቸው።
ግን ይሄው መቶ ዓመታት አለፉ። ባቡሩ ጅማ ደረሰን? ሁሌም ትውልድን የሚያናጋ ጥያቄ ነው።
የታሪክ ሰዎቻችንም ሆኑ ፖለቲከኞቻችን ምናለ እንዲህ አይነቱን ቢነግሩን?
ይሄ መጽሐፍ ሌሎች እልፍ ቁም ነገሮች አሉት። አንዷን ጉዳይ ብቻ እየመዘዙ ካልተወያዩበት ጠቅልሎ እንዲህ ለማለት ያስቸግራል። የታጨቁ ሁነቶችና ታሪኮች የሞሉት ነውና።
ታነብቡት ዘንድ ግን በደስታ እጋብዛችኋለሁ።
ደራሲ ንጉሴ አየለ ተካ ሆይ እጅግ እናመሰግናለን።
ለብርታትህም ኮፍያችንን አውልቀን ክብርችንን እንገልጻለን። ቀሪዎቹንም ታደርስልናለህ ብለን ተስፋ እንደርጋለን።
ሰናይ ንባብ።
Reviewer : © ውብአረገ አድምጥ
© Think Ethiopia | 1 828 |
| 11 | ጎንደር ቤቴ፣ ርስቴና ጉልቴ - ከኦዛና ምኒልክ
ታላቁ ክብር
ኢትዮ አትላንቲክ ዘዳግማዊ ምኒልክ ወ ልጅ እያሱ!
(ተጻፈ ከንጉሴ አየለ ተካ!)
ይሄንን መጽሐፍ እንደወጣ ተስገብግቤ ነው የገዛሁት። ምክንያቱም ደራሲው ንጉሴ አየለ ከዚህ በፊት ‘ታላቁ ጥቁር’ በሚለው መጽሐፉ ያስነበበን ታሪክ አጃይብ የሚያስብል ነበርና ነው።
እናም ቶሎ ገዛሁት። አነበብሁትም። ተደነቅሁም።
ታሪኩ የሚያጠነጥነው የእኛ ታሪክ በተለይ የአድዋን ድል ተከትሎ በአሜሪካና በካረቢያን ምን ይመስል ነበር?
ንጉሶቻችን ምን አይነት ቦታ ነበራቸው? የአሜሪካ ጋዜጦች ስለእኛ ምን ይሉ ነበር? እኛስ እንደ ሀገር ምን አይነት ቦታ ነበረን የሚሉና ተመሳሳይ ታሪኮችን የሚያነሳ ነው። በአስራ አምስት ምዕራፎች የተከፋፈለው መጽሐፍ ስለ አስራ አምስት የተለያዩ ጉዳዮች በጥልቀት የሚያስስ ነው።
ጸሐፊው ስለ አንድ ጉዳይ ያነሳና ጭብጡን እየተከተለ ሰምተነው የማናውቀውን ታሪክ ከባህር ማዶ መዛግብቶችና ከዘመኑ የጋዜጣ እትሞች ላይ እያጣቀሰ አጃይብ ያስብለናል።
ጽሑፎቹ ከእነ ማስረጃቸው ባይሆኑ ኖሮ በተለይ በዚህ ዘመን ለመካድ የሚያስመኙ የሚመስሉ ብዙ ታሪኮች ተካተውበታል።
አሁን በሞቴ አንድ ወቅት ወደ ኢትዮጵያ ለሰርግ ሽርሽር (ሃኒሙን) ታላላቅ ሰዎች ይጎርፉ ነበር ቢባል ማን ያምናል?
አጤ ምኒልክ በሜዳ አህያ ብቻ አጠቃላይ የዲፕሎማሲ ስራቸውን ይሰሩ ነበር ቢባል ማን ያምናል?
እንዲያው በሞቴ አቢሲኒያ የሚሰኝ ቴአትር ይታይ ነበር። የእነ ሳባ ታሪክ ሰርክ መማሪያ፣ የእነ ጣይቱ ስም ለሴቶች መታገያ ነበር ቢባልስ ማን ያምናል?
ሀጂ አብደላሂ አሊ ሳዲቅ የተባሉ የምኒልክ መልዕክተኛ በአሜሪካ ያገኙት አቀባበልና በኋይት ሃውስ የተደረገላቸውን ግብዣ ቢሰማ ማን በጄ ይላል?
ስለ ኢትዮጵያ ኮከብና ስለ ባንዲራችን። ስለ ጥቁሮች ትግልማ ምኑ ይወራል።
እንዲያው ደራሲው በታላቁ ጥቁር እንደነገረን አሜሪካ ከኢትዮጵያ ጋር የንግድ ውል ስትዋዋል የስምምነቱ አይነት እጅግ ከተወደዱና ከተመረጡ ሀገራት ጋር የሚደረግ “with great favored nation” እንደነበር ብናውቅ እውን ቁጭት ያድርብን ይሆን?
