Thoughts
ቸል የተባሉ እሳቤዎች፥ ያልታዩ እይታዎች የሚፈነጩበት ቤት ነው ፥ እናንተስ ጎራ አትሉም? comment for the writer : @Exquisiteperfume discussion group https://t.me/+uDtKY02cOho2NGZk Tiktok: https://www.tiktok.com/@the_author_nani?_t=8pGCAO5NksY&_r=1 Since:Dec-10-2022
Показати більше📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Thoughts
Канал Thoughts (@justhoughtsss) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 11 078 підписників, посідаючи 8 164 місце в категорії Релігія і духовність та 3 031 місце у регіоні Ефіопія.
📊 Показники аудиторії та динаміка
З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 11 078 підписників.
За останніми даними від 05 вересня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 105, а за останні 24 години на -1, загальне охоплення залишається високим.
- Статус верифікації: Не верифікований
- Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 20.29%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 9.18% реакцій від загальної кількості підписників.
- Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 2 246 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 1 016 переглядів.
- Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 24.
📝 Опис та контентна політика
Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
“ቸል የተባሉ እሳቤዎች፥ ያልታዩ እይታዎች የሚፈነጩበት ቤት ነው ፥ እናንተስ ጎራ አትሉም?
comment for the writer : @Exquisiteperfume
discussion group https://t.me/+uDtKY02cOho2NGZk
Tiktok: https://www.tiktok.com/@the_author_nani?_t=8pGCAO5NksY&_r=1
Since:Dec-10-2022”
Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 06 вересня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Релігія і духовність.
Триває завантаження даних...
| Дата | Залучення підписників | Згадування | Канали | |
| 06 вересня | +6 | |||
| 05 вересня | 0 | |||
| 04 вересня | +16 | |||
| 03 вересня | +8 | |||
| 02 вересня | +1 | |||
| 01 вересня | +11 |
| 2 | ምናልባት
ክፍል 12
እንደልማዱ የዛፉን ግንድ ተደግፎ እየጠበቀኝ ነበር። ተደጋጋሚ ነገር ይሰለቻል የሚሉ ሰዎች የሚደጋገመው ነገር ጥሩነት ላይ እንደሚመሰረት አያውቁም ማለት ነው። ምክንያቱም ኤሚን በተመሳሳይ ቦታ ላይ በየቀኑ ማግኘት አሰልቺ ሳይሆን መታደል ነው
"ዛሬ ወደስቱድዮ አንሄድም እሺ?" አለ ፈገግ ብሎ ያቀደው ሌላ ነገር አለ ማለት ነው
"ለምን? ማለቴ ብዙ መደረግ ያለበት ነገር እያለ?" ኤግዚቢሽኑ ሳምንት ነው የቀረው
"ዛሬ ልጆቹ ቀለም እንዲቀቡ ነግሬያቸዋለሁ እኛ ምንም ስለማንሰራ አብረን እንዋል ብዬ እኮ ነው"
አብረን ነው የምንውለው አላልኩትም እኔም ብሆን ከስራ ውጪ አብሬው ብውል ደስታዬ ነው
...
ስንሽከረከረ ከቆየን በኋላ ለምሳ ስንቀመጥ
"እስከዛሬ እንዴት ስለእነሱ አውርተን አናውቅም ቆይ?" አልኩት ማኪያቶዬን እያማሰልኩ
"ስለነማ?" አለ ኤሚ ግራ ተጋብቶ
"ስለአና እና ስለወንድምህ ነዋ መቼም የሆነ ነገር ሳይነግርህ አይቀርም ወይስ የኔ እህት ብቻ ነች እያበደች ያለችው"
"እሱንም አላየሽውም ባክሽ እኔ እንደዚህ ሲሆን አይቼው አላውቅም እኮ የገዛላትን መፅሀፍ አይተሽዋል አይደል? የትናየት ሄዶ እንደገዛው ብታውቂ ያለበት ሁኔታ ይገባሽ ነበር" አለ
"እኔ እንደዚህ ደስተኛ ሆና እንድትቆይ ነው የምፈልገው አንድ ቀን በሱ ምክንያት ብታዝን እንደምገለው ይወቅ"
"ያንቺን እህት ሲያስከፋት እኔ ዝም ብዬ የማይ ይመስልሻል?"
"ባይሆን ከግጥም ምሽቱ ውጪ በስነስርዓቱ ተገናኝተው እንደማያውቁ ታውቃለህ አይደል?" አልኩት
"ምን እያሰብሽ እንደሆነ አውቃለሁ። እና መቼ ይሁን?" አለ ሹራቡን እስከክንዱ እየሰበሰበ
....
አና
ሊያና ስትገባ አልጋ ላይ ተጠቅልዬ እያነበብኩ ነበር። "በእሁድ ምድር ምንድነው አልጋ ላይ አስተኝቶ የሚያሽኮረምምሽ?" አለች አጠገቤ አልጋ ውስጥ እየገባች
"ግጥሞቹ ተዪኝ በቃ በጣም ሮማንቲክ ናቸው" አልኳትና አጥፌ አስቀመጥኩት
ወደኔ ዞራ ራሷን መዳፏ ላይ አስደግፋ "የዛሬ መቶ አመት የተፃፈ መፅሀፍ እያነበብሽ ከምትሽኮረመሚ የእውነት ሮማንስ ላሳይሽ" አለች
የወሰነችው ነገር እንደሆነ ስለሚያስታውቅ ምንም ብል ስለማይቀርልኝ "የት ነው የምንሄደው?" አልኳት
"ኤሚ ልጋብዝሽ ብሎኝ ነው ብቻዬን መሄድ ስለደበረኝ ነው በዛ ላይ ፏ ብዬ ስወጣ ወዴት ነው ከምባል አብረን ስንሆን ፈታ ልንል ነው ብንል ራሱ ያምኑናል አይመስልሽም"
"እሺ ግን..."
"ችግር የለም ልብስሽን ሜካፕ ምናምን እኔ አለሁ ዋናው እሺ ማለትሽ ነው" ብላ እየሮጠች ሄደች
....
ሊያና
እንዳልኩትም ፏ ብለን ስንወጣ አባ የጥርጣሬ አስተያየቱ አልቀረልንም። ሆ! እና መኝታ ቤት ውስጥ ተወሽቀን ባል የምናገኘው በመስኮት አንኳኩቶ ሲመጣ ነው?
ኤሚ text ላከልኝ "እንደምንም አሳምኜው ነው የመጣው መነጫነጭ ጀምሯል አፍጥኑት" ይላል "ኤሚ ነው አይደል?" አለች አና ሲሰለቻት እንደምትሆነው ፊቷን አጨፍግጋ "ከኤሚዬ ውጪ ማን ሊሆን ይችላል ብለሽ ነው?" አልኳት
"ሞዛዞች" አለችና "እኔ እኮ ያልገባኝ እናንተ ለምትገናኙት የኔ መልበስ ምን ይሉታል"
"እና እንደዛ መስለሽ ከኔ ጋር ልትወጪ ነበር የፈለግሽው" እየተጨቃጨቅን ደረስን እና ወደካፌው ስንሄድ ኤሚን አየሁት። ቆይ በየቀኑ እየተገናኘን ባየሁት ቁጥር ልቤን ምን አዘለላት?
