ar
Feedback
ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

الذهاب إلى القناة على Telegram

"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖

تُعد قناة ከመጻሕፍት ዓለም - Book shelf 📗📚📖 (@bookshelf13) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 18 540 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 900 في فئة الكتب والمرتبة 1 830 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 18 540 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 30 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -119، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 0، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 9.66‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 3.88‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 1 791 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 720 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 6.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
"ስለመጻሕፍት ከመጻሕፍት መንደር እንዘምራለን!"

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 31 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الكتب.

18 540
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-167 أيام
-11930 أيام

جاري تحميل البيانات...

سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يوليو '26
يوليو '26
+31
في 0 قنوات
يونيو '26
+12
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '26
+108
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+31
في 1 قنوات
Get PRO
مارس '26
+16
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+15
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+21
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+36
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+42
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+31
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+31
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+60
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+44
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+72
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+451
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+460
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+500
في 4 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+317
في 2 قنوات
Get PRO
يناير '25
+421
في 1 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+481
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+275
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+244
في 1 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+254
في 2 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+307
في 2 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+388
في 1 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+231
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+241
في 1 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+354
في 3 قنوات
Get PRO
مارس '24
+325
في 2 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+251
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '24
+96
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+184
في 1 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+141
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+96
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+46
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+119
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+158
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+143
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+79
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+59
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+62
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+182
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+195
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+468
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+92
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+399
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+71
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+91
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+205
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+198
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+317
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+718
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+177
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+356
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+36
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '21
+213
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '21
+243
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '21
+908
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '21
+917
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '21
+873
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '21
+219
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '21
+59
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '21
+125
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '21
+430
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '21
+396
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '21
+304
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '21
+354
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '20
+14 056
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
31 يوليو0
30 يوليو+1
29 يوليو0
28 يوليو+1
27 يوليو+4
26 يوليو0
25 يوليو+1
24 يوليو+3
23 يوليو+1
22 يوليو0
21 يوليو+2
20 يوليو0
19 يوليو0
18 يوليو+1
17 يوليو+2
16 يوليو0
15 يوليو+1
14 يوليو+1
13 يوليو+1
12 يوليو+4
11 يوليو+1
10 يوليو+4
09 يوليو0
08 يوليو+1
07 يوليو0
06 يوليو0
05 يوليو+1
04 يوليو0
03 يوليو0
02 يوليو+1
01 يوليو0
منشورات القناة
