ch
Feedback
አለ ሕግ

አለ ሕግ

前往频道在 Telegram

ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service Website: alehig.com https://linktr.ee/alehig WhatsApp👉 #+251920666595 Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ

显示更多

📈 Telegram 频道 አለ ሕግ 的分析概览

频道 አለ ሕግ (@alehig) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 940 名订阅者,在 法律 类别中位列第 506,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 113

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 940 名订阅者。

根据 10 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -91,过去 24 小时变化为 6,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.10%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.21% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 160 次浏览,首日通常累积 1 309 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 15

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ከጠበቃና የሕግ አማካሪ አማራጭ የሕግ እውቀትና አገልግሎት Alternative legal enlightenment & Service Website: alehig.com https://linktr.ee/alehig WhatsApp👉 #+251920666595 Telegram👉 @MikiasMelak የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ #የሕግ_መረጃ

凭借高频更新(最新数据采集于 11 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 法律 类别中的关键影响点。

15 940
订阅者
+624 小时
+207
-9130
帖子存档
Repost from የሕግ ቤት
😭😭​በገዛ ባሏን በመግደል ወንጀል ተከሳ የሞት ፍርድ ተበይኖባት የነበረችው ኬትሊን ሄይስ የተባለችው ግለሰብ፣ የፍርድ አፈጻጸሙ ሊከናወን አምስት ደቂቃ ብቻ ሲቀረው በስምንት ዓመት ታናሽ ልጇ ምስ
😭😭​በገዛ ባሏን በመግደል ወንጀል ተከሳ የሞት ፍርድ ተበይኖባት የነበረችው ኬትሊን ሄይስ የተባለችው ግለሰብ፣ የፍርድ አፈጻጸሙ ሊከናወን አምስት ደቂቃ ብቻ ሲቀረው በስምንት ዓመት ታናሽ ልጇ ምስክርነት ከስቅላት መትረፏ ተገልጿል። ​ከስድስት ዓመታት በፊት በነበረ አንድ ምሽት፣ የኬትሊን ሄይስ ባለቤት በኩሽና ውስጥ በስለት ተወግቶ ሕይወቱ አልፎ ተገኝቶ ነበር። በወቅቱ በነበረው ፈጣን ምርመራ፣ የደም ጠብታ ያለበት የኪስ መሣሪያ (ቢላዋ) በኬትሊን መኝታ ክፍል ውስጥ ከአልጋዋ ስር የተገኘ ሲሆን፣ በላዩ ላይም የእሷ የጣት አሻራ አርፎበት ነበር። ​ምንም እንኳን ግለሰቧ ወንጀሉን ፈጽሞ እንዳልፈጸመችና ንጽሕት መሆኗን በተደጋጋሚ ብትገልጽም፣ ፍርድ ቤቱ የቀረቡትን የፎረንሲክ ማስረጃዎች መሠረት በማድረግ የሞት ፍርድ ውሳኔ አስተላልፎባት ነበር። በዚህም ምክንያት ለስድስት ዓመታት ያህል በጽኑ እስራት ስትማቅቅ ቆይታለች። ​የሞት ፍርዱ የሚፈጸምበት ዕለት ሲደርስ፣ ቤተሰቦቿ ለመጨረሻ ጊዜ እንዲሰናበቷት ተፈቅዶላቸው ነበር። በወቅቱ ዕድሜው ገና ስምንት ዓመት የነበረው ትንሹ ልጇ ኢታን፣ እናቱን ለመጨረሻ ጊዜ ለማቀፍ በተጠጋበት ወቅት በሹክሹክታ የተናገረው ቃል ግን መላውን ተቋም አስደንግጧል። ​ኢታን ለእናቱ "ቢላዋውን ከአልጋሽ ስር ማን እንዳስቀመጠው አውቃለሁ" ማለቱን ተከትሎ፣ በአቅራቢያው የነበሩ የማረሚያ ቤቱ ጠባቂዎች እና የprison ኃላፊው ሂደቱን በአስቸኳይ እንዲቆም ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። ​የስምንት ዓመቱ ሕፃን ኢታን በዕንባ ታጥቦ ለባለሥልጣናት በሰጠው ቃል፣ ወንጀሉ በተፈጸመበት ምሽት (ዕድሜው የሁለት ዓመት ሕፃን ሳለ) ከአስፈሪ ሕልም ባንኖ ወደ ኩሽና ሲወርድ የአባቱን ወንድም — አጎቱን ቪክቶር ሄይስን ከአባቱ አስከሬን በላይ ቆሞ ማየቱን ይፋ አድርጓል። ​እንደ ምስክርነቱ ቃል፣ አጎቱ ቪክቶር ወንድሙን ከገደለ በኋላ፦ ​እናቱ በወሰደችው ማስታገሻ ምክንያት ተኝታ ሳለች እጇን በመያዝ የጣት አሻራዋን በቢላዋው ላይ አስፍሯል። ​ደሙን በለበሰችው የሌሊት ልብስ ላይ በመቀባት ወንጀሉን በእሷ ላይ አሳብቧል። ​ከመውጣቱ በፊትም ትንሹን ኢታንን በማየት "ይህንን ለሰው ብትናገር አንተንም ሆነ እህትህን እገድላችኋለሁ" በማለት አስፈራርቶት ነበር። ሕፃኑም በዚህ ፍርሃት ምክንያት ለስድስት ዓመታት ምስጢሩን ደብቆ ለመቆየት ተገዷል። ​ይህንን አስደንጋጭ ምስክርነት ተከትሎ የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎች በሰነባበተው መዝገብ ላይ አዲስ ምርመራ እንዲጀመር አድርገዋል። የፎረንሲክ ባለሙያዎች በድጋሚ ባደረጉት የላብራቶሪ ምርመራ፣ በትግሉ ወቅት በአስከሬኑ ሸሚዝ ኮሌታ ላይ የቪክቶር የዲኤንኤ (DNA) ቅሪት ማግኘት የቻሉ ሲሆን፣ ከቤት ውጭ በጭቃ ላይ የነበረው የጫማ አሻራም የአጎቱ መሆኑ ተረጋግጧል። ​ወንጀሉ የተፈጸመው በቤተሰብ ንግድ ድርሻ እና በቁማር ዕዳ ምክንያት እንደነበር የደረሰበት ፍርድ ቤት፣ ላለፉት ስድስት ዓመታት በንጽሕናዋ የታሰረችው ካሮላይን ሄይስ በአስቸኳይ ከእስር እንድትፈታ እና ክሷ ሙሉ በሙሉ እንዲሰረዝ ወስኗል። እውነተኛው ገዳይ ቪክቶር ሄይስ ደግሞ በከባድ መነሻ ወንጀል ጥፋተኛ ሆኖ በመገኘቱ፣ ያለ ምንም የዋስትና መብት የዕድሜ ልክ ጽኑ እስራት ተፈርዶበት ወደ ወህኒ ተላኳል። ***** የኔ ጥያቄ፣ አዲሱ የኢትዮጵያ የወንጀል ሥነሥርዓትና የማስረጃ ሕግ ከረጅም ጊዜ በኋላ ፍርድ እንዲከለስ ይፈቅዳል ??? ከ ንጋቱ በቀለ-ጠበቃና የሕግ-አማካሪ የፌስቡክ ገፅ ተገኘ🙏🙏✍️✍️✍️

photo content
+1

#ለመረጃ: በኮንትሮባንድ ጭነት ምክንያት ተሽከርካሪ እንዲወረስ የሚያስችል ድንጋጌ የያዘው የተሻሻለው የጉምሩክ አዋጅ ፀደቀ! ሙሉ ሰነዱን ማንበብ ለምትፈልጉ ከላይ ተቀምጧል!

