cookie

Sizning foydalanuvchi tajribangizni yaxshilash uchun cookie-lardan foydalanamiz. Barchasini qabul qiling», bosing, cookie-lardan foydalanilishiga rozilik bildirishingiz talab qilinadi.

avatar

ፍልስፍና ለላቀ አስተሳሰብ Philosophy

ፍልስፍና  እውነትን በመፈለግ- ሀሳዊ እምነቶችን በማጋለጥ እና ጭፍን አመለካከቶችን በጥበብ በመመርመር ወደ ላቀ አሰተሳሰብ ያሻግራል። በዚህ ቻናል አለም ላይ ያሉ ፍልስፍናዎች ፤ ርዕዮት አለሞች ፤  ሀይሞኖቶች እና አስተሳሰቦች በነፃነት ይዳሰሳሉ።

Ko'proq ko'rsatish
Reklama postlari
19 345
Obunachilar
+624 soatlar
+397 kunlar
+60530 kunlar

Ma'lumot yuklanmoqda...

Obunachilar o'sish tezligi

Ma'lumot yuklanmoqda...

Consequentialism Vs Hedonism ምንጭ ፦ የፍልስፍና ትምህርት ቅፅ ፪ አርታኢና አዘጋጅ ፦ ብሩህ አለምነህ እነዚህ ሁለቱ የሥነ ምግባር ፅንሰ ሐሳቦች ልዩነታቸው ትንሽ ያምታታል፡፡ አንድ የሚያደርጋቸው ሁለቱም ውጤት ተኮር መሆናቸው ሲሆን፤ ልዩነታቸው የሚመጣው የውጤቱ ዓይነት ሲመረመር ነው፡፡ •Consequentialism ውጤቱን ከላይ እንደገለጽነው በጥሩነትና በመጥፎነት ሲገልፀው ማለትም አንድ ድርጊት ትክክለኛ የሚባለው ጥሩ ውጤት ሲኖረው ነው በማለት የሚከራከር ሲሆን ጥሩና መጥፎ ማለት ደግሞ እንዳቀማመጣቸው ጠቃሚና ጎጂ፤ አስደሳችና አስከፊ፣ ገንቢና አፍራሽ፣ የሚያስቅና የሚያሳዝን፣ ጤናና በሽታ ማለት ሊሆን ይችላል፡፡ .Hedonism በበኩሉ በመሠረታዊ ባህሪው ጥሩ የሆነ ነገር አካላዊ/ጊዜያዊ እርካታ(Pleasure) ሲሆን መጥፎ የሆነው ደግሞ ህመም (Pain) ብቻ እንደሆነ ያስቀምጣል፡፡ Hedonism የሚመራበት መርህ pleasure principle ይባላል፡፡ ሄዶኔ (Hedone) ማለት በግሪክ እርካታ (Pleasure) ማለት ነው፡፡ አንድ ሰው ‹‹ሄዶኒስት ነው›› የሚባለው ግቡ አካላዊ እርካታ (Pleasure) ብቻ ሲሆን ነው፡፡ አንዳንድ ጊዜ በHappiness (ደስታ) እና በPleasure (እርካታ) መሐከል ያለው ልዩነት የHedonismን ትክክለኛ ሓሳብ ሲያወሳስበው ይታያል፡፡ ‹‹እርካታ›› ከአካላዊ ፍላጎቶች መሟላት (ምግብ፣ መጠጥ፣ ወሲብ) ጋር የተገናኘ ሲሆን (ለዚሀም ይመስላል አሪስቶትል ይህ ለእንስሳት እንጂ ለሰው ልጅ የሚሆን ግብ አይደለም በሚል የሚተቸው) ደስታ ግን ዘለቄታ ያለውና በራሱ የህይወት ግብ መሆን የሚችል ነው (Aristotlc 1996 10)፡፡ ከላይ ወደተነሳንበት የConsequentialism እና Hedonism ልዩነት ስንመለስ ለምሳሌ እኔ ‹‹እንቅስቃሴ የምሰራው ለጤናዬ ስለሚረዳኝ ነው›› ካልኩ ‹‹እንቅስቃሴ መስራቱ ጥሩ ነው›› የሚለው አመለካከቴ የእንቅስቃሴን ትክክለኛነት በውጤቱ መሆን ላይ የተንጠለጠለ ስለሚያደርገው Consequentialist ነኝ፤ ሆኖም ግን ሄዶኒስት አይደለሁም፡፡ ምክንያቱም፣ ግቤ እርካታ ሳይሆን ጤና ስለሆነ፡፡ ስለዚህ፣ Consequentialist የሆነ ሁሉ ሄዶኒስት ነው ማለት አይደለም፡፡ Consequentialist ሄዶኒስት የሚሆነው የሚፈለገው ውጤት እርካታ ሲሆን ብቻ ነው፡፡ ሆኖም ግን፣ እኛ የምንፈልጋቸው ውጤቶች በህይወታችን ውስጥ እርካታ ብቻ አይደለም፡፡ ልክ እንደ ጤና፣ ገንዘብ፣ እውቀትን እንዲሁም ስልጣንን ግብ አድርገን ልንነሳ እንችላለን፡፡ በዚህ ጊዜ Consequentialist ሆነን፣ ሄዶኒስት አልሆንንም ማለት ነው፡፡ ሆኖም ግን፣ አንድ ሰው፣ ‹‹የአንድ ድርጊት ውጤት ጥሩ ነው የሚባለው አርኪ ሲሆን ነው ብሎ የሚያምን ከሆነ ይሄ ሰው Consequentialist ብቻ ሳይሆን hedonistም ነው ማለት ነው፡፡ @zephilosophy @zephilosophy
Hammasini ko'rsatish...
