es
Feedback
ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

Ir al canal en Telegram

✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል! የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ። ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ @firaolbm እና @tekletsadikK ተጠቀሙ።

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ከስነ-ፅሁፍ ዓለም

El canal ከስነ-ፅሁፍ ዓለም (@ethiobooks) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 10 286 suscriptores, ocupando la posición 3 695 en la categoría Libros y el puesto 3 204 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 10 286 suscriptores.

Según los últimos datos del 26 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 11, y en las últimas 24 horas de 1, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 10.63%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 3.01% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 1 093 visualizaciones. En el primer día suele acumular 310 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 6.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
✍ አዝናኝ፣ አስተማሪና ቁም ነገር የሚያስጨብጡ የብዕር ውጤቶች የሚቀርቡበት የናንተው ቻናል! የቻናላችን https://t.me/Ethiobooks ቤተሰብ ሁኑ፣ ለወዳጅ ጓደኞቻችሁም 'share' አድርጉ። ለአስተያየት፣ ስነ-ፅሁፋዊ ጥቆማና ማስታወቂያ @firaolbm እና @tekletsadikK ተጠቀሙ።

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 27 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Libros.

10 286
Suscriptores
+124 horas
-67 días
+1130 días
Archivo de publicaciones
ባ ዕ ድ / ባ ዳ 🫩 🫩 🫩 ባዕድ ከሳመው፣ ዘመድ የነከሰው። 🫩 ከባዕድ ጋር የበሉት በሶ፣ ይወጣል ደም ጎርሶ። 🫩 የባዳ ሞኝ 'ከዘመድህ እኩል አርገኝ' ይላል። 🫩 ባዕድና ጨለማ አንድ ነው
ባ ዕ ድ / ባ ዳ 🫩 🫩 🫩 ባዕድ ከሳመው፣ ዘመድ የነከሰው። 🫩 ከባዕድ ጋር የበሉት በሶ፣ ይወጣል ደም ጎርሶ። 🫩 የባዳ ሞኝ 'ከዘመድህ እኩል አርገኝ' ይላል። 🫩 ባዕድና ጨለማ አንድ ነው። 🫩 ከባዕድ ለስላሳ፣ የራስ ከርካሳ። 🫩 በባዳ ቢቆጡ፣ በጨለማ ቢያፈጡ። 🫩 የደግ ጊዜ ባዕድ፣ የክፉ ጊዜ ዘመድ። 🫩 ለሰዉ ባዳ፣ ለቋንቋው እንግዳ። 🫩 ጆሮ ለባለቤቱ ባዳ ነው። 🫩 ለባዕድ ስር የለው፣ ለሰማይ ምሰሶ የለው። 🫩 ጠላው የባዕድ፣ አሳላፊው ዘመድ። 🫩 ከባዕድ እየጎረስክ፣ ወደ ዘመድህ ዋጥ። 🫩 ወገኛ፣ በባዳ ምድር ልሁን ይላል ሠርገኛ። 🫩 ከባዕድ ወደ ዘመድ፣ ከጫካ ወደ መንገድ። 🫩 የባዕድ ፍቅር በአዲሱ፣ የዳጉሳ እንጀራ በትኩሱ። 🫩 🫩 ነገር በምሳሌ @ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

