ar
Feedback
ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

الذهاب إلى القناة على Telegram

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

تُعد قناة ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖 (@bookshelf13) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 18 562 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 893 في فئة الكتب والمرتبة 1 824 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 18 562 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 24 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -151، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 10.86‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 3.88‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 016 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 721 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 25 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الكتب.

18 562
المشتركون
+224 ساعات
-287 أيام
-15130 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يوليو '26
يوليو '26
+25
في 0 قنوات
يونيو '26
+12
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '26
+108
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+31
في 1 قنوات
Get PRO
مارس '26
+16
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+15
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+21
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+36
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+42
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+31
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+31
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+60
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+44
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+72
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+451
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+460
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+500
في 4 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+317
في 2 قنوات
Get PRO
يناير '25
+421
في 1 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+481
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+275
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+244
في 1 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+254
في 2 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+307
في 2 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+388
في 1 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+231
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+241
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+354
في 3 قنوات
Get PRO
مارس '24
+325
في 2 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+251
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '24
+96
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+184
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+141
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+96
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+46
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+119
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+158
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+143
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+79
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+59
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+62
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+182
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+195
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+468
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+92
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+399
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+71
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+91
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+205
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+198
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+317
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+718
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+177
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+356
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+36
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+213
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+243
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+908
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+917
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+873
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+219
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+59
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+125
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+430
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+396
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+304
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+354
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+14 056
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
25 يوليو+1
24 يوليو+3
23 يوليو+1
22 يوليو0
21 يوليو+2
20 يوليو0
19 يوليو0
18 يوليو+1
17 يوليو+2
16 يوليو0
15 يوليو+1
14 يوليو+1
13 يوليو+1
12 يوليو+4
11 يوليو+1
10 يوليو+4
09 يوليو0
08 يوليو+1
07 يوليو0
06 يوليو0
05 يوليو+1
04 يوليو0
03 يوليو0
02 يوليو+1
01 يوليو0
منشورات القناة
2
ትቅርብን ጨረቃ! (በድሉ ዋቅጅራ) እሷ እያለች፣ ‹‹ዳቦ ናት›› ምናልባት፣ ከራባት፣ . . .. ልትበላት፡፡ እሱ ሲል፣ ‹‹የብረት አሎሎ¹›› ሊቀጠቅጣት አግሎ፡፡ እንደጦር ሊወረውራት፤ ምናልባት፡፡ እና የመጨረሻ፣ መጨረሻ፤ እሷ ሌማት²፣ እሱ መዶሻ፤ ይዘው፣ ሲቋምጧት እያየሽ፤ ‹‹ጨረቃስ›› ብለሽ ታኮርፊያለሽ? ይልቅ ሳቂልኝ ውዴ፣ ትቅር ጨረቃን ተያት፤ ትገለጥበት አንደበት፣ ትታይበት መልክ የቸገራት፤ የየነብሳችም ስእል፣ የመሻታችን ፍቺ ናት፡፡³ ተያት፡፡ ------------- ሚያዝያ 2017 (በቅርብ የሚታተም) . . . Keep the Moon Away! (By Bedilu Wakjira) While she claims, "It's a loaf of bread"— Perhaps, Starving, to feast upon it. While he calls it "an iron cannonball"— To heat and hammer it down, Or perhaps, to hurl it like a spear. And so, In the end, the very end— As you watch her with her basket, And him with his hammer, both coveting it... Will you still pout and ask, "What about the moon?" Instead, laugh for me, my love, and leave the moon alone; It lacks the tongue to speak itself, The true form through which to be seen. For it is merely a canvas of our souls, A reflection of our own desires. Let it be. ---------- April 2025 Translation: Google Gemini ¹ "የብረት አሎሎ" (Iron Cannonball / Iron Ball): Refers to a heavy iron projectile or ball used in forging or warfare, emphasizing how different minds reduce beauty to raw, functional, or destructive matter. ² "ሌማት" (Basket / Lemat): The traditional woven basket used for serving injera, capturing the hunger and consumer mindset in the metaphor. ³ "የየነብሳችን ስእል፣ የመሻታችን ፍቺ ናት": A profound closing thought—the moon has no objective meaning of its own in human eyes; it is simply a projection ("portrait/canvas") of each person's inner hunger, desire, or state of mind.
1 117
3
لا يوجد نص...
1 026
4
መልክዐ ምስል በሚለው ድርሰቱ በቅዥት እና በእውን አለም መሀከል ያለውን ልዩነት ይጠይቃል። ሰው ስሆን ቢራቢሮን ነበርኩ ወይስ ቢራቢሮ ሆኜ ነው ሰው መሆንን ያለምኩት? ሲል እናገኘዋለን ገፀባህሪው በዚህም እውነት ምንድነው? እውነታው የቱ ነው? እያለ በፍልስፍናው ዘርፍ ስነእውቀት( epistemological) ጥያቄ ያነሳል። ሪኔ ዴካርት የተጠራጣሪነት ( skepticism ) መንገድ አሰተዋውቋል። ሁሉንም ነገር ከመጠርጠሩ የተነሳ ይሄ እውነት የሚመስለኝ አለም ቅዠት ቢሆንስ የተማርኩት አወቅኩት የምለው ነገር ሁሉ የሚጠረጠር አለመሆኑን እንዴት አውቃለሁ ይላል። የሲራክ ጥርጣሬ ጨለማ ከወረሰው ሽሽግ ጨቅላ ማንነታችን ( ጥላ) እና በገላችን መሀከል የሚዋዥቀው መልክዐ ምስላችን ላይ ነው። ቀቢፀ ተስፋ፣ መነጠል፣ ከዘመን ጋር መኳረፍ የመሳሰሉ የተብሰልሳይ እጣፈንታን በብዛት ይዳስሳቸዋል። ማህበረሰብ እና የማህበረሰብ ዘልማዳዊ አኗኗር፣ የጋራ የስሜት ቁስሉ(collective trauma)፣ በትውልድ መሀከል ያለ ክፍተት በሶምሶማ የተረገጡ ዳናዎች ናቸው። አፃፃፉ ምስል ገላጭ ቢሆንም እያንዳንዱ ምስል የራሳቸው ሚታዊ አንድምታ ያላቸው ይመስላሉ። ሚታዊተረኮችን የምናቡ አጋፋሪ አድርጎ ተጠቅሟቸዋል። አብዛኞቹ ታሪኮች በተምሳሌታዊ ዘይቤየቀረቡ ናቸው። አሁንም የቤቷ ከፈፍ ላይ የቁራ ድምፅ ይሰማታል።እየቆየ እየቆየ ያንቋርራል። በመሀል ዝምታ ሸማውን አንጥፎ የድምፅ እርጥባን እየተመፀወተ እልፍ ይላል። የእረፍት የአድባራቱን ስም በጥንቃቄ መርጦ እየጠራ የምስጋናውን ቡራኬ በለጋ እጁ ይለግሳል። በርጥብ ልቡ ፈገግ ይላል።የመጨረሻውን የቁራ ድምፅ ተከትላ ቀና ስትል ጥቁር ዓይነ ድፍርስ ፍጡር ጋር ዐይን ለዐይን ተገጣጠሙ። ገፅ 36 ስደተኛ ወንዞች ከሚለው አጭር ታሪክ ቴዎድሮስ ገብሬ እንደሚለው ሚት ለቋንቋ አልገብር ያሉ ዲበአካላዊ ( metaphysical) የሆኑ ጉዳዮች ዘይቤያዊ መገለጫ ነው። ዘይቤ ደግሞ ቋንቋ እና ሚት የሚሰናኙበት ኋልዮ መሆኑን እንደ ካሲረር ያሉ የሚታዊ ቋንቋ ልሂቃን እንደሚመሰክሩ ይናገራል። ሲራክ ሚታዊ ተረኮችን ዘይቤያዊ(metaphorically) በሆነ መንገድ በማሰናኘት የማህበረሰቡን የጋራ ደመነፍስ ተምሳሌታዊ ቋንቋ የመረዳት አቅሙን አስመስክሯል። ድርሰቱ ጠንከራ ሀሳቦዎችን፣ ተምሰልስሎቶችን፣ ቁጭቶችን በውብ ቋንቋ በዚህ ልክ መፃፍ እንደሚቻልም ያየሁበት ነው። Reviewer : © Yodit Ammanuel is an associate editor at © Think Ethiopia.
