fa
Feedback
ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

رفتن به کانال در Telegram

✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል! የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ። ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ @firaolbm እና @tekletsadikK ተጠቀሙ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

کانال ከስነ-ፅሁፍ ዓለም (@ethiobooks) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 10 255 مشترک است و جایگاه 3 732 را در دسته کتب و رتبه 3 261 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 10 255 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 10 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -13 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -5 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 10.95% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 3.24% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 1 123 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 332 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 6 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል! የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ። ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ @firaolbm እና @tekletsadikK ተጠቀሙ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 11 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته کتب تبدیل کرده‌اند.

10 255
مشترکین
-524 ساعت
-67 روز
-1330 روز
آرشیو پست ها
ግ ፍ 😩😩 😩 ግፍ ባገር ሲሞላ፣ እርስ በርስ ያባላ። 😩 ግፍ አይፈሬ መሬት እንክርዳድ ያበቅላል። 😩 የግፍ ግፍ፣ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ። 😩 ግፍ የተሠራ በኛ፣ ካሱ ይሉናል በዳኛ። 😩
ግ ፍ 😩😩 😩 ግፍ ባገር ሲሞላ፣ እርስ በርስ ያባላ። 😩 ግፍ አይፈሬ መሬት እንክርዳድ ያበቅላል። 😩 የግፍ ግፍ፣ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ። 😩 ግፍ የተሠራ በኛ፣ ካሱ ይሉናል በዳኛ። 😩 ግፍ ሲቆም፣ ጸሎት አያሻም። 😩 ግፍስ በባህር ይሞላል፣ ዓሣ ዓሣውን ይበላል። 😩 ግፈኛ፣ የሰይጣን መላክተኛ። 😩 ግፍ ባገር ሲናኝ፣ ኩበት ጠልቆ ድንጋይ ይዋኝ። 😩 ሁለተኛ ግፌ፣ ጀርባዬን ተገርፌ፣ ልብሴን መገፈፌ። 😩 😩 ነገር በምሳሌ @ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