>>> «ማን ... ማን ልበል?» ተንቀጠቀጠ። «አይ የሰው ነገር? ምነው እንዲህ ልብህ ጨከነ የኔ ልጅ? ... ለጌትዬ? ... ለጓደኛህ? ለአብሮ አደግህ? ... ምነው አንተዬ? ቢሞትም ይሄው ነበር! እርሙን በልተህ በዚያው ትጠፋ ነበር! አበስኩ ገበርኩ! ...» እያለቀሱ ሳይሆን አይቀርም። «እማምዬ ... ኧረ እንደዚህ አይደለም! ኧረ አልገባዎትም! በፍፁም በዚህ መልክ ሊያስቡ አይገባም! የኔና የጌትዬን ፍቅር ያውቁ የለም?» የሚለውን አጣ። «እኔማ ብዬ ነበር! ጌትዬ አንድ ነገር ቢሆን የሚደርስለት እሱ ነው እል ነበር። አንተ ግን ሌላ ሆንክ... ተወው ልጄ ድሮም ባዳነት ይኸው ነው! ስግነት ባይኖርህ ነው!» አሉ። እያለቀሱ ነው። «እውነቴን ነው እማምዬ! አባባ ይሙት ይሄው አንድ ወር ሆነኝ ከአዲስ አበባ ውጭ ነኝ! ለፊልድ ሥራ ወጥቼ ጋምቤላ ነኝ። ገና ትናንት ነው ጌትዬ በመኪና አደጋ እንዲህ መሆኑን የሰማሁት። አውሮፕላን ካገኘሁ ዛሬ ከሰዓት በኋላ እመጣለሁ ...» ምክንያት አላጣም። «እስቲ ይሁን ... ይሁን ... እኔ ግን እንዲህም አትመስለኝ ነበር! ... በል ተወው...» ተቀይመዋል በጣም ተከፍተዋል። «አልሰማሁ ሆኖ እንጂ ጌትዬ መታመሙን ሰምቼ ይህን ያህል ጊዜ መቆየት የምችል ሰው አይደለሁም። ... እውነት እማመይ! እንደምንም ብዬ ዛሬውኑ እደርሳለሁ ...» መፍጠን አለበት። ለምሳ ሲወጣ ሁለት ኪሎ ሙዝ አንጠልጥሎ ወደ ጓደኛው መብረር አለበት። መዘግየት የለበትም። የሚችለው ሁለት ኪሎ ሙዝ መግዛትና ፈጥኖ ወደ ታማሚ ጓደኛው መድረስ ብቻ ነው። «እሱማ ስምህን እየጠራ ሲቃዥ ነው የሰነበተው... 'ጓደኛዬ የክፉ ቀኔ' እያለ ሲለፈልፍ ይቆይና 'ናልኝ... ማር አማረኝ አልሰኝ' እያለ ይጣራል። ምኑ ቅጡ። አንተም ጠፋህ ... እሱም ማር እንዳማረው ቀረ። ለበሽተኛ የሚሆን ንፁህ ማር በማንኪያ እንኳን የሚሰጠኝ ለክፉ ቀን የሚሆን ሰው ጠፋ። ተወውማ የኔን ጉድ ... ማሩ ይቅር ባይሆን እንደማር የሚወድህ የልጅነት ጓደኛው አንተ...» ንግግራቸው ተቆራረጠ። «እውነት እማምዬ ዛሬውኑ እመጣለሁ። መርካቶ አካባቢ ማር የመሸጥ ታዋቂ ነጋዴ ሰው አውቃለሁ። እሱ ጋ እወስድዎታለሁ ... በጥሩ ዋጋ ይሸጥልዎታል።» በደሉን ለማቃለል መለፍለፍ ጀመረ። «አይ አንተ ... ደ'ሞ የዘንድሮ ማር ምኑንም ምኑንም እየጨመሩበት ተበላሽቶ የለ! ... ሙዝ እኮ ነው በማር ሚዛን ስናስለካ የኖርነው ... ጌትዬን ደግሞ ታውቀዋለህ ሙዝ አይስማማውም። የመንደር ሰው መታመሙን ሰምቶ ይዞለት የመጣው ሙዝ አንዷን ቢቀምስ ሲያስመልሰው አደረ። ቢቸግር እኮ ነው! ... ከሙዝ የተቀላቀለ የመርካቶ ማር ይስማማው ብለህ ነው?» የተጨነቀ ድምጽ። «እሱ... አዎ... ንፁህ ማር ካልሆነ... » መቀጠል አልቻለም። እሳቸው ቀጠሉ። «ይልቅ ልጄ ... ጋምቤላ ንፁህ ማር አለ ሲሉ ሰምቻለሁ። አንድ ሁለት ኪሎ አምጣለት።» ፈጥኖ መመለስ አልቻለም። «ነገርኩህ እንዳታበዛው! ሁለት ኪሎ ይበቃል ... ብቻ ማስቸገር እንዳይሆን! መቼም አንተ ነህ ብዬ ነው። ፍቅራችሁን ስለማውቅ ነው "እማምዬ" እያልህ ስትጠራኝ እኮ ራሱን አምጬ የወለድኩትን ጌትዬን ነው የምትመስለኝ። ... ንፁሁን መርጠህ ...» ስልኩ ተቋረጠ። ጓደኛው ሁለት ኪሎ የጋምቤላ ማር እንጂ ሁለት ኪሎ ሙዝ አይመጥነውም። ━━━━━━━━ 📔 መልስ አዳኝ እና ሌሎች አጫጭር ልብ-ወለዶች 📄 178 - 181 🗓 2003 ዓ.ም. 📖 📖 📖 📖 📖 https://t.me/Ethiobooks