#ለመረጃ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ መረጃዎች የሚደራጁበት እና የሚተነተኑበት (የዋጋ ንረትን ጨምሮ) የኢትዮጵያ የስታቲስቲክስ አዋጅ ተሻሽሏል! ሙሉ ሰነዱን ማንበብ ለምትፈልጉ ከላይ ተቀምጧል!

photo content
+6

⚖️ የሰበር ሰሚ ችሎት ፦ "ስራ ባልተሰራበት የጦርነት ወቅት ደመወዝ አይከፈልም!" ​የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሰበር ሰሚ ችሎት በትግራይ ክልል በተከሰተው ጦርነት ምክንያት ስራ ተቋርጦባቸው በነበሩ ፕሮጀክቶች ላይ ሲያከራክር የነበረውን ጉዳይ መቋጫ ሰጥቷል። ​📌 የጉዳዩ መነሻ ​በትግራይ ክልል በመንገድ ስራ ላይ ተሰማርቶ የነበረው የቻይና ገዙባ እና ሰንሻይን ኮንስትራክሽን ጆይንት ቬንቸር (GDGC-Sunshine JV) ሰራተኞች፤ "ከጥቅምት 2013 ዓ.ም ጀምሮ ለ34 ወራት ከ15 ቀናት ያልተከፈለን ደመወዝ ይከፈለን" በማለት ክስ መስርተው ነበር። የቀድሞ የመቀሌ ወረዳ፣ ከፍተኛ እና የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤቶች ሰራተኞቹ ደመወዙ ሊከፈላቸው ይገባል በማለት ወስነው ነበር። ​⚖️ የሰበር ሰሚ ችሎት ውሳኔ ​ኩባንያው "በጦርነት ምክንያት ስራ ባልተሰራበት ሁኔታ ደመወዝ መክፈል የለብኝም" በማለት ያቀረበውን አቤቱታ የመረመረው የፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት የክልሉን ፍርድ ቤቶች ውሳኔ በሙሉ ድምፅ ሽሮታል። ​ፍርድ ቤቱ ለውሳኔው የጠቀሳቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦ ​ደመወዝ ለስራ የሚሰጥ ክፍያ ነው፦ በአዋጅ ቁጥር 1156/2011 አንቀጽ 54(1) መሰረት ደመወዝ የሚከፈለው ለተሰራ ስራ ብቻ ነው። ​የአቅም በላይ ምክንያት፦ ጦርነቱ ኩባንያው ስራ እንዳያሰራ፣ ሰራተኞቹም ስራቸውን እንዳያከናውኑ የከለከለ "የአቅም በላይ ምክንያት" (Force Majeure) ነው። ​የአሰሪው ጥፋት አለመኖር፦ ሰራተኛው ስራ ለመስራት ዝግጁ ሆኖ እያለ አሰሪው የስራ መሳሪያ ባለማቅረቡ ስራ ቢፈታ ደመወዝ ሊከፈለው ይችል ነበር። ነገር ግን በዚህ ጉዳይ ስራው የተቋረጠው በሁለቱም ወገኖች ቁጥጥር ውጭ በሆነ የጦርነት ሁኔታ ነው። ​የውል መቋረጥ፦ ስራው ከተቋረጠ ከ90 ቀናት በላይ ከሆነ ውሉ በህግ እንደተቋረጠ የሚቆጠር በመሆኑ፣ ኩባንያው በጦርነት ለቆመ ስራ የዓመታት ደመወዝ የመክፈል ግዴታ የለበትም። ​🔍 ትርጉሙ ​ይህ ውሳኔ በጦርነት ወይም በተመሳሳይ ከአቅም በላይ በሆኑ ምክንያቶች ስራ አቁመው ለነበሩ በርካታ ተቋማት እንደ ትልቅ የህግ መመሪያ (Precedent) ሆኖ የሚያገለግል ነው። ውሳኔው ከታች ተያይዟል!!!