«ገፊ» መጻሕፍት ━━✦━━ ፕሌቶ «ፋኢዶ» (PHAEDO) በሚል ርዕስ የጻፈው አንድ ጽሑፍ አለ። ይህም ጽሑፍ ሶቅራጠስ ከባልንጀሮቹ ጋር በሕይወቱ ፍጻሜ የመጨረሻ ሰዓት ላይ ያደረገውን ምልልስና ውይይት የሚተርክ ነው። ታዲያ ፈላስፋው ክሊአምብሮተስ ይህንኑ የፕሌቶን ፋኢዶ የተሰኘውን መጽሐፍ አንብቦ ከጨረሰ በኋላ ራሱን ገድሏል። እንዲሁም የሮማው የስቶይክ ፈላስፋ ካቶ፥ በነጋታው ሊሞት ሌሊቱን ይህንኑ ፋኢዶ የተባለ መጽሐፍ ሲያነብ ማደሩ ታውቋል። በ18ኛው ክፍለ ዘመን ላይም የእንግሊዙ ባለቅኔ ኢውስተስ ቡድጌል በተዘዋዋሪ መንገድ ይኸው ፋኢዶ የተሰኘ ጽሑፍ ባሳደረበት ተጽዕኖ ሕይወቱ ማለፉ ተጠቅሷል። ባለቅኔው ቡድጌል ራሱን ውሃ ውስጥ ጨምሮ ከመግደሉ በፊት ጽፎ ያስቀራት ማስታወሻው «ካቶ ያደረገውና አዲሰን ያረጋገጠው ነገር ስህተት ሊሆን አይችልም» የምትል ነበረች። ጀርመናዊው የግጥም፣ የተውኔትና የረዥም ልቦለድ ደራሲ ጆን ዎልፍ ጎቴ (1749 - 1832) «The Sorrows of young Werther» በሚል ርዕስ በ1774 ላይ የጻፈው የፍቅር ልቦለድ ውስጥ ዋናው ገጸባህርይ ራሱን ይገድላል። ታዲያ የዚሁ መጽሐፍ ተጽዕኖ ለአያሌ ሰዎች ራሳቸውን ማጥፋት ምክንያት መሆን ቢችልም፥ በተለይ ፍራውሌይን ቮን ላስሊንግ የተባለች ወጣት ሴት ግን መጽሐፉን አንብባ እንደጨረሰች ወዲያውኑ ሕይወቷን ማጥፋቷ ታውቋል። በዓለም ላይ ሰዎችን ለሞት በመዳረግ (በመገፋፋት) ከፍልስፍናና ከልቦለድ መጻሐፍት ይህን ያህል ኃያል የሆኑ እንደመገኘታቸው ከመዝሙርም በዚህ ጉዳይ የሚጠቀስለት አለ። የመዝሙሩ ርዕስ «ጥቁር እሁድ» (ብላክ ሰንዴይ) ይባላል። ይህ መዝሙር በ1930ዎቹ ላይ የብዙ ሰዎችን ስሜት በመንካት ራሳቸውን እንዲያጠፉ ምክንያት ከመሆኑም በላይ፥ ራሱ የመዝሙሩ ደራሲ እንኳ ከዓመታት በኋላ በአንድ ዕለተ-ሰንበት (እሁድ ዕለት) መዝሙሩን ሲያዳምጥ ቆይቶ ወዲያውኑ ራሱን ገድሏል። ጀምስ ኤ. ሀርድን - ሂኬይ የተባለ የብዕር ሰው በ1894 ላይ «Euthanasis of Suicide» በሚል ርዕስ ያወጣው መጽሐፍም በርካታ ሰዎች ሕይወታቸውን በራሳቸው እጅ እንዲያጠፉ ተጽዕኖ አሳድሯል። መጽሐፉ የራስን ሕይወት ለማጥፋት የሚያስችሉ 90 የመርዝ፣ 50 የመሣሪያ ዓይነቶችን የሚጠቁምና የሚያብራራ ከመሆኑም በላይ፣ ሌሎች አያሌ የግል ሕይወት መቅጠፊያ ዘዴዎችንም በስዕል አስደግፎ ያስረዳል። (የመጽሐፍ "ወንጀለኛ" ይሏል ይህ ነው።) ታዲያ ይህንኑ ጉደኛና ሰው ሊያጠፋ ቆርጦ የተነሳ መጽሐፍ የጻፈው ሀርድን - ሂኬይ፥ በ1898 ላይ በ44 ዓመት ዕድሜው፣ የሞርፊን መድኃኒት ከልክ በላይ ወስዶ ራሱን መግደሉን ስትሰሙ ወትሮስ ጤነኛ ነው ትላላችሁ? ━━━━━━━━━━━ 📔 ጣዝማ - አስደናቂው የደራሲያን ሕይወት ✍ ንጉሤ አየለ እና ደጀኔ ጥላሁን 📄 166 - 168 🗓 2007 ዓ.ም. 📖 📖 📖 📖 📖 https://t.me/Ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

💿 ማ ለ ፊ ያ 💿 ══❁══ 🎤 ብስራት ሱራፌል 🎧 @ethiobooks 🎼🎵🎶🎵🎶🎵 ያልፋል ይህ ሃሳብ ያልፋል ይህ ደመና ከፋም ያሉት ቀን ከፍ ያደርጋል ገና ያልፋል ይህ ንፋስ ያልፋል ይህ ደመና መልካም ይሆናል መልካም ነበርና 🎵🎵 ያልቃል ሲሉት እየሰፋ ቀን ሲመስል የማይገፋ መንገድ አለ መውጫ ቦታ ቀን ይመጣል በቀን ፋንታ ይለካዋል ወርቅ ብርታቱን ማለፊያ ነው ብሎ እሳቱን ተስፋ ከእምነት ከተሠራ ያሻግራል ከመከራ 🎵 ማለፊያ ሲል ነው ማለፊያ ሰው የማይድን ከሃሳብ ጥድፊያ ማለፊያ ሲል ነው ማለፊያ ሰው የማይድን ከሃሳብ ካፊያ [ያልፋል እንደ ጉም ያልፋል እንደ ጉም ያልፋል እንደ ጉም ያልፋል እንደ ጉም ችግር ፈተናው ያልፋል እንደ ጉም ቢልም ጉም ጉም ያልፋል እንደ ጉም] 2× 🎵🎶🎵🎶🎵 ያልፋል ይህ ሃሳብ ያልፋል ይህ ደመና ከፋም ያሉት ቀን ከፍ ያደርጋል ገና ያልፋል ይህ ንፋስ ያልፋል ይህ ደመና መልካም ይሆናል መልካም ነበርና 🎵🎵 ያጡትን ለማግኘት በተስፋ መውደቅ መቆም ምን ቢያለፋ ተስፋ ካለ ብርሃንማ ይወለዳል ከጨለማ አትሸበር በወጀቡ ተራራ ነው ጎበዝ ል ቡ እ.ል.ፍ. ባለ ቁጥር እልፍ ያተርፋል ሰው በፍቅር 🎵 ማለፊያ ሲል ነው ማለፊያ ሰው የማይድን ከሃሳብ ጥድፊያ ማለፊያ ሲል ነው ማለፊያ ሰው የማይድን ከሃሳብ ካፊያ [ያልፋል እንደ ጉም ያልፋል እንደ ጉም ያልፋል እንደ ጉም ያልፋል እንደ ጉም ችግር ፈተናው ያልፋል እንደ ጉም ቢልም ጉም ጉም ያልፋል እንደ ጉም] 2× || 🎶🎵🎶 @ethiobooks

