ar
Feedback
ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

الذهاب إلى القناة على Telegram

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

تُعد قناة ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖 (@bookshelf13) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 18 416 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 933 في فئة الكتب والمرتبة 1 878 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 18 416 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 04 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -98، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 14.40‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 4.00‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 2 651 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 736 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 39.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 05 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الكتب.

18 416
المشتركون
-224 ساعات
-267 أيام
-9830 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
سبتمبر '26
سبتمبر '26
+4
في 0 قنوات
أغسطس '26
+28
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '26
+31
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '26
+12
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '26
+108
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+31
في 1 قنوات
Get PRO
مارس '26
+16
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+15
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+21
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+36
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+42
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+31
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+31
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+60
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+44
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+72
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+451
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+460
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+500
في 4 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+317
في 2 قنوات
Get PRO
يناير '25
+421
في 1 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+481
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+275
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+244
في 1 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+254
في 2 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+307
في 2 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+388
في 1 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+231
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+241
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+354
في 3 قنوات
Get PRO
مارس '24
+325
في 2 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+251
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '24
+96
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+184
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+141
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+96
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+46
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+119
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+158
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+143
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+79
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+59
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+62
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+182
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+195
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+468
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+92
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+399
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+71
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+91
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+205
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+198
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+317
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+718
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+177
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+356
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+36
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+213
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+243
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+908
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+917
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+873
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+219
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+59
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+125
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+430
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+396
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+304
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+354
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+14 056
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
