Assaye Derbie
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Assaye Derbie
تُعد قناة Assaye Derbie (@asayede) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 14 346 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 649 في فئة المدوّنات والمرتبة 2 354 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 14 346 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 24 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -112، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -7، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 39.43%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 12.21% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 656 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 1 752 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 33.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
وصف القناة غير متوفر.
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 25 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة المدوّنات.
14 346
المشتركون
-724 ساعات
-387 أيام
-11230 أيام
أرشيف المشاركات
14 346
የትኛውንም ማንበብና መጻፍ የሚችል መንገደኛ ከጎዳና ላይ አፍሰህ አራት ኪሎ ብታስገባው፣ ከጫካ ቤት ይልቅ በየጫካው የሚረግፍ ሕይወት የሚያሳስበው፣ የተሻለ መሪ የመሆን እድል አለው።
14 346
ከምዕራብ ወደ ምሥራቅ ወለጋ የተዛወረው የብልጽግና ሸኔ የጫካ ፕሮጀክት..!
አሳዬ ደርቤ
ግብ እና ዓላማው
▬▬▬▬
➔ስልታዊና መዋቅራዊ በሆነ መልኩ በምዕራብ ወለጋ ዞን የተፈጸመውን አማራን የማጽዳትና የማጥፋት ፕሮጀክት ወደ ምሥራቅ ወለጋ በመውሰድ ከአማራዎች የጸዳ ክልል ተፈጥሮ ማየት፤
➔አማራዎችን ማደኽየትና ክልሉን በተፈናቃዮች መሙላት፤
➔የዜጎችን ጥሪት እና መሬት ወርሶ በመሸጥ ሕይወቱ የተለወጠ የካድሬ ቤተሰብ ተፈጥሮ ማየት፤
➔በአዲስ አበባ ትምህርት ቤቶች ውስጥ እየተፈጠሩ ስላሉ ተቃውሞዎች፣ ስለጫካ ቤቶች እና ከሕግ በላይ ስለሆኑ ሙሠኞች ማውራት የጀመረውን ኤሊት እረፍት መንሳትና ትኩረቱን መቀማት፤
ምቹ ሁኔታ የፈጠረላቸው
▬▬▬▬▬▬▬▬
➔በከባድ መሣሪያ የሚረግፈውን ሕይወት ከሰማይ አማልክት ባለፈ የሚታደገው መንግሥትም ሆነ ሠራዊት አለመኖሩ፤
➔ከወገኑ እልቂትና ከንጹሐን ደም ይልቅ የኡራጋይ ስንብትና የሸዋሬዝ እንባ የሚያንገበግበው የአማራ ኤሊት መፈጠሩ፤
➔በብአዴን እና በአብን በኩል ይሰነዘራል ተብሎ የሚገመት ተመጣጣኝ እርምጃም ሆነ የኀዘን መግለጫና ግልምጫ አለመኖሩ፤
➔ሞትን የተለማመደ ሕዝብና አገር መፈጠሩ፤
➔ጥቃቱን የሚያከሽፍ የፌደራል ኃይል አለመኖሩ፤
እንቅፋት ሆኖ ያስቸገራቸው
▬▬▬▬▬▬
➔በምሥራቅ ወለጋ የሚኖረው የአማራ ገበሬ ከምዕራብ ወለጋው ጥቃት ተምሮ በተወሰነ መልኩ እራሱን ማደራጀቱና ከባለሹርቤው ሠራዊት አቅም በላይ ሆኖ መገኘቱ፤
እንደ መፍትሔ የተቀመጠው
▬▬▬▬
➔እራሱን አደራጅቶ የአልሞት ባይ ተጋዳይ ትግል የጀመረውን ገበሬ የኦሮሞ ንጹሐን ላይ ጥቃት ሊሰነዝር ከአጎራባች አካባቢዎች የመጣ ፋኖ እና ልዩ ኃይል ነው›› እያሉ ሕዝብን የማደናገር ሥራ መሥራት፤