photo content

sticker.webp0.33 KB

ናዚዎችን ያታለለው ሬሳ - 2 የመጨረሻው!

ናዚዎችን ያታለለው ሬሳ - 1

▶ ኦፕሬሽን ሚንስሚት (Operation Mincemeat) ━━━━━━━━━━ «ናዚዎችን ያታለለው ሬሳ» @ethiobooks
+1
▶          ኦፕሬሽን ሚንስሚት         (Operation Mincemeat)           ━━━━━━━━━━            «ናዚዎችን ያታለለው ሬሳ»                  @ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

📔 አልንበረከክም ነገ ጅል አይደለም በፍርሃት ጣት የተለቀለቀ፣ ዛሬ ላይ ተውቦ በትላንት ትዝታ ሀብል ያጠለቀ። ራስ ሳያርፍበት ባዶ አንገት ነው ባዶ፣ ቃርሚያ 'ሚያግበሰብስ ትላንትና ሄዶ፤ እውነት፣ እምነት፣ ጽናት፣ የማለዳ ጮራ፣ አርነት ወጪ ናት ነፍስ ማተብ አስራ። ════════ ✍ ዋሲሁን በላይ (አዋበ) 🗓 ሰኔ ፪ ሺህ ፲፯ ዓ.ም. 📖 📖 📖 📖 📖 https://t.me/Ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

ባ ዶ ━•━ (የአጭር አጭር ልቦለድ) ✍ ካሳሁን ተሾመ ' ደራሲው ተስፈንጥሮ ከእንቅልፉ የተነሳው ድሮ ይዳብር ብሎ ውስጡ የቀበረው ልብ ወለድ ሊያስመልሰው ሲተናነቀው ነው። ሰዓቱን ተመለከተ። ሌት 7፡01። ወረቀት ላይ ብዕር ደቅኖ ማማጥ ጀመረ። አርቆ አሠበ። በምናቡ በረረ። ተመላለሰ። ባዶው ወረቀት ላይ በፊት ካወጣለት «ኑሮ» ከምትል ርዕስ በቀር ያሠፈረበት ነገር የለም። ብዕሩ ሙሉ፤ ውስጡም ምሉዕ። ወረቀቱ ባዶ። ጠብ የምትል ነገር አጣ። ፨ ፨ ፨ "ኡ ... ፍ!!" ተነፈሰ። ምንም እንኳ አንዲት ቃል ብትሆንም ከርዕሱ ሥር አሰፈራት።ሰዓቱን ሲያይ 11፡45 ይላል። ውስጡ ሰላምን ተጎናፅፏል። "መልካም እንቅልፍ" የምትል የትራሱን ጥልፍ ተንተርሶ ጥቅልል ብሎ ተኛ። «ኑሮ» ለምትል ርዕስ «ኤጭ» የሚል ልብ-ወለድ ጽፎ። ━━━━━━━ 📔 የሐረግ ጸሎት 📖 📖 📖 📖 📖 https://t.me/Ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