05 سبتمبر+1
04 سبتمبر+2
03 سبتمبر0
02 سبتمبر0
01 سبتمبر+1
منشورات القناة
የሰው ልጅ ሞትን የሚፈራ ይመስላችኋል? እኔ አይመስለኝም! በርግጥ ሞት የሚያስፈራ ነገር ነው። ግን ሞትን ብቻውን አንፈራውም። ከሞት ወዲያ ያለውን መረሳትን ነው የምንፈራው፡፡ እዚህ ጋር የሄኖክ በቀለ ለማ “ሀገር ያጣ ሞት” መፅሐፍ ውስጥ ያለ ‘ተስፋ’ የተባለ አንድ ሚስኪን ገፀ ባሕርይ ትዝ አለኝ፡፡ ‘ተስፋ’ እንዲህ ይላል… «ሞትን እፈራዋለሁ? አ! አ! ይልቅ መረሳትን ነው የምፈራው፡፡ ነገ ውስጥ ዕድል ፈንታ ማጣትን ነው የምፈራው፡፡ ነገ የማልተነፍሰው አየር ይነፍሳል፤ ነገ አበጀህ የማልለው፤ አጠፋህ የማልለው ንጉሥ ይነግሣል፡፡ ነገ የማልጠለለው ዝናብ ይዘንባል፤ ነገ የማልሰማው ወሬ ሀገሩን ያዳርሳል፡፡ የምፈራው ይህንን ነው፡፡ የምፈራው መብነን ነው፡፡ ነገ ተስፋ ማን እንደሆነ ትርጉም የማይሰጥበት ጊዜ ይመጣል፡፡ የምፈራው እርሱን ነው፡፡» በቃ ይኼው ነው፡፡ በዚች ምድር አንድ ሰው በሠራው ሥራ እንደሚታወስ እርግጠኛ ከሆነ ሞትን ለምን ብሎ ነው የሚፈራው? አሁን ሻለቃ አትሌት ኃይሌ ገ/ሥላሴ ሞትን የሚፈራ ይመስላችኋል? አስቴር አወቀስ? እኔን'ጃ! እኔ አይመስለኝም፡፡ ምክንያቱም ነገ የሚታወሱበትን ሥራ ባላቸው ጊዜ ሠርተዋልና ነው፡፡ አጋፋሪ እንደሻው ሞትን የሚፈሩትና የሚሸሹት ለመታወስ የሚያበቃቸውን ሥራ ስላልሠሩ ይመስለኛል፡፡ አገር እያሳበሩ ምድርን በዱካቸው ከሚያዳርሱ… ምናለ በሰዎች አእምሮ ውስጥ ትውስታቸውን ለማኖር ቢኳትኑ!? ቀላሉ መንገድ ይሄ ነበር፡፡ ምክንያቱም ሞትን ሸሽተን አናመልጠውምና፡፡ ሕይወት አጭር ናት፤ በእጃችን እንዳለ አረፋ አልያም ቀና ብለን ሰማይ ላይ እንደምናየው ጉም፡፡ ሰዎች ካለፉ በኋላ በክፉም በደጉም ይታወሳሉ፡፡ ሁሉም ሰው በተመሳሳይ መንገድ አይታወስም፡፡ እነ ሂትለርን፣ ጆሴፍ ስታሊንን፣ ኤዲ አሚንን ዛሬም እናስታውሳቸዋለን፤ ግን ጥሩ ባልሆነ መልኩ ነው፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ማንዴላን፣ ጋንዲን፣ ካትሪን ሀምሊንን፣ ማዘር ትሬዛን…. ወ.ዘ.ተ ምድር ለይ ሠርተዉት በሄዱት መልካም ሥራ እናስታውሳቸዋለን፡፡ Herostratus የተባለ ሰው ‘Madman’ ብለው ይጠሩታል ፈረንጆቹ፤ የታላቁ እስክንድርን መወለድ እና የአማልክቱን መዘገናጋት ተጠቅሞ ከሰባቱ የዓለም ድንቅ ቅርሳ ቅርስ መካከል የሚቆጠረውን ‘Temple of artemesium’ (የአርጤምሲስን ቤተ መቅደስ) ጣርያ በእሳት አያይዞ ያቃጠለው በታሪክ ስሙ እንዲታወስ ስለፈለገ ብቻ እንደሆነ ይነገራል። በዚህም ምክንያት ‘Herastratus’ የሚለው ቃል በመዝገበ ቃላት ውስጥ ራሱን በየትኛውም ዓይነት መንገድ ተጠቅሞ ዝነኛ እና የሚታወስ ሰው ለማድረግ ለሚጥር ሰው የተሰጠ ገላጭ ሆኖ የእንግሊዘኛ ቋንቋ ውስጥ ገብቷል። ይህ ሰው ተሳክቶለት ዘመን አልፎ እኛም በዚህ ሰበብ የምናስታውሰው ሆነናል። አንድ ነገር ግን ልብ በሉ! እንደነ ‘Herostratus’ በክፉ ነገር ከመታወስ መረሳት ይሻላል ባይ ነኝ፡፡ ሰው በመልካም ነገር መታወስ ሲችል ነው ያልባከነ ሕይወት ኖሮ አለፈ የሚባለው፡፡ ◉ ወደ ተነሳሁበት ፊልም ልመልሳችሁ፤ ሄክቶር ‘Remember Me’ የሚለውን ሙዚቃ የፃፈው ለልጁ "coco" ነበር፡፡ ምክንያቱም በ ራቅ ወዳለ ቦታ ሊሄድ ስለነበር፡፡ coco በዛ ሰዓት ህጻን ነበረች፡፡ ዝም ብሎ መሄድ ይችል ነበር፡፡ ግን እንዴት ብሎ? የሰው ልጅ አይደል? የሆነ ነገር ሳይጥል ርቆ መሄድ አይችልም፡፡ እንድታስታወሰው ስለፈለገ ‘Remember Me’ን ደርሶ ዘፈነላት፡፡ ከዛ ግን አልተመለሰም ነበር፡፡ ልጁ coco አባቷን የምታስታውሰው ሌላ በምንም አልነረም፤ በሙዚቃው ነው፤ በሰራው ስራ፡፡ የመጨረሻውን Final death ያመለጠውም በህይወት እያለ መታወሻ እንዲሆነኝ ብሎ በሰራው ስራ ነው፡፡ ይሄው ነው፡፡ ለሰው ልጅ የዛሬ ስራው ለነገ ቤዛው ነው፡፡ ዝም ብሎ እንዲሄድ አልተፈቀደለትም፡፡ እርሱም አይችልም፡፡ እና ምን ለማለት ፈልጌ ነው? REMEMBER ME. ▭▭ NB: ከመዲና መፅሔት ተሻሽሎና ተመጥኖ የተወሰደና ዳግም የተለጠፈ © Mes Oud

2
◉ ከመረሳት ወዲያ... [REMEMBER ME] “የሰው ልጅ ለምን የተወለደበትን ቀን ብቻ ያከብራል? የሞተበትስ ለምን አይከበርም?” ብለው ሚክሲኳዊያን “dia de los muertos” የሙታን ቀንን (Day of the dead) ያከብራሉ፡፡ በዓለም ላይ የማጂላንን ዱካ ተከትላችሁ ብታስሱ ከሜክሲኮ ውጭ የሙታንን ቀን የሚያከብር አንድም ሀገር አታገኙም፡፡ ታዲያ ይሄ ገራሚ ባህል ለአንድ ልዩ፣ አስደናቂና አይረሴ አኒሜሽን ፊልም መነሻ ሆኗል፡፡ COCO. የፊልሙን ታሪክ በአጭሩ ላወራበት ካሰብኩት ጉዳይ ጋር አስተሳስሬ ሳቀርበው እንዲህ ነው…ፊልሙ ላይ ሰዎች ከሞቱ በኋላ የሚሄዱበት ዓለም አለ፤ "Land of dead" ይባላል፡፡ ሕያዋን የሚኖሩበት ደግሞ "Land of living" ይሰኛል፡፡ ሟቾች የሚሄዱበት 'Land of dead' የሚባለው ቦታ ድጋሚ ሳይሞቱ፣ አፅማቸው ሳይፈርስ፤ ሉሲን ወይም አርዲን መስለው የሚኖሩበት ቦታ ነው፡፡ ታዲያ እኒህ ሕያዋን አፅሞች የሚኖሩት በምድር ላይ እነርሱን የሚያስታውሳቸው ሰው አስካለ ድረስ ብቻ ነው፡፡ ፊልሙ ላይ አንድ የሚያሳዝን ሄክቶር የሚባል ገጸ ባሕርይ አለ፡፡ 'በጨው ደንደስ በርበሬ ተወደስ' የሚሉት ብሂል ደርሶበት መታወሻ ምግባር ሳያንሰው - ተዘንግቶ… ተረስቶ የመጨረሻውን ሞት ሊሞት ጫፍ የደረሰ … ህላዌው በአንድ ሰው ማስታወስ ብቻ ተንጠልጥላ የቀረች… ላለመረሳትና ለመታወስ ሲባዝን የምናየው ምስኪን ፍጡር፡፡ ምስኪኑ ሄክቶር ስለገጠመው እጣ ፈንታ እንዲህ ይላል... “When there’s no one left in the living world who remembers you , you disappear from this world. we call it the final death.” አዎ! በሕይወት ያለ አንድም ሰው የሚያስታውስህ ካልሆነ የመጨረሻ ሞትን (final death) ጽዋ ትቀምሳለህ፡፡ ሄክቶርም የገጠመው ይሄ ነበር። መረሳት!!! ፊልሙ ላይ ዝነኛ የሆነች አንድ ዘፈን አለች። 'Remember Me' የምትል። የፊልሙን ሃሳብ የተሸከመች ናት፡፡ ሄክቶር ለልጁ የደረሳት የነፍስ ሙዚቃ፡፡ ሄክቶር ቀድሞ ይህ እጣ ፈንታ እንደሚገጥመው ሳይታወቀው አልቀረም፡፡ ➊ መረሳት - እውነትም የመጨረሻ ሞት በሰዎች Memory ውስጥ ቦታ ማጣት እውነትም የሞት ሞት ነው፡፡ ታዲያ ይህንን ሚስጥር ለሰው ልጅ ማን ሹክ ብሎት ነው? ልክ እንደፊልሙ ሁሉ ከሞት በኋላ ያለው ሕይወቱም እዚህ በቀሩት ሕያዋን ትውስታ ላይ ተንጠልጥሎ ይቀራል ብሎ ማነው የነገረው? እንጃ! ድርጊቱን ከታዘባችሁ ግን የሰማው አልያም የደረሰበት ሚስጥር እንዳለ የሚያሳብቅ ነው፡፡ የአደም ዘር እንደመረሳት የሚፈራው ነገር በዚህ ምድር ላይ የለም፡፡ እሩቅ ሳንሄድ ሰውን በተለያዩ አጋጣሚዎች 'አላስታወስኩህም!' ስትሉት እንዴት ነው የሚንጨረጨረው? መረሳትን ፍፁም አይፈልግምና ነው፡፡ የሰው ልጅ በዚች ዓለም የሚከውናት እያንዳንዷ ቅንጣት ተግባር መታወስን ዒላማ ያደረገች ናት፡፡ የዛሬ ልፋቱ ነገ በሰዎች አእምሮ ላይ የራሱን የትውስታ መስክ አጥሮ ይዞ ለመቦረቅ በማለም ነው፡፡ ቢችል በመላው ዓለም ካልሆነ ደግሞ በሚወዳቸው ሰዎች ዘንድ ብቻ ለመታወስ ይፍገመገማል፡፡ ታዲያ እንደመልኩ ሁሉ ለመታወስ የሚጥርበት መንገድም የተለያየ ነው፡፡ አባ ወራው ዛሬ በሚስቱ በኩል ያለውን ዋሻ የሚምሰው ከዘኪዮስ ያጠረችውን ሐሴት ለማጣጣም ብቻ አይደለም! ነገ የእርሱን ስም እንደባቡር ፉርጎ ከኋላቸው አስከትለው በዘመን ሀዲድ ላይ የሚነጉዱ መታወሻዎቹን ለማግኘት ነው፡፡ «ስም ከመቃብር በላይ ይውላል» ማለቱስ ሊዚህ አይደል? አንዴ አምባሰል አንዴ አንቺ ሆዬ እያለ በጉሮሮው ላይ ታች እያለ የሚንከለከለው ዘፋኝ ምን ከጅሎ ነው? ትንፋሹን ጆሯችን ላይ ሁ ብሎ ፈለጉን ሊያኖር… ከዚያም ባለ 3 መኝታ የተንጣለለ የትውስታ ጎጆ ከአእምሯችን ሊገዛ አስቦ ነው፡፡ 🎶 “በቁም ካፈቀርሽኝ ስሞት እንዳትረሽኝ” ብሎ ጨርሶታልኮ ጥሌ፡፡ አንገቱን ቀብሮ ወረቀቱን በእስክርቢቶው እያረሰ ዘሩን የሚዘራው ደራሲም ግቡ የጥበብ ሃራራውን ማስታገስ አልያም ውስጣዊ ሃሴትን መሸመት ብቻ አይመስለኝም፡፡ ስሙን በተነቀሱ የጥበብ ፍሬዎቹ ነገ ሊታወስ ፈልጎ ነው፡፡ ለሌላ አይደለም፡፡ ሰሞኑን አንብቤ የጨረስኩት አንድ መፅሐፍ አለ። በ ኧርነስት ቤከር የተፃፈው «The Denial of Death» ...እና በመፅሐፉ ሰውዬው “Immortality Project” የሚለው ነገር አለ። ቤከር እንደሚያስረዳው ሰው ሞትን ስለሚፈራና ገላው የምስጥ ፍሪዳ ሁኖ እንደሚጠፋ ስለሚያውቅ፣ በማህበረሰቡ ውስጥ፣ በሀገሩ...