ብቻ አሁን ካለንበት ምስቅልቅል ጋር አገናኝታችሁ በፍፁም አይደረግም እንዳትሉ። ሆኗል። ነበርም።
ብዙ ብዙ ማለት ያስችል ነበር። ግና አንብባችሁ ፍረዱኝ ብዬ ወደ ጉዳዬ ልግባ
እንደሚታወቀው በሀገራችን ባቡር ያስገቡት ዳግማዊ ምኒልክ ናቸው። ይሄን ባቡር ወደ ሀገራችን ለማስገባት በሞከሩት ወቅት ታላላቅ የአውሮፓ ሀገራት በተለይ እነ እንግሊዝ ጣሊያን የከፋ ጫና እያደረጉብን ነበር። የባቡሩን ግንባታም ለማሰናከል እየጣሩ ነበር።
ዳግማዊ ምኒልክ ከእያንዳንዱ ግለሰብ በጭራ ገንዘብ ሰብስበው፣ የዓለምን ዲፕሎማሲም በደንብ ተጫውተው ባቡሩን አስቀጠሉት። ከመናገሻቸው ደርሶ የደከሙለትን ባቡር ፍጻሜውን ሳያዩት ቢያልፉም ህልማቸው ግን እውን ሆኗል። ለካ እያንዳንዱ ህዝብ አዋጥቶ የገነባው አባይን ብቻ አይደለም። ለመጀመሪያ ጊዜ ባቡሩንም በዚያ መልኩ ነው የገነባነው።
አስራ አምስት ከብት ያለው አንዱን ለሀገሩ እያዋጣ ነው ባቡር የገነባው። እንዲያውም አንዳንዶቹ የከብት ቁጥራቸውን እየቀነሱ አስቸገሩ። ከሁሉም ግን ዘመቻውን ተቃውመው ወደ ጎረቤት ሀገር ማለትም ወደ እንግሊዝና ፈረንሳይ ቅኝ ግዛት እንዳይሄዱ መኖሪያቸውን ቋሚ አድርገው ሃብት እስኪያፈሩ ድረስ የሁለት ዓመት የግብር እፎይታ እንዲሰጣቸው አጼ ምኒልክ የጻፉት ደብዳቤ እንዲህ ይላል።
(ደብዳቤ 1243
ይድረስ ከሼህ ሆጀሌ
የዘመቻው ጊዜ እየሸሸ ወደ እንግሊዝ አገር የገባው ሰው ሁሉ የሁለት ቀን መጥቶ ተቀበለኝ ብለህ የላክኸውን ደብዳቤ አይቼ ደስ አለኝ። አሁንም የቀረውን ያንተን ሰው ሁሉ በዝግታ እንዲገባ ማድረግ ነው። ደግሞም አገሩ እንዲለማ ለአንድ ዓመትና ሁለት ዓመት ግብሩን አንነካውም።
የመጋቢት 3 ቀን 1900 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ተጻፈ
(ምንጭ፣ አጤ ምኒልክ በሀገር ውስጥ የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች። በጳውሎስ ኞኞ ገጽ 322))
በዚህ መልኩ በሀገሬው ብርታት በንጉሱም አስተዳደር ባቡሩ እውን ሆነ።
ቀልቤን የሳበው ግን ሌላም ነገር አለ። ከዚህ በፊት ታሪክ ላይ ማንበቤን አላስታውስም። ይሄን ክስተት ጸሐፊው ንጉሴ አየለ ተካ በዚህ መጽሐፉ እኝዲህ ይገልጸዋል።
“በዚህ ወቅት ያጋጠመ አንድ አስገራሚ ክስተትም ነበር። በወቅቱ በጌምድር ተብሎ በሚጠራው የጎንደር አካባቢና የሰሜን አውራጃዎች ከብቶች በድርቅና በበሽታ አልቀው ስለነበር ንጉሱ ከዚያ አካባቢ የተሰደደው ህዝብ እንዲመለስና እንዲቋቋም በማረሻ ከብቶች እጥረት ሳይታረስ ጦም ያደረው መሬት እንዲለማ ተጨማሪ ዘመቻ ያስፈጽሙ ነበር።” ይላል።
(ኦዛና ምኒልክ ገጽ 164)
ይሄም ከሌላ አካባቢ ሰዎችን እየወሰዱ በጌምድር ማስፈር ነው። ለዚህም አስረጂ ይሆኑ ዘንድ በወቅቱ ንጉሱ የጻፏቸውን ደብዳቤዎች እንጠቅሳለን።
(ደብዳቤ 1186
ይድረስ ከሼህ ሆጀሌ አሊ ሐሰን
በጌምድር የሚባለው አገር ከብድ ካለቀ ወዲህ ሳይታረስ ቀርቶ ጠፍ ሆኗል። አሁንም ከብትም ገበሬም ሰድጄ በጌምድርን አቀናለሁ ብያለሁና አንተም ገበሬ የሚሆኑ (የቤንሻንጉል) ሰዎች ከነሚስቶቻቸው ከዘመድህም ከወዳጅህም ፈልገህ እንድትሰድልኝ ይሁን። ቁጥሩን ግን እኔ ይህን ያህል አልልህም። የተገኘልህን ያህል ስደድልኝ።
የካቲት 22 ቀን 1900 ዓ.ም አዲስ አበባ ከተማ ተጻፈ ።
(ምንጭ፣ አጤ ምኒልክ በሀገር ውስጥ የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች። በጳውሎስ ኞኞ ገጽ 322))
ሌላ አንድ እንጨምር. . .
(ደብዳቤ 1187
ይድረስ ከራስ ወልደ ጊዮርጊስ
በጌምድርስ ከብት ካለቀ ወዲህ ሳይታረስ ቀርቶ ጠፍ ሆኗል። አሁንም ከብትም ገበሬም ሰድጄ በጌምድርን አቀናለሁ ብያለሁና አንተም ገበሬ የሚሆኑ መቶ ወንድ (የኦሮሞ ሰዎችህን) ከነሚስቶቻቸው ከዘመድህም ከወዳጅህም ፈልገህ እንድትሰድልኝ ይሁን። ይህንንም መቶ እስቲሞላ አትጠብቅ። የተገኘ የተገኘልህን ቶሎ ቶሎ ስደድልኝ።
የካቲት 22 ቀን 1900 ዓ.ም አዲስ አበባ ተጻፈ ።
*በዚሁ ቃል ለራስ ተሰማ፣ ለደጃዝማች ጆቴ፣ ለደጃዝማች ገብረ እግዚአብሔር፣ ለደጃዝማች ደምሰው፣ ለአባ ጅፋር፣ ለደጃዝማች ለማ፣ ለደጃዝማች ገብሩ፣ ለአዛዥ ባደግ ተጽፏል።
(ምንጭ፣ አጤ ምኒልክ በሀገር ውስጥ የተጻጻፏቸው ደብዳቤዎች። በጳውሎስ ኞኞ ገጽ 323))
እነዚህ ፈቃዳቸውን የሰጡ ሰዎች ቋሚ ህይወት መስርተው እንዲኖሩ ባልና ሚስት መሆን ይገባቸው ነበር። እንዲያውም ከድሃው ህዝብ የሚሄድ ቢጠፋ የሹማምንቱ ዘመዶች እምቢ እንደማይሉ ንጉሱ የተረዱ ይመስላሉ። ከደቡብ፣ ከምዕራብ፣ ከምስራቅና ከመካከለኛው የሀገራችን ክፍል እየተመለመሉ ወደ ንጉሱ ይቀርባሉ። ንጉሱም ጥማድ በሬና ቀለብ ሰጥተው፣ ግብር አብልተው ወደ በጌምድር ይልኳቸዋል።
እነዚህ ሰዎች በንጉሱ ትዕዛዝ ሰፍረው፣ ህይወታቸውን መስርተው የልጅ ልጆቻቸውን ተክተው አልፈዋል። ይህ ከመቶ ዓመት በፊት የሆነ ታሪክ ነው።
ዛሬ እነ ጥርት ያልሁ ጎንደሬ ነኝ!
እኔ ጽድት ያልሁ ጎጃሜ ነኝ።!
እኔ ሽቅርቅር ወሎዬ፣ እኔ ምርጥ ትግራዋይ!
እኔ ጥርት ያልሁ ኦሮሞ ነኝ!
እኔ የበቃሁ የነቃሁ እንዲህ ነኝ እያልን ስንፎክር እገረማለሁ። እንኳን የጥንቶቹን ይቅርና ይሄን በመቶ ዓመት ውስጥ እንዲህ ያለ ታሪክ አለን። | 1 798 |
| 12 | 没有文字... | 1 378 |
| 13 | ◉ አትፍረድ !