1 404
5
ርዕስ : ሶምሶማ ደራሲ : ሲራክ ወንድሙ ዘውግ: ልቦለድ የሕትመት ዓመት: በዮዲት አማኑኤል የሰውን ልጅ ሁለት ነገሮች ይመሩታል። ፍርሀት እና ፍላጎት ሰው ህይወቱን ሙሉ ፍርሀቱን ሲሸሽ ፍላጎቱን ሲያሳድድ ይኖራል። ፍላጎቱ ከየት መጣ ብትሉኝ ከፍርሀቱ የተፈለፈሉ ግልገሎቹ እንደሆኑ ልነግራችሁ እችላለሁ። ዋነኛውም የሞት ፍርሀቱ ነው። ፍርሀቱስ ከየት መጣ ብባል ግን መልሼ ከፍላጎቱ ይሆናል መልሴ። ዞሮ ዞሮ በህይወት የመኖር ፍላጎቱ መልሶ ከፍርሀቱ ጋር ያጋፍጠዋል። እነዚህ በአንድ ቀጭን ማዕዘን አልባ ገመድ ላይ የተሰፉ ወፋፍራም ሀቆች ናቸው። ሀቆቹ መነሻም መቋጫም የላቸውም። የተነሳንበት ከመሰለን ጋር ተነስተን አንዴ ሽቅብ ሌላ ጊዜ ቁልቁል እየተንደረደርን በደረስንበት ሁሉ የት ጋር እንዳለን ቢጠይቁን የምንመልሰው የለንም። ለህይወት ማቆሚያዋ ሞት የሚል መታጠፊያ ለማበጃጀት ብንሞክርም ይሄ ሞት ግን ከህይወት ጋር ወጥ በሆነ አንድ ቀጥታ መስመር የተሰፋ ይመስላል። ታድያ ይሄ መከረኛ የሰው አእምሮ ከመነሻ ወደ መድረሻ ፣ከማዕዘን ሌላ ማዕዘን፣ ከቀኝ ወደ ግራ ፣ከላይ ወደታች ካልሆነለት ጭንቅ ነው። ከጭንቁ የተነሳ ሰው ብዙ ጠየቀ ህይወት ምንድነው፣ ለምን መጣሁ፣ሞትስ ምንድነው? እያለ የህልውና ጥያቄዎችን ሲያዘንብ ኖረ። ይሄን የተረዳው አልበርት ካሙ የሰው መዋቅራዊው እና ምክንያታዊ የሆነው አእምሮ ይህቺ ቅርፅ አልባ እና ምክንያት የለሽ ሁለንታ ውስጥ ምክንያት የመፈለግን አብዘርድነት አስረግጦ ይነግረዋል። እንግዲያውስ ከአንድ ነጋዴ ጋር በዋጋ ተደራድረህ የመጨረሻውን ዋጋ እቅጩን ያረዳህ እንደሆነ እና ኪስህን የጠየቅከውን ለመክፈል በበቂ ሁኔታ ካላደለብክ ከዛ ነጋዴ ጋር ጀንበር ወጥታ እስትገባ ስትከራከር አትውልም። ሌላ ኪስህን ያገናዘበ ሱቅ ገልመጥ ማድረግህ አይቀርም። ሞት የሁሉም የጊዜ ዋንጫ ላይ በየተራ የሚቀዳ ፅዋ ነው። ለሰው ልጅ ይሄ ፅዋ መራራ እና አይቀሬ ነው። የህይወት በሞት መቋጨት ደግሞ ወለፈንዲ ነው። ከዚህ ወለፈንደነት ለመሸሽ ሞትህን የተለያየ መልክ እያለበሱ የሚያቀርቡልህ ሶስት ሱቆች አሉልህ። አንደኛው እንደመጀመሪያው ነጋዴ ናቸው ሞትን አንተን ሊያጠፋ ጥርሶቹን እያፏጨ እንደመጣ እስቀያሚ እንግዳ ያቀርቡልሀል። ሞት ሞት ነው ያው ሌላ ማሽሞንሞን አያውቁም። ስትሞት ትጠፋለህ ነው።የሆንኩትን ሁሉ የሆንኩት ለምንድነው? የመኖር ትርጉምስ ምንድነው? እንዲው እንደተራ ነገር መጥፋት? እንዲሁ እንዳልተፈጠረ መረሳት? ለሚለው ጥያቄህ ምላሻቸው አዎ ነው። እነዚህ የህላዌነት ፈላስፎች እንደነ ኪርጋርድ እና ሳርትሬ ያሉት ፈላስፎች ናቸው። ቋሚ ትርጉም አሰሳህን ትተህ የራስህን ትርጉም እንድትፈጥር ግብዣ ያቀርቡልሃል። ምክንያቱም ሞትህም ህይወትም ቋሚ ትርጉም የላቸውም። ግብዣቸውን ለመቀበል ግን ፈርጠም ያለ ጫንቃ ያስፈልግሀል። ካላዋጣህ እንዳቅምህ ወደ ሌላኛው ሱቅ ጎራ ትላለህ። ለሰው ልጅ ከዚህ በላይ አደገኛ እና አስፈሪ ነገር የለማ። ሁለተኞቹ ነገሩን አያከብዱብህም ሞትን ብቻውን አያቀርቡልህም ይልቅስ ትንሽ አስውበው ከሞት በኋላ ህይወት የሚል ባጅ ይለጥፉበታል። ከመጀመሪያዎቹ ይሻላል ቢያንስ የዋና ተዋናይነቱን ሚና አትቀማም። ግን ቢሆንም ሞትን ልትወደው እና በሙሉ ልብህ ልትቀበለው አትሻም። በስብሀት 5_6_7 ላይ ሞትና አጋፋሪ እንደሻው በምትል አጭር ታሪክ የሞት አፋፍ ላይ ያለውን አጋፋሪ እንደሻውን አቡዬ ይጠይቁታል። የብርሀን ሰረገላ አለኝ ሳትሞት ወደ ሰማይ ቤት ልውሰዶት። እዛ ርሀብ የለ፣ ብርድ የለ፣ሀሩር የለ፣.....አውቃለሁ አጋፋሪ ይመልሳሉ። እንደኔ እንደኔ ግን እኔን ወደ አዲሳባዬ ብትመልሰኝ በወደድኩ ይሉታል። ከሰማይ ቤት አዲስ አበባ ይሻልሀል? አስር እጅ ይላሉ አጋፋሪ። ከማያውቁት መላክ የሚያውቁት ሰይጣን ነው ነገሩ።ሌላው ልክ ብዙሀኑ ሰው እንዲህ ቢሆንስ የሚል የተጨባጩን አለም ድንበር አሻጋሪ መሲህ ትፈልግ ይሆናል። ይሄኔ ደራሲ አለልህ በምናቡ አለም አፈናጦህ ያሻው ድረስ የምኞቱን ፈረስ ሰርጥ እያስጋለበ ያለከልካይ ያነጉድሀል። የገፀባህሪው አጋፋሪ እንደሻው የሞት ፍራቻ ጋሽ ስብሀት የራሳቸውን ፍርሀት ያንፀባረቁበት ድርሰት እንደሆነ ይጠረጠራል። እና አንዴ አለቤ ሾው ስብሀትን እንዲህ ሲል ይጠይቀዋል። እንደው ሞትን ትፈራለህ ይባላል? ስብሀትም መልሶ አንተስ? ብለው ይጠይቁታል። እውነት ነው በአጋፋሪ የተወከለው አንድ ነጠላ ስብሀትን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የሰው ልጅ ነው።ስብሀት ገ/እግዜአብሄር ይህንን የሰው ልጅ የሞት ፍርሀት አጋፋሪ እንደሻውን ታከው ተርከውልናል። አጋፋሪ በየጊዜው የሳምንት ስንቃቸውን የተሸከመች በቅሏቸው ላይ ተጭነው በየመንደሩ እየዞሩ እዛ አካባቢ ለቅሶ ወይም የታመመ ሰው ይኖር እንደሆን አሽከሮቻቸውን ይጠይቃሉ። ታድያ አንዳች ለቅሶ ወይም ሊሞት የሚያጣጥር በእዛ መንደር ውስጥ ያለ እንደሆን በሉ በሰላም ዋሉ ብለው ሌላ ሰላማዊ መንደር ፍለጋ ጉዟቸውን ይቀጥላሉ። ይሄ ሁሉ ሞትን ሽሽት ነው። በኋሏ እንደቀልድ የተጎነጯት የጠላ ትንታ ከሞት ደጃፍ አድርሳ ከቢሾፍቱው ቆሪጥ ጋር አቋምራ ትመልሳቸዋለች። ከሞት ደጃፍ ላይ በቆሪጥ ጨዋታ ተሽለኩልከው መመለሳቸው ያልተዋጠለት ሲራክ ወንድሙ ጋሽ አጋፋሪን ጅማ ወስደው ከደብተራው ተዋነይ ጋር ያጣምሩታል። በድህረ ዘመናዊ የአፃፃፍ ስልት ወስጥ የሚታወቀው Metatextual የአፃፃፍ ስልትን የሆነውን ቴክኒክ ተጠቅሞ አጋፋሪ እንደሻውን በተዋነይ እና አጋፋሪ እንደሻው ሜዳ ላይ ሲጫወቱ እናያለን። ይህም በሲራክ ተዋነይ እና አጋፋሪ እንደሻው ውስጥ ስለ ስብሀት ሞትና አጋፋሪ እንደሻው ድርሰት ማውራት። እዛ የሞት አፋፍ ላይ ከቆሪጥ ጋር አይሆኑ ጨዋታ ተጫውቶ እድሜውን ለማርዘም ያን ሁሉ ጦር መሳበቅ ምን አመጣው? ለቆሪጥ ያዘነለት ይመስላል። ገፀባህሪው እንደሻው የሞት ሙከራ ያደረሰብትን ደራሲው ስብሀትን ሲከስ እናየዋለን። ሲራክ በድርሰቱ ለገፃባህሪዎቹ በቀጥታ የተጋለጠ ደራሲ ባይሆንም በምናብ አለም እና በእውነተኛው አለም ያለው መስመር ተጣፍቷል። ይህም በድህረ ዘመናዊ አፃፃፍ ስልት የተለመደ ነው። ደራሲው አጋፋሪን የሞትን ድራሽ የሚያጠፋ ደብተራ ተዋነይ ጋር ያዛምደዋል። በእርግጥ የደራሲው ሲራክ ፍርሀት ከጋሽ ስብሀትም የከፋው ሳይሆን አይቀርም። የደራሲ ዋነኛ መሳሪያ ምናቡ ነው። የሲራክ ምናቡ ጥልቀት እና ሰፊ ነው። አጋፋሪን በስብሀት ምናብ አጨዋወት እንዲያኮርፍ ካደረገው በኋላ በራሱ የምናብ ሜዳ ላይ ያጫውተዋል። የእክሱም ሀውልት እና የላሊበላ ግንብ አሻግሮ አውሮፓ ላይ ተአምር ሊያሳየው፣የቻይና ግንብ ስር እስከመሽናት የሚያስጉዝ የኢ መዋቲነት የምናብ ሀዲድ ይዘረጋል። የአጋፋሪ የሞት ፍርሀት መቅበዝበዝ ያስጨነቀው ደራሲው እስከወዲያኛ የሞት መድሀኒቱን ሰጥቶ ሊገላግለውም የፈለገ ይመስላል። የቋንቋው ስነፅሁፋዊ ውበቱ እና ገለፃዎቹ ተዝቆ የማያልቅ የቃላት ቋት ከብዕሩ ስር ካለትዕዛዝ የሚፈልቁለት እንጂ ሀሳቡን ለመግለጽ ቃላትን የሚያምጥ ደራሲ አያስመስሉትም። ሶምሶማ ወደ 15 አጫጭር የሚሆኑ ታሪኮችን የያዘ ሲሆን እነዚህ ታሪኮች በስፋት ከሚዳስሳቸው የተለያዩ ጭብጦች ሞት እና ፍርሀት፣ የህይወት ትርጉም የመሳሰሉ ወሳኝ የህልውናዊ ( Existential) ጥያቄዎችን እያነሳ ይቆዝምባቸዋል።
1 055
6
لا يوجد نص...
