fa
Feedback
ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ

رفتن به کانال در Telegram

✨Philosophy For Higher Consciousness✨

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ

کانال ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ (@zephilosophy) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 31 165 مشترک است و جایگاه 2 251 را در دسته دین و مذهبی و رتبه 1 085 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 31 165 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 326 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 25.96% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 6.60% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 8 090 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 057 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 106 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
✨Philosophy For Higher Consciousness✨

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته دین و مذهبی تبدیل کرده‌اند.

31 165
مشترکین
-424 ساعت
+807 روز
+32630 روز
آرشیو پست ها
The Republic The Republic የአፍላጦን ዋነኛ ተጠቃሽ ስራው ነው። የመጀመሪያው ብስል የፖለቲካዊ ፍልስፍና ስራም ነው። ስለመንግስት አስተዳደር ያለውን አስተያየት ጠቅልሎ አካቶበታል። ከፍተኛ ስነ ፁሁፋዊ ለዛ ያረፈበትን ይህን ታላቅ ዲያሎጉን (በውይይት መልኩ የሚቀርብ ሀተታ) የፃፈው ድርሰትን በሚገባ በተካነበት እና ኃሳብን የመግለፅ ጥበብን አሳምሮ ባወቀ! ወቅት በመሆኑ በፍልስፍናው አበክሮ የሚያወጣ የሚያወርዳቸውን ጉዳዮች በሚደንቅ ህብር አስሮ ለማቅረብ እስችሎታል። ፍፁም ነው የሚለውን ሐሳባዊ የጋራ ብልፅግና ሲተነትን (ይህም በስነፅሁፍ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያው ዩቶፒያ-- እንከን አልባ ምናባዊ ዓለም-- ተደርጎ ይቆጠራል።) በህይወቱ  ያተኮረበትን ተግባራዊ ፖለቲካ ያስዳስሳል። በሳል የህይወት ተሞክሮውን እና እውቀቱን ተጠቅሞ ለዓይነተ ብዙ ችግሮች (ከስነ ፅሁፍና ሙዚቃ ግልጋሎት እስከ የሴቶች እኩልነት፤ ከጋራ መኖሪያዎች እስከ የህዝብን ዕድገት በመቆጣጠር ምርጥ ዘር የመፍጠር ሳይንስ ወይም ኢዩጄኒክስ ድረስ) አስተያየቱን ለግሷል። በትምህርት እና በመንግስት መካከል ያለውን የጠለቀ ግንኙነት ካስተዋሉት የመጀመሪያዎቹ ጠቢባን መሃልም አንዱ ነው። ወጣቶችን ስለማስተማር፤ ስለማነፅ እና ስለማሰልጠን የሰጠው አፅንኦት በበርካቶች በአድናቆት ታይቷል። ዣን ዣክ ሩሶ «በዓለም ላይ በትምህርት ላይ የተሰራው እጅግ ምርጡ የምርምር ፅሁፍ » ሲል The Republicን ማወደሱን ልብ ይሏል። በአስር ቅፆች (መፅሃፍት) የተደራጀ ስራ ነው The Republic። በመጀመርያው ቅፅ ፍትህ የሰው ልጆች ነብስ በትክክል ስራዋን እንድትከውን የሚያስችል ጠበል ነው ይለናል። ህይወትን በአግባቡ የሚኖር ሰው የተባረከ እና ደስተኛ ነው ሲል ያክላል። በሁለተኛው ቅፁ መግቢያ ላይም ፍትህ ለራሱ ሲባል (መልካም እሴት ስለሆነ) እንዲሁም የሚያስገኘው ውጤት በጎ ስለሆነ ልንተገብረው እንደሚገባ ይመክረናል። በአራተኛው ቅፅ ደግሞ ፍትህን የሚተገብር ግለሰብ ሌሎቹን የምግባር እሶቹን በሙሉ እያስተባበረ እንደሆነ ያስረዳል። ፍትህን የማይተገብር ሰው በአንፃሩ ደፋርም አይደለም፡፡ ብልህም አይደለም። ትክክለኛም አይደለም፡፡ ከላይ ከላይ ሲያዩት የዲያሎጉ ዓላማ «ፍትህ ምንድን ነው? የሚለውን ጥያቄ መመለስ ቢመስልም ፍትህ (juctice) የሚለውን አቻ ትርጓሜ የሚያስገኝልን የግሪክ ቃል ከፖለቲካዊ እና ህጋዊ እኩልነት የዘለለ ፍቺ በውስጡ ያመቀ በመሆኑ ጉዳዩን አስፍተን እንድንመለከተው ይጋብዘናል። የምግባር ልዕልናን (virtue) የመፈንጠቅ ትክክለኛነት የሚል ትርጉምም አለው፡፡ አፍላጦን ይባትል የነበረው ትክከለኛውን ህይወት (ሰዎች እና አገራት ሰናይ ተፈጥሯቸውን አሟጠው እንዲያወጡ የሚያደርጉ መርሆችን) ፍለጋ ነው። The Republic በወቅቱ በነበረው ስርዓተ ፖለቲካ ላይ የቀረበ ኂስም ክስም ነው። አፍላጦን ከሰው ልጆች ተሞክሮ የሚልቅ ዘላለማዊ ህልውና አለ ብሎ ያምን ስለነበር ግብረ ገብ እና መልካሙ ህይወት የዚህ ህልውና መገለጫዎች ናቸው። መንግስታት እነኝህን እሴቶች ማበረታታት አለባቸው ይላል። ይህ አመለካከቱን ለማሳየት ባጠናቀረው አንድ ተረክ ላይ ሰዎች ዋሻ ውስጥ ፊቶቻቸውን ወደ ግድግዳ አዙረው በሰንሰለት ተጠፍንገዋል። ለብርሃኑ ጀርባቸውን ሰጥተዋል። ስለዚህ ያተኮሩበት ግድግዳ ላይ የሚታያቸው ትዕይንት ከጀርባቸው የሚከወነው እውነታ ነፀብራቅ ወይንም ጥላው ብቻ ነው። ለአፍላጦን ተራ ተርታው የዕለት ተዕለት ህይወት አታላይ ቅዠት ነው። በፖለቲካ ውስጥ የሚያቆጠቁጡት ክፋቶችም አውሬያዊ ደመ ነብስን የመከተል ውጤቶች ናቸው። ስለሆነም ከዚህ ክፉ ደመ ነብሳዊ ጥሪ ነፃ የወጡ ፈላስፎች የንግስናን መንበር ካልተቆናጠጡ ወይንም ነገስታቱ በቅንነት ሃቀኛ ፈላስፎች ሊሆኑ ካለቆረጡ በቀር ከክፋት መላቀቅ የለም። ፈላስፋ-ፖለቲከኛ ብቻ ነው ዜጎቹን ከታሰሩበት ፈትቶ ፊታቸውን ወደ ብርሃን ሊመራ የሚችለው ፤ ከዋሻውም አውጥቶ አምሳያውን ሳይሆን ትክክለኛውን እውነት የማሳየት ብቃት የታደለው። @zephilisophy

The Republic - Plato

የገዢ ኪሳራ ይህ ሰፊ ገበያ በመንፈስ ተሞልቶ በፍቅር ሲጣራ፤ ሸማች የሚጋፋው ቅራቅንቦ ተራ፡፡ “ያ ስንት ነው? ይላል፣ “ይሄኛውስ?” ይላል፤ የብልጭልጭ አይነት ያነሳል ይጥላል። ከመንፈስ ገበያ የውበት ጥሬ እቃ ሞልቶ ተትረፍርፏል፤ ሸማች ግን ልብ የለው ለኮልኮሌ ፍቅር ማልዶ ተሰልፏል። “ወዴት ነህ?” አይባል -                  “ወዴትም!” ነው መልሱ፤ “ምን በላህ?” ይሉታል -                   “ምንም!” ልትል ነፍሱ፡፡ እንዲያውም ካሰኘው! ምን እንደሚፈልግ ፈፅሞ ይዘነጋና፤ “ፀሃይ ስጡኝ!” ብሎ ብቅ ይበል ማምሻውን፤ ሰልፈኛ ነውና ' ከጨረቃ ቆርሶ '                     ይወስዳል ድርሻውን፡፡ የሸማች ሕሊናን መምሰል ከሸፈነው፤ ገበያ መታየት ከመግዛት እኩል ነው። የጠየቀም ገዝቶ፣የክፈለም ገዝቶ፣        የተላከም ገዝቶ፣ የላከም ሸምቶ፤ እዚያው ይሞታታል! ያልሞላ ቅርጫቱን ለአምሳዮቹ ትቶ ። ይኸው መጨረሻው ! ሸማቹ ለገላው እየተጨነቀ፣ ገዢው ለብልጭልጭ እየተደነቀ፤ የመንፈስ ከፍታ ተሸርሽሮ አለቀ፡፡ ገጣሚ- ሩሚ መፅሀፍ-የመንፈስ ከፍታ @zephilosophy

የሰው ልጆች የሚተዳደሩት በውሸት አንቀልባ ታዝለው ነው። ውሸት ሂዱ ከእኔ ራቁ ብትላቸው መግቢያ ቀዳዳ የላቸውም። በውሸት ውስጥ ስናልፍ ከነነፍሷ በድመት መንጋጋ ውስጥ እንደገባች አይጥ አይነት ህይወት እንኖራለን። በድመቷ ጥርሶች ተቆንጥጣ የተንጠለጠለችው አይጥ እስከምትሰለቀጥ ድረስ በህይወት መኖሯን እንደፀጋ ትቆጥራለች። መላመጥና መውዋጧ ግን አይቀርም። በውሸት እቅፍ ውስጥ መደላደልም እንዲህ ነው። እቅፏ አባብሎ እስከሚያፍነን የመተንፈሻ እድል የተሰጠን ይመስለናል። የባከኑ ሰከንዶች ያክል እንኖራለን። በተቃራኒው እውነት ምንጊዜም ገፊ ሀይል ናት። እንደወርቅ በእሳቱ ሳትፈትሸን የራሷ አታደርገንም። በግዛቷ ላይ ከሰፈርን በኋላም መፈናፈኛ የለንም። የማርያም መንገድ አትሰጠንም። እውነት በእኛ ዙሪያ የምታጥረው ክልል እጅግ ውዱ መከለልን ነው። ስለዚህም እንደፈለግን የምንፈነጭባትን የውሸት ዓለም ፈጠርን። በእሷም ጥላ ስር ተጠለልን። እኔ ግን የራሴን የእውነት ዓለም ልገነባ ነው.... መፅሀፍ-ጥሪ ወደ ሞት ደራሲ-አህመድ ሁስ @zephilosophy