ከተማ ተቀምጠው ከግላዊ ምክኒያት ወይ ከመሰላቸው አንድምታ ተነስተው ሀገራቸውን ወርደው ሳያውቋት የሚቃትቱ ጆርዲን መሳይ ሴቶች ስጋት ይሆኑብኛል ብሎ የሚያስብ ሰው ፤ፅንፍ እንደወጣ ሴታዊነት ሁሉ እርሱም ፅንፍ የወጣ ወንዳዊነትን የሚያራምድ መሆን አለበት። ለማንኘውም… ወደድክም ጠላሕም! ባለኮፍያው ሰውዬ ንዑስ ንባብ፣ በብልጠት ያልተቀባ ማስረጃ፣ ዝና ብቻ ያነፈነፈ አንጎል ይዞ ባይቀርብ ኖሮ ልጅቷ የምታነሳቸውን ሀሳቦች ለመሞገት እጅግ ቀላል ነበር። በግሌ ካለኝ ምልከታ የሷን አይነት ሰው መሞገት ቀላል ነው ምክኒያቱም የምታነሳው የሚጨበጥ ፍሬም ወርክ በመሆኑ እነዛን የምታነሳቸውን ሀሳቦች empirical በሆነ መንገድ የሚያሽሩ ሌሎች ሙግቶች ስላሉ፤ በቂ ዝግጅት ላለውና ከተንኮልና ዝና ጥማት ከፍ ላለ ሰው የሚከብድ አይሆንም። እሷንም ሆነ ሌላውን ህዝብ በተገቢው መልኩ በኃሳብ ሞግቶ ከስህተት ማትረፍና መግባባት ቀላል ይሆናል። የሆነው ሆኖ ፖስቱ በቀረበ በተወሰኑ ደቂቃዎች ውስጥ ደወለልኝ። አንዴት እንዲህ ትፅፍብኛለህ አለኝ። ማንም ሰው ቢሆን ያንን ከማድረግ እንደማልመለስ አስረዳሁት። ነገሩ ልክ አለመሆኑን ፤ ስለ ሳይንሰዊ ጥናትም ስለ አጋንንትም በአንዴ ሁለት የሚጋጩ ሙግቶችን በማተት መሞገት ልክ አለመሆኑን አስረድቼዋለሁ። በወቅቱ humble ሆኖ የተሳሳተ መሆኑን አምኖ የተማርኩትን ትምህርት ጠየቀኝ እሱም የት ሊማረው እንደሚችል ጭምር። ፍላጎቱ ይመስል ነበር። አስረድቼዋለሁ። ይልቁንም ልጅቷን በራሱ መድረክ እንዲሞግታት ለዚያ የሚሆኑ የሙግት ሀሳቦችን እንዳግዘው ጠየቀኝ። ደስተኛ ነኝ በሚል የሄድክበት መንገድ ልክ ስላልነበር፤ ህዝቡንም አሳስተሀል እውነተኛ ክርክር ማድረግ ከፈለክ ከኒሮ ሳይንስ እስከ ማህበራዊ ሳይንስ ኀልዮቶች ድረስ የሚነበቡ በቂ ማቴሪያሎች እንደማጋራው ቃል ገብቼ ፤ humbly ለክርክሩ ባሳየው ብቃት መሳሳቱን አምኖ በሰላም ምንም የተለየ ኢሞሽንና መጯጯህ እንኳን ሳይኖረን ነበር ስልኩ የተዘጋው። እርግጠኛ ነኝ በሱ ተንኮል ውይይታችንን ቀድቶታል። እንግዲህ እንደ ወዳጄ ኢዮብ ምህረተዓብ እሱንም እኔ ስሞት ጠብቆ ያወጣው ይሆናል : ) This Guy, ባለኮፍያው ሰውዬ ለካ በጣም አደገኛ አስመሳይ ሰው ነው። ተደበቀ። የተጠማውን ዝና ከሶሻል ሚዲያ እያንቆረቆረ እንደቆየ ጥርጥር የለውም። ብዙም አልቆየሁም በዚያ መንደር። ከዚያ ለመልቀቅ ብዙ ፋክተሮች ሲኖሩኝ፤ ይሄኛው ሁነት ምናልባት የመጨረሻው ስትራው መሆኑ ነው። ለቅቄ ወጣሁ። በርግጥ በጣም ፕሪስቲጂየስ የሆኑ በእውቀታቸው የተከበሩ ሰዎች በዚያ አውቃለሁ። ጥቂት የማይባሉት አውርተውኛል። የልጁ ናኢቭ አካሄድ የፃታ ጉዳይን በተቆርቋሪነት ስም ወደ ፅንፍ እንደሚወስደው ያላቸውን ስጋት ነግረውኛል። "ምን አላተመህ? ያልገባው ህዝብ በራሱ ሰዓት ይገለጥለታል" ያሉኝም ነበሩ። Brother! This is my own land! ቀላል እላተማለሁ እንዴ! በተለይ በቅንነት አላማወቁን የተጋፈጥክለት ደንቆሮ ባደባባይ እየወጣ በህዝብ ስጋትና መቆርቆር አስመስሎ ሲነግድ፣ ዝና ረሀቡን ሲያስታግስ፣ እውቀት ላይ ሲዘባበት፣ የገዛ ምንነትህን ሳይቀር ግዛኝ ልሽጥልህ እያለ ሲያሞኝ ዝም የምል አይነት አይደለሁም። መልሱ አንድ ነው። This is my own land! የኔ አለም ነው። ውሸታም ፣ አላዋቂ፣ አስመሳይ፣ ብልጣብልጥ፣ በፍርሀትህና በአለማወቅህ ስም የሚነግድ ካለ ፤ አንተ እንደጊንጥ እየነከስከኝም ቢሆን እስኪገለጥልህ ድረስ ንክሻህን ታግሼ ማስኩን እልጣለሁ። ላንተ ስል አይደለም! ለራሴ ስል። የእኔም ምድር የኔም ሀገር ስለሆነ። ለሀቅ ግትር ስለሆንኩ እና most importantly ድንቁርና በጣም እፀየፋለሁ። ከዚያን ጊዜ አንስቶ ይሄ ግለሰብ Mistook His Hat for Knowledge. አንዳንድ ሰው ያደረገው ኮፍያ እና ቀለሙ ምናንም ኮተቱ ማወቅ ይመስለዋል። እስትገልጠው ድረስ ብዙ ሰው ያታልላል። በተደጋጋሚ ራሱን ባለሙያ እና የማህበረሰብ ተቆርቋሪ አስመስሎ በማቅረብ እጅግ ውስብስብ የሆኑ የስነአዕምሮና ሥነልቡና እንዲሁም ማህበራዊ ጉዳዮችን በማንሳት የአዋቂ አስተምህሮ በሳይንስ ስም ማሳለጥ ጀመረ። ይማራል በሚል ለማለፍ ሞክሪያለሁ። በዚህኛው ዙር ግን በማልደራደርበት በአዕምሮ ጤና ጉዳይ ላይ ለመሸቀጥ ነበር የመረጠው። እናም የሚታለፍ ባለመሆኑ ሰውዬውን መግለጥ አስፈላጊ ሆኗል ለዚያም ሲባል ከጄነሲስ አንስቶ እስከ አሁን ድረስ ባለው ጉዞ የአካሄዱን ሀሳዊነት ማሳየት ይኖርብኛል። እርሱም ከተጋነነ ለራሱ ካለው ግምት ወጥቶ በገዛ ሞያው ወገኖቹን በመሳብና በማብቃት ሀቀኛ ስራ ለመመለስ እስካልጀመረ ድረስ በሳይንስና በሙያ ስም የሚያደርጋቸውን ሀሳዊ እንቶ ፈንቶዎች Debunk በማድረግ ለማህበረሰቡ ማጋለጥ አናቆምም። በሙያ ላይ በሚደረጉ አደገኛ ስህተቶቹ ደግሞ ለአስፈላጊው የህግ አካል ማሳወቃችንን እንቀጥላለን። ቀጣይ ክፍል አለው። ቀጥሎ የምነግርህ ባለኮፍያው ሰውዬ የዘመን ስጋትህ የሆነው ጉዳይን አስታኮ የራስህ የሆነውን ነገር ነጥቆ ሊሸጥልህ እንደተነሳ Debunk ያደርጋል። © Surafel A. https://open.substack.com/pub/surafela/p/the-guy-who-mistook-his-hat-for-knowledge?utm_source=share&utm_medium=android&r=5xmt33&fbclid=IwZXh0bgNhZW0CMTEAc3J0YwZhcHBfaWQPMjc1MjU0NjkyNTk4Mjc5AAEeZqcLzzD2K0Sx2VYZDPKbO4RHA5yr2GMvHEoGbxK88Zb5HckmpZxmfLa1Jxo_aem_vOKo050zW_lcqKiFgrSr4A&utm_id=97758_v0_s00_e0_tv0

2
The Guy Who Mistook His Hat for Knowledge ሐሳዊው Guru - ክፍል 1 Surafel Ayele የዛሬ ዓመት አካባቢ ነው። አንድ ግለሰብ ስልክ ይደውልልኛል። ደካማ ጎኔን ተረድቶታል። በደካማ ጎኔ ነው የመጣው። በኢዮብ ምህረተዓብ። ጥቂት አወራን። ስለ ኢዮብ አንድ ነገር ለመስራት እንዳሰበ እና ሰዎች ቃለመጠየቅ ለማድረግ ማሰቡን ነገረኝ። የኔንም ሀሳብ በቃለመጠይቅ ለመውሰድ ፈልጓል። የካሜራ ሰው አለመሆኔን ነገርኩት። ስለ ኢዮብ የተሻለው ሰው አጋሩ ትዕግስት መሆኗን ነገርኩት። የቪዲዮውን ሐሳብ ነገረኝ። የተፃፈውን እንዳየው ላከልኝ። አየሁት። ስለ ኢዮብ የተነሳ ነገር እዚህ ግባ የማይባል ሲሆን፤ ሌላው በሙሉ ወንድ ሁን የሚል ሀተታ ነው። I was perplexed by his thoughts. በቅጡ ሳነበው አንድም አይነት የማህበራዊ ሳይንስም ይሁን የሥነህይወት ንባብ እንደሌለው ገብቶኛል። በጣም የተምታታና ውርዴ ፅሁፍ ነበር የላከው። ልክ አለመሆኑን አስረዳሁት። መመስረቻ ኀልዮ ፣ ሙግት እና አመክንዮ እንደሚጎድለው፤ የራሱን ሐሳብ ከማንሳቱ በፊትም በነዚህ ጎዳዮች ላይ ሀሳቡን እንዲመሰረት ተደዋውለን ስለ Existential crisis, Will to power, will to pleasure will to meaning ወዘተ ሃሳቦችና አሳቢያን ቢያነሳና የራሱን ሀሳብ ከዚህ ሁሉ ጋር እንደገና እንዲቃኝ በቅንነት አሳየሁት። እኔ እንድፅፈው ነበር የፈለገው ሆኖም ፈቃደኛ አልነበርኩም ፍሬምወርኮቹን ፅፌ አንብብና እነዚህ ላይ ስራ አልኩት። ከዚያ ቪዲዮው ተሰራ። በጣም ደነገጥኹ። በጣም አፈርኩ። ሀሳቦቹን የነገርኩትን በተወሰነ መልኩ እያማጠም ተንተባትቦም ቢሆን ሸምድዶ አንብቧቸዋል። ይሁን። ነገር ግን ይህ ቪዲዮ ስለ ኢዮብ ምህረተዓብ የተሰራ አስመስሎ ለካ ሲያታልለኝ ነበር። ወይም ሌሎች ወዳጆችንም እንደዛ አድርጓል። ቢያንስ የኢዮብን ባለቤት ሳወራት እሷም ይሄ ተሰምቷት ነበር። This guy ሌላ level ላይ ያለ አስመሳይና የድሮ አራዳ ነው። ከምንም በላይ የኢዮብ የቅርብ ወዳጆች በወቅቱ ተደዋውለን ስንገረምበት የነበረ ጉዳይ ነበር። ባለኮፍያው ሰውዬ ኢዮብ ምህረተዓብን በህይወት በነበረበት ሰዓት የተደዋወሉ ጊዜ የነበራቸውን የስልክ ልውውጥ ቀድቶ አስቀምጧል። ያንን የስልክ ልውውጥ ለዚህ "ወንድ ሁን"ምናምን ጂኒ ለሚለው ደኪመንታሪ መሳይ እንቶ ፈንቶ ማድመቂያነት ተጠቀመው። በየትኛውም ሁኔታ ድምፁ አየር ላይ እንዲውል ፈቅዶ የማያውቀው ኢዮብ ምህረተዓብ ራሱን መከላከል በማይችልበት ሁኔታ እሳት ማንነቱ ከአፈር በታች ስለዋለ ብቻ የሚከላከልለት አጣ። አንድ በኢዮብ ምህረተዓብ ስም መታወቅ የተጠማ ስለ ሞራል፣ ኤቲክስ እና የወዳጅነት ነውሮች የተመታ ግንዛቤ ያለው ሰው ይሄንን ኢዮብ ምህረተዓብ ላይ አደረገ። ቪዲዮው ውስጥ የገባው የኢዮብ ምህረተዓብ ድምፅ ለቪዲዮው ምንም አስተዋፅኦ የሌለው ሲሆን፤ ኢዮብ ሁሉንም ሰው ሲያወራ ሁሌም እንደሚያደርገው ማንነትህን ክቦ፣ ሞያህን አዳንቆ፣ ጌታዬ ብሎህ ወዘተ ነውና ያንቺን ክፍል this little imposter guy used it. በጣም ያስቃል። እንደ ኢዮብ ወዳጅ ደግሞ ያስቆጣል። ምክኒያቱም ኢዮባ በህይወት ቢኖር ይሄ አይሆንም ነበር። ይሄን ባለኮፍያው ሰውዬም ፣ እኔም፣ የኢዮብ ወዳጆችም እናውቃለን። የሆነው ሆነ። አካሄዱ ገብቶኛል ዝና እንደጠማው ለማወቅ በቂ ምክኒያት ነው። አለፍኩት። በሌላ ጊዜ ስለፌሜኒዝም ክርክር ከማድረጉ በፊት ፅፎልኝ እንደነበር አስታውሳለሁ። ስለጉዳዩ የማወቀውን ጠየቀኝ። እናወራለን በሚል ማለፌን አስታውሳለሁ። ከሳምንታት በኃላ scroll ሳደርግ randomly ቪዲዮ መጣልኝ። This prompus with a hat sat with a lady to debate. ከምር ሳቄ መጥቷል። ልጅቷን አላውቃትም። ቲክታክ ተጠቃሚ አይደለሁም። ያለዛን ቀን ሐሳቦቿን አይቼም አላውቅም። እሱን አውቀዋለሁ። ቢያንስ እንደዚህ አይነት የሶሽል ሳይንስ ከንሰብቶች ላይ ያለው እውቀት እጅግ በጣም አናሳ፤ የተመታ እና ውስብስብ የሆኑ ቲየረቲካል እሳቤዎችን ካውንተር ለማድረግ በቂ ንባብ እንደሌለውም ጭምር ከዛ በፊት በነበረው ስራው አይቻለሁ። እና ሳቄ መጣ። ክርክር ከሆነ ክርክር ነው። የምትሞግተውን ሐሳብ ለመሞገት የሚያስችል ሐሳብ ላይ ብቻ የተመሰረተ ነገር ሊኖርህ ይገባል። ይሄ ሰው የለውም። ያንን ሳስብ ዛሬም እስቃለሁ። ብቻ I gave it 20/25 mins. ከዛ በቃኝ። በጣም አደገኛና በማህበራዊ መቆርቆር ስም ያደፈጠ ስምና ዝና የተጠማ ተንኮል የሰበቀ ሰው መሆኑን የሚያረጋግጥ ነበር። በአንፃሩ ተከራካሪዋ ሴት ተታላ ነበር። ሊከራከራት በሐሳብ ሊሞግታት አይደለም የተቀመጠው። የምታራመድው ሀሳብ ላይ ሰፊ ልዩነት ቢኖረኝም፤ ሰውዬው ያንን ሐሳብ በሐሳብ ሊሞግት ሳይሆን ዛሬም ድረስ የምመሰክረው ሊያዋርዳት እና በውርደቷ ላይ ራሱን ሊያጀግን ነበር የወጣው። ጆርዲ ፌሚኒዝም ላይ ቆርባለች። ከልክ በላይ ቆማለታለች። በሳይንስ ውስጥ አንድን ነገር ከልክ በላይ አታምነውም። ማምለክ ስለምትጀምር መሳሳትህን ወይም የነገሩን ስህተቶች ለመገንዘብ ትታወራለህ። እሷ እንዲያ ነው የምትታየኝ። ከልክ በላይ ላመነችው ኀልዮ የትኛውንም ነገር ለመቀበል አትፈቅድም። ይሄን ማለት ግን ባለኮፍያውን ሰውዬ እውነተኛ እና ባለሐሳብ አያደርገውም። የሰፈር መደጋፍህን እና መቧደን ትተህ በንፁ ሕሌና፤ በንፁ ህሌና ብቻ አይደለም ፤ በክርክር መሰረታዊ ህጎች፣ በማህበራዊ ሳይንስ መርሆና መሰረታዊ የፍልስፍና እና ስነአመክንዮ መርኆዎች ነገሩን ስትቃኝ ዛሬ ድረስ ባለኮፍያው ሰውዬ ነጥብ የጣለ ሲሆን፤ የአካሄዱ አደገኛነት የምታየው፣ ሳይንስ እንደሚለው ብሎ ያነሳና ለዚያ ነገር በቂ ሙግት ሲቀርብበት ወደ ሃይማኖት ይገባል ፤ በዚህ ስትለው ወደዛ ፤ ወዲያ ስትለው ወዲህ የተመታ የድንቁርና አካሄድ ነው። እደግመዋለሁ። የድንቁርና ትክክለኛ መታያ ባህሪ ነው። ብዙዎች አጨበጨቡ። ተከታይ አፈራ። ወንድ መሆንን የሚወክል ያህል ስለነገሩ ተባለ። ያ ያስደነግጣል። በተለይ ፌሚኒዝም እዚህ ግባ የማትለው ኀልዮ መሆኑን ለሚያውቅ፤ በቅጡ ግን መሞገት ያለበት እና መያዝ ያለበት፣ ሐሳቡን የሚያቀነቅነው ሰው ደግሞ መከበር ያለበት መሆኑን ለሚረዳ ሰው ነገርዬው አስቀያሚ ነው። ደስ አይልም። ግልብ ዕውቀት የሚያወድስ ህብረት አወዳደቁ የከፋ ነው። ፌስቡክ ላይ የተሰማኝን አቅርቤኣለሁ። አብዛኘውን ሰው እንደሚያስቆጣ አቀዋለሁ። ልክ ያልሆነ ነገር ግን ለንቦጭህን ስለጣልክ ብቻ የማመቻምች አይነት ግለሰብ አይደለሁም። መተዛዘል አይመቸኝም። ከዕውነት እወግናለሁ። ጀርባውን የሚቀማመለው ዝንጆሮ ብቻ ነውና በቨርቹዋሉ ዓለም በሀሰት የተመተባበር ዝንባሌ አይመቸኝም። ሰው መሆንን አከብራለሁ። ስለማላውቀው ነገር አደባባይ ወጥቼ አላውቅም። ህዝቤን በሶሽል ሚዲያ ሳይሆን በጓዳው አውቀዋለሁ። በየእያንዳንዷ የሀገሪቱ ገጠር ኮርነሮች ገብቻለሁ። ማህበረሰባዊ ሥነልቡና ሳይንስ ሸምድጄ ሳይሆን ሀገሬን አገልግዬበት ነው የማውቀው። የሰው ልጆች ፈተና ይገባኛል። የወንድ እና የሴት ልጆች ፈተና ማለት ነው። ፈተናቸው ማሳ ላይ እያረሰ ከደረቀ መሬት ሲታገል የሚውልን አባወራ አይተህ ፤ ሚስቱ ደግሞ ምጧ መጥቶ በቤት ውስጥ ያለረዳት ስትወልድ ሞት ያጋጠማትን እናት በአካል እስከማየት እና ከዚያም የሚከፉ ውስብስብ ኢኮኖሚክ እና ማህበራዊና ፖለቲክል ፈተናዎች ናቸው። እጅግ ከዚህ የሚከፉም አሉ።
771
3
لا يوجد نص...