901
7
◉ የእዮባ ጥያቄ [Missing someone ] እዮብ ምሕረተዓብ ዮሐንስ አምለሶም... ደፋር፣ ነገሮችን ሳያሽሞነሙን ወይደሞ ሳይሸፋፍን ፊት ለፊት የሚያስቀምጥ ፀሀፊ ነበር። የራሱን የስነፅሁፍ ዘውግ «ቀደዳ» ብሎ የቀደደ ነው። ነገሮችን በአዲስ መንገድ ለመመልከት ንቁ የሆነ አእምሮ ያለው... ጨዋታ አዋቂ ነው። በፅሁፎቹ እዮባ ራሱን መስሎ ራሱን ኮርጆ የዘለቀ ነው። የእሱ የግሉ ብቻ የሆኑ አገላለፆች ያሉት። «የዝንጆሮ ፌደራሊዝም... የኤቲስቱ ገብርኤል... ቀይ ሞንዳላ ...አትፍዘዝ ታመጣለህ መዘዝ...ጥሬ ሀቅ ነው ዋጠው!...» ብዙ ብዙ... ◉ ይሄ ሰው አንዲት መፅሐፍ ብቻ ሰጥቶን እንደሄደ ሳስብ እቆዝማለሁ። ግን ደግሞ ይቺው አንድ መፅሀፍ እንደ ዶላር የምትመነዘር ስራ መሆኗን ስረዳ እፅናናለሁ። «ቼ በለው!» በጣም ፀዴ መፅሐፍ ናት። ከዚች መፅሐፍ ደግሞ አንድ የሚያስገርመኝ ስቶሪ አለ። ደጋግሜዋለሁ ብዙ ግዜ። "Gender - of the Urban Context" ይሰኛል። የከተማ ህይወት በሴቶችና ወንዶች ግንኙነት ላይ ያለውን ተጽዕኖን ይፈተፍታል። የዘመናዊነት እና የማንነት ቀውስን ያስተነትናል። እና እኔ ቀደዳ ብቻ አድርጌ አላየውም። ጥናታዊ ፅሁፍም ይመስለኛል። እንዴት? ➊ ታሪኩ በአጭሩ ይሄን ይመስላል? ታሪኩ ሂሩት ስለምትባል የተማረችና በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ላይ ስለምትሰራ ስኬታማ ሴት ይተርካል። ግና...ቅሉ...ህይወቷ በተከታታይ ውድቀቶችና ስብራቶች የተሞላ ነው። ● ሂሩት ከራሷ በታች ለነበረ ነገር ግን ጎበዝና ታታሪ ለሆነ ወንድ የትምህርትና የኑሮ ወጪውን በመሸፈን፣ አስተምራ አሰልጥና ሰው አደረገችው። እሱ ግን እግሩ ተውተርትሮ እንደቆመ ፍላጎቶቹና የሴቶች ምርጫው እየጨመረ ስለመጣ እሷን ክዶ ሌላ ጓደኛ ይዞ ጥሏት ሄደ። ​ ● በወንዶች ላይ ባደረባት ከፍተኛ ጥላቻ የተነሳ "Radical Feminist" ሆነች። ወንዶችን ማጥላላትና መጠየፍ ጀመረች። እዮብ ይሄንን የተሰማትን የወንድ ጥላቻ በአይረሴ ቃላት አስፍሮታል። «ብቻዋን አልቀረችም። መሰሎቿንም ፈላልጋ አገኘች... ባል፣ ጓደኛ፣ መልክ፣ ወጣትነት፤ ፈገግታ፣ ወግ፣ አመል Femininity፣ ደስታ፣ ፍቅር፣ ሰላም፤ ፈላጊ፣ ለካፊ፤ አሽኮርማሚ፣ ሞካሪ፣ አፍቃሪ ካጡ... ተናዳፊ ጊንጥ የመሰሉ ብስጩ ፌሚኒስቶች ጋራ ገጠመች:: የግሩፓቸው አባል ሆነች። ወንድ የባሰ ጠላች። አቤት አጠላል... ... አውራ ዶሮ ሴት ዶሮን ሲያሽኮረምም ካየች በድንጋይ ታባርረዋለች:: ባጋጣሚ መኪናዋ ተበላሽታ በታክሲ ተሳፍራ ስትሄድ ወያላው ትርፍ ሰው ለመጫን 'እሙ ትንሽ ተጠጊለት' ሲላት "እምቢ! ሴት ስለሆንኩኝ ነው አይደል?" ብላ ኡኡ ትላለች። እንዳው በስህተት እንኳ ትንሽ ዘነጥ ነገር ያለች መስላ ቢሮ ከሄደችና የሥራ ባልደረቦቿ በአድናቆት ዓይን ከሾፏት፡ this is harassment! ብላ ታምባርቃለች....በጠቅላላው የወንድ ፍጡር ጠላች!» ይለናል። ሆኖም አብረዋት የነበሩት ፌሚኒስቶች አንድ በአንድ ትዳር ይዘው ሲቀነጠሱ ተስፋ ቆርጣ ያንን መስመር ተወችው። [በወንዶች ተስፋ የቆረጡ አኩራፊ ሴቶች ወደ ፌሚኒዝም ባስ ሲልም Radical Feminist የመሆን እድል አላቸው? Maybe ●​ ከፌሚኒዝም በመቀጠል ፍጹም ወደሆነ መንፈሳዊ ህይወት ዞረች። እዚያም በቤተክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊ ሰው መስሎ የቀረባትንና የታመነ የመሰላትን ወንድ አምና ብር አበደረችው። እሱ ግን ገንዘቡን ይዞባት ወደ ውጭ ፈረጠጠ። ​ ● በአገር ውስጥ ወንዶች ተስፋ የቆረጠችው ሂሩት፣ "የሴትን መብት ያከብራል" በሚል እሳቤ ከአንድ የውጭ ሀገር ዜጋ ጋር ፍቅር ጀመረች። ነገር ግን ያ ነጭ ለትዳር ስትጠይቀው እሱ የሚፈልገው ጊዜያዊ መዝናኛ ብቻ ነበር። ● ​በመጨረሻም ሂሩት ብቻዋን ለመሆን ወስና፣ ከአንድ ያገኘችው ወንድ አርግዛ Single Mother ለመሆን ትገደዳለች። አታሳዝንም? ❷ የእዮብ ጥያቄ እዮባ የዚችን ሴት ታሪክ ሲቋጨው አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ጠይቆ ነው። «ከተማሩና በትልቅ የሥራ ሃላፊነት ላይ ከሚገኙ ጨዋ ላጤ ሴቶች ይልቅ አለሌ፣ መሃይም፣ ጋለሞታ፤ ቅናተኛ፤ መልከ-ጥፉ፣ ወንድን አሰቃይ ወይንም ዱርዬ ሴት! ሲሆን አሪፍ ትዳር፣ ካልሆነም ቢያንስ መውደቂያ ባል አጥታ የማታውቀው ስለ ምንድን ነው?» አለም ላይ የሆኑ ሀቆች አሉ አይደል? እንዲሁ የምንስማማባቸው? ከአከባቢያችን ከዙሪያችን አስተውለን የምንቀስማቸው! ጥናት ያልተሰራባቸው! Data የሌላቸው! እዮብ እነዚህን ነው ፈልፍሎ ማሳየት የፈለገው። ሁሉንም ነገር በሪሰርች፣ በቁጥር...በግራፍ ብቻ መለካት አይቻልም። ​እውነት ሪሰርች ባይሰራበትም፣ በዙሪያችን የምናያቸው ተጨባጭ ሁኔታዎች የራሳቸው የሆነ ትልቅ Data ናቸው። እኔ በዓይኔ የማየው፣ በህይወቴ የማውቃቸው ሰዎች ታሪክ ከማንኛውም የዩኒቨርሲቲ ጥናት በላይ እውነተኛ ነው። ​ደመ-ነፍሳዊ መግባባት አላቸው። አእምሮአችን "መረጃ አምጣ?" ሳይለን ደመ-ነፍሳችን ወዲያውኑ "አያስፈልግም ማስረጃ። ልክ ነው!" ብሎ የሚቀበላቸው ናቸው። ● ያው ይሄንን የእዮባ ጥያቄ ስንመለከተው ሀቅነት አያጣውም። ​በእኛ ማህበረሰብ አስተዳደግ ወንድ ልጅ ሁልጊዜ በቤቱ ውስጥ መሪ እና የበላይ እንዲሆን ነው የሚጠበቀው። ሴቷ በጣም የተማረች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች ስትሆን፣ የብዙ ወንዶች Ego ያነጥሳል። በርበሬ እንደሸተተው አፍንጫ። ​ያልተማሩ ወይም ራሳቸውን ካልቻሉ ሴቶች ጋር ሲሆን ደግሞ ወንዱ ሙሉ የበላይነቱን በቀላሉ ያገኛል። ሴቷ ሙሉ በሙሉ በእሱ ላይ ጥገኛ ስለምትሆን የሚሰማው የጀግንነት ስሜት ለትዳሩ መቆየት (ጤናማ ቢሆንም ባይሆንም) እንደ ሰበብ ሆኖ ያገለግላል። በሌላ በኩል ደግሞ ​ታሪኩ ላይ እዮባ "አለሌ" ወይም "ጋለሞታ" ያላቸው ሴቶች ወንዶችንም ህይወትንም እስኪበቃቸው እየሾሩ ከብዙ አንግል ስላዩዋቸው ከወንድ ልጅ የሚጠብቁት መስፈርት በጣም አነስተኛ ነው። ​ወንዱ ጥቂት ነገር ሲያደርግላቸው በቀላሉ ይረካሉ (ያንን ነገር አይጨምርም) ... ፍፁም የሆነ ወንድ አይጠብቁም። ​በአንጻሩ የተማሩት...ጨዋዎቹ ሴቶች ግን ከፍ ያለ የህይወት መርህና መስፈርት ስላላቸው፣ የወንድን ስህተት በቀላሉ አያልፉም። ይህ ጥብቅ መስፈርት ደግሞ ወንዶች ረጅም ርቀት አብረዋቸው ለመጓዝ እንዲፈሩ ያደርጋቸዋል። [ እዩባ መሠረታዊ ጥያቄ ነው ያነሳ አይመስላችሁም? ዛሬ ላይ ደግሞ ጉዳዩ ያሳስባል። ያው ​የስነ-ጽሑፍ ዋናው ውበትና ጥቅሙ ጥናትና ምርምርን መተካት አይደለም። ማህበረሰቡ እያየው ግን ደፍሮ የማይናገረውን ሀቅ መስታወት ሆኖ ማሳየት ነው። እዮባ እነዚህን ሀላፊነቶች ሲወጣ የነበረ ሰው ነው። © Mes Oud
1 431
8
لا يوجد نص...