የሬኒ ዴስካሬት ፍልስፍናዊ ሃሳቦች ምንጭ ፦ የፍልስፍና ሀሁ ትርጉም ፦ ራሴላስ ጋሻነህ ዴካርት ይበልጡን "አስባለሁ፤ ስለዚህ አለሁ” በሚለው አባባሉ ይታወቃል፡፡ ለዴስካሬት የማሰብ ሂደት በራሱ ለግለሰባዊ ህያው መሆን ማረጋገጫ ነው፡፡ እንዲሁም የሰው ልጅ ማሰብና ምክንያት ማቅረብ መቻሉ የሰብአዊነቱ መሰረታዊ ባህሪ ነው፡፡ ምክንያቱም የሰው ልጅ ህያው ስለሆኑ ስለሌሎች ነገሮች እርግጠኛ መሆን በማይችልበት ሁኔታ ውስጥ፣ ማሰብ እና ምክንያት ማቅረብ መቻሉን እርግጠኛ መሆን ይቻላል ብሎ ያምናል፡፡ ሃሳቦች እንዲኖሩ ለማሰብ ግብዓት የሚሆኑ ነገሮች መኖር አለባቸው፡፡ ስለዚህ አንድ ሰው ካሰበ ህያው ነው ማለት ነው፡፡ ለዴስካሬት፣ ስዎች አመክንዮን ማቅረብ ይችላሉ፤ ይሄንን ካላደረጉ ግን በቀላሉ ሰዎች አይደሉም ማለት ነው፡፡ ዴካርት እውነት የሚመስል ህልም ካየ በኋላ ከእንቅልፉ ባነነ፤ ለራሱም አሁንስ እያለምኩ ቢሆን ምን ማስረጃ አለኝ? ብሎ ጠየቀው:: ዴካርት በአለም ውስጥ ሊያምነው እና በፍጹም እርግጠኛ ሊሆን የሚችልበትን ነገር ፈለገ። ህልሙ ስለ እውነታው አለም ሊያታልለው ከቻለ ሌላ እርግጠኛ ሊሆንበት የሚችል ምን ነገር ይኖረዋል? አንድ ሲደመር አንድ- ሁለት ባይሆንስ? የሆነ ሰይጣን አንድ ሲደመር አንድ ሁለት እንደሆነ እያሳመነው ቢሆንስ? ሁሌም አንድን ከአንድ ጋር ለመደመር ሲያስብ ሁለት እንደሆነ የሚነግረው ሰይጣን ቢኖርስ? ዴካርት ሁሉንም ነገር ጠረጠረ፤ የስሜት ሕዋሳቶቹ የሚነግሩትን ነገር በሙሉ ጠረጠረ፡፡ ምናልባትም የሰይጣን ቤተ ሙከራ ውስጥ ባለ በፈሳሽ ብልቃጥ ውስጥ ጭንቅላቴን ብቻ ዘፍቀውት ይሆናል፤ የማየው እና የምሰማው ሁሉም የውሸት እና የሌለ ነገርን ሊሆን ይችላል። ዴካርት በአለም ላይም እርግጠኛ ሊሆንበት የሚችልን ነገር ፈለገ፡፡ በመጨረሻም አንድ ነገር ላይ እርግጠኛ ሆነ - 'መኖሩን' የሰው ልጅ ማሰቡ ብቻውን፤ (ምንም ያስብ ምን) እርሱ ህላዊ እንደሆነ (እንዳለ) ይነግረዋል፡፡ ማንም እኔ ሳልኖር እንዳለሁ አድርጎ ሊያታልለኝ አይችልም:: ይህንን ሃሳብም ለማሰብ በቅድሚያ መኖር ይኖርብኛል:: የሞተ እና የሌለ ሰው አያስብም፡፡ ሰው ሃሳቡ' ይርባም ይጥቀምም፣ ካሰበ ለመኖሩ ማስረጃ ይሆነዋል፤ ሰይጣን ጭንቅላቴን በቤተ- ሙከራ ውስጥ ባለ ብልቃጥ ውስጥ ቢያስቀምጠውም ሆነ ሁሉም ነገር የውሽት ቢሆን፣ እኔ በዚህ ምድር አለሁ፤ እኔ ሳልኖር ሊያታልለኝ ፈጽሞ አይቻለውም። ለመኖሬ ማስረጃውም አሁን ላይ እያሰብኩ መሆኔ ነው፡፡ እናም ዴካርት እርግጠኛ የሆነበትን ነገር አገኘ እንዲህም አለ፤ “አስባለሁ፣ ስለዚህም አለሁ" ( I think, Therefore I am) በተጨማሪም ዴካርት ሰዎች በአመክንዮ ችሎታቸው እውነተኛ እውቀትንና ሳይንሳዊ ሃቀኝነትን (እርግጠኝነትን) ማግኘት ይችላሉ ብሎ ያምናል፡፡ ምክንያታዊነት ተፈጥሯዊ የሆነ፣ ለሁሉም ሰዎች የተሰጠ ስጦታ መሆኑን ስለሚያምን፣ እጅግ ውስብስብ በሆኑ ፍልስፍናዊ ጉዳዮች ላይ ለመፃፍ ገፋፍቶታል። ዕሁፎቹም ለአብዛኛው ሰው እንዲገቡ ተደርገው የተፃፉ ናቸው፡፡ አንዳንድ ጊዜ እንዲያውም ስራዎቹን ከላቲንኛ ይልቅ በፈረንሳይኛ ይፅፍ ነበር፡፡ ምክንያቱም ፈረንሳይኛ በጊዜው በምሁራን ዘንድ ጥቅም ላይ የሚውል ቋንቋ ስለነበር ነው፡፡ ከዚህም የተነሳ መጽሐፎቹ ለብዙሃን ህዝብ ተደራሽ መሆን ቻሉ፡፡ ዴካርት ፍልስፍናዊ ክርክሮች የሃሳብ አመክኖአዊ ልምምዶች ናቸው ብሎ ያምናል፡፡ እንዲሁም ማናቸውም ሰው በዚህ ልምምድ ውስጥ መሳተፍ ይችላልም ይላል፡፡ ማናቸውም ሃሳባዊ ችግር ወደ ቀላል ችግሮች ከተሰባበረ በኋላ፣ እነዚህ ትንንሽ ችግሮች ደግሞ በረቂቅ እኩልታዎች በኩል ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡ ይሄንን በማድረግም ማናቸውም ሰው (ዴካርት ተዓማኒ አይደሉም የሚላቸውን) የስሜት መረዳቶች ማስወገድ ይችላል ይላል፡፡ ከዚያም ችግሮቹን ለመፍታት ግላዊ ምክንያታዊነትን መጠቀም ይችላል፡፡ ስሜታዊ ወይም የስሜት መረጃዎች ተዓማኒ ባለመሆናቸው ዴካርት ብቸኛ እውነተኛ እና እርግጠኛ መሆን የቻለበት ጉዳይ ሰዎች አሳቢ ቁሶች እንደሆኑ ነው፡፡ ስለዚህ ምክንያታዊነት እና ሃሳብ የሰው ልጆች መሰረታዊ ባህሪ ናቸው፡፡ ደግሞም በንፁህ ምክንያታዊነትና በስሜታዊ መረጃዎች መካከል ልዩነት ስላለ የነፍስ መኖር ግዴታ ነው ሲል ዴካርት ይከራከራል፡፡ ህልወተ እግዚአብሔር እንዲያውም አንድ ጊዜ የሰው ልጅ ህያው ሆኖ ያለው፣ የሚያስብ ነገር ስለሆነ ብቻ ነው የሚል ድምዳሜ ላይ ደርሶ ነበር፡፡ ከዚያም ሌሎች ግላዊ ማረጋገጫ ያላቸውን እውነታዎች ለማግኘት ጥረት ጀመረ:: በስተመጨረሻም ዴካርት መረዳት እና ምናብ የንቃት መገለጫዎች ስለሆኑ፣ በአእምሮ ውስጥ መኖር አለባቸው ሲል ደመደመ፡፡ ነገር ግን እውነትን የግድ ሊይዙ የሚችሉ አይደሉም አለ፡፡ _ ስለዚህ ዴስካሬት በስተመጨረሻ ስለ ሌሎች ነገሮች ሀቀኛ እውቀት ሊኖረን የሚችለው፣ ስለ እግዚአብሔር እውቀት ሲኖረን ብቻ ነው ሲል ደመደመ። ዴካርት እግዚአብሔር ፍፁማዊ ነው ብሎ ከማመኑ የተነሳ፣ እግዚአብሔር ማንንም ሊያታልል አይችልም የሚል እምነት አለው፡፡ ዴካርት እራሱ እንኳን ፍፁማዊ እንዳልሆነ በማመን፣ ስለ ፍፅምና በተመለከተ ሃሳብ ለመፀነስ እንኳን፣ የግድ ፍፅምና መኖር አለበት ብሏል። ያ ፍዕምነት ደግሞ እግዚአብሔር ነው ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ስለ ፍፅምና ለማሰብ ራሱ ፍፁም የሆነ አካል መኖር አለበት፡፡ ያም ፍጽምና ደግሞ እግዚአብሔር ነው የሚል ድምዳሜ ላይ ደረሰ፡፡ @zephilosophy @zephilosophy
Hammasini ko'rsatish...
''ተነሱና እናመስግን።ምክንያቱም ዛሬ ብዙ ነገር እንኳን ባናገኝ ትንሽ ነገር አግኝተናል። ትንሽ ነገር እንኳን ባናገኝ ጤነኛ ነን። ብንታመም እንኳን ቢያንስ አልሞትንም። ስለዚህ ሁላችንም እናመስግን።''                               ጉተማ  ቡድሃ 🙏መልካም ምሽት🙏 @zephilosophy
Hammasini ko'rsatish...
ግሩም_ትረካ_-_ኦሾ_ (1).m4a11.28 MB
✍ካለፈው የቀጠለ✍ ሕያውነት (Resurrection) ክርስቶስ መጥቶ የክርስትናን አስተምህሮና የሰውን ልጅ መንፈሳዊ እሳቤዎች ከቀየረበት አብዮት በፊትም ቢሆን “ስለ ትንሳዔ (ሕያውነት) ምንም ፍልስፍና አልነበረም” ማለት አይቻልም። በግብጽ የኦስሪስ፣ በግሪክ አፈታሪክ የአችሊስና ሄሪኩለስ እንዲሁም በሂንዱኢዝሙ ሳምባዶር እንደ ምሳሌ ሆነው መቅረብ የሚችሉ ናቸው። ነገር ግን የሕያውነት ወይም ትንሳዔ ፍልስፍና ግልጽ ምስል መሰበክ የጀመረው በክርስቶስ ነው፤ በኋላም በእስልምና ሃይማኖት ተመሳሳይነት ያለው አስተምህሮ ተራምዷል። ይህም አስተምህሮ በምጽአት ጊዜ እያንዳንዱ ሰው በራሱ ነፍስ ትንሳዔን ያገኛል፤ ወይም በመጽሐፍ ቅዱስ እንደተጠቀሱ ታሪኮች ከሞቱ ኋላ የሚነሱ ሰዎች አሉ —(ክርስቶስ ራሱ እና ክርስቶስ ያስነሳው አላዛር)። “Resurrection” የሚለው ቃል ከተመሳሳዩ ላቲን ቃል የተገኘ ሲሆን ትርጓሜው “የሞተ ነገር ወደ ሕይወት ሲመለስ” ማለት ነው። ትንሳዔ ሁለት መገለጫዎች አሉት፤ መንፈሳዊ ትንሳዔና ቁስአካላዊ ትንሳዔ። በመንፈሳዊ ትንሳዔ ዕይታ ማንኛውም ሰው ዘለዓለማዊት ነፍስ ስላለችው ከሞት ይነሣል፤ ዘለዓለማዊ ፍርዱን ይዞ ኑሮውን ይኖራል። በቁስአካላዊ ትንሳዔ ደግሞ አንድ የሞተ ነገር ተመልሶ ህያው ሲሆን ማለት ነው። ነገር ግን ቁስአካላዊ ትንሳዔ እንበል እንጂ የነፍስን ረቂቅነት እስከተቀበለ ድረስ የሐሳባዊያን ተቃራኒ የሆነውን ቁስ አካላዊ ፍልስፍና ማለታችን አይደለም።