Thoughts
ቸል የተባሉ እሳቤዎች፥ ያልታዩ እይታዎች የሚፈነጩበት ቤት ነው ፥ እናንተስ ጎራ አትሉም? comment for the writer : @Exquisiteperfume discussion group https://t.me/+uDtKY02cOho2NGZk Tiktok: https://www.tiktok.com/@the_author_nani?_t=8pGCAO5NksY&_r=1 Since:Dec-10-2022
Mostrar más📈 Análisis del canal de Telegram Thoughts
El canal Thoughts (@justhoughtsss) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 11 072 suscriptores, ocupando la posición 8 164 en la categoría Religión y espiritualidad y el puesto 3 031 en la región Etiopía.
📊 Métricas de audiencia y dinámica
Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 11 072 suscriptores.
Según los últimos datos del 04 septiembre, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 110, y en las últimas 24 horas de 15, conservando un alto alcance.
- Estado de verificación: No verificado
- Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 20.04%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 9.00% de reacciones respecto al total de suscriptores.
- Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 2 219 visualizaciones. En el primer día suele acumular 997 visualizaciones.
- Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 22.
📝 Descripción y política de contenido
El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
“ቸል የተባሉ እሳቤዎች፥ ያልታዩ እይታዎች የሚፈነጩበት ቤት ነው ፥ እናንተስ ጎራ አትሉም?
comment for the writer : @Exquisiteperfume
discussion group https://t.me/+uDtKY02cOho2NGZk
Tiktok: https://www.tiktok.com/@the_author_nani?_t=8pGCAO5NksY&_r=1
Since:Dec-10-2022”
Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 05 septiembre, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Religión y espiritualidad.
Carga de datos en curso...
| Fecha | Crecimiento de Suscriptores | Menciones | Canales | |
| 05 septiembre | 0 | |||
| 04 septiembre | +16 | |||
| 03 septiembre | +8 | |||
| 02 septiembre | +1 | |||
| 01 septiembre | +11 |
| 2 | Sin texto... | 305 |
| 3 | file_200690 | 296 |
| 4 | ገበያ ለመሄድ ጊዜ ለሌላችሁ ሰዎች ይኸው መፍትሄ
በ0923516190 መደወል ብቻ ግልግል ማለት አይደል? | 579 |
| 5 | ሊያና
እማዬን እንደዛ እልል ያስባላት ዜና ምን አይነት ዱብ እዳ እንደሆነብኝ የሚያውቅ አለ? በተለይ የኤሚ አኳኋን፣ ስብር አባባሉ አላስችል አለኝ።
ታሪክ ራሱንም እየደገመ መሰለኝ ከአመታት በፊት እንደሆንነው... በፀጥታ ተሸኛኝተን ቤት ስገባ እማዬና አባዬ ሲኳረፉ እንደሚሆኑት እሷም የምታነብበት ክፍል እሱም ንድፉን የሚሰራበት ክፍል ገብተው መሸገዋል።
ልነፋረቅባት አና ጋር ስሄድ ትራሷን አቅፋ እየተንከባለለች ነው። የሚጋባ ሳቅ እየሳቀች "ሊ ምን እንዳደረገ አታውቂም እሱም አያውቅም ይሄ ለኔ ምን ማለት እንደሆነ የሚያውቅ ሰው አለ?" አለች መፅሀፍ አቅፋ
"ምንድነው መፅሃፍ እያነበብሽ ነው?" አልኳት
የያዘችውን መፅሀፍ ቀና አድርጋ አሳየችኝ One Hundred Love Sonnets by Pablio Neruda ይላል
"መፅሀፍ ገዛልኝ እሱ ነው የሚገርምሽ?" ልቤን ማንጠልጠሏ ነው "ሌላ ምን አደረገልሽ?" ቢያንስ ገፀባህርይ አይደለም እንደዚህ የሚያስፈነጥዛት
"ደብዳቤ ፅፎልኛል። የምወደውን የpablo nerudaን መፅሀፍ መግዛቱ ሳያንስ በአማርኛ እኮ ነው ደብዳቤውን የፃፈው እዪው ቃላት አጣጣሉ ሲያምር የሰዓሊ እኮ ነው የሚመስለው"
"የኔም የኤሚም ፅሁፍ አያምርም" አልኳት ሳበሳጫት እሷ እቴ "የምወደው የግጥም መድብል ነው ስለግጥም ያለሽን አቋም ያስቀይርሽ ይሆናል" ብሎ ነው የፃፈው ብላ አነበበችልኝ። እንደዚህ እንዳስደሰታት ቢያውቅ ምናለበት
...