1 384
9
ለዛሬ (ዕለተ ቅዳሜ) ዘፈኑን ያዳመጠ ሁሉ ጆሮ ሰጥቶ እንዲያደምጠው በማሰብ ይህን ያህል አልኩ። በጭፍን አስተያየት ተገፍቼ እንጂ ለወትሮዬ መጻፍም የሚቀናኝ ሰው አልነበርኩም። የተቀረውን ደግሞ አድማጭ ራሱ ያዳምጠውና ይፍረድ። ግን በዚህ ሁሉ ውስጥ ምን ብዬ አምናለሁ? አብረን ሠርግ ላይ አልተቀመጥንም ይሆናል፤ አብረንም አልተሠረግንም፣ አብረን ጨፍረንም አናውቅ። ግን አሁን ሁላችንም በአስቴር የተነሳ ቤተዘመዶች ሆነናል። በዚህ ሥራ ልክ እንደ ቅርብ አምቻዎችና ጋብቻዎች፣ እንደ ቅርብ ስጋ ዘመድ፣ ከያለንበት የዓለም ጥግ ሰብስባ፣ ወደ ሠርግ ትዝታ ማዕበል ወስዳናለች። ስሜታችንንም ንጣ አስነስታ አውረግርጋናለች። በአስቴር የሠርጌ ትዝታው ዳግመኛ ስራ ሁላችንም የምንተዋወቅ ቤተዘመዶች ሆነናል። ለጠሪያችን ለአክባሪያችን አስቴር ምሥጋና ይድረሳት። ድግሱን አጣፍጠው፣ ቀምመው፣ ተንጎዳጉደው፣ ኳኩለው ላሳመሩላት ባለሙያዎችና ሙዚቀኞች በሙሉ ለእነሱም ምስጋናችን የላቀ ነው! እሰይ አበጀህ አንተ የኛ ልጅ አንተ የኛ ልጅ... አስቴርዬ አንቺም እሰይ አበጀሽ። እሰይ አበጀሽ አንቺ የኛ ልጅ አንቺ የኛ ልጅ ባሳር ተገኘሽ በሺ አማላጅ። ጣፋጭ የቅዳሜ ውሎ ይሁንላችሁ። 🙏🏿🎵💙 — © ያፌት ተስፋዬ ( ጃፍ)፦ ስለ ጣፋጭ ገለፃህ እናመሠግናለን። ላንተም ሸጋ ቀዳሚት!🙏🏿
1 837
10
'የሠርጌ ትዝታው' — የከበሮው ምትና የትዝታው ማዕበል!! _________ (በጭፍን ትችት ላይ የተሰነዘረ ምክንያታዊ ምላሽ) በያፌት ተስፋዬ ( Yaphet Tesfaye ) "በስሜት እንተቸው፣ ግን በምክንያት እንውደደው💡!!" ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ/ም ______ 🕊️ መግቢያ፡ ከዝምታ ማኅደር 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ በአንድ ወቅት "ጪም-ጪሪሪም" የሚባል የቃላት ድርደራን ብቻ ዘፈን አድርጎ ሲያንጎራጉር የነበረን ድምፃዊ በአዎንታዊ መልኩ ሲያበረታታና ሲያቆለጳጵስ የነበረን አንድ ታዋቂ የሶሻል ሚዲያ ሰው፣ ከሰሞኑን በአስቴር አወቀ አዲሱ 'የሠርጌ ትዝታው' ሥራ ላይ 'መላቅጡን አሳጣችው' ብሎ አንጓጣጭ ቃሎችን ሲለጥፍ ተመለከትኩ። ይህን ስመለከት ዝም ብዬ መቀመጥ አልቻልኩም። ተገድጄ ከዝምታዬ ተፈነቀልኩ፤ እና እኔም ስሜቴን በብዕሬ ልለጥፍ ወደድኩ። ለመሆኑ በቀድሞውና በአሁኑ የሙዚቃ ሥራ ላይ አሉታዊ አስተያየት ሲሰጡ ከሰማኋቸው መሐል፣ የትኛው ‘መላ’ የቱጋ ‘መላቢስ’ እንደሆነና፣ የቱስ ‘ቅጥ’ ምን ተደርጎ ‘ቅጥ-እንዳጣ’ በምክንያትና በሙዚቃ ዕውቀት አብራርቶ የገለፀ አንድም ሰው አልገጠመኝም። ይልቁኑ ካለሁበት አሜሪካ ሆኜ የሀበሻን ማኅበረሰብ ስታዘብ፤ በጽሁፍ፣ በድምፅ፣ በምስል፣ አልፎ ተርፎም ፊትን ቅጭም በማድረግና እጅን ከወዲህ ወዲያ በማወናጨፍ የዕውር-ድንብር አሉታዊ ስሜትን ሲያንጸባርቁ አስተውያለሁ። ምንም ይሁን ምን፣ ስሜትን መግለጽ ተፈጥሯዊና የዕለት ተዕለት ሰውኛ ባህርያችን ቢሆንም፤ ‘የሠርጌ ትዝታው’ ተቺዎቹ እንደሚሉት ቅጥ-እንዳላጣ ግን ምክንያታዊ ጆሯቸውን እንዲመልሱልኝ ፈለግኩ። ጆሯቸውን 'መመዝለግ' አላልኩም — ጆሯቸውን አስልተው፣ ደግመው በጥሞና እንዲያዳምጡት ማድረግ ነው ፍላጎቴ። 🎛️ የቅንብሩ ረቂቅ ምሥጢር 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ የመጀመሪያው የሠርጌ ትዝታው ሥራ በስልተ-ምቱ፣ በዜማውና በአዛዜያሙ ከአሁኑ በእጅጉ የለሰለሰ መሆኑ እውነት ነው። ነገር ግን አሁን የቀረበልን ሥራ በጊዜ ርዝማኔ ውስጥ አብሮን የኖረውን ያንን የጋራ ትዝታ፣ በልዩና አዲስ የሙዚቃ ምርምር (Experiment) ፈትሾ፣ በሌላ ሥራ ያልተሰማ የቅንብር ትሩፋትን ጨማምሮ ያቀረበልን ድንቅ ፈጠራ ነው። የዘፈኑ አብዛኛው ግጥምና ዜማ ብዙዎቻችን እንግዳ ካልሆንንበት ከሠርግ ባህላችን የተቀዳ መሆኑ ግልፅ ነው። እርሷም በሰርጓ ጊዜ የተዘፈነውን ባህላዊ ዜማ እያስታወሰች 'እየተባለ የተዘፈነው' ስትል የራሷን ትዝታ ታጋራናለች። በአሁኑ ሥራዋ ላይ ግጥሙ፣ ዜማውና አብዛኛው የBasslineና Melody መሠረቱ ሳይናጋ ባለበት የተቀመጠ ሲሆን፤ በፊት ያልነበረ አዲስ ስልተ-ምት (Rhythm)፣ ድልድይ (Bridge) እና በዜማው ላይ ጥልቅ የነፍስ ስሜት ታክሎበታል። በዚህ አዲሱ ሥራ ላይ፣ ከአገባቡ ጀምሮ ያ የድሮው ትዝታ የቅርብ ጊዜ ትዕይንት ይመስል ይበልጥ ግልፅ በሆነ መልኩ ተቀረጻል። የሙሽራዋ ማማርና የሰዉም ጭፈራ ገና ከዓይኗ ላይ እንዳልጠፋ ለማሳየት — ጥሩምባው፣ እልልታው፣ ጭብጨባውና የአታሞው ድምድምታ በስሱ ተደርቧል። ይህም በሙዚቃዊ መንገድ ትዝታዋ አሁንም ዛሬም ጆሮዋ ላይ እያስተጋባ መሆኑን የሚያሳይ ጥበባዊ ስልት ነው። ይህ ስሜትን በዜማ ውስጥ የማንፀባረቅ ብቃት፣ የአርቲስቷ አሳምረን የምናውቅላትና የምንወደው መገለጫዋ ቢሆንም፤ በዚህ ዘፈን ላይ ግን በዘመን ያካበተችውን ልምዷን ተጠቅማ፣ በአእምሯችን ውስጥ ትልቅ ተንቀሳቃሽ ሲኒማዊ ትዕይንትን ህይወት ዘርታ አሽሞንሙናዋለች። 🔍 የዘፈኑ መዋቅራዊ ትንተና (Timestamp Breakdown) 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ 🥁 1ኛ/ 1 ደቂቃ ከ24 ሴኮንድ | (የሰርጌ ሁኔታው) ~~~~~~~~ 'ሁኔታው' የሚለው ቃልና ዜማው ተቀይሮ፣ በቅጽበት ከፍ ብሎ ድንገት ቁልቁል እንዲወርድ መደረጉ፤ እና በመሐል ሙዚቃውን አቁሞ በከበሮው ምት ብቻ እንዲቀጥል መደረጉ የረቂቅ ጥበብ መገለጫ ነው። ይህ ዘዴ የትዝታ ስሜት ድንገት ፈንቅሎ ከውስጣችን እንዲወጣ ከማድረግ አልፎ፣ ሰውን ነሽጦ ድንገት ከጭፈራው መካከል የሚያስገባ ታላቅ ስሜት ፈጣሪ ስልት ነው። ይህ ዓይነቱ ስልት በቤተክርስቲያን ማኅሌትና ዜማዎችም ላይ ያለ፣ ማኅበረሰቡ ከጥንት ጀምሮ የፈጠረውና የጠበቀው የሙዚቃ ዕውቀት (Indigenous Knowledge) ነው። 🙅‍♂️ 2ኛ/ 2 ደቂቃ ከ27 ሴኮንድ | (አናስገባም) ~~~~~~ ይህ ቃል ከተቀየረው ዜማ ጋር ሲዋሀድ በትክክል እሷ እንደምታቀነቅነው ሁሉ፤ የሙሽራው ቤተሰቦች ዓይናቸውን ፈጠጥ አድርገው፣ እጃቸውን በአይሆንምታና በፉከራ አየር ላይ እያወዛወዙ... እዛው ቆሜ በዓይኔ ያየኋቸውን ያህል ሕያው ስሜት እንዲሰማኝ አድርጎኛል። 🕺 3ኛ/ 3 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ | (አለበለዚያማ ልጃችን አትሄድም!) ~~~~~~ ለሙሽራው ልጃቸውን የሰጡት ቤተሰቦች በሚዜዎቹ መፍዘዝ የተነሳ በውሳኔያቸው ወደ ጥርጥር ሲገቡ ይታያሉ። ታዲያ አንዱ የቤተሰብ አባል (አጎቷ ይመስሉኛል) ድንገት ተነስተው... እጃቸውን ከፍ፣ አመልካች ጣታቸውን ወደላይ ቀሰር አድርገው፣ ክንዳቸውን እያወዛወዙ፤ ቀኝ እግራቸውን ከፍ! አስቴርን በአዲሱ ሙዚቃዋ ያጀቧት መሣሪያ ተጫዋቾች ወደፊት ቀደም አድርገው... ከመጨረሻዋ ከበሮ ምት ጋር እኩል መሬቱን ረገጥ ሲያደርጉትና... ወዲያው የከበሮው ምት ሲቀጥል፣ በትከሻቸውም ጭምር መታ መታ መታ ሲያደርጉት... እኔም ተከትዬ ቸብ ቸብ ቸብ ቸብ.......!! 😢 4ኛ/ 1 ደቂቃ ከ39 ሴኮንድ | (አይበልሽ ከፋ) ~~~~~~~ ይህ አገላልጽ ዛሬ ላይ ሆና ያኔ በሠርጓ ቀን የተደሰተችው ሙሽራ... መለስ ብላ ከቤተሰቦቿና ከቀዬው የምትርቅበትም ቀን መሆኑ ትውስ ሲላት... እዝን ብላ ስታለቅስ ያዩዋት እናቷ ወይም አክስቷ (አልያም ያሳደጏት ጎረቤቷ)፤ አድጋ ለዚህ ቀን ብትበቃም ዛሬም እንደልጅ እያዩአት... የመለያየት ስሜታቸውን በሆዳቸው አምቀው እንባዋን እያበሱ፤ ከጉንጮቿ ላይ ቦጭቀው ሊጎርሱ ይመስል በጣቶቻቸው ጉንጯን ይዘው በልጅ አንደበት 'አይዞሽ የኔዋ፣ አይበልሽ ከፋ' ብለው ሲያፅናኗትና ሲያበረቷት ሳይ... እህቴ ልትሄድ ነው ብዬ ሆዴ እንዲረበሽ ያደርገኛል። 🏛️ ማጠቃለያ፡ በአስቴር ዜማ የተሳሰረው ቤተሰብ ~~~~~~~~ በእነዚህና በብዙ በዚህ ዘፈን ውስጥ በተካተቱ የትዝታ ስሜት አገላለጾች አንጻር ስመዝነው፣ ይህ አዲሱ ሥራዋ በሀገራችን ሙዚቃ ታሪክ ሰምቼው የማላውቀውን የአንድን ዘፈን የቀደመ እትም (Version) ውበት ሳይበክል፣ በተሳካ ጥበባዊ ሙከራ አዲስ ቀለም ሊፈጠር እንደሚችል ያሳየ የሙዚቃ ምርምር ውጤት ነው። ይህን የምለው ዘፈኑን ደጋግሜ አድምጬው ነው። ሳደምጠውም የቀደመው የሠርጌ ትዝታው ዘፈኗ 'ተለወጠብኝ' የሚል ምንም ዓይነት የባዕድነት ስሜት ሳይሰማኝና ሳይጎረብጠኝ.... በራሱ መንገድ አዲሱን ቅኝት ማጣጣም መቻሌን እጅግ እየተደሰትኩበት ጭምር ነው።
1 676
11
لا يوجد نص...
1 136
12
Mandefro_Maru,_YeHilawe_Enqoqilish_የሕላዌ_እንቆቅልሽ.pdf
1 236
13
لا يوجد نص...