ስለዚህም ሁለቱም ዕይታዎች ተመሳስሎሽ ያለባቸው መሆኑን ልብ ማለት ይቻላል። ነገር ግን አንዳንዶች ደግሞ አይጠፉም፤ “የሰው ልጅ የተሠራው ከቁስ ነው፤ ትንሳዔም ቢኖረው ቁሳዊ ትንሳዔ እንጂ ነፍስ የሚባል የለም” የሚሉ አይጠፉም። በመካከለኛው ዘመን ፈላስፎች በተለይ በ“ቅዱስ አውጉስቲን”ና “ቅዱስ ቶማስ አኩይናንስ” ይሄ አስተምህሮ ይበልጥ ተስፋፍቶና ፍልስፍናዊ ብያኔዎች እየተሰጡት ሊብራራ ችሏል። እንደ አኩይናንስ ዕይታ ሞት ለሰው ልጅ አስፈላጊ ብቻ ሳይሆን መሠረታዊም ነው፤ መሠረታዊነቱም ዘለዓለማዊ የሆነችው ነፍስ አዲስ ትንሳዔን ታይ ዘንድ ሞት ግድ መሆኑ ነውና ነው። እንዲህም እያለ ይሞግታል፤ —ነፍስ ከሥጋ ውጭ መኖር ይቻላታል፤ ምክንያቱም ነፍስ በሥጋ ውስጥ ትኖራለች እንጂ የሥጋ ጥገኛ አይደለችምና። ነፍስ በሥጋ ውስጥ ስትኖር ይህን ዓለም መስላ ትኖራለች፤ እናም የሥጋ ጥገኛ መስላ ትታያለች፤ እውነታው ግን “ሥጋ የነፍስ ጥገኛ እንጂ ነፍስ የሥጋ ጥገኛ አይደለችም።” የሚለው የአኩይናንስ ፍልስፍና ነው። ስለዚህም ይላል አኩይናንስ ነፍስ ከሥጋ ስትነጠል ይህን ዓለም የምታይበት መንገዱ ሌላ የኑሮ ዘይቤዋም ሌላ ይሆናል። የሥጋና ነፍስ መለየት ለነፍስ ውጤቱ፤ አዲስ ሁኔታ ውስጥ ገብቶ እንደ መብራት ዓይነት እንጂ አምፖል ቢሰበር መብራቱ ድርግም እንደሚለው ዓይነት አይደለም። ይሁንና በትንሳዔ ጊዜ አምፖሉና ኤሌክትሪኩ ይገናኙና ያ ቀዳማዊው ሁነት (ዓለም) እንደገና ይታያል። አውጉስቲን ደግሞ ነፍስ ኢ-መዋዕቲ መሆን አለባት የሚለውን የፕሌቶን ፍልስፍና አብራራው እንጂ ኢ-መዋዕቲ መሆኗን አይደለም። ነፍስ በተፈጥሮዋ ንጽሕና፣ ብጽዕናና ፍጽምና የሚስማማት ናትና ይላል። ፕሌቶ “ፍጹም ደስታ የነፍስ ጠባይ ነው” እንዳለው አውጉስቲንም “ለእዚህ እውነተኛና ፍጹም ደስታ ደግሞ ሞት የሚስማማው ባሕርይ አይደለም፤ እናም ነፍስ መዋዕቲ መሆን የለባትም፣ አይደለችምም” ይላል። ለአውጉስቲን ሞት ሁለት ዓይነቶች (ደረጃዎች) አሉት። የመጀመሪያው አንደኛ ሞት የሚለው የማትሞተው ነፍስ ከሚሞተው ሥጋ ስትለይ ነው። እንዲህ ያለው ሞት የሰው ልጆች ሁሉ ባሕርይ (ዕጣ ፈንታ) የሆነው አዳምና ሄዋን በሠሩት ኃጢአት ምክንያት ከአባቶቻችን በወረስነው መርገም የተነሣ ነው። “ይህኛው ሞት የአምላክ ቅጣት ነውና በበጎ መታየት አለበት” —ይላል አውጉስቲን። በጎነቱ ግን እንደ ቅጣት እንጂ እንደ ውስጣዊ ስሜት አይደለም። ውስጣዊ ስሜትን ያጤንን እንደሆነ ለበጎው በጎ ለመጥፎው መጥፎ ውጤት ያለው ነው። በውጤቱ መልካም ከሆነ ነፍስን ወደቀጣዩ ጥሩ ሽግግር መግፍኤ ይሆናል። ለአውጉስቲን ሁለተኛው የሞት ዓይነት ወይም ደረጃ ደግሞ የነፍስ መሞት ነው። እዚህ ላይ “ነፍስ ኢ-መዋዕቲ ናት” ከተባለ በኋላ “የነፍስ መሞት እንዴት ይመጣል?” የሚለው ቁም ነገር መነሣት አለበት። አውጉስቲን እዚህ ጋ የነፍስ ሞት የሚለው እግዚአብሔር ነፍሳችንን በኃጢአታችን ሰበብነት ሲርቃት ነው። "It falls on us as a result of our own personal sin we commit in our life; and it is characterize by eternal dam- nation of our soul in the purgatory and then, when rejoin with the body, in hell; this death is good to none for it happen to nothing good” —(Augustine, 1908: 3-4). በእነዚህ ዕይታዎች መሠረትነት በሕያውነት (ትንሳዔ) ለሚያምኑ ሞት ዳግም ዕድል የላትም፤ አንድ ናት፤ ነፍስም አንዴ ዘላለማዊ ሆና ተፈጥራለች እንጂ ድጋሚ የምትፈጠርበት ዳግም ዕድል የላትም። @Zephilosophy @Zephilosophy
Hammasini ko'rsatish...