750
4
ነፋስ እየነዳ የወሰዳቸው ዘሮቿ በነፋስ ይመጣሉ። እዚህም ይሆናሉ። ኮረብታዎቻችን መቼም ቢጫ የማይጎልባቸው ለዚህ ነው። አሁን አሁን መርሳትን እየተማራችሁ ነው። እውነት እውነት እላችኋለሁ እንደ አስተማሪነቴ የአደይዋን የሚያክል እውቀት ለወገኔ ያስተላለፍኩ አይመስለኝም። የራሳችሁን የግል ታሪክ ብትመረምሩ ከታሪክ አዋቂዎች የበለጠ ወደ ምር ትጠጋላቸሁ። በቅንነት ያለፋችሁበትን አስታውሱ። እውነትን ከኑሮአችሁ ታገኛላችሁ። ትንንሹን ነገር ስትገጣጥሙ የአገራችሁ ትልቅ ምስል ይሆናል። ለዚህ ሁሉ ለአወራሁት የአደይ ጉዳይ ማሰሪያ ትርጉም ላግኝለት? አዎ የራሳችሁን ትከክለኛ ልምድ አስታውሱ እና በምንም ምክንያት ተስፋ አትቁረጡ…… አለመቁረጣችሁ ደሞ በትክክለኛው ጎዳና ይሁን” ቲቸር ሰለሞን እንዲህ ተናግረው፣ ፊታቸውን አዙረው ሄዱና አፋቸውን እየዳበሱ፣ እና እየሳሉ እንጨት ወንበራቸው ላይ ተቀመጡ። ከፊት ረድፍ የሚቀመጠው አማን ዞሮ የደረሰውን የአደይ ዘር የያዘ ብርጭቆ አምጥቶ ጠረጴዛቸው ላይ ቀስ ብሎ አስቀመጠው። © Adam Reta
1 316
5
ከ"መዝሙረ ሄላም" “......ይህቺ በእጄ የያዝኳት እና የምናያት አበባ፣ ሁላችንም እንደምናውቀው አደይ ናት። አይደለም? ለሁለት ወሮች ያህል ከምንነቷ ወይም ማንነቷ ምንም ሳላጎል፣ ማለት አበባዎቿን ሳልነካ፣ አጥንቷን ሳልሰብርና ሳልፍቅ እና የሆነ ምቹ ቦታ እንዳትደርቅ አድርጌ አስቀምጬ ዛሬ አመጣኋት። ቅድም ይህቺ አበባ ምን ትባላለች? ስላችሁ ብዙ ሳትቸገሩ አወቃችኋት። ከእናንተ መሃል አንድም ተማሪ ተሳስቶ፡ ‘ቲቸር በእጅዎ የያዟት አበባ ፅጌሬዳ ናት’ ያለኝ የለም። ይህቺ አበባ ክረምት መጠናቀቅ ሲጀምርና አዲስ አመት ሲገባ፣ በየቦታው፣ ለማንም በሚታይ መልክ በመብቀልና በመፍካት የክረምትን መጠናቀቅ፣ የጨለማና የእርጥብ ወሮችን ማለፍ የምትነግረን ባህላዊ ምልክታችን ናት። ይሄንንም ሁላችን እናውቃለን። የማያውቅ አለ? በየካቲትና በመጋቢት ወር ይህቺ አበባ የትም አትታይም። የአበባዋ ዝርያ የአገራችን ብቻ ስለሆነ፣ ጠባይዋም የሚገኘው በአገራችን ብቻ ነው። አንዳንድ ፈላስፎች ዜጎች/ሰዎች ፀባያቸውን የሚቀዱት አደጉበት አካባቢ ካሉ የዋና ዋና ተክሎች ወይም እንስሳት ጠባይ ነው ይላሉ። ወደ ማህበራዊ ስነልቦና፣ ወደ አንትሮፖሎጂ፣ ወደ ሌላ የተወሳሰበ ጉዳይ መጠምዘዝ አቁመን እግዜር አደይን ሲሰራት ምን ቢያቅድ ነው? ብለን የምናብ፣ የጥርጣሬና የኑሮአችንን ጠረን ተደግፈን ጥያቄ እንጠይቃለን። ይህቺ አበባ ችላ ያልነው አንድ ዋና ጠባይ አላት፤ እና ያ ጠባይዋ ምንድን ነው?” አሉና ጥቁርና ቀይ ዘንባላ ሰንበሮች የተሳለበት ክራቫታቸውን፣ ምንም ባይጎልበትም፣ እንደ መዳበስ አድርገው አስተካከሉ። “ምን የተለየ ነገር አላት?“ ብለው ደግመው ጠየቁና መልስ ፍለጋ በዐይኖቻቸው ክፍሉን ማተሩ። ጎኔ የምትቀመጠው አራዳ ነኝ ባይ ትሁት ባሌማ ወደ እኔ ዞር ብላ በጆሮዬ ‘ምንድነው?’ አለችኝ። ‘ቢጫ መሆን’ አልኳት። አፏን በእጇ ጋርዳ ያለ ድምጽ ሳቀች። ቲቸር ሰለሞን አለበል፣ በቅጽል ስማቸው ‘ሼክስፒር’ የአስረኛ ‘H’ ክፍል ተማሪዎችን ሁሉ ያደከመንን ‘አርአያ’ የተባለ ልብወለድ መፅሐፍ ከጠረጴዛቸው ላይ እንደ አሰር ስራ በፈታ እጃቸው ወደ ጎን ገፉት። ከዛም መልስ ያልሰጣቸውን ተማሪ ከዳር እዳር ገረመሙና፡ “የአደይ አስገራሚነቷ የማስታወስ ስልጣንዋ ነው” ብለው ክራቫታቸውን ድጋሚ ዳበሱ። ሁላችንም ባንሆንም ብዙዎቻችን ለአባባላቸው ምርኮ ሆነን በአግራሞት ትንፋሻችንን ዋጥን። ኮስተር ብለው ቀጠሉ፡ “በበጋ በፀሐያማው ወቅት የአገሪቷን ተራራና ሸለቆ የሞላው ባሕር ዛፍ፣ እሾህ፣ ዝግባ፣ የሆነ የዛፍ ጉቶ፣ የተሸረሸረ አፈርና አመዳም ቢጫ ሳር ነው። ሶስት ወር ክረምት ሆኖ ሲጠናቀቅና መስከረም ሲገባ የምንረግጠው መሬት ሁሉ በአደይ አበባ መፍካት ይጀምራል፡፡ የት ነበሩ አበቦቹ አስራ አንድ ወራት ሙሉ? አደይ አበባን ለሁለት ከፍለን አድገናል። እነዚህም የመሰወሯና የመፍካቷ ናቸው። መስከረም ወር መጨረሻ አደይ አበቦች አይታዩም፤ እዚህ እዛ አንዳንድ ሊኖሩ ይችላሉ፤ ብዙም ሳይቆይ ሁሉም ይደርቁና ይሰወራሉ። ግን ከመሰወራቸው በፊት ምን አድርገው ነው?” አሁንም መልስ ጠበቁ፤ የመለሰ አልነበረም። ቀጠሉ፡ “ከመሰወራቸው በፊት ተፈጥሮ በሰጠቻቸው ሕግና ስጦታ መሰረት፣ ዘራቸውን አሉበት አካባቢ ረጭተው ነው። የአደይ አበባን ዘር የማታውቁ ከሆነ ይሄውና እዩ” አሉና ይዘው ያመጡትን፣ እውስጡ ጥቁር ነገር ያለበት፣ ለዚህ ብለው ያዘጋጁት የተከደነ የማርመላታ ብርጭቆ ፊት ለፊት ለተቀመጠው ‘ምህረተአብ’ ለተባለ አንድ ኋደኛዬ ሰጡት። ምህረተአብ የብርጭቆውን ይዘት ሳያይ በንቀት ቄንጥ ወደ ጀርባው አሳለፈው። ‘ቲቸር ሼክስፒር’ አተኩረው አዩትና ንግግራቸውን ቀጠሉ፡ “እንደምታዩት ጥቋቁር ሆነው ይህቺን የሚያካክሉ ናቸው” እጃቸውን ከፍ አድርገው ሊያሳዩን የሚሞክሩት ቅንጣት፣ በአመልካች ጣታቸውና በአውራ ጣታቸው ተቆንጥጣ የተያዘች ስለሆነች፣ ጀርባ ላለነው ልጆች በፍፁም አትታየንም። ለእሳቸውም የምትታይ አይመስለኝም፤ ምክንያቱም ‘ይህቺ’ የተባለች አመልካች ተውላጠስም አእምሮአቸው ውስጥ ያለችውን ቅንጣት ብቻ መጠቆም የምትችል ናት። “እንደምታዩት እነዛ ኑግ የመሳሰሉ ዘሮቿ ከወደቁበት መሬት እያሉ ለሰው ዐይን አይታዩም፣ በሰውም እጅ አይዳሰሱም። ሰለማናያቸውና ስለማንዳስሳቸው ይኑሩ አይኑሩ ሁላችንም አናውቅም። በላያቸው እንረማመዳለን፣ ወፎች ይለቅሟቸዋል፣ አሞሮች በልተው በኩሳቸው በኩል እንግዳ መሬት ላይ አርቀው ይጥሉአቸዋል።” (ሁለት ልጆች ሳቁ) “ከብቶች ሳሩን ይግጣሉ፣ ሲግጡም የአደዮቹን ደቃቃ ዘሮች አብረው ከሳር ጋር ይበሉአቸዋል፣ በከብቶቹ እበት ውስጥ ሆነው በረት ዙሪያ መፍኪያ ቀናቸውን ይጠብቃሉ። ምናልባትም ከጭቃ ጋር ተቦክተው መደብ ይሰራባቸዋል፣ ወለልና ግድግዳ ይመረግባቸዋል፣ ይለሰንባቸዋል፣ ኩበትም ሆነው ዳቦ ይጋገርባቸዋል፤ በጫማችን ከቦታ ቦታ እናንከራትታቸዋለን፣ የበልግ ጎርፍ ጠርጎ ተሸክሞ የትም ይጥላቸዋል፣ የግንቦት ፀሐይ ስር ይቃጠላሉ፣ በጥቅምት ውርጭ ይታፈናሉ፣ በነፋስ ከወረዳ ወረዳ እየተነዱ ይንገላታሉ፣ ብዙ ወሮችን በፈተና መሃል ድምፃቸውን አጥፍተው ይቆያሉ፣ እናም በሐምሌ ዶፍ ከመደምሰስ አልፈው በነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ወርቅ መስለው ያብባሉ። ትክክል የውሃ ብዛትና አርጥበት፣ ትክክል አነፋፈስ ሲያጋጥማቸው፣ ከተሰወሩበት ብቅ ብለው በአስደናቂ መልክ ይፈካሉ። ይሄ የማስታወስ ስጦታ ነው። የአደይ ውበቷ ልክ ሄዳ መምጣቷ ነው። ጠቢቡ ሰለሞን የተባለው ሰው በመፅሐፍ ቅዱስ ‘አንደ ገብረጉንዳን ሁኑ’ ይላል። ምናልባት ሰለሞን እንዲህ የተረተው ጉንዳናም አገር ስለኖረ ይሆናል። ምናልባትም ከሰማርያ ወይዛዝርት ጋር ሲዳራ በመጎናፀፊያው የጉንዳን ሰልፈኛ ገብቶ እየነከሰ ከሴሰኛነቱ ስላናጠበው ለኑዛዜ ያዘጋጀው ምሳሌ ይሆናል። እሱ አያገባንም። እኔ ግን እላችኋለሁ እንደ አደይ አበባ ሁኑ። ሰማችሁ? ምሳሌ አድርጉኝ ብላ ስንት ዘመን ተለማመጠችን? በዚህ ምሳይ ምን ልበላችሁ? አደዮች ቢጫቸው የተመልሶ መምጣት የዳግም መወለድ ምልክትነታቸው ነው። የዚህ አይነት ሕልም ያለው ማነው? ለመሆኑ ምሳሌዋን አስበን እናውቃለን? ከዐይነግቡ የመስከረም ተራሮች ውጭ ያቺን አበባ እንደ ፈላስፋ በእጃችን ይዘን ‘ማነሽ?’ ብለናታል? በየአመቱ አንደ እሷ የማይሞት ቃልኪዳን አንገባለን? አደይ በመምጣቷና በመጥፋቷ መሃል ያለው እርቀት አንድ አመት ሳይሆን አንድ ሰአት ሳይሆን ወይ አንድ ደቂቃ የማስታወስ ብርታት ነው። እናንተ የአስረኛ ክፍል ተማሪዎች ሆይ ካለፈው የምታስታውሱት ቀለምን ብቻ ነውን? “አደይን እኛ ብንረሳት ታስታውሰናለች። በአጠገቧ ስናልፍ ያረፈባት ጥላሞታችንን ታስታውሳለች። በሰማይ በላይዋ የሚበሩትን ወፎች ሁሉ ቁጥራቸውንና የላባቸውን ህብረ ቀለም ታስታውሳለች። የበቀለችበትን አፈር ቅላት፣ ንጣትና ጠይምነት ታስታውሳለች። ባንቀርባትም ከሩቁ የሰማችውን የልጃገረዶች ‘አበባዬ ሆይ’ የመስቀልንም ‘ኢዮሃ አበባዬ’ ትሰማለች እና እነሱንም ታስታውሳለች። እያንዳንዷ አበባ የበቀለችበት አካባቢ የሚኖሩ ሰዎችን ስም ታስታውሳለች። ለዚህም እላችኋለሁ በመስከረም ወር ወገኖቻችሁን ጮክ እያላችሁ በስማቸው ጥሩአቸው። በፌሽታ የፈሰሰ ጠላን ጠብታውን ታስታውሳለች። የጠብታው ድምፅ ሳይቀር። ከእናቱ የሚጠባ ልጅ የሚያወጣው የጉሮሮው ድምፅ አይቀራትም፡ እሱን ሁሉ ታስታውሳለች። እሷን ሁኑ። መሳ ለመሳ እሷን ሁኑ።
1 069
6
لا يوجد نص...