ኦዚያን
እቤት እንደገባ የእለቱን ዜናዎች ሲከፍት ሶስተኛ ግድያ መፈፀሙ የዜናዎቹን አውታሮች እንዳጨናነቀ አየ። ከግድያውም ከተገኘውም ደብዳቤ በላይ ትኩረቱን የያዘው የሟች የትውልድ ቦታ ነበር። ፔሊ
✍ናኒ
ይቀጥል የምትሉ ብቻ react እያደረጋችሁ
https://t.me/justhoughtsss | 1 041 |
| 6 | ክፍል 11
ምናልባት
የሌሎቹን ባላውቅም እኔ ግን አድካሚ ቀን ነው የነበረኝ። እንደሌላ ቤተሰብ የውሸት የጓጓን አስመስለን "ውሎ እንዴት ነበር ታድያ" አንባባልም ምክንያቱም ሁላችንም ከስራ የዘለለ ህይወት የለንም
የአባዬን ማባርያ የሌለው ተጣጣፊ ኮንክሪት ወሬ ወይም አዲስ ገበያ ላይ ስለዋለ ቀለም ሊያ ስታወራ ስለማይገባን ይሰለቸናል። እማዬ ስለታካሚዎቿ ማውራት በህግ ትከለከላለች እኔ ደግሞ አንጀቱ ተዘርግፎ እግሩ ተቆርጦ ከማለት የዘለለ አስደሳች ውሎ ኖሮኝ አያውቅም።
ለዛ ነው ራት ስንበላ ብዙውን ጊዜ ምግብ ቤት ውስጥ ጠረጴዛ መጋራት እንዳለበት የማይተዋወቅ ሰው የምንሆነው
ይሄንና ምን እንደሆነ ባላውቅም ጭንቅላቴ ያንንም እያነሳ እየጣለ ጭንቅላቴ ይባትላል። አባ ዜናው ላይ ተመስጧል።
ቀና ስል ሊያና ፈገግ ብላ ጠቀሰቺኝ። የሆነ ነገር ስታቅድ ነው እንደዚህ የምትሆነው "ስሙማ" አለች እማን ከሀሳቧ አባን ከዜናው እያደናቀፈቻቸው
"እ" ስትል እማ
"ሰበር ዜና" የሚል ድምፅ የሁላችንንም ትኩረት ሰረቀው "ቆይ ቆይ አንዴ አዳምጡ" ብሎ አባ ድምፁን ጨመረው
"በሁለት ወር ውስጥ የተሰራው ከተማ የሚጠናቀቅ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታውቋል። ከፔሊ የመጣችሁ ሰዎች በፈቃደኝነት ወደዛ ሄዳችሁ መኖር የምትችሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።"
"እልልል" እማ አቀለጠችው "ተመስገን ከዚህ የተረገመ ከተማ እንደዚህ በቀላሉ ልንወጣ ነው እልልል"
ሊያና ፊቷ ገርጥቷል አባ ምንም ስሜት አይታይበትም እሺ እኔ ምን እንደዚህ ልቤን አራደው?
"ሊያ ምን ልትነግሪን ነበር?" አለ አባ ምንም እንዳልተፈጠረ
"እነእትዬ ትሬዛን ነገ ማታ ምሳ እንድንጠራቸው ነበር" አለች ድምጿ ፈዝዞ
"እንችላለን ምን ችግር አለው ስለጠራችን ውለታ የዋለችልን እንዳይመስላት እንጂ አብሮ ለመኖር የሚያስገድደን ነገር የለም ልንወጣ አይደለ" ደስታዋ በድምጿ በፊቷ ይንፀባረቃል።
እማ እዚህ መኖራችንን እንደዚህ ጠልታው ነበር?
...
ኤሞን
ሰዓቱ ለሁለት ሩብ ጉዳይ ይላል። ቆይ ለእራት ግበዣ ስንት ሰዓት መሄድ ነው ትክክል? አንድ ሰዓት ገና ላይዘጋጅ ይችላል ሶስት ሰዓት እንደመቅረት ይቆጠር ይሆናል።
ስለዚህ ሁለት ሰዓት ነው። በሩብ ደቂቃ ውስጥ ብንሄድ ትክክል ስለመሰለኝ ተዘጋጅቼ ጨርሻለሁ። "ይሄ ልጅ ይቆያል እንዴ? በጣም መሸ እኮ" አለች እማ እንደልማዷ እየተጨናነቀች
"እየደረስኩ ነው ብሏል አትጨናነቂ" አልኳትና ወደሳሎን ስሄድ እሱ ሲያንኳኳ ተገጣጠምን። ስከፍትለት
"አላመሸሁም አይደል? ጥሪ ኖሮ ማርፈድ ልክ አይደለም" እያለ እየተጣደፈ ወደክፍሉ ገባ
አቻኩሎ ደብቆ ሊያስገባው የፈለገውን መፅሐፍ አይቼበታለሁ። ተከትዬው ክፍሉ ስገባ ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦታል።
"እኔ እኮ አላምንም"አልኩት መፅሀፉን አገላብጬ እያየሁ
እንዳልሰማኝ ልብሱን ይቀይራል። "የከተማዋ ጫፍ ድረስ ሄደህ ገዛኸው?" ሌላ ቦታ ማግኘት አቅቶት የተወው መፅሃፍ ነው።
"ምን ችግር አለው?" ለክት ብቻ የሚያወጣትን ሽቶ ኮሌታው ላይ እየቀባ
"ለሊያ እህት ነው አይደል?" አልመለሰልኝም
"እንውጣ ልጆች" እማ ተጣራች
"ጨርሰናል መጣን" መብራቱን እላዬ ላይ አጥፍቶ ወጣ ያመለጠኝ መስሎት
...
ኪራኮስ
በሩን ስናንኳኳ "መጡ መጡ መጡ" የሚል ድምፅ ከውስጥ ሰማሁ። የከፈተችው አናን የምትመስል ሴት ናት እህቷ ናት ማለት ነው። እየሮጠች መጥታ እንደከፈተች ያስታውቃል።
"እንኳን ደህና መጣችሁ" አለች ኤሚ በአይኖቿ እያቀፈችው። ደስ ሲሉ
ስንገባ አና እና እናቷ ምግብ እያቀራረቡ ነበር። እንደነገሩ ያዝያዘችው ፀጉሯ ታጥፎ ራሱ አለሁ ይላል። ከፀጉር ማስያዣው ጥቂት ወጥቶ ጀርባዋ ላይ ተኝቷል። ሁሉም ሰላም ሲባባል ውስጥ ነበረች። አባታቸው ኑ ተቀመጡ ብሎ ገና ከመግባታችን የምግብ ጠረጴዛው ጋር ወሰደን።
አባትየውና እና እናትየው ትዕዩ ተቀመጡ። ኤሚና ሊያና ደግሞ በግራ በኩል ተቀመጡ ከኤሚ አጠገብ ማሚ ተቀመጠች ከአባታቸው አጠገብ መሆኑ ነው።
ኦዚያን እናታቸው በስተቀኝ ተቀምጦ ወሬ ጀምረዋል። እኛ አልሰማ የምንለውን ወሬ ከእሷ ጋር ሲሆን እኩል በእኩል ሲያወሩ ደስ ይለኛል። ሁሉም ሰው እንደራሱ ሆኖ የሚያወራው ሰው ይፈልጋል አይደል?