"ማንን ነው ከኤሚ ጋር የማየው?" ቆነጠጠቺኝ "እኔንጃ ማነው?" አልኳት ከኤሚ ፊት ለኛ ጀርባውን ሰጥቶ ነበር የተቀመጠው
"አንቺ ከሀዲ ሲጀመር አውቀሽ ነዋ ያመጣሺኝ?" ቆንጥጣ ጨረሰቺኝ አጠገባቸው ስንደርስ እኔ ኤሚ ላይ ተጠምጥሜ ሳበቃ አጠገቡ ተቀመጥኩ
አና ጨብጣው አጠገቡ ስትቀመጥ ሁለቱም ወደኛ በዛቻ አስተያየት ያፈጡብናል። ብዙም ሳይቆዩ "መፅሀፍህን አነበብኩት እኮ" አለችው ከዛ በኋላ "እንዴት ነው ያማረብሽ ባክሽ" ሲል ኤሚ መኖራቸውንም ረሳሁት
...
ኪራኮዝ
ያለምክንያት በእኩለ ቀን አንቀዥቅዦ እንደማያስመጣኝ አውቄያለሁ ግን እሷን ሊያገናኙን ኤሚና ሊያና እዚህ ርቀት ድረስ ይሄዳሉ ብዬ አልገመትኩም።
እኔ እንደምመጣ እንዳላወቀች ግልፅ ነው። እንዴት ስትደነባበር እንደነበረ ኤሚ ጥርሱን ገጥሞ ሲነግረኝ ነበር።
ከግጥም ምሽቱ ቀን በላይ አምሮባታል። ታናናሾቻችን እኛን ለማገናኘት የጠነሰሱት ባይሆን ነፃ ሆነን ልናወራ እንችል ይሆን ይሆናል። ምናልባት ምቾት የሚነሳት ሁኔታ ላይ እንደሆነች ልጠይቃት ስል "መፅሀፍህን አነበብኩት እኮ" አለች ፈገግ ብላ
እንደዚህ ፈገግ ብላ ጠላሁት አትለኝም ብዬ "ወደድሽው?" አልኳት "በጣም! እኔ እኮ ከመቶ አመት በፊት ተፅፎ እንደዚህ ተመሳሳይ ስሜት ማስተናገዳችን የስነፅሁፍ ውበት ይመስለኛል"
"ውይ በጣም! ሰው እንዳለ ሙሉ ሰሜቱ የሚታይበት መሆኑ ሰው መሆን እስካላቆምን ድረስ relate የምናደርገው ነገር ማግኘት አይቀርም" አልኳት
"አንተስ አነበብከው?" አለች "አዎ እንደፈራሁት አይደለም የዘንድሮ የፍቅር ልብወለዶች በተለይ የእንግሊዘኛ መፅሀፎች የአኒሜሽን እና የደማቅ ቀለማት የመፅሀፍ ሽፋን መፅሀፉ ሳይነበብ እንዲናቅ ያደርገዋል። አልዋሽሽም እንዳልጠላው ፈርቼ ነበር ግን ታሪኩ ለክፉ አይሰጥም"
"ከሽፋኑ ውጪ ምኑን ነው የጠላኸው?" ለክርክር ተዘጋጅታለች
"ሙሉ መፅሀፉ ስለሁለት ሰዎች አብሮ መሆን አለመሆን ሽኩቻ ብቻ ባይሆን ጥሩ ነበር። ትንሽ ሴራ ወይ የሆነ ነገር ቢኖረው ሙሉ ትኩረቱ የፍቅር ታሪኩ መሆኑ ነው ያልወደድኩት" አልኳት ለመልስ ምቷ ራሴን እያዘጋጀሁ
"ለምን? የፍቅር ታሪክ ብቻውን መፅሀፍ መሆን አይችልም? ሴራ ምናምን የምትፈልግ ከሆነ ሌላ መፅሀፍ ገዝተህ አንብብ" ብላ ፊቷን ወደነ ኤሚ አዞረች
አብሬያት ስዞር እንዳያቋርጡን እየጠበቁ ነበር። "በርሀብ ልሞት እኮ ነው እንብላና ትጨቃጨቃላችሁ" አለች ሊያ
✍ናኒ
እኔ ይሄ ሁሉ ቃላት ስፅፍ እናንተ አንዴ react ማድረግ አይከብዳችሁም አይደል?
https://t.me/justhoughtsss | 853 |
| 3 | Немає тексту... | 792 |
| 4 | file_200690 | 777 |
| 5 | ገበያ ለመሄድ ጊዜ ለሌላችሁ ሰዎች ይኸው መፍትሄ
በ0923516190 መደወል ብቻ ግልግል ማለት አይደል? | 579 |
| 6 | ሊያና
እማዬን እንደዛ እልል ያስባላት ዜና ምን አይነት ዱብ እዳ እንደሆነብኝ የሚያውቅ አለ? በተለይ የኤሚ አኳኋን፣ ስብር አባባሉ አላስችል አለኝ።
ታሪክ ራሱንም እየደገመ መሰለኝ ከአመታት በፊት እንደሆንነው... በፀጥታ ተሸኛኝተን ቤት ስገባ እማዬና አባዬ ሲኳረፉ እንደሚሆኑት እሷም የምታነብበት ክፍል እሱም ንድፉን የሚሰራበት ክፍል ገብተው መሸገዋል።
ልነፋረቅባት አና ጋር ስሄድ ትራሷን አቅፋ እየተንከባለለች ነው። የሚጋባ ሳቅ እየሳቀች "ሊ ምን እንዳደረገ አታውቂም እሱም አያውቅም ይሄ ለኔ ምን ማለት እንደሆነ የሚያውቅ ሰው አለ?" አለች መፅሀፍ አቅፋ
"ምንድነው መፅሃፍ እያነበብሽ ነው?" አልኳት
የያዘችውን መፅሀፍ ቀና አድርጋ አሳየችኝ One Hundred Love Sonnets by Pablio Neruda ይላል
"መፅሀፍ ገዛልኝ እሱ ነው የሚገርምሽ?" ልቤን ማንጠልጠሏ ነው "ሌላ ምን አደረገልሽ?" ቢያንስ ገፀባህርይ አይደለም እንደዚህ የሚያስፈነጥዛት
"ደብዳቤ ፅፎልኛል። የምወደውን የpablo nerudaን መፅሀፍ መግዛቱ ሳያንስ በአማርኛ እኮ ነው ደብዳቤውን የፃፈው እዪው ቃላት አጣጣሉ ሲያምር የሰዓሊ እኮ ነው የሚመስለው"
"የኔም የኤሚም ፅሁፍ አያምርም" አልኳት ሳበሳጫት እሷ እቴ "የምወደው የግጥም መድብል ነው ስለግጥም ያለሽን አቋም ያስቀይርሽ ይሆናል" ብሎ ነው የፃፈው ብላ አነበበችልኝ። እንደዚህ እንዳስደሰታት ቢያውቅ ምናለበት
...