➊
ይህ «Aattam» (The Play) የተሰኘው የMalayalam ፊልም በተለየ መልኩ እወደዋለሁ። ከራሴ ጋር እንዳወራ አድርጎኛል። ታሪኩ የሚያተኩረው Arangu በተሰኘ የአንድ የቲያትር ቡድን አባላት ዙሪያ ነው። በዚሁ የቲያትር ቡድን ውስጥ ብቸኛ ሴት ተዋናይ አለች። እና ይቺ ሴት ከአንድ ትርኢት በኋላ በተዘጋጀ የምሽት ግብዣ ላይ በቡድኑ ውስጥ ካሉ ወንዶች በአንዱ የጾታ ትንኮሳ ጥቃት ይደርስባታል።
ድርጊቱ ይፋ ከወጣ በኋላ በቡድኑ ውስጥ ያሉትን 11 ወንዶች ያካተተ አስቸኳይ ስብሰባ ይጠራል። ታሪኩ ሙሉ በሙሉ የሚያተኩረው እነዚህ ወንዶች ጥቃቱን በሰሙበት ወቅት በሚያሳዩት የተለያየ ባህሪና በሚያደርጉት ሙግት ዙሪያ ነው። ወንዶቹ መጀመሪያ ላይ ለሴቷ ሙሉ ድጋፍና አጋርነት ያሳዩ ቢመስሉም፣ ቀስ በቀስ የራሳቸው የግል ጥቅም፣ ዝና እና የሚያገኟቸው የገንዘብ እድሎች ጥያቄ ውስጥ ሲገቡ አቋማቸውን መለዋወጥ እና ጥቃቱን ማሳነስ ይጀምራሉ።
❷
ይህን ፊልም ካየሁ በኋላ በቀጥታ ታዋቂው የሆሊውድ ክላሲክ ፊልም "12 Angry Men" ነው ትዝ ያለኝ። በቅርፅም ሆነ በይዘት እጅግ በጣም የሚቀራረቡ ናቸው። በ12 Angry Men ውስጥ 12 የዳኞች ማህበር አባላት የአንድን ልጅ እጣ ፈንታ ለመወሰን እንደሚከራከሩት ሁሉ፣ በAattam ውስጥም 11 የቡድኑ ወንዶች በአንዲት ሴት ላይ በደረሰው ጥቃት ዙሪያ ይከራከራሉ።
በሁለቱም ፊልሞች መጀመሪያ ላይ ሁሉም ሰው በአንድ ወገን የተሰለፈ ቢመስልም፣ ውይይቱና ክርክሩ እየጠነከረ ሲሄድ ግን የሰዎች አቋም እንደ ፍላጎታቸውና ጥቅማቸው ሲዋዥቅና ሲቀያየር ይታያል።
❸
Aattam የ12 Angry Menን መዋቅር ቢወስድም የስነ-ልቦና ብርበራውን ከፍ ወዳለ ደረጃ ያሳድገዋል። ወንዶቹ ለሴቷ የቆሙ መስለው፣ በመጨረሻ ግን የራሳቸውን ጥቅም ለማስከበር ሲሉ ተጎጂዋን ዳግመኛ እንዴት እንደሚበድሏት እናያለን።
ፊልሙ ሲያልቅ ፍርዱን በቀጥታ ለተመልካች በመተው ነው። ፊልሙ መጨረሻ ላይ "ተጠርጣሪው ጥቃቱን በእርግጥ ፈጽሟል ወይስ አልፈጸመም? ወንዶቹስ ምን ሆኑ?" የሚለውን ፍርድ ቤት ወይም ፖሊስ ዘንድ አድርሶ በቁጥጥር ስር ሲውሉ አያሳየንም። ዳይሬክተሩ ይህንን ያደረገበት ምክንያት ፊልሙ ትኩረት እንዲሰጠው የፈለገው በአንድ ወንጀለኛ ላይ ብቻ ሳይሆን ጠቅላላው ማህበረሰቡ ራሱን እንዲፈትሽና እንዲመለከት ስለፈለገ ይመስለኛል ።
● ፊልሙ ለእኛ የተወልን ጥያቄ ሲመስለኝ ይሄ ነው...
"አንድ በደል ሲፈጸም፣ ለተበዳዩ የምንቆመው እውነትንና ፍትህን ፈልገን ነው ወይስ የራሳቸውን ጥቅም እስካልነካ ድረስ ብቻ?"
የፊልሙ ደራሲ ወይንም አዘጋጅ በታሪኩም ጭምር መፍረድ የፈሩት ክብደቱን ስለተረዱ ይሆናል።
❹
ያው የሰው ልጅ ፍፁም ነፃ (እንደ ነጭ ወረቀት) ሆኖ አይፈርድም። እያንዳንዱ የሚያሳልፈው ውሳኔ፣ ፍረጃ ወይም አቋም ከውስጣችን ማንነት፣ ከኖርንበት ህይወት፣ ካለን ፍርሃትና ከግል ጥቅማችን የሚቀዳ ነው። ለዚህ ነው በህግና በፍትህ ሥርዓት ውስጥ Objective Truth ላይ መድረስ እጅግ ከባድ የሚሆነው። አንድ ዳኛ ፍፁም ፍትሃዊ ለመሆን መጀመሪያ የራሱን ውስጣዊ ጭፍን ጥላቻ፣ ፍላጎትና ስሜት ድል ማድረግ አለበት። ይሄ ደሞ ሲሲፈስ ከዛ አለት ጋር እንደሚታገለው ትግል ሆነ ማለት ነው። ከሰው ልጅ ተፈጥሮ ጋር መታገል ማለት ስለሆነ አስቸጋሪ ነው።
● ከ 12 Angry Men ምሳሌ እንስረቅ
◉ ፊልሙ መገባደጃ ላይ 11ዱም ዳኞች ማስረጃዎቹን አንድ በአንድ እየመረመሩ ሲመጡ "ልጁ ጥፋተኛ አይደለም " ወደሚለው አቋም ይሻገራሉ። መጨረሻ ላይ የቀረው ብቸኛው ሰው ዳኛ ቁጥር 3 ይሆናል። "Not Guilty" ለማለት ያንቀዋል። ልጁ እንዲሰቀል ነበር የፈለገው።
እስከመጨረሻው ሰከንድ ድረስ በንዴትና በእልህ ልጁ ጥፋተኛ ነው እያለ ይሞግታል። ነገር ግን መጨረሻ ላይ በንዴት ውስጥ ሆኖ የራሱን ልጅ ፎቶግራፍ ከኪሱ አውጥቶ ሲቀደው ሽሽግ ምስጢሩ ይገለጣል። ዳኛው ልጁን ሊቀጣ የፈለገው ከራሱ ልጅ ጋር ባለው የግል ጠብና ቂም ምክንያት እንደነበረ ይረዳል። በራሱ ስሜት ተሸንፎ ስቅስቅ ብሎ ካለቀሰ በኋላ "ጥፋተኛ አይደለም!" ብሎ ድምፁን ይሰጣል። በዚህም 12ቱም ዳኞች በአንድ ድምፅ ልጁን ነፃ ያደርጉታል።
❺
