es
Feedback
አለ ሕግ

አለ ሕግ

Ir al canal en Telegram

ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service Website: alehig.com https://linktr.ee/alehig WhatsApp👉 #+251920666595 Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram አለ ሕግ

El canal አለ ሕግ (@alehig) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 965 suscriptores, ocupando la posición 499 en la categoría Ley y el puesto 2 114 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 965 suscriptores.

Según los últimos datos del 01 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 45, y en las últimas 24 horas de 2, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 31.08%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 10.11% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 962 visualizaciones. En el primer día suele acumular 1 614 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 20.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service Website: alehig.com https://linktr.ee/alehig WhatsApp👉 #+251920666595 Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Ley.

15 965
Suscriptores
+224 horas
Sin datos7 días
+4530 días
Archivo de publicaciones
በኢትዮጵያ ወቅታዊ የህግ አሰራር እና የፍትህ ስርዓት ለውጥ አንፃር፣ የጥብቅና ሙያ ሽርክና ማህበር (Law Firm/Partnership) ማቋቋም እጅግ አስፈላጊ እና ወቅታዊ ጉዳይ ነው። የሙያ ብቃት
+4
በኢትዮጵያ ወቅታዊ የህግ አሰራር እና የፍትህ ስርዓት ለውጥ አንፃር፣ የጥብቅና ሙያ ሽርክና ማህበር (Law Firm/Partnership) ማቋቋም እጅግ አስፈላጊ እና ወቅታዊ ጉዳይ ነው።
የሙያ ብቃት እና ስፔሻላይዜሽን (Specialization)
አንድ ጠበቃ ብቻውን ሲሰራ ሁሉንም የህግ ዘርፎች (ከቤተሰብ ህግ እስከ ኮርፖሬት ህግ፣ ከወንጀል እስከ ታክስ ህግ) ለመሸፈን ይገደዳል። በሽርክና ሲደራጁ ግን፡ 👉 እያንዳንዱ አጋር በራሱ ዘርፍ ላይ ማተኮር ይችላል።
ይህም ለደንበኞች ጥራት
ያለው፣ ጥልቅ እና ሙያዊ ምክር የመስጠት እድልን ይፈጥራል።
የአገልግሎት አሰጣጥ አቅም መጨመር (Scalability)
የንግድ ህግ እና ኢንቨስትመንት እየተወሳሰበ በመጣበት በዚህ ዘመን፣ ትላልቅ የህግ ጉዳዮችን ለመያዝ የሰው ኃይል፣ የጊዜ አጠቃቀም እና የፋይናንስ አቅም ወሳኝ ነው።
በሽርክና የሚቋቋም ተቋም
የሰው ኃይልን በማቀናጀት ትላልቅ እና ውስብስብ የሆኑ የድርጅት ጉዳዮችን፣ ውህደቶችን (Mergers) እና ማግኛዎችን (Acquisitions) የመምራት አቅም ይኖረዋል።
የቴክኖሎጂ
አጠቃቀም እና ዘመናዊነት ህጋዊ አገልግሎትን ዲጂታይዝ ማድረግ (Legal Tech) ለግለሰብ ጠበቃ ብቻውን ከባድ ሊሆን ይችላል።
የጥብቅና ማህበር ሲቋቋም፣
ለቴክኖሎጂ አጠቃቀም የሚሆን በጀት መመደብ፣ የህግ መረጃ ቋቶችን መገንባት እና የውስጥ አሰራርን በሶፍትዌር ማዘመን ቀላል ይሆናል።
ቀጣይነት እና አስተማማኝነት
(Institutional Continuity) አንድ ጠበቃ ብቻውን ሲሰራ፣ በህመም ወይም በሌላ ምክንያት ቢታገድ የደንበኞቹ ጉዳይ ይቋረጣል።
በማህበር ሲደራጁ ግን ተቋሙ
ከግለሰቡ ህልውና ተለይቶ የሚኖር በመሆኑ፣ ለደንበኞች ዘላቂነት ያለው የህግ አገልግሎት ዋስትና መስጠት ይቻላል። ይህም በህብረተሰቡ ዘንድ ለህግ ተቋማት የሚሰጠውን እምነት ይጨምራል።
የገበያ ተወዳዳሪነት
ዓለም አቀፍ የህግ ድርጅቶች ወደ ኢትዮጵያ ገበያ በሚገቡበት ወቅት፣ የሀገር ውስጥ ጠበቆች እንደ ማህበር አለመደራጀታቸው ተወዳዳሪነታቸውን ይቀንሳል።
የሽርክና ማህበር ማቋቋም
የሀገር ውስጥ ጠበቆች ከአለም አቀፍ ደረጃ ጋር እንዲጣጣሙ እና ትላልቅ ተቋማትን እንደ ደንበኛ ለመሳብ ያስችላቸዋል። የሙያ ስነ-ምግባር እና የጋራ ተጠያቂነት በሽርክና ማህበር ውስጥ የውስጥ ቁጥጥር ስርዓት ይኖራል። ይህም የሙያ ስነ-ምግባር ደንቦችን በተሻለ ሁኔታ ተግባራዊ ለማድረግ፣ ስህተቶችን ለመቀነስ እና ለደንበኞች የተሻለ የሙያ ኃላፊነት ለመውሰድ ያግዛል።
የጥብቅና ሙያ ከግል ጥረት ወደ ተቋማዊ አስተሳሰብ መሸጋገሩ የፍትህ ስርዓቱን ከማዘመኑ ባሻገር፣ እንደርስዎ አይነት የህግ ባለሙያዎች ያለውን እውቀት ለበለጠ ህዝባዊ ጥቅም ለማዋል እና የሙያውን ክብር ለማሳደግ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው።
ይህ የሽርክና ማህበር ምስረታ ጉዞዎ በህግ ተቋማት ግንባታ ላይ አዲስ ምዕራፍ ሊከፍት እንደሚችል ሙሉ እምነት አለኝ🙏