ኦዚያን
እቤት እንደገባ የእለቱን ዜናዎች ሲከፍት ሶስተኛ ግድያ መፈፀሙ የዜናዎቹን አውታሮች እንዳጨናነቀ አየ። ከግድያውም ከተገኘውም ደብዳቤ በላይ ትኩረቱን የያዘው የሟች የትውልድ ቦታ ነበር። ፔሊ
✍ናኒ
ይቀጥል የምትሉ ብቻ react እያደረጋችሁ
https://t.me/justhoughtsss | 1 264 |
| 7 | ክፍል 11
ምናልባት
የሌሎቹን ባላውቅም እኔ ግን አድካሚ ቀን ነው የነበረኝ። እንደሌላ ቤተሰብ የውሸት የጓጓን አስመስለን "ውሎ እንዴት ነበር ታድያ" አንባባልም ምክንያቱም ሁላችንም ከስራ የዘለለ ህይወት የለንም
የአባዬን ማባርያ የሌለው ተጣጣፊ ኮንክሪት ወሬ ወይም አዲስ ገበያ ላይ ስለዋለ ቀለም ሊያ ስታወራ ስለማይገባን ይሰለቸናል። እማዬ ስለታካሚዎቿ ማውራት በህግ ትከለከላለች እኔ ደግሞ አንጀቱ ተዘርግፎ እግሩ ተቆርጦ ከማለት የዘለለ አስደሳች ውሎ ኖሮኝ አያውቅም።
ለዛ ነው ራት ስንበላ ብዙውን ጊዜ ምግብ ቤት ውስጥ ጠረጴዛ መጋራት እንዳለበት የማይተዋወቅ ሰው የምንሆነው
ይሄንና ምን እንደሆነ ባላውቅም ጭንቅላቴ ያንንም እያነሳ እየጣለ ጭንቅላቴ ይባትላል። አባ ዜናው ላይ ተመስጧል።
ቀና ስል ሊያና ፈገግ ብላ ጠቀሰቺኝ። የሆነ ነገር ስታቅድ ነው እንደዚህ የምትሆነው "ስሙማ" አለች እማን ከሀሳቧ አባን ከዜናው እያደናቀፈቻቸው
"እ" ስትል እማ
"ሰበር ዜና" የሚል ድምፅ የሁላችንንም ትኩረት ሰረቀው "ቆይ ቆይ አንዴ አዳምጡ" ብሎ አባ ድምፁን ጨመረው
"በሁለት ወር ውስጥ የተሰራው ከተማ የሚጠናቀቅ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታውቋል። ከፔሊ የመጣችሁ ሰዎች በፈቃደኝነት ወደዛ ሄዳችሁ መኖር የምትችሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።"
"እልልል" እማ አቀለጠችው "ተመስገን ከዚህ የተረገመ ከተማ እንደዚህ በቀላሉ ልንወጣ ነው እልልል"
ሊያና ፊቷ ገርጥቷል አባ ምንም ስሜት አይታይበትም እሺ እኔ ምን እንደዚህ ልቤን አራደው?
"ሊያ ምን ልትነግሪን ነበር?" አለ አባ ምንም እንዳልተፈጠረ
"እነእትዬ ትሬዛን ነገ ማታ ምሳ እንድንጠራቸው ነበር" አለች ድምጿ ፈዝዞ
"እንችላለን ምን ችግር አለው ስለጠራችን ውለታ የዋለችልን እንዳይመስላት እንጂ አብሮ ለመኖር የሚያስገድደን ነገር የለም ልንወጣ አይደለ" ደስታዋ በድምጿ በፊቷ ይንፀባረቃል።
እማ እዚህ መኖራችንን እንደዚህ ጠልታው ነበር?
...
ኤሞን
ሰዓቱ ለሁለት ሩብ ጉዳይ ይላል። ቆይ ለእራት ግበዣ ስንት ሰዓት መሄድ ነው ትክክል? አንድ ሰዓት ገና ላይዘጋጅ ይችላል ሶስት ሰዓት እንደመቅረት ይቆጠር ይሆናል።
ስለዚህ ሁለት ሰዓት ነው። በሩብ ደቂቃ ውስጥ ብንሄድ ትክክል ስለመሰለኝ ተዘጋጅቼ ጨርሻለሁ። "ይሄ ልጅ ይቆያል እንዴ? በጣም መሸ እኮ" አለች እማ እንደልማዷ እየተጨናነቀች
"እየደረስኩ ነው ብሏል አትጨናነቂ" አልኳትና ወደሳሎን ስሄድ እሱ ሲያንኳኳ ተገጣጠምን። ስከፍትለት
"አላመሸሁም አይደል? ጥሪ ኖሮ ማርፈድ ልክ አይደለም" እያለ እየተጣደፈ ወደክፍሉ ገባ
አቻኩሎ ደብቆ ሊያስገባው የፈለገውን መፅሐፍ አይቼበታለሁ። ተከትዬው ክፍሉ ስገባ ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦታል።
"እኔ እኮ አላምንም"አልኩት መፅሀፉን አገላብጬ እያየሁ
እንዳልሰማኝ ልብሱን ይቀይራል። "የከተማዋ ጫፍ ድረስ ሄደህ ገዛኸው?" ሌላ ቦታ ማግኘት አቅቶት የተወው መፅሃፍ ነው።
"ምን ችግር አለው?" ለክት ብቻ የሚያወጣትን ሽቶ ኮሌታው ላይ እየቀባ
"ለሊያ እህት ነው አይደል?" አልመለሰልኝም
"እንውጣ ልጆች" እማ ተጣራች
"ጨርሰናል መጣን" መብራቱን እላዬ ላይ አጥፍቶ ወጣ ያመለጠኝ መስሎት
...
ኪራኮስ
በሩን ስናንኳኳ "መጡ መጡ መጡ" የሚል ድምፅ ከውስጥ ሰማሁ። የከፈተችው አናን የምትመስል ሴት ናት እህቷ ናት ማለት ነው። እየሮጠች መጥታ እንደከፈተች ያስታውቃል።
"እንኳን ደህና መጣችሁ" አለች ኤሚ በአይኖቿ እያቀፈችው። ደስ ሲሉ
ስንገባ አና እና እናቷ ምግብ እያቀራረቡ ነበር። እንደነገሩ ያዝያዘችው ፀጉሯ ታጥፎ ራሱ አለሁ ይላል። ከፀጉር ማስያዣው ጥቂት ወጥቶ ጀርባዋ ላይ ተኝቷል። ሁሉም ሰላም ሲባባል ውስጥ ነበረች። አባታቸው ኑ ተቀመጡ ብሎ ገና ከመግባታችን የምግብ ጠረጴዛው ጋር ወሰደን።
አባትየውና እና እናትየው ትዕዩ ተቀመጡ። ኤሚና ሊያና ደግሞ በግራ በኩል ተቀመጡ ከኤሚ አጠገብ ማሚ ተቀመጠች ከአባታቸው አጠገብ መሆኑ ነው።
ኦዚያን እናታቸው በስተቀኝ ተቀምጦ ወሬ ጀምረዋል። እኛ አልሰማ የምንለውን ወሬ ከእሷ ጋር ሲሆን እኩል በእኩል ሲያወሩ ደስ ይለኛል። ሁሉም ሰው እንደራሱ ሆኖ የሚያወራው ሰው ይፈልጋል አይደል?