"እውነታው የሰው ልጅ የሰውን ልጅ መጠበቅ አለበት ይላል። ቅዠት ግን ሌላ አካል ከሰማይ እስኪወርድ ይጠብቃል።" "ያለ ሰላም፣ ስለ ብልጽግና የሚደረግ  ንግግር በመቃብር ላይ የሚተወን ትያትር ነው።" ✍️ዮናታን አቢስ በሀገራችን ሟቾችን ቶሎ ነው የምንቀብረው። ሀዘናችን አጥሮ ሳይሆን ሞት የተለመደ የዕለት ተዕለት ኑሯችን ስለሆነ። ሌላ ጭF:ጨFa። ሌላ የቤተ ክርስቲያን ቃ:*ጠሎ። በፍርሃት ባዶዋን የቀረች ሌላ መንደር። የሟ*ቾ*ች ዝርዝር ውስጥ ስም እስኪወጣ የሚጠብቁ ሌላ ቤተሰቦች። ሌላ ዙር መግለጫዎች፣ ውግዘቶች፣ ጸሎቶች እና ቃል ኪዳኖች። ከዚያም ዝምታ፤ እስከ ቀጣዩ ጭF:ጨFa ድረስ። በቅርብ ጊዜያት ውስጥ ምሥራቅ አርሲ ተደጋጋሚ የጥ**ቃት መድረክ ሆናለች። ሪፖርቶች እንደሚያሳዩት ንጹሐን ተገdl:ዋል፣ ኦርቶዶክስ ክርስቲያኖች ኢላማ ተደርገዋል፣ አብያተ ክርስቲያናት ተጠktዋል፣ ቤተሰቦች ተፈናklዋል፣ እንዲሁም ማኅበረሰቦች ከታጠቁ ሰዎች ለማምለጥ ወደየአቅጣጫው ለመሰ*ደድ ተገደዋል። ቁጥሮቹ እንደ ምንጩ ይለያያሉ። ዘጠኝ ሟ*ቾ*ች። ሠላሳ ሟ*ቾ*ች። አርባ ሟ*ቾ*ች። ከዚያም በላይ። ወይም ያነሰ። ማንም ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ የሆነ አይመስልም። ሁሉም የሚስማማበት አንድ ሀቅ ግን ሰዎች እየሞtu መሆናቸውን እና ለረዥም ጊዜም ሲሞtu እንደነበር ነው። ምርመራው ከመጀመሩ በፊት ደ*ሙ ደርቋል። መንግሥት መግለጫዎችን ያወጣል። አብያተ ክርስቲያናት ደወል ይደውላሉ። ፖለቲከኞች ስሌት ያሰላሉ። ሟ*ቾ*ች ግን እንደሞtu ቀርተዋል። አርሲም ቀጣዩን የቀብር ሥነ-ሥርዓት እየጠበቀች ነው። የሥልጣን ጠበቆች ሁልጊዜም ማብራሪያ አላቸው። ግጭቱ ውስብስብ ነው። የጸጥታው ሁኔታ አስቸጋሪ ነው። ገዳ*ዮቹ አይታወቁም። ምርመራዎች በመካሄድ ላይ ናቸው። እነዚህ ተመሳሳይ ሰበቦች ደጋግመው ከመነገራቸው የተነሳ፣ ከማብራሪያነት ይልቅ እንደ ኑዛዜ መሰማት ጀምረዋል። መንግሥት ሕይወትን ለመጠበቅ ከተቋቋመ ተቋምነት ባለፈ ሌላ ምንድን ነው? አንድ መንግሥት በኢኮኖሚ ዕድገት ላይሳካለት ይችላል። በመሠረተ ልማት ላይሳካለት ይችላል። በትምህርት ላይሳካለት ይችላል። ነገር ግን ዜጎቹን ደጋግሞ ከግ*ድያ መታደግ ከተሳነው፣ ከተመሰረተበት መሠረታዊ ዓላማ መውጣት ይጀምራል። የአንድ መንግሥት ቀዳሚ ኃላፊነት ልማት አይደለም። ጥበቃ (ደህንነት ማረጋገጥ) ነው። ያለ ሰላም፣ ስለ ብልጽግና የሚደረግ ማንኛውም ንግግር በመቃብር ላይ የሚተወን ትያትር ነው። የአርሲ አሳዛኝ ክስተት ሰዎች መሞtaቸው ብቻ አይደለም። ትልቁ አሳዛኝ ነገር ብዙዎች መሞtaቸው እንደሚቀጥል አምነው መቀበላቸው ነው። ጭfጨfaዎች ወቅታዊ ሆነዋል። እንደ ዝናብ። እንደ መኸር። እንደ ድርቅ። የሚጠበቁ። የሚገመቱ። የተለመዱ። ነገር ግን ከዚህ ሁሉ በስተጀርባ የተደበቀ ሌላ አሳዛኝ ነገር አለ። ከእያንዳንዱ ጥ*ቃት በኋላ የሚሰማውን ቋንቋ በጥሞና ያዳምጡ። "ኦርቶዶክሶች ተገ*ደሉ።" "አማራዎች ተገ*ደሉ።" "ኦሮሞዎች ተገ*ደሉ።" "ሙስሊሞች ተገ*ደሉ።" እያንዳንዱ ቡድን የራሱን ሟች ይቆጥራል። እያንዳንዱ ቡድን በራሱ ድንበር ውስጥ ብቻ ያዝናል። አስከሬኖች አስቀድመው በምድብ ተለይተው ይመጣሉ። ብሔር በመጀመሪያ። ሃይማኖት በሁለተኛ ደረጃ። ሰብዓዊነት በመጨረሻ። በጥ*ይ'ት የተገdለ ሕጻን የኦርቶዶክስ ደ*ም ወይም የሙስሊም ደ*ም አይደለም የሚደማው። የሚፈሰው የሰው ደ*ም ነው። መቃብር ስለ ብሔር ግድ የለውም። ቤት የሚያ*ወድም እሳት ሰለባዎቹ የትኛውን ቋንቋ እንደሚናገሩ አይጠይቅም። ሞት የጎጠኝነት ትልቁ ጠላት ነው፣ ምክንያቱም ሁሉም ርዕዮተ ዓለሞች ዕድሜ ልካቸውን ሊደብቁት የሚሞክሩትን ሀቅ፣ ከማንኛውም ማንነት ስር ሰው የሚባል ተመሳሳይ ምስኪን ፍጡር እንዳለ ያጋልጣል። ሆኖም በዚህ አስከፊ ሁኔታ ውስጥም ቢሆን ሌላ ነገር ይጀምራል። ጸሎት። አጥብቃችሁ ጸልዩ። አብዝታችሁ ጸልዩ። ተግታችሁ ጊዜ ጸልዩ። በአንድነት ጸልዩ። ለምህረት ጸልዩ። ለሰላም ጸልዩ። ለፍትህ ጸልዩ። ጸልዩ። ጸልዩ። ጸልዩ። ሰዎች እየጸለዩ አብያተ ክርስቲያናት ተቃ*ጥለ*ዋል። ሰዎች እየጸለዩ መንደሮች ባዶ ቀርተዋል። ሰዎች እየጸለዩ ገዳ*ዮቹ ተመልሰዋል። ሰዎች እየጸለዩ የቀብር ሥነ-ሥርዓቶች ቀጥለዋል። መደጋገም እምነት መሆኑ አብቅቶ እውነታን መካድ መሆን የሚጀምረው የትኛው ነጥብ ላይ ነው? አማኞች አምላክ ፍጥረቱን ይጠብቃል ይሉናል። ፍጥረቶቹ ግን በጥ*ይ*ት አልቀዋል። አምላክ ቤቱን ይጠብቃል ይሉናል። ቤቱ ግን በእሳት አመድ ሆኗል። አምላክ ምዕመናኑን ይጠብቃል ይሉናል። ምዕመናኑ ግን ዛሬም ልጆቻቸውን እየቀበሩ ነው። ከዚያም የተለመደው መከላከያቸው ይመጣል። የፈጣሪ መንገድ አይመረመርም፤ የሚሰራው በሚስጥር ነው። ግን ሚስጥር ማለት ማብራሪያ ሲያልቅ የሚቀር መጽናኛ ነው። ዓይናችን እያየ እየሆነ ያለውን እንግዳ የሆነ የተገላቢጦሽ ሁኔታ አስተውሉ። ሃይማኖት የሰው ልጅ በፈጣሪ ላይ እንደሚደገፍ ያስተምራል። እውነታው ግን የሚያሳየው ፈጣሪ በሰው ልጅ ላይ እንደተደገፈ ነው። ሰዎች የአምልኮ ስፍራዎችን ይገነባሉ። ይጠብቃሉ። ሲወድምም መልሰው ይገነባሉ። መልሰው ይከላከላሉ። እሱን ለመጠበቅ ይሞ*ታሉ። የሰው ልጅ እጁን ቢሰበስብ፣ እያንዳንዱ ስፍራ ፍርስራሽ ይሆናል። እያንዳንዱ ቅዱስ መጽሐፍ አቧራ ይለብሳል። እያንዳንዱ ተቋም ይወድቃል። በግልጽ እንደሚታየው ፈጣሪ አማኞችን ከሚጠብቀው ይልቅ፣ አማኞች ናቸው ፈጣሪን የሚጠብቁት። ሁሉን አድራጊ የሆነው አምላክ የራሱን መቅደስ እንዳይፈርስ መከላከል ካልቻለ፣ በአርሶ አደር ላይ የተተኮሰችን ጥ*ይ*ት ይመክታል ብሎ መጠበቅ ምን ዓይነት አመክንዮ ነው? መንደሮች ሲቃጠሉ አምላክ ዝም ካለ፣ ኃላፊነቱ ከጅምሩም የሱ አልነበረም ማለት ነው። ኃላፊነቱ ሁልጊዜም የኛው ነው። ይህ የሰዎችን ነጻነት የሚቃወም ሙግት አይደለም። ይልቁንም ቅዠትን የሚቃወም ሙግት ነው። ምክንያቱም ቅዠት ተግባርን ሲተካ አደገኛ ነውና። በተሰበረ ድልድይ የሚተማመን ሰው፣ ሲሻገር ሊሞት ይችላል። በተዓምራዊ ጥበቃ የሚያምን ማኅበረሰብ፣ ሰብዓዊ ጥበቃን ቸል ሊል ይችላል። እናም ብጥብጥ ሲመጣ፣ እውነታው ዕዳውን ይሰበስባል። የአርሲ ትምህርት ሥነ-መለኮታዊ አይደለም። ሰብዓዊ ነው። ምንም መልአክ አልመጣም። ምንም ተዓምር ጣልቃ አልገባም። ምንም መለኮታዊ ጋሻ ከዳመና አልወረደም። ሰዎች ከተርፉ፣ የተረፉት ሌሎች ሰዎች እንዲተርፉ ስለረዷቸው ነው። ማኅበረሰቦች ከጸኑ፣ የጸኑት የሰው ልጆች እርስ በርሳቸው ስለተጠባበቁ ነው። የቆሰሉትን የተሸከሙት እጆች የሰው ልጅ እጆች ናቸው። ለሟቾች የፈሰሰው እንባ የሰው ልጆች እንባ ነው። ፍትሕ የጠየቁት ድምጾች የሰው ልጆች ድምጾች ናቸው። እና ምናልባትም ከሁሉም መራራው እውነት ሁሉም መረጃዎች ወደ ሰው ልጅ ራሱ እየጠቆሙ ሳለ፣ እኛ ከሰው ልጅ በላይ የሆነ መዳኛን መፈለጋችንን ቀጥለናል። አርሲ በሃይማኖቶች መካከል የሚደረግ የጦር ሜዳ አይደለችም። በብሔሮች መካከል የሚደረግ የጦር ሜዳም አይደለችም። በአማልክት መካከል የሚደረግ የጦር ሜዳም አይደለችም። ይልቁንም በእውነታና በቅዠት መካከል ያለች የጦር ሜዳ ናት። እውነታው የሰው ልጅ የሰውን ልጅ መጠበቅ አለበት ይላል። ቅዠት ግን ሌላ አካል ከሰማይ እስኪወርድ ይጠብቃል። የአርሲ መቃብሮች ለጊዜው የትኛው ወገን እያሸነፈ እንደሆነ እየነገሩን ነው። ፍትሕ ለሰብዓዊነት!! ፍትሕ ለእውነት!! ፍትሕ ለአርሲ!! @zephillosophy

