es
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

Ir al canal en Telegram

📈 Análisis del canal de Telegram Assaye Derbie

El canal Assaye Derbie (@asayede) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 14 346 suscriptores, ocupando la posición 2 649 en la categoría Bloques y el puesto 2 354 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 14 346 suscriptores.

Según los últimos datos del 24 junio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -112, y en las últimas 24 horas de -7, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 39.43%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 12.21% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 5 656 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 752 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 33.

📝 Descripción y política de contenido

No se ha proporcionado la descripción del canal.

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 25 junio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Bloques.

14 346
Suscriptores
-724 horas
-387 días
-11230 días
Archivo de publicaciones
በአራጁ የኦሮሞ ብሔርተኛ የተገደሉ...!!
በአራጁ የኦሮሞ ብሔርተኛ የተገደሉ...!!

የትኛውንም ማንበብና መጻፍ የሚችል መንገደኛ ከጎዳና ላይ አፍሰህ አራት ኪሎ ብታስገባው፣ ከጫካ ቤት ይልቅ በየጫካው የሚረግፍ ሕይወት የሚያሳስበው፣ የተሻለ መሪ የመሆን እድል አለው።
የትኛውንም ማንበብና መጻፍ የሚችል መንገደኛ ከጎዳና ላይ አፍሰህ አራት ኪሎ ብታስገባው፣ ከጫካ ቤት ይልቅ በየጫካው የሚረግፍ ሕይወት የሚያሳስበው፣ የተሻለ መሪ የመሆን እድል አለው።

ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ ወለጋ የተዛወረው የብልጽግና ሸኔ የጫካ ፕሮጀክት..! አሳዬ ደርቤ ግብ እና ዓላማው ▬▬▬▬ ➔ስልታዊና መዋቅራዊ በሆነ መልኩ በምዕራብ ወለጋ ዞን የተፈጸመውን አማራን የማጽዳትና የማጥፋት ፕሮጀክት ወደ ምሥራቅ ወለጋ በመውሰድ ከአማራዎች የጸዳ ክልል ተፈጥሮ ማየት፤ ➔አማራዎችን ማደኽየትና ክልሉን በተፈናቃዮች መሙላት፤ ➔የዜጎችን ጥሪት እና መሬት ወርሶ በመሸጥ ሕይወቱ የተለወጠ የካድሬ ቤተሰብ ተፈጥሮ ማየት፤ ➔በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች ውስጥ እየተፈጠሩ ስላሉ ተቃውሞዎች፣ ስለጫካ ቤቶች እና ከሕግ በላይ ስለሆኑ ሙሠኞች ማውራት የጀመረውን ኤሊት እረፍት መንሳትና ትኩረቱን መቀማት፤ ምቹ ሁኔታ የፈጠረላቸው ▬▬▬▬▬▬▬▬ ➔በከባድ መሣሪያ የሚረግፈውን ሕይወት ከሰማይ አማልክት ባለፈ የሚታደገው መንግሥትም ሆነ ሠራዊት አለመኖሩ፤ ➔ከወገኑ እልቂትና ከንጹሐን ደም ይልቅ የኡራጋይ ስንብትና የሸዋሬዝ እንባ የሚያንገበግበው የአማራ ኤሊት መፈጠሩ፤ ➔በብአዴን እና በአብን በኩል ይሰነዘራል ተብሎ የሚገመት ተመጣጣኝ እርምጃም ሆነ የኀዘን መግለጫና ግልምጫ አለመኖሩ፤ ➔ሞትን የተለማመደ ሕዝብና አገር መፈጠሩ፤ ➔ጥቃቱን የሚያከሽፍ የፌደራል ኃይል አለመኖሩ፤ እንቅፋት ሆኖ ያስቸገራቸው ▬▬▬▬▬▬ ➔በምሥራቅ ወለጋ የሚኖረው የአማራ ገበሬ ከምዕራብ ወለጋው ጥቃት ተምሮ በተወሰነ መልኩ እራሱን ማደራጀቱና ከባለሹርቤው ሠራዊት አቅም በላይ ሆኖ መገኘቱ፤ እንደ መፍትሔ የተቀመጠው ▬▬▬▬ ➔እራሱን አደራጅቶ የአልሞት ባይ ተጋዳይ ትግል የጀመረውን ገበሬ የኦሮሞ ንጹሐን ላይ ጥቃት ሊሰነዝር ከአጎራባች አካባቢዎች የመጣ ፋኖ እና ልዩ ኃይል ነው›› እያሉ ሕዝብን የማደናገር ሥራ መሥራት፤ ➔ባለሹርቤውን እና ሚሊታሪ ለባሹን ሠራዊት በማቀናጀት በከባድ መሣሪያ የታገዘ መጠነ ሰፊ ጥቃት መክፈት፤ ➔የመንግሥትና የግል ሚዲያዎች የዓለም ዋንጫ ትንታኔ ላይ እንዲያተኩሩ ሥምሪት መስጠት፤ ➔የፌደራል የጸጥታ ኃይሎችን አለማስገባት፤