የሞት ፍልስፍና (Philosophy of Death) ምንጭ ፦የፍልስፍና መግቢያ ደራሲ ፦ ደሳለኝ ስዩም የምንኖርበት ዓለም ያልተሟላ፣ የርኩሳን ፈተና ያለበትና ስቃይን ያዘለ ከመሆኑም በላይ መጨረሻው በሞት የሚደመደም ነው። “ሞት ማንም እርግጠኛ ሊሆንበት የሚችለው ብቸኛ እውነት ነው” —(Frankl V. 1984:96) እዚህ ጋ ነው ጥያቄው “የእኛ ሕይወት ማለት ያልተሟላን ኑሮ መኖር ነውን?፤ ሞትስ ልናመልጠው የማንችለው የሁላንችንም ዕጣ ፈንታ ነውን?” ሰው የትም ይኑር፤ ቢያንስ ያለፉትን ዘመናት ሕይወቱን አይተንበታልና በየትኛውም ባሕል ይቀረጽ ለእዚህ ጥያቄ “እርግጡን ይመልሳል” ብሎ ማሰብ አይቻልም። ከጥንታዊያን ግሪኮች ሄዴዝ (Hades) እሰከ ዘመናዊው የክርስትና ገነትና ሲኦል ምልከታ ድረስ “ሕይወት በምድራዊ ኑረት ታበቃለች” ብለው የማያስቡት ብዙ ናቸው። ይሁንና “ከእዚህ ሕይወት በኋላ ሌላ ሕይወት አለ፤ ሞትም የመጨረሻ አይደለም በሚለው ምልከታ ውስጥ ደግሞ ልዩ ልዩ ዓይነት የቀጣይ ሕይወት ብያኔዎች ይገኛሉ። ከእነዚህ ብያኔዎች አንደኛው መንገድ “ከዚህ ሕይወት በኋላ ዳግም መፈጠር (Re-incarnation) ይቀጥላል።” የሚል ሲሆን ሌላኛው ደግሞ ሕያውነት (Re-surrection) ነው። የመጀመሪያው ምልከታ “ሰው ሆኖ የሞተ ሌላ ተክል ወይም እንስሳ ሆኖ ይመጣል።” የሚል ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በእግዚአብሄር ዓለም ዘንድ ዘላለማዊ ሕይወትን የሚቀጥለው የሰው ልጅ ነፍስ የእዚህኛው ዓለም ሞቱ ወደ ቀጣዩ ዓለም ሕይወት የሚሸጋገርበት ነው። ጥቂት ጥቂት እንዘርዝር! ዳግም ውልደት (Reincarnation) ከጥንታዊያን የሂንዱ (ህንድ) ሥነ-ጽሑፍ ጀምሮ ሲተረክ የመጣ ነው። ነፍስ ከአንድ ፍጡር ስትወጣ ሌላ ስጋን ይዛ የምትፈጠርበት ሌላ አጋጣሚ እንጂ የእዚያች ነፍስ መጨረሻዋ “ያ” ሞት አይደለም። ከሂንዱይዝም ወደ ቡድሂዝም የተሻገረው ይህ እምነት ወደ ምዕራባዊያን ባሕልነት ከዚያም ወደ ፓይታጎረሳዊያን ከዚያም ወደ ፕላቶንያን አስተምህሮዎች ሲሸጋገር ኖሯል። የፍልስፍናው መሠረታዊ እሳቤዎች ሁለት ቁልፍ ጉዳዮች ላይ የሚያጠነጥኑ ናቸው፤ አንደኛው የዳግም ውልደት ዑደት ሲሆን ሁለተኛው የነፍስ ኢ-መዋቲነት ነው። በቡድሂዝም የዳግም ውልደት ዑደት “ሳሚሳር” ተብሎ ይታወቃል፤ ትርጓሜውም “መደነቂያ” ማለት ነው። ምንጩንና መሠረቱን ለማወቅ የሚያዳግት፣ ትርጉም አልባ፣ መጀመሪያው የማይታወቅ ረጅም ዑደት ነው ይሉታል። ቡድሃ ሲገልጸው እንዲህ ነው —“ሞት ወይም ዳግም ውልደት ተመሳሳይ ሥሜትንና ሁነትን የሚገልጹ መገለጫዎች ናቸው”። የሰውን ልጅ ስቃይ፣ አለመርካት፣ እንግልት፣ ስጋት (ድሁካ ይሉታል በራሳቸው ቃል) እነዚህን የሚገልጽ ሲሆን እኚህም የሰው ልጅ ቋሚ ባልሆነ ሁነት ውስጥ በመኖሩ ምክንያት በየጊዜው ከሚገጥሙት ለውጦች የሚከሰቱ ናቸው (Harvey, 1990:32,47,48) የዳግም ውልደት ነገር ለእንስሳትና ሕይወት ላላቸው ነገሮች በሙሉ እንጂ፤ ለሰው ልጅ ብቻ የሚሠራ አይደለም። በቡድሃ የዳግም ውልደት ነገር በሁሉም ሕይወት ያላቸው ፍጥረታት ላይ ያለ ነው። “ፔታ” ብለው ከሚጠሩት የሲኦል አምሳል ተነሥቶ ሃያ ስድስት ደረጃዎች እስካሉት የገነት አምሳል የሚደርስ ክፍፍል አለ። የገነት አምሳል ክፍፍሉም ከሕይወት ርዝማኔ፣ የሕይወት ጣዕም፣ እንዲሁም ነጻነት ጋር የተያየዙ ልዩነቶችን የያዘ ነው። የሰው ልጅ የዳግም ውልደት ሕይወት ጥራት የሚወሰነውም በሰውየው ቀዳሚ የሕይወት ታሪክ ነው። የሰው ልጅ ያማረ ዕድልን በዳግም ውልደት ጊዜ እንዲጎናፀፍ በመንፈሳዊነት የጎለበተ፣ በቅን አመለካከቱ የሰለጠነ፣ ለሰውና ለመላው ፍጥረት ሁሉ መልካምን የሚከውን መሆን አለበት፤ ሳር ሆኖ ተወልዶ ከብት እንዳይግጠው፤ አህያ ሆኖ ተፈጥሮ ለጭነት እንዳይውል ሊታደገው የሚችለው ሁሉ የቀዳሚ ሕይወቱ ትሩፋትና ተዘክሮ ብቻ ነው። (ዝኒከመአሁ፡ 38) በኋላ የመጡት የዓለማችን ፈላስፎችም እንዲህ ያለውን እምነት ሲያንጸባርቁ ታይተዋል። ከፓይታጎረስ ተነሥቶ እስከ ፕሌቶ የሄደው ይህ ዓይነቱ ፍልስፍና በተደራጀውና ቅርጽ ባለው ፍልስፍና ውስጥ ዳግም ውልደት ቅርጽ የያዘ ትንታኔ እንዲሆን አስችሎታል። “ፊዲዮ” በሚለው ሥራው ውስጥ ፕሌቶ ነፍስ ኢ-መዋዕቲ መሆኗን ይሞግታል። የፕሌቶ የዲበ-አካል ፍልስፍናውና የሥነ-ዕውቀት ንድፈ- ሐሳቡ የሚነመጨው ከእዚህ የነፍስ ኢ-መዋዕቲነት ላይ ተነሥቶ ነው ። ለፕሌቶ ሞት ማለት የነፍስና ሥጋ መለያየት ነው፤ መለያየቱ እርግጥ ሲሆን ነፍስ ከሥጋ ተላቃ በራሷ ሕያው ትሆናለች፤ ከሥጋ ተጽዕኖ ነጻ የሆነችው ነፍስም በራሷ ትቆማለች። (Benjamin, 1952:223). ፕሌቶ በእዚህ ድርሳኑ አብዝቶ እንደሚሞግተው እያንዳንዱ ነገር ሁለት አጣማጆች አሉት። እነዚህም አንደኛው ብልሽት (መጥፎ) እና ነገሩ የሚሠራበት አላባ (መልካምነት) ናቸው። አንድ ነገር ተበላሽቶ ቢገኝ ወይም ቢከስም የብልሽቱ ወይም የክስመቱ ምክንያት ከነገሩ ጋር አብሮ በነበረው የብልሽት አላባ (አጣማጅ) የተነሣ ነው። በብልሽት ማለትም ግድ የለሽነት፣ ጨካኝነት፣ ጋጠወጥነት በመሳሰሉት የምትበላሽ ናት። ይህ ብልሽት ነፍስን የማትረጋና እርካታ የለሽ ያደርጋታል እንጂ ጨርሶ የሚያጠፋት ነገር አይደለም፤ ስለዚህም ነፍስ ኢ-መዋዕቲ ናት። —(ዝኒከመአሁ፡ 436) ፕሌቶ ነገሮች በአጣማጅ ወይም በተቃርኖ የቆሙ ናቸው ብሎ ያምናል። ለሞቃቱ ቀዝቃዛ ተቃራኒው ነው፤ ግን የቀዘቀዘው እንደሚሞቀው የሞቀውም ይቀዘቅዛል። ሞትም የሕይወት ተቃራኒ ነው፤ ሞት የሕይወት አዲስ ምዕራፍ ሕይወትም የሞት አዲስ ምዕራፍ ነው። ስለሆነም እንደገና መወለድ የሞት ተቃራኒ ነው። የነፍስን ኢ-መዋዕቲነት ከሚሞግቱት አንዱ ሶቅራጥስ የሆሜርን አባባል ተውሶ እንዲህ ይላል፤ “ከዝንጋኤ ወንዝ ጠጥተው (ያለፈውን ረስተው፣ በበፊቱ ሥጋቸው ውስጥ የነበራቸውን ልምድ ሁሉ ረስተው)፣ ነፍሶች እንደገና ይመጣሉ” (ዝኒከመአሁ፡ 436) ✍ ይቀጥላል✍ @Zephilosophy @Zephilosophy
Hammasini ko'rsatish...
