Thoughts
ቸል የተባሉ እሳቤዎች፥ ያልታዩ እይታዎች የሚፈነጩበት ቤት ነው ፥ እናንተስ ጎራ አትሉም? comment for the writer : @Exquisiteperfume discussion group https://t.me/+uDtKY02cOho2NGZk Tiktok: https://www.tiktok.com/@the_author_nani?_t=8pGCAO5NksY&_r=1 Since:Dec-10-2022
Show more📈 Analytical overview of Telegram channel Thoughts
Channel Thoughts (@justhoughtsss) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 11 122 subscribers, ranking 8 111 in the Religion & Spirituality category and 3 017 in the Ethiopia region.
📊 Audience metrics and dynamics
Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 122 subscribers.
According to the latest data from 06 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 156 over the last 30 days and by 50 over the last 24 hours, overall reach remains high.
- Verification status: Not verified
- Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 20.01%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.03% reactions from the total number of subscribers.
- Post reach: On average, each post receives 2 225 views. Within the first day, a publication typically gains 1 004 views.
- Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 29.
📝 Description and content policy
The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
“ቸል የተባሉ እሳቤዎች፥ ያልታዩ እይታዎች የሚፈነጩበት ቤት ነው ፥ እናንተስ ጎራ አትሉም?
comment for the writer : @Exquisiteperfume
discussion group https://t.me/+uDtKY02cOho2NGZk
Tiktok: https://www.tiktok.com/@the_author_nani?_t=8pGCAO5NksY&_r=1
Since:Dec-10-2022”
Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 07 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.
Data loading in progress...
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 07 September | 0 | |||
| 06 September | +50 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | +16 | |||
| 03 September | +8 | |||
| 02 September | +1 | |||
| 01 September | +11 |
| 2 | ይበቃሀል ነፃ ልውጣ እስኪ ደግሜ ልውደድ ደግሜ ልሽኮርመም ደግሜ በናፍቆት ልሰቃይ
ደግሜ ልሰበር ብቻ ተወኝ ሄደህም ሁለት አመት አልፎትም በግዞት አታኑረኝ ይበቃሀል" ብዬ ጨረስኩ በደማቅ ጭብጨባ ተቀበሉኝ
ወደቦታዬ ስመለስ ኪራኮስ ቦታው ላይ የለም። ከማላውቃቸው ሰዎች ጭብጨባ በላይ የእሱን አስተያየት ይሆናል የበለጠ የፈለኩት። "ኤጭ የት ሄዶ ነው" ብዬ ወደመድረኩ ስዞር ማይኩን እያስተካከለ ነው።
እሱም ሊያቀርብ ነው?
✍ናኒ
react በማድረግ የዜግነት ግዴታችንን እንወጣ😁
https://t.me/justhoughtsss | 850 |
| 3 | ክፍል 13
ምናልባት
ሊያና
የሚካኤል በላይነህ ዘፈን ከጣራ በላይ ተከፍቷል። ይሄ ነገር ስር እየሰደደ ነው እያልኩ ሲሊፐሬን ሰክቼ ወደክፍሏ ስሄድ መታጠቢያ ቤቱ በር ላይ ባዶ ባልዲ ተቀምጧል።
ደስ አላለኝም
ክፍሏ ስገባ
"ተፈጥራ እንጂ ይወደድሽ ተብላ
ስሜቴን ምን ለየው ከሌላ ከሌላ
መላመድ አልለው ገና በሳምንቱ
አይኖቿን መናፈቅ ምንድነው ምክንያቱ"
ጮሀ እየዘፈነች ኩሏን ታስተካክላች። ለመደበቅ የምትፈልገውን ቅርጿን የሚያጎላ ቀሚስ ለብሳለች። "እስኪ ስትወራጪ ኩሉ አይንሽ ውስጥ እንዳይገባ" አልኳት እሷ አልጋ ውስጥ ገብቼ እየተጠቀለልኩ
"ፀጉሬን ወደ ላይ ላድርገው ወደ ታች" የኔ ሀሳብ ምንም ቢሆን ስለማትሰማኝ ተውኳት። በጥቂቱ ዘረክረክ አድርጋ ወደ ላይ አስያዘችው። ምናልባት የሰው ውበት በደስታው ልክ ነው መሰለኝ ምክንያቱም አይኖቿ እያበሩ ነው።
ራሷን መስታወት ውስጥ እያየች ፈገግ ብላ ትሽኮረመማለች። ጉድ እኮ ነው። "ዛሬ ባትሄጂስ?!" አልኳት
"እየቀለድሽ ነው? እንደዚህ አምሮብኝ የሚያውቅም አይመሰለኝም እንደባለፈው ዝም ካለ ተጋደልን" ሶስተኛ ሽቶዋን መነስነስ ጀመረች
"እውነቴን ነው ባዶ ባልዲ አይቻለው። ሄደሽ ከሚደብርሽ ወይ ደስ የማይል ነገር ከሚፈጠር ዛሬ አይመቸኝም በዪው እና ፊልም እንይ" ከልመና ባልተናነሰ ድምፅ
"ጀመርሽ ደግሞ ይሄን... ምንድነው የሚባለው? ባዕድ አምልኮ ምልኪ ምናምን እኔ እንደማላምንበት ታውቂያለሽ። Good Hair Day Good Day ሲባል አልሰማሽም? ምንም አይፈጠርም ባክሽ በይ ቻው" ብላ አየር ላይ ስማኝ ወጣች።
ኪራኮስ
ህፃን ሆኜ ልብስ ሲገዛልኝ እና ለበዓል ብቻ ነው የምትለብሰው ስባል እንደምሆነው ከአንድ ሰዓት በፊት ነው ለባብሼ የተቀመጥኩት
አስራ አንድ ሰዓት ሊሆን አስር ደቂቃ ሲቀረው አልቻልኩም ወጥቼ መንጎራደድ ጀመርኩ። አምስት ደቂቃ ሲቀረው በሯ ላይ ደርሻለሁ። እስከ ስልሳ አምስት ጊዜም መቁጠር አማረኝ። ያለችውን ትበል ብዬ አንኳኳሁ
ወዲያው ከፈተች
በሩ ጋር ነበረች?
የመጀመሪያ የግጥም ምሽቱ ጋር ከሄድንበትም ባለፈው እነኤሚ ያገናኙን ቀን ከነበረውም በላይ አምሮባታል። የመጀመሪያው የግጥም ምሽቱ ቀን ጥርጣሬ ነበረባት የምን እንደሆነ ባላውቅም
ያገናኙን ቀን ደግሞ እኔን ማግኘት ያልጠበቀችው ነገር ስለነበር ከለበሰችው በላይ ድንጋጤዋ ነበር ጎልቶ የሚታየው
ዛሬ ግን ተለይታለች። አይኗ ዙርያ የተቀባችው ነገር የበለጠ አደገኛ አድርጓታል ፈገግታዋ "እስኪ ወንድ ከሆንክ" የሚል መልዕክት አለው
ቃላቶቹ እየደረሱ ጉሮሮዬ ጋር ይወተፋሉ "wow...አምሮብሻል" ማለት ብቻ ነበር የቻልኩት
ኤድያ
አናቤል
ስንደርስ ብዙ ሰው አልነበረም የነበረው ለዛ ሁለተኛው መደዳ ጋር ሄደን ተቀመጥን። ሰዎች መምጣት ሲጀምሩ እና መሙላት ሲጀምር "መጣሁ" ብሎ አንሻካሾከ እና ተነስቶ ሄደ።
የዛሬ አቅራቢዎች መጥታችሁ መመዝገብ ትችላላችሁ ተብሎ ተመዘግቤ ስመለስም አልመጣም ነበር። ሁለተኛ አቅራቢ መሆኔን ነግረውኝ እስኪጀመር የማቀርበውን ፅሀፍ ደግሜ ማንበብ ጀመርኩ።
የመጀመሪያዋ አቅራቢ መድረኩ ላይ ስትወጣ እሱም ተመልሶ መጥቶ አጠገቤ ተቀመጠ። "የት ሄደህ ነው?" አልኩት በሹክሹክታ ሁለት ሰዎች ገላመጡን "በኋላ ቆይ" ብሎ ትኩረቱን ወደምታቀርበው ሴት አደረገ
ከፍሪዝ ወደ መንጨባረር ያደላ አጭር ፀጉሯ ከቀዩ መብራት ጋር ቡኒ ሆኖ ቀድሞ ቀልብ ይይዛል። ደማቅ ቡኒ ሙሉ ከንፈሯ ከዛ በኋላ የጎደጎደው አይኗ ያሰምጣል። መድረኩ ላይ ስትወጣ ስታነክስ አይቻት ዞር ብዬ ሳየው በራሱ ንቅናቄ አረጋገጠልኝ።
ገና ቁጭ ከማለቷ በለበሰችው ነጭ ሸሚዝ ከንፈሯን ጠረገችው። ግና ተጋባን። ሸሚዙን አዙራ ስታሳየን የሊፕስቲክ መስመር የለውም። የተኳለ አይኗን ጠረገችው ሸሚዙ ነጭነቱን አለቀቀም።
"ምንም አልተቀባሁም። እንዳያችሁት ከንፈሬ ቡኒ ነው አይኔም የተኳለ ነው የሚመስለው እሺ እኔ ምን ላድርግ? ፀጉሬ ጠዋት ነው የታጠበው ቅባት እንኳን አላየውም" ብላ በእጇ ስትበትነው የበለጠ ተንጨባረረ ዳሩ ከውበቷ የቀነሰው አንድ ነገር አለመኖሩ ነው።
"ጉራሽን ልትነዢ ነው የመጣሽው የሚል አይጠፋም። እንደውም በተቃራኒው እንዴት ጦስ እንደሆነብኝ ልነግራችሁ ነው። በየሄድኩበት መስሪያቤት እዚህ ያደረግኩትን እዛም ማድረግ አለብኝ ካልሆነማ ሰራተኞቻቸው ልታስባርረን መጣች ይሉኛላ ሆ" ስትል የተወሰነ ሰው ሳቀ
"እውነቴን እኮ ነው እንዴ ሀሳቤን እንኳን የሚሰማኝ የለም ከተሰማሁም 'ስትስለመለሚ ድሮስ ላይሰሙሽ ነው' የሚል ሽንቆጣ አይቀርልኝም። እሺ እኔ ከስንት ወንድ ሚስት ጋር ነው መቀያየም ያለብኝ? ከዛስ አትሉም
ከዛስ?
ከዛማ የሆነች አደጋ ገጥማኝ ማነከስ ጀመርኩ። ብዙ አትዘኑ ይሄ ጥሩ ዜና ነው። ይቀኑብኝ የነበረበት ፍፅምና ሲጠፋ ሴቶቹም ያዝኑልኝ ጀመር። ወንዶቹም ለምን ብለው አንካሳ ሴት ይወዳሉ። አሁን ያወሩት የነበረው ውበት ጎድሎ ተገኘ። ስሜ ጎዶሎ ሆነ የማወራው መሰማት ጀመረ። አይገርምም?
ሁሉም መጥፎ ነገር እኮ መጥፎ አይደለም ቢያንስ አሁን የአካል ጉዳተኞች ማህበር ውስጥ ያሉት ሰዎች እንደአንዳቸው ይቆጥሩኛል። አይገርምም?
ብላ እያነከሰች ወረደች። አንድ ጭብጨባ አልተሰማም። ሁሉም ፀጥ አለ የሆነ አይነት ጥያቄ ውስጥ የከተተችን አይነት ነገር ሆነ። ትዝ ሲለኝ ለካ ቀጣይ የማቀርበው እኔ ነኝ።
ልቤ አታሞ መደለቅም ጀመረ እጄንም ላብ አራሰው። ምነው በቀረብኝ የሚለው የጭንቅላቴ ክፍል መጮህ ጀመረ። እንደምንም መድረኩ ላይ ወጥቼ መሀል ላይ የተሰየመው ሶፋ ላይ ስቀመጥ ህልም ህልም እየመሰለኝ ነበር።
አስተባባሪው ማይኩን ሰጥቶኝ ሲወርድ እና ቀዩ መብራት አይኔን ሲወጋው ነው ወደቀልቤ የተመለስኩት። ታዳሚው በጨለማ ተውጦ ለባዶ አዳራሽ የማወራ መሰለኝ ፍርሀቴ ልቅቅ ሲያደርገኝ ይታወቀኛል። ግን ማይኩ በላቤ ረጥቦ ይንሸራተታል።
ማንም የለም ምንም የሚያስፈራ ነገር የለም ለተወሰነ ጊዜ ለራሴ አነበነብኩ።
"ይበቃሀል" ነው ርዕሱ ስል በተወሰነ ጭብጨባ አበረታቱኝ። ብቻዬን አይደለሁም ማለት ነው ግን ቢያንስ ይሰሙኛል ብዬ ቀጠልኩ።
"ሁለት አመት ከአንድ ወር ከሰባት ቀን በፊት ከሰዓት በኋላ እንደውም አመሻሹ ላይ፥ ከተገናኘን ሶስተኛ አመታችንን ከጠየከኝ ሁለት አመት ከስድስት ወራችንን እሺ ካልኩህ እና አብረን ከሆንን ሁለት አመታችንን ልናከብር እየተኳኳልኩ ነበር
የሚገርምህ ጭላጭ የቀረውን የእማዬን ሽቶ ሳይቀር ተቀብቼ ነበር። የማልወደውን ጥፍር እንኳን አስተክዬ ነበር። ለሙሽራ የማይተናነስ ሜካፕ ተቀብቼ ጨርሼ ነበር። ኪሳራ! ከጊዜዬም ከእድሜዬም ከቀልቤም በላይ የሜካፑ መባከን
ሜካፕ ስንት እንደሆነ ታውቃለህ? ኪሳራ"
የተወሰኑ ሳቆች አጀቡኝ
"ለነገሩ የሜካፕ እውቀት እንደሌለህ ለማወቅ እኮ የወሸምካት ሴት የላከችልኝ ፎቶ በቂ ማስረጃዬ ነው። ሰማያዊ ሻዶ ከምትቀባ ሴት ጋር? ቱ ማፈሪያ እኮ ነህ።
"ሁለት አመት ከአንድ ወር ከሰባት ቀን በፊት ምን እንደሰረቅክ ታውቃለህ? ነፃነቴን በራስ መተማመኔን እና ብዙ ብነግርህ የማይገቡህን ነገሮች። ደግሜ መውደድ የማልችል ደካማ የሆንኩ እስኪመስለኝ ራሴን እንድጥራጠር አደረግከኝ።
አሁን ግን ይበቃሀል። እንደጎዶሎ ሴት ኖርኩ። ወሬ አይደበቅ መቼስ ከእሷ ጋርም እንዳልቆየህ አውቃለሁ ግን ምን ዋጋ አለው። የሆነው ሆኗል ከሆነም ሁለት አመት አልፎታል። | 803 |
| 4 | No text... | 768 |
| 5 | Mikael_Belayneh_ሚካኤል_በላይነህ_Liwedat_New_Mesel_ልወዳት_ነው_መሰል.mp3 | 764 |
| 6 | ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት። የዝናቡ ውሽንፍር የጥንታዊውን ሕንፃ መስኮቶች ያንቀጠቀጣቸዋል። መብራቱ ድንገት ጠፍቶ ሙሉ በሙሉ በጨለማ ስንዋጥ የእርሷ አየር አወጣጥ ብቻ ነበር በክፍሉ ውስጥ የሚሰማው።
እጄ ላይ ያለው የቆየ ማስታወሻ ደብተር በደም የተበከሉ ገጾች አሉት። ደብተሩን ያገኘሁት ከሃያ ዓመታት በፊት በድንገት ከተሰወረው ወንድሜ አልጋ ስር ነበር። ገጹ ላይ ከተጻፉት አጫጭር ዓረፍተ ነገሮች መካከል አንዱ መስመር የልብ ምቴን አፈጠነው
"ይህንን ካነበብክ እኔ በሕይወት የለሁም። ነገር ግን በሩን ከከፈትከው... እርሷን ታገኛታለህ። እባክህን ወደ ምድር ቤቱ እንዳትወርድ!"