"ሸኔ" ማለት ዩኑፎርም ያልተገዛለት የሽመልስ ሠራዊት በመሆኑ፤ አንገር ጉትን ከሚሊታሪ ለባሹ ልዩ-ኃይል ጋር ጥምረት ፈጥሮ አማራዎች ላይ እየተኮሰ ነው።
"ሸኔ" ማለት ዩኑፎርም ያልተገዛለት የሽመልስ ሠራዊት በመሆኑ፤ አንገር ጉትን ከሚሊታሪ ለባሹ ልዩ-ኃይል ጋር ጥምረት ፈጥሮ አማራዎች ላይ እየተኮሰ ነው።

አሁን በዚህ ሰዓት ወለጋ አንገር ጉትን ወረዳ የሚኖሩ አማራዎች በክልሉ ልዩ ሃይል ጥይት እየተጨፈጨፉ ነውና ድምጽ እንሁናቸው።
አሁን በዚህ ሰዓት ወለጋ አንገር ጉትን ወረዳ የሚኖሩ አማራዎች በክልሉ ልዩ ሃይል ጥይት እየተጨፈጨፉ ነውና ድምጽ እንሁናቸው።

የዘመነን ጉዳይ በሽምግልና መፍታት የሚፈልግ አካል መሄድ ያለበት ፊንፊኔ እንጂ ባሕር ዳር አልነበረም። ብአዴን እኮ "ዘመነን ፍታው" ብለህ ሽምግልና ስትልክበት "ሽማግሌዎቹን ምን ልበላቸው?" የሚል
የዘመነን ጉዳይ በሽምግልና መፍታት የሚፈልግ አካል መሄድ ያለበት ፊንፊኔ እንጂ ባሕር ዳር አልነበረም። ብአዴን እኮ "ዘመነን ፍታው" ብለህ ሽምግልና ስትልክበት "ሽማግሌዎቹን ምን ልበላቸው?" የሚል ጥያቄ የያዙ ሽማግሌዎች መርጦ ወደ በላይ አካል የሚልክ የወሕኒ ቤት ካቦ ነው!😆

ጋበዝኳችሁ

በዞን ደረጃ የተወሰነው የፋኖ አደረጃጀት ጎንደር ላይ ተሰባስቦ የአማራ ፋኖን መሥርቷል። ስለሆነም ይሄን አደረጃጀት በብቸኝነት በማጠናከር ሁሉም የፋኖ ክንፎች እንዲሰባሰቡ ማድረግ ይገባናል።
በዞን ደረጃ የተወሰነው የፋኖ አደረጃጀት ጎንደር ላይ ተሰባስቦ የአማራ ፋኖን መሥርቷል። ስለሆነም ይሄን አደረጃጀት በብቸኝነት በማጠናከር ሁሉም የፋኖ ክንፎች እንዲሰባሰቡ ማድረግ ይገባናል።

የእራሱን ሕንጻ መሥራትና የተፈናቀሉ ወገኖችን ወደ ጎጇቸው ማስገባት የሚቻለው ድርጅት፥ የመኖሪያ ቤት ምኞትና የጥሬ ሥጋ አምሮት ከሚያሰቃያቸው መሪዎች እጅ ወድቆ አከራዩን እና አማራውን ሲታገል ከከረመ በኋላ ማሕተሙን ይዞ ወደ ጎዳና ሲወጣ አስበው እስቲ...😆 ከዚህ በላይ የሚያስገርመው ደግሞ አብንን ጎዳና አዳሪ ያደረጉት እኒህ ብላኔ ሰዎች እንደ ቢሯቸው ሁሉ አፋቸውን ዘግተው መቀመጥ ሲገባቸው መካሪ ሆነው የሚከሰቱ መሆናቸው ነው።