ኤሚና ሊያና ምንም እንደማይተዋወቅ ሰው የሚያደርጉት ጥረት ያስቀኛል። አይነስውር የሚያየው መሳሳብ በመላሀቸው ኖሮ ለደቂቃ መነጣጠል ሳይፈልጉ ወላጆቻቸው እንዳያውቁባቸው የሚያደርጉት ጥረት ረብ የለሽ ይሆንብኛል። የፍቅራቸው አምላክ አይናቸውን ጋርዶላቸው እንጂ አልቆላቸው ነበር።
አቀራርባ ስትጨርስ እና ስትመጣ የነበረው ቦታ በኔና በኦዚ መሀል ያለው ወንበር ብቻ ነበር። አጋጣሚ መሆን አለበት (አይደል?)
ስትቀመጥ ለስላሳ ሽቶዋ አወደኝ። የግጥም ምሽቱ ቀን የተቀባችው ነው። በትግል ከጭንቅላቴ ያወጣሁትን አደሰችልኝ።
"በሁለት ወር ውስጥ መውጣት ትችላላችሁ አሉ ደግሞ አይደል" እማ ፀጥታውን አፈረሰችው
ጋሽ ኤስሮም መልስ እየመለሰላት ነው። ግዴታ እንዳልሆነና መሄድ ከፈለጉ ብቻ እንደሚሄዱ እየነገራት ነው
ከዛ በኋላ ያሉትን አልሰማሁም መብረቅ እንደወረደበት ደርቄ ቀረሁ። ሁለት ወር? ስምንት ሀሙስ? ከዛ በኋላ እንደልማዴ ብቻዬን ልሄድ ነው።
ፊቴ ላይም ድንጋጤዬ ታይቷል መሰል "አባ ምነው አመመህ እንዴ?" ስትል ማሚ "ኧረ ትንሽ ብርድ አግኝቶኛል መሰለኝ ውጋት ይዞኝ ነው አልኳት ደህናውን ወገቤን ደግፌ
"አና እኮ ነርስ ናት እሷን ጠይቃት መድሀኒቱን" አለ አባታቸው ኤስሮም "አባ ደሞ ወጌሻ መሰልኩህ እንዴ"
ስትለው በሳቅ ተቀበልናት።
የእሷ ወንበር ላይ ስደገፍ ትከሻዋን ዳበስ አድርጌው አለፍኩ ፈገግ ያለችበትን ከንፈሯን ነክሳ ስታስቆመው አይቻታለሁ። እጄን እዛው ተውኩት ትከሻዋ ጋር ጉንጮቿ እየቀሉ ነው።
"ሌላ ምን አዲስ ነገር አለ?" ስትለው የእነአና እናት እትዬ ማሊካ "ምንም የለም ያው የከተማዋ ነባር ነዋሪዎች ላይ ብቻ ስለሆነ እየተፈፀመ ያለው የተገመተው አዲስ ከሰፈሩት ሰዎች መሀል ሊሆን ይችላል እየተባለ ነው" አላት ቆይ ይሄ ልጅ ያለዚህም ጉዳይ ስራ የለውም እንዴ?
"ለዛ ነው አይደል በየመንገዱ የሚገላምጠኝ ሰው በዝቷል" አለች አና ቀጥላም እህቷ ከሌሎች ጎረቤቶች ስለገጠማት ዘለፋ ነገረችን
ማን አባቱ ነው የሚገላምጣት
"መፅሀፉን ገዝቼልሀለው እሰጥሀለው ስትወጡ" አለች ለሌላ ለማንም በማይሰማ ድምፅ
"ደስ ይለኛል"
ከዛ በኋላ ምሽቱ ያለቃላት ልውውጥ ከእሷ ጋር ስናወራ ቀና ብላ ባየቺኝ ቁጥር ልቤ ብትንትኑ እየወጣ፣
ማሚ እና ጋሽ ኤስሮም ስለሆነ አዲስ ተክል ቅጠል አበቃቀል ሲያወሩ ኤሚና ሊያ በዝምታ ሲቆዝሙ እናታቸውና ኦዚ ስለግድያ አይነቶች ሲዘረዝሩ አምሽተን
"ሰዓቱ እንዴት ሄዷል ባካችሁ" ስትል እናታቸው ሂዱ ማለቷ እንደሆነ ገብቶን ተነሳን። ልንወጣ ስንል ጥንድ ጥንድ ሆነው ሲያወሩ በነበሩበት አኳኋን ወጡ።
ልብሴን ጎተት አድርጋ ስታስቀረኝ ለመፅሀፉ መሆኑ ገብቶኝ ሌሎቹ ወጥተው እኛ ስንቀር መፅሀፉን ሮጣ አምጥታ ሰጠቺኝ።
ሰማያዊ የሽፋን ገፅ በቢጫ ፊደላት ርዕስ ያለው መፅሀፍ ነው። መቸገሬ ነው እንግዲ። እኔም ስገባ ከሰቀልኩት ከኮቴ ኪስ ውስጥ የገዛሁላትን መፅሀፍ ሰጠኋት። ፊቷ ላይ የነበረው ያለማመን እና የደስታ ጥግ ደጋግመህ መፅሀፍ ግዛላት የሚል ምኞት አሳደረብኝ።
ሳብ አድርጌ ለጥቂት ሰከንዶች ካቀፍቋት በኋላ ሀሙስ እንገናኛለን ብያት እዛው ደርቃ በቆመችበት ወጣሁ ትኩረት ከመሳባችን በፊት።
... | 937 |
| 7 | እማዬን እንደዛ እልል ያስባላት ዜና ምን አይነት ዱብ እዳ እንደሆነብኝ የሚያውቅ አለ? በተለይ የኤሚ አኳኋን፣ ስብር አባባሉ አላስችል አለኝ።
ታሪክ ራሱንም እየደገመ መሰለኝ ከአመታት በፊት እንደሆንነው... በፀጥታ ተሸኛኝተን ቤት ስገባ እማዬና አባዬ ሲኳረፉ እንደሚሆኑት እሷም የምታነብበት ክፍል እሱም ንድፉን የሚሰራበት ክፍል ገብተው መሸገዋል።