910
7
በእውነት ያልተገነባ ህሊና አይታመንም፤ በአመክንዮ ያልታነፀ ልብ ዋሾ ነው፡፡ (The Science of Becoming Better) (እ.ብ.ይ.) ሰው ሁሉን ነገር ስለማያውቅ በሁሉም ነገር ምክንታዊ ልሁን ቢል አይችልም፡፡ በማናውቀው ነገር ምክንታዊ መሆን አይቻለንም፡፡ ምክንያት የምንደረድረው፣ ማስረጃ የምንቆጥረው፣ አስረጂዎችን የምናቀርበው ነገርየውን ስንገነዘበው ነው፡፡ በማያውቁት ነገር ምክንያት የሚደረድሩ ሰዎች በጨበጣ ቁማር እንደሚጫወቱ ዓይነት ሰዎች ናቸው፡፡ ለምናውቀው ነገር እንኳን በቂና ትክክለኛ ምክንያት መደርደር መቻል በራሱ ማስተዋል ይፈልጋል፡፡ ብዙ ተምረውና ተመራምረው ምክንያታዊ ያልሆኑ ሰዎች የትየለሌ ናቸው፡፡ በጣም ያውቃሉ የምንላቸው ብዙዎቹ ሰዎች ለምክንያታዊነት አይገዙም፡፡ ስለአመክንዮ የሚያስተምሩና የሚደሰኩሩትም ራሳቸው ምክንያታዊ አይደሉም፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹አትስረቅ ብለህ የምትሰብክ ትሰርቃለህን?›› የሚለው የሚናገሩትን የማይተገብሩ፤ የሚሰብኩትን የማይኖሩበትን ሰዎችን ለማስጠንቀቅ ነው፡፡ መተንተንና መገንዘብ የተለያዩ ነገሮች ናቸው፡፡ ማወቅና ማድረግ አይገናኙም፤ መምሰልና መሆን አንድ አይደሉም፡፡ የሚመስሉ ነገር ግን ያልሆኑ ሺ ናቸው፡፡ በንድፈሃሳብ ደረጃ የምናውቀውን በተግባር ልንቀይረው ስንሞክር የሚከብደን ማወቅና መተግበር የተለያዩ ነገሮች በመሆናቸው ነው፡፡ የዓለማችን ታሪክ በአስቂ፣ በአስደናቂ፣ በአሳዛኝ፣ በግራአጋቢ እና እንግዳ በሆኑ ነገሮቸ የተሞላ ነው፡፡ አይዛክ ኒውተን ህይወቱን በሙሉ የፈላስፋ ድንጋይ (Philosopher’s stone)ን ሲፈልግ ነው የኖረው (የፈላስፋ ድንጋይ ወይም Philosopher’s stone ማለት የኬሚስትሪ፣ የፍልስፍና፣ የሚስጥራዊነት (Mysticism) እና የመንፈሳዊነትን ዕውቀት አጣምሮ የያዘ ጥበብ ነው)፡፡ ኒውተን የፈላስፋን ድንጋይ የሚፈልገው ብረትን ወደወርቅ የሚቀይር የአንጥረኝነት እውቀት ፈልጎ አይደለም፡፡ የእሱ ፍላጎት በዘመኑ የፈላስፋን ድንጋይ ያገኘ ሰው የትኛውንም ህመም የመፈወስና ዕድሜን ለማስረዘም የሚረዳ ጥበብ ባለቤት ይሆናል የሚል እምነትና አስተሳሰብ ስለነበረ ነው፡፡ ቶማስ ኤዲሰንም የራዲዮአክቲቭ (Radioactive) ቴክኖሎጂ የትኛውንም ህመም እንደሚፈውስ ሲናገር ነበር፤ ነገር ግን የቅርብ ረዳቱ የነበረው ክላረንስ ዳሊ (Clarence Dally) የተባለ ሰው በራዲዬሽን ቆስሎና ተሰቃይቶ ከሞተ በኋላ ‹‹ስለራጅ ወይም ስለኤክስሬይ አታውሩኝ፤ እሱን ነገር እፈራዋለሁ›› በማለት ሃሳቡን ቀይሯል፡፡ የአፕል ኩባንያ መስራች የነበረው ስቲቭ ጆብስ ደግሞ አትክልት አዘውትረው የሚመገቡ (Vegan) ሰዎች ዘወትር መታጠብ (regular bathing) አያስፈልጋቸውም ይል ነበር፡፡ እነዚህ ሁሉ ሃሳቦች በዘመናዊው ሳይንስ ያልተረጋገጡ ስሁት ሃሳቦች ነበሩ፡፡ እነዚህ ሰዎች በሙያቸው የተጨበጨበላቸውና አንቱታን ያተረፉ ናቸው፡፡ ነገር ግን ሰዎች ናቸውና ሁሉን ያውቁ ዘንድ አይችሉም፡፡ ይሄ የሆነው ሰው ስለሆኑ ብቻ ነው፡፡ የትኛውም ሰው የሚያውቀው አንዱን ነገር የሁሉም ነገር መፍትሄ አድርጎ የመመልከት ኢ-ምክንያታዊ አባዜ አለበት፡፡ በዓለማችን የጤና ዶክተሮች ራሳቸውን የሁሉ ነገር አዋቂ አድርገው ይመለከታሉ፡፡ የህግ አዋቂዎችም የዚህ አመለካከት ሰለባ ናቸው፡፡ ኢኮኖሚስቶቹም ሐገር የሚያሳድገው የነሱ እውቀት ብቻ እንደሆነ አድርገው ይደሰኩራሉ፡፡ ሁሉም እንደየሙያው ትክክሉ የእሱ ግንዛቤ ብቻ እንደሆነ መናገር የተለመደ ነው፡፡ አዋቂ፣ ምሁር የምንላችው፣ ከተራው ሰው በተለየ የክብር ወንበር የምንስብላቸው ሰዎች በትናንሽ ሃሣቦች ሲወድቁ፤ ኢ-ምክንያታዊ ሲሆኑ ተመልክተናል፡፡ ብዙ የምንጠብቅባቸው፣ ሀገራችንን አደራ የሰጠናቸው ሁሉ አድሏዊ ሆነው ከምክንያታዊ ህግ አፈንግጠው እውነትን ሲጨፈልቁ፣ ፍትህ ላይ ሲረማመዱ አይተን ታዝበናል፡፡ ስለአንድ ነገር ያለን ዕውቀት ስለሁሉም ነገር ዋስትና እንደማይሰጥ ለማወቅ አስተዋይ ሰው መሆን ብቻ በቂ ነው፡፡ ዛሬ ያለን ዕውቀት እንኳን የነገ ዕውቀታችንን አያረጋግጥም፡፡ ዕውቀት ልክ እንደሰው ያድጋል ይመነደጋል፡፡ በትናንትና እና ዛሬ ዕውቀት መኩራራት የማይቻልበት ጊዜ ላይ ደርሰናል፡፡ ሰውም ያለፈው ላይ ተጣብቄ እቀራለሁ ቢል ከዘመኑ ጋር እኩል መራመድ አይችልም፡፡ ሁሉም ነገር እንደጅረት ወደፊት ይፈስሳል፡፡ አንድ ወንዝ የተለያየ ውሃ እንደሚያፈስሰው ሁሉ ሰውም የተለያየ ሃሳብ እያስተናገደ ነው ወደፊቱ የሚነጉደው፡፡ ጊዜ የሚያመጣው፤ ጭንቅላት የሚያፈልቀው አዲስ ነገር አያጣም፡፡ ያለፈውን የሚያስረጅ፣ የዛሬውን የሚሽር፣ የዕለቱን የሚያድስ አዲስ ዕውቀት ዕለት ዕለት ይመነጫል፡፡ የእውቀት ምንጩ አይደርቅም፡፡ ጥንታዊው የግሪክ ፈላስፋ ሄራክሊተስ ‹‹ተፈጥሮ በማያቋርጥ ፍሰት ውስጥ ነው ያለው፣ ዓለም እንደጅረት ቁልቁል ይፈስሳል›› ብሎ ያምናል፡፡ የሰው ዕውቀቱ፣ ሃሳቡ፣ ስሜቱ ወጥ በሆነ መንገድ ይለዋወጣል፡፡ መለዋወጥ ቋሚ ተፈጥሮው ነው፡፡ ጊዜ ሊያቆመው ወይም ሊመልሰው አይችልም፡፡ ሄራክሊተስ ‹‹ማንም አንድን ወንዝ ሁለት ጊዜ ሊሻገር እንደማይችለው ሁሉ ሰውም አንድ ዓይነት አስተሳሰብ አይኖረውም፡፡ የወንዙ ውሃ አንድ እንዳልሆነ ሁሉ ሰውም አንድዓይነት ሆኖ አይቀጥልም (“No man ever steps in the same river twice, for it’s not the same river and he’s not the same man”)፡፡›› የሚለው ለዚህ ነው፡፡ ወዳጄ ሆይ… ሃሳብ ወላዋይ ነው፤ ስሜት አሳሳች ነው፡፡ ሕሊና አስመሳይ ነው፤ ውሸቱን እውነት አስመስሎ ያቀርባል፡፡ ደመነፍሳቸውን ብቻ ተከትለው ገደል የገቡ መዓት ናቸው፡፡ የገዛ ፍላጎታቸው ያጠፋቸው ተቆጥረው አያልቁም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ለኢጓችን የሚስማማ ሃሳብ እስካገኘን ድረስ እውነትና አመክንዮን ረግጠን እንረማመድበታለን፡፡ እውነት ከሚሰጠን ይልቅ ስሜት የሚሰጠንን እናምናለን፡፡ ደስታን ብቻ ስናሳድድ ሰላም፣ ፍትሐዊነትና እውነት ያመልጡናል፡፡ ሰላም በደስታ ውስጥ እንደማይገኝ አይገባንም፡፡ ደስታ ቅፅበታዊ ነው፤ ሰላም ግን ቋሚ ነው፡፡ ከደስታ ይልቅ ሰላምን የያዘ ህይወቱ ብሩህ፣ አዕምሮው ንፁህ ይሆናል፡፡ ሰላም ከእውነት፤ ደስታ ከስሜት የሚወለዱ ናቸው፡፡ ሰላም የሌለው ደስታ አለ፤ እውነት የሌለው የአዕምሮ ሰላም ግን አይኖርም፡፡ የአዕምሮና ሰላምና የልብ ደስታ ስሙም የሚሆኑት እውነት ሲኖራቸው ነው፡፡ ያልተፈተሸ ሃሳብ፣ ልቅ ፍላጎትና ያልሰከነ ስሜት አደጋው ብዙ ነው፡፡ ውስጥህ የነገረህን ብቻ ማመን ጥሩ አይደለም፡፡ ዓይንህ ያየው፣ ጆሮህ የሰማው፣ አፍንጫህ የማገው፣ ምላስህ የቀመሰው፣ እጅህ የዳሰሰው፣ ደመነፍስህ ሹክ ያለህ ሁሉ እውነት አይደለም፡፡ መጣራት፣ መፈተሸ፣ ጥሬና ብስሉ መለየት፣ መበጠር፣ ሃሳቡን ማንከሽከሽ፣ ስሜቱን አስክኖ ጥቅምና ጉዳቱን መለየት ያስፈልጋል፡፡ ውስጥህን ማመን ደረጃ ላይ የምትደርሰው ለውስጥህ የተለያየ ሃሳብ ስትመግበውና በእውነት፣ በምክንያት፣ በፍትህና በሰላም ስትገነባው ነው፡፡ በእውነት ያልተገነባ ህሊና አይታመንም፤ በአመክንዮ ያልታነፀ ልብ ዋሾ ነው፡፡ ምክንያታዊ ሕሊና፤ አመዛዛኝ ልቦና! ቸር ጊዜ! ------------------------------------ © እሸቱ ብሩ ይትባረክ (እ.ብ.ይ.) ሠኞ ሐምሌ ፳ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም.