በኪነ ጥበብ፣ በልጆች ወይም በታላላቅ ሥራዎች ውስጥ ስሙና አሻራው እንዲኖር ይፍገመገማል፡፡ ልጅ ሲወልድ፣ በጎ ሲሰራ፣ ህንፃ ሲያቆም፣ ዝነኛ ሲሆን "የሰራሁት ነገር ከሞት በኋላም ይኖራል" በሚል ነው። ❷ መታወስን የማይፈልግ ይኖር ይሆን? እውን በዚች ምድር መታወስ የማይፈልግ ሰው ይኖር ይሆን? እኔንጃ። በምሳሌነት የሚቀርቡ ሰዎች አሉ በርግጥ። እንደፍራንዝ ካፍካ እና ፈርናንዶ ፔሽዋ ያሉ በሠሩት ሥራ መታወስ የማይፈልጉ ደራሲያን መኖራቸውን አልዘነጋሁም። ሁለቱም በሕይወት ዘመናቸው በስማቸው ያሳተሙት ነገር በብዛት ካለመኖሩም በተጨማሪ ሲሞቱም ጽሑፎቻቸው እንዲቃጠሉ ወይ እንዳይታተሙ ተናዝዘው የሞቱ ናቸው። ምንም እንኳ በኑዛዜ አስፈጻሚዎቹ መልካም ፈቃድ እና አለመታዘዝ ሥራዎቻቸው ለትውልድ ተርፎ ዘመን አልፈው ቢታወሱም። በተለይ ፈርናንዶ ፔሽዋ ለመታወስ ካለመፈለጉ የተነሳ ሲፅፍ ከመቶ በላይ የብዕር ስሞችን እና ማንነቶችን ይጠቀም ነበር። ልጨኛ ሥራውን 'The Book of Disquite'ን ይመለከቷል። ይሄን ታሪክ ስሰማ መጀመሪያ ገረሞኝ ነበር፡፡ “የመታወስን ፍላጎት በአዕምሮው ሸጉጦ ያላኖረ ሰብዕ እውን ይኖራልን?” ብዬ ትንሽ አሰሳ አደረግኩኝ፡፡ እናም ላለመታወስ ብሎ ለቁጥር በሚያታክቱ የብዕር ስሞች ሲፅፍ ኑሮ የሞተው ገጣሚ If, After I Die በተሰኘ ግጥሙ ልክ እንደ ማንኛውም ሰው መታወስን በሩቁ ሲታከክ እንደነበር አስተዋልኩ፡፡ If, after I die, they want to write my biography, There is nothing more simple. There are only two dates – the one of my birth and that of my death. Between the two every day things are mine. I’m pretty easy to define. I saw myself as a fool. I loved things without any sentimentality. I never had a desire that I couldn’t realise, because I never blinded myself. እኒህን ስንኞች ለማስረጃ ባቀርብ በቂ ይመስለኛል፡፡ አንዳንዴ እንዲህ ይሆናል፡፡ መታወስን እሸሻለሁ የሚልን ጀግና፣ ቀረብ ብላችሁ ብታጤኑት በስውር መታወስን ሲያባርር ልትይዙት ትችላላችሁ፡፡ በርካቶችም የዝና ማማ ላይ ተንጠላጥለው መሰቀል የሚፈልጉት ከማማው ላይ ሆነው ንፋስ ሊቀበሉ አስበው አይደለም፡፡ ይልቁንስ በበርካቶች ዘንድ ዘመናትን ተሻግሮ ለመታወስ ነው፡፡ ❸ ከሞት ወዲያ
916
3
+1
لا يوجد نص...
856
4
‹‹ባልሆንከው ከምትወደድ በሆንከው ብትጠላ ይሻላል!›› (Unity without uniformity) (እ.ብ.ይ.) ከሰው ጋር ለመመሳሰል ብሎ ያልሆነውን የሚሆን ብዙ ነው፡፡ በሌሎች ፊት አዲስ ዓመል የሚያሳይ፣ ሰው ሲያይ የሚለወጥ ሞልቷል፡፡ ያልነበረውንና የሌለውን ባህሪ ለሰው ሲል የሚያሳይ እልፍ ነው፡፡ ከሰው ጋር ለመኖር ተብሎ ያልሆንከውን መሆን ልክ አይደለም፡፡ መመሳሰል ማለት ራስን መካድ አይደለም፡፡ የራስህን ይዘህ ከሰው ጋር መቀላቀል ይቻላል፡፡ ሌሎች የሆኑትን መምሰል ግን እነሱን መሆን ነው፡፡ በሚያስማማህ፣ በሚያግባባህ፣ በምታምነውና በምትመራበት ፍልስፍና ውስጥ ሆነህ ከሰው ጋር ተስማምቶ መኖር ይቻላል፡፡ ማህበራዊ ህይወት ላይ ለመሳተፍ፣ የሌሎችን ተቀባይነት አገኛለሁ ብለህ ራስህን መተው የለብህም፡፡ ለሰው ብለህ የምታምነውን ክደህ፣ የምትመራበትን ፍልስፍና ችላ ብለህ፣ መገኘት በሌለብህ ቦታ የምትገኝ ከሆነ አንተ ራስህን ሳይሆን ሌሎችን ለመሆን እየባከንክ ነው፡፡ እስከነአቋምህ፣ እስከነእምነትህ፣ እስከነጉድለትህ፣ እስከነምናምንህ ራስህን ሆነህ ነው ከሰው ፊት መቆም ያለብህ፡፡ የሆንከውን አንተነትህን የማይቀበል ወዳጅም ይሁን ባልንጀራ ካጋጠመህ መንገዱን ጨርቅ ያድርግልህ ብለህ ቻው ማለት ነው፡፡ በሌሎች መስፈርትና ፍላጎት ራስህን አታባክን፤ ይሄ ለራስህ የምትውልለት ትልቅ ውለታ ነው፡፡ ይልቁንስ የእኔ የህይወት መንገድና መስፈርት ያዋጣል ወይ፣ ልክ ነው ወይ ብለህ ራስህን እየጠየቅክ አካሄድህን፣ ፍልስፍናህን፣ እምነትህን፣ አቋምህን እየፈተሽክ፤ ራስህን እያረምክና እያሻሻልክ ወፊት መገስገስ ነው፡፡ በመርህ ደረጃ በማትቀበለውና መሆን በማትፈልግበት ቦታ ለሰው ብለህ አትገኝ፡፡ ባልሆንከው ከምትወደድ በሆንከው ብትጠላ ይሻላልና (“It is better to be hated for what you are than to be loved for what you are not.”) አንድን ክፉ ልማድ ብዙ ሰዎች ደጋግመው ስለሚፈፅሙት ልክ ነው ማለት አይደለም፡፡ ምንም ነገር ቢሆን አስበህበት፣ አምነህበትና ፈትሸኸው ተቀበለው እንጂ ሌላ ሰው አይተህ አታድርገው፡፡ መፅሐፈ ሲራክ ምዕራፍ 6 ቁጥር 17 ላይ ‹‹ብዙ ናቸው ብለህ ከሐጢያተኞች ጋር አንድ አትሁን›› የሚለው ብዛት ጥራት አለመሆኑን ሲያስረዳ ነው፡፡ በኦሪት ዘጽአት ምዕራፍ 23 ቁጥር 2 ላይም ‹‹ክፉውን ለማድረግ ብዙ ሰዎችን አትከተል፤ ፍርድንም ለማጥመም ከብዙ ሰዎች ጋር ተስማምተህ አትመስክር (Do not follow the crowd in doing wrong.)›› ይላል፡፡ ንጉስ ዳዊትም በመዝሙሩ የመጀመሪያ ምዕራፍና ቁጥር ላይ ‹‹ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፤ በኃጢያተኞችም መንገድ ያልቆመ፤ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ›› ሲል ራሱን ከመንጋው የሚጠብቅን ሰው ያመሰግናል፡፡ ሰው ስለበዛበት ብቻ ብዙ ሰው የሚያደርገው ነገር ሁሉ ሁልጊዜ ልክ አይሆንም፡፡ ትክክልን ወይም ስህተትን በሰው ብዛት ሳይሆን ነገሩንና ሁኔታውን መርምረህ ለይ፡፡ እንደውም ሰው የበዛበት ነገር በጥርጣሬ የሚታይና ከስር መሠረቱ ሊጠና የሚገባ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ክፉ ስራንና አጉል ልማድን መሸሽ ሰውን መጥላት የሚመስላቸው አሉ፡፡ ከማይመችህ አጉል ልማድ መሸሽ፤ ከማታምንበት አስተሳሰብ መራቅ ራስን መጠበቂያ መንገድ ነው፡፡ ነገር ግን ሐጢያቱን መራቅ ሃጢያተኛውን መጥላት አይሆንም፡፡ ኩነኔውን መቃወም ሰሪውን ማውገዝ አይደለም፡፡ ሰሪው ሃጢያት በሰራበት ህይወቱ የፅድቅ ስራም ሊሰራበት አቅም አለው፡፡ ከሐጢያተኞች ሃጢያት እንጂ ከሰዎቹ አትሽሽ፡፡ በክፉ ስራቸው አትተባበራቸው እንጂ ከሰውነታቸው አትራቅ፡፡ ልትጠላው የሚገባው ክፉ ስራቸውን ነው፡፡ ሰው እንደሰው በደግም በክፉም ሊለዋወጥ ስለሚችል የምናወግዘውም ሆነ የምናደንቀው ስራውን ነው፡፡ ሃጢያተኛውን እንደሰው ውደድ ነገር ግን የሀጢያቱ ተከታይ ወይም ደጋፊ አትሁን፡፡ ዛሬ ሃጢያተኛ የሆነ ሰው ነገ ፃድቅ መሆን የሚችል አቅም እንዳለው ተረዳ፡፡ የዛሬ ፃድቁም የነገ ሃጢያተኛ ሊሆን ይችላል፡፡ ማንንም በዛሬው ሁኔታው ብቻ ጠቅልለህ እስከወደፊት ማንነቱ አትደምድም፡፡ የወደቀ ይነሳል፤ የተነሳ ይወድቃል፡፡ ከፍ ያለ ዝቅ የሚልበት፤ ዝቅ ያለ ከፍ የሚልበት ዓለም ውስጥ ነን ያለነው፡፡ ትናንት የት ይደርሳል የተባለ “መልካም ሰው” ሰይጥኖ አይተነዋል፡፡ ትናንት አይለወጥም ያልነው “ክፉ ሰው” ተለውጦ መልካም ዜጋ ሲሆን ተመልክተናል፡፡ አይደለም በሌላ ሰው በራስ እንኳን እርግጠኛ ሆኖ መናገር አይቻልም፡፡ ታዋቂዎች፣ አዋቂዎች፣ ዝነኞች፣ በህብረተሰቡ ዘንድ የተከበሩ ሰዎች የሚያደርጉት ነገር ሁሉ ልክ ላይሆን ይችላል፡፡ ተሞክሮ መውሰድ አሪፍ ነገር ነው፤ ልምድና እውቀት ካላቸው ሰዎች ሃሳብ መጋራት፤ እውቀት መካፈል ያለ ነው፡፡ ነገር ግን ስትከተላቸው መርምረህ ተከተላቸው፡፡ ብትችል ተከታይ አትሁን፤ ራስህን በራስህ ምራ፡፡ አርአያ የሚሆኑህን ሰዎች ፈትሸህ እወቅ፡፡ አዋቂነትም ይሁን ታዋቂነት የመልካም ሞራልና የጥሩ ስነምግባር ማረጋገጫ አይደለም፡፡ ስም ያላቸው፤ መልካም ስራ ግን የሌላቸው መዓት ናቸው፡፡ ብዙ ወረቀት የሰበሰቡ፤ ቅንነት ግን የጎደላቸው አይጠፉም፡፡ ህብረተሰቡ የሚያከብራቸው ነገር ግን በድብቅ ነውር የሚፈፅሙ አስመሳዮች ተቆጥረው አያልቁም፡፡ የማንነታቸው መጋረጃ ቢገለጥ ጉድ የሚሆኑ ብዙ አሉ፡፡ ውስጡን ለቄስ፣ ሰው መሳይ በሸንጎ የሆኑ የትየለሌ ናቸው፡፡ ማንም ንፁህ የለምና ከሰዎች የምትወስደውን ትምህርት አስተውለህ ምረጥ፡፡ ኦስካር ዋይልድ ‹‹የትኛውም ፃድቅ ትናንት አለው፤ የትኛውም ሃጢያተኛ ነገ አለው (“Every saint has a past, and every sinner has a future”)›› የሚለው የትኛውም ሰው ይብዛም ይነስም ደግም ክፉም ስራ እንዳለው ለማሳየት ነው፡፡ ስለሰው አንዲቷን ነገር ብቻ ዓይቶ አፍን ሞልቶ በርግጠኝነት መናገር ከባድ ነው፡፡ ዛሬ ጥሩ የሆነ ሰው ትናንት የወደቀበት ሐጢያት ሊኖረው ይችላል፡፡ ከስህተቱ ተምሮና ሃጢያቱ ዋጋ አስከፍሎት ዛሬ መልካም የሆነ ሰው ብዙ ነውና፡፡ ዛሬ ሐጢያተኛ ሆኖ የተገኘም እሱ ራሱ በራሱ ላይ እስካልፈረደ ድረስ ሃጢያተኛ ሆኖ ዘላለሙን እንዲኖር አልተፈረደበትም፡፡ የመቀየር፣ የመለወጥ፣ ንስሃ የመግባት፣ ራሱን የመግዛት፣ የበደለውን ይቅርታ የመጠየቅና ለራሱም ምህረት የማድረግ፣ እንዲሁም አዲስ ሰው የመሆን እድል አለው፡፡ ወዳጄ ሆይ…. በሰው ለመወደድ ብለህ የማይወደድ ስራ አትስራ፡፡ ትክክለኛ የሰው ፍቅር በታይታና በማስመሰል የሚገኝ አይደለም፡፡ ሰዎች የበዙበት ነገር ሁሉ ልክ ላይሆን ስለሚችል ነገሩን መርምር፡፡ ነውርን አውግዝ፤ ክፉ ስራን ጥላ፡፡ ለተበዳዩ ቁም፤ ፍትህ ላጣው ድምጽ ሁንለት፡፡ ሰውን በሰውነቱ ውደድ፡፡ ማንም ሲጎዳ ስታይ እዘንለት፡፡ ያዘነን ሰው ለማፅናናት፣ የተከፋን ሃዘኑን ለመካፈል ያንተ ወገን እስከሚሆን ብቻ አትጠብቅ፡፡ ሰው ሁሉ የሰው ወገን ነው፡፡ ከሰውነትህ በፊት ጎጥህን፣ ዘመድህን፣ ብሔርህን አታስቀድም፡፡ ጭካኔን ኮንን፣ ክፉ ስራን ተቃወም፤ ጨካኙን ግን እዘንለት፡፡ ሰው መሆንን ልመድ! ራስህን መሆን ተለማመድ፡፡ ሌሎችን በመምሰል ዕድሜህን አታባክን፡፡ ባልሆንከው ከምትወደድ በሆንከው ብትጠላ ይሻላልና! ቸር ጊዜ! ------------------------------------ © እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.) ሠኞ ነሐሴ ፳፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.