“አትፍረድ ይፈረድብሃል!” የሚለው አባባል በትክክልም የሰው ልጅን ጉድለትና የስነ-ልቦና ሀቅ የሚፈትሽ መርህ ነው። በአንድ ሰው ላይ የምንሰነዝራት ፍርድ ወይም የምንወረውራት ትችት ስለ ተከሳሹ ሳይሆን ስለ እኛ ውስጣዊ ማንነት የሚናገረው ነገር ይበልጣል። በ12 Angry Men ላይ ያለው ዳኛ በተከሳሹ ልጅ ላይ በጭካኔ ሲፈርድ የነበረው በራሱ ህይወት ውስጥ ካለው ቁስልና ቂም የተነሳ እንደነበረው።
መፍረድ ከባድ ነገር ነው። ምክንያቱም እውነተኛ ፈራጅ ለመሆን መጀመሪያ ከራስ ጥቅም፣ ከራስ ስሜት፣ ከራስ ታሪክና ጥላቻ ነፃ መሆንን ይጠይቃል። አለዚያ አንዷን ጣት ስትቀስር አራቱ ወደ ራስ ያመለክታል እንደሚባለው ይሆናል።
ባጭሩ ሁለቱም ፊልሞች የሚያሳዩን በሸንጎ ስለሚቆሙት ተከሳሾች ሳይሆን፣ በፈራጆቹ ወንበር ላይ ተቀምጠን ስለምንፈርደው ስለ እኛ ማንነት ነው።
▭▭
© Mes Oud | 2 808 |
| 14 | 没有文字... | 2 167 |
| 15 | የሆነው ሁሉ ሁኖ መጨረሻ ላይ ሕሊና አዕምሮን ፈልጋ ስትሔድ በሩን ዘግተው ሊያስቆሟት የሚሞክሩት እኒያው ደባል ሱሶቹ ነበሩ። የዚያኔ ግን ድክመቷን ብቻ ሳይሆን ድክመቶቹንም ጠንቅቃ ስለተረዳች ማናቸውም ሊያስቆሟት አልቻሉም።
የወይን አበባዬ 📯 የወይን 🎶
© Mickael Azmeraw | 2 573 |
| 16 | የወንዶች ጉዳይን ከሳቅ በዘለለ መረዳት የሚፈልግ አንድም ጤነኛ ሰው ያለ አይመስለኝም። እኔ ግን ጤና ስለሚጎለኝ የወደድኩትን ነገር እስክጠላው ድረስ መጎርጎሬን አላቆምም።
የመጀመሪያው ጥያቄዬ "ደራሲው የዋና ገፀባሕሪዎቹን ስም አዕምሮ እና ሕሊና ያለው ባጋጣሚ ነው?" የሚለው ነበር።
በርግጥ ይሕ ጥያቄ ብቻውን ወደ ሌላ አለም ይወስደኛል ብዬ አላሰብኩትም። ምክኒያቱም ሌሎች ደራሲዎች እንዲህ አይነት ነገር የሚያደርጉት ከላይ ሲታይ ደስ ስላላቸው ብቻ ነው የሚሆነው። አድማሱ ግን የደበቀውን ታሪክ እንድናገኝበት ያስቀመጠልን ካርታ ነበር።
ፊትለፊታችን ሁኖ የተሰወረው ስቶሪ ባጭሩ ይሕ ነው።
አዕምሮ ውስጣዊ ሰላም ለማግኘት ሲል ሕሊናውን እየዋሻት ነው። እንዲዋሻት የሚተባበሩት ደግሞ ስድስት ደባል ሱሶች አሉበት😃
ላይሆን ይችላል...ይሕ ቲዎሪ ብቻ ነው። እስከሚያስኬደን ድረስ እንሒድበት🙂
ወዳጆቹ...እስከጥግ የሚገዙለት አንድ ነገር አላቸው።
አንደኛው ያገኘውን የሚያገበሰብስ ሆዳም ነው።
አንደኛው አላፊ አግዳሚውን የሚያስረግዝ ዘማዊ ነው።
አንደኛው ሰርግ ቤት ሳይቀር ከመለኮስ የማይመለስ አጫሽ ነው።
አንደኛው ከሰከንድ በፊት ያገኛትን ሴት ቂጧን ካልጨበጥኩ የሚል ሴሰኛ ነው።
አንደኛው እቁብ ሲወጣለት ልብስ ልግዛ ሶፋ ልቀይር ሳይሆን "ዛሬ ይጠጣል!" የሚል ጠጃም ነው።
አንዳቸውም በሰውነታቸው ላይ ሀይል የላቸውም። ህይወታቸው በሱሳቸው ዙሪያ ነው የሚያጠነጥነው። ሱሰኛ ብቻ ሳይሆን ሱስ ራሱ ናቸው። ግን አትጠሏቸውም። በጣም ነው የሚያዝናኑት። ሲጫወቱ ለምናያቸው ለኛ "ጓደኞቼ በሆኑ!" የሚያስብሉ ናቸው።
ያው ሱስ ሱስን ይወዳልና አንድ ላይ ሰብሰብ ብለው የመሰረቱት ማሕበርም አላቸው። የዚህ ማሕበር አስተባባሪ እና ዋና ፀሀፊ ቀጮ ነች። ቀጮ እንደሌሎቹ ሱስን አትወክልም። "ታዲያ ሱስ ካልሆነች ሱሶችን የምትሰበስባቸው እሷ ማነች?" ልትሉ ትችላላችሁ።
ቀጮ ማለት ሴት ሁና ሳለ ራሷን እንደ ሴት የማታይ ሰው ነች። "ሴቶች" እየተባለ ሲወራ እንኳን እኔን ይመለከተኛል ብላ አትሰማም። ለዛም ነው ወንዶች ሴቶች ላይ ለሚፈፅሙት ተንኮል ተባባሪ ሁና የምትገኘው። ያ ማለት ግን ሴቶችን ትንቃለች ማለት አይደለም። የምትንቀው ራሷን ነው።
አዕምሮን ስትመርቅ እንኳን "ቀጠን ያለችዋን፤ እንደ እንዝርት ተሽከርካሪዋን፤ እንደ ዳር ተወርዋሪዋን ያጋጥምህ!" ነው የምትለው። የሷ ምርጥ ሴት...እሷን የማትመስል ነች።
ስለዚህ የነዚህ ሱሶች ሰብሳቢ የወረደ በራስ መተማመን ያላት እና ከተቃራኒ ወገን ተሰልፋ የምትዋጋ ፍጡር መሆኗ ስሜት ይሰጣል። ሱሶችን የሚጠራቸው ይሔ አይነቱ ራስ ጠልነት ነው'ና! (ቀጮ Insecurity ነች እያልኩ ነው ምዕመናን😭)
አዕምሮም ወደነሱ የተሳበው በዚችው ጎኑ ነው። ማሕበራቸውን እንዲቀላቀል ያላደርጉት ጥረት አልነበረም። አንዱም አልሰራም። የሚወዳት ፍቅረኛው ከውጭ ለመጣ ሰው ጥላው መሔዷም ለሽንፈት አላበቃውም። ከዛ በፊትም ብዙ ሴት ጋ ተለያይቷል። ብርቁ አይደለም ፍቅሩን ማጣት። ለሽንፈት ያጋለጠው ከመሔዷ በፊት የጣለችበት ንግግር ነው።