የጥሪ ማስታወቂያ 👇 ለኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር አባላት በሙሉ የኢትዮጵያ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር በማህበራዊ ጉዳዬች ቋሚ ኮሚቴ የመገናኛ እና ሚዲያ ንዑስ ኮሚቴ (Communication and Media Sub-Committee) የሙያውን ክብር ለማሳደግ፣ የመረጃ ልውውጥን ለማዘመን እና የማህበሩን ተደራሽነት ለማስፋት በትጋት እየሰራ ይገኛል። በዚህ ንዑስ ኮሚቴ ውስጥ በንቃት በመሳተፍ፣ ልምድዎን በማካፈል እና የማህበሩን የህዝብ ግንኙነት ስራዎች በጋራ በመምራት ማገልገል የምትፈልጉ የህግ ባለሙያዎችን (ጠበቆችን) ለመጋበዝ እንወዳለን። በንዑስ ኮሚቴው የሚጠበቁ ዋና ዋና ተግባራት፡ ✍️ የማህበሩን ገጽታ የሚገነቡ የህዝብ ግንኙነት ስራዎችን ማቀድ። ✍️ ከሚዲያ ተቋማት ጋር የጠበቀ ግንኙነት መፍጠር። ✍️ የህግ መረጃዎችን ለህብረተሰቡ ተደራሽ የሚያደርጉ ይዘቶችን ማዘጋጀት። ✍️ የማህበሩን የማህበራዊ ሚዲያ ገጾች እና ሌሎች የመገናኛ መንገዶችን ማስተባበር። መስፈርቶች፡✍️ ✅ የፌዴራል ጠበቆች ማህበር የሙሉ ጊዜ አባል መሆን። ✅ በመገናኛ፣ በጋዜጠኝነት ወይም በህዝብ ግንኙነት ስራዎች ላይ ፍላጎት እና መሰረታዊ ክህሎት ያለው/ያላት። ✅ ለማህበሩ ስራ በፈቃደኝነት ጊዜን መስጠት የሚችል/የምትችል።