1 379
5
لا يوجد نص...
1 150
6
ስለሆነም በጥበብም ሆነ በሕይወት ውስጥ ውበት ከትርጉም ጋር አብሮ የሚነቃው ፈጽሞ ያልተነካ ...ያልተባለ አዲስ ነገርን ፍለጋ ከመባከን ሳይሆን፤ ያንኑ አሮጌውን የሰው ልጅ ሕይወት በራሳችን ምናብ ዳግም አዲስ አድርጎ ማቅረብ ሲቻል ነው። ​አሮጌው ታሪክ በሌላ ሰው ብዕር ሲቀርብ አዲስ ተአምር ሆኖ ይገለጣል፤ እውነተኛ ጥበበኛም አዲስ ነገር ፈጣሪ ሳይሆን ለጥንቱ ተፈጣሪ አዲስ ሩህ የሚዘራው ነው። ምን ትላላችሁ? © Mes Oud
1 362
7
◉ «አዲስ ነገር የለም ...ዳግም ልደት'ንጂ» ከዓመታት በፊት ተማሪ ሳለሁ ያየሁት አንድ ፊልም ነበር። Upside Down ይሰኛል። ዛሬ ድረስ አስታውሰዋለሁ። "እንዴት ያለ አዲስ ፈጠራ ነው?" ብዬ በወቅቱ ተደምሜበታለሁ። "ደራሲው እንዴት አሰበው? እንዴት እንደዚህ ያለ አዲስ ሀሳብ ሊፈጥር ቻለ?" ብዬ አስብ ነበር ለብዙ ግዜ። ኋላ ላይ ብዙ ነገር ስረዳ ያ የተደመምኩበት ስራ አዲስ የሚባል አልነበረም። እንደውም አሮጌ ነበር። ተደጋግሞ የተነገረን እኔም ደጋግሜ የሰማሁት ታሪክ ነበር። ምግቡ ሳይሆን የቀረበበት ትሪ ነበር አዲሱ። እንደውም ሀዲስ አለማየሁ የተባሉ የሀገሬ ደራሲ ከፃፉት "ፍቅር እስከመቃብር" ከተባለው ድርሰት ነጥዬ ማየት አልቻልኩም ነበር። እንዴት አላችሁ? ​➊ ፍቅር እስከ መቃብር ​ያው እንደምታውቁት በዛብህ የደሃ ገበሬ ልጅ ነው። የተሻለ እውቀት ሊቀስም ወደ ዲማ የተጓዘ፤ በዚያም የፊውዳሉ ባላባት የፊታውራሪ መሸሻ ልጅ የሆነችውን ሰብልወንጌልን አስተማሪነት እቤቷ ድረስ እየሄደ እንዲያስተምራት የተመደበ ሰው ነው። በዚህ አጋጣሚ በሁለቱ መካከል ጠጠር ያለ የፍቅር ስሜት ይፈጠራል። ​ነገር ግን በጊዜው በነበረው የፊውዳል ስርዓት፣ የባላባት ልጅ ከተራ ድሃ ጋር መጋባት ፈጽሞ የማይታሰብ ነበር። በዛብህ ፍቅሩን ማጣት ስላልቻለ ወዲህም የተቃጣበትን አደጋ ለመሸሽ ከአካባቢው ይኮበልላል...ከዛም ተንከራቶ ይሞታል። ሰብልዬም ቢሆን የወላጆቿን ፍላጎት ተቃውማ፣ ፍቅሯን ጠብቃ ለመኖር አለም በቃኝ ብላ ገዳም ትገባለች። ታሪኩ የሰው ልጅ ማህበራዊ መደብ ከእውነተኛ ፍቅር ጋር ሲጋጭ የሚያስከትለውን ስቃይ ያሳያል። ከብዙ በትንሹ። ❷ Upside Down ​የዚህ ፊልም ታሪክ የሚሰግረው ደግሞ Dual Gravity ባላቸው ሁለት ተቃራኒ ፕላኔቶች ላይ ነው። የመጀመሪያው Up Above ወይም የላይኛው ዓለም በመባል ይታወቃል። በሀብት የበለጸገ እና በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የተንበሻበሸ ነው። ሁለተኛው ደሞ Down Below ወይም ታችኛው አለም ይሰኛል። ድሃ፣ የወደመ እና የተበዘበዘ ዓለም ነው። የሁለቱ አለማት ህግ ፈጽሞ እንዳይገናኙ ያዝዛል። የታችኛው አለም ሰው ወደ ላይኛው አለም ቢሄድ በስስበት ሀይል ህግ ምክንያት አካሉ የመቃጠል አደጋ ያጋጥመዋል። ​Adam ከታችኛው ድሃ አለም የተወለደ ወጣት ሲሆን፣ Eden ደግሞ ከላይኛው ሀብታም አለም የወጣች ሴት ናት። ሁለቱ ገና በልጅነታቸው ሁለቱ አለማት በሚገናኙበት ተራራ ጫፍ ላይ ተገናኝተው በምስጢር ይፋቀራሉ። ነገር ግን የድንበር ጥበቃዎች ፍቅራቸውን ደርሰውበት ሲያሳድዷቸው ኤደን ተከስክሳ ትወድቃለች፤ አዳም ደግሞ ኤደን የሞተች ይመስለዋል። ​ከአመታት በኋላ አዳም ኤደን በህይወት መኖሯን እና «TransCorp» በሚባል ሁለቱን አለማት በሚያገናኝ ትልቅ ኩባንያ ውስጥ እንደምትሰራ ያውቃል። አዳም ከታችኛው አለም የተገኘን ልዩ ፈጠራ በመጠቀም የራሱን የሰውነት ስስበት በመቀየርና አደጋውን ተቋቁሞ ወደ ላይኛው አለም በመግባት ኤደንን ፍለጋ ይጓዛል። ታሪኩ የፊዚክስ ህግ በመጣስ አዳም ከኤደን ጋር ለመገናኘት የሚያደርገውን ተጋድሎ የሚያሳይ በሳይንስ-ልብወለድ ዘውግ የቀረበ ፊልም ነው። ◉ ሁለቱም ስራዎች የተገነቡት Forbidden Love ላይ ነው። ሀዲስ አለማየሁ በፍቅር እስከ መቃብር ውስጥ የሰዎችን የመደብ ልዩነት በታሪክ፣ በባህል እና በፊውዳላዊ አስተሳሰብ ገለጹት። የUpside Down ደራሲ ደግሞ አሁንም ድረስ በሰው ልጅ መካከል ያለውን የሀብታም እና የድሃ ወይም የበላይ እና የበታች ክፍፍልን ወስዶ በ Physical Metaphor ወደ ሁለት ተቃራኒ የስስበት ሀይል ወዳላቸው ፕላኔቶች ለወጠው። የማህበራዊ መደብ ልዩነቱን በሳይንስ ማዕድ ላይ ፈትፍቶ ወደ ተፈጥሮ ህግ ቀየረው። ​እዚህ ጋር ነው «በጥበብ ውስጥ አዲስ ነገር የለም፤ ነባሩን እንደ አዲስ መስራት እንጂ» የሚለው ታዋቂ ሀሳብ የሚገዛን። Forbidden Love በስነ-ጽሁፍ እና በፊልም ውስጥ በጣም ከተደጋገሙ ጭብጦች አንዱ ነው። በቅርቡ በ Pixar አኒሜሽን የተሰራውን Elemental ፊልም አይቼ ነበር። በተፈጥሮ ህግ ፈጽሞ የማይገናኙ እና የማይነካኩ ሁለት ንጥረ ነገሮች እሳት እና ውሃ ተፋቅረው ነው። «እሳት እና ውሃ መነካካት አይችሉም» የሚለውን የተፈጥሮ ህግ እና የልማድ አጥር በመጣስ ፍቅራቸውን ለማስቀጠል የሚያደርጉት ጥረትን ያሳያል። ልክ እንደ ሰብለና በዛብህ። የሼክስፒር Romeo and Juliet እና Titanicን የሚለያቸው ምንድነው? የብስና ባህር አይደለምን? ታዲያ አዲሱ ነገር ምንድንነው? ❸ «አዲስ ነገር የለም ...ዳግም ልደት'ንጂ» «በአስማት በትር ከአለመኖር ወደመኖር የሚመጣ ነገር የለም» በሚለው ሀሳብ ተጠምቄያለሁ። በፊት " አዲስ ፈጠራ አያልቅም" የምል ሰው ነበርኩ። «ዓለም ሰርክ አዲስ ሁና ሳለ ያልተባለ አዲስ ነገር ይኖራታልንጂ» ብዬ የማስብ። ኋላ ግን «በዱንያ ላይ ያልተባለ አዲስ ነገር መፍጠር የለም» ወደማለት ተቃረብኩ። ሁሉም አሮጌ ነው። ነገሮችን አዲስ የሚያስመስላቸው የቀረቡበት መንገድና የታዩበት የእይታ መነፅር ብቻ ነው። ጓደኛዬ በቅርቡ Habte Awalom የተባሉ ዘፋኝ በ 1978 የዘፈኑትን "እንደ ቢራቢሮ" የሚል ሸጋ ዘፈን ላከልኝ። ቴዲ በመጀመሪያ አልበሙ እንዳዲስ ዘፍኖታል። (ከመጀመሪያው አንፃር የቴዲ ብሽቅ ነው) እና ምናልኩ? ማንኛውም ጥበበኛ የቀደሙትን ትከሻ ተንተርሶ ነው የሚቆመው። ምናልባት habte awalom "እንደ ቢራቢሮ"ን በተዓምር አልከሰቱትም። የሆነ አዝማሪ ወይም አንድ እረኛ ሲያንጎራጉሩት ሰምተው ሊሆን ይችላል። በጥበብ ውስጥ መኮረጅ እና በተጽዕኖ መውደቅ ያሉ ናቸው። መጥፎው ኩረጃ የሌሎችን ቅርጽ እንዳለ መቅዳት ሲሆን፣ በጎው ተጽዕኖ ግን ነባሩን ሀሳብ ወስዶ የራስን ነፍስ ዘርቶበት እንደ አዲስ ማቅረብ ነው። ​◉ ባጭሩ በጥበብ አለም ጥሬ እቃው ያው አሮጌው የሰው ልጅ ህይወት ነው። አዲሱ ነገር ግን ያንን አሮጌ የምንቀርጽበት የራሳችን ምናብ፣ ፈጠራ እና ስሜት ነው። ግና «አዲስ ፈጠራ የለም» ሲባል የሰውን ልጅ የፈጠራ አቅም ዝቅ ለማድረግ አይደለም። የፈጠራን አኸላለቅ ለመረዳትንጂ። በጥበብ አለም ውስጥ ሙሉ በሙሉ ከምንም ተነስተን የምንፈጥረው አዲስ ነገር አለመኖሩን ለማመልከት ብቻ ነው። እንጂ ፈጠራ አለ። በሌላ ቋንቋ ፈጠራ ማለት ነባር ሀሳቦችን፣ ስሜቶችንና እውነታዎችን በራሳችን አዲስ መነፅር አጣጥሞ እንደገና የማቅረብ ጥበብ ነው። በጥበብ ዓለም የምናነሳቸው ጭብጦች በሙሉ የተደጋገሙ ናቸው። ስላላገኘናቸው፣ ስላልደረሱን ነውንጂ በሆነ ቦታና በሆነ ሰው ተብለዋል። ፍቅር፣ ሞት፣ አገር፣ ክህደት፣ ብቸኝነት... የህይወት ትርጉም ፍለጋ ....ከጥንት እስከ ዛሬ ተስተጋብተዋል። አዲስ ነገር የሚሆነው ጭብጡ ሳይሆን የጥበበኛው እይታ ነው። ​አሜሪካዊው ደራሲ Mark Twain "ፈጠራ ማለት የተበታተኑ ነባር ሀሳቦችን አጣጥሞ አዲስ ቅርጽ መስጠት ነው" ያለው ለዚህ መሰለኝ። ​«There is no such thing as a new idea. It is impossible. We simply take a lot of old ideas and put them into a sort of mental kaleidoscope. We give them a turn and they make new and curious combinations.» ​
1 426
8
+1
لا يوجد نص...
1 217
9
እስቲ ዛሬ ስለደበረኝ ላስደብራችሁ። የካርል ማርክስ የትርፍ ዋጋ (Surplus Value) ቲዎሪ በፎቶ ሳገኘው የገባኝን ያህል ላስረዳችሁ ወደድኩ። የካርል ማርክስ የትርፍ ዋጋ «Surplus Value» ቲዎሪ የካፒታሊዝም ትርፍ እንዴት ነው የመጣው የሚለውን ለማብራራት የቀረበ ሀሳብ ነው። ካርል ማርክስ እንዲህ የምትል አባባል አለችው፦«The worker creates the wealth, capital claims the profit» ምን ማለቱ መሰላችሁ ሰራተኛው ከሚከፈለው ደሞዝ በላይ ዋጋ ይፈጥራል፤ ያ ተጨማሪ ዋጋ ግን ለካፒታሊስቱ ነው ትርፍ የሚሆነው። በፎርሙላ ሲቀመጥ፦Surplus Value (s) = Total Value Created (v) − Wages (w) ይመስላል። በአጭሩ ሳስረዳችሁ፦ S= V−W S= የትርፍ ዋጋ (Surplus Value) V= ሰራተኛው የፈጠረው ጠቅላላ ዋጋ W= የተከፈለው ደሞዝ ይወክላል። ለምሳሌ አንድ ዳቦ ጋጋሪ በቀን 1000 ብር የሚያህል ዋጋ ይሰራል እንበል። ደሞዙ ግን 400 ብር ነው። S= 1000 − 400= 600 ብር ይመጣል። እዚህ ጋር ማርክስ ይህ 600 ብር ከየት መጣ አይልም። ይልቅስ ለምንስ ለካፒታሊስቱ ብቻ የሚገባ ዋጋ ሆነ ነው ጥያቄው። ይህን ጭዌ አልሰማችሁም። አንድ የኩባንያ ባለቤት አዲስ መኪና ገዝቶ ወደድርጅቱ ያቀናል። አዲሱን መኪና የተመለከተው ሰራተኛም በጉጉት አለቃውን ይጠይቀዋል፦«በጣም ምርጥ መኪና ነው የገዛኸው የምር አስቀናኸኝ» አለቃውም ፈገግ እንዳለ፦«አንተም አሁን ባለህበት አቋም ጠንከረ የምትሰራ ከሆነ ቀጣይ አመት ሌላ የተሻለ መኪና እቀይራለሁ!» 🤓 ማርክስ የሚለን ይሄንኑ ነው። ሰራተኛው ደሞዙን ለማግኘት ግማሽ ቀን ይሰራል፤ የቀረውን ግማሽ ቀን ደግሞ ለአለቃው ትርፍ ይሰራል። ሰራተኛው ጠንክሮ ይሰራል፤ አለቃው ጠንክሮ ትርፍ ይሰበስባል። ለምሳሌ አንድ ሰራተኛ በቀን 8 ሰዓት ይሰራል። በመጀመሪያው 4 ሰዓታት የቀኑን ደሞዝ 500 ብር ቢሰራ፤ በቀሪው 4 ሰዓት ደግሞ ሌላ 500 ብር ዋጋ መፍጠር ይጠበቅበታል። ነገር ግን የሚከፈለው 500 ብር ብቻ ነው። ያን ተጨማሪ 500 ብር ትርፍ ካላመጣ ቀጥታ ይባረራል። ስለዚህ የፈጠረው ጠቅላላ ዋጋ 1000 ብር ይሆናል። የሚያገኘው ደግሞ 500 ብር ነው። በመጨረሻም የትርፍ ዋጋ 500 ብር ይመጣል። ማርክስ ይህንን ነው «Surplus Value» የሚለው። ነገር ግን ማርክስ የሚያነሳው ጉዳይ የገንዘብ ብቻ አይደለም፤ በሥነ-ልቦናም ጭምር የሚፈተሽ ነው። ሰራተኛው ይህ ሥራ ከሌለው ገቢ እንደማይኖረው ያውቃል። ቤት ኪራይ፣ ምግብ፣ ቤተሰብ እና ዕለታዊ ወጪዎች ይጠብቁታል። ስለዚህ ሥራውን የማጣት ፍርሃት ብዙ ጊዜ የድርድር ኃይሉን ያዳክማል። በሌላ አነጋገር ሰራተኛው ስለደሞዝ ጥያቄ ካነሳ ስራውን የማጣት ስጋት ይጋረጥበታል። ይህን ፍርሃት የካፒታሊዝም ስርዓት እስከዛሬ እንዲቀጥል ካደረጉ ኃይሎች መካከል ነው። ምክንያቱም ሰራተኛው የተሻለ ክፍያ ቢፈልግም ሥራ አጥነትን ስለሚፈራ ያለውን ሁኔታ ለመቀበል ሊገደድ ይችላል። በዚህ ምክንያት ማርክስ የካፒታሊዝም ትርፍ surplus value «ያልተከፈለ የሰራተኛ ላብ» ነው ብሎ ያምናል። እዚህ ጋር ግን ካፒታሊስቶች መልስ አላጡም። መልሳቸውም ይሄ ነው። ባለካፒታሉ ገንዘብ አፍስሷል፣ የኪሳራ ስጋቱንም የሚሸከመውም እሱ ነው፣ ማሽኖችንና ቁሳቁሶችን የሚያቀርበውም እሱ ነው፣ ንግዱ ቢከስርም ኪሳራውን የሚሸከመው ለብቻው ነው፣ ስለዚህ ትርፉም ለካፒታሊስቱ የተገባ ነው። ብቻ የማርክስ «Surplus value» የትርፍ እሴት ቲዎሪ በኢኮኖሚክስ ውስጥ እስከዛሬ ድረስ ክርክር የሚያስነሳ ሃሳብ ሆኖ ቀጥሏል። ማርክስ የሚለው ባጭሩ የካፒታሊዝም ትርፍ የሚመጣው ሰራተኛው ከሚከፈለው በላይ ባፈሰሰው የላብ ዋጋ ነው፤ እና ይህ ሁኔታም በሰራተኛው የሥራ መልቀቅ ወይም የሥራ ማጣት ፍርሃት ላይ ጥገኛ ነው። እኔ ግን የካፒታሊስቶችን አስተሳሰብ ከግማሽ ፐርሰት በላይ እቀበለዋለሁ። በአጭሩ በምሳሌ እንግባባ ዘንድ ላስረዳችሁና ልሰናበት። «የዳቦው ዋጋ ለማን የተገባ ነው?» እስቲ በአይነ ህሊናችን አንድ ዳቦ ቤት እንሳል። የዳቦ ቤቱ ባለቤት ህንፃውን ተከራየ፣ ምድጃውን ገዛ፣ ዱቄቱን አመጣ፣ ንግድ ፈቃድም አወጣ። ይህ ሁሉ ወጪ እና ስጋት የባለቤቱ risky ነው። ከዚያ አንድ ዳቦ ጋጋሪ ቀጠረ። ይህም ሰራተኛ በቀን 100 ዳቦ ይጋግራል። እያንዳንዱ ዳቦ 20 ብር ቢሸጥ የቀኑ ገቢ 2000 ብር ይሆናል። ከ2000 ብሩ ውስጥ የዱቄት፣ የኤሌክትሪክ፣ የቤት ኪራይ እና ሌሎች ወጪዎች 1000 ብር ቢሆኑ 1000 ብር ይቀራል። ከዚያ የሰራተኛው ደሞዝ 400 ብር ቢሆን ቀሪው 600 ብር ለባለቤቱ ይሆናል። እዚህ ላይ ነው የካርል ማርክስ ጥያቄ የሚጀምረው፦«ያ 600 ብር ከየት መጣ?» እሱ ብቻ አይደለም ማርክስ የሚለን፦«ዳቦውን የጋገረው ሰራተኛው ነው። ዋጋውን የፈጠረውም እሱ ነው። የተከፈለው ግን 400 ብር ብቻ ነው፤ ቀሪው 600 ብር ግን የሰራተኛው ያልተከፈለ የላብ ዋጋ ነው።» ካፒታሊስቶች ግን ይህ ሃሳብ ውድቅ በማድረግ እንዲህ ይላሉ፦«ዳቦውን የጋገረው ሰራተኛው ቢሆንም ዳቦ ቤቱን የከፈተው፣ የፋይናንስ ስጋቱን የሚወስደው፣ ኪሳራ ቢመጣ እራሱ ሊሸከም የሚችለው ባለቤቱ ብቻ ነው።» እውነት ለመናገር ግን ከዚህ በላይ ውስብስብ ነው። ምክንያቱም ኢኮኖሚ በቁሳቁስ ብቻ አይገነባም፤ በአዕምሮም የተዋቀረ ሂደትም ጭምር ነው። አንድ ቀን ይህ ዳቦ ጋጋሪ በምሬት እንዲህ አለ፦«ይህን ሁሉ ዳቦ የምጋግረው እኔ ነኝ።» ባለቤቱም ፈገግ ብሎ መለሰለት፦«አዎ ነገር ግን ያለእኔ ምድጃ የት ትጋግረዋለህ?» ሰራተኛው እዚህ ጋር ዝምታ ብቻ ነው መልሱ። ይህ የኢኮኖሚ ጨዋታ ብቻ አይደለም፤ የአዕምሮ ጨዋታ Mind Game ጭምር ነው። ሰራተኛው ለራሱን «እድለኛ ነኝ ምክንያቱም ስራ አግኝቻለሁ» ብሎ ያስባል። ባለቤቱ ደግሞ እንዲህ ይላል፦«እኔ ነኝ እድል የሰጠሁት» እዚህ ጋር ሁለቱም በከፊል ትክክል ናቸው። በመጨረሻም ማርክስ ያነሳውን ጥያቄ ባጭሩ ስንዘጋው ትርፍ የምንለው ከየት መጣ ሳይሆን። ይህ ትርፍ ተገቢ በሆነ መልኩ ክፍፍል አልተደረገለትም ነው። ምክንያቱም ዳቦውን አንድ ሰው ብቻ አልጋገረውም፤ አንድ ሰውም ብቻም አይሸጠውም። ቢሆንም ሁላችንም እንደሕዝብ እራሳችንን ብንፈትሽ ስለ ዳቦው ዋጋ እንጂ ስለ ጋጋሪው ዋጋ አንከራከርም። ስለጋጋሪው ዋጋ ግድ የማይለው ገዢ ደግሞ ዳቦ መወደዱን አስመልክቶ ማማረር አይችልም። በርግጥ ግን የዳቦ ቤቱ ባለቤት ለዳቦ ጋጋሪው ደሞዝ ቢጨምር ኖሮ ካሉበት ሌሎች ወጪዎች ጋር ተደምሮ 20 ብር ይሸጥ የነበረው ዳቦ 25 መግባቱ አይቀሬ ነው። ስለዚህ መልሱ በአጭሩ መንግስት ጋር ተቀምጧል። የቤት ክራይ፣ የስንዴ ዱቄት እና ምድጃ እነዚህ ሁሉ የአንድ ሀገር ግብር መጨመርን ተከትሎ የሚመጣ የዋጋ ንረት ወይም መወደድ ነው!። © ሞገስ ዘአምድ
3 038
10
لا يوجد نص...
2 292
11
------------------------------------ © እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.) ሠኞ ነሐሴ ፬ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.
2 947
12
‹‹አዲስ ሃሳብ ከፈለግክ የድሮ መፅሐፍትን አንብብ! (Old ideas, new minds) (እ.ብ.ይ.) አዲሱ ትውልድ የድሮን ነገር ሲያጥላላ አያለሁ፤ አሮጌው ትውልድ ደግሞ አዲሱን ዘመን በብዙ መንገድ ሲተች እሰማለሁ፡፡ ሁለቱም የየራሳቸውን ዘመን ብቻ በማደናነቅ ያለበቂ ምክንያት ስለሚተቻቹ ልክ አይሆኑም፡፡ በደምሳሳው የዛሬውን ሙሉ በሙሉ የሚያናንቁ የትናንት ናፋቂዎችም ብዙ ናቸው፡፡ የሆነው ሆኖ ከትናንቱም የሚወሰድ፣ ከዛሬውም የሚጣል አይጠፋም፡፡ ካለፈውም ሆነ ከወትሮው የማይወደድ ሃሳብ ይኖራል፡፡ የማያስፈልገውን ለማወቅ የትናንቱን ዘመን አስተሳሰብ መረዳት ግድ ይላል፡፡ አዲስ ሃሳብ ወይም አዲስ ፈጠራ እንዲሁ ከሰማይ ዱብ የሚል አይደለም፡፡ አዲስ ነገር ከአሮጌው ነው የሚወለደው፡፡ ዛሬ የትናንት ቀጣይ ነው፡፡ ነገም የዛሬ ውላጅ ነው፡፡ አዲስ ሃሳብ በራሱ አይፈጠርም፤ ካለፈው ጊዜ ሃሳብ ጋር በተራክቦ፣ በሙግት፣ በውይይትና በጥልቀት በማሰብ የሚመጣ ነው፡፡ ይሄን ለማወቅ ግን ትናንትን ማጥናት ግድ ይላል፡፡ ሰው አንድም ከተፈጥሮው ይማራል፤ አንድም ከተሞክሮው ይማራል፤ አንድም በማየትና በመስማት ብቻ ነገሮችን ይገነዘባል፤ አንድም ከመደበኛ ትምህርት ቤት አስኳላ ገብቶ አመለካከቱን ይቀርፃል፡፡ የሰው አዕምሮ የሚጎለብበትና የሚነቃበት መንገድ ብዙ ነው፡፡ ከችግሩ የሚማር አለ፤ ወድቆ በመነሳት አዲስ ሃሳብ የሚያገኝ አለ፤ በህይወት ውጣ ውረድ ውስጥ ሆኖ የኑሮ ፊደል የሚቆጥር ሞልቷል፤ በማጣት የሚማር አለ፤ በማግኘት የሚማር አለ፡፡ ከፍቅር የሚማር አለ፤ ከጸብና ከጥላቻም ግንዛቤ የሚያገኝ አለ፡፡ ከሀዘን የሚማር አለ፤ ከደስታው የህይወት ነገር የሚገባው ይኖራል፡፡ ከብቸኝነቱ፣ ከሰፊ ማህበራዊ ግንኙነቱ፣ ከአካባቢው፣ ከባህሉ፣ ከሃይማኖቱ፣ ከፖለቲካው፣ ወዘተ የሚማር አለ፡፡ ተፈጥሮን አንብቦ አመለካከቱን የሚያጎለብትም የትየለሌ ነው፡፡ ከነዚህ ሁሉ መጽሐፍ ማንበብም አንደኛው የዕውቀት መሰብሰቢያ፣ አዕምሮን ማንቂያ፣ አመለካከትን ማስፊያ መንገድ ነው፡፡ ነገር ግን ያነበበ ሁሉ የነቃ ነው ማለት አይቻልም፡፡ መረጃ ያለው ሁሉ ዕውቀት ያለው ነው ብሎ መደምደም ስህተት ነው፡፡ አዋቂ የሆነ ሁሉ ትክክል፤ ቅንና ደግ ሰው ነው አይባልም፡፡ በዕውቀቱ የሚያጭበረብር፣ በመረጃው የሚሰርቅ የተማረ ሌባ እልፍ ነው፡፡ መረጃ ኖሮት ዕውቀት ከሌለው ከመዝገብ-ቤት አይለይም፤ ዕውቀት ኖሮት ቅንነትና ደግነት ከጎደለው ሰብዓዊነት የማይሰማው የሰው ሮቦት ነው የሚሆነው፡፡ በመረጃው ተጠቅሞ፣ ባነበበው አገናዝቦ አዲስ ጠቃሚ ሃሳብ ማመንጨት ሲችል ነው አንባቢው በማንበቡ ተጠቅሞበታል የሚባለው፡፡ ሩሲያዊው የባይሎጂ ተመራማሪ የነበረው ኢቫን ፓቭሎቭ ‹‹አዲስ ሃሳብ ከፈለግክ የድሮ መፅሐፍትን አንብብ!