ኤሚና ሊያና ምንም እንደማይተዋወቅ ሰው የሚያደርጉት ጥረት ያስቀኛል። አይነስውር የሚያየው መሳሳብ በመላሀቸው ኖሮ ለደቂቃ መነጣጠል ሳይፈልጉ ወላጆቻቸው እንዳያውቁባቸው የሚያደርጉት ጥረት ረብ የለሽ ይሆንብኛል። የፍቅራቸው አምላክ አይናቸውን ጋርዶላቸው እንጂ አልቆላቸው ነበር።
አቀራርባ ስትጨርስ እና ስትመጣ የነበረው ቦታ በኔና በኦዚ መሀል ያለው ወንበር ብቻ ነበር። አጋጣሚ መሆን አለበት (አይደል?)
ስትቀመጥ ለስላሳ ሽቶዋ አወደኝ። የግጥም ምሽቱ ቀን የተቀባችው ነው። በትግል ከጭንቅላቴ ያወጣሁትን አደሰችልኝ።
"በሁለት ወር ውስጥ መውጣት ትችላላችሁ አሉ ደግሞ አይደል" እማ ፀጥታውን አፈረሰችው
ጋሽ ኤስሮም መልስ እየመለሰላት ነው። ግዴታ እንዳልሆነና መሄድ ከፈለጉ ብቻ እንደሚሄዱ እየነገራት ነው
ከዛ በኋላ ያሉትን አልሰማሁም መብረቅ እንደወረደበት ደርቄ ቀረሁ። ሁለት ወር? ስምንት ሀሙስ? ከዛ በኋላ እንደልማዴ ብቻዬን ልሄድ ነው።
ፊቴ ላይም ድንጋጤዬ ታይቷል መሰል "አባ ምነው አመመህ እንዴ?" ስትል ማሚ "ኧረ ትንሽ ብርድ አግኝቶኛል መሰለኝ ውጋት ይዞኝ ነው አልኳት ደህናውን ወገቤን ደግፌ
"አና እኮ ነርስ ናት እሷን ጠይቃት መድሀኒቱን" አለ አባታቸው ኤስሮም "አባ ደሞ ወጌሻ መሰልኩህ እንዴ"
ስትለው በሳቅ ተቀበልናት።
የእሷ ወንበር ላይ ስደገፍ ትከሻዋን ዳበስ አድርጌው አለፍኩ ፈገግ ያለችበትን ከንፈሯን ነክሳ ስታስቆመው አይቻታለሁ። እጄን እዛው ተውኩት ትከሻዋ ጋር ጉንጮቿ እየቀሉ ነው።
"ሌላ ምን አዲስ ነገር አለ?" ስትለው የእነአና እናት እትዬ ማሊካ "ምንም የለም ያው የከተማዋ ነባር ነዋሪዎች ላይ ብቻ ስለሆነ እየተፈፀመ ያለው የተገመተው አዲስ ከሰፈሩት ሰዎች መሀል ሊሆን ይችላል እየተባለ ነው" አላት ቆይ ይሄ ልጅ ያለዚህም ጉዳይ ስራ የለውም እንዴ?
"ለዛ ነው አይደል በየመንገዱ የሚገላምጠኝ ሰው በዝቷል" አለች አና ቀጥላም እህቷ ከሌሎች ጎረቤቶች ስለገጠማት ዘለፋ ነገረችን
ማን አባቱ ነው የሚገላምጣት
"መፅሀፉን ገዝቼልሀለው እሰጥሀለው ስትወጡ" አለች ለሌላ ለማንም በማይሰማ ድምፅ
"ደስ ይለኛል"
ከዛ በኋላ ምሽቱ ያለቃላት ልውውጥ ከእሷ ጋር ስናወራ ቀና ብላ ባየቺኝ ቁጥር ልቤ ብትንትኑ እየወጣ፣
ማሚ እና ጋሽ ኤስሮም ስለሆነ አዲስ ተክል ቅጠል አበቃቀል ሲያወሩ ኤሚና ሊያ በዝምታ ሲቆዝሙ እናታቸውና ኦዚ ስለግድያ አይነቶች ሲዘረዝሩ አምሽተን
"ሰዓቱ እንዴት ሄዷል ባካችሁ" ስትል እናታቸው ሂዱ ማለቷ እንደሆነ ገብቶን ተነሳን። ልንወጣ ስንል ጥንድ ጥንድ ሆነው ሲያወሩ በነበሩበት አኳኋን ወጡ።
ልብሴን ጎተት አድርጋ ስታስቀረኝ ለመፅሀፉ መሆኑ ገብቶኝ ሌሎቹ ወጥተው እኛ ስንቀር መፅሀፉን ሮጣ አምጥታ ሰጠቺኝ።
ሰማያዊ የሽፋን ገፅ በቢጫ ፊደላት ርዕስ ያለው መፅሀፍ ነው። መቸገሬ ነው እንግዲ። እኔም ስገባ ከሰቀልኩት ከኮቴ ኪስ ውስጥ የገዛሁላትን መፅሀፍ ሰጠኋት። ፊቷ ላይ የነበረው ያለማመን እና የደስታ ጥግ ደጋግመህ መፅሀፍ ግዛላት የሚል ምኞት አሳደረብኝ።
ሳብ አድርጌ ለጥቂት ሰከንዶች ካቀፍቋት በኋላ ሀሙስ እንገናኛለን ብያት እዛው ደርቃ በቆመችበት ወጣሁ ትኩረት ከመሳባችን በፊት።
... | 1 110 |
| 8 | እማዬን እንደዛ እልል ያስባላት ዜና ምን አይነት ዱብ እዳ እንደሆነብኝ የሚያውቅ አለ? በተለይ የኤሚ አኳኋን፣ ስብር አባባሉ አላስችል አለኝ።
ታሪክ ራሱንም እየደገመ መሰለኝ ከአመታት በፊት እንደሆንነው... በፀጥታ ተሸኛኝተን ቤት ስገባ እማዬና አባዬ ሲኳረፉ እንደሚሆኑት እሷም የምታነብበት ክፍል እሱም ንድፉን የሚሰራበት ክፍል ገብተው መሸገዋል።
ልነፋረቅባት አና ጋር ስሄድ ትራሷን አቅፋ እየተንከባለለች ነው። የሚጋባ ሳቅ እየሳቀች "ሊ ምን እንዳደረገ አታውቂም እሱም አያውቅም ይሄ ለኔ ምን ማለት እንደሆነ የሚያውቅ ሰው አለ?" አለች መፅሀፍ አቅፋ
"ምንድነው መፅሃፍ እያነበብሽ ነው?" አልኳት
የያዘችውን መፅሀፍ ቀና አድርጋ አሳየችኝ One Hundred Love Sonnets by Pablio Neruda ይላል
"መፅሀፍ ገዛልኝ እሱ ነው የሚገርምሽ?" ልቤን ማንጠልጠሏ ነው "ሌላ ምን አደረገልሽ?" ቢያንስ ገፀባህርይ አይደለም እንደዚህ የሚያስፈነጥዛት
"ደብዳቤ ፅፎልኛል። የምወደውን የpablo nerudaን መፅሀፍ መግዛቱ ሳያንስ በአማርኛ እኮ ነው ደብዳቤውን የፃፈው እዪው ቃላት አጣጣሉ ሲያምር የሰዓሊ እኮ ነው የሚመስለው"
"የኔም የኤሚም ፅሁፍ አያምርም" አልኳት ሳበሳጫት እሷ እቴ "የምወደው የግጥም መድብል ነው ስለግጥም ያለሽን አቋም ያስቀይርሽ ይሆናል" ብሎ ነው የፃፈው ብላ አነበበችልኝ። እንደዚህ እንዳስደሰታት ቢያውቅ ምናለበት
...