ከእግሬ ስር ያለው እንጨት የወለል ሳህን "ክራክ..." ብሎ ሲሰነጠቅ ድንገት ከጀርባዬ የሚቃጠል የእንፋሎት ትንፋሽ ተሰማኝ። ዞሬ ለማየት ስቃዥ፣ የቀዝቃዛ እጅ ጣቶች ከአንገቴ በስተጀርባ በዝግታ ይዳብሱኝ ጀመር...
ሙሉውን ታሪክ ለማግኘት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/addlist/wj1FH6fJLSExZmM0 | 293 |
| 7 | የክፍል 13 ማጀቢያ አይደለም
ስሙት ብዬ ነው😁 | 959 |
| 8 | Wendi_Mak_&_Rahel_Getu_ወንዲ_ማክ_እና_ራሄል_ጌቱ_Fashion_New_ፋሽን_ነው.mp3 | 936 |
| 9 | የታሪክ አፍቃሪያን የታላቹ?
የሀገራችንን ድንቅ ስነ-ፅሁፎች፣ ወጎች፣ ግጥሞች እ የሚያቀርቡ ምርጥ የቴሌግራም ቻናሎችን በአንድ ቦታ አዘጋጅተንላችኋል።
📖 ልብ ወለድ እና አጫጭር ታሪኮች
✍️ ልብ የሚነኩ ግጥሞች እና ቅኔዎች
🧠 የፍልስፍና እና የ ስነ-ልቦና ፅሁፎች
📜 የታሪክ እና የባህል ማስታወሻዎች
ሁሉንም በአንድ ላይ
👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇👇
https://t.me/addlist/wj1FH6fJLSExZmM0 | 524 |
| 10 | ምናልባት
ክፍል 12
እንደልማዱ የዛፉን ግንድ ተደግፎ እየጠበቀኝ ነበር። ተደጋጋሚ ነገር ይሰለቻል የሚሉ ሰዎች የሚደጋገመው ነገር ጥሩነት ላይ እንደሚመሰረት አያውቁም ማለት ነው። ምክንያቱም ኤሚን በተመሳሳይ ቦታ ላይ በየቀኑ ማግኘት አሰልቺ ሳይሆን መታደል ነው
"ዛሬ ወደስቱድዮ አንሄድም እሺ?" አለ ፈገግ ብሎ ያቀደው ሌላ ነገር አለ ማለት ነው
"ለምን? ማለቴ ብዙ መደረግ ያለበት ነገር እያለ?" ኤግዚቢሽኑ ሳምንት ነው የቀረው
"ዛሬ ልጆቹ ቀለም እንዲቀቡ ነግሬያቸዋለሁ እኛ ምንም ስለማንሰራ አብረን እንዋል ብዬ እኮ ነው"
አብረን ነው የምንውለው አላልኩትም እኔም ብሆን ከስራ ውጪ አብሬው ብውል ደስታዬ ነው
...
ስንሽከረከረ ከቆየን በኋላ ለምሳ ስንቀመጥ
"እስከዛሬ እንዴት ስለእነሱ አውርተን አናውቅም ቆይ?" አልኩት ማኪያቶዬን እያማሰልኩ
"ስለነማ?" አለ ኤሚ ግራ ተጋብቶ
"ስለአና እና ስለወንድምህ ነዋ መቼም የሆነ ነገር ሳይነግርህ አይቀርም ወይስ የኔ እህት ብቻ ነች እያበደች ያለችው"
"እሱንም አላየሽውም ባክሽ እኔ እንደዚህ ሲሆን አይቼው አላውቅም እኮ የገዛላትን መፅሀፍ አይተሽዋል አይደል? የትናየት ሄዶ እንደገዛው ብታውቂ ያለበት ሁኔታ ይገባሽ ነበር" አለ
"እኔ እንደዚህ ደስተኛ ሆና እንድትቆይ ነው የምፈልገው አንድ ቀን በሱ ምክንያት ብታዝን እንደምገለው ይወቅ"
"ያንቺን እህት ሲያስከፋት እኔ ዝም ብዬ የማይ ይመስልሻል?"
"ባይሆን ከግጥም ምሽቱ ውጪ በስነስርዓቱ ተገናኝተው እንደማያውቁ ታውቃለህ አይደል?" አልኩት
"ምን እያሰብሽ እንደሆነ አውቃለሁ። እና መቼ ይሁን?" አለ ሹራቡን እስከክንዱ እየሰበሰበ
....
አና
ሊያና ስትገባ አልጋ ላይ ተጠቅልዬ እያነበብኩ ነበር። "በእሁድ ምድር ምንድነው አልጋ ላይ አስተኝቶ የሚያሽኮረምምሽ?" አለች አጠገቤ አልጋ ውስጥ እየገባች
"ግጥሞቹ ተዪኝ በቃ በጣም ሮማንቲክ ናቸው" አልኳትና አጥፌ አስቀመጥኩት
ወደኔ ዞራ ራሷን መዳፏ ላይ አስደግፋ "የዛሬ መቶ አመት የተፃፈ መፅሀፍ እያነበብሽ ከምትሽኮረመሚ የእውነት ሮማንስ ላሳይሽ" አለች
የወሰነችው ነገር እንደሆነ ስለሚያስታውቅ ምንም ብል ስለማይቀርልኝ "የት ነው የምንሄደው?" አልኳት
"ኤሚ ልጋብዝሽ ብሎኝ ነው ብቻዬን መሄድ ስለደበረኝ ነው በዛ ላይ ፏ ብዬ ስወጣ ወዴት ነው ከምባል አብረን ስንሆን ፈታ ልንል ነው ብንል ራሱ ያምኑናል አይመስልሽም"
"እሺ ግን..."