1 407
14
‹‹ታዲያ በዚህ አገር የፍቅር ማደሪያው የትኛው ልብ ነው?›› ብሎ በመጠየቅ በገንዘብና በቪላ ተደልላ ለሄደችበት ሴት የተፃፈ በማስመሰል ረዥሙ የግጥም ወንዝ ይፈሳል፡፡ ገጽ 1 ‹‹ዕለተ ቅዳሜ ፒያሳና ቦሌ›› በቃ ከዚህ ጀምሮ እስከ ገጽ 100 ድረስ አንድ የግጥም ሃሳብ ያነባሉ:: ለዚህ ነው በአለም ረዥሙ የግጥም ስንኝ በማለት በአለም ድንቃድንቅ መዝገቦች ስፍራ የሸለምኩት፡፡ ከአንድ ታሪክ ከአንድ ቅዳሜ ተነስቶ አዲ አበባን የአዲስ አበባን ሰዎች ወጣቶች ሴቶች ልጆች ኢትዮጵያን የምናይባቸው ግጥሞች ቀርበዋል:: በተለይ ከመጀመሪያው ገጽ የቀረቡት ----የቤት ልጅ ( ፀጉሯን የምትሰራውን እፎይ ብላ ተቀምጣ ያረፈቸውን የፒያሳ ልጅ ከቦሌ ቀለማት ቆነጃጅት ጋር ያነፃፀረበትን ወገን ስቄበትም ተደንቄበትም አልፌዋለሁ፡፡ ለአራት ሰባት ምግብ አዘው፤ በጋዜጣ ምናምን ነገር ያየዙትን ወጣቶች ‹‹ቀኑ ቅዳሜ ነው›› ያለበትን ምክንያት ወድጄዋለሁ፡፡ በአንዳንዱ ገጽ የተለያዩ ግጥሞች የሚመስሉ ስንኞች በተለያየ ርዕስ ስር ቢቀርቡም እርስ በርሳቸው የተያያዙና የተደጋገፉ አንዱን ካለነበብን የሌላኛው የማይገባን ግጥሞች ናቸው፡፡ ምናልባት እንደ ሌሎች የግጥም መድበሎች ከመሃል አንድ፤ ከዳር አንድ እያደረግን የምናነበው ከኾነ አይገባንም፡፡ በአብዛኛው ሁሉም ማለት ይቻላል በ 21 -04-2004 እስከ 29 -04 2004 ባሉት ቀናት ውስጥ የተጻፉ መኾናቸውን በግርጌ ማጣቀሻቸው ማየት ይቻላል፡፡ ኤፍሬም ስዩም በዚህ የግጥም ስራው አንዲት የወደዳት ያፈቀራት አብሮ ትኖር የነበረችን ሴት እያስተዋወቀ ለሌላ ባል የተሰጠችውን ፍቅረኛውን የበለጠ ሃብት ፈለጋ ወደ ሌላ ወንድ ጋር ሄዳ የምታሳልፈውን ሕይወት ከጓደኛዋ ከጎረቤት ከሰራተኛ እና እራሱም የሚያየውን እየጠቀሰ ይተርክልናል፡፡ ምናልባት ትግስተኛ አንባቢ ካልሆኑ በዚህ ዘመን ደግሞ ‹‹ምን ያለ ፍቅር ነው›› ልትሉ ትችላላችሁ፡፡ የዋዛ እንዳይመስላችሁ፡፡ በገጽ 87 ላይ በምናገኛት ‹‹ደባል ታቦት›› የግጥም ስንኝ ብዙ ልንማር ብዙ ልናውቅ ብዙ ልንለወጥበት የምንችልበትን ሃሳብ በአዲስ ቀን 01-03-2003 ወደ ኃላ በመመለስ ያቀርብልናል፡፡ አዲስ ቀን ነው፡፡ ምናልባት ግን 2003 ዓ/ም በስህተት የተገለጸ ሊሆን እንደሚችል ገመትኩ፡፡ ምክንያቱም በገጽ 87 የምናየው ‹‹መቼም›› የተሰኘችው ግጥም የተጻፈችው በ02-03-2004 በመሆኑ፡፡ ከዚህ በገጽ 91 ስንበት በሚል ያቀረበው ግጥም የዚህ ሁሉ ታሪክ መገባደጃ በመሆን ቻዋ !! ይላታል፡፡ ‹‹ሁሉም ከንቱ ነበር›› የሚለው ቀጣይ ግጥም በገጽ 92 ይቀርብልናል፡፡ አራት ጊዜ አንብቤዋለሁ፡፡ ወድጄዋለሁ! የመጣሁበትን ጉዞ ሁሉ አሳረፈኝ፡፡ አስተማረኝ፣ መክረኝ፣ እንድጠይቅ አደረገኝ፡፡ ተባረክ ኤፍሬም! ለዚህ ዘመን፣ ለዚህች አገር፣ ለዚህ ትውልድ፣ ለሽማግሌ ለነገስታት የተጻፈ ግጥም፡፡ ህልማችን መተኛት ህልማችን መጠጣት ተሰብስቦ ማውራት ማውራት ማውራት ማውራት-- --- አዎን በዚህ ሀገር ሁሉም ከንቱ ነበር፡፡ ሽማግሌው መውራት ወጣቶቹ ማውራት ነገስታቱ ማውራት ማውራት ብቻ ጥበብ ሕይወት የሆነበት እርስ ኢትዮጲያ ናት፡፡ ያንብቡት! ከዚያ በገጽ 97 ላይ ሐያሲ በሚል የግጥም ስንኝ የግጥሙ ፍሰት ይቋጫል፡፡ በ 30 02- 2004፡፡ በገጽ 101 መውጫ ወዳሻችሁ በሚል ርዕስ የተጻፈን ደብዳቤ ከምጠብቀው በላይ በእያንዳንዱ መስመር እፈልጋት የነበረችውን የመድበሏን ዋና ገጸ-ባሕርይ ‹‹ምንም›› አጥብቂ እንድፈልግና ያቀረበበትን የአፋልጉኝ ርዳታ በምልክተ ያስቀመጠበትን ‹‹ዘይቤ›› ከሚገባው በላይ ለመረዳትና ልጁንም በማድነቅ ምነው ፅሑፍ ባለለቀ አስብሎኛል፡፡ እነዚህ 4 ገጾች የጸሐፊውን ልዩ ችሎታ ያሰዩ ሃሳቦች የተሰነቁበት ልዩ ክፍል ነው፡፡ በዚህ ዘመን የምንፈልገው ጸሐፊ ከራሱና ከፈጣሪው ጋር ተጣልቶ እኛንም የሚያጣላን፤ ውዥንብር ፍልስፍና ሳይኾን በብዙ መንገዶች በስነ-ጥበባዊ ወዝ እያዋዛ ራሳችንን፣ አገራችንን ፈጠሪያችንን ፈልገን ለለውጥው የምንነሳበት ሀሳብ የሚጠቁምን ነው፡፡ ጥበብ ከሰይፍ ከጦር የበለጠ ሀይል አላት ያልኩበት ምክንያትም ይህ ነው፡፡ ጸሐፊዎች- ገጣሚዎች ስነ-ጽሑፍ ሰዎች ከዚህች ስራ ብዙ ሊማሩ ይገባል፡፡ አንባቢያን ከዚህ መጽሐፍ ብዙ ነገር ትፈልጋላችሁ፡፡ እናትን ፈልጎ ለማግኘት ቢያንስ ወደ እውነት ፍለጋ መንገድ የምትመራ ድንቅ መጽሐፍ፡፡ ኤፍሬም ስዩም በእውነት ትችላለህ! የራስን ፍለጋ ጨርሰህ እርፍትህን ሽተህ ሌሎች እንዲፍልጉና እንዲያርፉ ለማድረግ መሞከርህ ያስመሰግንሃል፡፡ እውነትን እንድንይዝ እውቀትን ጥበብን እናገኝ ዘንድ ፈጣሪ ይርዳን፡፡ እናታችን ጠፍታለች ጭራሽ ደግሞ መገኛዋ ጠፍቶ ላትገኝ ስትዋትት ከማየት ፍለጋው ይጠንከር፡፡በማንም እጅ ስር ተይዛ ሲያሻቸው ሊጨብጧት ሲያሻቸው ሊገነጣጥሏት የሚሹ ሀይሎች አሉና ሁላችንም እንታደጋት፡፡ እናታችን ጠፍታለች፡፡ አፋልጉን ከጠፋች ልክ 38 አመቷ፡፡ © Tesfa Belayneh blogpost, May 12, 2013.