ልነፋረቅባት አና ጋር ስሄድ ትራሷን አቅፋ እየተንከባለለች ነው። የሚጋባ ሳቅ እየሳቀች "ሊ ምን እንዳደረገ አታውቂም እሱም አያውቅም ይሄ ለኔ ምን ማለት እንደሆነ የሚያውቅ ሰው አለ?" አለች መፅሀፍ አቅፋ
"ምንድነው መፅሃፍ እያነበብሽ ነው?" አልኳት
የያዘችውን መፅሀፍ ቀና አድርጋ አሳየችኝ One Hundred Love Sonnets by Pablio Neruda ይላል
"መፅሀፍ ገዛልኝ እሱ ነው የሚገርምሽ?" ልቤን ማንጠልጠሏ ነው "ሌላ ምን አደረገልሽ?" ቢያንስ ገፀባህርይ አይደለም እንደዚህ የሚያስፈነጥዛት
"ደብዳቤ ፅፎልኛል። የምወደውን የpablo nerudaን መፅሀፍ መግዛቱ ሳያንስ በአማርኛ እኮ ነው ደብዳቤውን የፃፈው እዪው ቃላት አጣጣሉ ሲያምር የሰዓሊ እኮ ነው የሚመስለው"
"የኔም የኤሚም ፅሁፍ አያምርም" አልኳት ሳበሳጫት እሷ እቴ "የምወደው የግጥም መድብል ነው ስለግጥም ያለሽን አቋም ያስቀይርሽ ይሆናል" ብሎ ነው የፃፈው ብላ አነበበችልኝ። እንደዚህ እንዳስደሰታት ቢያውቅ ምናለበት
...
ኦዚያን
እቤት እንደገባ የእለቱን ዜናዎች ሲከፍት ሶስተኛ ግድያ መፈፀሙ የዜናዎቹን አውታሮች እንዳጨናነቀ አየ። ከግድያውም ከተገኘውም ደብዳቤ በላይ ትኩረቱን የያዘው የሟች የትውልድ ቦታ ነበር። ፔሊ
✍ናኒ
ይቀጥል የምትሉ ብቻ react እያደረጋችሁ
https://t.me/justhoughtsss | 3 |
| 8 | Sin texto... | 811 |
| 9 | ክፍል 11
ምናልባት
የሌሎቹን ባላውቅም እኔ ግን አድካሚ ቀን ነው የነበረኝ። እንደሌላ ቤተሰብ የውሸት የጓጓን አስመስለን "ውሎ እንዴት ነበር ታድያ" አንባባልም ምክንያቱም ሁላችንም ከስራ የዘለለ ህይወት የለንም
የአባዬን ማባርያ የሌለው ተጣጣፊ ኮንክሪት ወሬ ወይም አዲስ ገበያ ላይ ስለዋለ ቀለም ሊያ ስታወራ ስለማይገባን ይሰለቸናል። እማዬ ስለታካሚዎቿ ማውራት በህግ ትከለከላለች እኔ ደግሞ አንጀቱ ተዘርግፎ እግሩ ተቆርጦ ከማለት የዘለለ አስደሳች ውሎ ኖሮኝ አያውቅም።
ለዛ ነው ራት ስንበላ ብዙውን ጊዜ ምግብ ቤት ውስጥ ጠረጴዛ መጋራት እንዳለበት የማይተዋወቅ ሰው የምንሆነው
ይሄንና ምን እንደሆነ ባላውቅም ጭንቅላቴ ያንንም እያነሳ እየጣለ ጭንቅላቴ ይባትላል። አባ ዜናው ላይ ተመስጧል።
ቀና ስል ሊያና ፈገግ ብላ ጠቀሰቺኝ። የሆነ ነገር ስታቅድ ነው እንደዚህ የምትሆነው "ስሙማ" አለች እማን ከሀሳቧ አባን ከዜናው እያደናቀፈቻቸው
"እ" ስትል እማ
"ሰበር ዜና" የሚል ድምፅ የሁላችንንም ትኩረት ሰረቀው "ቆይ ቆይ አንዴ አዳምጡ" ብሎ አባ ድምፁን ጨመረው
"በሁለት ወር ውስጥ የተሰራው ከተማ የሚጠናቀቅ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታውቋል። ከፔሊ የመጣችሁ ሰዎች በፈቃደኝነት ወደዛ ሄዳችሁ መኖር የምትችሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።"
"እልልል" እማ አቀለጠችው "ተመስገን ከዚህ የተረገመ ከተማ እንደዚህ በቀላሉ ልንወጣ ነው እልልል"
ሊያና ፊቷ ገርጥቷል አባ ምንም ስሜት አይታይበትም እሺ እኔ ምን እንደዚህ ልቤን አራደው?
"ሊያ ምን ልትነግሪን ነበር?" አለ አባ ምንም እንዳልተፈጠረ
"እነእትዬ ትሬዛን ነገ ማታ ምሳ እንድንጠራቸው ነበር" አለች ድምጿ ፈዝዞ
"እንችላለን ምን ችግር አለው ስለጠራችን ውለታ የዋለችልን እንዳይመስላት እንጂ አብሮ ለመኖር የሚያስገድደን ነገር የለም ልንወጣ አይደለ" ደስታዋ በድምጿ በፊቷ ይንፀባረቃል።
እማ እዚህ መኖራችንን እንደዚህ ጠልታው ነበር?