ማር Vs ሙዝ ━━✦━━ ✍ አንተነህ ይግዛው ' ከሰማ ሰነባብቷል። አልሞላለት ብሎ እንጂ ወሬው ከ'ሱ ከደረሰ ቀናት ተቆጥረዋል። የልጅነት ጓደኛው በመኪና አደጋ ተጎድቶ አልጋ ላይ መዋሉን ከሰማ ሰነባብቷል። አብሮ አደግ ጓደኛው ጌትዬ መታመሙን ሰምቷል። ይወደዋል። እንደሚወደውም በተግባር አሳይቶታል። ጌትዬ ከሥራ ተፈናቅሎ አንገቱን በደፋባቸው ቀናት ከጎኑ ሆኖ አለሁልህ ብሎታል። ዛሬ ግን መውደዱን ፈጥኖ በተግባር ማሳየት አልቻለም። ይህን ማድረግ ባለመቻሉ ራሱን ጠላ። አቅጣጫዋን ስታ በጓደኛው ላይ የወጣችው ክልፍልፍ መኪና ወደ እርሱ አቅጣጫ ብትመጣ ተመኘ። ጓደኛው ከተገጨ ከሦስት ቀናት በኋላ ወሬውን ከሰው ሰማ። የእውነቱን አዘነ። ጓደኛውን ከጎዳና ላይ አፋፍሰው ወደ ሆስፒታል ከወሰዱት አዛኝ ሰዎች መካከል እሱ የለበትም። ከሥራ የተፈናቀለ፣ አደጋ ደርሶበት በደም አበላ የጨቀየ ልጃቸውን ሕይወት ለማዳን ተበዳድረው ወደ ሆስፒታል የወሰዱት እናቱ ናቸው። ማንም ሳይረዳቸው፣ ዘመድ ጓደኛ ሳያግዛቸው። ታማሚ ጓደኛውን እየተመላለሱ የጠየቁት ሌሎች ጓደኞቹና ዘመዶቹ ናቸው። እሱ ዘግይቶ ነው ሁሉንም የሰማው። ዘግይቶ እንደ መስማቱ መፍጠን ነበረበት። ግን አልቻለም። 'እወድሃለሁ' የሚለውን ጓደኛውን አርፍዶ መጠየቅ አስፈራው። በደለኛነት አባከነው። «ምን ይለኛል? እንዲህ ቆይቼ ልጠይቀው ስሄድ ምን ይሰማዋል?» እያለ ነጋ ጠባ ማሰብ ያዘ። ምን ማድረግ እንዳለበት ሲያስብ አሁንም ዘገየ። ቀኑ ሲጨምር በደሉም እየጨመረ መምጣቱ ተሰማው። «ያለኝን ይበለኝ እንጂ ከዚህ በኋላስ መዘግየት የለብኝም» ብሎ ተነሳ። ተነስቶ ግን አልሄደም። «ምን ይዤ ነው የምሄደው?» አለ። ደመወዙን አሟጦ ጨርሷል። የሚያበድረው አጥቶ ለቀናት ባዝኗል። ጌትዬ ሆስፒታል አልጋ ላይ ተንጋሎ ጣራው ላይ እሱን ጓደኛውን ሲፈልግ ይታየዋል። ሰውነቱን የሚጠግን ሁነኛ ምግብ አምሮት የድሃ እናቱን አቅም በማየት ዝል ሲል ይታየዋል። የተሰበረ አጥንት የሚጠግን ጥሩ ምግብ ይዞለት ሊሄድ አስቦ ነበር። ግን በቂ ገንዘብ የለውም። ኪሎ ሙዝ ከመግዛት የሚያልፍ ገንዘብ የለውም። ቢሆንም ግን ወደ ጓደኛው መሄድ አለበት። ያገኘውን ይዞ ከፊቱ መቆም ይገባዋል። አሳፋሪ ቢሆንም መሄድ እንዳለበት አምኗል። እንኳን የሚወደው ጓደኛውን፣ ጓደኝነታቸውን የሚያውቁትን እናቱን ዓይን ማየት ቢያሳፍረውም መሄድ አለበት። ዛሬን ሊያልፋት አልፈቀደም። ዛሬ ጠዋት ቆርጦ ነው ከቤቱ የወጣው። በምሳ ሰዓት ከቢሮ ወጥቶ ሙዝ ገዝቶ ወደ ጓደኛው ይሄዳል። ይቅርታውን ይቀበላል። ምሳ ሰዓት ላይ ወደ ታማሚ ጓደኛው ለመሄድ እያሰበ ቁርስ ሰዓት ላይ ስልኩ ጮኸ። «ምነው ልጄ? ... የአንተና የጌትዬ ነገር እንዲህ ሆኖ ቀረ? ... የናንተ ጓደኝነት መጨረሻው ይሄ ነው?» የተቆራረጠ ድምጽ። የባልቴት፣ የታማሚ ጓደኛው የጌትዬ እናት ድምጽ። >>> @ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ - 2 የመጨረሻው!

አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ - 1

▶ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ━━━━━━━━ «ተሟጋቹ መነኩሴ» @ethiobooks
+1
▶   አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ━━━━━━━━ «ተሟጋቹ መነኩሴ»               @ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

💬 ❝ሕይወት የምትመዘነው ከፍ ያለ ዋጋ እንደሚያወጣ አልማዝ፣ በስፋቷ ሳይሆን በክብደቷ ነው። ስለዚህ ሕይወታችንን በተግባር እንጂ በዘመን ብዛት አንለካ።❞ ሴኔካ 💬 ❝ግብረገብ የሌለው ሰው፣ በጫካ
💬 ❝ሕይወት የምትመዘነው ከፍ ያለ ዋጋ እንደሚያወጣ አልማዝ፣ በስፋቷ ሳይሆን በክብደቷ ነው። ስለዚህ ሕይወታችንን በተግባር እንጂ በዘመን ብዛት አንለካ።❞ ሴኔካ 💬 ❝ግብረገብ የሌለው ሰው፣ በጫካ ውስጥ ግዳይ ሊጥል ከሚንጎማለል ጨካኝ አውሬ ተለይቶ ሊታይ አይችልም።❞ አልበርት ካሙ 💬 ❝የመጀመሪያውን ደረጃ በእምነት ተራመዱ። ሙሉውን መወጣጫ ደረጃ ማየት የለባችሁም። የመጀመሪያው በቂ ነው።❞ ዶ/ር ማርቲን ሉተር ኪንግ 💬 ❝አእምሮ እንደ ሆድ ነው። ያስገባው በሙሉ ሳይሆን ያዋሃደው ነው ዋጋ ያለው።❞ ላፎንቴን 💬 ❝አንድን ነገር ለማከናወን የሚወስድባችሁን ጊዜ በመፍራት በጉዟችሁ ላይ እንቅፋት እንዲሆንባችሁ አትፍቀዱለት። ጊዜው እንደሆነ ማለፉ አይቀርም። ደግሞም ምናልባት እያለፈ ያለውን ጊዜም በተሻለ መልኩ ጥቅም ላይ ልናውለው እንችል ይሆናል።❞ ኧርል ናይቲንጌል 💬 ❝ሰው የሚያስበው ሁሉና የሚያደርገው ሁሉ ተሟልቶልኛል፣ ረክቻለሁ ብሎ የነፍሱን ፍላጎት በማሳደግ ፋንታ በአንድ ቦታ ላይ ገትቶ መቆም የጀመረበት ያ ዕለት አሳዛኝ ነው።❞ ፊሊፕስ ብሩክስ 💬 ❝ታላላቅ ሰዎች የሚባሉት፣ ዓለም የምትተዳደረው በሃሳቦች መሆኑን መረዳት የቻሉ ናቸው።❞ ራልፍ ዋልዶ ኤመርሰን 💬 💬 ጥቅሶች @ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