አግባባዊ የመድኃኒት አጠቃቀም መመሪያ ቁጥር 1138/2018 የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን የሕክምና መድኃኒቶች ያለአግባብ መወሰድና መላመድን ለመግታት የሚያስችል ጠንካራ ቁጥጥር ሥርዓት የ
+1
አግባባዊ የመድኃኒት አጠቃቀም መመሪያ ቁጥር 1138/2018 የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን የሕክምና መድኃኒቶች ያለአግባብ መወሰድና መላመድን ለመግታት የሚያስችል ጠንካራ ቁጥጥር ሥርዓት የያዘ አዲስ «አግባባዊ የመድኃኒት አጠቃቀም መመሪያ ቁጥር 1138/2018» በሥራ ላይ ውሏል። 💊 የመድኃኒት በድጋሚ ዕደላና ቁጥጥር • ታካሚዎች በታዘዘላቸው መመርያ መሠረት መድኃኒት በአግባቡ አለመጠቀማቸው፣ ለሱስ የመጋለጥ ሥጋት ማሳየታቸው ወይም የሕክምና ውጤታማነት ማጣት እንደገጠማቸው ሲታወቅ የመድኃኒት ባለሙያዎች መድኃኒቱን በድጋሚ ከመስጠት ተቆጥበው ታካሚውን ወደ ታከመበት ሐኪም ቤት እንዲልኩ መመሪያው ያስገድዳል። • ማንኛውም የመድኃኒት ባለሙያ መድኃኒት በአንድ ማዘዣ እንደገና ለማደል የሚችለው የሕክምና ባለሙያ በመድኃኒት ማዘዣው ላይ በድጋሚ ማደል እንደሚቻል የገለጸ እንደሆነ ብቻ ነው። • ማንኛውም የመድኃኒት ባለሙያ መድኃኒት በድጋሚ ሲያድል በመድኃኒት ማዛዣው ላይ ከተገለጸው መድኃኒት ዓይነት፣ የአወሳሰድ መንገድ፣ መጠን፣ ብዛት፣ ወይም ድግግሞሽ የተለየ ማደል እንደማይችልም ተገልጿል። የመድኃኒት ባለሙያ መድኃኒት በድጋሚ ሲያድል፤ - ታካሚው መድኃኒትን በአግባቡ አለመጠቀም፣ - በመድኃኒቱ ሱስኝነት መጋለጥ፣ - የታዘዘን መመሪያ አለመከተል፣ - የሕክምና ውጤታማነት ማጣት ወይም የደኅንነት ሥጋቶች መኖሩን ሲጠረጥር መድኃኒቱን በድጋሚ ከመስጠት መቆጠብና ታካሚውን ወደ ሚመለከተው የሕክምና ክፍል ወይም ተቋም መላክ ይኖርበታል። አንድ ፋርማሲስት ማንኛውንም መድኃኒት በድጋሚ ሲያድል እንደገና ማደሉ የተከናወነበት ቀን፣ በዕለቱ የታደለው መጠንና የሚቀረው ድግግሞሽ የተመለከተ መረጃን በአግባቡ መዝግቦ መያዝ አለበት። 🦠 የፀረ-ተዋህስያን መድኃኒቶች አጠቃቀም ሥርዓት • መመሪያው፣ የፀረ ተዋህስያን መድኃኒቶች በተዋህሲያን መላመድን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ጥብቅ ድንጋጌዎችን አካቷል። • ማንኛውም ሆስፒታል፣ ጤና ጣቢያ ወይም ልዩ የሕክምና ማዕከል ይህንን ሥጋት ለመግታት የሚያስችል አግባባዊ የፀረ ተዋህስያን መድኃኒቶች አጠቃቀም ሥርዓት የመዘርጋት ሕጋዊ ግዴታ ተጥሎበታል። • ማንኛውም የሕክምና ባለሙያ ክሊኒካዊ ወይም የላቦራቶሪ ምርመራ ማስረጃ ሳይኖረው ለታካሚ የፀረ ተዋህስያን ሕክምና ማስጀመር እንደሌለበት ተደንግጓል። ሆኖም ለሕይወት አሥጊ የሆነ ኢንፌክሽን መኖሩ ከተጠረጠረ ሕክምናውን ወዲያውኑ መጀመር እንደሚቻል ተፈቅዷል። የፀረ-ተዋስያን መድኃኒቶች መጋቢ ኮሚቴ ፦ እያንዳንዱ ሆስፒታልና ጤና ጣቢያ " የፀረ-ተዋስያን መድኃኒቶች መጋቢ ኮሚቴ" የማቋቋም ግዴታ አለበት። ኮሚቴው የፀረ-ተዋስያን መድኃኒቶችን አቅርቦት፣ አያያዝ፣ አዘዘዝና አጠቃቀም ይከታተላል፤ ተገቢነቱን ለማረጋገጥም የቅድመ ኦዲትና የቅድመ ፈቃድ አሠራሮችን ተግባራዊ ያደርጋል። መድኃኒቶቹን "በተደራሽ"፣ "ትኩረት የሚሹ" እና "መጠባበቂያ" በማለት ይመድባል። ብክነትን ለመከላከል፣ በብሔራዊ መዘርዝር "በመጠባበቂያ" ሥር ያሉትን መድኃኒቶች ወደ ትኩረት የሚሹ ወይም ተደራሽ ዝርዝር ዝቅ አድርጎ ማካተት ፈጽሞ የተከለከለ ነው። 💻 የኤሌክትሮኒክስ ማዘዣ (Electronic Prescription) ሥርዓት፦ • እያንዳንዱ የኤሌክትሮኒክስ ማዘዣ ተከታታይ መለያ ቁጥር (Serial Number) ሊኖረውና ለተፈቀደላቸው የጤና ባለሙያዎች ብቻ ተደራሽ መሆን አለበት። • አንዴ ከተሰጠ በኋላ ከራሱ ከሐኪሙ ውጪ በማንም ሊቀየር አይችልም፤ ከተቀየረም የተሟላ መረጃው መመዝገብ አለበት። • ታካሚው መድኃኒቱን ከተቋሙ መግዛት ካልፈለገ፣ ተቋሙ ማዘዣውን አትሞ (Print አድርጎ) የመስጠት ግዴታ አለበት። • ማዘዣዎች በማዕከላዊ ቋት (Database) ወይም በወረቀት ታትመው ቢያንስ ለሁለት ዓመታት መቀመጥ አለባቸው። ሲስተሙም አስተማማኝ የምትክ ቅጂ (Backup) ሊኖረው ይገባል። ⚖️ ጥፋቶችና አዲሱ የአስተዳደራዊ ቅጣት መሰላል ፦ ነባሩ መመሪያ ፈቃድ ለማያሳግዱ ጥፋቶች ማስጠንቀቂያ የሚሰጥና ማስተካከያ ካልተደረገ ወደ ሌላ እርምጃ የሚሻገር የነበረ ሲሆን፣ አዲሱ መመሪያ ግን ይበልጥ ግልጽና ጠንካራ የቅጣት መሰላል ዘርግቷል። በዚህም ማንኛውም ሰው ግዴታውን ካልተወጣ ወይም ሕገወጥ ድርጊት ፈጽሞ ከተገኘ፣ ፈቃድ የሰጠው አካል ከማስጠንቀቂያና ከገንዘብ መቀጮ ባለፈ የብቃት ማረጋገጫን ወይም የሙያ ፈቃድን እስከ ማገድና መሰረዝ የሚደርስ ከባድ እርምጃ በቀጥታ የመውሰድ ሥልጣን ተሰጥቶታል። ባለሥልጣኑ መመሪያው መጣሱን ካረጋገጠ፣ ምርቱን ከመያዝ፣ እንዲወገድ ወይም ወደ መጣበት ተቋም እንዲመለስ ከማዘዝ በተጨማሪ፣ ጥፋቱን ፈቃድ ለሰጠው አካል በማሳወቅ እርምጃ እንዲወሰድ ያደርጋል። አግባብ ያለው አካል የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ እንዲሰጥ የሚያስገድዱ 11 የጥፋት ዓይነቶች ተለይተዋል። ከእነዚህም መካከል ፦ ° ያለ ምርመራ መድኃኒት ማዘዝ፣ ° ሕግ ያላሟላ ማዘዣ መጠቀም፣ ° ያለ በቂ ምክንያት በንግድ ስም (Brand Name) ማዘዝ ወይም ማደል ይገኙበታል። የአገልግሎት ጊዜያቸው ያለፈባቸውን ማዘዣዎች መጠቀም የተከለከለ ሲሆን፣ ከተጻፈ 30 ቀናት ያለፈበትን መደበኛ ማዘዣ ወይም ከተገዛ 7 ቀናት ያለፈበትን የአንቲባዮቲክስ ማዘዣ በመጠቀም መድኃኒት ያደለ ባለሙያ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ ይሰጠዋል። መመሪያው ጥፋት በሚያዘወትሩና የደኅንነት ሥጋት በሚፈጥሩ ባለሙያዎችና ተቋማት ላይ እስከ 1 ዓመት የሚደርስ የፈቃድ ዕገዳ ጥሏል። እርምጃው የሚወሰደውም፦ - በኮፒ ማዘዣ መድኃኒት በጨመረ፣ - በአንድ ማዘዣ ከአንድ ጊዜ በላይ ባደለ፣ - የተሳሳተ ወይም ያልታዘዘ መድኃኒት በሰጠ፣ - የታካሚን ክብርና ሚስጥር ባልጠበቀ፣ እንዲሁም ያለ ማዘዣ ወይም ባልተፈቀደ ተቋም መድኃኒት በቀመመ ላይ ነው። ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው። @tikvahethiopia