1 210
8
لا يوجد نص...
1 099
9
لا يوجد نص...
1 561
10
ትቅርብን ጨረቃ! (በድሉ ዋቅጅራ) እሷ እያለች፣ ‹‹ዳቦ ናት›› ምናልባት፣ ከራባት፣ . . .. ልትበላት፡፡ እሱ ሲል፣ ‹‹የብረት አሎሎ¹›› ሊቀጠቅጣት አግሎ፡፡ እንደጦር ሊወረውራት፤ ምናልባት፡፡ እና የመጨረሻ፣ መጨረሻ፤ እሷ ሌማት²፣ እሱ መዶሻ፤ ይዘው፣ ሲቋምጧት እያየሽ፤ ‹‹ጨረቃስ›› ብለሽ ታኮርፊያለሽ? ይልቅ ሳቂልኝ ውዴ፣ ትቅር ጨረቃን ተያት፤ ትገለጥበት አንደበት፣ ትታይበት መልክ የቸገራት፤ የየነብሳችም ስእል፣ የመሻታችን ፍቺ ናት፡፡³ ተያት፡፡ ------------- ሚያዝያ 2017 (በቅርብ የሚታተም) . . . Keep the Moon Away! (By Bedilu Wakjira) While she claims, "It's a loaf of bread"— Perhaps, Starving, to feast upon it. While he calls it "an iron cannonball"— To heat and hammer it down, Or perhaps, to hurl it like a spear. And so, In the end, the very end— As you watch her with her basket, And him with his hammer, both coveting it... Will you still pout and ask, "What about the moon?" Instead, laugh for me, my love, and leave the moon alone; It lacks the tongue to speak itself, The true form through which to be seen. For it is merely a canvas of our souls, A reflection of our own desires. Let it be. ---------- April 2025 Translation: Google Gemini ¹ "የብረት አሎሎ" (Iron Cannonball / Iron Ball): Refers to a heavy iron projectile or ball used in forging or warfare, emphasizing how different minds reduce beauty to raw, functional, or destructive matter. ² "ሌማት" (Basket / Lemat): The traditional woven basket used for serving injera, capturing the hunger and consumer mindset in the metaphor. ³ "የየነብሳችን ስእል፣ የመሻታችን ፍቺ ናት": A profound closing thought—the moon has no objective meaning of its own in human eyes; it is simply a projection ("portrait/canvas") of each person's inner hunger, desire, or state of mind.
2 069
11
لا يوجد نص...
1 679
12
መልክዐ ምስል በሚለው ድርሰቱ በቅዥት እና በእውን አለም መሀከል ያለውን ልዩነት ይጠይቃል። ሰው ስሆን ቢራቢሮን ነበርኩ ወይስ ቢራቢሮ ሆኜ ነው ሰው መሆንን ያለምኩት? ሲል እናገኘዋለን ገፀባህሪው በዚህም እውነት ምንድነው? እውነታው የቱ ነው? እያለ በፍልስፍናው ዘርፍ ስነእውቀት( epistemological) ጥያቄ ያነሳል። ሪኔ ዴካርት የተጠራጣሪነት ( skepticism ) መንገድ አሰተዋውቋል። ሁሉንም ነገር ከመጠርጠሩ የተነሳ ይሄ እውነት የሚመስለኝ አለም ቅዠት ቢሆንስ የተማርኩት አወቅኩት የምለው ነገር ሁሉ የሚጠረጠር አለመሆኑን እንዴት አውቃለሁ ይላል። የሲራክ ጥርጣሬ ጨለማ ከወረሰው ሽሽግ ጨቅላ ማንነታችን ( ጥላ) እና በገላችን መሀከል የሚዋዥቀው መልክዐ ምስላችን ላይ ነው። ቀቢፀ ተስፋ፣ መነጠል፣ ከዘመን ጋር መኳረፍ የመሳሰሉ የተብሰልሳይ እጣፈንታን በብዛት ይዳስሳቸዋል። ማህበረሰብ እና የማህበረሰብ ዘልማዳዊ አኗኗር፣ የጋራ የስሜት ቁስሉ(collective trauma)፣ በትውልድ መሀከል ያለ ክፍተት በሶምሶማ የተረገጡ ዳናዎች ናቸው። አፃፃፉ ምስል ገላጭ ቢሆንም እያንዳንዱ ምስል የራሳቸው ሚታዊ አንድምታ ያላቸው ይመስላሉ። ሚታዊተረኮችን የምናቡ አጋፋሪ አድርጎ ተጠቅሟቸዋል። አብዛኞቹ ታሪኮች በተምሳሌታዊ ዘይቤየቀረቡ ናቸው። አሁንም የቤቷ ከፈፍ ላይ የቁራ ድምፅ ይሰማታል።እየቆየ እየቆየ ያንቋርራል። በመሀል ዝምታ ሸማውን አንጥፎ የድምፅ እርጥባን እየተመፀወተ እልፍ ይላል። የእረፍት የአድባራቱን ስም በጥንቃቄ መርጦ እየጠራ የምስጋናውን ቡራኬ በለጋ እጁ ይለግሳል። በርጥብ ልቡ ፈገግ ይላል።የመጨረሻውን የቁራ ድምፅ ተከትላ ቀና ስትል ጥቁር ዓይነ ድፍርስ ፍጡር ጋር ዐይን ለዐይን ተገጣጠሙ። ገፅ 36 ስደተኛ ወንዞች ከሚለው አጭር ታሪክ ቴዎድሮስ ገብሬ እንደሚለው ሚት ለቋንቋ አልገብር ያሉ ዲበአካላዊ ( metaphysical) የሆኑ ጉዳዮች ዘይቤያዊ መገለጫ ነው። ዘይቤ ደግሞ ቋንቋ እና ሚት የሚሰናኙበት ኋልዮ መሆኑን እንደ ካሲረር ያሉ የሚታዊ ቋንቋ ልሂቃን እንደሚመሰክሩ ይናገራል። ሲራክ ሚታዊ ተረኮችን ዘይቤያዊ(metaphorically) በሆነ መንገድ በማሰናኘት የማህበረሰቡን የጋራ ደመነፍስ ተምሳሌታዊ ቋንቋ የመረዳት አቅሙን አስመስክሯል። ድርሰቱ ጠንከራ ሀሳቦዎችን፣ ተምሰልስሎቶችን፣ ቁጭቶችን በውብ ቋንቋ በዚህ ልክ መፃፍ እንደሚቻልም ያየሁበት ነው። Reviewer : © Yodit Ammanuel is an associate editor at © Think Ethiopia.