4. አብዛኛው ስሜታዊ ህመም ተቃውሞ እንጂ እውነታው አይደለም። ይህ ማለት ስቃይ ምናባዊ ነው ማለት ሳይሆን ብዙ ስቃይ የሚመጣው እውነታው ከሆነው የተለየ እንዲሆን ከመፈለግ ነው ማለት ነው። ስቶይኮች ይህንን በጥልቀት ተረድተውታል፡ ህመም የማይቀር ነው፤ ስነ-ልቦናዊ ስቃይ ግን ብዙ ጊዜ ትርጓሜ ነው። ማርጀት ያማል፣ ማጣት ያማል፣ መገለል ያማል፣ ሞት ያማል፤ ነገር ግን አእምሮ ህመሙን በተቃውሞ ያባዛዋል፦ "ይህ መሆን አልነበረበትም"፣ "ይህ ማንነቴን ያፈርሰዋል"፣ "ከዚህ መትረፍ አልችልም"፣ "ህይወት ዘላቂነት ሊሰጠኝ ይገባ ነበር"። ቡድሂዝም ሙሉ ፍልስፍናውን በዚህ ግንዛቤ ላይ ገንብቷል፡ መጣበቅ ስቃይን ይፈጥራል፣ ምክንያቱም እውነታው ራሱ በየጊዜው የሚለዋወጥ ነውና። አሁን ላይ neuroscience እንደሚያሳየው፣ ስሜታዊ ስቃይ በአእምሮ ተደጋጋሚ የሃሳብ ዑደቶች አማካኝነት ይባባሳል — አእምሮ ድርጊቱ ካለፈ ከረጅም ጊዜ በኋላም ህመሙን ደጋግሞ ይለማመደዋል እንዲሁም ይተረጉመዋል። የሰው ልጅ ከአካል ጉዳቱ ከሚድንበት ፍጥነት ይልቅ ከውስጣዊ ትረካው የሚድንበት ፍጥነት ይዘገያል። ነፃነት የሚመጣው ህልውናን በመቆጣጠር አይደለም፤ ይልቁንም በህልውና ላይ የሚደረገን አላስፈላጊ ስነ-ልቦናዊ ፍጭት በመቀነስ ነው። የሚታጠፍ ዛፍ ማዕበሉን ተቋቁሞ ያልፋል፤ ደረቁ ቅርንጫፍ ግን ይሰበራል። 5. ራሳችሁን በንቃት ካልገነባችሁ፣ ማህበረሰቡ በአጋጣሚ ይገነባቹሃል። ይህ ምናልባት ከሁሉም የበለጠ አደገኛው እውነት ሊሆን ይችላል። የሰው ልጅ እጅግ በቀላሉ ሊቀረጽ የሚችል ፍጡር ነው። ፍላጎቶቻችን፣ ፍርሃቶቻችን፣ ምኞቶቻችን፣ የፖለቲካ እምነቶቻችን፣ የውበት መመዘኛዎቻችን፣ የትኩረት አቅማችን፣ ስነ-ምግባራችን እና ስብዕናችን እንኳ 'ego' ሊቀበለው ከሚችለው በላይ በአካባቢያችን የሚቀረጹ ናቸው። ከወላጆቻችሁ፣ ከአልጎሪዝም፣ ከባህል፣ ከሃይማኖት፣ ከጓደኞቻችሁ፣ ከደረሰባችሁ ጉዳት፣ ከብሄራዊ ተረቶች፣ ከማህበራዊ ሚዲያ፣ ከማስታወቂያ እና ከምትኖሩበት ዘመን ሁልጊዜ ሞዴሎችን እየቀዳችሁ ነው። አብዛኛው ሰው በውስጡ የተጫነለትን "ስክሪፕት" እየተወነ እንጂ ህይወቱን እየመረጠ አይደለም። ዩንግ እንዲህ ሲል አስጠንቅቋል፡ "unconscious የሆነውን ነገር ወደ conscious እስካላመጣኸው ድረስ፣ ህይወትህን ይመራዋል፤ እናም ዕጣ ፈንታ ብለህ ትጠራዋለህ።" ዘመናዊው ስነ-ልቦና ይህንን "conditioning" ይለዋል፤ neuroscience "neuroplasticity" ይለዋል፤ ጥንታዊ ፍልስፍና ደግሞ "unconscious slavery" ይለዋል። አስፈሪው ነገር ይህ ነው፡ አንድ ሰው "በውስጤ እውን እየተናገረ ያለው ማነው?" ብሎ ሳይጠይቅ ሙሉ ህይወቱን ሊኖር ይችላል። እናንተ ናችሁ? ፍርሃታችሁ ነው? ጎሳችሁ ነው? ጉዳታችሁ? ባዮሎጂያችሁ ነው? ባህላችሁ ነው? ወይስ የተቀባይነት ጥማታችሁ? ማነው እየተናገረ ያለው? የባከነ ህይወት ማለት ብዙ ጊዜ አስደንጋጭ ጥፋት ማለት አይደለም። ለአስርተ ዓመታት የተዘረጋ፣ ሳያውቁት፣ ሳይረዱት መተወን፣ መምሰል ነው። እናም ምናልባት በሁሉም ፍልስፍናዎች ውስጥ ያለው ጥልቅ ጥበብ ይህ ነው፡ የሰው ልጅ በራሱ ላይ የተጫነበትን ማንነት በዝምታ ከመቀበል ተላቆ ራሱን በንቃት መፍጠር ሲጀምር አደገኛ እና ህያው ይሆናል። ንቁ!! እንንቃ!! @zephilisophy

ከመጽሃፍት እና በትንሿ እድሜዬ ከሕይወት የተረዳሁትን አምስት ከባድ እውነቶች ልንገራችሁ። ይጠቅማችሁ ይሆናልና ልብ ብላችሁ አንብቡት። ፀሀፊ- ዮናስ በጋሻው 1. አእምሯችን እውነትን አይፈልግም፤ የሚፈልገው ስነ-ልቦናዊ ህልውናውን ማስጠበቅ ነው። የሰው ልጅ ራሱን የሚያየው እውነታን እንደሚሻ ምክንያታዊ ፍጡር ነው። ግን አብዛኛውን ጊዜ አእምሮ "እውነቱ ምንድነው?" ብሎ አይጠይቅም። ይልቁንም የሚጠይቀው፡ "ማንነቴን ምን ይጠብቅልኛል?" "ተቀባይነት እንዲኖረኝ የሚያደርገኝ ምንድነው?" "በሰላም እንድተኛ የሚፈቅድልኝ ምንድነው?" የሚሉትን ጥያቄዎች ነው። ሰዎች የሚጎዷቸው ግንኙነቶች ላይ የሚጣበቁት፣ በሞቱ ሃይማኖቶች ላይ ሙጭጭ የሚሉት፣ ርዕዮተ-ዓለሞችን የሚያመልኩት፣ በሚጠሉት የሥራ መስክ ውስጥ የሚቆዩት እና ለብዙ አሥርተ ዓመታት እራሳቸውን የሚገድል ልማዶችን የሚደጋግሙት ለዚህ ነው። Ego ተቃርኖን የህልውና ስጋት አድርጎ ነው የሚቆጥረው። ጥንታዊያን ስቶይኮች ይህንን በ "attachment" ውስጥ አይተውታል። ቡድሂዝም በ "desire" እና "illusion" ውስጥ ተመልክቶታል። ካርል ዩንግ ደግሞ እራሳችንን ላለመጋፈጥ በምንገነባቸው "shadows" እና "masks" ውስጥ አይቶታል። ዘመናዊው neuroscience ደግሞ "predictive processing" ውስጥ እየተመለከተው ነው፡ አእምሮ ከትክክለኛ patterኖች ይልቅ የታወቁ (የተለመዱ) patterኖችን ይመርጣል፤ ምክንያቱም መረጋጋት ከለውጥ ይልቅ በሃይል አጠቃቀም ረገድ ርካሽ ነውና። ሰዎች መንቃት ማለት አዳዲስ ሀሳቦችን ማግኘት ይመስላቸዋል። አብዛኛውን ጊዜ ግን መንቃት ማለት ስሜታችሁን አደንዝዘው የያዙትን ውሸቶች መጣል ነው። አብዛኛው ሰው ነፃ የማይወጣው ምቾትን ከእውነት ጋር ስለሚያምታታ ነው። 2. እኛ አንድ ሰው አይደለንም፤ ተፋላሚ ማንነቶች የሚጋደሉበት የጦር ሜዳ ነን። በውስጣችን የበላይነትን ለማግኘት የሚፋለሙ ጥንታዊ የዝግመተ-ለውጥ ስርዓቶች አሉ፡ ደስታን የሚፈልገው እንስሳ፣ ደህንነትን የሚፈልገው ህጻን፣ ደረጃን የሚፈልገው ego፣ ትርጉምን የሚፈልገው ነፍስ፣ መታየትን የሚፈልገው ጥላ እና ሰላምን የሚፈልገው ህሊና። የሰው ልጅ ወጥ ያልሆነው ለዚህ ነው። አንድን ሰው በአንድ ጊዜ እየወደዳችሁዕ ልትጠሉት ትችላላችሁ። ስኬትን እየተመኛችሁ የራሳችሁ እንቅፋት ልትሆኑ ትችላላችሁ። ታላቅነትን እየፈለጋችሁ መታየትን ልትፈሩ ትችላላችሁ። "ራስን መፈለግ" የሚለው ዘመናዊ ቅዠት ስነ-ልቦናዊ ሞኝነት ነው። እንደተቀበረ ሀብት ተቆፍሮ የሚወጣ አንድ ወጥ የሆነ እኔነት የለም። ያለው በሃይሎች መካከል የሚደረግ ድርድር ብቻ ነው። ሲግመንድ ፍሮይድ "ego, id, super ego" ብሎታል። ዩንግ "archetypal conflict" ሲለው፣ ቡድሂዝም "non-self" ይለዋል። neuroscience እንደሚያሳየው ንቃተ-ህሊና ራሱ አንድ ወጥ ገዥ ሳይሆን፣ ከተለያዩ የነርቭ ሥርዓቶች የተገነባና በየጊዜው እንደገና የሚታደስ ሂደት ነው። ውስጣዊ ዘላቂነትን በጠበቃችሁ ቁጥር ስቃያችሁ ይጨምራል። ጥበብ የሚጀምረው "የኔ እውነተኛ ማንነት የትኛው ነው?" ብላችሁ መጠየቅ ስታቆሙ እና "የትኛውን ማንነቴን ነው መመገብ ያለብኝ?" ብላችሁ መጠየቅ ስትጀምሩ ነው። 3. አዕምሮ የመዘናጊያዎች ሱሰኛ ነው ምክንያቱም ዝምታ ሟችነትን ያስታውሳል። ሰዎች የትኩረት መከፋፈልን እንደ ስንፍና ይቆጥሩታል። ግን ስንፍና አይደለም፤ የትኩረት መከፋፈል ህልውናዊ ማደንዘዣ ነው። ሰዎች ለምን ያለ ማቋረጥ ስልካቸውን ይነካካሉ፣ ወሬ ያወራሉ፣ በቁጣ ይሞላሉ፣ ተቀባይነትን ይፈልጋሉ፣ ስራ ያበዛሉ፣ በመዝናኛ ይተበተባሉ፣ ወይም ሁልጊዜ ማነቃቂያ ይፈልጋሉ? ምክንያቱም ስክነት አደገኛ ነው። በዝምታ ውስጥ፣ አእምሮ በህይወት ዘመኑ ሁሉ ሲሸሻቸው የኖረውን ነገሮች መስማት ይጀምራል፡ ሞት፣ ብቸኝነት፣ ጸጸት፣ ባዶነት፣ ነፃነት፣ የጊዜ መክነፍ፣ ትርጉም አልባነት እና የህልውና አስፈሪ ሃላፊነት። ብሌዝ ፓስካል ከክፍለ ዘመናት በፊት እንደጻፈው፣ "የሰው ልጅ ችግሮች የሚመነጩት በአንድ ክፍል ውስጥ ለብቻው በጸጥታ መቀመጥ ባለመቻሉ ነው።" ዘመናዊው neuroscience የሚያስደነግጥ እውነት አረጋግጧል፡ በእረፍት እና በself-reflection ጊዜ ንቁ የሚሆነው የአዕምሯችን ክፍል ብዙ ጊዜ ወደ ራስ-ተኮር አስተሳሰብ፣ ጭንቀት፣ ማብሰልሰል እና የትረካ ማንነት ግንባታ ያመራል። አማካዩ ሰው እራሱን በቀጥታ ከመጋፈጥ ይልቅ የትኩረት አቅሙ ቢጠፋ ይመርጣል። meditation ከመፈወሱ በፊት የማይቻል የሚመስለው ለዚህ ነው። በዝምታ ውስጥ ትኩረት ከሚሰርቁ ነገሮች ጋር ብቻ አይደለም የምትታገሉት፤ የህልውና ፍርሃታችሁን አርክቴክቸር ነው የምትጋፈጡት። ይቀጥላል @zephilosophy