ሆን ተብሎ ደረቅ ቼክ መስጠት በወንጀል ህግ ያስቀጣል። ጥፋቱ ከባድ ከሆነ እስከ 10 ዓመት የሚደርስ ፅኑ እስራትና መቀጮ ያስቀጣል። በቸልተኝነት ከሆነ ደግሞ እስከ 1 ዓመት ቀላል እስራት ወይም መቀጮ ያስቀጣል። ​ደረቅ ቼክ የሚሰጡ ሰዎች በብሔራዊ ባንክ መመሪያ መሰረት "በጥቁር መዝገብ" ውስጥ ይገባሉ፤ ይህ ደግሞ የቼክ ሂሳብን ከመጠቀም እስከመከልከል ያደርሳል። ​ተቀባዩ ቼኩ ሳይከፈልለት ቢቀር፣ በፍትሐ ብሔር ህግ መሰረት ከሰሰው ገንዘቡን ማስመለስ ይችላል። ​ ቼክ ሲቀበሉ የቼኩን ትክክለኛነት (ፊርማ፣ ቀን፣ የገንዘብ መጠን፣ የባንክ ቅርንጫፍ) ማረጋገጥ የግድ ነው። እንዲሁም ቼኩ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ6 ወር ጊዜ ውስጥ ለክፍያ ማቅረብ አለብዎት:: ቼክ ለዘመናዊ ግብይት ጠቃሚ መሳሪያ ቢሆንም፣ ክፍያ ሲፈጽሙ በሂሳብዎ ውስጥ በቂ ገንዘብ መኖሩን ማረጋገጥና ቼክ ሲቀበሉ ጥንቃቄ ማድረግ ህጋዊ ችግሮችን ለመቀነስ ወሳኝ ነው።

photo content

ፍርድ ቤት በዋስ እንዲፈቱ የወሰነላቸው የ76 ዓመቷ አዛውንት ከሦስት ቀናት መዘግየት በኋላ ከእስር ተለቀቁ። ሰኔ 8/2018 ዓ.ም ከሚኖሩበት ቀበሌ ተወስደው በመቐለ ታስረው የነበሩት የ76 ዓመቷ አ
+1
ፍርድ ቤት በዋስ እንዲፈቱ የወሰነላቸው የ76 ዓመቷ አዛውንት ከሦስት ቀናት መዘግየት በኋላ ከእስር ተለቀቁ። ሰኔ 8/2018 ዓ.ም ከሚኖሩበት ቀበሌ ተወስደው በመቐለ ታስረው የነበሩት የ76 ዓመቷ አዛውንት ወ/ሮ አኸዛ ሕሉፍ፣ ፍርድ ቤት የዋስ መብት ቢፈቅድላቸውም ፖሊስ ትእዛዙን ሳይተገብር ቆይቶ ዛሬ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 ሰዓት ላይ በዋስ መለቀቃቸው ታወቀ። የሰባ እንደርታ ወረዳ ፍርድ ቤት ሰኔ 10/ 2018 ዓ.ም በዋለው ችሎት አዛውንቷ በ5 ሺህ ብር ዋስ ከእስር እንዲፈቱ ወስኖ የነበረ ቢሆንም የፖሊስ አካላት የፍርድ ቤቱን ሕጋዊ ትእዛዝ በማዘግየት ዛሬ ከ3 ቀን በኃላ ተግባራዊ አድርገውታል። የአዛውንቷን ውክልና በመያዝ "Access for Human Rights and Social Justice" የተባለው የሰብአዊ መብት ተሟጋች ድርጅት ፍርድ ቤት በመቅረብ የተሟገተ ሲሆን፣ ግለሰቧ የተከሰሱበት "የመኸተ አዋጅ" በትግራይ የሚገኘውን የኢፌዴሪ ሕገ-መንግሥት የሚጥስና ሕገ-መንግሥቱ የማያውቀው በመሆኑ ክሱ ተቀባይነት የለውም ሲል ተከራክሯል። ፍርድ ቤቱም የቀረበውን የሕግ መከራከሪያ በመቀበል በአዛውንቷ ላይ የቀረበውን ክስ ውድቅ በማድረግ የዋስ መብታቸው ተጠብቆ እንዲፈቱ መወሰኑ ይታወሳል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ መቐለ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