ከብልጽግና በላይ ኢዜማ ጋር መጣላት ከባድ ዋጋ እንደሚያስከፍል ለመረዳት የታምራትን ስዴት እና የአቶ ታዲዮስ ታንቱን እስራት መመልከት በቂ ነው!! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ባንድ ወቅት የህውሓትን ሥርዓት የሚጠሉ፣ ለሕዝብና ለአገር እናስባለን የሚሉ፣ ለዲሞክራሲና ለነጻነት የሚታገሉ፣… ወገኖች እስራትን እና ሞትን ፈርተው ወደ ውጭ አገር ከተሰደዱ በኋላ አንዳንዶቹ ኢሳት የሚባል ሚዲያ መሥርተው ጋዜጠኞች ሆኑ፡፡ አንዳንዶቹ የትግል ድርጅት ፈጥረው የነጻነት ታጋዮች ተባሉ፡፡ በህውሓት ወንበር ላይ ብልጽግና በተቀመጠ ጊዜም ፖለቲከኞቹ "የምንፈልገው ሥርዓት መጥቷል›› በሚል ድምዳሜ ወደ አገራቸው መጥተው ኢዜማ የሚባል ሀይ ኮፒ ፓርቲ ከመሠረቱ በኋላ በተቃዋሚነት የገነቡትን ግዙፍ ሥም በእርባና የለሽ ወንበርና ጥቅም ለወጡ። ወደ አገራቸው መምጣት ያልፈለጉት ጋዜጠኞች ደግሞ የገዥው ፓርቲ አንደበት ሊሆኑ ፈርመው በሥማቸው የሚጠራ የኮንዶሚንየም ቤት እና ባዶ መሬት ተሰጡ፡፡ ከዚያም የሕዝብ ዐይንና ጆሮ በሚል ሚዲያ ያለፈውን ሥርዓት ሲያብጠለጥሉና አፋኙን ሥርዓት ሲታገሉ የኖሩት ጋዜጠኞች የመንግሥት ዐይንና ጆሮ ሆነው ባርነትን የሚዘሩ እንዲሁም ለሕሊናቸውና ለሙያቸው ተገዢ የሆኑ ጋዜጠኞችንና አንቂዎችን የሚያሳስሩ ሆኑ፡፡ የመንግሥት ልሳን የሆኑት የፋና እና የኢቲቪ ጋዜጠኞች እንኳን የተለያዩ ሐሰተኛ ዶክመንታሪዎችን እያዘጋጁ የእውነተኛ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን ሥም ማጠልሸት ባቆሙበት ዘመን፣ ከብልጽግና ካድሬዎች በላይ የገዢው ፓርቲ አገልጋዮች ሆነው መገኘት በሚሹ የኢሳትና የግንቦት ሰባት ኃይሎች የሚዲያ ዘመቻ ለሕዝባቸውና ለእራሳቸው የታመኑ ወገኖች ይታሰሩ ጀመር፡፡ እነ ሳጥናኤል፣ እነ ደረጀ ሃብተ ሆድ፣ እነ ቶኪቸው፣ እነ ግርማ… በሚጽፉት የእስር ማዘዣም እነ ታምራት ነገራ፣ እነ እስክንድር ነጋ፣ እነ ተመስገን ደሳለኝ፣ እነ ጎበዜ ሲሳይ፣ እነ ታዲዮስ ታንቱ... በየሩብ ዓመቱ ይታሰሩና ይፈቱ ጀመር፡፡ ከእነዚህም መሀከል ጋዜጠኛ ታምራትና አቶ ታዲዮስ ታንቱ ኸገዥው ፓርቲ ባለፈ የአቃጣሪውን ፓርቲ ዋነኛ አመራር በመተቸታቸው የተነሳ ታሜ አገር ጥሎ ሲሰደት፣ አቶ ታዲዮስ ደግሞ ከሌሎች ሁሉ ተነጥለው በእስራት ላይ ይገኛሉ፡፡ ምክንያቱም... ኢዜማ የጠመደውን ብልጽግና አይታደገውም!!

"ለአንድ ሕዝብ ሕልውና ተብሎ አይሻሻልም" የተባለውን ሕገ መንግሥት መሠረት በማድረግ አማራነቱን የሚያስከብርና የትኛውንም ኃይል የሚገዳደር ትውልድ እንፈጥራለን!! ዝንታለም አማራ!!
"ለአንድ ሕዝብ ሕልውና ተብሎ አይሻሻልም" የተባለውን ሕገ መንግሥት መሠረት በማድረግ አማራነቱን የሚያስከብርና የትኛውንም ኃይል የሚገዳደር ትውልድ እንፈጥራለን!! ዝንታለም አማራ!!