ኦዚያን
እቤት እንደገባ የእለቱን ዜናዎች ሲከፍት ሶስተኛ ግድያ መፈፀሙ የዜናዎቹን አውታሮች እንዳጨናነቀ አየ። ከግድያውም ከተገኘውም ደብዳቤ በላይ ትኩረቱን የያዘው የሟች የትውልድ ቦታ ነበር። ፔሊ
✍ናኒ
ይቀጥል የምትሉ ብቻ react እያደረጋችሁ
https://t.me/justhoughtsss | 3 |
| 9 | Немає тексту... | 966 |
| 10 | ክፍል 11
ምናልባት
የሌሎቹን ባላውቅም እኔ ግን አድካሚ ቀን ነው የነበረኝ። እንደሌላ ቤተሰብ የውሸት የጓጓን አስመስለን "ውሎ እንዴት ነበር ታድያ" አንባባልም ምክንያቱም ሁላችንም ከስራ የዘለለ ህይወት የለንም
የአባዬን ማባርያ የሌለው ተጣጣፊ ኮንክሪት ወሬ ወይም አዲስ ገበያ ላይ ስለዋለ ቀለም ሊያ ስታወራ ስለማይገባን ይሰለቸናል። እማዬ ስለታካሚዎቿ ማውራት በህግ ትከለከላለች እኔ ደግሞ አንጀቱ ተዘርግፎ እግሩ ተቆርጦ ከማለት የዘለለ አስደሳች ውሎ ኖሮኝ አያውቅም።
ለዛ ነው ራት ስንበላ ብዙውን ጊዜ ምግብ ቤት ውስጥ ጠረጴዛ መጋራት እንዳለበት የማይተዋወቅ ሰው የምንሆነው
ይሄንና ምን እንደሆነ ባላውቅም ጭንቅላቴ ያንንም እያነሳ እየጣለ ጭንቅላቴ ይባትላል። አባ ዜናው ላይ ተመስጧል።
ቀና ስል ሊያና ፈገግ ብላ ጠቀሰቺኝ። የሆነ ነገር ስታቅድ ነው እንደዚህ የምትሆነው "ስሙማ" አለች እማን ከሀሳቧ አባን ከዜናው እያደናቀፈቻቸው
"እ" ስትል እማ
"ሰበር ዜና" የሚል ድምፅ የሁላችንንም ትኩረት ሰረቀው "ቆይ ቆይ አንዴ አዳምጡ" ብሎ አባ ድምፁን ጨመረው
"በሁለት ወር ውስጥ የተሰራው ከተማ የሚጠናቀቅ መሆኑን የከተማው አስተዳደር አስታውቋል። ከፔሊ የመጣችሁ ሰዎች በፈቃደኝነት ወደዛ ሄዳችሁ መኖር የምትችሉ መሆኑንም አስታውቀዋል።"
"እልልል" እማ አቀለጠችው "ተመስገን ከዚህ የተረገመ ከተማ እንደዚህ በቀላሉ ልንወጣ ነው እልልል"
ሊያና ፊቷ ገርጥቷል አባ ምንም ስሜት አይታይበትም እሺ እኔ ምን እንደዚህ ልቤን አራደው?
"ሊያ ምን ልትነግሪን ነበር?" አለ አባ ምንም እንዳልተፈጠረ
"እነእትዬ ትሬዛን ነገ ማታ ምሳ እንድንጠራቸው ነበር" አለች ድምጿ ፈዝዞ
"እንችላለን ምን ችግር አለው ስለጠራችን ውለታ የዋለችልን እንዳይመስላት እንጂ አብሮ ለመኖር የሚያስገድደን ነገር የለም ልንወጣ አይደለ" ደስታዋ በድምጿ በፊቷ ይንፀባረቃል።
እማ እዚህ መኖራችንን እንደዚህ ጠልታው ነበር?
...
ኤሞን
ሰዓቱ ለሁለት ሩብ ጉዳይ ይላል። ቆይ ለእራት ግበዣ ስንት ሰዓት መሄድ ነው ትክክል? አንድ ሰዓት ገና ላይዘጋጅ ይችላል ሶስት ሰዓት እንደመቅረት ይቆጠር ይሆናል።
ስለዚህ ሁለት ሰዓት ነው። በሩብ ደቂቃ ውስጥ ብንሄድ ትክክል ስለመሰለኝ ተዘጋጅቼ ጨርሻለሁ። "ይሄ ልጅ ይቆያል እንዴ? በጣም መሸ እኮ" አለች እማ እንደልማዷ እየተጨናነቀች
"እየደረስኩ ነው ብሏል አትጨናነቂ" አልኳትና ወደሳሎን ስሄድ እሱ ሲያንኳኳ ተገጣጠምን። ስከፍትለት
"አላመሸሁም አይደል? ጥሪ ኖሮ ማርፈድ ልክ አይደለም" እያለ እየተጣደፈ ወደክፍሉ ገባ
አቻኩሎ ደብቆ ሊያስገባው የፈለገውን መፅሐፍ አይቼበታለሁ። ተከትዬው ክፍሉ ስገባ ጠረጴዛው ላይ አስቀምጦታል።
"እኔ እኮ አላምንም"አልኩት መፅሀፉን አገላብጬ እያየሁ
እንዳልሰማኝ ልብሱን ይቀይራል። "የከተማዋ ጫፍ ድረስ ሄደህ ገዛኸው?" ሌላ ቦታ ማግኘት አቅቶት የተወው መፅሃፍ ነው።
"ምን ችግር አለው?" ለክት ብቻ የሚያወጣትን ሽቶ ኮሌታው ላይ እየቀባ
"ለሊያ እህት ነው አይደል?" አልመለሰልኝም
"እንውጣ ልጆች" እማ ተጣራች
"ጨርሰናል መጣን" መብራቱን እላዬ ላይ አጥፍቶ ወጣ ያመለጠኝ መስሎት
...