ክብርት ዳኛዋን በችሎት የገደለው እራሱን አጠፋ። በችሎት አዳራሽ በሽጉጥ ክብርት ዳኛዋን እና ባለቤቱን የገደለው ግለሰብ ከ3ኛ ፎቅ ላይ እራሱን ወርውሮ ህይወቱን አጠፋ። ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ/
ክብርት ዳኛዋን በችሎት የገደለው እራሱን አጠፋ። በችሎት አዳራሽ በሽጉጥ ክብርት ዳኛዋን እና ባለቤቱን የገደለው ግለሰብ ከ3ኛ ፎቅ ላይ እራሱን ወርውሮ ህይወቱን አጠፋ። ግንቦት 27 ቀን 2018 ዓ/ም በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ሸዋ ዞን በሆለታ ወልመራ ወረዳ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በችሎት አዳራሽ የቤተሰብ ክርክርን መዝገብ ስትመለከት የነበረችው ክብርት ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ እንዲሁም የክርክሩ አካል የሆነች የተከሳሹ የቀድሞ ባለቤት ወይዘሮ አልማዝ መኮንን በተከሳሹ በተተኮሰ ጥይት ህይወታቸውን እንዲያልፍ ማድረጉ አይዘነጋም። በዕለቱም እራሱ ላይ በመተኮስ ቆስሎ የነበረዉ አቅነዉ በቀለ የተባለው ግለሰብ በፖሊስ ጥበቃ እየተደረገ በቅዱስ ጳውሎስ ሆስፒታል የሕክምና ክትትል ላይ ነበር። ሆኖም ግለሰቡ በዛሬው ቀን ሕክምናውን ጨርሶ ከሆስፒታሉ ለማውጣት ዝግጅት እየተደረገ ባለበት ጊዜ ላይ ከሆስፒታሉ ሕንፃ 3ኛው ፎቅ በመስኮት እራሱን በመወርወር እራሱን ማጥፋቱ ተረጋግጧል። Via: ታሪክ አዱኛ

photo content

photo content

ጥሩ ጠበቃ ክርክርን የሚያሸንፍ ብቻ ሳይሆን፣ ግጭትን የሚያስቀር ነው🙏✍️

CALL FOR VOLUNTEERS BE PART OF SOMETHING MEANINGFUL Inspired Development is seeking passionate, committed, and purpose-driven
CALL FOR VOLUNTEERS BE PART OF SOMETHING MEANINGFUL Inspired Development is seeking passionate, committed, and purpose-driven individuals who are ready to learn, grow, and create lasting impact through volunteer service. AVAILABLE ROLES • Website Development • Content Creation • Social Media Management • Host • Volunteer Manager • Training Facilitator ABOUT THE OPPORTUNITY This is a flexible half-day volunteer opportunity designed for individuals who want to gain practical experience while balancing their studies, work, or other commitments. DURATION 3–6 Months WHAT YOU WILL RECEIVE 🏆 Certificate of Recognition 📝 Professional Recommendation Letter 📄 Official Support Letter 💼 Practical Work Experience 📈 Skills Development Opportunities 🤝 Professional Networking 🎯 Mentorship and Career Growth 🌍 Opportunity to Contribute to Meaningful Social Impact LEARN. GROW. LEAD. IMPACT. CONTACT US +251 98 685 6264 INSPIRED DEVELOPMENT Empowering People. Inspiring Change.