የአዲስ አበባ ፖሊስ የውጭ ሀገር ዜጎችን በታጋችነት የያዙ ወንጀለኞችን በቁጥጥር ስር አዋለ የአዲስ አበባ ፖሊስ በኢትዮጵያ የስሪላንካ ኤምባሲ ተወካዮች ጥቆማ መሠረት፣ በታጋችነት ተይዘው የነበሩ ሦስ
+3
የአዲስ አበባ ፖሊስ የውጭ ሀገር ዜጎችን በታጋችነት የያዙ ወንጀለኞችን በቁጥጥር ስር አዋለ የአዲስ አበባ ፖሊስ በኢትዮጵያ የስሪላንካ ኤምባሲ ተወካዮች ጥቆማ መሠረት፣ በታጋችነት ተይዘው የነበሩ ሦስት የስሪላንካ ዜጎችን ነጻ በማውጣት ወንጀለኞቹን በቁጥጥር ስር ማዋሉን አስታውቋል። ታጋቾቹ በሻሸመኔ ከተማ ወረዳ ቡቄ ቀበሌ፣ ደራርቱ ሆቴል ጀርባ በሚገኝ መኖሪያ ቤት ውስጥ በአንድ ክፍል ተቆልፎባቸው ተገኝተዋል። ለስራ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ሦስት የስሪላንካ ዜጎች መጥፋታቸውን ተከትሎ፣ በስሪላንካ የሚገኙ ቤተሰቦቻቸው እያንዳንዳቸው 30 ሺህ ዶላር እንዲከፍሉ ተጠይቀው ነበር ነው የተባለው። የአዲስ አበባ ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ቡድን ባቋቋመው ክትትል፣ ታጋቾቹ ከኤርፖርት በኮድ 2C- 40461 ሰሌዳ ቁጥር ባላት ሱዚኪ ዲዛየር መኪና መሄዳቸውን በቴክኖሎጂ ታግዞ ማረጋገጡን ገልጿል። ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታ አካላት ጋር በመቀናጀት ባደረገው ኦፕሬሽን ሁለት ኢትዮጵያውያን እና አራት የፓኪስታን ዜግነት ያላቸውን በአጠቃላይ ስድስት ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ማዋል ችሏል። @Tikvahethmagazine

በሆለታ ወልመራ ወረዳ ፍርድ ቤት በተፈጠረው አሰቃቂ ድርጊት የተሰማኝን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽኩ፣ ይህ አሳዛኝ ክስተት የፍትህ አካላት ደህንነት ምን ያህል ስጋት ላይ እንደሆነ የሚያሳይ ማንቂያ ደወል ነው። በስራ ገበታዋ ላይ ፍትህን ለማስፈን ስትጥር የነበረችው ዳኛ ወርቄ ፈካንሳ እና ከሳሹ በግፍ መገደላቸው መላውን የህግ ማህበረሰብ ክፉኛ አሳዝኗል። በተለይም የቤተሰብ ችሎቶች ላይ እየታዩ ያሉ ማስፈራራቶች ችግሩ በየጊዜው እየተባባሰ መምጣቱን ያሳያል። እኔም ቀደም ሲል በአራዳ እና በኮልፌ ምድብ ችሎቶች በተመሳሳይ ሁኔታ የፍርድ ቤት ታዳሚዎች እና የህግ ባለሙያዎች ሲዛቱ አይቻለሁ። ይህ አደገኛ አካሄድ የፍትህ ስርዓቱን እንዳያቀጭጭ መንግስት የፍርድ ቤት ደህንነትን (Security) በአስቸኳይ ሊያጠናክር ይገባል። ለዳኛ ወርቄ ፈካንሳ ቤተሰቦችና ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መጽናናትን እመኛለሁ። #ፍትህ #የህግባለሙያ #ደህንነት #ሆለታ #የፍትህስርዓት

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አዲስ የፍራንኮ ቫሉታ መመሪያ ይፋ አድርጓል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬ ክምችት ላይ ጫና ሳይፈጥሩ ኢንቨስትመንትና ንግድን ለማሳለጥ ያስችላል ያለውን “የፍራንኮ ቫሉታ ገቢ ዕቃዎች መመሪያ ቁጥር FVD/01/2026” የተሰኘ አዲስ የሕግ ማዕቀፍ ይፋ አድርጓል። ይህ አዲስ መመሪያ ከዚህ ቀደም በፍራንኮ ቫሉታ አሠራር ላይ ይታዩ የነበሩ የቁጥጥር ክፍተቶችን ለመድፈንና ግልጽነትን ለማስፈን ያለመ መሆኑ ተገልጿል። ባንኩ በመመሪያው መግቢያ ላይ እንደገለጸው፣ ከዚህ ቀደም አጠቃላይና ዘመናዊ የቁጥጥር ሥርዓት ባለመኖሩ ምክንያት በፍራንኮ ቫሉታ ስም ሕገ-ወጥ የገንዘብ ዝውውር፣ የተዛባ ሪፖርት አቀራረብ እና የውጭ ምንዛሬ ቁጥጥርን የማለፍ አዝማሚያዎች ሲታዩ ቆይተዋል። በአዲሱ መመሪያ መሠረት በፍራንኮ ቫሉታ ዕቃዎችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዲያስገቡ የተፈቀደላቸው አካላት በዝርዝር ተቀምጠዋል። እነዚህም:- • የሀገር ውስጥ (በኢኮኖሚ ቀጠናዎች ያሉ)፣ የዲያስፖራ እና የውጭ ሀገር ባለሀብቶች፣ • በውጭ ባለሀብቶች የተያዙ የማኑፋክቸሪንግ እና የኢንዱስትሪ ተቋማት፣ • ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ያላቸው የልማት ፕሮጀክቶች፣ • ዲፕሎማቶች፣ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (NGOs)፣ • ዕርዳታ የሚቀበሉ የሃይማኖት እና የሲቪክ ማኅበራት፣ እንዲሁም የግል ንብረቶቻቸውን የሚያስገቡ ግለሰቦች ናቸው። ከእነዚህም በተጨማሪ የግል ንብረቶቻቸውን የሚያስገቡ ግለሰቦችና በቋሚነት ወደ ሀገር የሚመለሱ ኢትዮጵያውያንም ተጠቃሚ ይሆናሉ። ለሰው ሕይወት አስፈላጊ የሆኑ መድኃኒቶች ያለምንም የዋጋ ገደብ በፍራንኮ ቫሉታ እንዲገቡ የተፈቀደ ሲሆን፤ የማምረቻ ጥሬ ዕቃዎች፣ የካፒታል ዕቃዎችና የቴክኖሎጂ መሣሪያዎችም በመመሪያው ውስጥ ተካተዋል። የጉምሩክ ኮሚሽን ሁሉንም የፍራንኮ ቫሉታ ግብይቶች "FEMoUS" በሚባለው የውጭ ምንዛሬ ክልከላና ቁጥጥር ሥርዓት ውስጥ የመመዝገብ ግዴታ ተጥሎበታል። ተጠቃሚዎችም ትክክለኛ የንግድ ፈቃድ የመያዝ፣ አስፈላጊ ሰነዶችን ለጉምሩክ የማቅረብ እና ኦዲት ሊደረጉ የሚችሉ መዝገቦችን በሥርዓቱ የመያዝ ግዴታ አለባቸው። በመመሪያው ላይ የተቀመጡ ደንቦችን በመተላለፍ የተሳሳተ መግለጫ መስጠት፣ አሠራሩን ለሕገ-ወጥ ተግባር ማዋል እና የቁጥጥር ሥርዓቱን ለማለፍ መሞከር ጥብቅ ቅጣት እንደሚያስከትል ተደንግጓል። ማንኛውም ጥፋት ፈጽሞ የሚገኝ አካል በገንዘብ ቅጣት፣ ንብረቱ በመወረስ አልፎ ተርፎም በብሔራዊ ባንክ አዋጅ መሠረት በወንጀል ተጠያቂ እንደሚሆን መመሪያው ያስረዳል። ይህ አዲስ የፍራንኮ ቫሉታ መመሪያ ከዛሬ ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ.ም (May 29, 2026) ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሆኗል። በብሔራዊ ባንክ መመሪያ (አንቀጽ 2.4) ላይ በተቀመጠው ትርጓሜ መሰረት እንዲሁም የኢኮኖሚ ባለሞያዎች ትርጉም መሰረት "ፍራንኮ ቫሉታ" ማለት አንድ አስመጪ ዕቃዎችን ወደ ሀገር ውስጥ ለማስገባት የሚያስፈልገውን የውጭ ምንዛሬ (ለምሳሌ ዶላር ወይም ዩሮ) ከሀገር ውስጥ ባንኮች ሳይጠይቅ፣ በራሱ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ዕቃዎችን ወደ ሀገር የሚያስገባበት አሠራር ነው። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ግንቦት 21 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