"አንተን ብዬ መቼም ከምመኛት አሜሪካ መቅረት አልችልም!!!" 😃
ይሕ ንግግር ጥላቻም የለውም። ርሕራሔም የለውም። ምርር ያለ እውነት ብቻ ነው። ይሔንን እውነት ለመዋጥ አዕምሮን Pride ያንቀዋል። ያጥወለውለዋል። ስራ ትቶ መኝታ ላይ ይውላል።
የዚያኔ ማሕበርተኞቹ ደም እንዳሸተተ ሻርክ ተቀላቀለንና ከሀዘንህ እናድንህ እያሉ ይዞሩታል። የደረሰበትን ሽንፈት እምደሚያስረሱት ደጋግመው ቃል ይገቡለታል። መፍትሔው ያለው በነሱ እጅ እንደሆነ ጨቅጭቀው ያሳምኑታል
ልክ ሁነውም ይገኛሉ።
በአጭር ጊዜ ውስጥ ከወደቀበት ተነስቶ መሳቅ መጫወት ይጀምራል። ሕሊናውን ከመዋሸት ቢሆንም ደስታው የተገኘው ከነበረበት መጥፎ ስሜት አንፃር ይሔ አስር እጥፍ የሚሻል መንገድ ይሆንለታል።
"አሁንማ እንከባከብሀለን ቅድም እኮ ቅጥል ነው ስታደርገን የነበረው!" እያሉ የበለጠ ሰምጦ እንዲገባ ያበረታቱታል። ውሸቱ እንዲሰራ መንገዱን ያሳልጡለታል። ፅዋ ያነሱለታል። እጃቸውን ጭነው ይመርቁታል። ሁሉም ነገር አልጋ ባልጋ ይሆናል።
ችግሩ ይሔንን ስሜት ለማስቀጠል ሁሌም ጧት ተነስቶ አንድ አዲስ ውሸት መዋሸት አለበት። ዛሬ አለቃውን አታልሎ ከስራ የቀረ እንደሆነ ነገ ደግሞ የእህቱን ሽቶ ሰርቆ ቤቱን መበጥበጥ ይኖርበታል።
ደባል ሱሶቹ ለሚሰጡት ደስታ በምላሹ ከሱ የሚጠይቁት ሕሊናን እንዲተኛት፤ በውሸት አለም ውስጥ እንዲያባክናት...ባጭሩ Corrupt እንዲያደርጋት ነው። እንደመጀመሪያዎቹ ጊዜያትም ቶሎ ቶሎ አይስቁለትም። በሆነ ባልሆነው ነው የሚነጫነጩበት።
"ታዲያ አዕምሮ ይሔ ሁሉ ውሸት ውስጥ ሲዋኝ ሕሊና እንዴት መጠርጠር ይሳናታል?" የሚለው ሁለተኛው ጥያቄዬ ነበር።
እንግዲህ አዕምሮ የምናዬው የምንዳስሰው የማሰቢያ ማሽን ነው። ይሕን ማሽን የሚጠልፉትም የምናያቸው የምንዳስሳቸው አደንዛዥ ዕፆች ናቸው።
ሕሊና ግን የማናያት፤ 'ማንዳስሳት...አዕምሯችንን እየወቀሰች በትክክለኛው መንገድ እንዲሔድ የምታስገድደው ስውር አለቃችን ነች። ህሊናን ሱስ አያሸንፋትም። እሷን ሚጠልፋት እንደሷ ለማዬት ለመዳሰስ የሚከብደው ዲያቢሎስ አልያም እርኩስ መንፈስ ነው።
ሸዊት የምትጫወታት ገፀባህርይ (ማርታ) የምትወክለው ይቺን ከሕሊናችን ጆሮ ላይ የማትጠፋውን አንሾካሿኪ ድምፅ ነው🙂
ከመጀመሪያው ቀን ጀምሮ ለአዕምሮ ውሸቶች የምትማልለው እሷ ነች እንጂ ሕሊና አልነበረችም። በፍቅሩ ተይዛለች። "ሶፋ ብናስቀይረው፤ ወርቅ ብናስገዛው" እያለቻት ነው ጆሮዋ ላይ ቁማ። ሐሳቧን ውድቅ እንዳታደርግባት ደግሞ ለቤተሰባችን ስንል ነው እያለች ታግባባታለች።
ቤት የጋበዘችው ቀን ሶፋቸው መበላሸቱን ነግራ ልታስገዛው ስትሞክር አዕምሮ "እሰራዋለሁ!" ብሎ መዶሻ ነገር ፍለጋ ይገባል።
ማርቲ አመዷ ቡን ብሎ "ምንም ነገር የለንም...ጎረቤትም የላቸውም!" ስትለው ሕሊና ተነስታ ከጠረንጴዛው ስር የተቀመጠውን ዘነዘና ትሰጠዋለች። የአዕምሮ እውነተኛ ማንነነቶች ፈንቅለውት በሚወጡበት ቅፅበቶች ሁሉ ሕሊናን ይማርካታል። በተቃራኒው ማርታን ያቅለሸልሻታል።
ሁለቱ ያለ ሶስተኛ ወገን ብቻቸውን ሲገናኙ የሆነ ደስ የሚል ነገር አላቸው። አንዳቸው ላንዳቸው ነው የተፈጠሩት ያስብላሉ። መዋደዳቸውም ያስቀናል። ነገር ግን መሰረቱ ወሸት ላይ ነው'ና ሒሳቡ ሳይወራረድ ግኑኝነቱ ሊፀና አይችልም።
አዕምሮ መቼም መቼም መቼም ቢሆን ከገባበት ክብ መውጣት አይችልም። ከገባበት ክብ ልታወጣው የምትችለው ሕሊናው ብቻ ነች።
እሷ ደግሞ እሱን ማውጣት እንድትችል በቅድሚያ ጆሮዋ ላይ ያለችውን መንፈስ ጠንቅቃ መረዳት ይኖርባታል። መረዳት ብቻ ሳይሆን ንቃ መተው መቻልም አለባት። ያን ማድረግ እንድትችል መንፈሳዊ እገዛ ትፈልጋለች።
ለዛ ነው የቤተክርስቲያኑ ትዕይንት ትክክለኛ ቦታ ላይ ገብቷል የምለው።
አዕምሮ እንደልማዱ "ጌታዬ ውሸቴን የማስቀጥልበት ገንዘብ ስጠኝ!" አይነት ፀሎት ይፀልያል። እሷ ግን እውነቱን መኖር እንዲጀምሩ ነው የምትማፀነው። ጌታም የሕሊናን ልመና ሰምቶ የጠዬቀችውን ብርታት ይሰጣታል። ማርታ ያስጀመረቻትን ድራማ ትታ ሀቁን በማፍረጥረጥ አዕምሮን ከገባበት ስካር ታባንነዋለች።
ነፍሱ ስትያዝ ይናዘዛል። መክፈል ያለበትን የንስሀ ዋጋ ይከፍላል። እውነቱን ማውራት ሲጀምር እሷም እንዳዲስ እየወደደችው ትመጣለች። | 2 466 |
| 17 | 没有文字... | 1 822 |
| 18 | መብለጥ አያኩራራም፤ መበለጥ አያሳምምም!