...
ኤሞን
ሰዓቱ ለሁለት ሩብ ጉዳይ ይላል። ቆይ ለእራት ግበዣ ስንት ሰዓት መሄድ ነው ትክክል? አንድ ሰዓት ገና ላይዘጋጅ ይችላል ሶስት ሰዓት እንደመቅረት ይቆጠር ይሆናል።
ስለዚህ ሁለት ሰዓት ነው። በሩብ ደቂቃ ውስጥ ብንሄድ ትክክል ስለመሰለኝ ተዘጋጅቼ ጨርሻለሁ። "ይሄ ልጅ ይቆያል እንዴ? በጣም መሸ እኮ" አለች እማ እንደልማዷ እየተጨናነቀች
"እየደረስኩ ነው ብሏል አትጨናነቂ" አልኳትና ወደሳሎን ስሄድ እሱ ሲያንኳኳ ተገጣጠምን። ስከፍትለት
"አላመሸሁም አይደል? ጥሪ ኖሮ ማርፈድ ልክ አይደለም" እያለ እየተጣደፈ ወደክፍሉ ገባ
አቻኩሎ ደብቆ ሊያስገባው የፈለገውን መፅሐፍ አይቼበታለሁ። ተከትዬው ክፍሉ ስገባ ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦታል።
"እኔ እኮ አላምንም"አልኩት መፅሀፉን አገላብጬ እያየሁ
እንዳልሰማኝ ልብሱን ይቀይራል። "የከተማዋ ጫፍ ድረስ ሄደህ ገዛኸው?" ሌላ ቦታ ማግኘት አቅቶት የተወው መፅሃፍ ነው።
"ምን ችግር አለው?" ለክት ብቻ የሚያወጣትን ሽቶ ኮሌታው ላይ እየቀባ
"ለሊያ እህት ነው አይደል?" አልመለሰልኝም
"እንውጣ ልጆች" እማ ተጣራች
"ጨርሰናል መጣን" መብራቱን እላዬ ላይ አጥፍቶ ወጣ ያመለጠኝ መስሎት
...
ኪራኮስ
በሩን ስናንኳኳ "መጡ መጡ መጡ" የሚል ድምፅ ከውስጥ ሰማሁ። የከፈተችው አናን የምትመስል ሴት ናት እህቷ ናት ማለት ነው። እየሮጠች መጥታ እንደከፈተች ያስታውቃል።
"እንኳን ደህና መጣችሁ" አለች ኤሚ በአይኖቿ እያቀፈችው። ደስ ሲሉ
ስንገባ አና እና እናቷ ምግብ እያቀራረቡ ነበር። እንደነገሩ ያዝያዘችው ፀጉሯ ታጥፎ ራሱ አለሁ ይላል። ከፀጉር ማስያዣው ጥቂት ወጥቶ ጀርባዋ ላይ ተኝቷል። ሁሉም ሰላም ሲባባል ውስጥ ነበረች። አባታቸው ኑ ተቀመጡ ብሎ ገና ከመግባታችን የምግብ ጠረጴዛው ጋር ወሰደን።
አባትየውና እና እናትየው ትዕዩ ተቀመጡ። ኤሚና ሊያና ደግሞ በግራ በኩል ተቀመጡ ከኤሚ አጠገብ ማሚ ተቀመጠች ከአባታቸው አጠገብ መሆኑ ነው።
ኦዚያን እናታቸው በስተቀኝ ተቀምጦ ወሬ ጀምረዋል። እኛ አልሰማ የምንለውን ወሬ ከእሷ ጋር ሲሆን እኩል በእኩል ሲያወሩ ደስ ይለኛል። ሁሉም ሰው እንደራሱ ሆኖ የሚያወራው ሰው ይፈልጋል አይደል?
ኤሚና ሊያና ምንም እንደማይተዋወቅ ሰው የሚያደርጉት ጥረት ያስቀኛል። አይነስውር የሚያየው መሳሳብ በመላሀቸው ኖሮ ለደቂቃ መነጣጠል ሳይፈልጉ ወላጆቻቸው እንዳያውቁባቸው የሚያደርጉት ጥረት ረብ የለሽ ይሆንብኛል። የፍቅራቸው አምላክ አይናቸውን ጋርዶላቸው እንጂ አልቆላቸው ነበር።
አቀራርባ ስትጨርስ እና ስትመጣ የነበረው ቦታ በኔና በኦዚ መሀል ያለው ወንበር ብቻ ነበር። አጋጣሚ መሆን አለበት (አይደል?)
ስትቀመጥ ለስላሳ ሽቶዋ አወደኝ። የግጥም ምሽቱ ቀን የተቀባችው ነው። በትግል ከጭንቅላቴ ያወጣሁትን አደሰችልኝ።
"በሁለት ወር ውስጥ መውጣት ትችላላችሁ አሉ ደግሞ አይደል" እማ ፀጥታውን አፈረሰችው
ጋሽ ኤስሮም መልስ እየመለሰላት ነው። ግዴታ እንዳልሆነና መሄድ ከፈለጉ ብቻ እንደሚሄዱ እየነገራት ነው
ከዛ በኋላ ያሉትን አልሰማሁም መብረቅ እንደወረደበት ደርቄ ቀረሁ። ሁለት ወር? ስምንት ሀሙስ? ከዛ በኋላ እንደልማዴ ብቻዬን ልሄድ ነው።
ፊቴ ላይም ድንጋጤዬ ታይቷል መሰል "አባ ምነው አመመህ እንዴ?" ስትል ማሚ "ኧረ ትንሽ ብርድ አግኝቶኛል መሰለኝ ውጋት ይዞኝ ነው አልኳት ደህናውን ወገቤን ደግፌ
"አና እኮ ነርስ ናት እሷን ጠይቃት መድሀኒቱን" አለ አባታቸው ኤስሮም "አባ ደሞ ወጌሻ መሰልኩህ እንዴ"
ስትለው በሳቅ ተቀበልናት።
የእሷ ወንበር ላይ ስደገፍ ትከሻዋን ዳበስ አድርጌው አለፍኩ ፈገግ ያለችበትን ከንፈሯን ነክሳ ስታስቆመው አይቻታለሁ። እጄን እዛው ተውኩት ትከሻዋ ጋር ጉንጮቿ እየቀሉ ነው።
"ሌላ ምን አዲስ ነገር አለ?" ስትለው የእነአና እናት እትዬ ማሊካ "ምንም የለም ያው የከተማዋ ነባር ነዋሪዎች ላይ ብቻ ስለሆነ እየተፈፀመ ያለው የተገመተው አዲስ ከሰፈሩት ሰዎች መሀል ሊሆን ይችላል እየተባለ ነው" አላት ቆይ ይሄ ልጅ ያለዚህም ጉዳይ ስራ የለውም እንዴ?