ያገር ባህል ━━•━━ ✍ ከፍቅሩ ኪዳኔ ' ጥንት ልጆች ሆነን ባገራችን ባህል መሠረት የሚከበሩትን በዓሎች በሙሉ በደንብ እናከብር ነበር። ዋናው የወንዶች ልጆች በዓል በነሐሴ ወር የሚከበረው ቡሄ ነው። ለቡሄ ሳምንት ሲቀረው እያንዳንዳችን ጅራፍ ገምደን ስናጮህ እንውላለን እንጂ አንጋረፍም። በቅርብ የሚተዋወቁ የሠፈር ልጆች የራሳቸውን ቡድን አቋቁመው በቡሄ ማግስት ፀሐይ ሲጠልቅ ጀምረው ዱላቸውን ይዘው እየጨፈሩ ወደ ቤተሰብ ዘንድ እየሄዱ የቡሄ ዳቦና ፍራንክ በመሰብሰብ ያገኙትን ሁሉ ያለ ጭቅጭቅ ይካፈላሉ። የኛ ሕዝብ ደግነቱንና ቸርነቱን የሚገልፀው በብዙ መንገድ በመሆኑ፣ በድሃም ሆነ በሀብታም ቤት፣ ልጆች ኖሩ አልኖሩ፣ እናቶች የቡሄ ዳቦን መጋገር እንደ ግዴታ በመውሰድ ወጣቱን ያስደስታሉ። የሚሰበሰበው ዳቦ ስለሚበዛ ለተቸገረ ማካፈል የተለመደ ነው።
የቡሄ ጭፈራና ዘፈኖች ሆያ ሆዬና አሲዮ ቤሌማ ወግና ሥርዓት አላቸው። ሆያ ሆዬ ጉዴ፣ ጨዋታ ነው ልማዴ፤ በማለት እውነት መናገር ነው።
የሴቶች ልጆች በዓል ደግሞ ከዕንቁጣጣሽ በዓል ጋር የተያያዘ ነው። ከሜዳ የሚቀጥፉትን አደይ አበባ ይዘው እየዘፈኑ አበባ መስጠት ገንዘብ ያስገኛል። ወንዶቹም የተለያዩ የአበባ ሥዕሎችን በቀለም በመሳል ለቅርብ ቤተሰብና ለዘመዶቻቸው በማበርከት ሣንቲም ያጠራቅማሉ። ለመጀመሪያ ጊዜ ሸራ ጫማ የገዛሁት በዕንቁጣጣሽ ባገኘሁት ብር ነው። ፒያሳ የነበረው (አሁን የፈረሰው) ኪንግ ጆርጅ ቡና ቤት ገብቼ ኬክና አረንቻታ ገዝቼ የቀመስኩት በዚያን ወቅት መሆኑን አውቃለሁ። በመስቀል በዓል ሁሉም ችቦውን አዘጋጅቶ ወይም ገዝቶ እያንዳንዱ ሰው በአጥር ግቢው ውስጥ ከማቀጣጠሉ በፊት በየሠፈሩ ልክ እንደ ቡሄ ይጨፈራል። ያኔ ጉለሌ ጫካ ስለነበረው የአበባ፣ ዱላ፣ ጅራፍና ችቦ ችግር አልነበረም። ገናን ሁሉም ከቤተሰቡ ጋር የሚያከብር ሲሆን፣ በጥምቀት ሁላችንም የሠፈራችንን ታቦት (ዮሐንስን) ተከትለን ወደ ጃንሆይ ሜዳ በመሄድ ብርድ እየፈደፈደን እናድራለን። በዚያን ጊዜ ሰዓት እላፊ ስለነበረ ከእኩለ ሌሊት በኋላ መነቃነቅ አይቻልም። ከቤታችን ውጭ የማደር ነፃነት የምናገኘው በጥምቀት በዓል ምክንያት ነው። በየሠፈራችን ከሚገኘው ዓረብ ሱቅ ዕቃ ለመግዛት ስንላክ ዓረቡ "ምራቂ" ብሎ ከሚሰጠን ብትን ስኳር በስተቀር ከረሜላ፣ ሸንኮራ አገዳ፣ ቴምር፣ ስኳር ድንች፣ ጉልባን፣ ተልባና እርጎ እንደልብ የምናገኘው በበዓላት ወቅት ነው። በፋሲካ ትላልቆቹ ስለሚጾሙ እኛም በግድ እንጾማለን። ለፋሲካ ወደ ቤተክርስትያን መሄድ የተለመደ ነው። ትላልቆቹ ኃጢአታቸውን ከተናዘዙ በኋላ ስንት መስገድ እንዳለባቸው ሲነገራቸው፣ እኛ ደግሞ ተሰባስበን አንዱ የሌላውን ኃጢአት እያጋለጠ ስግደቱን ወደ ስፖርት ቀይረን ስንሰግድ ውለን እንገባለን። እግዚአብሔርም አልተቆጣንም። ... በኛ ዘመን ልጆች ካባትና እናታቸው ጋር ወይም ከትላልቆቹ ሰዎች ጋር አብረው መብላት ክልክል ስለነበረ ቅልጥሙና የዶሮው ቆዳ ለኛ አይደርሰንም። እኔ ልጄን ሳሳድግ ጥሩ ጥሩውን ብልት እየመረጥኩ ስሰጠውና የፈለገውን ብስኩት፣ ጀላቲና ፉርኖ ገዝቼ ሳበላው ዕድለኛ መሆኑን የሚያውቅ አልመሰለኝም። የዶሮ ዳቦ የሚደፋው ለፋሲካ ስለነበር ዕድል ያጋጠመው ዕንቁላል ያገኛል። ሌሊት ተነስተን ለማስፈሰክ ጠዋት ስንነሳ ፍትፍታችንን ግጥም አድርገን መብላት ነው። እኔ ከዶሮ ወጥ ይልቅ የሥጋ ወጥ የምመርጠው በእንጀራ የሚጠቀለል የተከተፈ ሥጋ ስለሚገኝበት ነው። በዚያ በልጅነት ዕድሜ ቤተሰቦቻችን ናቸው ግብረ ገብን፣ ጨዋነትን፣ ታዛዥነትንና ሰው አክባሪነትን ያስተማሩን። ለኑሮ አስፈላጊ የሆኑትን ፀባይና ልምድ ያወረሱን። >>> ━━━━━━━━ 📔 የፒያሳ ልጅ 📄 25 - 27 📖 📖 📖 📖 📖 https://t.me/Ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