2 071
13
ርዕስ : ሶምሶማ ደራሲ : ሲራክ ወንድሙ ዘውግ: ልቦለድ የሕትመት ዓመት: በዮዲት አማኑኤል የሰውን ልጅ ሁለት ነገሮች ይመሩታል። ፍርሀት እና ፍላጎት ሰው ህይወቱን ሙሉ ፍርሀቱን ሲሸሽ ፍላጎቱን ሲያሳድድ ይኖራል። ፍላጎቱ ከየት መጣ ብትሉኝ ከፍርሀቱ የተፈለፈሉ ግልገሎቹ እንደሆኑ ልነግራችሁ እችላለሁ። ዋነኛውም የሞት ፍርሀቱ ነው። ፍርሀቱስ ከየት መጣ ብባል ግን መልሼ ከፍላጎቱ ይሆናል መልሴ። ዞሮ ዞሮ በህይወት የመኖር ፍላጎቱ መልሶ ከፍርሀቱ ጋር ያጋፍጠዋል። እነዚህ በአንድ ቀጭን ማዕዘን አልባ ገመድ ላይ የተሰፉ ወፋፍራም ሀቆች ናቸው። ሀቆቹ መነሻም መቋጫም የላቸውም። የተነሳንበት ከመሰለን ጋር ተነስተን አንዴ ሽቅብ ሌላ ጊዜ ቁልቁል እየተንደረደርን በደረስንበት ሁሉ የት ጋር እንዳለን ቢጠይቁን የምንመልሰው የለንም። ለህይወት ማቆሚያዋ ሞት የሚል መታጠፊያ ለማበጃጀት ብንሞክርም ይሄ ሞት ግን ከህይወት ጋር ወጥ በሆነ አንድ ቀጥታ መስመር የተሰፋ ይመስላል። ታድያ ይሄ መከረኛ የሰው አእምሮ ከመነሻ ወደ መድረሻ ፣ከማዕዘን ሌላ ማዕዘን፣ ከቀኝ ወደ ግራ ፣ከላይ ወደታች ካልሆነለት ጭንቅ ነው። ከጭንቁ የተነሳ ሰው ብዙ ጠየቀ ህይወት ምንድነው፣ ለምን መጣሁ፣ሞትስ ምንድነው? እያለ የህልውና ጥያቄዎችን ሲያዘንብ ኖረ። ይሄን የተረዳው አልበርት ካሙ የሰው መዋቅራዊው እና ምክንያታዊ የሆነው አእምሮ ይህቺ ቅርፅ አልባ እና ምክንያት የለሽ ሁለንታ ውስጥ ምክንያት የመፈለግን አብዘርድነት አስረግጦ ይነግረዋል። እንግዲያውስ ከአንድ ነጋዴ ጋር በዋጋ ተደራድረህ የመጨረሻውን ዋጋ እቅጩን ያረዳህ እንደሆነ እና ኪስህን የጠየቅከውን ለመክፈል በበቂ ሁኔታ ካላደለብክ ከዛ ነጋዴ ጋር ጀንበር ወጥታ እስትገባ ስትከራከር አትውልም። ሌላ ኪስህን ያገናዘበ ሱቅ ገልመጥ ማድረግህ አይቀርም። ሞት የሁሉም የጊዜ ዋንጫ ላይ በየተራ የሚቀዳ ፅዋ ነው። ለሰው ልጅ ይሄ ፅዋ መራራ እና አይቀሬ ነው። የህይወት በሞት መቋጨት ደግሞ ወለፈንዲ ነው። ከዚህ ወለፈንደነት ለመሸሽ ሞትህን የተለያየ መልክ እያለበሱ የሚያቀርቡልህ ሶስት ሱቆች አሉልህ። አንደኛው እንደመጀመሪያው ነጋዴ ናቸው ሞትን አንተን ሊያጠፋ ጥርሶቹን እያፏጨ እንደመጣ እስቀያሚ እንግዳ ያቀርቡልሀል። ሞት ሞት ነው ያው ሌላ ማሽሞንሞን አያውቁም። ስትሞት ትጠፋለህ ነው።የሆንኩትን ሁሉ የሆንኩት ለምንድነው? የመኖር ትርጉምስ ምንድነው? እንዲው እንደተራ ነገር መጥፋት? እንዲሁ እንዳልተፈጠረ መረሳት? ለሚለው ጥያቄህ ምላሻቸው አዎ ነው። እነዚህ የህላዌነት ፈላስፎች እንደነ ኪርጋርድ እና ሳርትሬ ያሉት ፈላስፎች ናቸው። ቋሚ ትርጉም አሰሳህን ትተህ የራስህን ትርጉም እንድትፈጥር ግብዣ ያቀርቡልሃል። ምክንያቱም ሞትህም ህይወትም ቋሚ ትርጉም የላቸውም። ግብዣቸውን ለመቀበል ግን ፈርጠም ያለ ጫንቃ ያስፈልግሀል። ካላዋጣህ እንዳቅምህ ወደ ሌላኛው ሱቅ ጎራ ትላለህ። ለሰው ልጅ ከዚህ በላይ አደገኛ እና አስፈሪ ነገር የለማ። ሁለተኞቹ ነገሩን አያከብዱብህም ሞትን ብቻውን አያቀርቡልህም ይልቅስ ትንሽ አስውበው ከሞት በኋላ ህይወት የሚል ባጅ ይለጥፉበታል። ከመጀመሪያዎቹ ይሻላል ቢያንስ የዋና ተዋናይነቱን ሚና አትቀማም። ግን ቢሆንም ሞትን ልትወደው እና በሙሉ ልብህ ልትቀበለው አትሻም። በስብሀት 5_6_7 ላይ ሞትና አጋፋሪ እንደሻው በምትል አጭር ታሪክ የሞት አፋፍ ላይ ያለውን አጋፋሪ እንደሻውን አቡዬ ይጠይቁታል። የብርሀን ሰረገላ አለኝ ሳትሞት ወደ ሰማይ ቤት ልውሰዶት። እዛ ርሀብ የለ፣ ብርድ የለ፣ሀሩር የለ፣.....አውቃለሁ አጋፋሪ ይመልሳሉ። እንደኔ እንደኔ ግን እኔን ወደ አዲሳባዬ ብትመልሰኝ በወደድኩ ይሉታል። ከሰማይ ቤት አዲስ አበባ ይሻልሀል? አስር እጅ ይላሉ አጋፋሪ። ከማያውቁት መላክ የሚያውቁት ሰይጣን ነው ነገሩ።ሌላው ልክ ብዙሀኑ ሰው እንዲህ ቢሆንስ የሚል የተጨባጩን አለም ድንበር አሻጋሪ መሲህ ትፈልግ ይሆናል። ይሄኔ ደራሲ አለልህ በምናቡ አለም አፈናጦህ ያሻው ድረስ የምኞቱን ፈረስ ሰርጥ እያስጋለበ ያለከልካይ ያነጉድሀል። የገፀባህሪው አጋፋሪ እንደሻው የሞት ፍራቻ ጋሽ ስብሀት የራሳቸውን ፍርሀት ያንፀባረቁበት ድርሰት እንደሆነ ይጠረጠራል። እና አንዴ አለቤ ሾው ስብሀትን እንዲህ ሲል ይጠይቀዋል። እንደው ሞትን ትፈራለህ ይባላል? ስብሀትም መልሶ አንተስ? ብለው ይጠይቁታል። እውነት ነው በአጋፋሪ የተወከለው አንድ ነጠላ ስብሀትን ብቻ ሳይሆን ሁሉንም የሰው ልጅ ነው።ስብሀት ገ/እግዜአብሄር ይህንን የሰው ልጅ የሞት ፍርሀት አጋፋሪ እንደሻውን ታከው ተርከውልናል። አጋፋሪ በየጊዜው የሳምንት ስንቃቸውን የተሸከመች በቅሏቸው ላይ ተጭነው በየመንደሩ እየዞሩ እዛ አካባቢ ለቅሶ ወይም የታመመ ሰው ይኖር እንደሆን አሽከሮቻቸውን ይጠይቃሉ። ታድያ አንዳች ለቅሶ ወይም ሊሞት የሚያጣጥር በእዛ መንደር ውስጥ ያለ እንደሆን በሉ በሰላም ዋሉ ብለው ሌላ ሰላማዊ መንደር ፍለጋ ጉዟቸውን ይቀጥላሉ። ይሄ ሁሉ ሞትን ሽሽት ነው። በኋሏ እንደቀልድ የተጎነጯት የጠላ ትንታ ከሞት ደጃፍ አድርሳ ከቢሾፍቱው ቆሪጥ ጋር አቋምራ ትመልሳቸዋለች። ከሞት ደጃፍ ላይ በቆሪጥ ጨዋታ ተሽለኩልከው መመለሳቸው ያልተዋጠለት ሲራክ ወንድሙ ጋሽ አጋፋሪን ጅማ ወስደው ከደብተራው ተዋነይ ጋር ያጣምሩታል። በድህረ ዘመናዊ የአፃፃፍ ስልት ወስጥ የሚታወቀው Metatextual የአፃፃፍ ስልትን የሆነውን ቴክኒክ ተጠቅሞ አጋፋሪ እንደሻውን በተዋነይ እና አጋፋሪ እንደሻው ሜዳ ላይ ሲጫወቱ እናያለን። ይህም በሲራክ ተዋነይ እና አጋፋሪ እንደሻው ውስጥ ስለ ስብሀት ሞትና አጋፋሪ እንደሻው ድርሰት ማውራት። እዛ የሞት አፋፍ ላይ ከቆሪጥ ጋር አይሆኑ ጨዋታ ተጫውቶ እድሜውን ለማርዘም ያን ሁሉ ጦር መሳበቅ ምን አመጣው? ለቆሪጥ ያዘነለት ይመስላል። ገፀባህሪው እንደሻው የሞት ሙከራ ያደረሰብትን ደራሲው ስብሀትን ሲከስ እናየዋለን። ሲራክ በድርሰቱ ለገፃባህሪዎቹ በቀጥታ የተጋለጠ ደራሲ ባይሆንም በምናብ አለም እና በእውነተኛው አለም ያለው መስመር ተጣፍቷል። ይህም በድህረ ዘመናዊ አፃፃፍ ስልት የተለመደ ነው። ደራሲው አጋፋሪን የሞትን ድራሽ የሚያጠፋ ደብተራ ተዋነይ ጋር ያዛምደዋል። በእርግጥ የደራሲው ሲራክ ፍርሀት ከጋሽ ስብሀትም የከፋው ሳይሆን አይቀርም። የደራሲ ዋነኛ መሳሪያ ምናቡ ነው። የሲራክ ምናቡ ጥልቀት እና ሰፊ ነው። አጋፋሪን በስብሀት ምናብ አጨዋወት እንዲያኮርፍ ካደረገው በኋላ በራሱ የምናብ ሜዳ ላይ ያጫውተዋል። የእክሱም ሀውልት እና የላሊበላ ግንብ አሻግሮ አውሮፓ ላይ ተአምር ሊያሳየው፣የቻይና ግንብ ስር እስከመሽናት የሚያስጉዝ የኢ መዋቲነት የምናብ ሀዲድ ይዘረጋል። የአጋፋሪ የሞት ፍርሀት መቅበዝበዝ ያስጨነቀው ደራሲው እስከወዲያኛ የሞት መድሀኒቱን ሰጥቶ ሊገላግለውም የፈለገ ይመስላል። የቋንቋው ስነፅሁፋዊ ውበቱ እና ገለፃዎቹ ተዝቆ የማያልቅ የቃላት ቋት ከብዕሩ ስር ካለትዕዛዝ የሚፈልቁለት እንጂ ሀሳቡን ለመግለጽ ቃላትን የሚያምጥ ደራሲ አያስመስሉትም። ሶምሶማ ወደ 15 አጫጭር የሚሆኑ ታሪኮችን የያዘ ሲሆን እነዚህ ታሪኮች በስፋት ከሚዳስሳቸው የተለያዩ ጭብጦች ሞት እና ፍርሀት፣ የህይወት ትርጉም የመሳሰሉ ወሳኝ የህልውናዊ ( Existential) ጥያቄዎችን እያነሳ ይቆዝምባቸዋል።
1 560
14
لا يوجد نص...