➔ባለሹርቤውን እና ሚሊታሪ ለባሹን ሠራዊት በማቀናጀት በከባድ መሣሪያ የታገዘ መጠነ ሰፊ ጥቃት መክፈት፤
➔የመንግሥትና የግል ሚዲያዎች የዓለም ዋንጫ ትንታኔ ላይ እንዲያተኩሩ ሥምሪት መስጠት፤
➔የፌደራል የጸጥታ ኃይሎችን አለማስገባት፤
14 346
"ሸኔ" ማለት ዩኑፎርም ያልተገዛለት የሽመልስ ሠራዊት በመሆኑ፤ አንገር ጉትን ከሚሊታሪ ለባሹ ልዩ-ኃይል ጋር ጥምረት ፈጥሮ አማራዎች ላይ እየተኮሰ ነው።
14 346
የዘመነን ጉዳይ በሽምግልና መፍታት የሚፈልግ አካል መሄድ ያለበት ፊንፊኔ እንጂ ባሕር ዳር አልነበረም።
ብአዴን እኮ "ዘመነን ፍታው" ብለህ ሽምግልና ስትልክበት "ሽማግሌዎቹን ምን ልበላቸው?" የሚል ጥያቄ የያዙ ሽማግሌዎች መርጦ ወደ በላይ አካል የሚልክ የወሕኒ ቤት ካቦ ነው!😆
14 346
በዞን ደረጃ የተወሰነው የፋኖ አደረጃጀት ጎንደር ላይ ተሰባስቦ የአማራ ፋኖን መሥርቷል። ስለሆነም ይሄን አደረጃጀት በብቸኝነት በማጠናከር ሁሉም የፋኖ ክንፎች እንዲሰባሰቡ ማድረግ ይገባናል።
14 346
የእራሱን ሕንጻ መሥራትና የተፈናቀሉ ወገኖችን ወደ ጎጇቸው ማስገባት የሚቻለው ድርጅት፥ የመኖሪያ ቤት ምኞትና የጥሬ ሥጋ አምሮት ከሚያሰቃያቸው መሪዎች እጅ ወድቆ አከራዩን እና አማራውን ሲታገል ከከረመ በኋላ ማሕተሙን ይዞ ወደ ጎዳና ሲወጣ አስበው እስቲ...😆
ከዚህ በላይ የሚያስገርመው ደግሞ አብንን ጎዳና አዳሪ ያደረጉት እኒህ ብላኔ ሰዎች እንደ ቢሯቸው ሁሉ አፋቸውን ዘግተው መቀመጥ ሲገባቸው መካሪ ሆነው የሚከሰቱ መሆናቸው ነው።
14 346
ከብልጽግና በላይ ኢዜማ ጋር መጣላት ከባድ ዋጋ እንደሚያስከፍል ለመረዳት የታምራትን ስዴት እና የአቶ ታዲዮስ ታንቱን እስራት መመልከት በቂ ነው!!
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬▬
ባንድ ወቅት የህውሓትን ሥርዓት የሚጠሉ፣ ለሕዝብና ለአገር እናስባለን የሚሉ፣ ለዲሞክራሲና ለነጻነት የሚታገሉ፣… ወገኖች እስራትን እና ሞትን ፈርተው ወደ ውጭ አገር ከተሰደዱ በኋላ አንዳንዶቹ ኢሳት የሚባል ሚዲያ መሥርተው ጋዜጠኞች ሆኑ፡፡ አንዳንዶቹ የትግል ድርጅት ፈጥረው የነጻነት ታጋዮች ተባሉ፡፡
በህውሓት ወንበር ላይ ብልጽግና በተቀመጠ ጊዜም ፖለቲከኞቹ "የምንፈልገው ሥርዓት መጥቷል›› በሚል ድምዳሜ ወደ አገራቸው መጥተው ኢዜማ የሚባል ሀይ ኮፒ ፓርቲ ከመሠረቱ በኋላ በተቃዋሚነት የገነቡትን ግዙፍ ሥም በእርባና የለሽ ወንበርና ጥቅም ለወጡ።
ወደ አገራቸው መምጣት ያልፈለጉት ጋዜጠኞች ደግሞ የገዥው ፓርቲ አንደበት ሊሆኑ ፈርመው በሥማቸው የሚጠራ የኮንዶሚንየም ቤት እና ባዶ መሬት ተሰጡ፡፡
ከዚያም የሕዝብ ዐይንና ጆሮ በሚል ሚዲያ ያለፈውን ሥርዓት ሲያብጠለጥሉና አፋኙን ሥርዓት ሲታገሉ የኖሩት ጋዜጠኞች የመንግሥት ዐይንና ጆሮ ሆነው ባርነትን የሚዘሩ እንዲሁም ለሕሊናቸውና ለሙያቸው ተገዢ የሆኑ ጋዜጠኞችንና አንቂዎችን የሚያሳስሩ ሆኑ፡፡
የመንግሥት ልሳን የሆኑት የፋና እና የኢቲቪ ጋዜጠኞች እንኳን የተለያዩ ሐሰተኛ ዶክመንታሪዎችን እያዘጋጁ የእውነተኛ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን ሥም ማጠልሸት ባቆሙበት ዘመን፣ ከብልጽግና ካድሬዎች በላይ የገዢው ፓርቲ አገልጋዮች ሆነው መገኘት በሚሹ የኢሳትና የግንቦት ሰባት ኃይሎች የሚዲያ ዘመቻ ለሕዝባቸውና ለእራሳቸው የታመኑ ወገኖች ይታሰሩ ጀመር፡፡
እነ ሳጥናኤል፣ እነ ደረጀ ሃብተ ሆድ፣ እነ ቶኪቸው፣ እነ ግርማ… በሚጽፉት የእስር ማዘዣም እነ ታምራት ነገራ፣ እነ እስክንድር ነጋ፣ እነ ተመስገን ደሳለኝ፣ እነ ጎበዜ ሲሳይ፣ እነ ታዲዮስ ታንቱ... በየሩብ ዓመቱ ይታሰሩና ይፈቱ ጀመር፡፡
ከእነዚህም መሀከል ጋዜጠኛ ታምራትና አቶ ታዲዮስ ታንቱ ኸገዥው ፓርቲ ባለፈ የአቃጣሪውን ፓርቲ ዋነኛ አመራር በመተቸታቸው የተነሳ ታሜ አገር ጥሎ ሲሰደት፣ አቶ ታዲዮስ ደግሞ ከሌሎች ሁሉ ተነጥለው በእስራት ላይ ይገኛሉ፡፡
ምክንያቱም...
ኢዜማ የጠመደውን ብልጽግና አይታደገውም!!
14 346
"ለአንድ ሕዝብ ሕልውና ተብሎ አይሻሻልም" የተባለውን ሕገ መንግሥት መሠረት በማድረግ አማራነቱን የሚያስከብርና የትኛውንም ኃይል የሚገዳደር ትውልድ እንፈጥራለን!!
ዝንታለም አማራ!!
14 346
የምንሰማው ነገር እውነት ከሆነ ፥ ከግርማ የሺጥላ ይልቅ ሺመልስ አብዲሳ የአማራ ክልል ፕሬዝዳንት ቢሆን መልካም መሪ ይሆንልናል።
14 346
ለፖለቲከኞች የምንቸረው ሙገሣም ሆነ ወቀሣ፥ አገራዊ፣ ምክንያታዊ እና ሚዛናዊ... በመሆኑ የወደድነው ይገዝፋል። የጠመድነው ይረግፋል።
ለዚያም ነው...
አማራ ከሚጠላህ የሚያድግ ልጅ ይርገምህ የምንለው!😆
እናም ዛሬ ከአማራ ጋር ተቃቅረህ ብሎም ሰውነትህን ጥለህ ከገዢው ፓርቲ ጋር የተጣበቅክ መዥገር ሁላ "በሕይወት አለሁ" አትበል!
ትምክሕት እንዳይመስልህ! እውነት እንጂ!!
አማራ ለዘላለም ይኑር! ኢትዮጵያም ጭምር!!
14 346
እጅግ የወረደው የዶክተር ደረጀ ዘለቀ ቃለ-መጠይቅ
አሳዬ ደርቤ
▬▬▬
➔የአማራ ሕዝብ በርካታ የሕይወት ዋጋ የከፈለለትን የወልቃይት የማንነት ጥያቄ ያላንዳች ጥናት ከአማራ ሕዝብ መዳፍ ነጥቆ የርስት ጥያቄ በሚል ሥም ለሰሜን ጎንደር የወረወረ…
➔የአማራ ፖለቲካን አጀንዳው አድርጎ የሚንቀሳቀሰውን ሙሕር ሁሉ ‹‹በአማራ ሕዝብ ጫንቃ ላይ የበቀለ ካንሰር ነው›› ለማለት የደፈረ
➔ድፍረትና እርግጠኝነት በሞላው አንደበቱ ‹‹አማራ የሚባል ማሕበረሰብ አለመኖሩን ካብራራ በኋላ ‹‹የለም›› ያለውን አማራ አፈላልጎ ከትግራይ ሕዝብ ጋር አቧድኖ የታሪካዊቷ ኢትዮጵያ (የአቢሲኒያ) ባለቤት ያደረገ
➔የወለደውን ሕዝብ ሕልውና ከካደ በኋላ ‹‹አማራ አማራ አማራ›› እያለ ችግሩን እና ታሪኩን የተነተነ
➔ዶክተሩ በነቀርሳነት የፈረጀው የትኛውም ኤሊት እንኳን ሊናገራቸውም ሆነ ሊሰማቸው የማይፈልጋቸውን እጅግ ነውረኛና አደገኛ ንግግሮች በርዕዮት ሚዲያ ላይ የበተነ…
➔የሌሎችን ብሔርተኝነት በአልቃሻነት ከፈረጀ በኋላ በርካታ ዙር የዘር ፍጅቶችን አስተናግዶ ‹‹በማንነቴ መገደል በቃኝ›› በሚል ድምጸት የተፈጠረውን የአማራ ብሔርተኝነት ‹‹ከሌሎች ኢትዮጵያውያን የላቅኹ እና የተለየኹ ብሔር ነኝ በሚል የበላይነት ስሜት የተፈጠረ ነው" በማለት የተነተነ
➔ይሄውም ‹‹ልዕለ ሰብ ነኝ" በሚል መንፈስ የተወለደው የአማራ ብሔርተኝነት ወደ ሥልጣን ቢመጣ ናዚን በሚያስንቅ መልኩ መላውን ፍጡር እንደሚጨፈጭፍ ያላንዳች ማቅማማት የተናገረ፤
➔እንግሊዘኛ ስድብን እንደ ምጡቅ ሐሳብ፣ እብደትን እንደ ድፍረት፣ አማራ ላይ መትፋትን እንደ መብት፣ መናኛ ድምዳሜንና ባዶ ፍረጃን እንደ ጥናት የቆጠረ….