1 399
15
ፍቅር ከዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር፡፡ /የአለማችን ረዥሙ የግጥም መድበል/ በተስፋ በላይነህ የጥበብን ሃይል የምናውቀው የተደበቀን ምስጢር ወደ ገሃድ ማውጣቱ፤ የተሰወረን አዚም፤ የጠፋን መንገድ በማመላከት መስመር ማስያዝ መቻሉ፤ በጦር በሰይፍ እንኳ የቀረበን ፍርድ ለእውነትና ለእውቀት ወግኖ መገኘቱ ከዛም ለትውልድ ቅርስ ሆኖ መዘከሩ ነው፡፡ ምንም እንኳ ጥቂት ሃጥአን ብዙዎችን ነፍሳት የማጥፋት ሃይል ቢኖራቸውም፤ ጥቂት ወይንም አንድ እውነት አለምን እንደሚገዛም አይተናል፡፡ በዚህ እውነት ስር የሚወጡም በርካታ የጥበብ ስራዎች ብዙዎችን የመለወጥ ሃይል ሲኖራቸዋል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ብዙ ነገሮች ጠፍተውብን፤ መድረሻው ርቆብን፤ ማረፊያው በጠጠር ተደግፎ በአሜኬላ ታጥሮ፤ ፍጻሜው ታክቶን የምንንከራተት ስንቶቻችን ነን? ‹‹አፋልጉን›› በሚል ጩኸት የምናሰማ ብዙዎቻችን መሆናችንን ቤት ይቁጠረው፡፡ በዚህ የጩኸት ዓለም ውስጥ እውነትንና የጠራ እውቀትን ማግኘት ከባድ በሆነበት ዘመን እውነትና እውቀት የለችም ብሎ እጅን አጣጥፎ መቀመጥ ከሰውነት ተርታ የሚያስወጣን በመሆኑ መቼም ቢሆን ለእውነት መታገል ይኖርብናል፡፡ ‹‹አፋልጉን!›› እያሉ የመጮኽ ትግል :: አሜሪካኖች ለየት ያለ የሙዚቃ አቀንቃኝ ብቅ ካለች /ካለ/ በአለማችን አስገራሚዋ/ው የሙዚቃ አቀንቃኝ ብለው መጮኽ ያዘወትራሉ፡፡ ሌላኛውን ዓለም ሳያዩ ፣ ሳይወዳደሩ በአለም አንደኛ! ማለት ይወዳሉ:: ይህም ትልቁ የንግድ ሴራቸው ነው:: እኔም በእነርሱ ንግድ አለም ሥርዓት አይደል ያደኩት:: አዎ! በአለም ረዥሙ የግጥም ስንኝ በሚለው ጩኸት ርዕስ ስር የኤፍሬም ስዩምን ‹‹ፍቅር እዚህ በተፈለገ ብሎ ነበር›› የሚለውን የግጥም መደበል በአለም አንደኛ ረዥሙ የግጥም ስንኝ ለማለት ተገደድኩ፡፡ እውነት ነው በአለም ረዥም ግጥም ስንኝ ማነው ቢባል ማንም ይወራረደኝ ፍቅር ኢዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር የሚለው ግጥም ነው ኤፍሬም እነርሱ ባይጽፉትም ፤ አነርሱ ባያነቡትም እኔ ግን አንብቤ ፅፌዋለሁ ትችላልህ! ኤፍ፡፡ ኤፍሬም ስዩም “ሶሊያናን” የግጥም ሲዲ በ 1998 ሲያቀርብልን ለግጥም የስነ ጥበብ ዘርፍ ከፍተኛ ትርጉምና ዋጋ ያስጠበት ዓመት ነበር፡፡ ተፈጥሮ በለገሰችው ስልቅልቅ ጉሮሮ፤ ቅላፄ፣ ዐርምሞና ምሳጤ መሰረት የተለያዩ ሃሳቦችን በያዙ ግጥሞች ወደ ትልቅ ባህር ወደ ሚወሰዱ ዜማዎች ታጂቦ አስከመኮመን፡፡ ግጥምን ልክ አንደ ሙዚቃ ስራ ወስደን በቤተሰብ መሃል እያዳመጥን የምንወያይበትን መድረክ ከፈተልን፡፡ ግጥምን በድምፅ በማሰማት እነ ሎሬት ባለ ቅኔ ፀጋዬ ገ/ መድህን ፣ እና አበባው መላኩም ሞክረውልናል ታገልም ሊካተት ይችላል፡፡ ሌሎችም… መዚ ቃል ( የብርሃን ክንፎች) ለኤፍሬም ቀጣይ ስራው ነበር፡፡ በ 2004 ዓ/ም የለቀቀው ይኸው ስራ አሁንም ጥበብ የጋለ ብረቷን ለኩሳው በ 2005 ዓ/ም ‹‹ፍቅር እዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር›› በሚል ርዕስ ለየት ባለ አቀራረብ በሚስብ ይዞታ በሰማያዊ መደብ ሁለት ተበአትና እንስት የአዕዋፍ ፍጡራን በፍቅር ማዕድ ተቆላልፈው ተስለው በነጭ ቀለም ዳርቻ ስር ፍቅር እዚህ ቦታ ፈገግ ብሎ ነበር የሚለውን መድበል እንኳችሁ አለን ኤፍሬም:: የሸፉኑን ሥዕል አልፈን አንድ ገጽ ስናልፍ በጥቁርና ነጭ ቀለም የተጣለ የገጣሚውን ከደረት በላይ ምስል እናገኛለን፡፡ አንድ ፈላጊ የሚመስል አትኩሮ የሚያይህ ሰው ይመለከትሃል፡፡፡ በመጠኑም ቢኾን እንደ ግጥም ለማንበብ ለተወሰኑ ደቂቃዎች ይዘህ ልትቆይ ትችላለህ፡፡ ትገልጣለህ “ተበረከተ” ለሶልያና የሚል ጽሑፍ ታገኛለህ በሶልያና ፍቅር እንደተነካ በግልጽ ማየት ችያለሁ:: ፍቅር ደግ ነገር ነው! ከዛም ስትገልጥ ማውጫው ላይ በግጾች አምድ ስር ሀ፣ሐ፣ሠ፣ኀ እና አ በሚሉ ፊደላት ለየት ያሉ ሃሳቦችን እናያለን፡፡ በብዛት የለመድነው በሮማን ቁጥር ሊኸን ይችላል፡፡ በአሁኑ ወቅት የገጽ ዉጥሮችን በግዕዝ ቁጥር ማየት አልተለመደም፡፡ ይስማዕክ ወርቁ የቀንድ አውጣ ኑሮ የግጥም መድበል ላይ ገጾች በግዕዝ ቁጥር መፃፋቸውን አድንቄ ነበር፡፡ አሁን ደግሞ በፊደል ማየቴ ደስ አለኝ፡፡ ነገር ግን ሌሎች የግጥሞች ገጾች የቀረቡት በህንድ/አረብኛ ቁጥር በ1 2 3 ተጽፈዋል፡፡ በግዕዝቁጥር ቢጻፉ ኖሮ የመድበሉን ውበት በጣም ሊያሳምሩት እንደሚችሉ አሰብኩ፡፡ ትገልጣለህ የግጥሞቹ ማውጫ ያልቅና ባዶ ገጽ ታያለህ፡፡ በጣም የስነ-ጽሁፍ አድናቂ ፍልስፍናም ነካ የሚያደርገህ ኮኾነ ባዶ ገፁን ልታነበው ትችል ይኾናል፡፡ ባዶ መኾኑን ሳትገነዘብም ታልፍ ይኾናል ይሆናል፡፡ የምስጋናው ክፍል ይከተላል፡፡ ቤተሰቦችንም ለማመስገን ያቀረበውን ምክንያት በጣም ወድጃዋለሁ፡፡‹‹የእናንተን ለእናንተ መናገር ራሴን በራሴ ከማክበር እኩል ስለሚኾን በልብ ከልብ ለልብ›› ይላል፡፡ ለገፀ ሀ ደግሞ ከዛው ይህችን መድበል ሕይወት የዘራበትን ሰው ዘሚካኤልን ያመስግነዋል፡፡ እኔም በበኩሌ እጅጉን አመሰግኜዋለሁ፡፡ እንዲህ ሰው በጣፋበት ዘመን ስው ሲገኝ ያሰደንቃል፡፡ “ዘ” ብድራቱን የላይኛው ይከፍልህ፡፡ ከዛም ስንገልጥ በገጽ ሠ ላይ የምናገኘውን የዚህን መጽሐፍ ትልቁን ክፍል ነው:: ጠማረ አሚን የሚለውን እናገኛለን፡፡ ‹‹ሁላችንም የግላችን የሆነ sound truck አለን ያ sound track ያለፈ ጊዜያችን የአሁን ማንነታችን ነው፡፡ እያለ ሕይወትን በሙዚቃ እያዋዛ እያመሳሰለ የህይወታችን መሰረት የሆኑትን አሁን ቅድም ዛሬ ትላንት አምና ካቻምናን ያስቃኘናል:: ያለፈው ሕይወታችን በአሁንና በነገ ማንነታችን ላይ ያለውን ተጽዕኖ ምላሽም ያስቃኘናል:: አራተኛው አንቀጽ ላይም …ትናንሽ የሸክላ ጭረቶች የሙዚቃውን ጣዕም ይረብሹታል… ከሙዚቃ ሐዘንተኛ መንፈስ ይልቅ ባለዋቂ ጥፍሮች የተቧጨሩ የሸክላው ጀርባዎች…ዜማውን ያበላሹታል፡፡ አንድ ወዳጄ ውብ እኔነቱን ብዙ ምርጥ ዜማዎችን በማንነቱ ላይ እንደተሸከመ ራሱን በራሱ ለመስበር ሲሞክር ሞክሮም ተሰባብሮ ስብርባሪው ተለቅምና ታሸጎ ወደ ዘላለም ፀጥታ ሲጓዝ ተመልክቼአለሁ፡፡ በዚህም ከታላላቆች መስበር የታናናሾች ጭረት እንዲጎዳ አስተውያለሁ፡፡ የምትለውን አንቀጽ ውበቷ ጎልቶ ታይቶኛል፡፡ ቀሪውን ጦማረ አሚን /እውነተኛ-የታመነ ደብዳቤ/ ሃሳብና ይዞታ እስከ ገጽ ተ ድረስ ያንብቡ፡፡ ብዙ ይማራሉ፤ ብዙ ያስባሉ፤ ብሉ ይጠይቃሉ ይመራመራሉ፡፡ምናልባት ፀጥታ የሌለበት ስፍራ ወይንም ህሊናዎን ሰብሰብ አድርገው ካለነበቡት ምን ለማለት እንደፈተለገ ሊያገኙት ስለማይችሉ በትህትናና በትዕግስት ኢኒዱያነቡት እመክራለሁ፡፡ ይቀጥላል በ ኀ ገጽ ደግሞ ‹‹ዋዜማ›› በሚል ርዕስ ስር ከደመና ልትቀዳ ተራራውን ወጣች የሚል የመዝገቡ ተስማን አድባር ስዕል አስታወስኩት በማለት ህልሙን ይነገራናል …ህልም…ከዛም የዮፍትሄን ስለት ጠቅሶልን ህልሙን ለመፍታት ሊተረጉምልን ይተርክልናል፡፡ ‹‹ቅደመ ታሪክ›› የሚል ግጥም ይጀምራል፡፡ ያንብቡት! የግጥሙም የመጨረሻ ስንኝ እንዲህ ትላለችበ ግርጌው ላይ በ29 -02 2004 ተጻፈ ይላል፡፡
1 496
16
لا يوجد نص...