"ችግር የለም ልብስሽን ሜካፕ ምናምን እኔ አለሁ ዋናው እሺ ማለትሽ ነው" ብላ እየሮጠች ሄደች
....
ሊያና
እንዳልኩትም ፏ ብለን ስንወጣ አባ የጥርጣሬ አስተያየቱ አልቀረልንም። ሆ! እና መኝታ ቤት ውስጥ ተወሽቀን ባል የምናገኘው በመስኮት አንኳኩቶ ሲመጣ ነው?
ኤሚ text ላከልኝ "እንደምንም አሳምኜው ነው የመጣው መነጫነጭ ጀምሯል አፍጥኑት" ይላል "ኤሚ ነው አይደል?" አለች አና ሲሰለቻት እንደምትሆነው ፊቷን አጨፍግጋ "ከኤሚዬ ውጪ ማን ሊሆን ይችላል ብለሽ ነው?" አልኳት
"ሞዛዞች" አለችና "እኔ እኮ ያልገባኝ እናንተ ለምትገናኙት የኔ መልበስ ምን ይሉታል"
"እና እንደዛ መስለሽ ከኔ ጋር ልትወጪ ነበር የፈለግሽው" እየተጨቃጨቅን ደረስን እና ወደካፌው ስንሄድ ኤሚን አየሁት። ቆይ በየቀኑ እየተገናኘን ባየሁት ቁጥር ልቤን ምን አዘለላት?
"ማንን ነው ከኤሚ ጋር የማየው?" ቆነጠጠቺኝ "እኔንጃ ማነው?" አልኳት ከኤሚ ፊት ለኛ ጀርባውን ሰጥቶ ነበር የተቀመጠው
"አንቺ ከሀዲ ሲጀመር አውቀሽ ነዋ ያመጣሺኝ?" ቆንጥጣ ጨረሰቺኝ አጠገባቸው ስንደርስ እኔ ኤሚ ላይ ተጠምጥሜ ሳበቃ አጠገቡ ተቀመጥኩ
አና ጨብጣው አጠገቡ ስትቀመጥ ሁለቱም ወደኛ በዛቻ አስተያየት ያፈጡብናል። ብዙም ሳይቆዩ "መፅሀፍህን አነበብኩት እኮ" አለችው ከዛ በኋላ "እንዴት ነው ያማረብሽ ባክሽ" ሲል ኤሚ መኖራቸውንም ረሳሁት
...
ኪራኮዝ
ያለምክንያት በእኩለ ቀን አንቀዥቅዦ እንደማያስመጣኝ አውቄያለሁ ግን እሷን ሊያገናኙን ኤሚና ሊያና እዚህ ርቀት ድረስ ይሄዳሉ ብዬ አልገመትኩም።
እኔ እንደምመጣ እንዳላወቀች ግልፅ ነው። እንዴት ስትደነባበር እንደነበረ ኤሚ ጥርሱን ገጥሞ ሲነግረኝ ነበር።
ከግጥም ምሽቱ ቀን በላይ አምሮባታል። ታናናሾቻችን እኛን ለማገናኘት የጠነሰሱት ባይሆን ነፃ ሆነን ልናወራ እንችል ይሆን ይሆናል። ምናልባት ምቾት የሚነሳት ሁኔታ ላይ እንደሆነች ልጠይቃት ስል "መፅሀፍህን አነበብኩት እኮ" አለች ፈገግ ብላ
እንደዚህ ፈገግ ብላ ጠላሁት አትለኝም ብዬ "ወደድሽው?" አልኳት "በጣም! እኔ እኮ ከመቶ አመት በፊት ተፅፎ እንደዚህ ተመሳሳይ ስሜት ማስተናገዳችን የስነፅሁፍ ውበት ይመስለኛል"
"ውይ በጣም! ሰው እንዳለ ሙሉ ሰሜቱ የሚታይበት መሆኑ ሰው መሆን እስካላቆምን ድረስ relate የምናደርገው ነገር ማግኘት አይቀርም" አልኳት
"አንተስ አነበብከው?" አለች "አዎ እንደፈራሁት አይደለም የዘንድሮ የፍቅር ልብወለዶች በተለይ የእንግሊዘኛ መፅሀፎች የአኒሜሽን እና የደማቅ ቀለማት የመፅሀፍ ሽፋን መፅሀፉ ሳይነበብ እንዲናቅ ያደርገዋል። አልዋሽሽም እንዳልጠላው ፈርቼ ነበር ግን ታሪኩ ለክፉ አይሰጥም"
"ከሽፋኑ ውጪ ምኑን ነው የጠላኸው?" ለክርክር ተዘጋጅታለች
"ሙሉ መፅሀፉ ስለሁለት ሰዎች አብሮ መሆን አለመሆን ሽኩቻ ብቻ ባይሆን ጥሩ ነበር። ትንሽ ሴራ ወይ የሆነ ነገር ቢኖረው ሙሉ ትኩረቱ የፍቅር ታሪኩ መሆኑ ነው ያልወደድኩት" አልኳት ለመልስ ምቷ ራሴን እያዘጋጀሁ
"ለምን? የፍቅር ታሪክ ብቻውን መፅሀፍ መሆን አይችልም? ሴራ ምናምን የምትፈልግ ከሆነ ሌላ መፅሀፍ ገዝተህ አንብብ" ብላ ፊቷን ወደነ ኤሚ አዞረች
አብሬያት ስዞር እንዳያቋርጡን እየጠበቁ ነበር። "በርሀብ ልሞት እኮ ነው እንብላና ትጨቃጨቃላችሁ" አለች ሊያ
✍ናኒ
እኔ ይሄ ሁሉ ቃላት ስፅፍ እናንተ አንዴ react ማድረግ አይከብዳችሁም አይደል?
https://t.me/justhoughtsss | 1 331 |
| 11 | No text... | 1 153 |
| 12 | file_200690 | 1 133 |
| 13 | ገበያ ለመሄድ ጊዜ ለሌላችሁ ሰዎች ይኸው መፍትሄ
በ0923516190 መደወል ብቻ ግልግል ማለት አይደል? | 579 |
| 14 | ሊያና
እማዬን እንደዛ እልል ያስባላት ዜና ምን አይነት ዱብ እዳ እንደሆነብኝ የሚያውቅ አለ? በተለይ የኤሚ አኳኋን፣ ስብር አባባሉ አላስችል አለኝ።
ታሪክ ራሱንም እየደገመ መሰለኝ ከአመታት በፊት እንደሆንነው... በፀጥታ ተሸኛኝተን ቤት ስገባ እማዬና አባዬ ሲኳረፉ እንደሚሆኑት እሷም የምታነብበት ክፍል እሱም ንድፉን የሚሰራበት ክፍል ገብተው መሸገዋል።
ልነፋረቅባት አና ጋር ስሄድ ትራሷን አቅፋ እየተንከባለለች ነው። የሚጋባ ሳቅ እየሳቀች "ሊ ምን እንዳደረገ አታውቂም እሱም አያውቅም ይሄ ለኔ ምን ማለት እንደሆነ የሚያውቅ ሰው አለ?" አለች መፅሀፍ አቅፋ
"ምንድነው መፅሃፍ እያነበብሽ ነው?" አልኳት
የያዘችውን መፅሀፍ ቀና አድርጋ አሳየችኝ One Hundred Love Sonnets by Pablio Neruda ይላል
"መፅሀፍ ገዛልኝ እሱ ነው የሚገርምሽ?" ልቤን ማንጠልጠሏ ነው "ሌላ ምን አደረገልሽ?" ቢያንስ ገፀባህርይ አይደለም እንደዚህ የሚያስፈነጥዛት
"ደብዳቤ ፅፎልኛል። የምወደውን የpablo nerudaን መፅሀፍ መግዛቱ ሳያንስ በአማርኛ እኮ ነው ደብዳቤውን የፃፈው እዪው ቃላት አጣጣሉ ሲያምር የሰዓሊ እኮ ነው የሚመስለው"
"የኔም የኤሚም ፅሁፍ አያምርም" አልኳት ሳበሳጫት እሷ እቴ "የምወደው የግጥም መድብል ነው ስለግጥም ያለሽን አቋም ያስቀይርሽ ይሆናል" ብሎ ነው የፃፈው ብላ አነበበችልኝ። እንደዚህ እንዳስደሰታት ቢያውቅ ምናለበት
...