የራስ ተፈሪ የፈረስ ስምና     የቀለበቷ ምስጢር ━━━━✦━━━━ ✍ ካሕሳይ ገብረ እግዚአብሔር ' ራስ ብሩ፣ ልጅ ኢያሱና ልዑል አልጋ ወራሽ ተፈሪ ከዐፄ ምኒልክ ዘንድ ሥርዓተ ቤተ መንግሥት እየተማሩ ማደጋቸው ይነገራል። ራስ ብሩ የዐፄ ምኒልክ ልጅ እንደነበሩ በሰፊው ይነገር ነበር። ነገሩ እንዲህ ነው፦ ከዕለታት በአንዱ ቀን እቴጌ ቤተ መንግሥት ውስጥ ባልነበሩበት ሰዓት ምኒልክ አንዷን ደንገጡር ደረሱባትና ፀነሰች። ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ደንገጡራቸው ማርገዝዋን የተጠራጠሩት እቴጌ ነገሩን ሰው ሳያውቀው (ሳይሰማው) ደንገጡራቸውን ለደጃች ወልደ ገብርኤል ዳሩላቸው። በዚሁ የተነሣ ራስ ብሩ የደጃዝማች ወልደ ገብርኤል ልጅ ናቸው ተባሉ። ይሁን እንጂ ዐፄ ምኒልክ ያደረጉትን ያውቁ ነበርና እርሳቸው ዘንድ በማስመጣት በሚገባ አሳደጓቸው። አንድ ቀን ምኒልክና እቴጌ ጣይቱ ከራስ ብሩ፣ ልጅ ኢያሱና ራስ ተፈሪ ጋራ አንድ ላይ ሆነው በማውጋት (በመጫወት)  ላይ እያሉ ዐፄ ምኒልክ ወደ እቴጌ ጣይቱ ዘወር ብለው «እቴጌ እስቲ ለሦስቱም የፈረስ ስም አውጪላቸው» አሉዋቸው። እቴጌም፦ «ጃንሆይ ከፈቀዱ እሺ» ብለው ለራስ ብሩ «አባ ሥራው»፣ ለልጅ ኢያሱ «አባ ጤና» ካሉ በኋላ ራስ ተፈሪ ላይ ሲደርሱ «አባ ጠቅል» ከማለታቸው ዐፄ ምኒልክ እንደ መደንገጥ ብለው «ውይ! ጠቅል አልሽው? በሕልሜም ከኔ ኋላ ተፈናጦ አልወርድም ሲለኝ አይቻለሁ» አሉ ይባላል። ንጉሡ ይህንን ምስጢር  በልባቸው ይዘው የእቴጌን ትንቢታዊ የፈረስ ስም ጉዳይ በሌላ መልክ ለማረጋገጥ ፈለጉ። በመሆኑም በወቅቱ በነበረው ባህል መሠረት መጪውን መተንበይ ይችላሉ ወደሚባሉ አንድ ባሕታዊ «ለመሆኑ ከኔ በኋላ የሚነግሠው ተፈሪ ነው ወይንስ ኢያሱ?» በማለት መልእክት ላኩ። መልእክቱ የደረሳቸው ባሕታዊም በቀጥታ «እገሌ ነው» ከማለት ይልቅ «ለሁለቱም ምግብ ሲሰጡዋቸው ከፍትፍት ውስጥ ቀለበትዎን አስገብተው (ጨምረው) ያቅርቡላቸው፤ ቀለበትዎን ያገኘ ይነግሣል» በማለት መልስ ላኩላቸው። ራስ ተፈሪና ልጅ ኢያሱ ምንጊዜም የሚመገቡት ንጉሡ ከበሉ በኋላ የንጉሡ ማዕድ ከፍ ካለ በኋላ ነበርና ዐፄ ምኒልክ ባሕታዊው በነገሩዋቸው መሠረት የጣት ቀለበታቸውን ከፍትፍት ውስጥ አስገብተው ሰጡዋቸው። ሁለቱም ወጣት መሳፍንት እንደተለመደው አንድ ላይ በመመገብ ላይ እያሉ ቀለበቷ ራስ ተፈሪ እጅ ገባች። ተፈሪ ቀለበቷን ቀስ አድርጎ (ኢያሱ ሳያየው) ኪሱ ውስጥ አስቀምጦ ምንም እንዳልሆነ መመገቡን ቀጠለ። ማዕዱ ከፍ እንዳለ ንጉሡ ሁለቱንም እልፍኛቸው ድረስ በማስጠራት «ለመሆኑ ከሁለታችሁ ከምግቡ ውስጥ አንድ ነገር ያገኘ አለን?» በማለት ጠየቋቸው። በዚህን ጊዜ ልጅ ኢያሱ፦ «ጃንሆይ በበኩሌ ምንም አላገኘሁም» በማለት መለሰ። ራስ ተፈሪ ግን ረጋ ባለ መንፈስ ኪሱ ውስጥ ያስቀመጠውን ቀለበት አውጥቶ ለዐፄ ምኒልክ እያሳየ «ይህችን አግኝቻለሁ» አለ ይባላል። ━━━━━━━━ 📔 ኅብረ - ብዕር ሦስተኛ መጽሐፍ 🗓 2009 ዓ.ም. 📄 59 - 51 📖 📖 📖 📖 📖 https://t.me/Ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