ኪራኮስ
በሩን ስናንኳኳ "መጡ መጡ መጡ" የሚል ድምፅ ከውስጥ ሰማሁ። የከፈተችው አናን የምትመስል ሴት ናት እህቷ ናት ማለት ነው። እየሮጠች መጥታ እንደከፈተች ያስታውቃል።
"እንኳን ደህና መጣችሁ" አለች ኤሚ በአይኖቿ እያቀፈችው። ደስ ሲሉ
ስንገባ አና እና እናቷ ምግብ እያቀራረቡ ነበር። እንደነገሩ ያዝያዘችው ፀጉሯ ታጥፎ ራሱ አለሁ ይላል። ከፀጉር ማስያዣው ጥቂት ወጥቶ ጀርባዋ ላይ ተኝቷል። ሁሉም ሰላም ሲባባል ውስጥ ነበረች። አባታቸው ኑ ተቀመጡ ብሎ ገና ከመግባታችን የምግብ ጠረጴዛው ጋር ወሰደን።
አባትየውና እና እናትየው ትዕዩ ተቀመጡ። ኤሚና ሊያና ደግሞ በግራ በኩል ተቀመጡ ከኤሚ አጠገብ ማሚ ተቀመጠች ከአባታቸው አጠገብ መሆኑ ነው።
ኦዚያን እናታቸው በስተቀኝ ተቀምጦ ወሬ ጀምረዋል። እኛ አልሰማ የምንለውን ወሬ ከእሷ ጋር ሲሆን እኩል በእኩል ሲያወሩ ደስ ይለኛል። ሁሉም ሰው እንደራሱ ሆኖ የሚያወራው ሰው ይፈልጋል አይደል?
ኤሚና ሊያና ምንም እንደማይተዋወቅ ሰው የሚያደርጉት ጥረት ያስቀኛል። አይነስውር የሚያየው መሳሳብ በመላሀቸው ኖሮ ለደቂቃ መነጣጠል ሳይፈልጉ ወላጆቻቸው እንዳያውቁባቸው የሚያደርጉት ጥረት ረብ የለሽ ይሆንብኛል። የፍቅራቸው አምላክ አይናቸውን ጋርዶላቸው እንጂ አልቆላቸው ነበር።
አቀራርባ ስትጨርስ እና ስትመጣ የነበረው ቦታ በኔና በኦዚ መሀል ያለው ወንበር ብቻ ነበር። አጋጣሚ መሆን አለበት (አይደል?)
ስትቀመጥ ለስላሳ ሽቶዋ አወደኝ። የግጥም ምሽቱ ቀን የተቀባችው ነው። በትግል ከጭንቅላቴ ያወጣሁትን አደሰችልኝ።
"በሁለት ወር ውስጥ መውጣት ትችላላችሁ አሉ ደግሞ አይደል" እማ ፀጥታውን አፈረሰችው
ጋሽ ኤስሮም መልስ እየመለሰላት ነው። ግዴታ እንዳልሆነና መሄድ ከፈለጉ ብቻ እንደሚሄዱ እየነገራት ነው
ከዛ በኋላ ያሉትን አልሰማሁም መብረቅ እንደወረደበት ደርቄ ቀረሁ። ሁለት ወር? ስምንት ሀሙስ? ከዛ በኋላ እንደልማዴ ብቻዬን ልሄድ ነው።
ፊቴ ላይም ድንጋጤዬ ታይቷል መሰል "አባ ምነው አመመህ እንዴ?" ስትል ማሚ "ኧረ ትንሽ ብርድ አግኝቶኛል መሰለኝ ውጋት ይዞኝ ነው አልኳት ደህናውን ወገቤን ደግፌ
"አና እኮ ነርስ ናት እሷን ጠይቃት መድሀኒቱን" አለ አባታቸው ኤስሮም "አባ ደሞ ወጌሻ መሰልኩህ እንዴ"
ስትለው በሳቅ ተቀበልናት።
የእሷ ወንበር ላይ ስደገፍ ትከሻዋን ዳበስ አድርጌው አለፍኩ ፈገግ ያለችበትን ከንፈሯን ነክሳ ስታስቆመው አይቻታለሁ። እጄን እዛው ተውኩት ትከሻዋ ጋር ጉንጮቿ እየቀሉ ነው።
"ሌላ ምን አዲስ ነገር አለ?" ስትለው የእነአና እናት እትዬ ማሊካ "ምንም የለም ያው የከተማዋ ነባር ነዋሪዎች ላይ ብቻ ስለሆነ እየተፈፀመ ያለው የተገመተው አዲስ ከሰፈሩት ሰዎች መሀል ሊሆን ይችላል እየተባለ ነው" አላት ቆይ ይሄ ልጅ ያለዚህም ጉዳይ ስራ የለውም እንዴ?
"ለዛ ነው አይደል በየመንገዱ የሚገላምጠኝ ሰው በዝቷል" አለች አና ቀጥላም እህቷ ከሌሎች ጎረቤቶች ስለገጠማት ዘለፋ ነገረችን
ማን አባቱ ነው የሚገላምጣት
"መፅሀፉን ገዝቼልሀለው እሰጥሀለው ስትወጡ" አለች ለሌላ ለማንም በማይሰማ ድምፅ
"ደስ ይለኛል"
ከዛ በኋላ ምሽቱ ያለቃላት ልውውጥ ከእሷ ጋር ስናወራ ቀና ብላ ባየቺኝ ቁጥር ልቤ ብትንትኑ እየወጣ፣
ማሚ እና ጋሽ ኤስሮም ስለሆነ አዲስ ተክል ቅጠል አበቃቀል ሲያወሩ ኤሚና ሊያ በዝምታ ሲቆዝሙ እናታቸውና ኦዚ ስለግድያ አይነቶች ሲዘረዝሩ አምሽተን
"ሰዓቱ እንዴት ሄዷል ባካችሁ" ስትል እናታቸው ሂዱ ማለቷ እንደሆነ ገብቶን ተነሳን። ልንወጣ ስንል ጥንድ ጥንድ ሆነው ሲያወሩ በነበሩበት አኳኋን ወጡ።
ልብሴን ጎተት አድርጋ ስታስቀረኝ ለመፅሀፉ መሆኑ ገብቶኝ ሌሎቹ ወጥተው እኛ ስንቀር መፅሀፉን ሮጣ አምጥታ ሰጠቺኝ።
ሰማያዊ የሽፋን ገፅ በቢጫ ፊደላት ርዕስ ያለው መፅሀፍ ነው። መቸገሬ ነው እንግዲ። እኔም ስገባ ከሰቀልኩት ከኮቴ ኪስ ውስጥ የገዛሁላትን መፅሀፍ ሰጠኋት። ፊቷ ላይ የነበረው ያለማመን እና የደስታ ጥግ ደጋግመህ መፅሀፍ ግዛላት የሚል ምኞት አሳደረብኝ።
ሳብ አድርጌ ለጥቂት ሰከንዶች ካቀፍቋት በኋላ ሀሙስ እንገናኛለን ብያት እዛው ደርቃ በቆመችበት ወጣሁ ትኩረት ከመሳባችን በፊት።
...