›› ይላል፡፡ እንደኢቫን አገላለፅ የድሮ መፅሐፍት የሚገልጡልህ አዳዲስ አተያዮች አሉ ለማለት ነው፡፡ ትናንትን መረዳት ዛሬን ለማቅናት ጠቃሚ ነው፡፡ ብዙዎቹ የዛሬ ችግሮቻችን ዋና ምንጮች ትናንት ላይ የተፈጠሩ ናቸው፡፡ የትናንትን ሁኔታ ለመገንዘብ ስለትናንት የተፃፉ መፃህፍትን ማንበብ ጥሩ ነው፡፡ አንዳንዶቹ ጠቃሚ ሃሳቦች በዘመናዊነት ስም ተረስተዋል ወይም ዘመን አልፎባቸው እንደኋላ ቀር ታይተዋል፡፡ ሌሎቹ ደግሞ ትንሽ ለወጥ ተደርገው፣ ስም ተቀይሮላቸው እንደአዲስ ዘመናዊ ሃሳብ ተብለው ይቀርባሉ፡፡ የተረሱ ሃሳቦች ወይም ችላ የተባሉ ችግሮች መፍትሄ እስካልተበጀላቸው ድረስ የዛሬም ሆነ የነገ አደጋዎች እንደሆኑ ይቀጥላሉ፡፡ የቆዩ መፅሐፍትን ማንበብ ታሪክን ማጥናት ብቻ አይደለም፡፡ በጊዜው ያልታዩ ሃሳቦችን ነፃና ገለልተኛ ሆኖ መልሶ በማየት ከዛሬ ጋር ተወራራሽ እንዲሆኑ ለማድረግ ይጠቅማል፡፡ የአዲሱን ዘመን መፅሐፍትን ማንበብ የአዲሱን ትውልድ አስተሳሰብ ለመረዳት ይጠቅማል፤ የቆዩ መፅሐፍትን ማንበብ ግን አመለካከታችንን ሰፊ፣ እይታችንን ሩቅ ተሻጋሪ እንዲሆን ያደርገዋል፡፡ ለዚህ ነው አይዛክ ኒውተን ‹‹አርቄ ማየት ከቻልኩኝ ከትላልቆቹ ትከሻ ላይ ቆሜ አያለሁ(“If I have seen further, it is by standing on the shoulders of giants.”)›› የሚለው፡፡ ኒውተን አዲስ ግኝት ወይም ፈጠራ ትናንትን በመተው የሚገኝ አይደለም፤ ያለፈውን በደንብ አንብበህ ስትረዳ ነው አርቀህ መመልከት የምትችለው ማለቱ ነው፡፡ ሬኔ ዴስካርቴም ‹‹አሪፍ መፃህፍትን ስታነብ ከድሮው ዘመን ምርጥ ጭንቅላቶች ጋር እንደመነጋገር ያለ ነው (“The reading of all good books is like a conversation with the finest minds of past centuries.”)›› ይላል፡፡ ሲ.ኤስ. ሊዊስም ‹‹አዲስ መፅሐፍ ካነበብክ በኋላ ሌላ አዲስ መፅሐፍ ከማንበብህ በፊት በመሐል አንድ የድሮ መፅሐፍ አንብብ፡፡ ይሄ አሪፍ ህግ ነው (“It is a good rule, after reading a new book, never to allow yourself another new one till you have read an old one in between.”)›› ሲል ያለፈውን ዘመን ካሁኑ ዘመን ጋር እያሰተያየንና እያነፃፀርን እንድናነብ ይመክረናል፡፡ በሌላ ጎኑ ደግሞ ፍራንስስ ቤከን የድሮ መፅሐፍቶችን ማንበብ ብዙ ጥቅም የለውም ብሎ ያምናል፡፡ ከዛ ይልቅ አዲስ ችግር አዲስ እውቀት፣ አዲስ አተያይና አዲስ መላ ስለሚፈልግ ወደድሮ መፃህፍት መመለስ አያስፈልግም ባይ ነው ቤከን፡፡ ይኸው ሰው በሌላ ሃሳቡ ላይ የድሮ መፃህፍትን አምኖ ከመቀበል ይልቅ መርምሮ መቀበል እንደሚገባ ያስጠነቅቃል፡፡ ቤከን ‹‹የድሮ መፅሐፍት ውርስ ዕውቀቶችን ይሰጡሃል፤ ልምድህ ግን አዲስ ዕውቀት ይሰጥሃል›› ሲል መከራከሪያውን ያቀርባል፡፡ ዴስካርትም እንደጠርጣራነቱ ‹‹ከድሮው የወረስኩት የተሳሳተ ቢሆንስ (What if what I inherited is wrong) ?›› ሲል ይጠይቃል፡፡ ዴስካርቴ ማለት የፈለገው የድሮ መፅሐፍ ስናነብ ቀጥታ ከመውረስ ይልቅ እየሞገትን፣ እየፈተንንና እየጠየቅን ቢሆን አዲስ ሃሳብ ማዋለድ እንችላለን ማለቱ ነው፡፡ ኒቼም በዚህ ጉዳይ ላይ ዝም አላለም፡፡ ኒቼ እንደውም ‹‹አዲስ ሃሳብ ፈጣሪም እንጂ ምሁር ብቻ ከመሆን ተጠበቅ (beware of becoming a scholar instead of a creator)›› ሲል ይመክራል፡፡ ብዙ በማንበብ ያለፈ ዘመን ታሪክ ብቻ በጭንቅላትህ ውስጥ አጭቀህ አዲስ ነገር ለመፍጠር እንዳይሳንህ ማለቱ ነው፡፡ የምታነበው አዲስ ሃሳብ ከመፍጠር ይልቅ አዕምሮህን በመረጃ ለማጨናነቅ ከሆነ ንባብህ ዋጋ የለውም እያለህ ነው፡፡ ወዳጄ ሆይ.. በርግጥ የድሮ መፃህፍት ሁሉ አሪፍ ናቸው ማለት አይደለም፡፡ ደስ የማይሉ፣ ብዙ ትርጉም የማይሰጡ፣ ተሻጋሪ ሃሳብ የሌላቸው መፅሐፍትም ይኖራሉ፡፡ ነገር ግን ይዘታቸውን ለመገምገምም እንኳን የግድ የመፅሐፍቶቹን ገጽ እየገለጥን ማንበብ ይጠበቅብናል፡፡ ሰው ስለነገረን ብቻ አንድን መፅሐፍ ማድነቅም ሆነ ማጥላላት አይቻልም፡፡ ራሳችን አንብበን ነው መፍረድ ያለብን፡፡ ያም ሆነ ይህ ግን አንብበህ በባህሪህ ላይ ለውጥ ካላመጣህ፤ ለሀገርህ ችግር ጠብ የሚል መፍትሄ ካላበጀህ ማንበብህ ትርፉ ምንድነው? ታሪክ መተንተኑ የተሻለ አዲስ ታሪክ ካላሰራ ትርፉ ወሬ ብቻ ነው የሚሆነው፡፡ ለማንኛውም የድሮውንም የአሁኑንም እየመዘንክ፣ እየሞገትክ፣ የራስህን አዲስ ሃሳብ እየፈጠርክ አንብብ!! ቸር ንባብ! ደግ ምናብ!
2 898
13
لا يوجد نص...
2 063
14
መንደሪን መንደሪን 🍊 ዛሬ ደሞ የጆርጂያ ፊልም ልጋብዛችሁ። ትላንት አይቼው እንዴት እንደወደድኩት። ከፊልሙ የርዕሱ ማማር። የምር የምር...ይሄን ፊልም ማየት መንደሪን ከመብላት እኩል ጣፋጭ ነው። «Tangerines» (Mandarines) በፈረንጆቹ 2013 የወጣ፣ የጆርጂያ እና ኢስቶኒያ anti-war ፊልም ነው። ፊልሙ Oscar እና በ Golden Globe ን ጨምሮ በሌለችም Best Foreign Language Film ዘርፍ እጩ ሆኖ የቀረበ ነው። ታሪኩ የተቀረፀው በ1992–1993 በጆርጂያ እና Abkhazia መካከል በተካሄደው ደም አፋሳሽ ጦርነት ወቅት ነው። ​በጦርነቱ ምክንያት አብዛኞቹ በዚያ አካባቢ ይኖሩ የነበሩ የኢስቶኒያ ተወላጆች ተሰደዋል። ነገር ግን ኢቮ የተባለ አረጋዊ አናጺ እና ጎረቤቱ ያልተሰበሰበውን የመንደሪን ምርት ስብስበው ለመጨረስ ሲሉ በቦታው ይቆያሉ። ​አንድ ቀን በሁለቱ አረጋውያን እርሻ አቅራቢያ በጆርጂያ ወታደሮች እና ከአብካዚያ ጎን በሚዋጉ የ Chechen ቅጥር ወታደሮች መካከል የተኩስ ልውውጥ ይካሄዳል። ከተኩሱ በኋላ ሁለቱም ወገኖች ሲያልቁ፣ ሁለት የቆሰሉ ወታደሮች ብቻ በሕይወት ይተርፋሉ። ​ከአብካዚያ ጎን የሚዋጋ የቼቼን ሙስሊም ቅጥር ወታደር የሆነው አህመድ እና የጆርጂያ ኦርቶዶክስ ክርስቲያን ወታደር የሆነው ኒካ። ኢቮ ሁለቱንም የቆሰሉ ጠላቶች ወደ ቤቱ ወስዶ ያክማቸዋል፤ ያስታምማቸዋል። ቀስ በቀስ ያገግማሉ። ግና አይጥና ድመት አንድ ቤት ኑረው ምን ሊከሰት ነበር? ሁለቱም በቤቱ ውስጥ ሳሉ እርስ በእርስ ለመገዳደል ቢፎካከሩም፣ ኢቮ በቤቱ ጣሪያ ስር ምንም ዓይነት ደም እንዳይፈስ እና እርስ በእርስ እንዳይጠቃቁ ቃል ያስገባቸዋል። እንግዲህ ፊልሙ ከዚህ በኋላ ያለው ነው። ​በአንድ ቤት ውስጥ ተዘግቶባቸው በሚያገግሙበት ወቅት የሚፈጠሩት ነገሮች ናቸው የፊልሙ ውበት። ❷ ​«Tangerines» በትልልቅ የጦርነት የውጊያ ትዕይንቶች ላይ የተመሠረተ አይደለም። ታንክ፣ ጀት፣ መትረየስ፣ የወታደር ጋጋታ የለውም። በትንሽ ቤት ውስጥ በሚደረጉ ቃለምልልሶች እና የስነ-ልቦና ለውጦች ላይ ያተኮረ ነው። አነስተኛ በጀት እና ጥቂት ገጸ-ባህሪያትን በመጠቀም ወደ ውስጠ ዘልቆ ልባችንን የሚነካ ሲኒማ ነው። "Humanity over Nationalism" ነው የፊልሙ መፈክር። ፊልሙ የፖለቲካ፣ የብሔር እና የሃይማኖት ልዩነቶች ሰዎችን እንዴት እንደሚያፋጁ የሚያሳይ ሲሆን፣ ሰብአዊነት እነዚህን ድንበሮች እንዴት እንደሚያፈርስ ደሞ ይጠቁማል። ዳይሬክተሩ Zaza Urushadze ራሱ ጆርጂያዊ ነው። በ1990ዎቹ በጆርጂያ የነበረውን የርስ በርስ ጦርነትና ውድመት በዓይኑ ያየ ሰው ነው። ፊልሙን ሲሰራ የትኛውንም ወገን (ጆርጂያንም ሆነ አብካዚያንን) ጥፋተኛ ወይም መልአክ አድርጎ አላቀረበም። ይልቁንም የራሱን ህዝብና ሀገር አጥፊነት ጭምር በግልጽ በመሞገት ሚዛናዊ እና የሰላም ድምፅ ለመሆን ተፍጨርጭሯል። ይሄ ደግሞ እንደ አንዳንድ የጦርነት ፊልሞች የፕሮፖጋንዳ ሰለባ አያደርገንም። ​ ❸ በፊልሙ ውስጥ መንደሪን (Tangerine) ተራ ፍራፍሬ ብቻ ሳይሆን የፊልሙን ዋና ፍልስፍና በተምሳሌትነት የሚሸከምም ነው። እርዕሱ ከፊልሙ ዋና ሀሳብ ጋር በብዙ መልኩ ይዛመዳል። ​በፊልሙ ውስጥ አረጋውያኑ ፍሬው መሬት ወድቆ ሳይበላሽ ለመሰብሰብ እና ለማዳን ይደክማሉ። ወታደሮቹ ደግሞ ሰዎችን ለመግደል እና ለማፍረስ ይፋጠናሉ። ይህ ንፅፅር አይደንቅም? በአንድ በኩል ሕይወትን ለማፍራት፣ በሌላ በኩል ሕይወትን ለማጥፋት የሚደረገውን የሰው ልጅ እብደትን አሳይተውኛል። ሌላኛው ደግሞ፤ ​መንደሪን የበሰለ ፍሬ ነው። በወቅቱ ካልተሰበሰበ ይበሰብሳል፣ ከመሬት ይወድቃል፣ ዋጋ አልባም ይሆናል። ይህ ፍሬው ከመሬት ሳይረግፍ የመሰብሰብ ስጋትና ጥረት፣ ከሰው ልጅ ሕይወት fragility ጋር ይገናኛል። ​በጦርነቱ መካከል ወጣቶቹ ወታደሮች የወደፊት ህይወታቸው ሳይበላሽ እና ሳይቀጠፍ ሰላምን ማውረድ እንዳለባቸው እያሳሰበ ቢሆንስ? ጊዜያቸው እያለቀ እንደሆነ እና እድሉ ካመለጣቸው ህይወታቸው እንደ መንደሪኑ ረግፎ እንደሚቀር ለማመልከት ቢሆንስ? ይሄ ለሁሉም መሳሪያ ታጣታቂ ያገለግላል። "መቼ ነው መኖር የምትጀምሩት?" የሚል ጥያቄ በቦስጣ አሽጎ ይልካል። "መርገፍ አይበቃችሁም?" ብሎ ይለምናል። "እናንተን የመሰለ ጣፋጭ መንደሪን ከመሬት ፈርጦ ተበላሽቶ መክሰም አለበት?" ብሎ ይብሰለሰላል። ​ ​አዘጋጁ በእርዕሱ አማካኝነት የሰው ልጅ ከጥላቻ ይልቅ ለሕይወት (ለፍሬያማነት) ትኩረት መስጠት እንዳለበት ነው ሹክ የሚለን። ከላይ እንዳልኩት ነው፤ ይሄን ፊልም ማየት መንደሪን እንደመብላት ጣፋጭ ነው። © Mes Oud
2 669
15
لا يوجد نص...