እኔም መንግሥት ብሆን... ━━━━✦━━━━ ✍ አሌክስ አብርሃም ' [ለጨዋታው ድምቀት አንዲት ሴት ከመጨመሬ ውጭ እውነተኛ ታሪክ ነው] አንዳንዱ ሰው ዕድለ ቢስ ነው። ሚስት አይወጣለትም። በደርግ ጊዜ በወጣትነቱ ድህነት አንገሸገሸውና በሱዳን ተሰዶ ብዙ አገርና ብዙ ዓመት ተሻግሮ በኢህአዴግ ዘመን አሜሪካ ገባ። አፈር ግጦ ሠርቶ ድህነትን ተበቀላት፤ ምርጥ ቤት ገዛ፣ የራሱን ቢዝነስ ጀመረ። እንዲህ ሲል ዕድሜው ቢገፋም በቃ ማግባትና ቤተሰብ መስርቼ በደስታ መኖር ነው ከዚህ በኋላ ብሎ ወሰነ። አንዲት የ22 ዓመት ቀበጥ ቆንጆ ከአዲስ አበባ አግብቶ ወሰደ፣ ጉድ ተባለ ቁንጅናዋ፤ በሦስት ወሯ ትታው ሄደች። እንደውም ቆየች ተባለ። የክፍለ ሀገር ልጅ አግባ፣ የከተማ ሴቶች አይታመኑም አሉት፤ ከክፍለ ሀገር አግብቶ አመጣ፤ በወሩ ትታው ጠፋች። የደሃ ልጅ ነው ማግባት አሉት ያጣች የነጣች ልጅ አገባ፤ አገኘች፣ ወዛች ጥላው ሄደች። ተው ሃይማኖተኛ ነው ማግባት አሉት፤ አንዲት ፆም ጸሎት ያደከማት የምትመስል ላንጌሳ አገናኙት፤ እየተስለመለመች "በጸሎት እንደ አንተ ዓይነት ሰው ነበር የለመንኩት" አለችው አሉ። አግብቶ ወሰደ... ገና ከኤርፖርት ቤተሰቧቿ ጠልፈዋት ጠፋች። በኋላ ሲሰማ ሁለት ልጅ ሁሉ ነበራት። አሁን ልጆቿን አምጥታ በሰላም ትኖራለች። አንዳንዱ ሰው በፌክ ጸሎት ሁሉ ይሳካለታል። በመጨረሻ "ጋሽ ጎዳናው ወጣት አትምረጥ፣ ዘላ ያልጠገበች ሴት ለትዳር አትሆንም፣ በዕድሜ ስክን ያለች ፈልገህ አግባ ብለው መከሩት "ምነው ሸዋ" የምትል ደርባባ ሴትዮ አገባ... በዓመቱ "ንሽ እቴ" ብላ ትታው ሄደች። እንደውም ከአገር ቤት ጎረምሳ አገባች አሉ። አዘነ፤ ልቡ ተንኮታኮተ። ንብረቴን የሚወርስ ልጅ ሳላፈራ እያለ ሲተክዝ ጭራሽ በቀደም "ታሰረ'ኮ" አሉኝ። ምን አድርጎ ብል "የአሜሪካ መንግሥት በሕገ-ወጥ የሰዎች ዝውውር ጠርጥሮት" እኔም መንግሥት ብሆን የምጠረጥረው ነው!!! ━━━━━━━━━ 📖 📖 📖 📖 📖 https://t.me/Ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

ዱሳን ፖፖቭ - 2 የመጨረሻው!