ሊያና | 21 |
| 11 | 7088fdf3-11ca-4cfa-b2a5-5631cf6a4952.mp3 | 1 050 |
| 12 | @Jaymasangula_bot | info | 1 |
| 13 | ስለካራሞን ብዙ የማወራው ስላለኝ አንድ ቀን በሰፊው እነግራችኋለሁ። ለዛሬ ግን በጥቂቱ
ካራሞን ከዴርቶጋዳ በኋላ እጅግ የወደድኩት የአማርኛ fantasy ሆኖ ተገኝቷል። የሚሰለች አንድ መስመር ባለመኖሩ በአንድ ቀን ነው ፉት ያደረግኩት። ከcharacter development ጀምሮ እስከ world building እንከን የለሽ ሆኖ አግኝቼዋለሁ። plot twist ለምትወዱ ሰዎች ትክክለኛው መፅሀፍ ነው
እና ገዝታችሁ አንብቡት በጣም enjoy እንደምታደርጉት አልጠራጠርም ያነበባችሁት ደግሞ ቅዳሜ ጃፋር ጋር ሄዳችሁ መፅሀፋችሁን አስፈርሙ | 1 268 |
| 14 | የፊታችን ቅዳሜ የመጽሐፍ ፊርማ ስነስርአት !
በጃዕፈር መጻሕፍት መደብር !
" ካራሞን " | 1 099 |
| 15 | እንበልና...
ነገ ናኒ የመጀመሪያ መፅሀፏ ታትሞ ጃፋር እየተሸጠ ነው ብትባሉ ስንቶቻችሁ ትገዛላችሁ? | 1 353 |
| 16 | ክፍል 10
ኤስሮም
በሩ ሲንኳኳ በባዶ ሳሎኑ ተስተጋብቶ ተጋኖ አስደነገጠኝ። የኔ ነገር ይኸው ነው አንድ ስራ ከጀመርኩ መመለሻ የለኝም። ስነሳ ወገቤ ሲንቋቋ ነው ብዙ እንደተቀመጥኩ የታወቀኝ።
ስከፍት ትሬዛ ትንሽዬ አበባ ከነማስቀመጫው ይዛ ቆማለች። አንዴ እሷን አንዴ አበባውን አፈራርቄ እያየሁ "እንዴት አደርሽ?" አልኳት
"እንዴት አደርሽ? ቀኑ ተጋምሷል እኮ! ምሳ አልበላህም ማለት ነው?" አለች በፈገግታ ታጅባ
ፀጉሯ ላይ የተሰመሩት ነጫጭ መስመሮች እና ፊቷን ከፈገግታዋ በኋላ የሚፈጠሩት ሽብሽቦች እንደሌላው ትልቅ ሰው አያጎሳቁላትም። ምናልባት ወጣት እያለች የነበራት ውበት እድሜ ቢታገለውም ሊያሸነው አልቻለም
ደግሞ የያዘችው አበባ ማማሩ
"አይገርምሽም! ሰዓቱን ራሱ አላየሁትም ነበር" አልኳት እያዛጋሁ
"ምነው እቤት ማንም የለም እንዴ?" ወደ ቤት አንገቷን እያማተረች
"ያው ስራ ሄደው ነው። ብቻዬን ነበርኩ" አልኳት
"እኔም ቡና የሚያጣጣኝ አጥቼ ደብሮኝ ነበር። ና እስኪ እንጫወታለን። የተከልካቸው አልፀድቅ እንዳሉህ ስላየሁ ነው። ይሄኛው በደንብ ይይዛል ሞኝ ነው" ብላ አበባውን ሰጠቺኝ
"እንዴት እንደማመሰግንሽ አላውቅም" አበባው አድጎ ዙርያውን ሲያለብሰው በአይነህሊናዬ እየሳልኩ
"የምን ምስጋና አመጣህብኝ ና ይልቅ" ብላኝ ሄደች።
ያመጣችልኝን አበባ በጥንቃቄ አስቀምጬ ቤቷ ስሄድ እጣኑ ቀድሞ ተቀበለኝ። ረከቦቱ ተዘርግቶ እንኳን ደህና መጣችሁ ይላል። ከረከቦቱ ፈትለፊት የተቀመጠው ቢጫ ኩኪስ የረሳሁትን ርሀቤን ቀሰቀሰው
"ጠረጴዛው ይሻሀል ወይስ እዛው እንብላ?" ብላ ወደተቀመጥኩበት ሶፋ እየጠቆመች
ቶሎ አልመለስኩላትም ጎረቤት እንደዚህ ነው ማለት ነው እያልኩ እየተገረምኩ ነበር
...
አናቤል
"ለቅሶ መሰለሽ እንዴ የሚወስድሽ ምንድነው እንደዚህ መጨላለም?" አለች ሊያ ፊልሟን አቋርጣ
ለሶስተኛ ጊዜ የቀየርኩትን ልብስ እያየሁ ተበሳጨሁ። "ወይ በቃ ልቅር? አልፈልግም ልበለው?" አልኳት። ከዚህ በላይ መጓጓትም ትኩረት መስጠትም አልፈልግም።
"እንዴዴ ያምሻል እንዴ? እኔ እኮ ፈካ ያለ ቀለል ያለ ነገር ልበሺ አልኩ እንጂ ቅሪ አልኩ? ቆይ መጣሁ" ብላ ወደቁምሳጥኔ ሄደች።
"በጣም የፈካ ነገር አልፈልግም በጣም የጓጓሁ እንዲመስለው አልፈልግም" አልኳት መስታወቱ ፊት ቆሜ የፀጉሬን አኳኋን እየመረጥኩ
"ግን እኮ ጓጉተሻል" አለች ጮክ ብላ "ዝም በይ"
አስታዋሽ ያስፈልገኛል እንዴ? ከሶስት ቀን በፊት እነሱ ቤት ለምሳ ተጠርተን ይዤሽ እሄዳለሁ ካለኝ ቀን ጀምሮ ሌላ ስለምን ማሰብ ችያለሁ?
ፈዛዛ ሮዝ ቀሚሷን ይዛ መጣችና አጠገቤ ቆመች "አርፈሽ ይሄንን ልበሺ" አለች አስታቅፋኝ ወደፊልሟ ተመለሰች
"ግን እኮ እጁ ባዶ ነው ስንመለስ ቢበርደኝስ? ጃኬቱን እንዲሰጠኝ እያስገደድኩት ቢመስልብኝስ?" አልኳት ቡዳ የሆነች ልጅ ቀሚሱን እንዴት እንደምወደውና እንደሚያሳምረኝ ታውቃለች
"እና ካፖርት ደርቢበትና ትንሽ ሮማንቲክ መሆኑን የሚያሳይበትን መንገድ አሳጪው" አለች እውነትም እድል መስጠት ያስፈልጋል እኮ!