1 258
15
◉ የእዮባ ጥያቄ [Missing someone ] እዮብ ምሕረተዓብ ዮሐንስ አምለሶም... ደፋር፣ ነገሮችን ሳያሽሞነሙን ወይደሞ ሳይሸፋፍን ፊት ለፊት የሚያስቀምጥ ፀሀፊ ነበር። የራሱን የስነፅሁፍ ዘውግ «ቀደዳ» ብሎ የቀደደ ነው። ነገሮችን በአዲስ መንገድ ለመመልከት ንቁ የሆነ አእምሮ ያለው... ጨዋታ አዋቂ ነው። በፅሁፎቹ እዮባ ራሱን መስሎ ራሱን ኮርጆ የዘለቀ ነው። የእሱ የግሉ ብቻ የሆኑ አገላለፆች ያሉት። «የዝንጆሮ ፌደራሊዝም... የኤቲስቱ ገብርኤል... ቀይ ሞንዳላ ...አትፍዘዝ ታመጣለህ መዘዝ...ጥሬ ሀቅ ነው ዋጠው!...» ብዙ ብዙ... ◉ ይሄ ሰው አንዲት መፅሐፍ ብቻ ሰጥቶን እንደሄደ ሳስብ እቆዝማለሁ። ግን ደግሞ ይቺው አንድ መፅሀፍ እንደ ዶላር የምትመነዘር ስራ መሆኗን ስረዳ እፅናናለሁ። «ቼ በለው!» በጣም ፀዴ መፅሐፍ ናት። ከዚች መፅሐፍ ደግሞ አንድ የሚያስገርመኝ ስቶሪ አለ። ደጋግሜዋለሁ ብዙ ግዜ። "Gender - of the Urban Context" ይሰኛል። የከተማ ህይወት በሴቶችና ወንዶች ግንኙነት ላይ ያለውን ተጽዕኖን ይፈተፍታል። የዘመናዊነት እና የማንነት ቀውስን ያስተነትናል። እና እኔ ቀደዳ ብቻ አድርጌ አላየውም። ጥናታዊ ፅሁፍም ይመስለኛል። እንዴት? ➊ ታሪኩ በአጭሩ ይሄን ይመስላል? ታሪኩ ሂሩት ስለምትባል የተማረችና በከፍተኛ የኃላፊነት ቦታ ላይ ስለምትሰራ ስኬታማ ሴት ይተርካል። ግና...ቅሉ...ህይወቷ በተከታታይ ውድቀቶችና ስብራቶች የተሞላ ነው። ● ሂሩት ከራሷ በታች ለነበረ ነገር ግን ጎበዝና ታታሪ ለሆነ ወንድ የትምህርትና የኑሮ ወጪውን በመሸፈን፣ አስተምራ አሰልጥና ሰው አደረገችው። እሱ ግን እግሩ ተውተርትሮ እንደቆመ ፍላጎቶቹና የሴቶች ምርጫው እየጨመረ ስለመጣ እሷን ክዶ ሌላ ጓደኛ ይዞ ጥሏት ሄደ። ​ ● በወንዶች ላይ ባደረባት ከፍተኛ ጥላቻ የተነሳ "Radical Feminist" ሆነች። ወንዶችን ማጥላላትና መጠየፍ ጀመረች። እዮብ ይሄንን የተሰማትን የወንድ ጥላቻ በአይረሴ ቃላት አስፍሮታል። «ብቻዋን አልቀረችም። መሰሎቿንም ፈላልጋ አገኘች... ባል፣ ጓደኛ፣ መልክ፣ ወጣትነት፤ ፈገግታ፣ ወግ፣ አመል Femininity፣ ደስታ፣ ፍቅር፣ ሰላም፤ ፈላጊ፣ ለካፊ፤ አሽኮርማሚ፣ ሞካሪ፣ አፍቃሪ ካጡ... ተናዳፊ ጊንጥ የመሰሉ ብስጩ ፌሚኒስቶች ጋራ ገጠመች:: የግሩፓቸው አባል ሆነች። ወንድ የባሰ ጠላች። አቤት አጠላል... ... አውራ ዶሮ ሴት ዶሮን ሲያሽኮረምም ካየች በድንጋይ ታባርረዋለች:: ባጋጣሚ መኪናዋ ተበላሽታ በታክሲ ተሳፍራ ስትሄድ ወያላው ትርፍ ሰው ለመጫን 'እሙ ትንሽ ተጠጊለት' ሲላት "እምቢ! ሴት ስለሆንኩኝ ነው አይደል?" ብላ ኡኡ ትላለች። እንዳው በስህተት እንኳ ትንሽ ዘነጥ ነገር ያለች መስላ ቢሮ ከሄደችና የሥራ ባልደረቦቿ በአድናቆት ዓይን ከሾፏት፡ this is harassment! ብላ ታምባርቃለች....በጠቅላላው የወንድ ፍጡር ጠላች!» ይለናል። ሆኖም አብረዋት የነበሩት ፌሚኒስቶች አንድ በአንድ ትዳር ይዘው ሲቀነጠሱ ተስፋ ቆርጣ ያንን መስመር ተወችው። [በወንዶች ተስፋ የቆረጡ አኩራፊ ሴቶች ወደ ፌሚኒዝም ባስ ሲልም Radical Feminist የመሆን እድል አላቸው? Maybe ●​ ከፌሚኒዝም በመቀጠል ፍጹም ወደሆነ መንፈሳዊ ህይወት ዞረች። እዚያም በቤተክርስቲያን ውስጥ መንፈሳዊ ሰው መስሎ የቀረባትንና የታመነ የመሰላትን ወንድ አምና ብር አበደረችው። እሱ ግን ገንዘቡን ይዞባት ወደ ውጭ ፈረጠጠ። ​ ● በአገር ውስጥ ወንዶች ተስፋ የቆረጠችው ሂሩት፣ "የሴትን መብት ያከብራል" በሚል እሳቤ ከአንድ የውጭ ሀገር ዜጋ ጋር ፍቅር ጀመረች። ነገር ግን ያ ነጭ ለትዳር ስትጠይቀው እሱ የሚፈልገው ጊዜያዊ መዝናኛ ብቻ ነበር። ● ​በመጨረሻም ሂሩት ብቻዋን ለመሆን ወስና፣ ከአንድ ያገኘችው ወንድ አርግዛ Single Mother ለመሆን ትገደዳለች። አታሳዝንም? ❷ የእዮብ ጥያቄ እዮባ የዚችን ሴት ታሪክ ሲቋጨው አንድ መሠረታዊ ጥያቄ ጠይቆ ነው። «ከተማሩና በትልቅ የሥራ ሃላፊነት ላይ ከሚገኙ ጨዋ ላጤ ሴቶች ይልቅ አለሌ፣ መሃይም፣ ጋለሞታ፤ ቅናተኛ፤ መልከ-ጥፉ፣ ወንድን አሰቃይ ወይንም ዱርዬ ሴት! ሲሆን አሪፍ ትዳር፣ ካልሆነም ቢያንስ መውደቂያ ባል አጥታ የማታውቀው ስለ ምንድን ነው?» አለም ላይ የሆኑ ሀቆች አሉ አይደል? እንዲሁ የምንስማማባቸው? ከአከባቢያችን ከዙሪያችን አስተውለን የምንቀስማቸው! ጥናት ያልተሰራባቸው! Data የሌላቸው! እዮብ እነዚህን ነው ፈልፍሎ ማሳየት የፈለገው። ሁሉንም ነገር በሪሰርች፣ በቁጥር...በግራፍ ብቻ መለካት አይቻልም። ​እውነት ሪሰርች ባይሰራበትም፣ በዙሪያችን የምናያቸው ተጨባጭ ሁኔታዎች የራሳቸው የሆነ ትልቅ Data ናቸው። እኔ በዓይኔ የማየው፣ በህይወቴ የማውቃቸው ሰዎች ታሪክ ከማንኛውም የዩኒቨርሲቲ ጥናት በላይ እውነተኛ ነው። ​ደመ-ነፍሳዊ መግባባት አላቸው። አእምሮአችን "መረጃ አምጣ?" ሳይለን ደመ-ነፍሳችን ወዲያውኑ "አያስፈልግም ማስረጃ። ልክ ነው!" ብሎ የሚቀበላቸው ናቸው። ● ያው ይሄንን የእዮባ ጥያቄ ስንመለከተው ሀቅነት አያጣውም። ​በእኛ ማህበረሰብ አስተዳደግ ወንድ ልጅ ሁልጊዜ በቤቱ ውስጥ መሪ እና የበላይ እንዲሆን ነው የሚጠበቀው። ሴቷ በጣም የተማረች፣ በኢኮኖሚ ራሷን የቻለች ስትሆን፣ የብዙ ወንዶች Ego ያነጥሳል። በርበሬ እንደሸተተው አፍንጫ። ​ያልተማሩ ወይም ራሳቸውን ካልቻሉ ሴቶች ጋር ሲሆን ደግሞ ወንዱ ሙሉ የበላይነቱን በቀላሉ ያገኛል። ሴቷ ሙሉ በሙሉ በእሱ ላይ ጥገኛ ስለምትሆን የሚሰማው የጀግንነት ስሜት ለትዳሩ መቆየት (ጤናማ ቢሆንም ባይሆንም) እንደ ሰበብ ሆኖ ያገለግላል። በሌላ በኩል ደግሞ ​ታሪኩ ላይ እዮባ "አለሌ" ወይም "ጋለሞታ" ያላቸው ሴቶች ወንዶችንም ህይወትንም እስኪበቃቸው እየሾሩ ከብዙ አንግል ስላዩዋቸው ከወንድ ልጅ የሚጠብቁት መስፈርት በጣም አነስተኛ ነው። ​ወንዱ ጥቂት ነገር ሲያደርግላቸው በቀላሉ ይረካሉ (ያንን ነገር አይጨምርም) ... ፍፁም የሆነ ወንድ አይጠብቁም። ​በአንጻሩ የተማሩት...ጨዋዎቹ ሴቶች ግን ከፍ ያለ የህይወት መርህና መስፈርት ስላላቸው፣ የወንድን ስህተት በቀላሉ አያልፉም። ይህ ጥብቅ መስፈርት ደግሞ ወንዶች ረጅም ርቀት አብረዋቸው ለመጓዝ እንዲፈሩ ያደርጋቸዋል። [ እዩባ መሠረታዊ ጥያቄ ነው ያነሳ አይመስላችሁም? ዛሬ ላይ ደግሞ ጉዳዩ ያሳስባል። ያው ​የስነ-ጽሑፍ ዋናው ውበትና ጥቅሙ ጥናትና ምርምርን መተካት አይደለም። ማህበረሰቡ እያየው ግን ደፍሮ የማይናገረውን ሀቅ መስታወት ሆኖ ማሳየት ነው። እዮባ እነዚህን ሀላፊነቶች ሲወጣ የነበረ ሰው ነው። © Mes Oud
2 162
16
لا يوجد نص...