መከላከል ከማከም፣ የሕግ ምክርም ከክስ ሂደት ይበልጣል✍️🙏
መከላከል ከማከም፣ የሕግ ምክርም ከክስ ሂደት ይበልጣል✍️🙏

እውነት የፍትህ ነፍስ ናት፤ ሕግ ደግሞ የፍትህ አካል‼️🙏✍️
እውነት የፍትህ ነፍስ ናት፤ ሕግ ደግሞ የፍትህ አካል‼️🙏✍️

1142_የኤሌክትሮኒክ_ደረሰኝ_ሥርዓት_አስተዳደር_መመሪያ_ቁጥር_1142_2018.pdf6.48 KB

መብትህ የሚያበቃው የሌላው መብት በሚጀምርበት መስመር ላይ ነው።

ክስ ከመቅረቡ በፊት ፍርድ፣ አቤቱታ ከመሰማቱ በፊት ውሳኔ የሚሹ ሰዎች እየበዙ ነው።✍️✍️🙏
ክስ ከመቅረቡ በፊት ፍርድ፣ አቤቱታ ከመሰማቱ በፊት ውሳኔ የሚሹ ሰዎች እየበዙ ነው።✍️✍️🙏

Repost from የሕግ ቤት
😭😭​በገዛ ባሏን በመግደል ወንጀል ተከሳ የሞት ፍርድ ተበይኖባት የነበረችው ኬትሊን ሄይስ የተባለችው ግለሰብ፣ የፍርድ አፈጻጸሙ ሊከናወን አምስት ደቂቃ ብቻ ሲቀረው በስምንት ዓመት ታናሽ ልጇ ምስ
😭😭​በገዛ ባሏን በመግደል ወንጀል ተከሳ የሞት ፍርድ ተበይኖባት የነበረችው ኬትሊን ሄይስ የተባለችው ግለሰብ፣ የፍርድ አፈጻጸሙ ሊከናወን አምስት ደቂቃ ብቻ ሲቀረው በስምንት ዓመት ታናሽ ልጇ ምስክርነት ከስቅላት መትረፏ ተገልጿል። ​ከስድስት ዓመታት በፊት በነበረ አንድ ምሽት፣ የኬትሊን ሄይስ ባለቤት በኩሽና ውስጥ በስለት ተወግቶ ሕይወቱ አልፎ ተገኝቶ ነበር። በወቅቱ በነበረው ፈጣን ምርመራ፣ የደም ጠብታ ያለበት የኪስ መሣሪያ (ቢላዋ) በኬትሊን መኝታ ክፍል ውስጥ ከአልጋዋ ስር የተገኘ ሲሆን፣ በላዩ ላይም የእሷ የጣት አሻራ አርፎበት ነበር። ​ምንም እንኳን ግለሰቧ ወንጀሉን ፈጽሞ እንዳልፈጸመችና ንጽሕት መሆኗን በተደጋጋሚ ብትገልጽም፣ ፍርድ ቤቱ የቀረቡትን የፎረንሲክ ማስረጃዎች መሠረት በማድረግ የሞት ፍርድ ውሳኔ አስተላልፎባት ነበር። በዚህም ምክንያት ለስድስት ዓመታት ያህል በጽኑ እስራት ስትማቅቅ ቆይታለች። ​የሞት ፍርዱ የሚፈጸምበት ዕለት ሲደርስ፣ ቤተሰቦቿ ለመጨረሻ ጊዜ እንዲሰናበቷት ተፈቅዶላቸው ነበር። በወቅቱ ዕድሜው ገና ስምንት ዓመት የነበረው ትንሹ ልጇ ኢታን፣ እናቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለማቀፍ በተጠጋበት ወቅት በሹክሹክታ የተናገረው ቃል ግን መላውን ተቋም አስደንግጧል። ​ኢታን ለእናቱ "ቢላዋውን ከአልጋሽ ስር ማን እንዳስቀመጠው አውቃለሁ" ማለቱን ተከትሎ፣ በአቅራቢያው የነበሩ የማረሚያ ቤቱ ጠባቂዎች እና የprison ኃላፊው ሂደቱን በአስቸኳይ እንዲቆም ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ​የስምንት ዓመቱ ሕፃን ኢታን በዕንባ ታጥቦ ለባለሥልጣናት በሰጠው ቃል፣ ወንጀሉ በተፈጸመበት ምሽት (ዕድሜው የሁለት