2 250
16
ስብሃት:- ''የሚጥል በሽታ ነበረብኝ። የእኔ እንደ ዶስቶየቪሲኪ እያነሣ የሚያፈርጥ አይነት አይደለም። እኔ ላይ የደረሰብኝን ወንድሞቼ እንደነገሩኝ ሌሊት እነሳና በኃይል! በኃይል እጮሃለሁ። ተነስቼ እሮጣለሁ። ይዘውኝ ያስተኙኛል። ጡንቻዬ ደግሞ የዛን ጊዜ በጣም ጠንካራ ነው። ጠዋት ስነሣ በጣም ድክም ያደርገኛል። አንዳንዴም ጉንጬን እነክሳለሁ። አንዳንዴ ጧት ስነቃ ለመጀመሪያዎቹ ጥቂት ሰከንዶች ማን እንደሆንኩና የት እንደሆንኩ አላውቅም። በዚህ በሽታ ምክንያት ልጅ ላለመውለድ ወስኜ ነበር። ዘነበ ወላ : ''ለምን?'' ስብሃት : በምወልደው ልጅ ይተላለፋል የሚል እምነት ነበረኝ። ዘነበ ወላ : ባለቤትህ በዚህ ተስማማች?'' ስብሃት : ምን አማራጭ አላት? የሚቸልኮትስ ቼርማን እንደ አባቷ ነበር። ኤውሮፓ ውስጥ ከሚገኙት አራት ዋነኛ የንዲህ አይነት በሽታዎች እስፔሻሊስት አንዱ ከሆነው ሀኪም ጋር ሚስተር ዲክ ቀጠሮ ያዘልን። ''በሽታህ በዘር አይተላለፍም'' አለን ''ነገር ግን ማንኛውም ልጅ ሲወለድ ኤፕሌፕቲክ ለመሆን ሦስት ከመቶ እድል አለው። ስለዚህ ምናልባት ያንተ ልጅ ኤፕሌፕቲክ ቢሆን፣ ሎተሪው ሦስት ከመቶው ደርሶት ነው እንጂ ካንተ ወርሶት አይደለም'' አለኝ። መድኃኒት አዘዘልኝ በቀን አንዴ ጊዜ የሚዋጡ። ''ለብላታ ደሬሳ ያመኛል ሳልላቸው ላማክራቸው ወሰንኩ። ይህ በሽታ በእኛ ሀገር <የባርያ በሽታ> ይባላል። አነሣሁና ጠየቅኳቸው። ይህንን ጥያቄ ለመመለስ እንደ ማርኮ ፖሎ ጉዞ ከአንድ ሰአት በላይ በባርያ በሽታ ትንታኔ ይዘውኝ ተጓዙ። በመጨረሻ መልሣቸው እኔ ሠርቼበት አላውቅም ሆነ። እንደኔው የሀገራችንን መድሃኒት የሚያውቅ ጓደኛዬ እገሌ እንደነገረኝ ብለው አንድ መድሃኒት ጠሩ። ተጠቀምኩባት። ብዙም ሳልቆይ ከበሽታዬ ዳንኩኝ። ኬኒኑን መዋጥ አቆምኩ። ከሃና ጋርም የመጀመሪያ ልጃችንን ያለምንም ስጋት ለመውሰድ ተስማማንን። ዘነበ : መድሃኒቱን ብትነግረኝ ስብሃት : ታስሬበታለሁ ዘነበ : ለምን? ስብሃት : ፖሊስ ተወው ብሎ ዘነበ : በሕግ የተከለከለ ነው? ስብሃት : ይላሉ ዘነበ : ታዲያ አንተ በተፈጥሮህ ሕግ አክባሪ ሰው ነህ ለምን ሕገ ወጥነቱን መረጥከው? ስብሃት : መድሐኒቴ ከሕመም ፈውሶኛል። ደስታንም ይፈጥርልኛል። ዘነበ : መድሃኒቱን አልነገርኸኝም ስብሃት : አንዳንዱ ሰው በሰው ሕይወት ውስጥ ገብቶ ይፈተፍታል። ዘነበ : በምን? ስብሃት : ደግሞ እኮ ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው ሲል ትሰማዋለህ ዘነበ : አልገባኝም? ስብሃት : ግን የእኔም በባሕሪዬ አደባባይ መሆን የጎዳኝ መሰለኝ ዘነበ : አዎን እንደሀበሻ በአደባባይ ተከናንበህ ጨለማን ተገን አርገህ የልብህን መከወን ስብሃት : እንደዛ ነው የሚደረግ፣ ሰው ምን ይለኛል እያልክ ዘነበ : መድሃኒቱን ግን አልነገርከኝም ስብሃት : አልነግርህም ዘነበ : ለምን? ስብሃት : ዘነበ አምንሃለሁ። አንተም ሌላ የምታምንም ወዳጅ አለ። ስለዚህ ትነግረውና ሳይታወቅ መድሐኒቱን ታረክሱብኛላችሁ። "ማስታወሻ - ዘነበ ወላ"
2 902
17
ስብሃት:- ''የሚጥል በሽታ ነበረብኝ። የእኔ እንደ ዶስቶየቪሲኪ እያነሣ የሚያፈርጥ አይነት አይደለም። እኔ ላይ የደረሰብኝን ወንድሞቼ እንደነገሩኝ ሌሊት እነሳና በኃይል! በኃይል እጮሃለሁ። ተነስቼ እሮጣለሁ። ይዘውኝ ያስተኙኛል። ጡንቻዬ ደግሞ የዛን ጊዜ በጣም ጠንካራ ነው። ጠዋት ስነሣ በጣም ድክም ያደርገኛል። አንዳንዴም ጉንጬን እነክሳለሁ። አንዳንዴ ጧት ስነቃ ለመጀመሪያዎቹ ጥቂት ሰከንዶች ማን እንደሆንኩና የት እንደሆንኩ አላውቅም። በዚህ በሽታ ምክንያት ልጅ ላለመውለድ ወስኜ ነበር። ዘነበ ወላ : ''ለምን?'' ስብሃት : በምወልደው ልጅ ይተላለፋል የሚል እምነት ነበረኝ። ዘነበ ወላ : ባለቤትህ በዚህ ተስማማች?'' ስብሃት : ምን አማራጭ አላት? የሚቸልኮትስ ቼርማን እንደ አባቷ ነበር። ኤውሮፓ ውስጥ ከሚገኙት አራት ዋነኛ የንዲህ አይነት በሽታዎች እስፔሻሊስት አንዱ ከሆነው ሀኪም ጋር ሚስተር ዲክ ቀጠሮ ያዘልን። ''በሽታህ በዘር አይተላለፍም'' አለን ''ነገር ግን ማንኛውም ልጅ ሲወለድ ኤፕሌፕቲክ ለመሆን ሦስት ከመቶ እድል አለው። ስለዚህ ምናልባት ያንተ ልጅ ኤፕሌፕቲክ ቢሆን፣ ሎተሪው ሦስት ከመቶው ደርሶት ነው እንጂ ካንተ ወርሶት አይደለም'' አለኝ። መድኃኒት አዘዘልኝ በቀን አንዴ ጊዜ የሚዋጡ። ''ለብላታ ደሬሳ ያመኛል ሳልላቸው ላማክራቸው ወሰንኩ። ይህ በሽታ በእኛ ሀገር <የባርያ በሽታ> ይባላል። አነሣሁና ጠየቅኳቸው። ይህንን ጥያቄ ለመመለስ እንደ ማርኮ ፖሎ ጉዞ ከአንድ ሰአት በላይ በባርያ በሽታ ትንታኔ ይዘውኝ ተጓዙ። በመጨረሻ መልሣቸው እኔ ሠርቼበት አላውቅም ሆነ። እንደኔው የሀገራችንን መድሃኒት የሚያውቅ ጓደኛዬ እገሌ እንደነገረኝ ብለው አንድ መድሃኒት ጠሩ። ተጠቀምኩባት። ብዙም ሳልቆይ ከበሽታዬ ዳንኩኝ። ኬኒኑን መዋጥ አቆምኩ። ከሃና ጋርም የመጀመሪያ ልጃችንን ያለምንም ስጋት ለመውሰድ ተስማማንን። ዘነበ : መድሃኒቱን ብትነግረኝ ስብሃት : ታስሬበታለሁ ዘነበ : ለምን? ስብሃት : ፖሊስ ተወው ብሎ ዘነበ : በሕግ የተከለከለ ነው? ስብሃት : ይላሉ ዘነበ : ታዲያ አንተ በተፈጥሮህ ሕግ አክባሪ ሰው ነህ ለምን ሕገ ወጥነቱን መረጥከው? ስብሃት : መድሐኒቴ ከሕመም ፈውሶኛል። ደስታንም ይፈጥርልኛል። ዘነበ : መድሃኒቱን አልነገርኸኝም ስብሃት : አንዳንዱ ሰው በሰው ሕይወት ውስጥ ገብቶ ይፈተፍታል። ዘነበ : በምን? ስብሃት : ደግሞ እኮ ከባለቤቱ ያወቀ ቡዳ ነው ሲል ትሰማዋለህ ዘነበ : አልገባኝም? ስብሃት : ግን የእኔም በባሕሪዬ አደባባይ መሆን የጎዳኝ መሰለኝ ዘነበ : አዎን እንደሀበሻ በአደባባይ ተከናንበህ ጨለማን ተገን አርገህ የልብህን መከወን ስብሃት : እንደዛ ነው የሚደረግ፣ ሰው ምን ይለኛል እያልክ ዘነበ : መድሃኒቱን ግን አልነገርከኝም ስብሃት : አልነግርህም ዘነበ : ለምን? ስብሃት : ዘነበ አምንሃለሁ። አንተም ሌላ የምታምንም ወዳጅ አለ። ስለዚህ ትነግረውና ሳይታወቅ መድሐኒቱን ታረክሱብኛላችሁ። "ማስታወሻ - ዘነበ ወላ"
1
18
لا يوجد نص...