ኦዚያን
እቤት እንደገባ የእለቱን ዜናዎች ሲከፍት ሶስተኛ ግድያ መፈፀሙ የዜናዎቹን አውታሮች እንዳጨናነቀ አየ። ከግድያውም ከተገኘውም ደብዳቤ በላይ ትኩረቱን የያዘው የሟች የትውልድ ቦታ ነበር። ፔሊ
✍ናኒ
ይቀጥል የምትሉ ብቻ react እያደረጋችሁ
https://t.me/justhoughtsss | 1 457 |
| 15 | ክፍል 11
ምናልባት
የሌሎቹን ባላውቅም እኔ ግን አድካሚ ቀን ነው የነበረኝ። እንደሌላ ቤተሰብ የውሸት የጓጓን አስመስለን "ውሎ እንዴት ነበር ታድያ" አንባባልም ምክንያቱም ሁላችንም ከስራ የዘለለ ህይወት የለንም
የአባዬን ማባርያ የሌለው ተጣጣፊ ኮንክሪት ወሬ ወይም አዲስ ገበያ ላይ ስለዋለ ቀለም ሊያ ስታወራ ስለማይገባን ይሰለቸናል። እማዬ ስለታካሚዎቿ ማውራት በህግ ትከለከላለች እኔ ደግሞ አንጀቱ ተዘርግፎ እግሩ ተቆርጦ ከማለት የዘለለ አስደሳች ውሎ ኖሮኝ አያውቅም።
ለዛ ነው ራት ስንበላ ብዙውን ጊዜ ምግብ ቤት ውስጥ ጠረጴዛ መጋራት እንዳለበት የማይተዋወቅ ሰው የምንሆነው
ይሄንና ምን እንደሆነ ባላውቅም ጭንቅላቴ ያንንም እያነሳ እየጣለ ጭንቅላቴ ይባትላል። አባ ዜናው ላይ ተመስጧል።
ቀና ስል ሊያና ፈገግ ብላ ጠቀሰቺኝ። የሆነ ነገር ስታቅድ ነው እንደዚህ የምትሆነው "ስሙማ" አለች እማን ከሀሳቧ አባን ከዜናው እያደናቀፈቻቸው
"እ" ስትል እማ
"ሰበር ዜና" የሚል ድምፅ የሁላችንንም ትኩረት ሰረቀው "ቆይ ቆይ አንዴ አዳምጡ" ብሎ አባ ድምፁን ጨመረው
"በሁለት ወር ውስጥ የተሰራው ከተማ የሚጠናቀቅ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታውቋል። ከፔሊ የመጣችሁ ሰዎች በፈቃደኝነት ወደዛ ሄዳችሁ መኖር የምትችሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።"
"እልልል" እማ አቀለጠችው "ተመስገን ከዚህ የተረገመ ከተማ እንደዚህ በቀላሉ ልንወጣ ነው እልልል"
ሊያና ፊቷ ገርጥቷል አባ ምንም ስሜት አይታይበትም እሺ እኔ ምን እንደዚህ ልቤን አራደው?
"ሊያ ምን ልትነግሪን ነበር?" አለ አባ ምንም እንዳልተፈጠረ
"እነእትዬ ትሬዛን ነገ ማታ ምሳ እንድንጠራቸው ነበር" አለች ድምጿ ፈዝዞ
"እንችላለን ምን ችግር አለው ስለጠራችን ውለታ የዋለችልን እንዳይመስላት እንጂ አብሮ ለመኖር የሚያስገድደን ነገር የለም ልንወጣ አይደለ" ደስታዋ በድምጿ በፊቷ ይንፀባረቃል።
እማ እዚህ መኖራችንን እንደዚህ ጠልታው ነበር?
...
ኤሞን
ሰዓቱ ለሁለት ሩብ ጉዳይ ይላል። ቆይ ለእራት ግበዣ ስንት ሰዓት መሄድ ነው ትክክል? አንድ ሰዓት ገና ላይዘጋጅ ይችላል ሶስት ሰዓት እንደመቅረት ይቆጠር ይሆናል።
ስለዚህ ሁለት ሰዓት ነው። በሩብ ደቂቃ ውስጥ ብንሄድ ትክክል ስለመሰለኝ ተዘጋጅቼ ጨርሻለሁ። "ይሄ ልጅ ይቆያል እንዴ? በጣም መሸ እኮ" አለች እማ እንደልማዷ እየተጨናነቀች
"እየደረስኩ ነው ብሏል አትጨናነቂ" አልኳትና ወደሳሎን ስሄድ እሱ ሲያንኳኳ ተገጣጠምን። ስከፍትለት
"አላመሸሁም አይደል? ጥሪ ኖሮ ማርፈድ ልክ አይደለም" እያለ እየተጣደፈ ወደክፍሉ ገባ
አቻኩሎ ደብቆ ሊያስገባው የፈለገውን መፅሐፍ አይቼበታለሁ። ተከትዬው ክፍሉ ስገባ ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦታል።
"እኔ እኮ አላምንም"አልኩት መፅሀፉን አገላብጬ እያየሁ
እንዳልሰማኝ ልብሱን ይቀይራል። "የከተማዋ ጫፍ ድረስ ሄደህ ገዛኸው?" ሌላ ቦታ ማግኘት አቅቶት የተወው መፅሃፍ ነው።
"ምን ችግር አለው?" ለክት ብቻ የሚያወጣትን ሽቶ ኮሌታው ላይ እየቀባ
"ለሊያ እህት ነው አይደል?" አልመለሰልኝም
"እንውጣ ልጆች" እማ ተጣራች
"ጨርሰናል መጣን" መብራቱን እላዬ ላይ አጥፍቶ ወጣ ያመለጠኝ መስሎት
...