የምንሰማው ነገር እውነት ከሆነ ፥ ከግርማ የሺጥላ ይልቅ ሺመልስ አብዲሳ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ቢሆን መልካም መሪ ይሆንልናል።
የምንሰማው ነገር እውነት ከሆነ ፥ ከግርማ የሺጥላ ይልቅ ሺመልስ አብዲሳ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ቢሆን መልካም መሪ ይሆንልናል።

ለፖለቲከኞች የምንቸረው ሙገሣም ሆነ ወቀሣ፥ አገራዊ፣ ምክንያታዊ እና ሚዛናዊ... በመሆኑ የወደድነው ይገዝፋል። የጠመድነው ይረግፋል። ለዚያም ነው... አማራ ከሚጠላህ የሚያድግ ልጅ ይርገምህ የምንለ
ለፖለቲከኞች የምንቸረው ሙገሣም ሆነ ወቀሣ፥ አገራዊ፣ ምክንያታዊ እና ሚዛናዊ... በመሆኑ የወደድነው ይገዝፋል። የጠመድነው ይረግፋል። ለዚያም ነው... አማራ ከሚጠላህ የሚያድግ ልጅ ይርገምህ የምንለው!😆 እናም ዛሬ ከአማራ ጋር ተቃቅረህ ብሎም ሰውነትህን ጥለህ ከገዢው ፓርቲ ጋር የተጣበቅክ መዥገር ሁላ "በሕይወት አለሁ" አትበል! ትምክሕት እንዳይመስልህ! እውነት እንጂ!! አማራ ለዘላለም ይኑር! ኢትዮጵያም ጭምር!!

እጅግ የወረደው የዶክተር ደረጀ ዘለቀ ቃለ-መጠይቅ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔የአማራ ሕዝብ በርካታ የሕይወት ዋጋ የከፈለለትን የወልቃይት የማንነት ጥያቄ ያላንዳች ጥናት ከአማራ ሕዝብ መዳፍ ነጥቆ የርስት ጥያቄ በሚል ሥም ለሰሜን ጎንደር የወረወረ… ➔የአማራ ፖለቲካን አጀንዳው አድርጎ የሚንቀሳቀሰውን ሙሕር ሁሉ ‹‹በአማራ ሕዝብ ጫንቃ ላይ የበቀለ ካንሰር ነው›› ለማለት የደፈረ ➔ድፍረትና እርግጠኝነት በሞላው አንደበቱ ‹‹አማራ የሚባል ማሕበረሰብ አለመኖሩን ካብራራ በኋላ ‹‹የለም›› ያለውን አማራ አፈላልጎ ከትግራይ ሕዝብ ጋር አቧድኖ የታሪካዊቷ ኢትዮጵያ (የአቢሲኒያ) ባለቤት ያደረገ ➔የወለደውን ሕዝብ ሕልውና ከካደ በኋላ ‹‹አማራ አማራ አማራ›› እያለ ችግሩን እና ታሪኩን የተነተነ ➔ዶክተሩ በነቀርሳነት የፈረጀው የትኛውም ኤሊት እንኳን ሊናገራቸውም ሆነ ሊሰማቸው የማይፈልጋቸውን እጅግ ነውረኛና አደገኛ ንግግሮች በርዕዮት ሚዲያ ላይ የበተነ… ➔የሌሎችን ብሔርተኝነት በአልቃሻነት ከፈረጀ በኋላ በርካታ ዙር የዘር ፍጅቶችን አስተናግዶ ‹‹በማንነቴ መገደል በቃኝ›› በሚል ድምጸት የተፈጠረውን የአማራ ብሔርተኝነት ‹‹ከሌሎች ኢትዮጵያውያን የላቅኹ እና የተለየኹ ብሔር ነኝ በሚል የበላይነት ስሜት የተፈጠረ ነው" በማለት የተነተነ ➔ይሄውም ‹‹ልዕለ ሰብ ነኝ" በሚል መንፈስ የተወለደው የአማራ ብሔርተኝነት ወደ ሥልጣን ቢመጣ ናዚን በሚያስንቅ መልኩ መላውን ፍጡር እንደሚጨፈጭፍ ያላንዳች ማቅማማት የተናገረ፤ ➔እንግሊዘኛ ስድብን እንደ ምጡቅ ሐሳብ፣ እብደትን እንደ ድፍረት፣ አማራ ላይ መትፋትን እንደ መብት፣ መናኛ ድምዳሜንና ባዶ ፍረጃን እንደ ጥናት የቆጠረ…. ➔በሚጣረሱ ንግግሮች፣ አገርን እና ብሔርን በሚከፋፍሉ ሐሳቦች፣ እውን ሊሆኑ ቀርቶ ባግባቡ ሊብራሩ በማይችሉ ትንቢቶች ብሎም እጅግ በወረዱ ትንታኔዎች የተሞላ… ሲጠቃለል... በቀጣይ ዶክተሩን መጠየቅ የምትፈልጉ ወገኖች ወደ ሚዲያ አምጥታችሁ ሳይሆን ሆስፒታል አስገብታችሁ ብትጠይቁት ጥሩ ነው። ለዚያውም ማይክ ሳይሆን ሙዝ ይዛችሁ...