(The Mind Under Comparison)
(እ,ብ,ይ.)
ሰው ሁሉ እኩል አይደለም፡፡ ሰው ከሰው የሚለያይበት ብዙ ነገር አለው፡፡ ተፈጥሮ አንድዓይነት ቢሆን ያሰለቻል፡፡ የስምንት ቢሊየን ህዝብ ፊት የተደጋገመ ቢሆን ኖሮ ሰውን ከሰው መለየት አዳጋች ይሆን ነበር፡፡ ፈጣሪ ይህቺን ዓለም የሰራት በልዩነት ጥበብ ነው፡፡ ልዩነት ለዘላለም ይኑርና መንታዎች እንኳን ከአንድ እንቁላል ተፈጥረው በሁሉም ነገር አንድ አይሆኑም፡፡ አምላክ የእናትን ሆድ ዥጉርጉር ያደረገው ልዩነት ጥበብ ብቻ ሳይሆን ውበትም ጭምር ስለሆነ ነው፡፡ ሰው በመልኩ፣ በቁመቱ፣ በአስተሳሰቡ፣ በፀጋው፣ በዝንባሌው፣ በፍላጎቱ፣ በብርታቱ፣ በምኞቱ፣ በግቡ፣ በዕቅዱ፣ በዓላማው፣ በአፈፃፀሙ፣ በምግባሩ፣ ወዘተ በብዙ ነገሩ አንድ ዓይነት ስላልሆነ ሊበላለጥ ይችላል፡፡ አንዱ ካንዱ የሚያንስበትና የሚበልጥበት ብዙ ነገር አለው፡፡ እሱ ያለው፤ ሌላው የሌለው፤ ሌላው ያለው እሱ የሌለው የትየለሌ ነው፡፡ አንድ ከሚያደርገን ይልቅ የምንለያይበት ነገር እልፍ ነው፡፡ አካላችን ቢመሳሰልም አስተሳሰባችን ለየቅል ነው፡፡ ማፍቅርና መፈቀር መፈለጋችን፣ ከምንወደው ስንለይ ማዘናችን፣ መራብ መጠማታችን፤ መጥገብ መፈንጠዛችን፣ ማጣት ማግኘታችን፣ የመሳሰሉት ተፈጥሯዊ ስሜቶቻችን ሁሉ የጋራ ፀጋዎቻችን ቢሆኑም እነሱን የምንተረጉምበት መንገድ ግን እንደአኗኗራችን፣ እንደአስተዳደጋችን፣ እንደአስተሳሰባችንና እንደልምዳችን የተለያየ ነው፡፡
ከሁሉም እበልጣለሁ ወይም ክሁሉም አንሳለሁ ብሎ ማሰብ ሁለቱም ስህተት ነው፡፡ የምናንስበትና የምንበልጥበት ጉዳይ መኖሩን መረዳት ነው ባነስንበት ጉዳይ እንድንሻሻልና በበለጥንበት ደግሞ እንድንበረታ የሚያደርገን፡፡ የትኛውም ሰው በሁሉም ነገር አንደኛ አይሆንም፤ በሁሉም ነገርም መጨረሻ አይወጣም፡፡ ማንም ማነፃፀሪያውን ሌሎች ሰዎችን ካደረገ በሰው መስፈርት ነው ራሱን የሚለካው፡፡ ከሰዎች ተሞክሮን መውሰድ፣ አዲስ ሃሳብ መማር ብልህነት ነው፤ ቁጭ እነሱን ለመሆን መሞከር ግን ድንቁርና ነው፡፡ ሰው ራሱን እንጂ ሌላውን ልሁን ቢል አይችልም፡፡ ሌላውን ለመምሰል መታገል ራስን መጥላት ነው፡፡ ራሱን የሚወድ ሰው ራሱን ነው የሚሆነው፡፡ ለዚህ ነው ኦስካር ዋይልድ “ በፍቅር ውስጥ መሆን ማለት ራስን ማሽነፍ ማለት ነው (To be in love is to surpass one’s self) ” የሚለን፡፡
ሌሎችን ለመብለጥ ደፋ ቀና የሚል ሰው የራሱ መለኪያና መስመር የለውም፡፡ የሌሎች መስፈርት ጥገኛ ነው፡፡ በራሱ ላይ ትክክለኛ ለውጥና እድገት የሚፈልግ ሰው ግን ከሌሎች መስመር ነጻ ነው፡፡ ዓላማችን ሌሎችን መብለጥ፤ ግባችን ሌሎች ላይ የበላይ ለመሆን ከሆነ እውነተኛ ደስታ አናገኝም፡፡ ሌሎችን በመብለጥ የምናገኘው ደስታ እኛም በሌሎች ስንበለጥ ደስታችን ወደሀዘን ይለወጣል፣ ዓይናችን ደም ይለብሳል፤ የሌሎች ማግኘት የእኛ መውደቅ ይመስለናል፡፡ አርስጣጢሊስ “ድላችን ሌሎች ላይ የበላይ ለመሆን ከሆነ መቼም ቢሆን አሸናፊ መሆን አንችልም፡፡ እውነተኛ ስኬት ሌላ ሰውን መብለጥ ሳይሆን ራስን መብለጥ ነው፡፡” ይላል፡፡ ኤፔኪቲተስ ደግሞ “ሌሎችን ለመብለጥ እና በሌሎች ዘንድ ተቀባይነት ለማግኘት ስንል የምናደርገው ነገር መጨረሻው ህመም ነው የሚያመጣብን፡፡” ሲል ጤናማ ውድድር ከራስ ጋር የሚደረግ ስለመሆኑ ይናገራል፡፡ ለዚህ ነው አለማየሁ ገላጋይም በ”ፈሪሳ” መጽሐፉ ገጽ 44 ላይ “መበለጥ የሚያሳምመውን ያህል ታመምኩ፡፡” በማለት በመበለጥ የሚሰቃዩ እንዳሉ የሚነግረን፡፡ በመበለጡ የሚታመም ሰው በቀላሉ ተስፋ ይቆርጣል፤ “አይሆንልኝም፣ ከሌሎች አንሳለሁ፣ አልችልም” እያለ ራሱን ወደኋላ ይጎትታል፡፡ የተሰጠውን ፀጋ ፈልጎ አያገኝም፡፡ የራሱን ትቶ የሌላውን ይመኛል፡፡