1 672
17
ለዛሬ (ዕለተ ቅዳሜ) ዘፈኑን ያዳመጠ ሁሉ ጆሮ ሰጥቶ እንዲያደምጠው በማሰብ ይህን ያህል አልኩ። በጭፍን አስተያየት ተገፍቼ እንጂ ለወትሮዬ መጻፍም የሚቀናኝ ሰው አልነበርኩም። የተቀረውን ደግሞ አድማጭ ራሱ ያዳምጠውና ይፍረድ። ግን በዚህ ሁሉ ውስጥ ምን ብዬ አምናለሁ? አብረን ሠርግ ላይ አልተቀመጥንም ይሆናል፤ አብረንም አልተሠረግንም፣ አብረን ጨፍረንም አናውቅ። ግን አሁን ሁላችንም በአስቴር የተነሳ ቤተዘመዶች ሆነናል። በዚህ ሥራ ልክ እንደ ቅርብ አምቻዎችና ጋብቻዎች፣ እንደ ቅርብ ስጋ ዘመድ፣ ከያለንበት የዓለም ጥግ ሰብስባ፣ ወደ ሠርግ ትዝታ ማዕበል ወስዳናለች። ስሜታችንንም ንጣ አስነስታ አውረግርጋናለች። በአስቴር የሠርጌ ትዝታው ዳግመኛ ስራ ሁላችንም የምንተዋወቅ ቤተዘመዶች ሆነናል። ለጠሪያችን ለአክባሪያችን አስቴር ምሥጋና ይድረሳት። ድግሱን አጣፍጠው፣ ቀምመው፣ ተንጎዳጉደው፣ ኳኩለው ላሳመሩላት ባለሙያዎችና ሙዚቀኞች በሙሉ ለእነሱም ምስጋናችን የላቀ ነው! እሰይ አበጀህ አንተ የኛ ልጅ አንተ የኛ ልጅ... አስቴርዬ አንቺም እሰይ አበጀሽ። እሰይ አበጀሽ አንቺ የኛ ልጅ አንቺ የኛ ልጅ ባሳር ተገኘሽ በሺ አማላጅ። ጣፋጭ የቅዳሜ ውሎ ይሁንላችሁ። 🙏🏿🎵💙 — © ያፌት ተስፋዬ ( ጃፍ)፦ ስለ ጣፋጭ ገለፃህ እናመሠግናለን። ላንተም ሸጋ ቀዳሚት!🙏🏿
2 432
18
'የሠርጌ ትዝታው' — የከበሮው ምትና የትዝታው ማዕበል!! _________ (በጭፍን ትችት ላይ የተሰነዘረ ምክንያታዊ ምላሽ) በያፌት ተስፋዬ ( Yaphet Tesfaye ) "በስሜት እንተቸው፣ ግን በምክንያት እንውደደው💡!!" ሐምሌ 10 ቀን 2018 ዓ/ም ______ 🕊️ መግቢያ፡ ከዝምታ ማኅደር 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ በአንድ ወቅት "ጪም-ጪሪሪም" የሚባል የቃላት ድርደራን ብቻ ዘፈን አድርጎ ሲያንጎራጉር የነበረን ድምፃዊ በአዎንታዊ መልኩ ሲያበረታታና ሲያቆለጳጵስ የነበረን አንድ ታዋቂ የሶሻል ሚዲያ ሰው፣ ከሰሞኑን በአስቴር አወቀ አዲሱ 'የሠርጌ ትዝታው' ሥራ ላይ 'መላቅጡን አሳጣችው' ብሎ አንጓጣጭ ቃሎችን ሲለጥፍ ተመለከትኩ። ይህን ስመለከት ዝም ብዬ መቀመጥ አልቻልኩም። ተገድጄ ከዝምታዬ ተፈነቀልኩ፤ እና እኔም ስሜቴን በብዕሬ ልለጥፍ ወደድኩ። ለመሆኑ በቀድሞውና በአሁኑ የሙዚቃ ሥራ ላይ አሉታዊ አስተያየት ሲሰጡ ከሰማኋቸው መሐል፣ የትኛው ‘መላ’ የቱጋ ‘መላቢስ’ እንደሆነና፣ የቱስ ‘ቅጥ’ ምን ተደርጎ ‘ቅጥ-እንዳጣ’ በምክንያትና በሙዚቃ ዕውቀት አብራርቶ የገለፀ አንድም ሰው አልገጠመኝም። ይልቁኑ ካለሁበት አሜሪካ ሆኜ የሀበሻን ማኅበረሰብ ስታዘብ፤ በጽሁፍ፣ በድምፅ፣ በምስል፣ አልፎ ተርፎም ፊትን ቅጭም በማድረግና እጅን ከወዲህ ወዲያ በማወናጨፍ የዕውር-ድንብር አሉታዊ ስሜትን ሲያንጸባርቁ አስተውያለሁ። ምንም ይሁን ምን፣ ስሜትን መግለጽ ተፈጥሯዊና የዕለት ተዕለት ሰውኛ ባህርያችን ቢሆንም፤ ‘የሠርጌ ትዝታው’ ተቺዎቹ እንደሚሉት ቅጥ-እንዳላጣ ግን ምክንያታዊ ጆሯቸውን እንዲመልሱልኝ ፈለግኩ። ጆሯቸውን 'መመዝለግ' አላልኩም — ጆሯቸውን አስልተው፣ ደግመው በጥሞና እንዲያዳምጡት ማድረግ ነው ፍላጎቴ። 🎛️ የቅንብሩ ረቂቅ ምሥጢር 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ የመጀመሪያው የሠርጌ ትዝታው ሥራ በስልተ-ምቱ፣ በዜማውና በአዛዜያሙ ከአሁኑ በእጅጉ የለሰለሰ መሆኑ እውነት ነው። ነገር ግን አሁን የቀረበልን ሥራ በጊዜ ርዝማኔ ውስጥ አብሮን የኖረውን ያንን የጋራ ትዝታ፣ በልዩና አዲስ የሙዚቃ ምርምር (Experiment) ፈትሾ፣ በሌላ ሥራ ያልተሰማ የቅንብር ትሩፋትን ጨማምሮ ያቀረበልን ድንቅ ፈጠራ ነው። የዘፈኑ አብዛኛው ግጥምና ዜማ ብዙዎቻችን እንግዳ ካልሆንንበት ከሠርግ ባህላችን የተቀዳ መሆኑ ግልፅ ነው። እርሷም በሰርጓ ጊዜ የተዘፈነውን ባህላዊ ዜማ እያስታወሰች 'እየተባለ የተዘፈነው' ስትል የራሷን ትዝታ ታጋራናለች። በአሁኑ ሥራዋ ላይ ግጥሙ፣ ዜማውና አብዛኛው የBasslineና Melody መሠረቱ ሳይናጋ ባለበት የተቀመጠ ሲሆን፤ በፊት ያልነበረ አዲስ ስልተ-ምት (Rhythm)፣ ድልድይ (Bridge) እና በዜማው ላይ ጥልቅ የነፍስ ስሜት ታክሎበታል። በዚህ አዲሱ ሥራ ላይ፣ ከአገባቡ ጀምሮ ያ የድሮው ትዝታ የቅርብ ጊዜ ትዕይንት ይመስል ይበልጥ ግልፅ በሆነ መልኩ ተቀረጻል። የሙሽራዋ ማማርና የሰዉም ጭፈራ ገና ከዓይኗ ላይ እንዳልጠፋ ለማሳየት — ጥሩምባው፣ እልልታው፣ ጭብጨባውና የአታሞው ድምድምታ በስሱ ተደርቧል። ይህም በሙዚቃዊ መንገድ ትዝታዋ አሁንም ዛሬም ጆሮዋ ላይ እያስተጋባ መሆኑን የሚያሳይ ጥበባዊ ስልት ነው። ይህ ስሜትን በዜማ ውስጥ የማንፀባረቅ ብቃት፣ የአርቲስቷ አሳምረን የምናውቅላትና የምንወደው መገለጫዋ ቢሆንም፤ በዚህ ዘፈን ላይ ግን በዘመን ያካበተችውን ልምዷን ተጠቅማ፣ በአእምሯችን ውስጥ ትልቅ ተንቀሳቃሽ ሲኒማዊ ትዕይንትን ህይወት ዘርታ አሽሞንሙናዋለች። 🔍 የዘፈኑ መዋቅራዊ ትንተና (Timestamp Breakdown) 〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️〰️ 🥁 1ኛ/ 1 ደቂቃ ከ24 ሴኮንድ | (የሰርጌ ሁኔታው) ~~~~~~~~ 'ሁኔታው' የሚለው ቃልና ዜማው ተቀይሮ፣ በቅጽበት ከፍ ብሎ ድንገት ቁልቁል እንዲወርድ መደረጉ፤ እና በመሐል ሙዚቃውን አቁሞ በከበሮው ምት ብቻ እንዲቀጥል መደረጉ የረቂቅ ጥበብ መገለጫ ነው። ይህ ዘዴ የትዝታ ስሜት ድንገት ፈንቅሎ ከውስጣችን እንዲወጣ ከማድረግ አልፎ፣ ሰውን ነሽጦ ድንገት ከጭፈራው መካከል የሚያስገባ ታላቅ ስሜት ፈጣሪ ስልት ነው። ይህ ዓይነቱ ስልት በቤተክርስቲያን ማኅሌትና ዜማዎችም ላይ ያለ፣ ማኅበረሰቡ ከጥንት ጀምሮ የፈጠረውና የጠበቀው የሙዚቃ ዕውቀት (Indigenous Knowledge) ነው። 🙅‍♂️ 2ኛ/ 2 ደቂቃ ከ27 ሴኮንድ | (አናስገባም) ~~~~~~ ይህ ቃል ከተቀየረው ዜማ ጋር ሲዋሀድ በትክክል እሷ እንደምታቀነቅነው ሁሉ፤ የሙሽራው ቤተሰቦች ዓይናቸውን ፈጠጥ አድርገው፣ እጃቸውን በአይሆንምታና በፉከራ አየር ላይ እያወዛወዙ... እዛው ቆሜ በዓይኔ ያየኋቸውን ያህል ሕያው ስሜት እንዲሰማኝ አድርጎኛል። 🕺 3ኛ/ 3 ደቂቃ ከ54 ሴኮንድ | (አለበለዚያማ ልጃችን አትሄድም!) ~~~~~~ ለሙሽራው ልጃቸውን የሰጡት ቤተሰቦች በሚዜዎቹ መፍዘዝ የተነሳ በውሳኔያቸው ወደ ጥርጥር ሲገቡ ይታያሉ። ታዲያ አንዱ የቤተሰብ አባል (አጎቷ ይመስሉኛል) ድንገት ተነስተው... እጃቸውን ከፍ፣ አመልካች ጣታቸውን ወደላይ ቀሰር አድርገው፣ ክንዳቸውን እያወዛወዙ፤ ቀኝ እግራቸውን ከፍ! አስቴርን በአዲሱ ሙዚቃዋ ያጀቧት መሣሪያ ተጫዋቾች ወደፊት ቀደም አድርገው... ከመጨረሻዋ ከበሮ ምት ጋር እኩል መሬቱን ረገጥ ሲያደርጉትና... ወዲያው የከበሮው ምት ሲቀጥል፣ በትከሻቸውም ጭምር መታ መታ መታ ሲያደርጉት... እኔም ተከትዬ ቸብ ቸብ ቸብ ቸብ.......!! 😢 4ኛ/ 1 ደቂቃ ከ39 ሴኮንድ | (አይበልሽ ከፋ) ~~~~~~~ ይህ አገላልጽ ዛሬ ላይ ሆና ያኔ በሠርጓ ቀን የተደሰተችው ሙሽራ... መለስ ብላ ከቤተሰቦቿና ከቀዬው የምትርቅበትም ቀን መሆኑ ትውስ ሲላት... እዝን ብላ ስታለቅስ ያዩዋት እናቷ ወይም አክስቷ (አልያም ያሳደጏት ጎረቤቷ)፤ አድጋ ለዚህ ቀን ብትበቃም ዛሬም እንደልጅ እያዩአት... የመለያየት ስሜታቸውን በሆዳቸው አምቀው እንባዋን እያበሱ፤ ከጉንጮቿ ላይ ቦጭቀው ሊጎርሱ ይመስል በጣቶቻቸው ጉንጯን ይዘው በልጅ አንደበት 'አይዞሽ የኔዋ፣ አይበልሽ ከፋ' ብለው ሲያፅናኗትና ሲያበረቷት ሳይ... እህቴ ልትሄድ ነው ብዬ ሆዴ እንዲረበሽ ያደርገኛል። 🏛️ ማጠቃለያ፡ በአስቴር ዜማ የተሳሰረው ቤተሰብ ~~~~~~~~ በእነዚህና በብዙ በዚህ ዘፈን ውስጥ በተካተቱ የትዝታ ስሜት አገላለጾች አንጻር ስመዝነው፣ ይህ አዲሱ ሥራዋ በሀገራችን ሙዚቃ ታሪክ ሰምቼው የማላውቀውን የአንድን ዘፈን የቀደመ እትም (Version) ውበት ሳይበክል፣ በተሳካ ጥበባዊ ሙከራ አዲስ ቀለም ሊፈጠር እንደሚችል ያሳየ የሙዚቃ ምርምር ውጤት ነው። ይህን የምለው ዘፈኑን ደጋግሜ አድምጬው ነው። ሳደምጠውም የቀደመው የሠርጌ ትዝታው ዘፈኗ 'ተለወጠብኝ' የሚል ምንም ዓይነት የባዕድነት ስሜት ሳይሰማኝና ሳይጎረብጠኝ.... በራሱ መንገድ አዲሱን ቅኝት ማጣጣም መቻሌን እጅግ እየተደሰትኩበት ጭምር ነው።
2 081
19
لا يوجد نص...
1 401
20
Mandefro_Maru,_YeHilawe_Enqoqilish_የሕላዌ_እንቆቅልሽ.pdf
1 608