#ኢትዮጵያ 🇪🇹 🚢 ለሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ብቻ ተከልለው ወይም በከፊል ባለቤትነት ተገድበው ከቆዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች አንዱ የሆነው የእቃ አስተላላፊነት (Freight Forwarding) ዘ
#ኢትዮጵያ 🇪🇹 🚢 ለሀገር ውስጥ ባለሀብቶች ብቻ ተከልለው ወይም በከፊል ባለቤትነት ተገድበው ከቆዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች አንዱ የሆነው የእቃ አስተላላፊነት (Freight Forwarding) ዘርፍ ለውጭ ባለሀብቶች ክፍት እንዲሆን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ቦርድ ወስኗል። ተጨማሪ 👇 www.facebook.com/61588053582297/posts/pfbid0DEL6Uy6Vf74UW4ZPohvipBJF3C9i1xTP74Y3GNsTh6i2E24NDUy53FQdtFYSzajyl/ @tikvahethiopia

የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተላለፈ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳ
+2
የሚኒስትሮች ምክር ቤት የፌዴራል ታክስ አስተዳደር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅን ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አስተላለፈ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ከነዚህ ጉዳዮች አንዱ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ነው። ምክር ቤቱ " የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ወጥቶ ሲሰራበት የቆየ ቢሆንም ባለፉት አመታት በሀገራችን በርካታ የኢኮኖሚ ለውጦች የተደረጉ በመሆኑ የታክስ አስተዳደር ሥርዓቱን ከዘመናዊ ዓለም አቀፍ ልምዶች ጋር ለማጣጣም፤ የታክስ አለመግባባቶችን በፍትሐዊነት፣ በሰላማዊ መንገድና በቅልጥፍና ለመፍታትና የተጠያቂነትና ግልጸኝነት አሰራር ለማስፈንና የታክስ ሕጎችን በተጠናከረ መልኩ ለማስፈጸም እንዲያስችል ተደርጎ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጁ ተዘጋጅቶ ቀርቧል " ሲል አሳውቋል። ምክር ቤቱ በረቂቅ አዋጁ ላይ በሰፊው ከተወያየ በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሀዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ (የሚኒስትሮች ምክር ቤት በሌሎች በርካታ ጉዳዮች ላይ ውሳኔ አሳልፏል ከላይ በተያያዘው ምስል ያንብቡ) ግንቦት 18 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