ኪራኮስ
በሩን ስናንኳኳ "መጡ መጡ መጡ" የሚል ድምፅ ከውስጥ ሰማሁ። የከፈተችው አናን የምትመስል ሴት ናት እህቷ ናት ማለት ነው። እየሮጠች መጥታ እንደከፈተች ያስታውቃል።
"እንኳን ደህና መጣችሁ" አለች ኤሚ በአይኖቿ እያቀፈችው። ደስ ሲሉ
ስንገባ አና እና እናቷ ምግብ እያቀራረቡ ነበር። እንደነገሩ ያዝያዘችው ፀጉሯ ታጥፎ ራሱ አለሁ ይላል። ከፀጉር ማስያዣው ጥቂት ወጥቶ ጀርባዋ ላይ ተኝቷል። ሁሉም ሰላም ሲባባል ውስጥ ነበረች። አባታቸው ኑ ተቀመጡ ብሎ ገና ከመግባታችን የምግብ ጠረጴዛው ጋር ወሰደን።
አባትየውና እና እናትየው ትዕዩ ተቀመጡ። ኤሚና ሊያና ደግሞ በግራ በኩል ተቀመጡ ከኤሚ አጠገብ ማሚ ተቀመጠች ከአባታቸው አጠገብ መሆኑ ነው።
ኦዚያን እናታቸው በስተቀኝ ተቀምጦ ወሬ ጀምረዋል። እኛ አልሰማ የምንለውን ወሬ ከእሷ ጋር ሲሆን እኩል በእኩል ሲያወሩ ደስ ይለኛል። ሁሉም ሰው እንደራሱ ሆኖ የሚያወራው ሰው ይፈልጋል አይደል?
ኤሚና ሊያና ምንም እንደማይተዋወቅ ሰው የሚያደርጉት ጥረት ያስቀኛል። አይነስውር የሚያየው መሳሳብ በመላሀቸው ኖሮ ለደቂቃ መነጣጠል ሳይፈልጉ ወላጆቻቸው እንዳያውቁባቸው የሚያደርጉት ጥረት ረብ የለሽ ይሆንብኛል። የፍቅራቸው አምላክ አይናቸውን ጋርዶላቸው እንጂ አልቆላቸው ነበር።
አቀራርባ ስትጨርስ እና ስትመጣ የነበረው ቦታ በኔና በኦዚ መሀል ያለው ወንበር ብቻ ነበር። አጋጣሚ መሆን አለበት (አይደል?)
ስትቀመጥ ለስላሳ ሽቶዋ አወደኝ። የግጥም ምሽቱ ቀን የተቀባችው ነው። በትግል ከጭንቅላቴ ያወጣሁትን አደሰችልኝ።
"በሁለት ወር ውስጥ መውጣት ትችላላችሁ አሉ ደግሞ አይደል" እማ ፀጥታውን አፈረሰችው
ጋሽ ኤስሮም መልስ እየመለሰላት ነው። ግዴታ እንዳልሆነና መሄድ ከፈለጉ ብቻ እንደሚሄዱ እየነገራት ነው
ከዛ በኋላ ያሉትን አልሰማሁም መብረቅ እንደወረደበት ደርቄ ቀረሁ። ሁለት ወር? ስምንት ሀሙስ? ከዛ በኋላ እንደልማዴ ብቻዬን ልሄድ ነው።
ፊቴ ላይም ድንጋጤዬ ታይቷል መሰል "አባ ምነው አመመህ እንዴ?" ስትል ማሚ "ኧረ ትንሽ ብርድ አግኝቶኛል መሰለኝ ውጋት ይዞኝ ነው አልኳት ደህናውን ወገቤን ደግፌ
"አና እኮ ነርስ ናት እሷን ጠይቃት መድሀኒቱን" አለ አባታቸው ኤስሮም "አባ ደሞ ወጌሻ መሰልኩህ እንዴ"
ስትለው በሳቅ ተቀበልናት።
የእሷ ወንበር ላይ ስደገፍ ትከሻዋን ዳበስ አድርጌው አለፍኩ ፈገግ ያለችበትን ከንፈሯን ነክሳ ስታስቆመው አይቻታለሁ። እጄን እዛው ተውኩት ትከሻዋ ጋር ጉንጮቿ እየቀሉ ነው።
"ሌላ ምን አዲስ ነገር አለ?" ስትለው የእነአና እናት እትዬ ማሊካ "ምንም የለም ያው የከተማዋ ነባር ነዋሪዎች ላይ ብቻ ስለሆነ እየተፈፀመ ያለው የተገመተው አዲስ ከሰፈሩት ሰዎች መሀል ሊሆን ይችላል እየተባለ ነው" አላት ቆይ ይሄ ልጅ ያለዚህም ጉዳይ ስራ የለውም እንዴ?
"ለዛ ነው አይደል በየመንገዱ የሚገላምጠኝ ሰው በዝቷል" አለች አና ቀጥላም እህቷ ከሌሎች ጎረቤቶች ስለገጠማት ዘለፋ ነገረችን
ማን አባቱ ነው የሚገላምጣት
"መፅሀፉን ገዝቼልሀለው እሰጥሀለው ስትወጡ" አለች ለሌላ ለማንም በማይሰማ ድምፅ
"ደስ ይለኛል"
ከዛ በኋላ ምሽቱ ያለቃላት ልውውጥ ከእሷ ጋር ስናወራ ቀና ብላ ባየቺኝ ቁጥር ልቤ ብትንትኑ እየወጣ፣
ማሚ እና ጋሽ ኤስሮም ስለሆነ አዲስ ተክል ቅጠል አበቃቀል ሲያወሩ ኤሚና ሊያ በዝምታ ሲቆዝሙ እናታቸውና ኦዚ ስለግድያ አይነቶች ሲዘረዝሩ አምሽተን
"ሰዓቱ እንዴት ሄዷል ባካችሁ" ስትል እናታቸው ሂዱ ማለቷ እንደሆነ ገብቶን ተነሳን። ልንወጣ ስንል ጥንድ ጥንድ ሆነው ሲያወሩ በነበሩበት አኳኋን ወጡ።
ልብሴን ጎተት አድርጋ ስታስቀረኝ ለመፅሀፉ መሆኑ ገብቶኝ ሌሎቹ ወጥተው እኛ ስንቀር መፅሀፉን ሮጣ አምጥታ ሰጠቺኝ።
ሰማያዊ የሽፋን ገፅ በቢጫ ፊደላት ርዕስ ያለው መፅሀፍ ነው። መቸገሬ ነው እንግዲ። እኔም ስገባ ከሰቀልኩት ከኮቴ ኪስ ውስጥ የገዛሁላትን መፅሀፍ ሰጠኋት። ፊቷ ላይ የነበረው ያለማመን እና የደስታ ጥግ ደጋግመህ መፅሀፍ ግዛላት የሚል ምኞት አሳደረብኝ።
ሳብ አድርጌ ለጥቂት ሰከንዶች ካቀፍቋት በኋላ ሀሙስ እንገናኛለን ብያት እዛው ደርቃ በቆመችበት ወጣሁ ትኩረት ከመሳባችን በፊት።
... | 1 277 |
| 16 | እማዬን እንደዛ እልል ያስባላት ዜና ምን አይነት ዱብ እዳ እንደሆነብኝ የሚያውቅ አለ? በተለይ የኤሚ አኳኋን፣ ስብር አባባሉ አላስችል አለኝ።
ታሪክ ራሱንም እየደገመ መሰለኝ ከአመታት በፊት እንደሆንነው... በፀጥታ ተሸኛኝተን ቤት ስገባ እማዬና አባዬ ሲኳረፉ እንደሚሆኑት እሷም የምታነብበት ክፍል እሱም ንድፉን የሚሰራበት ክፍል ገብተው መሸገዋል።
ልነፋረቅባት አና ጋር ስሄድ ትራሷን አቅፋ እየተንከባለለች ነው። የሚጋባ ሳቅ እየሳቀች "ሊ ምን እንዳደረገ አታውቂም እሱም አያውቅም ይሄ ለኔ ምን ማለት እንደሆነ የሚያውቅ ሰው አለ?" አለች መፅሀፍ አቅፋ
"ምንድነው መፅሃፍ እያነበብሽ ነው?" አልኳት
የያዘችውን መፅሀፍ ቀና አድርጋ አሳየችኝ One Hundred Love Sonnets by Pablio Neruda ይላል
"መፅሀፍ ገዛልኝ እሱ ነው የሚገርምሽ?" ልቤን ማንጠልጠሏ ነው "ሌላ ምን አደረገልሽ?" ቢያንስ ገፀባህርይ አይደለም እንደዚህ የሚያስፈነጥዛት
"ደብዳቤ ፅፎልኛል። የምወደውን የpablo nerudaን መፅሀፍ መግዛቱ ሳያንስ በአማርኛ እኮ ነው ደብዳቤውን የፃፈው እዪው ቃላት አጣጣሉ ሲያምር የሰዓሊ እኮ ነው የሚመስለው"
"የኔም የኤሚም ፅሁፍ አያምርም" አልኳት ሳበሳጫት እሷ እቴ "የምወደው የግጥም መድብል ነው ስለግጥም ያለሽን አቋም ያስቀይርሽ ይሆናል" ብሎ ነው የፃፈው ብላ አነበበችልኝ። እንደዚህ እንዳስደሰታት ቢያውቅ ምናለበት
...