"ለዛ ነው አይደል በየመንገዱ የሚገላምጠኝ ሰው በዝቷል" አለች አና ቀጥላም እህቷ ከሌሎች ጎረቤቶች ስለገጠማት ዘለፋ ነገረችን
ማን አባቱ ነው የሚገላምጣት
"መፅሀፉን ገዝቼልሀለው እሰጥሀለው ስትወጡ" አለች ለሌላ ለማንም በማይሰማ ድምፅ
"ደስ ይለኛል"
ከዛ በኋላ ምሽቱ ያለቃላት ልውውጥ ከእሷ ጋር ስናወራ ቀና ብላ ባየቺኝ ቁጥር ልቤ ብትንትኑ እየወጣ፣
ማሚ እና ጋሽ ኤስሮም ስለሆነ አዲስ ተክል ቅጠል አበቃቀል ሲያወሩ ኤሚና ሊያ በዝምታ ሲቆዝሙ እናታቸውና ኦዚ ስለግድያ አይነቶች ሲዘረዝሩ አምሽተን
"ሰዓቱ እንዴት ሄዷል ባካችሁ" ስትል እናታቸው ሂዱ ማለቷ እንደሆነ ገብቶን ተነሳን። ልንወጣ ስንል ጥንድ ጥንድ ሆነው ሲያወሩ በነበሩበት አኳኋን ወጡ።
ልብሴን ጎተት አድርጋ ስታስቀረኝ ለመፅሀፉ መሆኑ ገብቶኝ ሌሎቹ ወጥተው እኛ ስንቀር መፅሀፉን ሮጣ አምጥታ ሰጠቺኝ።
ሰማያዊ የሽፋን ገፅ በቢጫ ፊደላት ርዕስ ያለው መፅሀፍ ነው። መቸገሬ ነው እንግዲ። እኔም ስገባ ከሰቀልኩት ከኮቴ ኪስ ውስጥ የገዛሁላትን መፅሀፍ ሰጠኋት። ፊቷ ላይ የነበረው ያለማመን እና የደስታ ጥግ ደጋግመህ መፅሀፍ ግዛላት የሚል ምኞት አሳደረብኝ።
ሳብ አድርጌ ለጥቂት ሰከንዶች ካቀፍቋት በኋላ ሀሙስ እንገናኛለን ብያት እዛው ደርቃ በቆመችበት ወጣሁ ትኩረት ከመሳባችን በፊት።
...
ሊያና | 21 |
| 10 | 7088fdf3-11ca-4cfa-b2a5-5631cf6a4952.mp3 | 865 |
| 11 | @Jaymasangula_bot | info | 1 |
| 12 | ስለካራሞን ብዙ የማወራው ስላለኝ አንድ ቀን በሰፊው እነግራችኋለሁ። ለዛሬ ግን በጥቂቱ
ካራሞን ከዴርቶጋዳ በኋላ እጅግ የወደድኩት የአማርኛ fantasy ሆኖ ተገኝቷል። የሚሰለች አንድ መስመር ባለመኖሩ በአንድ ቀን ነው ፉት ያደረግኩት። ከcharacter development ጀምሮ እስከ world building እንከን የለሽ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። plot twist ለምትወዱ ሰዎች ትክክለኛው መፅሀፍ ነው
እና ገዝታችሁ አንብቡት በጣም enjoy እንደምታደርጉት አልጠራጠርም ያነበባችሁት ደግሞ ቅዳሜ ጃፋር ጋር ሄዳችሁ መፅሀፋችሁን አስፈርሙ | 1 157 |
| 13 | የፊታችን ቅዳሜ የመጽሐፍ ፊርማ ስነስርአት !
በጃዕፈር መጻሕፍት መደብር !
" ካራሞን " | 989 |
| 14 | እንበልና...