አሚሽ የተሰኘው የማኅበረሰብ ክፍል የሚኖረው በአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ ነው። አሚሾች ስዊዘርላንድና ፈረንሳይን ከመሳሰሉ ሀገሮች በመነሳት ወደ አሜሪካ የዘለቁት በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን መጨረሻ አካባቢ ነው። የአሚሽ ማኅበረሰብ አባላት "በሥልጡኗ" አሜሪካ ክፍለ ግዛቶች ውስጥ የሚኖሩት የራሳቸውን ጥንታዊ ወግ፣ ልማድና ባህል "የሙጥኝ" ብለው በመያዝ ነው። ማኅበረሰቡ በዋነኛነት ከሚታወቅባቸው የራሱ ብቻ ከሆኑት መገለጫዎች መካከልም የሚከተሉት ልዩነቶች በዋነኛነት ይጠቀሳሉ። እነዚህ ልዩነቶች ኦርዱንግ (Ordung) በሚባለው የማኅበረሰቡ መተዳደሪያ ደንብ ውስጥ በዝርዝር ተደንግገዋል። ➢ አሜሪካውያን አሚሾች "የሥልጣኔ ቁንጮ ላይ ተፈናጥጫለሁ" በምትለው ሀገር እየኖሩ በሰው ሠራሽ ሞተር ተሽከርካሪዎች በፍፁም አይገለገሉም። ይልቁንስ መጓጓዣቸው የጋማ ከብቶችና ጥንታውያን የፈረስ ጋሪዎች ናቸው። ➢ እንደ ስልክ፣ ኤሌክትሪክ፣ የልብስ ማጠቢያ ማሽን፣ ቴሌቪዥንና ሬድዮ የመሳሰሉትን የቴክኖሎጂ ውጤቶች አሚሾች በፍፁም አይጠቀሙም። ለመብራትና ለማገዶ የሚመርጡትም በአብዛኛው እንጨት፣ ኩበትና የመሳሰሉትን ማገዶዎች ነው። ➢ አሜሪካውያን ወጣቶች በሚማሩባቸው ትምህርት ቤቶች አሚሾች ልጆቻቸውን በጭራሽ አይልኩም። ባህላቸውና ወጋቸው የሚፈቅድላቸውን የራሳቸውን ትምህርት ቤት በመክፈት ያስተምራሉ እንጂ። ➢ በአጠቃላይ የአሚሽ ማኅበረሰብ አባላት ከልደት እስከ ሞት ያለው ማኅበራዊ እንቅስቃሴአቸውና ለቴክኖሎጂ ውጤቶች ያላቸው ግምት ከሌላው አሜሪካዊ የሕይወት ፍልስፍና በእጅጉ የራቀ ነው። አልባሳታቸው ጥንታዊ ነው፣ አመጋገባቸውም በጋራ ነው። በአሚሽ ማኅበረሰብ መንደር እንደ ሀገራችን የዛሬው የገጠር መንደሮች ጭስ ሲጨስ፣ ሴቶች በወገባቸውና በጭንቅላታቸው ውሃ ተሸክመው ሲሄዱ ይታያል። ገበሬዎች የሚከተሉት ጥንታዊውን የአስተራረስ ባህል ነው። ደፈር ብሎ መናገር ካስፈለገም የአሚሾች ኑሮ ጥንታዊውን የጋርዮሽ ሥርዓተ-ማኅበር ያስታውሳል ቢባል ከእውነታ አያርቅም። ለምን ከዚህ "ያረጀና ያፈጀ" የኑሮ ዘይቤ ጋር ሊጣበቁ ቻሉ? ለምንስ በቅንጡዎቹ የአሜሪካ ግዛቶች ውስጥ እኒህ ማኅበረሰቦች እጅግ ኋላ ቀር የሆነ የአኗኗር ሥርዓት ለመኖር ወሰኑ? ምክንያታቸውን የሚገልፁት በቋንቋቸውና በባህላቸው ነው። "ለምን ይህን መሰል ኑሮ መረጣችሁ?" ተብለው ሲጠየቁም የሚያስረዱትና የሚያሳምኑበት የራሳቸው የሆነ መከራከሪያ አላቸው። በአለባበሳቸውና በአጠቃላይ እንቅስቃሴና አኗኗራቸው አሚሾችን በቀላሉ መለየት አያዳግትም። በዋነኝነት ግን ቋንቋቸው ለሕይወት ፍልስፍናቸውና ለአኗኗር ዘይቤአቸው ተቀዳሚ አስረጃቸው ነው። >>> ━━━━━━━━━ 📔 የጥበባት ጉባኤ ✍ ጌታቸው በለጠ 📄 15 - 16 🗓 ፳፻፬ ዓ.ም. 📖 📖 📖 📖 📖 https://t.me/Ethiobooks

━━ የአሚሽ ማኅበረሰብ ━━ @ethiobooks
━━ የአሚሽ ማኅበረሰብ ━━ @ethiobooks

sticker.webp0.08 KB

አብደላ ኦቻላን - 2 የመጨረሻው!

አብደላ ኦቻላን - 1

▶ አ ብ ደ ላ ኦ ቻ ላ ን ━━━━━━━ «እስረኛው ታጋይ» @ethiobooks
+1
▶   አ ብ ደ ላ ኦ ቻ ላ ን ━━━━━━━ «እስረኛው ታጋይ»               @ethiobooks

sticker.webp0.08 KB