ፍቅር_የሞተበት-ግሩም_ዘነበ.mp314.68 MB
የኢሰመኮ ሪፖርት በኢትዮጵያ በተለያዩ አካባቢዎች በግጭት ዐውድ ውስጥና ውጭ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች አሳሳቢነትና ሥጋቶችን በተመለከተ የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ሪፖርት አውጥቷል። በሪፖርቱ ፦ - ከሕግ ውጭ ግድያ (በድሮን ጨምሮ) ፣ የሲቪል ሰዎች ሞት፣ የአካል ጉዳት፣ የንብረት ውድመትና ዘረፋ፤ - የዘፈቀደ፣ ሕገወጥ፣ የጅምላና የተራዘመ እስራትና የተፋጠነ ፍትሕ እጦት፤ - እገታ - አስገድዶ መሰወር እና ያሉበት ቦታ ሳይታወቅ አስሮ ማቆየት - የሀገር ውስጥ መፈናቀል ... ተዳሰዋል። ° በጸጥታ መደፍረስ፣ ° ከመንግሥት አካላት ተገቢውን ምላሽና ትብብር በወቅቱ ባለማግኘት ° በሌሎች ምክንያቶች ምርመራቸውና ክትትላቸው የዘገዩና የተጓተቱ በርካታ ጉዳዮችን መኖራቸው ተገልጿል። እነዚህን ጉዳዮች በመርመርና ክትትል በማድረግ በተገቢው ጊዜ ይፋ የሚያደርግ ይሆናል ተብሏል። ኢሰመኮ በግጭት ዐውድ ውስጥ እና ከዐውድ ውጭ የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶችንና ሥጋቶችን በአስቸኳይ ማቆም ይገባል ብሏል። @tikvahethiopia እስከመቼ ይሁን እንደዚህ እየተባላን የምንቀጥለው???
Hammasini ko'rsatish...
ፍቅር እና ፊዚክስ-3 .......✍ ካለፈው የቀጠለ በፍቅር፣ ሰው አእምሮ ውስጥ ግዛት መመስረት ወንጀል አይደለም፤ ምክንያቱም ዩኒቨርስ የሚገዛበት ሕግ የተለያየ ነውና፡፡ በፍቅር - በሰውና በእግዚአብሔር ላይ ባለመብት ትሆናላችሁ፡፡ በፍቅር ፣መንገድ ላይ አምስት ሳንቲም የሚለምናችሁ ድሃ ፣እናንተ ላይ ባለ መብት ይሆናል፡፡ ባለመብት ከሆናችሁ ደግሞ አዛዥ ትሆናላችሁ ፤ፍቅረኛችሁን ፣ጓደኞቻችሁን፣ ወላጆቻችሁንና ፈጣሪያችሁን ታዙታላችሁ። እነሱም ቢሆኑ ስለ እናንት ፍቅር የእናንተ አገልጋዮችና ተሸናፊዎች ይሆናሉ፡፡ ዳሩ ግን ፍቅር መልሶ እናንተንም የእነሱ አገልጋዮችና ተሽናፊዎትች ያደርጋችኋል፡፡ የምናፈቅረው አሸናፊና ገዢ ለመሆን ሳይሆን ተሸናፊና አገልጋይ ለመሆን ነው፡፡ በመሆኑም በፍቅር ምን አይነት ዓለም ለመፍጠር አቅሙ እንዳላን አስቡት፤ በፍቅር ዓለም ሁሉ ውብ ሆና አትታያችሁም!? መተዛዘን ሰፍኖ፣ ድህነት ተነቅሎ፣ ሀብት ተከፋፍሎ፣ ቴክኖሎጂ እስከ ጥግ ተዳርሶ፣ እኩልነትና ፍትሃዊነት በዓለም ላይ ሰፍኖ ምድር ልምላሜን ፈጥራ የፍቅር ቡራኬ ሲነግስባት አይታያችሁም!? "በምድር ላይ ..." አለ አንስታይን በአንድ ወቅት ስለ እድገት ተጠይቆ፣ “ "በምድር ላይ አንድ የተራበ ህፃን እስካለ ድረስ እድገት አለ ማለት አይቻልም።" ብርሃን በዚያ የፍጥነት የመጨረሻ ሃይሉን ተጠቅሞ እንኳን ብዙ የብርሃን ዓመታትን ወስዶ ማቋረጥ የማይችለውን ዩኒቨርስ እናንተ በፍቅር ከመቅፅበት ከዩኒቨርስ ባሻገር ወደሚገኘው ፈጣሪያችሁ ትደርሳላችሁ፡፡ ፍቅር እንዴት አይነት አስገራሚ መጓጓዣ ነው! ክንፍ የሌላችሁን ክንፍ ሰጣችሁ፣ በመሬት የተወሰናችሁትን ከዩኒቨርስ ባሻገር አገነናችሁ፣ ቁሳዊነታችሁን ሽሮ መንፈሳዊ አደረጋችሁ፤ አውሬነታችሁን አጥፍቶ ደግና ሩህሩህ አደረጋችሁ፡፡ በፍቅር ጊዜን አሳጠራችሁት፤ እድሜያችሁንም አስረዘማችሁት፡፡ አንስታይን ጊዜ የሚያጥረው፣ እድሜም የሚረዝመው ፍጥነት ሲጨምር ነው ቢልም እናንተ ግን በፍቅር የተለየ ሕግጋትን ተጎናፀፋችሁ፤ "አንድ ሺውን አመት እንደ አንድ አመት" አደረጋችሁት። በርግጥ አንስታይንም ቢሆን ጊዜን የሚያሳጥረው ፍጥነት ብቻ ሳይሆን ፍቅርም እንደሆነ በአንድ ወቅት "አንፃራዊነትን" ለሠራተኛው ሲያስረዳት እንዲህ ብሎ ነበር፣ "እጅሽን የጋለ ብረት ምጣድ ላይ ለ5 ሰከንድ ብታስቀምጪው 5 ሰዓታት ያህል የቆየሽ ይመስልሻል፤  ከፍቅረኛሽ ጋር 5 ሰዓታት ብትቆይ ግን 5 ደቂቃ እንኳን የቆየሽ አይመስልሽም፤" በፍቅር የጊዜን ህልውና ትገዘግዙታላችሁ፣ ህልውናንም ትፈታተኑታላችሁ፡፡ ለነገሩ ጊዜ ምን ህልውና አለው? ከአእምሮአችሁ ውጪ ጊዜ ህልውና የለውም፤ እናንተ መኖር ስታቆሙ ጊዜም አብሮ ይሞታል፡፡ ለመሆኑ ፍቅር፣ ዩኒቨርሰ እየተንቀጠቀጠ የሚገዛለትን የተፈጥሮ ሕግ የሚሽርበት ስልጣንና ሃይል ከየት አገኘ? ፍቅር ይሄንን ባህሪውን ፣ሃይሉንና ረቂቅነቱን ከየት አመጣው? ፕሌቶን ጠይቁት፤ ዓለምን ለሁለት ክፍሎ፣ የ"መሆን" እና የ"መምሰል" ዓለም፣ በቦታ - ጊዜ አውታር የተወሰነና ያልተወሰነ ዓለም፣ "የፍፁማዊና የጉድለት ዓለም" በማለት ለሁለት ከፍሎ ያስረዳችኋል፡፡ የ "መሆን ዓለም (The World of Being)..." ይላል ፕሌቶ፣ "የመሆን ዓለም በቦታ - ጊዜ አውታር የማይወሰንና በዓለም ላይ ያሉ ነገሮች ሁሉ በፍፁማዊነት ደረጃ የሚገኙበት ዓለም ነው፤ ፍቅርንም ጨምሮ።" በመሆኑም ፍቅር ፍፁማዊነት ደረጃን ተላብሶ ከቦታ - ጊዜ አውታር ውጭ ባለው ዓለም ውስጥ በነባራዊነት ይኖራል፡፡ ፍፁማዊ ፍቅር ስጋችን ሊሸከመው አይችልም ያልነው ለዚህ ነው፡፡ "እኔነት" የተጫነበት ስጋችን ፍፁማዊ ፍቅርን ለመሸከም አቅም የለውም፡፡ ፍፁማዊ ፍቅርን ለመሸከም የተለየ አካል ያስፈልገናል፤ ለቦታ-ጊዜ አውታር ሕግ የማይገዛ የተለየ አካልና ባህሪ፡፡ አለበለዚያ ፍፁማዊ ፍቅር አስለቅሶ ያሳልቀናል፡፡ ፍፁማዊ ፍቅር የደግነትና የርህራሔ ሰለባዎች ያደርገናል፡፡ እናም አቅማችን ታይቶ ከፍፁማዊ ፍቅር ተጨልፎ ተሰጠን፤ ጭላፊዋም ብትሆን ግን ምጡቅና ሃያል፤ ከሕግም በላይ አደረገችን፡፡ "ሰውም ቢሆን የፍፁማዊው ዓለም ፍንጣቂ ነው ፤" ይላል ፕሌቶ፡፡ ጠፈር ከአንድ ማእከላዊ ቁስ እንደተበተነው ሁሉ፣ እኛ ሰዎችም ከአንድ ማእከላዊ (ፍፁም) ፍቅር የተዘረጋን ሳንሆን አንቀርም፡፡ ታዲያ ከፍፁማዊ ፍቅር ተጨልፎ የተጫነበትን ሰው እንዲህ በቀላሉ እንዳትመለከቱት።  በአጭር ቁመት፣ በጠባብ ደረት መወሰኑን አትዩ፡፡ ፍቅር እንደ ሞገድ ሲያከንፈው፣ ስፍራና ጊዜን ደምስሶ ከሕግ በላይ ሲሆን እያያችሁ፤ ሰውን በአጥንት የቆመ፣ በስጋ የለሰለሰ፣ በደም የተሞላ፣ ለከርሱና ለፍትወቱ የሚጋደል ተራ ምድራዊ ፍጡር አድርጋችሁ እንዳትመለከቱት፡፡ የስሜት ሕዋሶቻችሁን የመጨረሻው እውነት አድርጋችሁ እንዳታምኗቸው፡፡ የስሜት ህዋሳቶቻችን ብዙ ነገር ደብቀውናል፤ ከብዙ ነገርም ወስነውናል፡፡ "የሰው ልጆች. . ." አለ ስለ አንስታይን ሥራዎች የፃፈው Lincoln Barnett. "የሰው ልጆች በሌላ በማንም ሳይሆን በራሳቸው የስሜት ህዋሳት ታስረዋል፤ ሌላው ይቅርና አይናችን የx-ray ን ጨረር ማየት ቢችል እንኳ ኖሮ የሰው ልጅ አጠቃላይ ሕይወት አሁን ከምናውቀው ዘይቤ ፈጽሞ የተለየ ይሆን ነበር፡፡" እናም "ሰው" በስሜት ሕዋሳታችን የተገለጠውን አይነት አይደለም፤ ከዛ በፍፁም የተለየ ነው፡፡ "ሰው..." ይላል ፕሌቶ፣ "ሰው በሕዋሳት አማካኝነት የምናየውን በቁመት፣ በመልክና በሁኔታ የተለያዩ ግለሰቦችን ብቻ ማለታችን አይደለም፡፡ ሰው አማራ - ትግሬ፣ ክርስቲያን - ሙስሊም፣ ጥቁር - ነጭ፣ ረጅም - አጭር፣ ቀጭን - ወፍራም፣ ወንድ- ሴት አይደለም፡፡ ሰው እከሌ ሳይሆን ሁለንተናዊ የሆነ፣ ሊዳስስ የማይችል፣ ግለሰቦች ከሚያሳዩት ተላዋዋጭና ግላዊ ጠባይ የተላቀቀ፣ የሰውን ዘለዓለማዊ ህልውና በሚገልጽ መለኮታዊ (ፍፁማዊ) አለም ውስጥ የሚመደብ ነባራዊ እውነት ነው፡፡" ነባራዊ እውነት ደግሞ ምንድ ነው? ነፍስ፣ ህያው ህልውና፡፤ ምንጭ ፦ ፍልስፍና ፩ ፀሀፊ ፦ ብሩህ አለምነህ @Zephilosophy @Zephilosophy
Hammasini ko'rsatish...