ዓመት ሕፃን ሳለ) ከአስፈሪ ሕልም ባንኖ ወደ ኩሽና ሲወርድ የአባቱን ወንድም — አጎቱን ቪክቶር ሄይስን ከአባቱ አስከሬን በላይ ቆሞ ማየቱን ይፋ አድርጓል። ​እንደ ምስክርነቱ ቃል፣ አጎቱ ቪክቶር ወንድሙን ከገደለ በኋላ፦ ​እናቱ በወሰደችው ማስታገሻ ምክንያት ተኝታ ሳለች እጇን በመያዝ የጣት አሻራዋን በቢላዋው ላይ አስፍሯል። ​ደሙን በለበሰችው የሌሊት ልብስ ላይ በመቀባት ወንጀሉን በእሷ ላይ አሳብቧል። ​ከመውጣቱ በፊትም ትንሹን ኢታንን በማየት "ይህንን ለሰው ብትናገር አንተንም ሆነ እህትህን እገድላችኋለሁ" በማለት አስፈራርቶት ነበር። ሕፃኑም በዚህ ፍርሃት ምክንያት ለስድስት ዓመታት ምስጢሩን ደብቆ ለመቆየት ተገዷል። ​ይህንን አስደንጋጭ ምስክርነት ተከትሎ የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች በሰነባበተው መዝገብ ላይ አዲስ ምርመራ እንዲጀመር አድርገዋል። የፎረንሲክ ባለሙያዎች በድጋሚ ባደረጉት የላብራቶሪ ምርመራ፣ በትግሉ ወቅት በአስከሬኑ ሸሚዝ ኮሌታ ላይ የቪክቶር የዲኤንኤ (DNA) ቅሪት ማግኘት የቻሉ ሲሆን፣ ከቤት ውጭ በጭቃ ላይ የነበረው የጫማ አሻራም የአጎቱ መሆኑ ተረጋግጧል። ​ወንጀሉ የተፈጸመው በቤተሰብ ንግድ ድርሻ እና በቁማር ዕዳ ምክንያት እንደነበር የደረሰበት ፍርድ ቤት፣ ላለፉት ስድስት ዓመታት በንጽሕናዋ የታሰረችው ካሮላይን ሄይስ በአስቸኳይ ከእስር እንድትፈታ እና ክሷ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ ወስኗል። እውነተኛው ገዳይ ቪክቶር ሄይስ ደግሞ በከባድ መነሻ ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ፣ ያለ ምንም የዋስትና መብት የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተፈርዶበት ወደ ወህኒ ተላኳል። ***** የኔ ጥያቄ፣ አዲሱ የኢትዮጵያ የወንጀል ሥነሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ከረጅም ጊዜ በኋላ ፍርድ እንዲከለስ ይፈቅዳል ??? ከ ንጋቱ በቀለ-ጠበቃና የሕግ-አማካሪ የፌስቡክ ገፅ ተገኘ🙏🙏✍️✍️✍️

photo content
+1

#ለመረጃ: በኮንትሮባንድ ጭነት ምክንያት ተሽከርካሪ እንዲወረስ የሚያስችል ድንጋጌ የያዘው የተሻሻለው የጉምሩክ አዋጅ ፀደቀ! ሙሉ ሰነዱን ማንበብ ለምትፈልጉ ከላይ ተቀምጧል!

#ለመረጃ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መረጃዎች የሚደራጁበት እና የሚተነተኑበት (የዋጋ ንረትን ጨምሮ) የኢትዮጵያ የስታቲስቲክስ አዋጅ ተሻሽሏል! ሙሉ ሰነዱን ማንበብ ለምትፈልጉ ከላይ ተቀምጧል!

photo content
+6