በርግጥ መበለጥ ሁሉ አሉታዊ ስሜት አለው ማለት አንችልም፡፡ በአግባቡ መበለጡን የሚተረጉም ሰው ከሌሎች ተሞክሮ በመውሰድ ለመሻሻልና ራሱን መስመር ለማስያዝ ይጠቀምበታል፡፡ ፍሬደሪክ ኒቼ “መበለጥ ከፉ ቅናትን ወይ ደግሞ ለማደግ የሚሆን ቆስቋሽ ስሜትን ይፈጥራል” የሚለው አተያያችን አጥፊም ሆነ አልሚ ስሜትን እንደሚያዋልድ አፅንኦት ለመስጠት ነው፡፡ መበለጡን በመልካም ቅናት ለተመለከተው ሰው ከበለጠው ሰው ትምህርት በመቅሰም ራሱን ለመለወጥ አቅጣጫ ያገኝበታል፡፡ ግለሰቡ መበለጡን እንደመስታወት ራሱን የሚመለከትበት ከሆነ ክፍተቱን በማወቅ፣ የጎደለውን በመረዳት መበለጡን ለበጎ ዓላማ ይጠቀምበታል፡፡ በተገቢው መንገድ ከመነዘርነው መልካም ቅናት ቁጭትን በማዋለድ አዲስ መንገድ ያስገኛል፡፡
ወዳጄ ሆይ..... ሁለት ሰዎች ስለአንድ ነገር ያላቸው አመለካከት አንድ አይሆንም፡፡ አንዱ ከእሱ የሚበልጠውን ነገር ሲያይ “ይሄን ነገር እኔ ላደርገው አልችልም፤ ብቁ አይደለሁም” ብሎ በተሸናፊነት ስሜት እያሰበ ራሱን ዝቅ ያደርጋል፤ ሌላኛው ደግሞ “የሌሎች ስኬት እኔም ከጣርኩ ላሳካው የምችለው ነገር ነው”” ብሎ በጎ በጎውን አስቦ ጥረት ይጀምራል፡፡ ጨዋታው ያለው የእያንዳንዳችን አሰተሳሰብ ላይ ነው፡፡ መበለጥን በቅን ዓይን ከተመለከትነው አዎንታዊ ለውጥ ያመጣል፡፡ በተቃራኒው ካየነውም ሁሌ በሰው ስኬት አንጀታችን ሲቆስልና ዓይናችን ደም ሲለብስ ይኖራል፡፡ መብለጥ አያኩራራም፤ መበለጥ አያሳምምም! መቀደም አያናድድም፤ መቅደምም አያስኮፍስም፡፡ ሌሎች በሁሉም ነገር ከአእኔ ያንሳሉ ብለህ በአንዲቷ ስኬትህ አትመካ፤ አንተም ከሌሎች የምታንስበት ብዙ ነገር መኖሩን አትዘንጋ፡፡ ተበልጫለውም ብለህ አትታመም፡፡ መበለጥህን ራስህን እንደማንቂያ ደወል ተጠቀምበት፡፡ ከፍ ያለ ስኬት በትናንሽ ስኬቶች እውን መሆን እንደሚጀምር ተረዳ፡፡
ቸር መበለጥ! ደግ መብለጥ!
------------------------------------
© እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.)
ሠኞ ሠኔ ፳፪ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም. | 2 724 |
| 19 | 没有文字... | 2 044 |
| 20 | ◉ Death in Tehran
➊ አጭሯ ተረት በአጭሩ
«በአንዱ ቀን አንድ ታላቅ የፋርስ ንጉስ በቅንጦት መናፈሻው ውስጥ እየተዘዋወረ ሳለ፣ በድንገት አንድ ትልቅ የጩኸት ድምፅ ይሰማል፤ ወዲያውኑም በፍርሃት የራደ አገልጋዩ እየሮጠ ይመጣል።
አገልጋዩም “ንጉስ ሆይ! እርዳታዎትን እሻለሁ! እዚህ መናፈሻ ውስጥ እየሰራሁ ሳለ «ሞትን» አገኘሁትና ሩሄ እስክትወጣ አስፈራራኝ። አምልጬ መምጣት የቻልኩ ቢሆንም፣ ለአንዲት ነፍሴ እጅጉን ፈርቻለሁ። እባክዎ ከፈረሶችዎ መካከል ፈጣኑን ይስጡኝ፤ እስከ ምሽት ድረስ ወደ ቴህራን ከተማ ገስግሼ መድረስ አያቅተኝም። ከዚያ በኋላማ ምን አለ? አመለጥኩ ማለት አይደለም? እዛ ሂጄ እደበቀዋለሁ” አለው።
ንጉሱም ለጥቂት ጊዜ አሰበበት። ንጉሱ ካሳ ቢሆን አገልጋዩ ገብርዬ ነበር ለሱ። የታማኝ አገልጋዩን የብዙ ዓመታት መልካም ግብሩን መዘነና ፈቀደለት። ፈረሱንና ጥቂት ፈረንካም አከለለት። አገልጋዩ ፈረሱን እየጋለበ ሲሄድ የሚሰማውን የኮቴ ድምፅ እያደመጠ ንጉሱ በመናፈሻው ውስጥ መጓዙን ቀጠለ። በመሀል ንጉሱ ራሱ ያንን «ሞት» የተባለውን ጉድ አገኘው።
ንጉሱም “አገልጋዮቼን ለምን አስፈራራሃቸው?” ሲል ጠየቀው።
ሞትም እራሱን እየነቀነቀ (ወይም እንደ ዱርዬ ራሱን እያከከ) “አፉ ይበሉኝ ጌታዬ፣ ከሀቅ እኔ ያንን ሰው አላስፈራራሁትም። ዛሬ እዚህ የእርስዎ መናፈሻ ውስጥ ሳገኘው የተሰማኝን ግርምት ብቻ ነበር የገለፅኩት” ሲል መለሰ።
ንጉሱም ቀጠል አድርጎ “ የኔ አገልጋይ እዚህ መገኘቱ እንዴት አስደነቀህ?” ብሎ ጠየቀ።
ሞትም ፈገግ ብሎ መለሰ፤ “ ንጉስ ሆይ፣ እዚህ እሱን በማግኘቴ የተገረምኩት እኮ... ዛሬ ምሽት ቴህራን ውስጥ አብረን እንድንገናኝ ቀጠሮ እንዳለን ስለማውቅ ነው!”