📝 የፖለቲካ ንቃተ ህሊናውን ያላዳበረ ማህበረሰብ  የፖለቲካ አመራሩን እርካብ ያለአገባብ በሚቆናጠጡ ኃይሎች ላይ ተጽእኖ የማሳረፍ አቅሙ ደካማ ነው። ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ማለት ማህበረሰብ ስለ መብቶቹ፣ ኃላፊነቶቹ እና በዙሪያው ባሉ የስልጣን አወቃቀሮች ላይ ያለው ግንዛቤ እና ንቁ ተሳትፎው ነው። ወይም በአጭሩ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ማለት ህዝብ መብቱን፣ ግዴታውን እና መንግስታዊ አወቃቀሮችን በግልጽ ማወቅ ማለት ነው። ንቃተ ህሊናውን ያላዳበረ ማህበረሰብ ፖለቲካዊ እንቅስቃሴው ውስን፣ ደካማ ወይም በቀጥታ በቁጥጥር ሥር የዋለ ሊሆን ይችላል። እንዲህ ያለው ማህበረሰብ የፖለቲካ እንቅስቃሴውን ፍትሃዊ ወይም ሚዛናዊ ባልሆነ ሁኔታ በሚቆጣጠሩ ኃይሎች ላይ ተጽእኖ የማሳረፍ አቅሙ ደካማ ስለሆነ፣ የሚከተሉትን ችግሮች ያስከትላል፦ 🔴 ሃብት እና ስልጣን በጥቂቶች እጅ ይከማቻል፤ 🔴 መንግሥታዊ ተጠያቂነት ይዳከማል፤ 🔴 የምርጫ ሂደት ሲከናወን፣ ዜጎች ችላ ይባላሉ፤ 🔴 ማህበረሰቡ ከማህበራዊ ፍትሕ እና ከፖለቲካዊ እርካብ ይርቃል። ስለዚህ ዘላቂ ዴሞክራሲ ለመገንባት የፖለቲካ ትምህርት እና ንቃተ ህሊና ማስፋፋት መሠረታዊ ጉዳይ ነው። ንቁ ዜጋ ብቻ ነው ሥርዓተ ፖለቲካውን የሚቀርጽ እና የራሱን እጣ ፈንታ የሚወስን ኃይል የሚሆነው። በመሆኑም የፖለቲካ ንቃተ ህሊና እጦት እና ጥቂት ተሳትፎ ያለው ማህበረሰብ የህዝባዊ አመራር ይዘት በሌላቸው የፖለቲካ ኃይሎች ላይ ተጽእኖ የማሳረፍ አቅሙ ደካማ ነው። ማንኛውም ማህበረሰብ በፖለቲካዊ፣ በኢኮኖሚያዊ እና በማህበራዊ ዕድገት እንዲገሰግስ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ከፍተኛ ሚና አለው። ምክንያቱም ጥልቅ የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ያላቸው ዜጎች ስለ መብታቸው፣ ስለ ግዴታቸው፣ ስለ መንግሥት አሠራር እና ስለ ህዝብ ተሳትፎ ፍትሃዊ ግንዛቤ ስለሚኖራቸው ነው። ይህ ግንዛቤ በማህበረሰቡ ውስጥ በበለጠ ሲያድግ ህዝቡ በራሱ ዕጣ ፈንታ ላይ ተጽእኖ ማሳረፍ ይችላል። የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ያላዳበረ ማህበረሰብ ግን በፖለቲካ ተሳትፎ ደካማ ይሆናል። እንዲህ ያለ ማህበረሰብ በምርጫ ጊዜ ብቻ የሚነቃ ሲሆን፣ ከዚያ ውጭ በሀገር ጉዳይ ላይ አስተያየት ለመስጠት ወይም ተጠያቂነት ለመጠየቅ ፍላጎቱ እና ችሎታው ዝቅተኛ ይሆናል። ይህም የፖለቲካ ኃይሎች ወይም የሥልጣን ባለቤቶች ያለ ቁጥጥር እንዲንቀሳቀሱ እድል ይፈጥራል። ንቃተ ህሊና የሌለው ማህበረሰብ ብዙ ጊዜ በወሬ፣ በፕሮፓጋንዳ ወይም በጊዜያዊ ስሜት ይመራል። እውነታን በመመርመር ፋንታ የሚነገረውን ብቻ ይቀበላል። ይህ ደግሞ ለፖለቲካ ማታለያ፣ ለክፍፍል እና ለግጭት በር ይከፍታል። አንድ ህዝብ መብቱን ካላወቀ መብቱን ማስከበር አይችልም፤ ተጠያቂነትንም ከመንግሥት መጠየቅ ይከብደዋል። በሌላ በኩል የፖለቲካ ንቃተ ህሊና ያደገበት ማህበረሰብ በሀገሩ ጉዳይ ላይ ንቁ ተሳታፊ ይሆናል። ዜጎች የራሳቸውን ድምጽ ያሰማሉ፣ ፍትሕን ይጠይቃሉ፣ መንግሥትንም በህግ እና በሥርዓት ውስጥ እንዲሠራ ግፊት ያደርጋሉ። ይህ የተሻለ ዴሞክራሲ፣ ፍትሕ እና ሀገራዊ መረጋጋት እንዲገነባ ያግዛል። ስለዚህ የፖለቲካ ንቃተ ህሊናን ማሳደግ የመንግሥት፣ የትምህርት ተቋማት፣ የሚዲያ እና የሲቪል ማህበራት የጋራ ኃላፊነት ነው። ንቁ እና አስተዋይ ማህበረሰብ ብቻ በፖለቲካው ላይ ተጽእኖ ማሳረፍ ይችላል፤ የራሱንም ዕጣ ፈንታ በራሱ እጅ ማስቀመጥ ይችላል። ፀሀፊ-አንበሴ ደበበ @zephilo

ዓለም በ“አሜን” ባዮች ስለተከበበች በየጊዜው መንታ መንገዶች ላይ ቆማ ወደ ፊት ለመራመድ ታመነታለች። በድንቁርና ውስጥ መጠፋፋትን ማለም ዕጣ ፈንታዋ ይሆናል።አዲስ አሻራና ታሪክን የሚያሳርፍ አይገኝም። አይደለም ሰዎች ከተማዎች በዚያ ዓይነት ድብታ ውስጥ ያንቀላፋሉ። ትውልድ እየመጣ ትውልድ ይሄዳል። ነገር ግን የተለየ አብዮት አይከሰትም። ሁሉም “አሜን” እያለ ያደገድጋል። የቀረበለትን ያነግሣል። “ጠላትህ ነው” ተብሎ የተነገረውን ይጠላል። “ወዳጅህ ነው” ተብሎ የተነገረውን ይወድዳል። ምክንያትን አይጠይቅም። ሲደሰትም፣ ሲቆጣም፣ ሲለግምም፣ ሲያብርም… በስሜት ላይ እንጂ በተረጋገጠ ገዢ እውነታ ላይ ተመሥርቶ አይደለም። ከዚህ ውስጥ ‘ለምን?’ ብሎ የሚጠይቅ ሰው ይዘን የመጣናቸውን ፍሬዎች በነሲብ ከመብላታችን በፊት በጥንቃቄ እንድንመዝናቸው ያነቃናል። ምክንያቱም ሁሉም የሐሳብ ፍሬ አይበላም። የተበላሹ ፍሬዎች ሊያጋጥሙን ይችላሉ። በመዳፋችን የያዝናቸውን መልካም በረከቶችና ክፉ መርገሞችን እናነጻጽራለን። እጃችን ላይ ያለው ምንድን ነው? ምንስ እናድርግበት? አንድ ማኅበረሰብ የመጣበትን መንገድ ቆም ብሎ እንዲፈትሽ የሚያደርጉት እንቢተኞች ናቸው። አልገባኝም ደራሲ -ዮናስ ዘውዴ @zephilosophy

ጎህ እንደቀደደ፤ በሚጣፍጥ ዜማ መላክ ከሰማይ ላይ፤ እንዲህ ሲል ተሰማ ቶሎ ቶሎ ውደድ የድሜህ ጀንበር ሳይጠልቅ፤ ሳይውጥህ ጨለማ በህይወት መስከር ነው፤በፍቅር መመርቀን የፊት የፊቱን ኑር፤ ምንድነው ሰቀቀን ህያው ፍጥረት ሁሉ ያከትማል አንድ ቀን። ኡመር ሀያም @zephilsophy