ኦዚያን
እቤት እንደገባ የእለቱን ዜናዎች ሲከፍት ሶስተኛ ግድያ መፈፀሙ የዜናዎቹን አውታሮች እንዳጨናነቀ አየ። ከግድያውም ከተገኘውም ደብዳቤ በላይ ትኩረቱን የያዘው የሟች የትውልድ ቦታ ነበር። ፔሊ
✍ናኒ
ይቀጥል የምትሉ ብቻ react እያደረጋችሁ
https://t.me/justhoughtsss | 3 |
| 17 | No text... | 1 078 |
| 18 | ክፍል 11
ምናልባት
የሌሎቹን ባላውቅም እኔ ግን አድካሚ ቀን ነው የነበረኝ። እንደሌላ ቤተሰብ የውሸት የጓጓን አስመስለን "ውሎ እንዴት ነበር ታድያ" አንባባልም ምክንያቱም ሁላችንም ከስራ የዘለለ ህይወት የለንም
የአባዬን ማባርያ የሌለው ተጣጣፊ ኮንክሪት ወሬ ወይም አዲስ ገበያ ላይ ስለዋለ ቀለም ሊያ ስታወራ ስለማይገባን ይሰለቸናል። እማዬ ስለታካሚዎቿ ማውራት በህግ ትከለከላለች እኔ ደግሞ አንጀቱ ተዘርግፎ እግሩ ተቆርጦ ከማለት የዘለለ አስደሳች ውሎ ኖሮኝ አያውቅም።
ለዛ ነው ራት ስንበላ ብዙውን ጊዜ ምግብ ቤት ውስጥ ጠረጴዛ መጋራት እንዳለበት የማይተዋወቅ ሰው የምንሆነው
ይሄንና ምን እንደሆነ ባላውቅም ጭንቅላቴ ያንንም እያነሳ እየጣለ ጭንቅላቴ ይባትላል። አባ ዜናው ላይ ተመስጧል።
ቀና ስል ሊያና ፈገግ ብላ ጠቀሰቺኝ። የሆነ ነገር ስታቅድ ነው እንደዚህ የምትሆነው "ስሙማ" አለች እማን ከሀሳቧ አባን ከዜናው እያደናቀፈቻቸው
"እ" ስትል እማ
"ሰበር ዜና" የሚል ድምፅ የሁላችንንም ትኩረት ሰረቀው "ቆይ ቆይ አንዴ አዳምጡ" ብሎ አባ ድምፁን ጨመረው
"በሁለት ወር ውስጥ የተሰራው ከተማ የሚጠናቀቅ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታውቋል። ከፔሊ የመጣችሁ ሰዎች በፈቃደኝነት ወደዛ ሄዳችሁ መኖር የምትችሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።"
"እልልል" እማ አቀለጠችው "ተመስገን ከዚህ የተረገመ ከተማ እንደዚህ በቀላሉ ልንወጣ ነው እልልል"
ሊያና ፊቷ ገርጥቷል አባ ምንም ስሜት አይታይበትም እሺ እኔ ምን እንደዚህ ልቤን አራደው?
"ሊያ ምን ልትነግሪን ነበር?" አለ አባ ምንም እንዳልተፈጠረ
"እነእትዬ ትሬዛን ነገ ማታ ምሳ እንድንጠራቸው ነበር" አለች ድምጿ ፈዝዞ
"እንችላለን ምን ችግር አለው ስለጠራችን ውለታ የዋለችልን እንዳይመስላት እንጂ አብሮ ለመኖር የሚያስገድደን ነገር የለም ልንወጣ አይደለ" ደስታዋ በድምጿ በፊቷ ይንፀባረቃል።
እማ እዚህ መኖራችንን እንደዚህ ጠልታው ነበር?
...
ኤሞን
ሰዓቱ ለሁለት ሩብ ጉዳይ ይላል። ቆይ ለእራት ግበዣ ስንት ሰዓት መሄድ ነው ትክክል? አንድ ሰዓት ገና ላይዘጋጅ ይችላል ሶስት ሰዓት እንደመቅረት ይቆጠር ይሆናል።
ስለዚህ ሁለት ሰዓት ነው። በሩብ ደቂቃ ውስጥ ብንሄድ ትክክል ስለመሰለኝ ተዘጋጅቼ ጨርሻለሁ። "ይሄ ልጅ ይቆያል እንዴ? በጣም መሸ እኮ" አለች እማ እንደልማዷ እየተጨናነቀች
"እየደረስኩ ነው ብሏል አትጨናነቂ" አልኳትና ወደሳሎን ስሄድ እሱ ሲያንኳኳ ተገጣጠምን። ስከፍትለት
"አላመሸሁም አይደል? ጥሪ ኖሮ ማርፈድ ልክ አይደለም" እያለ እየተጣደፈ ወደክፍሉ ገባ
አቻኩሎ ደብቆ ሊያስገባው የፈለገውን መፅሐፍ አይቼበታለሁ። ተከትዬው ክፍሉ ስገባ ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦታል።
"እኔ እኮ አላምንም"አልኩት መፅሀፉን አገላብጬ እያየሁ
እንዳልሰማኝ ልብሱን ይቀይራል። "የከተማዋ ጫፍ ድረስ ሄደህ ገዛኸው?" ሌላ ቦታ ማግኘት አቅቶት የተወው መፅሃፍ ነው።
"ምን ችግር አለው?" ለክት ብቻ የሚያወጣትን ሽቶ ኮሌታው ላይ እየቀባ
"ለሊያ እህት ነው አይደል?" አልመለሰልኝም
"እንውጣ ልጆች" እማ ተጣራች
"ጨርሰናል መጣን" መብራቱን እላዬ ላይ አጥፍቶ ወጣ ያመለጠኝ መስሎት
...