➔በሚጣረሱ ንግግሮች፣ አገርን እና ብሔርን በሚከፋፍሉ ሐሳቦች፣ እውን ሊሆኑ ቀርቶ ባግባቡ ሊብራሩ በማይችሉ ትንቢቶች ብሎም እጅግ በወረዱ ትንታኔዎች የተሞላ…
ሲጠቃለል...
በቀጣይ ዶክተሩን መጠየቅ የምትፈልጉ ወገኖች ወደ ሚዲያ አምጥታችሁ ሳይሆን ሆስፒታል አስገብታችሁ ብትጠይቁት ጥሩ ነው።
ለዚያውም ማይክ ሳይሆን ሙዝ ይዛችሁ...
14 346
ከኳታር ዝግጅት ጋር አብሮ በተጀመረ የእልቂት መርሐ ግብር ኪረሙና ደራ ላይ ወገኖቻችን እየረገፉ ነው። እናም "የኳታሩን የዓለም ዋንጫ የሚበላው ማን ነው" እያልን ከመጨቃጨቅ ባለፈ "ጠላትና መንግሥት የሚጠቃቀሱበትን ሕዝብ ከእልቂት ማዳን የሚቻለው እንዴት ነው?" ለሚለው ጥያቄ መልስ ማግኘት ይኖርብናል።
14 346
እንደ ሀገርስ ቢሆን ይሄንን ቋሚ ገመና ተሸክመን የት ልንደርስ ነው?
// አቶ የሱፍ ኢብራሒም//
ወለጋ ውስጥ በአማራዎች ላይ የሚፈፀመው የዘር ጭፍጨፋ ተጠናክሮ መቀጠሉን የሚያሳዩ መረጃዎች ደርሰውናል።
በዚህ መሰረት በዛሬው እለት በኪረሙ ወረዳ በሕፃናት እና እናቶች ላይ ሳይቀር መጠነ-ሰፊ፣ የተቀናጀ እና ዘግናኝ ጭፍጨፋ እየተካሄደ ነው። አስክሬኖችን ማንሳትና መቅበር እንኳን እንዳልተቻለ ታውቋል።
ይሄ ለእኛ አሳዛኝ ብቻ አይደለም፤ አሳፋሪና አዋራጅም ነው! እንደ ሃገርስ ቢሆን ይሄን ቋሚ ገመና ተሸክመን የት ልንደርስ ነው? ከእንግዲህ ሌላውን ሁሉ ተውት—ከምር የህሊና እዳ ያለብን ወገኖች ትኩረት ሰጥተን መፍትሄ ብንፈልግለት ጥሩ ነው!
14 346
በአማራ ትግል ውስጥ የፍትሕ ድምጽ በመሆን በቀዳሚነት ሥሙ ለሚጠቀሰው፣ የአቋምና የመርሕ ሰው ለሆነው፣ ቅንነትን እና መልካምነትን ለታደለው... ወንድማችን በፍቅር እና በስኬት የተሞላ መልካም የትዳር ዘመንን እመኛለሁ።
እንኳን ደስ አለህ አቤዋ!!
14 346
በፕሪቶሪያው ሰነድ ላይ "የጌቾ ቡድን ስምምነቱን ሽሮ ጦሩን እና ምሽጉን ለትግል ሲያዘገጃጅ፣ ይሄኛው ቡድን መድረክ እያዘጋጀ በድርድር የተጎናጸፈውን ዘላቂ ድል ያከብራል" የሚል አንቀጽ ይኖር ይሆን? 😆
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