የጋራ ህልም ድርቅ እና የነጠላ ሩጫ ዘመን! ወዳጄ ልቤ ... የሆድ ኑሮን አልፎ ወደ ሰውነት ልቀት መሻገር ለምን አቃተን? ትላንትና የጋራ ህልም ቢያጥረን እንኳን የጋራ ድብድብ ነበረን። ድህነቱም፣ ማኅበራዊ ስቃዩም፣ ደስታውም የጋራ ነበር። ዛሬ ግን ሁሉም ሰው ለየብቻው የሚሮጥበት The Atomized Society (የተበታተኑ ቅንጣቶች ማህበረሰብ) ውስጥ ወድቀናል። ወንድምህ ራሱ የራሱ ቀመር -Algorithm ነው የ አለው። እንደ ጓደኛ፣ እንደ ቤተሰብ አልፎም እንደ ሀገር የጋራ ግብም ህልምም የለንም። ይህ ዝም ብሎ የመጣ ክስተት አይደለም፤ ስር የሰደደ ማህበራዊ እና ፖለቲካዊ ውድቀት ውጤት እንጂ። ማህበረሰባችንን በአንድ ላይ አስሮ ያቆየው የጋራ እሴት -Social Capital ፈርሷል። ሁሉም ሰው የራሱን ህይወት ብቻ ለማሸነፍ በሚያደርገው ትንቅንቅ ውስጥ፣ አብሮነት እንደ ሸክም መታየት ጀምሯል። ለዚህ ነው ከእለት ጉርስ እና ከቁሳዊ ህልውና በላይ መሻገር ያቃተን። ሁኔታው ሲታይ... ሆን ተብሎ በሚሰራ Political Engineering ህዝቡ በአንድ ላይ ቆሞ ትላልቅ አገራዊ እና ህልውናዊ ጥያቄዎችን እንዳያነሳ የተደረገ ይመስላል ። ማህበረሰቡ የጋራ ግብና ህልም አጥቶ ፣ ፖለቲካው የሚመራው በመንጋ ጩኸት ሆኗል ። ስለ ትላልቅ ስትራቴጂካዊ እቅዶች በጋራ ማለምም ማቀድም መግባባትም የለም ይልቅም በእለት ተእለት የኑሮ ውድነት እና በሰፈር ብሽሽቅ ውስጥ ተጠምደናል ይህም ድንቁራናችን ቀለባቸው ለሆነ ምቹ ክፍተት ሆኗል ። ዛሬ አለም የደረሰችበት የሊበራሊዝም ጫፍ ሰውን ሁሉ ለብቻህ ሩጥ፣ ለብቻህ ግዛ፣ ለብቻህ ተፎካከር የሚል አስተሳሰብ ግቶታል ። የማህበራዊ ሚዲያ አልጎሪዝሞች እያንዳንዳችንን የየራሳችን የሀሳብ አረፋ ውስጥ ከትተው እያነሆለሉን ነው ። ታናሽ ወንድምህ ፣ ትንሿ ልጅህ የራሳቸው ቲክቶክ አላቸው ፣ አንተ የራስህ ፍልስፍና አለህ፣ ብቻህን የምትቃዥበት ፣ ስለሰው ስለሰው ቀድጄ ልበሰው ብለህ የምትደፈንበት ፣ ቴክኖሎጂው አለምን አገናኘሁ ቢልም፣ በተግባር ግን ሰውን ከቤተሰቡና ከወንድሙ ጋር ካራሱጋርም እንዳይገናኝ አድርጎ አጀዝቦ ነጣጥሎታል። ወዳጄ... የሆድ ኑሮን አልፈን ወደ ሰውነት ልቀት ለመሻገር፣ ያንን የጠፋውን የጋራ ህልም ዳግም መገንባት ካልቻለን ከንቱነት ላይ የከንቱ ከንቱ ስኩዌር ነው የምንሰራው ። ለየብቻ የምናደርገው ሩጫ መጨረሻው ድካምና የውስጥ ባዶነት ብቻ ነው። ለየብቻ መሮጡን አቁመን፣ በጋራ የምንራመድበትን አዲስ ንጋት እንድናገኝ እመኛለሁ። Tita abe @zephilosophy

1."ፓለቲከኛ የሰውን ልጅ በሁለት መደብ ይከፍለዋል። ጠላት መምቻ መሣሪያ እና ጠላት" ---ፍሬድሪክ ኒቼ 2."ምንም አያውቅም ግን ሁሉንም የሚያውቅ ይመስለዋል። ፖለቲከኛ ማለት እሱ ነው።" ---በርናርድ ሾው 3."ፖለቲከኛ እራሱ የሚናገረውን ራሱ አያምንም ሌሎች ሲያምኑት ግርም የሚለው ለዚህ ነው።" ---ቻርል ደጎል 4."የሰው ልጅ ተፈጥሮ ውስጥ ዋናው ነገር በሌሎች የመሞገስ ጉጉት ነው።ስለዚህ ከሰዎች የምትፈልገውን ለማግኘት የተፈላጊነት ስሜት እንዲሰማቸው አድረግ።" ---ዊሊያም ጀምስ 5."ያንተ ሀሳብ ሳይጨመርበት ማንም የበታችነት እንዲሰማህ አያደርግህም።" --ኤለኖር ሩዝቬልት 6."ከመጠን ያለፈ አድናቆት በመጨረሻ ገዝግዞ ነው የሚጥለን።" ---ጅለ ክርስቲ 7."ነፃ የምንሆነው ስለነፃነት ባለን የግንዛቤ ልክ ነው።" ---ማርቲን ሉተር ኪንግ 8."ጊዜ ማንኛውንም ሀዘን የሚያስወግድ ጥሩ መድሀኒት ነው።" ሲፈለክስ @zephilosophy @zephilosophy

የፅንፈኛ መገለጫዎች ...የቀጠለ በስድስተኛነት ፅንፈኞት የሚገለጡበት አስተሳሰብ "ተቃዋሚና ተቺዎቻቸውን የክፋት መልዕክተኞች አድርጐ መመልክት ነው፡፡ ለፅንፈኞች ከእነሱ የተለየ አስተሳሰብ የሚያራምድና ሃሳባቸውንም የሚተች ማንኛውም ስው ክፉ፣ ሞራል አልባ፣ ቅንነት የጐደለው፣ ጨካኝ፣ ለጥፋት የቆመ፣ መንፈሰ መራራ... ወዘተ ተደርጐ ይወስዳል፡፡ ፅንፈኞች ተቃዋሚና ተቺዎቻቸውን እንዲህ እንዲስሏቸው የሚያደርጋቸው በሃሳብና በአቋም ከእነሱ የተለዩ ወይም የማይስማሙ ሆነው በማግኘታቸው እንዳይመስላችሁ፤ ይልቁንም ከላይ የተዘረዘሩትን የክፋት ባህርያት ተሸክመዋል የሚል እምነት አጥብቀው በማራመዳቸው እንጂ፡፡ በሰባተኛነት ፅንፈኞች "ከእነሱ ጋር ያልቆመ ከጠላት ጋር ቆሟል የሚል አቋም በመያዝ" ይታወቃሉ። ዓለምን ሲመለከቷትም ፍፁም መልካም ወይም ፍፁም ክፉ በሆነ መስፈርት እንጂ ለእነሱ መካከለኛ ወይም አስታራቂ አስተሳሰብ አራማጅ አይታያቸውም፡፡ ማናቸውም የሚራመዱ አስተሳሰቦች ከሞራል አንፃር ትክክል ወይም ስህተት በሚል መዳኘትን ያዘወትራሉ። መፈክራቸውም ከእኛ ጋር ያልሆነ እሱ ይቃወመናል" የሚለው ነው፡፡ ስምንተኛው የፅንፈኞች መለያ "ሳንሱርን በተወሰነ ደረጃ መደገፍና የተቃዋሚንና የተቺዎቻቸውን ሃሳብ መጨቆንን" አጥብቀው ያምናሉ፡፡ እንዲህ ዓይነቱን አቋም በስውርና በግልፅ ሲያራምዱ በሚዲያ ላይ ያላቸውን ሞኖፖሊ ወይም ልዩ ቁርኝት እና ሕዝባዊ መድረኮችን በመጠቀም ሲሆን ዓላማቸውን የሚያስተጋቡትም የተቃዋሚና ተቺዎቻቸውን ስም በ"ጥቁር መዝገብ" ላይ በማስፈር፣ እገዳን በመጣል፣ አልፎም አጥብቀው የሚጠሉና የሚፈሯቸውን ከመካከላቸው "በማጥራት" (quarantining) እንዲሁም የተለያዩ አፋኝ ድንጋጌዎችን በላያቸው በማውጣትና ክልከላ የተጣለባቸውን መረጃዎች በማስተማርና በመቀስቀስ ነው፡፡   ዋነኛው ተልዕኮአቸው መረጃን ማገድ ሆኖ በጥቅሉ ሊቀመጥ ይችላል፡፡ እናም ፅንፈኞች በባህርያቸው ብቻቸውን መደመጥ የመሻት ፅኑ ፍላጐት የተጠናወታቸው ናቸው፡፡ በዘጠነኛ ደረጃ የፅንፈኞች መገለጫ የሆነው በርካታ መፈክሮችን፣ በተደጋጋሚ በሚዲያ በመተላለፍ ላይ የሚገኙ ቃላትና አባባሎችን እንዲሁም ሃሳብ አደናቃፊ የሆኑ አሰልቺ አገላለፆችን መጠቀም ነው፡፡ ፅንፈኞች የተወሳሰቡና ከፍተኛ ዕውቀትን የሚጠይቁ አስተሳሰቦችን ተጠየቃዊ በሆነ መንገድ ይፋ አውጥቶ ከመከራከር ይልቅ አቋምን የሚያስተጋቡ መፈክሮችን ደጋግሞ በማንሳት ሸፋፍኖ ማለፍን ይመርጣሉ። ሃሳባቸውንም ለማሳመን አቋራጩ መንገድ አድርገው የሚመርጡት ተቃራኒውን ሃሳብ መሞገትና በሌላ ምክንያታዊ ሃሳብ ማሸነፍ ሳይሆን በሕዝብ ዘንድ ሰርፀዋል በማለት የሚያምኑባቸውን ቃላትና አባባሎች (ዲሞክራሲ፣ ልማት፣ ሰላም፣ ብልፅግና፣ ዕድገት፣ እኩልነት...) ደጋግሞ በመጠቀም ዋናውን የመከራከሪያ ጭብጥ ሸፋፍኖ ማለፍ ነው። በአሥረኝነት ፅንፈኞች የሚታወቁት "የምፅአት ቀን አስተሳሰብን ማቀንቀናቸው" ነው፡፡ ፅንፈኞች አቋምና አስተሳሰባቸውን ተቃውሞ የሚቆም ወይም የሚያራምድ ፖለቲከኛ ወይም ተቺ ሲገጥማቸው በጥፋት መልዕክተኛነት የቆመ አድርገው ለሕዝብ ማቅረብንና ሃሳቡም የአመፅና የእልቂት መሣሪያ መሆኑን በማሳመን የተጠመዱ ናቸው፡፡ ከዚህ አንፃር የእነሱን ፕሮግራምና አጀንዳ የማይከተል፣ የእነሱን ልዩ ፖለቲካዊ ምልከታ የማያደምጥ ወይም የተገለጠላቸውን የፖለቲካ ጥበብ ያልተረዳም ከዚሁ የጥፋት ጥግ ራሱን ያቆመ ለመሆኑ ስጋት እንዲያድርበት ያደርጉታል፡፡ በዚህ መንገድ ከሚያቀነቅኑት አስተሳሰብ የተነሣ መቃወምም ሆነ መተቸትን መድፈር ለአመፃና ለጥፋት የተሰለፉ ወገኖች አቋም ተደርጐ በሕዝቡ ዘንድ እንዲታመንበት ጠንክረው ስለሚሰሩ የሕዝቡ ስሜት ከፍርሃትና ከዝምታ ባለፈ ግልፅና ዲሞክራሲያዊ ተሳትፎና ድጋፍ የሚታይበት አይሆንም፡፡ በመጨረሻም ዕንፈኞች "ለመልካም ዓላማ መጥፎ ነገርንም ቢሆን ፅንፈኞች የሚነሱባቸውን ተቃዋሚና ማድረግን አምነው  ይቀበላሉ።" ተቺዎችን ለመክሰስም ሆነ ፖለቲካዊ ገፅታቸውን ለማበላሸት አውቀውና ተዘጋጅተው በመዋሸት፣ በማጣመም፣ አባባላቸውን ሌላ ትርጓሜ በማላበስና ከሃገርና ከሕዝብ የውጭ ጠላቶች ጋር ግንባር የፈጠሩ አድርገው በማሳየት ዙሪያ ተግተው ይሰራሉ፡፡ እንዲህ ዓይነቱን ድርጊት ሲፈፅሙም ፖለቲካዊ ግባቸውን እስኪመቱ ድረስ አንዳች የኅሊና ፀፀት አይሰማቸውም፡፡ "ጠላትን" ድል እስከመቱ ድረስ ሌሎች ሞራላዊ እሴቶች ለድርድር የሚቀርቡ እንጂ በእነሱ ላይ ወሳኝነት የላቸውም፡፡ የእነሱ መመሪያ ውጤቱ ምክንያቱን ይወስነዋል" (the ends often justify the means) የሚለው ነው፡፡ ታዲያስ? ከላይ በጣም በጥቂቱ ቆንጥረን የፅንፈኞችን ማንነትና መገለጫቸውን ለማየት የተጓዝንበት መንገድ ለጊዜው በበቂ የገለጠልን ቁምነገር ያለ መስሎ ይሰማናል፡፡ መንገዳችንን የምንጠቀልለው ሁለት መሠረታዊ ሲዘነጉ የማይገባቸው ቁምነገሮችን በማስቀመጥ ይሁን። የመጀመሪያው አንዳንድ ሰው የቱንም ያህል ቅን፣ ታማኝና ለኅሊናው የተገዛ እንዲሁም በሌላው ላይ ጉዳትን የማያስብ ቢሆን እንኳን ለእንዲህ ዓይነቱ ፅንፈኛ አስተሳሰብ በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ የመጋለጥ ዕድሉ ሰፊ መሆኑን ነው፡፡ ለእንዲህ ዓይነቱ ተጋላጭነት የሚያበቁት በርካታ ምክንያቶች ሲኖሩ ከእነዚህ መካከል ደግሞ የዕውቀት አናሳነት ፣ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም (ለሆድ ማደር)፣ የሥልጣን ጥመኝነት፣ ለሞራላዊ እሴቶች ዋጋ አለመስጠት፣ ፣ ዲሞክራሲን ከሰው ልጅ ተፈጥሮአዊ መብትነት ይልቅ የጥቂቶች ችሮታ አድርጐ ከማመን.. ወዘተ የሚመነጩ ሆነው ይገኛሉ፡፡ ሁለተኛው ቁምነገር ፅንፈኝነት በራሱ አስተሳሰብ ተደርጐ ለመጠላትና ለመወንጀል የበቃው ከተሸከመው መልዕክትና ከሚያራምደው አቋም አንፃር በመቃኘት ሳይሆን የመልዕክቱና የአቋሙ አራማጅ "ማን ነው?" በሚለው ዓላማ ላይ የተንጠለጠለ ከመሆኑ በተነሳ ነው፡፡ በመሆኑም የአንድ መልዕክትም ይሁን አቋም እውነትነትና ተቀባይነት በሃሳቦች ዙሪያ የመወያየት ዲሞክራሲያዊ ባህል ላይ ብቻ ተመስርቶ ለክርክር እስካልቀረበ ድረስ በቀላሉ በፅንፈኞች መጨፍለቁ አይቀሬ ሆኖ ይቀጥላል፡፡ ከ"ፅንፈኝነት" አስቀድሞ የፅንፈኞችን" ምንነት በወጉ መረዳት የሚገባንም ለዚህ ነው:: ታዲያስ? የእኛ "ፅንፈኞች" ከመስፈርቱ ስንቱን አሟልተው ይሆን? @zephilosophy