2 104
19
ኒቼ «አምላክ ሞቷል» ያለበት ምሥጢራዊ አግባብ _______ — የፍልስፍናና የሥነ-ጽሑፍ አስተንትኖ — እነዚህ የኒቼ መጻሕፍት ዋና ዋና የፍልስፍና ምንጮቻችን ናቸው፦ The Gay Science፣ Thus Spoke Zarathustra እና On the Genealogy of Morals። ኒቼ "አምላክ ሞቷል" ሲል ምን ማለቱ ነው? ለምንስ እንዲህ አለ? — የኒቼ አባባል ጥልቅ ማኅበረሰባዊ ሂሱን ያቀረበበት የራሱ የአገላለፅ መንገድ ነው። የሰዎችን ቀልብ በሚያስደነግጥ አባባል የመሳብ ልማድም ነበረው። በዚያም ላይ አባባሉ ምፀታዊም ነገር አለበት። ግን የእግዜሩን መሞት ሲናገር የራሱን ኢአማኒነት እየተነተነ አልነበረም። በሰዎች ላይ ከታዘበው ተነስቶና የታዘበውንም ነው የተናገረው። ምናልባት ትዝብቱ ራሱንም ይጨምር ይሆናል። እንጂ ለኢአማኒነት የቀረበ ጥሪ አልነበረም የኒቼ አባባል። ኒቼ ስለ እግዜሩ መሞት ሲናገር እንዲህ ይላል፦ አምላክ ሰው በመሆናችን ብቻ በተፈጥሮ የለገሠንን ቅዱስ ፀጋና ክብር ሁሉ በገዛ እጃችን አቃጥለን አክስመነዋል። ሰላምን አቅፎ ሊሰጠን ፈለገ፤ እኛ ግን በጦርነት እሳት፣ በመድፍና ሚሳይል፣ በጠብመንጃና በፈንጂ አውሎ-ነፋስ አስወሰድነው። «ጎረቤትህን እንደ ራስህ ውደድ» የሚል መንፈሳዊ ጥሪ ተደወለልን፤ በተግባር ግን ጎረቤት ከጎረቤቱ ጋር በፍጅት ሲጫረስና ደም ሲቃባ ተገኘ። «አትስረቅ» የሚል የሕግ ድንጋጌ ተሰጠ፤ እኛ ግን ሥርቆትን፣ ብዝበዛን፣ ዘረፋን፣ በሰው ትከሻና ስቃይ ላይ መረማመድና ቅሚያን የባህሪያችን ዋና መገለጫ አደረግነው። «ለወንድምህ እዘን፣ የወንድምህ ጠባቂ ሁን» ተባልን፤ ወንድም ግን በወንድሙ ላይ ይበልጥ ጨካኝ አራዊት ሆኖ ተነሳ። እንድንራመድበትና እንድንሮጥበት የሕይወት እግር ተሰጠን፤ እኛ ግን በፈረስ፣ በመኪናና በአውሮፕላን ምጥቀት ታበይን። በረከትና አዝመራዎችን የምታፈራ ምድር ተለገሰችን፤ ጥቂቶች በሚተርፋቸው እህልና ሀብት ሲንደላቀቁ፣ እልፎች በረሃብና ጠኔ ጋንግሪን መከራ የሚማቅቁባት ጨካኝ ምድር አደረግናት። «ለአምላክህ ተገዛ» የሚል ሕያው ጥሪ መጣ፤ እኛ ግን ለወርቅና ለወረቀት ገንዘብ ተንበረከክን። «የዕውቀት ሁሉ ምንጭ አምላክ ነው፤ የጥበብም መጀመሪያ እርሱን መፍራት ነው» ተባለ። «ሀብትህን ጥለህ ተከተለኝ፤ ምድር ጊዜያዊ ድንኳን ነች፤ ለብልጭልጭ ቁስ አትገዙ» ተብለን ተነገረን። እኛ ግን አምላክንና መንፈሳዊ መገለጡን አሽቀንጥረን ጥለን፣ ምድራዊ ዲፕሎማና ዲግሪ የምናሳድድ አቧራ አብላሾች ሆንን። የጥበብ መጀመሪያችን ገንዘብ፣ አምላካችንም ገንዘብ፣ እውነተኛ የምኞታችንም ማቂያ ገንዘብ ሆነ። ፈጣሪን ወደ ጎን ገፍትረን ሀብትን አደንን። ምድሪቱ ዘላለማዊ መኖሪያችን እንደሆነች ሁሉ ቤትና ፎቅ፣ ጎጆና ፉካ መገንባት የምኞታችን ጣሪያ ሆነ። መንፈሳዊውን ዓለም ንቀን፣ ለቁሳዊው ዓለም ባሪያ ሆንን። ከአንደበታችን ክፉ ነገር እንዳይወጣ ተመከርን፤ እኛ ግን አፋችንን በዘለፋ፣ በሃሜትና በምቀኝነት አሟሸነው። «ተጎናበሱ፣ ዝቅ በሉ» ተባልን፤ እኛ ግን ደረታችንን ነፋን — ትዕቢታችንንም «በራስ መተማመን» በሚል አሸሸ ገዳሜ አጌጥንበት (ምንም እንኳ መጎናበስንና ዝቅ ማለትን ራሱ ኒቼ የማይወደው ቢሆንም)። «አታመንዝሩ» ተባልን፤ የልባችን ዋነኛ መሻት ግን የሥጋ አመንዝራነት ሆነ። ጭራሽ ፖርኖግራፊን የዕለት መተዳደሪያ፣ ሴተኛ አዳሪነትንም ህጋዊ ንግድ አደረግነው። ሰዶምን በእሳት አቃጥሎ ሰዶማዊነትን ከለከለን፤ እኛ ግን ግብረ-ሰዶማዊነትን እንደ ታላቅ ጀብዱና ነፃነት ቆጠርነው። እግዜር ከሰጠንና ከነገረን ቅዱስ ቃል ውስጥ ያስቀረነው ምን ነገር አለ? የሰጠንን ፀጋ ሁሉ ከላያችንም ከውስጣችንም አሽቀንጥረን ጥለነዋል። እግዜሩን ከነመኖሩ እንኳ አናምነውም፤ ብናምነው ኖሮማ ቃሉን እንከተል ነበር። አሁን የቀረን ነገር ቢኖር የተቀባባ ማስመሰልና የሐሰት ጭንብል ብቻ ነው። ሃይማኖተኛ እንመስላለን፤ ነገር ግን አምላካችን በውስጣችንም ሆነ በሕይወታችን ውስጥ የለም። ፍሬድሪክ ኒቼ «ዘ ጋይ ሳይንስ» (The Gay Science) በተሰኘው ድንቅ መጽሐፉ ያበሰረው ያ አስደንግጥ እውነት ዛሬም ያስተጋባል፦ አምላክ ለኛ ሞቷል! በሥራችን፣ በአኗኗራችንና በምርጫችን ገድለነዋል። እኛ አምላክን የገደልን የገዳዮች ሁሉ ገዳይ፣ ጨካኝ ፍጡራን ነን። ከገደልነው ዘንድ ምናልባት ሌላ አምላክ ፈልገን ይሆን? ወይስ ለሌላ ህልውና መገዛትን ውስጣችን አሻፈረኝ ብሎት ይሆን? ከሆነማ… ሰውን ራሱን አምላክ አድርገን እንፈብርከው! ኒቼ «ዛራቱስትራ እንዲህ ተናገረ» (Thus Spoke Zarathustra) በተሰኘው ፍልስፍናዊ ድርሰቱ እንደተነበየው፣ «ኡበርሜንሽን» (Übermensch)፣ ሱፐርማንን፣ «ሆሞ ዴውስን»፣ ዜውስንና አፖሎን ራሳችን እንሁን ይላል። ምክንያቱም ኒቼ «ኦን ዘ ጄኔአሎጂ ኦፍ ሞራልስ» (On the Genealogy of Morals) ላይ በጥበብ እንዳወሳው፣ እኛ ሰዎች በመታዘዝና በመገዛት ሳይኮሎጂ ራሳችንን ያሰለጠንን የመገዛት ሱሰኞች ነን። የራሳችንን ሃሳብ አመንጭተን አናውቅም፤ የያዝነው ሁሉ የኮረጅነው፣ የተከተልነው፣ የተሰጠንና የተነገረን ነው። ራሳችንን አናውቀውም፤ የራሳችን የሆነ ማንነትም የለንም። አሁን ምን ማድረግ እንዳለብንና እንደሌለብን የሚነግረንን አምላካችንን ገድለነዋል። ነገር ግን መታዘዝ ተፈጥሯዊ ፍላጎታችን ስለሆነ፣ እንግዲህ ተሰብስበን ወይም ደግሞ ወጣ ብለን የራሳችንን «የሰው አምላክ» እንፍጠር። ምን ይደረጋል? ያለ አምላክ መኖር አንችልም፤ ማን ይመራናል? ማን ምስጢር ይገልጥልናል? ማን ባህሩን ይከፍልልናል? ማን ከድንጋይ ውሃ ያፈልቅልናል? ማን ይፈውሰናል? ማን ያፅናናናል? አምላክ ያስፈልገናል! አምላካችንን ግን በፈቃዳችን ገድለነዋልና ከእንግዲህ አይመለስም። ስለዚህ የሰው አምላክ እንፍጠር! ታላቁን፣ አይበገሬውን፣ ሰማይን የሚያስሰውን፣ ምድሪቱን የሚቀደውን፣ ባህሩን የሚቀዝፈውን፣ «እንደ ሰው በምድር፣ እንደ ዓሣ በባህር» የሆነውን አምላካዊ ሰው እንፍጠር…! ኒቼ ያለው ይህንን ነበር! ይኸው ዘመኑ አምላኩን ገድሎ፣ ያንን «የሰው አምላክ» በመፍጠር ሂደት ላይ ይገኛል። ኒቼ ያለውም፣ የታዘበውም፣ በውስጠ-አዋቂ ምፀት ያወገዘውም ይህንኑ ነበር። አምላከ-ቢስ አስመሳዮች መሆናችንን መርምሮ ደርሶበት ነበር። ነገር ግን ኒቼ በመጨረሻ አብዶ ሲሞት፣ ዓለም እንዲህ ስትል ተሳለቀችበት፦ «እግዜር ሞቷል» — ኒቼ። (አራት ነጥብ) «ኒቼ ሞቷል» — እግዜር።፡ (ስድስት ነጥብ ነገሩ ዘርዘር ሲደረግ ይህንን ይመስላል ጥያቄ፦ ለመሆኑ የኒቼ «የሰው አምላክ» (Übermensch) ፍልስፍና የሰውን ልጅ ነፃ ያወጣዋል? ወይስ ይበልጥ ወደ ሌላ የቁስ አምልኮ ባርነት ይከተዋል? እስቲ እውነት ሃቁን እንናገር ለራሳችን! እውነት እግዜር በልባችን አለ? እውነት ከልብ እና በውስጣችን እግዜር አለን? እኔ የለሁበትም!🤪 የነፍስ አባትህም አይደለሁም። ምሥጢርህን ለራስህ ያዘው። ሸጋ ቀን! 🙏 © Assaf Hailu
2 699
20
لا يوجد نص...
1 755