1 172
17
ከተምኔት ወደ ሳይንስ የሚለው ያ ሶሻሊስታዊ መፈክር በነገራቼን ላይ ብዙ መሣጭ ነገሮች ነበሩት። ለዛዘመን እመርታዎችም ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ ነበር። "ኢህቲአኔደር"፣ ወይም "እንደሰው በሜድር፣ እንደዓሣ በባህር" በሚሉ ርዕሶች ከሶቭየቶች ፕሮግረስ (ራዱጋን ነበር የማስታውሰው ሁሌ) የተተረጎመው ይህ መፅሐፍ በውስጤ የማይረሳ ትውስታንና መነሳሳትን ጥሎ ያለፈ፣ ሁሌም ደማቅ (vivid) ምስሎቹ አብረውኝ የሚኖሩ አስገራሚ ሳይንሳዊ ልብወለድ መፅሐፍ ነበር። የመፅሐፉን ፎቶ ለጥፈው፣ ይህን የቆየ ትውስታ ለመቆስቆስና ለወዳጆቼ ለማጋራት ያነሳሱኝን ሰብለ የመፅሐፍት ማከፋፈያ (የፌስቡክ ገፅ) አመሠግናለሁ። ትናንት ያነበቡ፣ አሸና ያሰቡ፣ ትናንታቸውን አልፈው ዛሬያችንን አሸጋግረው አይተውት ነበር። እናንብብ፣ እና ጊዜያችንን እንቅደመው! እንሻገረው። ሠርተንበት፣ ተሳስበን፣ አፍቅረንበት፣ ተደስተንበት፣ አቅማችንን አሟጠን ተጠቅመንበት፣ ረክተን፣ አበርክተን፣ ተካፍለን፣ አንብበን.... እንለፈው ዛሬያችንን። ቺርስ! © Assaf Hailu
1 715
18
ኢህቲአንደር — እንደ ሰው በምድር፣ እንደ ዓሣ በባህር ________ (ከደርግ ዘመን ምርጥ ሥጦታዎች አንዱ) ይሄን መፅሐፍ ከሰብለ መጽሐፍት አከፋፋይ የፌስቡክ ገፅ ላይ ሳገኘው ተደንቄያለሁ። የሃይስኩል ትዝታዎቼን ጎልጉሎ አመጣብኝ። 10ኛ ክፍል ላይ ነበር ያነበብኩት። አማን የሚባል የክፍሌ ተማሪና ጓደኛዬ የነበረ (10ኛ ስፔሻል ክላስ) ይህንን የኢህቲአንደርን ታሪክ በፊልም አይቶ ይሁን መፅሐፉን አንብቦ የሚገርም አድርጎ ተረከልኝ። መች አግኝቼ ባየሁት እያልኩ ውስጤ ቀረ። በኋላ አሁን ማን እንዳዋሰኝ ብረሳውም - ምናልባት ራሱ አማን ይሆናል - አገኘሁት መፅሐፉን። "እንደ ሰው በምድር እንደ ዓሣ በባህር"። ምናልባት ይሄ መፅሐፍ ሁለቴ ሳይተረጎም አይቀርም፣ ሁለቴ ሳላነበውም አልቀረሁም። "ኢህቲአንደር" በሚል ርዕስም ታትሟል። ደራሲው የሶቭየት ራሺያ ደራሲ አሌክሳንደር ቤላዬቭ ለዚህ መፅሐፉ የሰጠው ርዕስ በእንግሊዝኛ ሲተረጎም "Amphibian Man" የሚል ነበር። የተፃፈውም በ1928 እኤአ ነው። ወደ አማርኛ የተተረጎመበት መንገድ፣ ከርዕሶቹ ጀምሮ፣ ድንቅ ይመስለኛል። ቤላዬቭ ሳይንሳዊ ልብወለዶችን በመፃፍ በዓለም የታወቀ ቀደምት ደራሲ ነው። ከሌሎች መፅሐፎቹ መሐል "አየር ቸርቻሪው" የሚለውን መፅሐፉንም አግኝቼያለሁ። በተመሳሳይ ዘውግ በመፃፍ በዓለም ከታወቁት ከፈረንሳዊው ደራሲ ዡልስ ቨርን እና ከእንግሊዛዊው ኸርበርት ዌልስ ጋር ያነፃፅሩታል። እኔ ደሞ ከእንግሊዛዊቷ ጉደኛ የፍራንከንስታይን ሳይንሳዊ ሆረር ልብወለድ ደራሲ ከሜሪ ሼሊ ጋር አነፃፅረዋለሁ። ሜሪ ሼሊ በአጭር መቀጨቷና ምሥጢራዊ አሟሟቷ (ሰጥማ መገኘቷ) ሁሌ አንጀቴን ይበላዋልና አልረሳትም። ብዙውን የመፅሐፉን ታሪክ ረስቼዋለሁ። ግን በውስጤ የቀረና ለዘለዓለሙ የማይረሳኝ የሚመስለኝ ገፀባህርይ፣ ከራሱ ከኢህቲአንደር ቀጥሎ፣ አርጀንቲናዊው ቀዶጠጋኝ ሃኪምና ሳይንቲስት የሆነው ዶክተር ሳልቫቶር ነው። ዶክተር ሳልቫቶር ኢህቲአንደርን ይወልዳል። ልጁ ነው። ግን ህፃኑ ልጅ ህይወቱን ለአደጋ የሚያጋልጥ የመተንፈስ ችግር ያጋጥመዋል። እና ልጁን ከሞት ለማዳን ሲል በላብሯቶሩ አኔዱን እንስሳ ከሌላው ጋር እያዳቀለ ከሚመራመርባቸው ፍጡራን መካከል እጅግ ጠንካራ የሆነውን የሻርክ ሳንባ መርጦ ይገጥምለታል ለልጁ። Transplantation ሠራለት። ይሄ ድርሰት በተፃፈበት ጊዜ የሰው አካል ንቅለ-ተከላ ገና እውን አልሆነም ነበር። እና ልክ ከላይ እንደጠቀስኳቸውና እንደሌሎቹም (እንደነ አይዛክ አሲሞቭ)፣ መፅሐፍቱ ወይም የደራሲያኑ የማሰላሰል አቅም፣ የእውነተኛውን ዓለም ሳይንስና ቴክኖሎጂ ቀድሞ የተራመደ ነበር። ምናልባትም ይሄን የመሠሉ መፃህፍት ለተከታዮቹ የሰውልጅ ሳይንሳዊ እርምጃዎች፣ ጥንስሱን ሃሳብ አቀብለዋል። ኤች ጂ ዌልስ ስለ ኢንቪዚቢሊቲ ሲፅፍ የዛሬ ዘመኖቹ ስቲልዝ ፋይተር ጄቶችናሌሎች እልፍ ቴክኖሎጂዎች አልታሰቡም። ዡልስ ምድርን በ80 ቀን ውስጥ ሳያቋርጡ ስለመሽከርከር አድቬንቸር ሲፅፍ፣ ገና እነዚያን የደደራሲውን ህልሞች እውን ሊያደርጉ የሚችሉ የአቪዬሽንም ሆነ የሌላ ትራንስፖርት ዘዴዎች ገና እንጭጭ ነበሩ። አልተፈጠሩም ነበር። ይህም ኢህቲአንደር መፅሐፍ የጀነቲክ ኢንጂነሪንግንና መሰል ባዮቴክ ሳይንሶችንና ግኝቶችን የቀደመ ነው። ማሰብ ከሳይንስ እንደሚቀድም፣ መፅሐፍትም ከጊዜ አፈናጥረው ወደ ወደፊቱ ዘመን የሚያሻግሩ እጅግ ኃይለኛ የአዕምሮ ትጥቆች መሆናቸውን በዚህ መፅሐፍና በሌሎቹም መረዳት ይቻላል። ኢህቲአንደር እንደ ሰው በምድር ላይ ኖርማል ሰው መስሎ ይኖራል። ግን ደሞ የሻርክ ሳምባ ስለተገጠመለት እና እንደ ዓሦች የመተንፈሻ ስንጥብ ሥርዓተ አካልም ስለተሠራለት፣ ያሰኘውን ያህል ጊዜ በባህር ውስጥ እየዋኘ መቆየት ይችል ነበር። ከሰዎችም ተነጥሎ ወደ ባህር ፍቅሩ ያዘነብል ነበር። በመሐል አንዲቷን ምድራዊ ጉብል ያይና በፍቅሯ ይነደፋል። እሷም ትወደዋለች። ግን ምሥጢሩን መናገር ይኖርበታል። በዚህ ጭንቅ መሐል አንድ የከበሩ ማዕድናት ስግብግብ ነጋዴ የኢህቲአንደርን የተለየ ችሎታ ይደርስበትና ከባህር ወለል ላይ የከበሩ ኮራሎችን እንዲያወጣለት ሊያግባባውና ሊያስገድደው ይሞክራል። በዚህ መሐል የዶክተር ሳልቫቶር ምሥጢራዊ ላቦራቶሪ ምሥጢሯ ያፈተልካል። ሀገሩ ሁሉ በእንግዳ ዜናዎች ይታመሳል። በአርጀንቲናው ዶክተር ሳልቫቶር የምርምር ግቢ ውስጥ የእባብ አካልና የድመት ጭንቅላት፣ የወፍ ጭንቅላትና የጅብ አካል፣ የአንበሳ መዳፍና የአህያ ፊት የያዙ፣ የተዳቀሉ እንግዳ ፍጥረታት ይገኛሉ። ዶክተሩ ለፍርድ ይቀርባል። የሀገሩ ጳጳስ ሊመሠክሩበት ይቀርባሉ በችሎት። እና ፈጣሪ ለሁሉም የሚበጀውን ተፈጥሯዊ አካል ፈጥሮለት፣ መልካም እንደሆነም አይቶ፣ ባርኮ ነው ወደ ምድር ያመጣን፣ እና አንዱን እንስሳ ከሌላው ጋር ማዛነቅ ፈጣሪን ማስቆጣትና ከፈጣሪ ጋር መፎካከር ነው፣ ውጉዝ ከመ አርዮስ ነው ይላሉ!! ዶክተር ሳልቫቶር በመስቀለኛ ጥያቄ ጊዜ አንድ ጥያቄ ያቀርብላቸዋል ለጳጳሱ፦ "እርስዎ ባለፈው ትርፍ አንጀት በሆድዎ ውስጥ ወጥቶብዎት፣ ቆርጬ አውጥቼልዎት ከሞት አትርፌዎታለሁ አይደል?" ብሎ ይጠይቃቸዋል። በአዎንታ ይመልሳሉ። ከዚያ፣ የእርስዎን ነፍስ ለማትረፍ በእግዜሩ ሥራ ገብቼ አካልዎትን ስቆርጥና ስቀጥል እግዜር አይወደውም ብለው አልተቃወሙኝም ነበር፣ እንዲያውምጰበጣም ተደስተው መረቁኝ አይደለም? — በአዎንታ ይመልሳሉ። ታዲያ የእርስዎን ትርፍ አንጀት ቆርጦ ማውጣት እግዜር የፈጠረውን የሰው አካል መንካት አይደለም? ለእርስዎ ሲሆን ብቻ የተባረከ፣ ለሌሎች ሲሆን ደሞ የተኮነነ ይሆናል ማለት ነው ተመሳሳይ ድርጊት? የሰዎችን ህይወት የሚያተርፍ ከሆነስ በእንስሳት ቤንመራመርና አካላቸውን ብንዋስ ምን አለበት? ሁሉ ለሰው አልተሰጠውም? በምድሪቱ ሁሉ ላይ እንዲሰለጥን አልተሰጠውም የአዕምሮ ፀጋ ለሰውልጅ? ያዥጎደጉድባቸዋል ጥያቄውን። ጳጳሱ ከንፈራቸው ይንቀጠቀጣል። በእፍረት ፊታቸው ይቀላል። ችሎት የተሰበሰበው ሰው ዶክተሩን ይደግፋል። በመጨረሻም ያሸንፋል መሠለኝ አርጀንቲናዊው ዶክተር ሳልቫቶር። ግን ሳይንሳዊ ላብራቶሪው ይወረስበትና ይዘጋበታል። የተለየ ፍጡራኑም ይጠፋሉ። የሰውን ልጅ ዘር ከሻርክ ሳንባና ስንጥብ ጋር ብትደቅለውም፣ ከመላዕክት ክንፍ ብትሠራውም፣ ከኔፊሊምስ ጋር ብታራክበውም፣ አሊያም የአህያ ሆድ ብታሸክመውም፣ የሰውልጅ የሰውነቅንጣት እውስጡ እስካለ ድረስ፣ የማፍቀር ፀጋው ከውስጡ አይጠፋም የሚል መልዕክቱን ሊያስተላልፍልን የፈለገ ይመስላል የኢህቲአንደር ደራሲ። በተጨማሪም በሰዎች ተፈጥሮ ውስጥ ያደረውን የስግብግብነት፣ ትርፍን በማንኛውም ዋጋና መሥዋዕትነት የማሳደድ ሰዋዊ አባዜያችንን ልክ ካላበጀንለት፣ ወደ ምዓይነት ትራጀዲ እንደሚጨምረንም ሊያሳይ ሞክሯል ደራሲው። ያው በ1928 እኤአ በሶቭየት ራሺያ ሳይኔቲፊክ ሶሻሊዝምን እንገነባለን ተብሎ ሸብ ረብ የሚባልበት የርዕዮተዓለሞች ዘመን ስለነበረ፣ እና ደራሲውም በሶቭየት ያለ ደራሲ ስለሆነ፣ ... ርዕዮተዓለማዊ መልዕክቶችም አይጠፉትም መፅሐፉ። ወደፊት ለሰውልጅ የጋራ ጥቅም እንዲውል አድርገን፣ ባህላዊና ኃይማኖታዊ ኩነኔዎችን ተሻግረን፣ ሳይንስን ብናዳብር፣ ተፈጥሮን በቁጥጥራችን ሥር ማዋል አይሳነንም፣ ... ሁሉ በእጃችን ነው፣ ሰውን ሰው ያደረገው ሥራና መተሳሰብ ነው፣ ሶሻሊስታዊ ቁስአካላዊነት ስግብግቡን ካፒታሊዝም ያሸንፋል፣ ወዘተ. የሚሉ መፈክሮችንም በውስጡ አንግቧል።
1 594
19
لا يوجد نص...