ፅንፈኞች ያልገባቸው የፅንፈኝነት ትርጉም ፀሀፊ- ጲላጦስ መፅሀፍ- ዝምታ እንግሊዛዊው ፈላስፋ ሮጀር ስኩርተን እ.ኤ.አ. በ1982  "የፖለቲካዊ አስተሳሰቦች መዝገበ ቃላት" (Dictionary of Political Thought) ለኅትመት ካበቃ በኋላ በርካታ አከራካሪ የፖለቲካ ፅንሰ ሐሳቦችን በዚሁ ምሁር የትርጉም ትንታኔ ላይ ተመስርቶ መፈተሽና መተንተን አቋምንም መግለፅ ተራጩ የምዕራባውያን ምሁራን መንገድ ሆኖ እስካለንበት ወቅት ዘልቋል።ስኩርተን በመዝገበ ቃላቱ ውስጥ የተለያዩ ፖለቲካዊ እሳቤዎችን ከፖለቲከኛ ወገንታዊነት በፀዳ መልኩ ለመተርጐም መሞከሩ ሰፊ ተቀባይነት እንዲያገኝ ስላስቻለው መሆኑን ሥራዎቹን ተንተርሶ የተሰጡ አስተያየቶች ይመሰክሩለታል:: ይኸ ምሁር የፖለቲካዊ አስተሳሰቦችን ትርጓሜ በመዝገበ ቃላት ቅርፅ አበጅቶ መተንተኑ በማወቅም ይሁን ባለማወቅ የግል፣ የቡድን ወይም የፓርቲን አቋም ለማራመድ በሽፋንነት የሚያገለግሉ አጀንዳዎችን ለመዳኘት የጐላ ጥቅም ማበርከቱም እንዲሁ ይታመንበታል። ፅንፈኝነት የመንግሥት ሚዲያ ላይ ተደጋግሞ የሚሰማና በተለይ ከፖለቲካ አቅጣጫ ሰፊ ቅስቃሳ  እየተሰራበት ይገኛል። ይህን ፅንፈኝነት  ለመፈተሽ ስንነሣ ቅድሚያ የሚገኘውን  የስኩርተንን ትርጓሜ መመልከቱ የተሻለ ሆኖ አገኘነው፡፡ በስኩርተን እምነት ፅንፈኝነት "ፅንፈኝነት በራሱ "ግልፅነት የሚጐድለው (Vague) ቃል መሆኑን በቅድሚያ ያስቀምጥና የሚከተሉትን ሦስት ትርጓሜዎች ሊይዝ እንደሚችል ግን ያሰፍራል፡- "1ኛ/ አንድ የፖለቲካ አስተሳሰብ ከሚያስከትለው መልካም ያልሆነ ውጤት፤ ኢ-ተግባራዊነት፤ እሰጥ አገባና እንዲሁም ከሚፈጥረው የተቃርኖ ስሜት ባሻገር ግጭትን ግቡ ባደረገና ተቃዋሚን በማጥፋት ዓላማ ላይ የተመሰረተ ሲሆን፣ 2ኛ/ ከራስ ወይም ከቡድን አመለካከት በስተቀር የሌላውን አለመታገስ (አለመቻቻል) እና 3ኛ የፖለቲካ ግብን ለማስፈፀም የያዙትን መንገድ የሌላውን ሕይወት፣ ነፃነት እንዲሁም ሰብዓዊ መብትን ከግምት ባልከተተ ሁኔታ ተግባራዊ ማድረግ...” ናቸው። ፅንፈኝነት በጥቅሉ ሲታይ እንዲህ ይቀመጥ እንጂ ዋና ዋና የሚባሉ መገለጫዎቹን በአጭር በአጭሩ መመልከቱ ደግሞ የተያዘውን ግራ ማጋባት ብቻ ሳይሆን የያዘንንም ግራ መጋባት የሚያጠራልን ይሆናልና ወደዚያው እናምራ፡- የመጀመሪያው ፖለቲካዊ ፅንፈኝንት መገለጫው "የግለሰብን ሰብእና ማቆሸሽ ነው። ፅንፈኞች ተቃዋሚያቸው ወይም ተቺዎቻቸው የሚያቀርቡባቸውን ተፃራሪ ሃሳብና መከራከሪያ እውነታዎች በማንሣት ከመሞገት ይልቅ የእነሱን ስብዕና እና ግላዊ ባህርይ በምላሹ በማራከስና በማሳጣት ላይ የተጠመዱ ይሆናሉ፡፡ በተቃዋሚዎቻቸውና ተቺዎቻቸው ላይ ጥያቄዎቻቸው አነጣጥረው የራሳቸውን ምላሽ ከሚሰጡባቸው መካከል... ከጀርባ አንግበውታል በሚሉት ፍላጐት፣ በቀድሞ ፖለቲካዊ ግንኙነቶቻቸው፣ በእምነትና ማኅበራዊ እሴቶቻቸው፣ ከሌሎች ፖለቲከኞች ጋር ባላቸው መስተጋብር፣ በትምህርት ደረጃቸው... ጥቂቶቹ ሲሆኑ በዚህም እያስታከኩ ከዋነኛው የመከራከሪያ ርዕስ ጉዳይ ማፈንገጥን የዘወትር ልምምዳቸው ያደርጉታል። - በሁለተኛ ደረጃ የፅንፈኞች መገለጫ ለተቃዋሚና ተቺዎቻቸው "ስም ማበጀትና መፈረጅ" ነው፡፡ በዚህ ረገድ ፅንፈኞች የሚነሱባቸውን የተቃውሞ አስተሳሰቦችና ትችቶች በሌላ አስተሳሰብ ከመጋፈጥና ከማሸነፍ ይልቅ እንደ ዘረኛ፣ አመፀኛ፣ ጥላቻ ዘሪዎች፣ የላሹቁ፣ የቀድሞ ሥርዓት ናፋቂዎች... ወዘተ የተሰኙትን ስሞች በማበጀትና በዚያም ጐራ በመፈረጅ የሚነሱ ጥያቄዎችንና የሚሰነዘሩ ትችቶችን ያድበስብሷቸዋል። በሦስተኛ ደረጃ ፅንፈኞች ማንነታቸውን የሚገልጡት "ኃላፊነት ለጐደለው አጠቃሎ ፈጣን በመሆን" ነው። ይኸውም አንዳች ማስረጃ ሳይዙ ወይም በጣም ጥቂት የሚያመሳስሉ ነገሮችን በመምዘዝ ብቻ ላይ ተመስርተው ተቃዋሚዎቻቸውንና ተቺዎቻቸውን የዚህ ወይም የዚያ ፖለቲካ አስተሳሰብ አራማጅ ወይም የፖለቲካ ፓርቲ አባል ነው በማለት በመኮነን የተጠመዱ ሲሆን በዚህም ምክንያት  በተቃርኖ የሚነሱ አስተሳሰቦች ተጨፍልቀው የማለፋቸው ዕድል የተረጋገጠ ይሆናል ማለት ነው። ለምሣሌ አንድ የኢኮኖሚ ምሁር የመንግሥትን ፖሊሲ አስመልክቶ የሚተች ወይም የሚያርም ጽሑፍ በሌላ የኢኮኖሚ ትንታኔ ላይ ተመስርቶ ቢያቀርብ ከምሁሩ ሃሳብ ይልቅ ምሁሩን ወደአንድ ጐራ በፍጥነት የመጠቅለል አካሄድን መከተል ይሆናል። በዚህም ተመሳሳይነትን አንድ ከመሆን ጋር በስፋት ሲያምታቱት ይስተዋላል።" አራተኛው የፅንፈኞች መገለጫ "ለአስተሳሰብና አቋማቸው በቂ ማረጋገጫና ድጋፍ አለማቅረባቸው ነው፡፡ በዚህ ረገድም የሚቀርብባቸውን ተቃውሞም ሆነ ትችት በራሳቸው አቋም ላይ ተመስርተው ለማሳመን በቂ ማረጋገጫ (proof) ስለሚያጥራቸው መከራከሪያቸው የቀድሞውን ክስተት አንስቶ ነገ እንደሚሆን ለማሳመን መጣር ላይ ያነጣጠረ ነው፡፡ ነገር ግን እንዲህ ዓይነቱ ከዛሬ ይልቅ በነገ ላይ የተንጠለጠለ ምኞትና ፍራቻ የዛሬውን ጠቃሚ መረጃ እንዲጥሉ የሚያደርጋቸው ብቻ ሳይሆን ክርክራቸው ተጠያቂያዊ መፋለስ የያዘም ይሆናል፡፡ በመሆኑም የተቃዋሚ አስተሳስብን ከመመርመር ይልቅ ማጥላላት የሚቀናቸው ናቸው፡፡ - በአምስተኛ ደረጃ የፅንፈኞች መታወቂያ የሆነው "ሁለት አቋሞችን ደርበው በአንድ ላይ የማራመድና ለእነሱም የመቆም ባህርይ መያዛቸው ነው፡፡ " ፅንፈኞች ራሳቸውን የሚዳኙት በሚያስቡት እንጂ በሚተገብሩት ነገር አይደለም፤ አንድን አቋም በእምነት ደረጃ ብቻ ተቀብለው ሲያበቁ ተግባራዊ ምላሽን ግን ይነፍጋሉ፡፡ የሚወክሉት ወገን ያሳለፈውን መከራ ወይም ያለፈበትን የትግል ታሪክ ምክንያት አድርገው ዛሬ እነሱ በልዩ መስፈርት እንዲዳኙ እንጂ በተቃዋሚያቸው ሃሳብ ላይ ተመርኩዞ የመደራደርን ዲሞክራሲያዊ አስተሳሰብ ከመርህ ባለፈ የሚሹት አይሆኑም። ይቀጥላል... @zephilosophy