ህግ ማጥናት ለሚፈልጉ ሰዎች አስፈላጊው ሁኔታ ምንድነው? በኢትዮጵያ ህግ እና የህግ ትምህርት አውድ ህግ ማጥናት ማለት የፍርድ ቤት ክርክር መማር አይደለም። ህግ ማለት ፍትሕን፣ ስርዓትን፣ መብትን፣ ግዴታን እና ማህበራዊ ሰላምን የሚጠብቅ ስርዓት ነው። ስለዚህ ህግ ለማጥናት የሚፈልግ ሰው በትዕግስት፣ በሥነ-ምግባር፣ በአስተሳሰብ ጥራት እና በእውነት ፍቅር መዘጋጀት አለበት። 1. የህግ ትምህርት ቤት ዋና አላማ የህግ ትምህርት ቤት ዋና አላማ ፍትሕን የሚያከብሩ ባለሙያዎች ማፍራት፤ህግን በትክክል የሚተረጉሙ ሰዎች ማዘጋጀት፤የህዝብ መብትን የሚጠብቁ ባለሙያዎች ማፍራት፤ሀገር ውስጥ የህግ የበላይነት (Rule of Law) ማጠናከር እና ማህበራዊ ግጭቶችን በህግ መፍታት ነው። ምሳሌ፦ አንድ ዳኛ ህጉን በትክክል ካልተረዳ ንፁህ ሰው ሊቀጣ ይችላል።ስለዚህ የህግ ትምህርት አላማ የሰው መብትን ከስህተት መጠበቅ ጭምር ነው። 2. ህግ ለማጥናት የሚያስፈልጉ መርሆች (ሀ). ትዕግስት ህግ ብዙ ንባብ ይፈልጋል።ህጎች፣ ፍርዶች፣ መፅሐፍት እና ህጋዊ መርሆች በብዛት ይነበባሉ። ምሳሌ፦አንድ ጉዳይ ለመረዳት የፍትሐ ብሔር ህግ፤የወንጀል ህግ የማስረጃ ህግ፤የፍርድ ሥነ-ሥርዓት ህግ፤የወንጀል ስነ ስርዓት ህግ፤ ሌሎችም ጠቅላላ እና ልዩ ህጎችን እንዲሁም ደንቦችን ማወቅ እና ሁሉንም አንድ ላይ ማንበብ ሊያስፈልግ ይችላል። (ለ). እውነትን መውደድ ጥሩ የህግ ባለሙያ ማለት ውሸትን በቃላት የሚያሸንፍ ሰው አይደለም።እውነትን በህግ የሚያረጋግጥ ሰው ነው። ምሳሌ፦ጠበቃ ደንበኛው በውሸት ሰነድ እንዲጠቀም ቢጠይቀው፣ በህግ ሥነ-ምግባር እሱን መከልከል ይጠይቃል። (ሐ). የመተንተን ችሎታ ህግ ማለት “ምን ተፈፀመ?” ብቻ አይደለም።“ለምን ተፈፀመ?” “ህጉ ምን ይላል?” “ፍትሕ ምን ይጠይቃል?” ብሎ ማሰብ ነው። ምሳሌ፦ አንድ ሰው ሰውን ቢመታ፣ራሱን ለመከላከል ነበር በድንገት ነበር? ሆን ብሎ ነበር? ይህ ሁሉ በህግ ትርጉም ይለያያል። 3. የህግ ትምህርት ጥቅሞች (ሀ). የመብት ግንዛቤ ይሰጣል ህግ የተማረ ሰው መብቱን እና ግዴታውን ያውቃል። ምሳሌ፦ ህግ የተማረ ሰው ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ ንብረቱ ሲወሰድ መቃወም እንዳለበት ያውቃል። (ለ). የመናገር እና የክርክር ችሎታ ያዳብራል የህግ ተማሪዎች ማስረጃን በሥርዓት ማቅረብ ይማራሉ። ምሳሌ፦በፍርድ ቤት፣ “እኔ እንዲህ አስባለሁ” ብቻ አይበቃም። ማስረጃ እና የህግ ድጋፍ ያስፈልጋል። (ሐ). የማህበረሰብ ክብር ያመጣል ጥሩ የህግ ባለሙያ በህዝብ ዘንድ ከፍተኛ እምነት ያገኛል። (መ). የስራ እድል ያሰፋል .ጠበቃ .ዳኛ ዐቃቤ ህግ .የህግ አማካሪ .የሰብዓዊ መብት ባለሙያ እና የዲፕሎማሲ ባለሙያ ወዘተ መሆን ይቻላል። 4. የህግ ትምህርት ችግርና ጉዳቶች (ሀ). ከፍተኛ ጫና ብዙ ንባብ፣ ምርምር እና ክርክር ይፈልጋል። ምሳሌ፦ አንድ የፍርድ ቤት ውሳኔ ለመረዳት 50 ገፅ በላይ ማንበብ ሊያስፈልግ ይችላል። (ለ). የሥነ-ምግባር ፈተና አንዳንድ ጊዜ ገንዘብ ወይም ግፊት ህግን እንዲጣስ ሊያደርግ ይችላል። ምሳሌ፦ ሰው የሀሰት ምስክር እንዲያቀርብ ቢጠይቅህ፣ የህግ ሙያ ሥነ-ምግባር እምቢ ማለትን ይጠይቃል። (ሐ). ሰዎች ሁሉ ህግን አይወዱም አንዳንድ ጊዜ እውነትን መናገር ጠላት ሊያበዛ ይችላል። ምሳሌ፦ ህገ-ወጥ ነገርን ስትቃወም አንዳንድ ሰዎች “አስቸጋሪ ሰው” ሊሉህ ይችላሉ። 5. ህግ ማጥናት ለሚፈልጉ ሰዎች ዋና ምክሮች ①. ንባብን ልመዱ በየቀኑ ማንበብ ካልቻላችሁ ህግ ከባድ ሊሆን ይችላል። ②. ጥያቄ መጠየቅን አትፍሩ ጥሩ የህግ ተማሪ “ለምን?” ብሎ ይጠይቃል። ③. ህግን ለፍትሕ ተጠቀሙበት ህግ ሰዎችን ለማስፈራራት ሳይሆን ለመጠበቅ ነው። ④. ሥነ-ምግባራችሁን ጠብቁ የህግ ባለሙያ ስም በአንድ ስህተት ሊበላሽ ይችላል። ⑤. ፍትሕን ከገንዘብ በላይ አድርጉ ህግ ትልቅ ኃይል አለው፤ ነገር ግን ያ ኃይል በእውነት እና በሥነ-ምግባር ሲመራ ብቻ የተከበረ ይሆናል። ማጠቃለያ ህግ ማጥናት ቀላል መንገድ አይደለም።ነገር ግን ፍትሕን ለማገልገል፣ መብትን ለመጠበቅ፣ ማህበረሰብን ለማሻሻል ከፍተኛ ዕድል ያለው ሙያ ነው። ጥሩ የህግ ባለሙያ ማለት ህግን ብቻ የሚያውቅ ሰው ሳይሆን፣ ፍትሕን የሚያከብር ሰው ነው። Alehegn Akal

የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ ላላቸው ደንበኞች የብድር ደብዳቤ (LC) እና የሰነድ መክፈያ (CAD) ፈቃዶችን ያለ ብሔራዊ ባንክ ቅድመ ሁኔታ ማጽደቅ እንዲችሉ የሚፈቅድ መመሪያ ወጥቷል። የኢት
+1
የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ ላላቸው ደንበኞች የብድር ደብዳቤ (LC) እና የሰነድ መክፈያ (CAD) ፈቃዶችን ያለ ብሔራዊ ባንክ ቅድመ ሁኔታ ማጽደቅ እንዲችሉ የሚፈቅድ መመሪያ ወጥቷል። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ወደ ገበያ መር የውጭ ምንዛሬ ተመን ሥርዓት እያደረገ ያለውን ሽግግር ለማጠናከር፣ የውጭ ምንዛሬ አስተዳደርን የሚያቀሉ አዳዲስ መመሪያዎችን ተግባራዊ ማድረጉን አስታውቋል። ባንኩ ባወጣው መግለጫ ማሻሻያው የውጭ ምንዛሬ አስተዳደርን ይበልጥ ለማቅለልና በንግድ እንቅስቃሴ ላይ እንቅፋት የሆኑ የቢሮክራሲ ሰንሰለቶችን ለመበጠስ ያስችላል ብሏል። በአዲሱ መመሪያ መሰረት የንግድ ባንኮች የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ (FX accounts) እና የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ሂሳብ (Retention accounts) ላላቸው ደንበኞች የብድር ደብዳቤ (Letter of Credit) እና የሰነድ መክፈያ (CAD) ፈቃዶችን ያለ ብሔራዊ ባንክ ቅድመ ሁኔታ ማጽደቅ እንዲችሉ ሙሉ ሥልጣን ተሰጥቷቸዋል። ይህ ማሻሻያ በተለይ በገቢና ወጪ ንግድ ላይ ለተሰማሩ ነጋዴዎች የጊዜና የቢሮክራሲ ጫናን በእጅጉ ይቀንሳል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪም የውጭ ምንዛሬ ሂሳብ ያላቸው ተቋማት (የውጭ ምንዛሬ ተመላሽ ሂሳብ ባለቤቶችን ጨምሮ) የባንኮችን ቅድመ ፈቃድ ሳይጠብቁ በሰነድ መክፈያ (Cash Against Documents) ስምምነት መሠረት የሸቀጦችን የጭነት ትዕዛዝ መስጠት ወይም ጭነት ማስጀመር ይችላሉ። የክፍያ ሂደቱ የሚከናወነው አስፈላጊ የሆኑ ሰነዶች ቀርበው ሲረጋገጡ ይሆናል። ባንኩ በንግድ ባንኮች የሚጠየቁ የብድር ደብዳቤ (LC) የአገልግሎት ክፍያዎችና ኮሚሽኖች ከዓለም አቀፍ አሰራር ጋር የማይጣጣሙ ሆነው ማግኘቱን ጠቁሟል። ይህንን ለማስተካከልም ከአሁን በኋላ ባንኮች የሚጠይቁት የአገልግሎት ክፍያ በዓመታዊ ስሌት (Annualized basis) ተሰልቶ፣ እንደ ሰነዱ ቆይታ ጊዜ (Tenor) ተመጣጣኝ (Pro-rata) በሆነ መልኩ እንዲቀነስ አዟል። በተጨማሪም ባንኮች የሚጥሉት ዓመታዊ የክፍያ መጠን ብሔራዊ ባንክ ቀደም ብሎ ካስቀመጠው ከፍተኛ የክፍያ ጣሪያ መብለጥ እንደሌለበት በመመሪያው በጥብቅ አሳስቧል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 17 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