ነገ ናኒ የመጀመሪያ መፅሀፏ ታትሞ ጃፋር እየተሸጠ ነው ብትባሉ ስንቶቻችሁ ትገዛላችሁ? | 1 305 |
| 15 | ክፍል 10
ኤስሮም
በሩ ሲንኳኳ በባዶ ሳሎኑ ተስተጋብቶ ተጋኖ አስደነገጠኝ። የኔ ነገር ይኸው ነው አንድ ስራ ከጀመርኩ መመለሻ የለኝም። ስነሳ ወገቤ ሲንቋቋ ነው ብዙ እንደተቀመጥኩ የታወቀኝ።
ስከፍት ትሬዛ ትንሽዬ አበባ ከነማስቀመጫው ይዛ ቆማለች። አንዴ እሷን አንዴ አበባውን አፈራርቄ እያየሁ "እንዴት አደርሽ?" አልኳት
"እንዴት አደርሽ? ቀኑ ተጋምሷል እኮ! ምሳ አልበላህም ማለት ነው?" አለች በፈገግታ ታጅባ
ፀጉሯ ላይ የተሰመሩት ነጫጭ መስመሮች እና ፊቷን ከፈገግታዋ በኋላ የሚፈጠሩት ሽብሽቦች እንደሌላው ትልቅ ሰው አያጎሳቁላትም። ምናልባት ወጣት እያለች የነበራት ውበት እድሜ ቢታገለውም ሊያሸነው አልቻለም
ደግሞ የያዘችው አበባ ማማሩ
"አይገርምሽም! ሰዓቱን ራሱ አላየሁትም ነበር" አልኳት እያዛጋሁ
"ምነው እቤት ማንም የለም እንዴ?" ወደ ቤት አንገቷን እያማተረች
"ያው ስራ ሄደው ነው። ብቻዬን ነበርኩ" አልኳት
"እኔም ቡና የሚያጣጣኝ አጥቼ ደብሮኝ ነበር። ና እስኪ እንጫወታለን። የተከልካቸው አልፀድቅ እንዳሉህ ስላየሁ ነው። ይሄኛው በደንብ ይይዛል ሞኝ ነው" ብላ አበባውን ሰጠቺኝ
"እንዴት እንደማመሰግንሽ አላውቅም" አበባው አድጎ ዙርያውን ሲያለብሰው በአይነህሊናዬ እየሳልኩ
"የምን ምስጋና አመጣህብኝ ና ይልቅ" ብላኝ ሄደች።
ያመጣችልኝን አበባ በጥንቃቄ አስቀምጬ ቤቷ ስሄድ እጣኑ ቀድሞ ተቀበለኝ። ረከቦቱ ተዘርግቶ እንኳን ደህና መጣችሁ ይላል። ከረከቦቱ ፈትለፊት የተቀመጠው ቢጫ ኩኪስ የረሳሁትን ርሀቤን ቀሰቀሰው
"ጠረጴዛው ይሻሀል ወይስ እዛው እንብላ?" ብላ ወደተቀመጥኩበት ሶፋ እየጠቆመች
ቶሎ አልመለስኩላትም ጎረቤት እንደዚህ ነው ማለት ነው እያልኩ እየተገረምኩ ነበር
...
አናቤል
"ለቅሶ መሰለሽ እንዴ የሚወስድሽ ምንድነው እንደዚህ መጨላለም?" አለች ሊያ ፊልሟን አቋርጣ
ለሶስተኛ ጊዜ የቀየርኩትን ልብስ እያየሁ ተበሳጨሁ። "ወይ በቃ ልቅር? አልፈልግም ልበለው?" አልኳት። ከዚህ በላይ መጓጓትም ትኩረት መስጠትም አልፈልግም።
"እንዴዴ ያምሻል እንዴ? እኔ እኮ ፈካ ያለ ቀለል ያለ ነገር ልበሺ አልኩ እንጂ ቅሪ አልኩ? ቆይ መጣሁ" ብላ ወደቁምሳጥኔ ሄደች።
"በጣም የፈካ ነገር አልፈልግም በጣም የጓጓሁ እንዲመስለው አልፈልግም" አልኳት መስታወቱ ፊት ቆሜ የፀጉሬን አኳኋን እየመረጥኩ
"ግን እኮ ጓጉተሻል" አለች ጮክ ብላ "ዝም በይ"
አስታዋሽ ያስፈልገኛል እንዴ? ከሶስት ቀን በፊት እነሱ ቤት ለምሳ ተጠርተን ይዤሽ እሄዳለሁ ካለኝ ቀን ጀምሮ ሌላ ስለምን ማሰብ ችያለሁ?
ፈዛዛ ሮዝ ቀሚሷን ይዛ መጣችና አጠገቤ ቆመች "አርፈሽ ይሄንን ልበሺ" አለች አስታቅፋኝ ወደፊልሟ ተመለሰች
"ግን እኮ እጁ ባዶ ነው ስንመለስ ቢበርደኝስ? ጃኬቱን እንዲሰጠኝ እያስገደድኩት ቢመስልብኝስ?" አልኳት ቡዳ የሆነች ልጅ ቀሚሱን እንዴት እንደምወደውና እንደሚያሳምረኝ ታውቃለች
"እና ካፖርት ደርቢበትና ትንሽ ሮማንቲክ መሆኑን የሚያሳይበትን መንገድ አሳጪው" አለች እውነትም እድል መስጠት ያስፈልጋል እኮ!
በሩ ሲንኳኳ ወንዶቹ ቢያዩት ኧረ ንፁህ ፊቷን ናት የሚሉትን ሜካፕ ሊያ በስሱ እየቀባባቺኝ ነበር። "በቃ በቃሽ መጥቷል" አልኳት እየተወራጨሁ
"ቆይ ትንሽ ያንኳኳ በአንዴማ ይዞሽ አይሄድም አንድ እህቴን" አለች ፊቴን እንደሸራዋ እየተራቀቀችበት
"ሊያገባኝ መሰለሽ እንዴ date እንኳን እንዳልሆነ ታውቂያለሽ" አልኳት ውስጤ የሚፈልገው ሌላ ቢሆንም
"አንድ ሳይባል ሁለት አይባልም በይ ሂጂ ብዙ መዝረክረክሽን አታሳዪው አደራ እንዳታዋርጂኝ" ስትል ወደበሩ መሮጥ ጀምሬ ነበር
ትንፋሼን አረጋግቼ በሩን ለመክፈት ደቂቃ አልፈጀብኝም።ሳየው ደነገጥኩ። ወጥ ጥይምናው የጎደጎዱ አይኖቹ ዛሬ እንደተከረከመ የሚያስታውቅ ጠንካራ ፀጉሩ ብቻ ብፅፈው ብዬ የምመኘው ሰው መሰለኝ።
እሱም ዝም ብሎ እያጤነኝ ነው አይኖቹ ውስጥ አድናቆት አለ። ግን የአድናቆት ቃል አልወጣውም። ጫማዬን ሲያየው ትንሽ ታኮ አለው።
"በመኪና እንሂድ?" አለኝ እያስፈቀደኝም እየወሰነም በሚመስል ድምፅ "ሩቅ ነው እንዴ?" አልኩት የምሄድበትን ሳላውቅ ያውም በቅጡ ከማላውቀው ሰው ጋር ጉድ እኮ ነው!