አንዳንድ ጊዜ የውሸት ደስታ ተስፈኝነት አይደለም። ከእውነታው መሸሽ ነው። ሰዎችም ልዩነቱ ሊሰማቸው ይችላል። አንዳንድ የአዎንታዊነት አይነቶች ስትሰሟቸው ባዶ ሆነው የሚሰሟችሁ ለዚህ ነው። ምክንያቱም እውነታውን በፍጥነት ዘለው ያልፋሉ። ምንም ነገር ሳይረዱ ለመጽናናት ይጣደፋሉ። ስሜትን ማዳመጥ እንዳለባችሁ ነገር ሳይሆን መቆጣጠር እንዳለባችሁ ነገር አድርገው ይቆጥሩታል። ይህ ማለት ስቃይ ከደስታ ይበልጣል ማለት አይደለም። ጨለምተኛ ወይም ስሜት አልባ መሆን አለብን ማለትም አይደለም። ዋናው ሀሳብ ደስታን መቃወም ሳይሆን ደስታን ማምለክ ማቆም ነው። ምክንያቱም ደስታ የሕይወት ዋና ግብ ሲሆን፣ እውነታውን በሐቀኝነት መጋፈጥ አትችሉም። እያንዳንዱን ተሞክሯችሁን በስሜት መመዘን ትጀምራላችሁ። "ይሄ ደስተኛ ያደርገኛል?" "አሁን ጥሩ ስሜት እየተሰማኝ ነው?" "በሕይወቴ በቂ ደስታ እያገኘሁ ነው?" እናም መልሱ አይደለም ከሆነ ድንጋጤ ይጀምራል። ግን ምናልባት ትርጉም ያለው ሕይወት ማለት ሁልጊዜ ጥሩ ስሜት የሚሰጥ ሕይወት ላይሆን ይችላል። ምናልባት ነገሮችን በግልጽ የሚያይ ሕይወት ሊሆን ይችላል። ግልጽነት ከደስታ የተለየ ነው። ግልጽነት ምቾት ማጣትን ሊያካትት ይችላል። እርግጠኛ አለመሆንን ሊያካትት ይችላል። ስለራሳችሁ እና ስለ ዓለም ከባድ እውነቶችን መጋፈጥን ሊያካትት ይችላል። ግን እውነተኛ ነው። እና ፍጹም ባይሆንም እንኳ፣ እውነታው ላይ መቆም በሚያስገርም ሁኔታ የሚያረጋጋ ነገር አለው። ~ ደስታና የዘመናዊው ዓለም ልክፍት ✍️ዮናታን በጋሻው @zephilosophy

በየቦታው እየተካሄደ ያለ አንድ ገራሚ የማስመሰል ትዕይንት አለ። በኢንተርኔት ላይ፣ በሰዎች ጭውውት ውስጥ፣ ሰዎች ሳያስቡ በሚደጋግሙት ምክር ውስጥ ታዩታላችሁ። ሁሉም ሰው ደስተኛ መስሎ ለመታየት ይሞክራል—ወይም ቢያንስ ወደ ደስታ የቀረበ ለመምሰል። ፈገግታ የሞላባቸው ፎቶዎች። የሚያነቃቁ ጽሑፎች። ስለ "ብርታት”፣ “አዎንታዊ አስተሳሰብ” እና “ምርጥ ሕይወት ስለመኖር” የማያቋርጡ ወሬዎች። ከጥቂት ጊዜ በኋላም፣ የሆነ የማይመች ስሜት ይጀምራቹሃል። እንደ ሀዘን ሳይሆን ጥርጣሬ!! ምክንያቱም በውስጣቹህ ከዚህ ሁሉ ነገር ጀርባ የሆነ አርቴፊሻል (የውሸት) ነገር እንዳለ ግማሹ እኔነታችሁ ያውቀዋል። ሰዎች ፈጽሞ ደስታ አይሰማቸውም ማለት አይደለም። በእርግጥ ይሰማቸዋል። እውነተኛ የደስታ ጊዜያት አሉ። እውነተኛ ሳቅ። እውነተኛ ግንኙነት። ጥሩ ጭውውት። ስክን፣ ረጋ ያለ ጠዋት። ውስጣችንን ጠልቆ የሚነካ ሙዚቃ። ከችግር በኋላ የሚመጣ እፎይታ። ፍቅር። ጓደኝነት። እረፍት። እነዚህ ነገሮች አሉ። ግን ዘመናዊው ሕይወት ሊሸጥልን የሚሞክረው የደስታ ምስል ሙሉ በሙሉ የተለየ ነገር ነው። ቅጽበት አይደለም። ሁኔታ ነው። ደስታ ቋሚ ስሜታዊ ጸባያችን መሆን ያለበት አይነት ሁኔታ ነው። የተሳካ ሕይወት ማለት ችግር የጠፋበት ሕይወት እንደሆነ አይነት። እናም ችግሩ የሚጀምረው እዚህ ላይ ነው። ምክንያቱም ማንም የሰው ልጅ በእውነቱ እንደዚያ አይኖርም። አንዳንድ ቀናት በተስፋ ተሞልታችሁ ትነቃላችሁ። ሌሎች ቀናት ደግሞ ያለ ምንም ግልጽ ምክንያት ባዶነት ይሰማቹሃል። አንዳንድ ጊዜ ጠዋት ላይ የሆነ ተነሳሽነት ይሰማችሁና ማታ ላይ ጠፍቶባችሁ ታመሻላችሁ። አንዳንድ ጊዜ አንድ ትልቅ ነገር አሳክታችሁ እንኳን በሚገርም ሁኔታ እርካታ ታጣላችሁ። የስሜት ዓለማችን ያለማቋረጥ ይለዋወጣል። ችግር ስላለብን አይደለም። የስሜት ሁኔታዎች በተፈጥሯቸው ያልተረጋጉ ስለሆኑ ነው። ይሁን እንጂ በዘመናዊው ባህል አለመረጋጋት እንደ ውድቀት ይቆጠራል። ሁልጊዜ ደስተኛ፣ የተረጋጋ፣ ተነሳሽነት ያለው፣ አምራች እና አመስጋኝ ካልሆናችሁ የሆነ ችግር አለባችሁ ማለት ነው። ስለዚህ ሰዎች ጤናማነትን እንዴት ማስመሰል እንዳለባቸው ይማራሉ። በየቦታው ታዩታላችሁ። ሰዎች ዝምታን ስለሚፈሩ በግድ ጥሩ ነገር ለማውራት ይሞክራሉ። እያንዳንዱን ትግል ገና በደንብ ሳይረዱት ወደ አነቃቂ ንግግር ይቀይሩታል። በውስጥ ታክተው እና ዝለው በአደባባይ ፈገግ ይላሉ። እርግጠኛ አለመሆን አሳፋሪ ስለሚመስል፣ የውስጥ ሰላም እንዳላቸው ያስመስላሉ። እናም ቀስ በቀስ፣ ደስታ ራሱ የውሸት ስሜት መምሰል ይጀምራል። ለዘለዓለም እንዲቆይ ያልተፈጠረን ስሜታዊ ሁኔታ ጠብቆ ለማቆየት መሞከር በጣም አድካሚ የሆነ ነገር አለው። ሕይወታችሁን ሙሉ ፊታችሁ ላይ አንድ ዓይነት ገጽታ ብቻ ይዛችሁ ለመቆየት መሞከርን አስቡት። ውሎ አድሮ፣ ከተፈጥሮ ውጪ ይሆናል። ህመም ሁሉ ይሆናል። ደስታ ተሞክሮ መሆኑ አብቅቶ ግዴታ (የሚጠበቅ ነገር) ሲሆን የሚፈጠረው ይሄው ነው። ስሜቶቻችሁን መቆጣጠር (መጠበቅ) ትጀምራላችሁ። ሀዘን ብቅ ባለበት ቅጽበት፣ ልታጠፉት ትሞክራላችሁ። መሰላቸት ሲመጣ፣ ራሳችሁን አዘናግታችሁ ለመላቀቅ ትጥራላችሁ። ጭንቀት ሲፈጠር ትደናገጣላችሁ—በጭንቀቱ ምክንያት ብቻ ሳይሆን፣ መጨነቅ የለብኝም ብለን ስለምናስብም ጭምር ነው። ግን ምናልባት ችግሩ መጥፎ ስሜቶች መኖራቸው ላይሆን ይችላል። ምናልባት ችግሩ ሊኖሩ አይገባም ብሎ ማመኑ ላይ ይሆናል። ከረጅም ዘመናት በፊት ኤፒኩረስ የተባለ ፈላስፋ ነበረ፤ ብዙ ጊዜ በደስታ (በስጋዊ እርካታ) ያበደ ሰው ተደርጎ በተሳሳተ መንገድ የሚተረጎም ፈላስፋ ነው።  ግን በጥልቀት ስትመለከቱት፣ እሱ በእርግጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ከዚህ እርካታ በጣም የረጋ ነገርን ነበር። ማለቂያ የሌለው ደስታ (እርካታ) አልነበረም። የስሜት መነቃቃት አልነበረም። ቀላልነትን ነበር። አላስፈላጊ ከሆነ ሥነ-ልቦናዊ ትርምስ ነጻ የሆነ ሕይወት። ከጓደኞች ጋር የምትጋሩት ትንሽ ምሳ። የተረጋጋ አእምሮ። ከማያቋርጥ መሻት (ምኞት) ነጻ መሆን። ይህ ዘመናዊው ዓለም ለደስታ ካለው ከልክ ያለፈ አባዜ በጣም የራቀ ይመስለኛል። ዛሬ፣ ደስታ በውስጣችሁ ያለማቋረጥ ማምረት ያለባችሁ ምርት ተደርጎ ነው የሚታየው። እርካታ ሊሰማችሁ ይገባል። ተነሳሽነት ማሳየት አለባችሁ። Passionate መሆን አለባችሁ። እርግጠኛ መሆን አለባችሁ። ይህ ካልሆነ ደግሞ፣ ራስ-አገዙ ባህል ሊያርማችሁ ከተፍ ይላል። በደንብ አሰላስል (Meditate አድርጉ)፣ positive ነገር አስቡ፣ mindሴትህን አስተካክል፣ የተሻለ energy ወደራሳችሁ ሳቡ (manifest አድርግ) ይሏቹሃል። የስሜት መወሳሰብ ማለት ልክ ራስን በአግባቡ ማስተዳደር አለመቻል እንደሆነ ተደርጎ ይቆጠራል። ግን ሕይወት እንደዚያ በተስተካከለ መንገድ አትጓዝም። ንቃተ-ህሊና ራሱ ያልተረጋጋ ነው። ስሜቶቻችን ለትዝታ፣ ለእርግጠኛ አለመሆን፣ ለፍርሃት፣ ለፍላጎት፣ ለድካም፣ ለብቸኝነት፣ ለሥነ-ህይወት፣ እና ለጊዜ ምላሽ ይሰጣሉ። ስሜቶቻችን የሚለዋወጡት በህይወት ስላለን ነው። ሲጀመርም አላፊ በሆነ ህልውና ውስጥ ቋሚ የስሜት ሁኔታ እንዲኖር መጠበቅ ፈጽሞ እውነታውን ያገናዘበ አይደለም። እና በእውነቱ አንዳንድ የሀዘን አይነቶች ችግሮች እንኳን አይደሉም። ግልጽነት (ነገሮችን አጥርቶ የማየት ውጤት) ናቸው። ስጋት ውስጥ መሆን ትክክለኛው ምላሽ የሚሆንባቸው ጊዜያት አሉ። ሕይወታችሁን በጥልቀት ስትመለከቱና እርግጠኛ እንዳልሆናችሁ ስትገነዘቡ። በዙሪያችሁ ካሉ ሰዎች ጋር መራራቅ ሲሰማችሁ። የወደፊቱ ጊዜ ግልጽ ያልሆነ ሲመስላችሁ። ሕይወት ምን ያህል አሰልቺና ተደጋጋሚ እንደምትሆን ስትረዱ። ስለነዚህ ነገሮች ያለን ግንዛቤ ለምን በአዎንታዊነት ይዋጣሉ?