መኪና በውክልና ለምትሻሻጡ ወገኖች:- ============== የተሽከርካሪ ሽያጭ ውል ህጋዊነት እና ማስረጃ አቀራረብ በሰበር መ/ቁ 283524 በቀን 27/05/2018 ዓ.ም በሰጠው ውሳኔ መኪና ሲገዙ ወይም ሲሸጥ በውልና ማስረጃ በኩል ሳያረጋግጡ በመንደር ውል መደረጉ ያለው እጣ ፈንታ በተለይም ግለሰቡ (ተጠሪ) ከአንድ ሻጭ (አመልካች) ጋር የመኪና ሽያጭ ውል ተፈራርመው፣ ከፊል ክፍያ ፈጽመውና መኪናውን ተረክበው ለዓመት ያህል ሲጠቀሙ ይቆያሉ ። ነገር ግን ሻጭ መኪናውን በሌላ ቁልፍ ከፍተው በመውሰድ "አልሸጥኩም፣ እንዲያስተዳድሩልኝ ውክልና ነው የሰጠኋቸው" በማለት በመካድ ተከራክረዋል ። በሰበር ሰሚ ችሎትም መኪና እንደ ተራ ንብረት ሳይሆን እንደ "ልዩ ተንቀሳቃሽ ንብረት" የሚቆጠር በመሆኑ፣ ዝውውሩ በህግ ፊት እንዲጸና በሚመለከተው የመንግስት አካል ዘንድ መመዝገብና መረጋገጥ አለበት ። በተጨማሪም የመኪና ሽያጭ መኖሩን ለማረጋገጥ በሚመለከተው አካል የተረጋገጠ የሽያጭ ሰነድ ማቅረብ እንጂ በሰው ምስክር ብቻ ማረጋገጥ የማይቻል ስለመሆኑ ተወስኗል

አቤቱታን ስለማሻሻል መብት እንጂ የግድ አይደለም አቤቱታ ማሻሻል የህግ መብት ቢሆንም፣ ፍርድ ቤት የሚቀበለው ጉዳዩን ይበልጥ ግልጽ ለማድረግ ወይም ትክክለኛ ፍትህ ለማስፈን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ብቻ ነው፡፡ የማሳመን ግዴታ አለበት ማለትም ማሻሻያ ጠያቂው ወገን "ለምን" ማሻሻል እንዳስፈለገ እና ምን እንደሚሻሻል በግልጽ ለፍርድ ቤቱ የማሳመን ግዴታ አለበት። በደፈናው ክሴን አሻሽዬ ላቅርብ ማለት በራሱ በቂ አይደለም፡፡ ማሻሻያው ፍርድ ከመሰጠቱ በፊት መሆን አለበት፡፡ እንዲሁም፣ ፍርድ ቤቱ ማሻሻያውን ከመፍቀዱ በፊት የማሻሻያው ነጥቦች ተገቢነት እና አስፈላጊነት አስቀድሞ መመርመር አለበት፡፡ ከለላ ለፍትህ እንጂ ለውድድር አይደለም፡ ማሻሻያ ተቃዋሚ ወገንን ለወጪ እና ለእንግልት ለመዳረግ ወይም የመከላከያ መልስ ክፍተቶችን ለመሸፈን መሞከሪያ ሊሆን አይገባም፡፡ ፍርድ ቤቶች ተከራካሪዎች በቸልተኝነት ወይም በስልት ክርክሩን ለማራዘም የሚያቀርቡትን ማሻሻያ ውድቅ ማድረግ እንዳለባቸው የሰበር ውሳኔዎች ያስረዳሉ፡፡ የክስ ማሻሻያ ጥያቄህ የሚሳካው፤ ማሻሻያው የክርክሩን ፍሬ ነገር በግልጽ የሚያስረዳ እና የፍትህ ሂደቱን ለማሳለጥ እንጂ ለማራዘም ያልታለመ እንደሆነ ለፍርድ ቤቱ በማረጋገጥ ነው፡፡