❷ በተለያዩ እረኞች የተራባው ተረት
ይሄ Death in Tehran" የተሰኘው ተረት በአለም አቀፍ ደረጃ በተለያዩ ስሪቶች የሚታወቅ ተረት ነው። ታሪኩ በተለያዩ እረኞች ተራብቷል። ሀሳቡ በአጭሩ «ከእጣ ፈንታ ወይም ከሞት ማምለጥ አይቻልም» የሚል ፍልስፍና አለው። አገልጋዩ ከሞት ለመሸሽ ወደ ቴህራን ሲጋልብ፣ ሳያውቀው ለካ ራሱ ወደ ቀጠሮው ቦታ እየሄደ ነበር።
ምንም እንኳን የፅሁፉ ባለቤት Anonymous ተብሎ ቢቀመጥም ይህ ታሪክ ሲበዛ እድሜ ጠገብ ነው። መጀመሪያ አካባቢ በሱፊ ፍልስፍና ውስጥ በሰፊው የሚነገር ነበር ይላሉ። ታዋቂው ፋርስ ባለቅኔ Rumi ተመሳሳይ ይዘት ያለው ታሪክ "The Man Who Fled from Azrael" በሚል በግጥሞቹ አካቶታል።
ይህ ታሪክ በምዕራቡ ዓለም በብዛት የሚታወቀው ደግሞ በደራሲ Somerset Maugham አማካኝነት ይመስለኛል። "The Appointment in Samarra" በሚል ርዕስ ባካተተው ስራው። ይህን ታሪክ ወዳጄ አገኘሁ አርባ «ሳማራ ላይ አለኝ ቀጠሮ» በሚል ርዕስ "አጫጭር ልቦለዶች ትርጉም" በሚለው የቴሌግራም ገፁ ላይ ለጥፎት አንብቤዋለሁ። ይህንኑ ተረት ትንሽ ለየት አድርገው መዝግበው ያስተላለፉ ሌሎች ሰዎችም ሊኖሩ ይችላሉ ልክ እንደ "Death in Tehran" ። ይህ ታሪክ በጥንታዊው የአይሁድ መጽሐፍ የባቢሎን ታልሙድ ላይም መቼቱን በጠቢቡ ሰሎሞን ቤተ መንግሥት አድርጎ ተከትቧል።
ብቻ ይህ ታሪክ በተለይ በስነ-ፅሁፍ፣ በፊልሞች እና በፍልስፍና ውይይቶች ላይ የሰው ልጅ ስለ ህይወት፣ ስለ ጊዜ እና ስለማይቀረው ሞት ያለውን ግንዛቤ ለማሳየት በተደጋጋሚ ጥቅም ላይ ይውላል።
❸ እጣ ፈንታና ነፃ ፍቃድ
ይህ ታሪክ እጅግ በጣም አሳማኝ የሆነ ምሳሌያዊ አተራረክ ስላለው፣ ታሪኩን ካነበብኩ በኋላ በእጣ ፈንታ ላይ እምነት ሳሳድር ራሴን አገኘዋለሁ። እኔ በ Free Will የተጠመቅኩ መስሎኝ።
ምክንያቱም አገልጋዩ ከሞት ለማምለጥ ያደረገው ጥረት ሳያውቀው ወደ ሞት ደጃፍ የሚያደርሰው መሆኑን ሳይ በውስጤ «የአደም ልጅ የቱንም ያህል ቢጥር የተከተበለትን ነገር መለወጥ አይችልም" የሚል ሀሳብ ወደ አእምሮዬ ይሰርጋል።
የምርም በህይወታችን ውስጥ የቱንም ያህል ብናቅድ፣ ብንጠነቀቅ እና በነጻ ፈቃዳችን ለመወሰን ብንሞክር፣ ሙሉ በሙሉ ከእኛ ቁጥጥር ውጪ የሆኑ ነገሮች አሉ። የምንወለድበት ቦታ፣ ድንገተኛ አደጋዎች፣ አጋጣሚዎች ህይወታችንን በቅፅበት ሲቀይሩት እናያለን። ይህ ሲሆን ደግሞ ታሪኩ ይበልጥ ሀቀኛ መስሎ ይሰማኛል።
❹ የቪክቶር ፍራንክል ምሳሌ
ይቺን ቁራጭ ታሪክ ፎቶ አንስቶ የላከልኝ ጓደኛዬ ሚሊየን ነው። ያገኘውም ከViktor Frankl መፅሐፍ "Man's Search for Meaning" ላይ ተካቶ ነው።
ፍራንክል በናዚ ማጎሪያ ካምፖች ውስጥ በነበረበት ወቅት የደረሰበትን መከራና የታዘበውን የሰው ልጅ ስነ-ልቦና ሲተነትን፣ የምርም ይህንን ታሪክ ማካተቱ የግድ ነበር ብያለሁ።
ምክንያቱም በካምፑ ውስጥ የነበሩ እስረኞች በየቀኑ የህይወትና የሞት ውሳኔዎችን መጋፈጥ ነበረባቸው። እስረኞቹ እጣፈንታቸውን በራሳቸው እጅ ለመለወጥ በሚያደርጉት ድንገቴ ምርጫ፣ ሳያውቁት ራሳቸውን ወደ ሞት አፍ ውስጥ ሊከቱ እንደሚችሉ ለማሳየት ፍራንክል ይህንን ታሪክ ተጠቅሞበታል።
ፍራንክል በታመመበት ካምፕ ውስጥ እያለ ከአንድ ጓደኛው ጋር ሆኖ የማምለጥ እድል አግኝቶ ነበር። ነገር ግን በካምፑ ውስጥ ያሉትን የቆሰሉና በታይፈስ በሽታ የሚሰቃዩ ህመምተኞችን ጥሎ መሄድ ህሊናው ስላልፈቀደለት፣ ላለማምለጥና ከእነሱ ጋር ለመቆየት ወሰነ።
በኋላ ላይ ምን ሆነ? እሱ ያመለጠ መስሎት በዝውውሩ የሄደውና ለማምለጥ የሞከረው ጓደኛው በጥፋት ካምፕ ውስጥ ህይወቱ አለፈ። ፍራንክል የቆየበት ካምፕ ግን ከጥቂት ቀናት በኋላ በዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ድርጅት ነፃ ወጣ።
ፍራንክል ይህንን ታሪክ በመጽሐፉ ውስጥ የጠቀሰው በእጣ ፈንታ ላይ ሙሉ በሙሉ ተስፋ ቆርጠን እጃችንን እንድንሰጥ አይመስለኝም። በህይወታችን ውስጥ የምናደርጋቸው የድንጋጤ እና የፍርሃት ውሳኔዎች አንዳንድ ጊዜ ዋጋ እንደሚያስከፍሉን ለማሳየት ይመስለኛል።
"ተይው መልሱን መጀመሪያ ጥያቄው ይግባሽ!" እንዳለው ያ እያዩ ፈንገስ እኔ አሁን Free will እና Destiny ነቅፌና ደግፌ ልከራከር አይደለም።
ብቻ ይቺ ሚጢጢ ታሪክ የሰው ልጅ ሁልጊዜም በነጻ ፈቃድ እና በማይቀረው እጣ ፈንታ መካከል ያለውን ሚዛን ለመረዳት የሚያደርገውን ዘላለማዊ ትግል ታሳየኛለች።
▭▭
© Mes Oud | 2 824 |