ጦርነት! (አሌክስ አብርሃም) ሳይጀመር...​ ዛቻው፣ ማስፈራሪያው፣ ቅስቀሳው፣ ፍርሃትና ስጋቱ፣ ጥላቻው መንፈስህን ይገድለዋል፤ ቀንህንና ጊዜህን ይቀማሃል። ጦርነቱ ይጀመራል...ሰላምህን ይነጥቅሃል፣
ጦርነት! (አሌክስ አብርሃም) ሳይጀመር...​ ዛቻው፣ ማስፈራሪያው፣ ቅስቀሳው፣ ፍርሃትና ስጋቱ፣ ጥላቻው መንፈስህን ይገድለዋል፤ ቀንህንና ጊዜህን ይቀማሃል። ጦርነቱ ይጀመራል...ሰላምህን ይነጥቅሃል፣ ደህንነትና የህግ ዋስትናህን ይነጥቅሃል፣ የምትወዳቸውን ሰዎች ይነጥቅሃል፤ ንብረትህን ይነጥቅሃል፤ ልማትህን፣ ተስፋህን፣ መተማመንህን፣ አካልህን፣ ዕድሜህንና ሕይወትህን ጭምር ይነጥቅሃል። በደም ያጨቀይሃል። ​ከቆመ በኋላ....ክፍለ ዘመን ወደኋላ ወስዶ ያቆመሃል።  "ይመለስ ይሆን?" የሚል ስጋት ያሸክምሃል፤ በርጋጊ ትሆናለህ፣ ትዝታው ዕድሜ ልክህን ያስቃዠሃል፤ የእድሜ ልክ የጥላቻና የሰቆቃ ታሪክ ያወርስሃል። ይሙቱ ይዳኑ የማታውቃቸው ልጆችህ፣ ወንድሞችህ፣ ጓደኞችህ ሞቱም ዳኑም ሳይባል ይጠፋሉ፤ ጠባቂ ልብ ታቅፈህ ትቀራለህ። የፈረሰ ከተማ ፣ የፈራረሰ ሰብዓዊነት፣ የፈራረሰ ፍቅር ፣ትሸከማለህ፤ የፈራረሰ እምነት ትሸከማለህ። ቂም በቀል ታረግዛለህ። ​ጦርነት ሳይጀመርም፣ ተጀምሮም፣ አቁሞም ሰቆቃ የሆነ የማይፀዳ የሕይወት ጥቀርሻ ነው። አትጀምረው፤ ከጀመርከው ለማቆም የመጨረሻ አቋምህን ተጠቀም፤ ከቆመ ደም የበከላት ምድርህን ተባብረህ አፅዳ። @zephilosophy

ፀሀይ ለሁሉም ቀን አዲስ ቀን ይዛ አትመጣም። አንዳንዱ ቀን ራሱን ይደግማል ።ደግሞ አንዳንዱ ዕለት የምስራች ይዞ ሲመጣ ፣ ሌላው ቀን መርዶ ሊተረክክ ወጋገን ይሰዳል። በሌላኛው ቀን ከእንቅልፌ ስነቃ የቤታችን ቆርቆሮ ክዳን በላይችን ላይ አልነበረም። ዓይኖቼ ያረፉት ወደ ሰማያዊ ሰማይ ነበር።በደመ ነፍስ እየተጣዳፍኩ ከወደቅኩበት ተነሰቼ ወደ አባ አመራሁ።ልባቸው እንደ ከበሮ መደለቅ ጀምራ ቁና ቁና እየተነፈሱ ሲያጣጥሩ  ከአልጋቸው አጠገብ ደረስኩ። ቤታችን ቅሪት እንኳ አልነበረውም። አውላላ ሜዳ ላይ ነበርን። ጦርነቱ በህልውናዬ ላይ የፈጠረው ኪሳራ ነበር። ሕይወቴንና ማንነቴን በአንድ አፍታ ቀይሮታል። የማንነቴ ካስማ የተጣለበት ስፍራ እንዳልነበር ኾኗል። በዙሪያዬ ነፍሴን የማስጠልልበት ዓለም አልነበረኝም። ደካሞች እግዚአብሔርን ምርኩዛቸው ሲያደርጉ ኃያላን ግን በሥልጣናቸው ይመካሉ። ታሪክ የሚያስረዳው ፈጣሪ ይህችን ምድር ይፍጠራት እንጂ በአዛዥ ናዛዥነት የሚያስተዳድሯት ሊቀ መናብርት ሰዎች ናቸው። በየዕለቱ ንጹሓን በግፍ ይገደላሉ። በጨለማ የማሰቃያ ማጎሪያዎች የምስኪኖች ቅስም እንደ አጥንት ሲከተከት እግዚአብሔር የፍጥረታቱን የማያልቅ ሰቆቃቸው እየታዘበ ስለምን ዝም አለ? ስንት ሰው ሲሞት ነው የእግዚአብሔር ኃይል የሚገለጠው? በመንግሥተ ሰማያት መካሻ ስላዘጋጀ በሰው ልጆች ምድራዊ ሕይወት ጣልቃ አይገባም? ወይስ እንደ ቅጠል የሚረግፉትን ንጹሐን ይታደጋቸው ዘንድ በእርሱ ላይ ያላቸው እምነት ጎዶሎ ነው? ፈጣሪን ልክ ለማድረግ በሚኬድ ርቀት እግዚአብሔር እንዲታደጋቸው ያስጥላቸው ዘንድ ቢማጸኑትም እጁን ከአርያም ሳይሰድላቸው ቀርቶ መከራ ሞትን የተቀበሉ ሰዎች የሰማዕትነት ማዕረግ አልተሰጣቸውምን? ይህስ የሕይወት ወለፈንዲዊነት አይደለምን? ይህ መከራና ሰቆቃ ዕውቅና የለሽ ነው። እንደ አደባባይ ምሥጢር በግልጽ የሚያወራው የለም። መሃል ከተማ ጥሩ ቀን እያለፈ ይመስላል። የዳር ሀገር ጩኸት የመሀሉ ሀገር ግድ አይሰጠውም እዚ የተለኮሰው እሳት እዛ አይደርስ ይመስል!! መሽቶ ሲነጋ ከፀሓይ መውጣት ጋር ለኑሯቸው የሚዳክሩ ሰዎች ማልደው ከእንቅልፋቸው ይነቃሉ። በዚህች ቀን ማን መንቃትን በብርቱ እየተመኘ እስከ መጨረሻው አሸልቦ ይኾን? ማንስ በጥልቅ ከዚህች መከረኛ ሕይወት መገላገል እንደ ፈለገ ሳይሳካለት ቀረ ይኾን? #No_More_War @zephilosophy