1 303
20
ወንጌላዊ ኦኔስሞስ ነሲብና ዳግማዊ ምኒልክ፣ (ፕሮፌሰር ባህሩ ዘውዴ በእንግሊዝኛ እንደጻፉት፣ ሲሣይ ተፈራ መኮንን ወደ አማርኛ እንደተረጎመው) እንደ ልጅ ልጃቸው አቶ ኢዶሳ ገመቺስ ከሆነ ኦኔስሞስ ነሲብ የተወለዱት በኢሉባቦር ሁርሙ በሚባለው አካባቢ ሲሆን ዘመኑም 1842 ዓ.ም ነው፡፡ የኦኔስሞስ ነሲብ የልጅነት ስማቸው ሂካ ሲሆን ሂካ ማለትም በኦሮምኛ ፈቺው ወይም ተርጓሚው እንደማለት ነው፡፡ ወላጆቻቸው እንደትንቢት ሂቃ ብለው የሰየሟቸው ኦኔስመስ፣ ልክ እንደስማቸው የመጀመሪያውን የመጽሀፍ ቅዱስ የኦሮሚኛ ትርጉም በማዘጋጀታቸው ታረክ ሲያስታውሳቸው ይኖራል፡፡ የሂካ የልጅነት ጊዜ አሳዛኝ ነበር፡፡ አባታቸው በ4 አመት እድሜያቸው እንደሞቱ ሂካ በባሪያ ፈንጋዮች ታፍነው ተወሰዱ፡፡ ጠረፍ እስከሚደርሱ ድረስም በተለያዩ ጌቶች ስር በባርነት አድረዋል፡፡ አንዳንዶች ሂካ ነጻ ከመውጣታቸው በፊት 4 ጊዜ በባርነት እንደተሸጡ ሲጽፉ ሌሎች ደግሞ የተሸጡበትን ጊዜ 8 ያደርሱታል፡፡ በመጨረሻም ምጽዋ ላይ በነበረው የፈረንሳይ ቆንሲል ዌርነር ሙዚንገር አማካኝነት ሂካ ከባርነት ነጻ ወጥተዋል፡፡ ዌርነር ሙዚንገር በጥቅምት ወር 1863 ዓ.ም ከባርነት ነጻ የወጡትን ሂካ ለስዊድናውያን ሚሲዮኖች ያስረከቡ ሲሆን የሂካም ህይወት ከዚህ ጊዜ ጀምሮ በዘላቂነት መለወጥ ጀመረ፡፡ በመጋቢት ወር 1864 ዓ.ም የፋሲካ ቀን ዋና ጠባቂ ሆነው በተመደቡላቸው ሉንድሃል አማካኝነት ሂካ ኦኔስሞስ በሚል አዲስ ስም እንዲጠመቁ ተደረገ፡፡ ኦኔስሞስ ነሲብ በ1868 ዓ.ም ወደ ስዊድን የተላኩ ሲሆን በዛም ለ5 አመት ያህል ሃይማኖታዊ ትምርት ተከታትለዋል፡፡ ከስዊድን እንደተመለሱም የአጼ ቴዎድሮስ የቀድሞ ጸሀፊና የስዊድን ሚሽን ት/ቤት መምህር የነበሩትን የጎጃሙን አለቃ ኃይሉ ልጅ ምህረት ሐይሉን አገቡ፡፡ ከዚህ በኋላም ከንቲባ ገብሩ አቅደው ከፍጻሜ ያላደረሱትን መጽሀፍ ቅዱስን ለኦሮሞ ህዝብ የማስተማር እቅድ በትውልድ አካባቢያቸው ለመፈጸም ሂካ ወደዛው ለመጓዝ ወሰኑ፡፡ ነገር ግን አጼ ዮሀንስ የሚሲዮናውያንን እንቅስቃሴ አግደው ስለነበር፣ ኦኔስሞስ ወደ ወለጋ ለመጓዝ በቅድሚያ በቀይ ባህር ቀዝፈው ሱአኪን ወደምትባለው የሱዳን ወደብ መጓዝ ነበረባቸው፡፡ ከሱዳን ግዛት ወደ በርበር ካቋረጡ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ ጠረፍ ወደ ሚያደርሰው አባይ በመጓዝ በታህሳስ ወር 1875 ዓ.ም ፋማካ ተብላ ወደምትጠራው የጠረፍ ከተማ ደረሱ፡፡ ነገር ግን ወደ ኢትዮጵያ ጠረፍ ማቋረጥ ከጀመሩ በኋላ ችግር እንዳለ በመስማታቸው ለመመለስ ተገደዱ፡፡ የመጀመሪያው ሙከራ ከከሸፈ ከ3 አመት በኋላ በ1878 ዓ.ም ኦኔስሞስ በታጁራና ሸዋ አድርገው ወደ ትውልድ አካባቢያቸው ለመጓዝ ያደረጉት ጥረትም ንጉሥ ምኒልክ አስቀድመው የሰጡትን ተስፋ በሚጻረር መልኩ የሸዋ ጳጳስ የነበሩት አቡነ ማቴዎስ ባሰሙት ተቃውሞ ምክንያት ውጤት አልባ ሆነ፡፡ በትውልድ አካባቢያቸው በአካል በመገኘት የወንጌልን ት/ት ለማስፋፋት በተደጋጋሚ ያደረጉት ጥረት ባለመሳካቱ ያዘኑት ኦኔስሞስ ነሲብ መጽሀፍ ቅዱስን የትውልድ አካባቢያቸው ህዝብ በሚገባው የኦሮምኛ ቋንቋ ለመተርጎም ወሰኑ፡፡ የ4 አመት ህጻን ሆኖ የትውልድ አካባቢውን ለለቀቀ ሰው መጽሀፍ ቅዱስን ወደ ኦሮምኛ መተርጎም ቀላል ባይሆንም፣ ኦኔስሞስ አስቴር ጋኖ በተባሉ የሊሙ ኦሮሞ ወዳጃቸው እየታገዙ የትርጉም ስራቸውን ቀጠሉ፡፡ በመጨረሻም ኦኔስሞስ አዲስ ኪዳንን እና ብሉይ ኪዳንን በቅደም ተከተል በ1885 ዓ.ም እና በ1891 ዓ.ም ወደ ኦሮምኛ በመተርጎም የትርጉም ስራቸውን አጠናቀቁ፡፡ የትርጉም ስራቸውን ለማከናወን በዋነኛነት የተጠቀሙት የአማርኛውን መጽሀፍ ቅዱስ ሲሆን በስዊድን ቋንቋ የተዘጋጀውን መጽሀፍ ቅዱስ ደግሞ ለማመሳከሪያነት ተጠቅመዋል፡፡ የመጀመሪያ ሚስታቸው ወ/ሮ ምህረት ከሞቱ ጥቂት አመታት በኋላ ኦኔስሞስ ሊዲያ ዲምቦ የተባሉትን የወለጋ ሲዮ አካባቢ ተወላጅ አገቡ፡፡ በአስመራ ከተማ ይገኙ ለነበሩ ወደ 500 የሚጠጉ የኦሮሞ ኮሚኒቲ አባላትም የወንጌል ትምህርትን ማስተማር ጀመሩ፡፡ ይህም የትውልድ አካባቢያቸውን ህዝብ በአካል በማስተማር ውጤታማ ስራ ከመስራታቸው በፊት በመፈጸሙ በጎ መንደርደሪያ ሆነላቸው፡፡ በ1885 ዓ.ም ኦኔስሞስ ሚስታቸውን፣ 3 ልጆቻቸውንና አዲስ ሰራተኞቻቸውን በመያዝ ከአስመራ ወደ አዲስ አበባ ተጓዙ፡፡ በአዲስ አበባም በከንቲባ ገብሩ አማካኝነት ኦኔስሞስ ከዳግማዊ ምኒልክና ከአቡነ ማታዎስ ጋር ተገናኙ፡፡ ኦኔስሞስም ለዳግማዊ ምኒልክ የተረጎሙትን የኦሮምኛ መጽሀፍ ቅዱስ ኮፒ በስጦታ አበረከቱ፡፡ በመጨረሻም ኦኔስሞስ በሚጓዙበት ሁሉ ድጋፍ እንዲደረግላቸው የሚያዘውን የዳግማዊ ምኒልክ ደብዳቤ ታጥቀው ወደ ወለጋ ተጓዙ፡፡ በወለጋ እንደደረሱም በደጃዝማች ገብረ እግዚአብሔር ሞሮዳ/ኩምሳ ሞሮዳ ከፍተኛ አቀባበል ተደረገላቸው፡፡ ኦኔስሞስ ለመጓዝ ያሰቡት ወደ ትውልድ አካባቢቸው ኢሉባቦር የነበረ ቢሆንም በዳግማዊ ምኒልክና በደጃዝማች ኩምሳ ሞረዳ በተደረላቸው የክብር አቀባበል ምክንያት ወንጌላዊ ስራቸውን በወለጋ ጀመሩ፡፡ ነጆ አካባቢ በምትገኘው ቦጂ ለኦኔስሞስ መሬት የተሰጣቸው ሲሆን በዛም የማስተማር ስራቸውን ጀመሩ፡፡ የኦኔስሞስን ሃይማኖታዊ ትምህርት በአደጋነት የተመለከቱ የኦርቶዶክስ አባቶች ባቀረቡት ክስ ምክንያት ኦኔስሞስ ወደ አዲስ አበባ ከተጠሩ በኋላ በአቡነ ማቴዎስ የእስራት ፍርድ ተፈረደባቸው፡፡ ነገር ግን ዳግማዊ ምኒልክ የአቡኑን ፍርድ ባለመቀበል ጉዳዩ በድጋሚ በአፈ ንጉሥ ኢስጢፋኖስ እንዲመረመር አዘዙ፡፡ በዚሁ መሰረት አፈ ንጉሡ ጉዳዩን በድጋሚ መርምረው ኦኔስሞስን ከቀረበባቸው ክስ በነጻ አሰናበቱ፡፡ ዳግማዊ ምኒልክ ከዚህም አልፈው ለኦኔስሞስ በንግድ ሚኒስቴር ስራ እንዲሰጣቸው አዘው የነበረ ቢሆንም፣ በወቅቱ የነበሩት ሹማምንት ኦኔስሞስ በንግድ ጉዳይ ለመስራት የሚያስችል እውቀትና ክህሎት የላቸውም በሚል የምኒልክን ትዕዛዝ ሳይፈጽሙ ቀርተዋል፡፡ ኦኔስሞስ ነሲብ ወደ ወለጋ ተመልሰው በተለይም ከልጅ ኢያሱ ዘመን ጀምሮ በነጻነት ሲያስተምሩ ከቆዩ በኋላ በሰኔ ወር 1923 ዓ.ም በድንገት ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል፡፡ ነፍስ ይማር! ምንጭ፣ Pioneers of Change in Ethiopia: The Reformist Intellectuals of the Early 20th Century, Prof Bahru Zewde, PP.46-49 ምስል፦ ኦኔስሞስ ነሲብ ከባለቤታቸውና ከልጆቻቸው ጋራ ኤርትራ ውስጥ የተነሱት ፎቶግራፍ ነው፡፡ ፎቶው የመቼ እንደሆነ አልተገለጸም። © Jemal Abdulaziz
2 195