በሩ ሲንኳኳ ወንዶቹ ቢያዩት ኧረ ንፁህ ፊቷን ናት የሚሉትን ሜካፕ ሊያ በስሱ እየቀባባቺኝ ነበር። "በቃ በቃሽ መጥቷል" አልኳት እየተወራጨሁ
"ቆይ ትንሽ ያንኳኳ በአንዴማ ይዞሽ አይሄድም አንድ እህቴን" አለች ፊቴን እንደሸራዋ እየተራቀቀችበት
"ሊያገባኝ መሰለሽ እንዴ date እንኳን እንዳልሆነ ታውቂያለሽ" አልኳት ውስጤ የሚፈልገው ሌላ ቢሆንም
"አንድ ሳይባል ሁለት አይባልም በይ ሂጂ ብዙ መዝረክረክሽን አታሳዪው አደራ እንዳታዋርጂኝ" ስትል ወደበሩ መሮጥ ጀምሬ ነበር
ትንፋሼን አረጋግቼ በሩን ለመክፈት ደቂቃ አልፈጀብኝም።ሳየው ደነገጥኩ። ወጥ ጥይምናው የጎደጎዱ አይኖቹ ዛሬ እንደተከረከመ የሚያስታውቅ ጠንካራ ፀጉሩ ብቻ ብፅፈው ብዬ የምመኘው ሰው መሰለኝ።
እሱም ዝም ብሎ እያጤነኝ ነው አይኖቹ ውስጥ አድናቆት አለ። ግን የአድናቆት ቃል አልወጣውም። ጫማዬን ሲያየው ትንሽ ታኮ አለው።
"በመኪና እንሂድ?" አለኝ እያስፈቀደኝም እየወሰነም በሚመስል ድምፅ "ሩቅ ነው እንዴ?" አልኩት የምሄድበትን ሳላውቅ ያውም በቅጡ ከማላውቀው ሰው ጋር ጉድ እኮ ነው!
"ኧረ ብዙ ሩቅ አይደለም ጫማሽ ምቾት እንዳይነሳሽ ብዬ ነው ቆይ መጣሁ" ብሎ መኪናውን አመጣውና ገባሁ። አምስት ደቂቃ በማትፈጀው ጉዞ በመንገዳችን ስላየናቸው ጥቂት መፅሀፍት ቤቶች እየነገረኝ ደረስን።
ከላዩ ቢሮዎች ያሉበት ህንፃ ወለል ላይ በቀን ኮፊ ሀውስ እንደሆነና ሀሙስ ሀሙስ ማታ ግን የግጥም ምሽቱ እንደሚዘጋጅ ነግሮኝ ገባን። ከመድረኩ ከሚመጣው ብርሀን ውጪ ሌላ ብርሀን ባለመኖሩ በጨለማ ከጀርባ ያሉት ወንበሮች ላይ ተቀመጥን።
ሶስት ሰዎች ተመዝግበው በተራ ካቀረቡ በኋላ ቀጣዬ ሌሎች ሶስት አቅራቢዎች የሚቀጥሉበት እንደሆነ ነገረኝ።
ልታቀርብ ቀድማ የወጣችው ፀጉሯን ልሙጥ አድርጋ አስይዛ ሱፍ የሚያስንቅ ኮትና ሱሪ የለበሰች ፅድት ያለች ሴት ናት። መድረኩ ላይ ወጥታ ቀጭኑ መብራት እሷ ላይ ብቻ ሲያበራ
"ከስራ ቀጥታ ስለመጣሁ ነው ይቅር በሉኝ formal መመሰል ፈልጌ አይደለም" አለች በትንሹ ፈገግ ብላ። ቤቱ በስላሳ ጭብጨባ ይቅር መባሏን ሲያበስራት ጀመረች
ስ.ም.ጥ
ት.ሙ.ክ
ታውቃላችሁ
ተረከዝ ውስጥ
እንደሚገኝ ልባችሁ
ታውቃላችሁ
ጫማ ሲመቻችሁ
በእያንዳንዱ እርምጃችሁ
ደስ እንደሚላችሁ
ክ.ት.ት
ም.ች.ት
ከዛ ሲቆረቁራችሁ
አንድ ጠጠር
ሰላም ስትነሳችሁ
አስባችሁታል
ጠጠሯ ስትጠፋችሁ
ቁ.ር.ቁ.ር
ቡ.ር.ቡ.ር
ሲጠዘጥዛችሁ
እስከጉልበታችሁ
ሲሰማችሁ
እስከወገባችሁ
ጥ.ዝ.ጥ.ዝ
ድ.ን.ዝ.ዝ
ገበያ ሙሉ ስትሸጡ
ቶርሽን ዘርግታችሁ
አዲዳስ አንጥፋችሁ
አያቴ ስትለምነኝ
የት ነበራችሁ
ኧረ ቁርቋሬው
የምታደርጋቸው
አጠነካከሩ
ሶሉ መርገጫቸው
ስትለምነኝ
እሺ ስላት
ስትለምነኝ
ሳልገዛላት
እንደቆረቆራት
አንድ ቀን ሳይመቻት
ሞተች!
ሰማችሁ?! ያልኩትን
ሞተች
ገበያው በጫማ ቢሞላ
ምን ያደርግልኛል
ፀ.ፀ.ት
ይወርሰኛል
ብ.ሽ.ቀ.ት
ያንቀኛል
ሰው እንዴት ጫማ
ይቸግረዋል?
ኧረ ኤድያ!
ብላ ከመድረክ ወረደች ጭብጨባው ቀለጠ።እኔ አያቷ በአይነህሊናዬ ተስለው ኖሮ አይኔ እንባ አቅርሮ ነበር። "ልታለቅሺ እንዳይሆን" አለኝ ከሰዉ ጋር እያጨበጨበ "ባለቅስስ?! አቀራረቧ ሴትየዋን እንድስላቸው አስገደደኛ" አልኩት ያልወረደ እንባዬን እንዳይወርድ እየታገልኩ
ሽሽ...ሽሽ የሚል ድምፅ እየተሰማንም እየተንሾካሾክን ጨርሰን ወጣን።
"የእንባ ጫፍ እስክትደርሺ ውስጥሽ ገብቶ enjoy አላደረግኩትም አትይኝም መቼም" አለኝ ወደመኪናው እየሄድን "ውይ በጣም ነው የወደድኩት በየሳምንቱ ሀሙስ ሌላ ፕሮገራም አልይዝም" የመኪናውን በር ከፍቶ አስገብቶኝ ሲመለስ
"የረባ ወግ ግን ስላልሰማሁ ቆንጆ የወግ መፅሀፍ እሰጥሀለው" አልኩት ቀበቶዬን እየታጠቅኩ "እስኪ የኖረ ሀሳቤን ታስቀይሪኝ እንደሆነ እናያለን" አለ ካቆመበት ጥግ ወደ ዋናው አስፓልት በጥንቃቄ እየነዳ
"እናያለን"
✍ናኒ
https://t.me/justhoughtsss | 1 454 |
| 17 | Немає тексту... | 1 227 |
| 18 | My All Mariah Carey.mp3 | 1 206 |
| 19 | Немає тексту... | 1 356 |
| 20 | Немає тексту... | 1 |