"ኧረ ብዙ ሩቅ አይደለም ጫማሽ ምቾት እንዳይነሳሽ ብዬ ነው ቆይ መጣሁ" ብሎ መኪናውን አመጣውና ገባሁ። አምስት ደቂቃ በማትፈጀው ጉዞ በመንገዳችን ስላየናቸው ጥቂት መፅሀፍት ቤቶች እየነገረኝ ደረስን።
ከላዩ ቢሮዎች ያሉበት ህንፃ ወለል ላይ በቀን ኮፊ ሀውስ እንደሆነና ሀሙስ ሀሙስ ማታ ግን የግጥም ምሽቱ እንደሚዘጋጅ ነግሮኝ ገባን። ከመድረኩ ከሚመጣው ብርሀን ውጪ ሌላ ብርሀን ባለመኖሩ በጨለማ ከጀርባ ያሉት ወንበሮች ላይ ተቀመጥን።
ሶስት ሰዎች ተመዝግበው በተራ ካቀረቡ በኋላ ቀጣዬ ሌሎች ሶስት አቅራቢዎች የሚቀጥሉበት እንደሆነ ነገረኝ።
ልታቀርብ ቀድማ የወጣችው ፀጉሯን ልሙጥ አድርጋ አስይዛ ሱፍ የሚያስንቅ ኮትና ሱሪ የለበሰች ፅድት ያለች ሴት ናት። መድረኩ ላይ ወጥታ ቀጭኑ መብራት እሷ ላይ ብቻ ሲያበራ
"ከስራ ቀጥታ ስለመጣሁ ነው ይቅር በሉኝ formal መመሰል ፈልጌ አይደለም" አለች በትንሹ ፈገግ ብላ። ቤቱ በስላሳ ጭብጨባ ይቅር መባሏን ሲያበስራት ጀመረች
ስ.ም.ጥ
ት.ሙ.ክ
ታውቃላችሁ
ተረከዝ ውስጥ
እንደሚገኝ ልባችሁ
ታውቃላችሁ
ጫማ ሲመቻችሁ
በእያንዳንዱ እርምጃችሁ
ደስ እንደሚላችሁ
ክ.ት.ት
ም.ች.ት
ከዛ ሲቆረቁራችሁ
አንድ ጠጠር
ሰላም ስትነሳችሁ
አስባችሁታል
ጠጠሯ ስትጠፋችሁ
ቁ.ር.ቁ.ር
ቡ.ር.ቡ.ር
ሲጠዘጥዛችሁ
እስከጉልበታችሁ
ሲሰማችሁ
እስከወገባችሁ
ጥ.ዝ.ጥ.ዝ
ድ.ን.ዝ.ዝ
ገበያ ሙሉ ስትሸጡ
ቶርሽን ዘርግታችሁ
አዲዳስ አንጥፋችሁ
አያቴ ስትለምነኝ
የት ነበራችሁ
ኧረ ቁርቋሬው
የምታደርጋቸው
አጠነካከሩ
ሶሉ መርገጫቸው
ስትለምነኝ
እሺ ስላት
ስትለምነኝ
ሳልገዛላት
እንደቆረቆራት
አንድ ቀን ሳይመቻት
ሞተች!
ሰማችሁ?! ያልኩትን
ሞተች
ገበያው በጫማ ቢሞላ
ምን ያደርግልኛል
ፀ.ፀ.ት
ይወርሰኛል
ብ.ሽ.ቀ.ት
ያንቀኛል
ሰው እንዴት ጫማ
ይቸግረዋል?
ኧረ ኤድያ!
ብላ ከመድረክ ወረደች ጭብጨባው ቀለጠ።እኔ አያቷ በአይነህሊናዬ ተስለው ኖሮ አይኔ እንባ አቅርሮ ነበር። "ልታለቅሺ እንዳይሆን" አለኝ ከሰዉ ጋር እያጨበጨበ "ባለቅስስ?! አቀራረቧ ሴትየዋን እንድስላቸው አስገደደኛ" አልኩት ያልወረደ እንባዬን እንዳይወርድ እየታገልኩ
ሽሽ...ሽሽ የሚል ድምፅ እየተሰማንም እየተንሾካሾክን ጨርሰን ወጣን።
"የእንባ ጫፍ እስክትደርሺ ውስጥሽ ገብቶ enjoy አላደረግኩትም አትይኝም መቼም" አለኝ ወደመኪናው እየሄድን "ውይ በጣም ነው የወደድኩት በየሳምንቱ ሀሙስ ሌላ ፕሮገራም አልይዝም" የመኪናውን በር ከፍቶ አስገብቶኝ ሲመለስ
"የረባ ወግ ግን ስላልሰማሁ ቆንጆ የወግ መፅሀፍ እሰጥሀለው" አልኩት ቀበቶዬን እየታጠቅኩ "እስኪ የኖረ ሀሳቤን ታስቀይሪኝ እንደሆነ እናያለን" አለ ካቆመበት ጥግ ወደ ዋናው አስፓልት በጥንቃቄ እየነዳ
"እናያለን"
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss | 1 365 |
| 16 | Sin texto... | 1 175 |
| 17 | My All Mariah Carey.mp3 | 1 157 |
| 18 | Sin texto... | 1 299 |
| 19 | Sin texto... | 1 |
| 20 | እናንተዬ ትብብራችሁ ያስፈልገኛል
ተመሳሳይ ዘፈኖችን መስማት ሰለቸኝና እስኪ በጣም የምትወዷቸውን ዘፈኖች ንገሩኝ | 1 191 |