ኪራኮስ
በሩን ስናንኳኳ "መጡ መጡ መጡ" የሚል ድምፅ ከውስጥ ሰማሁ። የከፈተችው አናን የምትመስል ሴት ናት እህቷ ናት ማለት ነው። እየሮጠች መጥታ እንደከፈተች ያስታውቃል።
"እንኳን ደህና መጣችሁ" አለች ኤሚ በአይኖቿ እያቀፈችው። ደስ ሲሉ
ስንገባ አና እና እናቷ ምግብ እያቀራረቡ ነበር። እንደነገሩ ያዝያዘችው ፀጉሯ ታጥፎ ራሱ አለሁ ይላል። ከፀጉር ማስያዣው ጥቂት ወጥቶ ጀርባዋ ላይ ተኝቷል። ሁሉም ሰላም ሲባባል ውስጥ ነበረች። አባታቸው ኑ ተቀመጡ ብሎ ገና ከመግባታችን የምግብ ጠረጴዛው ጋር ወሰደን።
አባትየውና እና እናትየው ትዕዩ ተቀመጡ። ኤሚና ሊያና ደግሞ በግራ በኩል ተቀመጡ ከኤሚ አጠገብ ማሚ ተቀመጠች ከአባታቸው አጠገብ መሆኑ ነው።
ኦዚያን እናታቸው በስተቀኝ ተቀምጦ ወሬ ጀምረዋል። እኛ አልሰማ የምንለውን ወሬ ከእሷ ጋር ሲሆን እኩል በእኩል ሲያወሩ ደስ ይለኛል። ሁሉም ሰው እንደራሱ ሆኖ የሚያወራው ሰው ይፈልጋል አይደል?
ኤሚና ሊያና ምንም እንደማይተዋወቅ ሰው የሚያደርጉት ጥረት ያስቀኛል። አይነስውር የሚያየው መሳሳብ በመላሀቸው ኖሮ ለደቂቃ መነጣጠል ሳይፈልጉ ወላጆቻቸው እንዳያውቁባቸው የሚያደርጉት ጥረት ረብ የለሽ ይሆንብኛል። የፍቅራቸው አምላክ አይናቸውን ጋርዶላቸው እንጂ አልቆላቸው ነበር።
አቀራርባ ስትጨርስ እና ስትመጣ የነበረው ቦታ በኔና በኦዚ መሀል ያለው ወንበር ብቻ ነበር። አጋጣሚ መሆን አለበት (አይደል?)
ስትቀመጥ ለስላሳ ሽቶዋ አወደኝ። የግጥም ምሽቱ ቀን የተቀባችው ነው። በትግል ከጭንቅላቴ ያወጣሁትን አደሰችልኝ።
"በሁለት ወር ውስጥ መውጣት ትችላላችሁ አሉ ደግሞ አይደል" እማ ፀጥታውን አፈረሰችው
ጋሽ ኤስሮም መልስ እየመለሰላት ነው። ግዴታ እንዳልሆነና መሄድ ከፈለጉ ብቻ እንደሚሄዱ እየነገራት ነው
ከዛ በኋላ ያሉትን አልሰማሁም መብረቅ እንደወረደበት ደርቄ ቀረሁ። ሁለት ወር? ስምንት ሀሙስ? ከዛ በኋላ እንደልማዴ ብቻዬን ልሄድ ነው።
ፊቴ ላይም ድንጋጤዬ ታይቷል መሰል "አባ ምነው አመመህ እንዴ?" ስትል ማሚ "ኧረ ትንሽ ብርድ አግኝቶኛል መሰለኝ ውጋት ይዞኝ ነው አልኳት ደህናውን ወገቤን ደግፌ
"አና እኮ ነርስ ናት እሷን ጠይቃት መድሀኒቱን" አለ አባታቸው ኤስሮም "አባ ደሞ ወጌሻ መሰልኩህ እንዴ"
ስትለው በሳቅ ተቀበልናት።
የእሷ ወንበር ላይ ስደገፍ ትከሻዋን ዳበስ አድርጌው አለፍኩ ፈገግ ያለችበትን ከንፈሯን ነክሳ ስታስቆመው አይቻታለሁ። እጄን እዛው ተውኩት ትከሻዋ ጋር ጉንጮቿ እየቀሉ ነው።
"ሌላ ምን አዲስ ነገር አለ?" ስትለው የእነአና እናት እትዬ ማሊካ "ምንም የለም ያው የከተማዋ ነባር ነዋሪዎች ላይ ብቻ ስለሆነ እየተፈፀመ ያለው የተገመተው አዲስ ከሰፈሩት ሰዎች መሀል ሊሆን ይችላል እየተባለ ነው" አላት ቆይ ይሄ ልጅ ያለዚህም ጉዳይ ስራ የለውም እንዴ?
"ለዛ ነው አይደል በየመንገዱ የሚገላምጠኝ ሰው በዝቷል" አለች አና ቀጥላም እህቷ ከሌሎች ጎረቤቶች ስለገጠማት ዘለፋ ነገረችን
ማን አባቱ ነው የሚገላምጣት
"መፅሀፉን ገዝቼልሀለው እሰጥሀለው ስትወጡ" አለች ለሌላ ለማንም በማይሰማ ድምፅ
"ደስ ይለኛል"
ከዛ በኋላ ምሽቱ ያለቃላት ልውውጥ ከእሷ ጋር ስናወራ ቀና ብላ ባየቺኝ ቁጥር ልቤ ብትንትኑ እየወጣ፣
ማሚ እና ጋሽ ኤስሮም ስለሆነ አዲስ ተክል ቅጠል አበቃቀል ሲያወሩ ኤሚና ሊያ በዝምታ ሲቆዝሙ እናታቸውና ኦዚ ስለግድያ አይነቶች ሲዘረዝሩ አምሽተን
"ሰዓቱ እንዴት ሄዷል ባካችሁ" ስትል እናታቸው ሂዱ ማለቷ እንደሆነ ገብቶን ተነሳን። ልንወጣ ስንል ጥንድ ጥንድ ሆነው ሲያወሩ በነበሩበት አኳኋን ወጡ።
ልብሴን ጎተት አድርጋ ስታስቀረኝ ለመፅሀፉ መሆኑ ገብቶኝ ሌሎቹ ወጥተው እኛ ስንቀር መፅሀፉን ሮጣ አምጥታ ሰጠቺኝ።
ሰማያዊ የሽፋን ገፅ በቢጫ ፊደላት ርዕስ ያለው መፅሀፍ ነው። መቸገሬ ነው እንግዲ። እኔም ስገባ ከሰቀልኩት ከኮቴ ኪስ ውስጥ የገዛሁላትን መፅሀፍ ሰጠኋት። ፊቷ ላይ የነበረው ያለማመን እና የደስታ ጥግ ደጋግመህ መፅሀፍ ግዛላት የሚል ምኞት አሳደረብኝ።
ሳብ አድርጌ ለጥቂት ሰከንዶች ካቀፍቋት በኋላ ሀሙስ እንገናኛለን ብያት እዛው ደርቃ በቆመችበት ወጣሁ ትኩረት ከመሳባችን በፊት።
...
ሊያና | 21 |
| 19 | 7088fdf3-11ca-4cfa-b2a5-5631cf6a4952.mp3 | 1 203 |
| 20 | @Jaymasangula_bot | info | 1 |