ከኳታር ዝግጅት ጋር አብሮ በተጀመረ የእልቂት መርሐ ግብር ኪረሙና ደራ ላይ ወገኖቻችን እየረገፉ ነው። እናም "የኳታሩን የዓለም ዋንጫ የሚበላው ማን ነው" እያልን ከመጨቃጨቅ ባለፈ "ጠላትና መንግሥት የሚጠቃቀሱበትን ሕዝብ ከእልቂት ማዳን የሚቻለው እንዴት ነው?" ለሚለው ጥያቄ መልስ ማግኘት ይኖርብናል።

እንደ ሀገርስ ቢሆን ይሄንን ቋሚ ገመና ተሸክመን የት ልንደርስ ነው? // አቶ የሱፍ ኢብራሒም// ወለጋ ውስጥ በአማራዎች ላይ የሚፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ ተጠናክሮ መቀጠሉን የሚያሳዩ መረጃዎች ደርሰውና
እንደ ሀገርስ ቢሆን ይሄንን ቋሚ ገመና ተሸክመን የት ልንደርስ ነው? // አቶ የሱፍ ኢብራሒም// ወለጋ ውስጥ በአማራዎች ላይ የሚፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ ተጠናክሮ መቀጠሉን የሚያሳዩ መረጃዎች ደርሰውናል። በዚህ መሰረት በዛሬው እለት በኪረሙ ወረዳ በሕፃናት እና እናቶች ላይ ሳይቀር መጠነ-ሰፊ፣ የተቀናጀ እና ዘግናኝ ጭፍጨፋ እየተካሄደ ነው። አስክሬኖችን ማንሳትና መቅበር እንኳን እንዳልተቻለ ታውቋል። ይሄ ለእኛ አሳዛኝ ብቻ አይደለም፤ አሳፋሪና አዋራጅም ነው! እንደ ሃገርስ ቢሆን ይሄን ቋሚ ገመና ተሸክመን የት ልንደርስ ነው? ከእንግዲህ ሌላውን ሁሉ ተውት—ከምር የህሊና እዳ ያለብን ወገኖች ትኩረት ሰጥተን መፍትሄ ብንፈልግለት ጥሩ ነው!

በአማራ ትግል ውስጥ የፍትሕ ድምጽ በመሆን በቀዳሚነት ሥሙ ለሚጠቀሰው፣ የአቋምና የመርሕ ሰው ለሆነው፣ ቅንነትን እና መልካምነትን ለታደለው... ወንድማችን በፍቅር እና በስኬት የተሞላ መልካም የትዳር
በአማራ ትግል ውስጥ የፍትሕ ድምጽ በመሆን በቀዳሚነት ሥሙ ለሚጠቀሰው፣ የአቋምና የመርሕ ሰው ለሆነው፣ ቅንነትን እና መልካምነትን ለታደለው... ወንድማችን በፍቅር እና በስኬት የተሞላ መልካም የትዳር ዘመንን እመኛለሁ። እንኳን ደስ አለህ አቤዋ!!

በፕሪቶሪያው ሰነድ ላይ "የጌቾ ቡድን ስምምነቱን ሽሮ ጦሩን እና ምሽጉን ለትግል ሲያዘገጃጅ፣ ይሄኛው ቡድን መድረክ እያዘጋጀ በድርድር የተጎናጸፈውን ዘላቂ ድል ያከብራል" የሚል አንቀጽ ይኖር ይሆን?
በፕሪቶሪያው ሰነድ ላይ "የጌቾ ቡድን ስምምነቱን ሽሮ ጦሩን እና ምሽጉን ለትግል ሲያዘገጃጅ፣ ይሄኛው ቡድን መድረክ እያዘጋጀ በድርድር የተጎናጸፈውን ዘላቂ ድል ያከብራል" የሚል አንቀጽ ይኖር ይሆን? 😆