የቃብድ (Earnest) ምንነትና ሕጋዊ ማዕቀፍ መግቢያ ሰዎች በእለት ከእለት እንቅስቃሴያቸው የተለያዩ ሕጋዊ ተግባራትን ያከናውናሉ። ከእነዚህ ሕጋዊ ተግባራት አንዱ ውል ነው። ጠዋት ታክሲ ከመሳፈር ጀምሮ የተለያዩ ሸቀጦችን መግዛት፣ ቤት መከራየት፣ የተለያየ ዋጋ ያላቸውን ንብረቶች መሸጥና መግዛት በየእለቱ በሰዎች የሚከናወኑ የውል ውጤቶች ናቸው። ውል በሁለትና ከዚያ በላይ በሆኑ ሰዎች መካከል የሚደረግ ለአንዱ ወገን መብትን የሚሰጥ፣ ለሌላው ወገን ተነጻጻሪ ግዴታን የሚጥል ሕጋዊ ስምምነት ነው። በዚህ ስምምነት ሂደት እንደውሉ ሁኔታ ተዋዋይ ወገኖች ውል ለመፈጸሙ ማረጋገጫ ይሆናቸው ዘንድ ቃብድ ሊቀባበሉ ይችላሉ፡፡ በዚህ ጽሑፍ የቃብድን ምንነትና በአገራችን ያለውን ሕጋዊ ማእቀፉ በአጭሩ እንመለከታለን፡፡ የቃብድ ምንነት በ1993 ዓ.ም በኢትዮጵያ ቋንቋዎች ጥናትና ምርምር ማዕከል የታተመው የአማርኛ መዝገበ ቃላት (ገጽ 176) ቃብድ (ቀብድ) እቃን ለመግዛት ወይም ለማሰራት በቅድሚያ የሚከፈል ገንዘብ፣ መያዣ እንደሆነ ትርጉም ሰጥቶታል። በሌላ በኩል ብላክ የሕግ መዝገበ ቃላት በ8ኛ እትሙ (Black’s Law Dictionary, 8th ed.) “Earnest is a nominal payment or token act that serves as a pledge or a sign of good faith, esp. as the partial purchase price of property”. በሚል ይተረጉመዋል። ይህ ወደ አማርኛ ሲመለስ ቃብድ ማለት በተለይም ለአንድ ንብረት ግዥ እንደ መያዣ ወይም ቅን ልቦና መገለጫ የሚሰጥ አነስተኛ ክፍያ ሲሆን ይህም አብዛኛውን ጊዜ ከጠቅላላው የሽያጭ ዋጋ ላይ በከፊል የሚታሰብ ክፍያ ነው የሚል ይሆናል። የቃብድ ሕጋዊ ማዕቀፍ የፍትሐብሔር ሕግ ከቁጥር 1883 እስከ 1885 ስለቃብድ የደነገገ ሲሆን በእነዚህ ድንጋጌዎች መሠረት ቃብድ እንደ ውል ማረጋገጫ ተደርጎ ይቆጠራል። ይኸውም አንዱ ወገን ለሌላኛው ወገን ቃብድ መስጠቱ በማያከራክር ሁኔታ ውል መደረጉን እንደሚያረጋግጥ በፍትሐብሔር ሕጉ በቁጥር 1883 በግልጽ ተደንግጓል። በዚህም ቃብድ ውሉ በቁርጠኝነት እንዲቀጥል የመፈጸም ፍላጎት ማሳያ ነው። ውሉ ሲፈጸምም ሌላ ተቃራኒ ስምምነት ከሌለ በስተቀር ቃብድ የተቀበለው ወገን በፍትሐብሔር ሕጉ ቁጥር 1884 መሠረት ከሚገባው ገንዘብ ላይ ታሳቢ ያደርጋል ወይም ቀብድ ለሰጠው ወገን ተመላሽ ያደርጋል። ለምሳሌ በሽያጭ ውል ላይ ውሉ ሲፈጸም ለሻጭ የተሰጠው ቃብድ ከሽያጭ ዋጋው ላይ ታሳቢ ይደረጋል። ሌላው እዚህ ጋር የሚነሳው ውሉ ቢፈርስ የቃብዱ እጣ ፈንታ ምን ይሆናል የሚለው ሲሆን ለዚህም የፍትሐብሔር ሕጉ ቁጥር 1885 ግልጽ መፍትሔ አስቀምጧል። ይኸውም  ቃብድ የሰጠው ሰው ውሉን ካፈረሰ የሰጠውን ቀብድ የማስመለስ መብት የለውም። ውል ማፍረስ የሚችለው ቃብዱን በመተው ነው። በአንፃሩ ቃብድ የተቀበለው ሰው ውሉን ካፈረሰ የተቀበለውን ቃብድ እጥፍ አድርጎ ለሰጪው የመመለስ ግዴታ አለበት። እዚህ ጋር ልብ ሊባል የሚገባው የቃብድ ገንዘብ ተቀባዩ የተቀበለውን ቃብድ አጠፌታ ከፍሎ ውሉን እንዲያፈርስ የሚገደደው በግራ ቀኙ ወገኖች መካከል ሕጋዊ ሥርዓቱን የጠበቀ የፀና ውል ሲኖር ስለመሆኑ የፌዴራል ሰበር ሰሚ ችሎት በቅጽ 26 በሰ/መ/ቁ. 211204 እና 215762 አስገዳጅ የሕግ ትርጉም ሰጥቶበታል። በእነዚህ ውሳኔዎችም ቃብድ ከሽያጭ ዋጋ ከፊል/ቅድሚያ/ ክፍያ የሚለይበት መንገድ ተገልጿል። ይኸውም ውሉ ሲፈርስ ቅድመ ክፍያ በሆነ ጊዜ ግራ ቀኙ ከውሉ በፊት ወደነበሩበት ሁኔታ ይመለሳሉ። ስለሆነም በቅድመ ክፍያ ጊዜ ሻጭ ውሉን ቢያፈርስ የተከፈለው ገንዘብ ብቻ ለገዥ ተመላሽ የሚደረግ ሲሆን ቃብድ ተከፍሎ የነበረ ሲሆን ሻጭ ውሉን ቢያፈርስ የቃብዱን አጠፌታ ለገዥ የመክፈል ግዴታ አለበት።(የፍትሐብሔር ሕግ ቁጥር 1885(2)፣ 1815(1)) ማጠቃለያ በተለያዩ የውል ሂደቶች ቃብድ መክፈልም ሆነ መቀበል የራሱ የሆነ ውጤት ያስከትላል። በተለይም በሽያጭና ኪራይ ውል ሂደት ቀብድ መክፈልና መቀበል የተለመደ ሲሆን ቃብድ ሰጪ ውሉን ካላከበረ የከፈለው ገንዘብ እንደማይመለስ፣ ተቀባይ ደግሞ ውሉን ካላከበረ የወሰደውን ገንዘብ እጥፍ አድርጎ የመመለስ ግዴታ ሊመጣ እንደሚችል ተገንዘቦ በጥንቃቄ መዋዋል ይገባል። ከዚህም በተጨማሪ ውሉ አስፈላጊ የሆኑ ሕጋዊ ፎርማሊቲዎችን መጠበቅ እና ቃብድ መሆኑ በግልጽ መስፈር እንዳለበት ግንዛቤ ሊወሰድ ይገባል። በንቃተ ሕግና ሥልጠና ዳይሬክቶሬት የተዘጋጀ ፍትሕ ሚኒስቴር

የገንዘብ ሚኒስቴር የታክስ አስተዳደር አዋጅን ለማሻሻል ያዘጋጀውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ ለውይይት አቀረበ። የገንዘብ ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን፣ ነባሩን የታክስ አስተዳደር አ
+1
የገንዘብ ሚኒስቴር የታክስ አስተዳደር አዋጅን ለማሻሻል ያዘጋጀውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ ለውይይት አቀረበ። የገንዘብ ሚኒስቴር ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመሆን፣ ነባሩን የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008 ለማሻሻል ያዘጋጀውን አዲስ ረቂቅ አዋጅ አስመልክቶ ከዘርፉ ባለሙያዎች ጋር ምክክር አካሂዷል። ቲክቫህ ኢትዮጵያም ምክክሩን ታድሟል። በተሻሻለው ረቂቅ አዋጅ ላይ በታክስ አስተዳደር ሥርዓቱ ውስጥ የነበሩ የአሠራርና የሕግ ክፍተቶችን ለመቅረፍ እንዲሁም የታክስ ሕግ ተገዥነትን ለማስፈን በርካታ ማሻሻያዎች መካተታቸውን በገንዘብ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሕግ አማካሪ የሆኑት አቶ ዋሲሁን አባተ ገልጸዋል። ስለ ተሻሻለው የታክስ አስተዳደር ረቂቅ አዋጅ የሕግ አማካሪው አቶ ዋሲሁን አባተ ምን አሉ ? በታክስ ክሊራንስ ዙሪያ የተደረገ ማሻሻያ ፦ " ከዚህ በፊት በነበረው አዋጅ ላይ ቅሬታ ወይም ክርክር ያለበት ግብር ከፋይ ከባንክ ብድር ለማግኘት የታክስ ክሪላንስ (የምስክር ወረቀት) አይሰጠውም ነበር፣ ምክንያቱም የምስክር ወረቀቱ ከተሰጠው ባንኮች ከመንግስት የቀደምትነት መብት ስለሚያገኙ። አሁን በተሻሻለው ግን ግብር ከፋዩ ያለበትን ዕዳ እና በፍርድ ቤት ክርክር ላይ መሆኑን በግልጽ ለባንኩ አሳውቆ ግብር ከፋዩ ያለበትን ዕዳ አውቆ ካለበት እዳ በላይ ባንኩ ማበደር የሚችል ከሆነ እንዲያበድር እና መንግስት የቀደምትነት መብት እንዳለው የሚገልጽ አሰራር ተደንግጓል።  " (ትርፍን ወደ ውጭ መላክ በተመለከተ) " ባንኮች እና የውጭ ባለሀብቶች ትርፋቸውን ወደ ውጭ ከመላካቸው በፊት ግብር መክፈላቸውን የሚያረጋግጥ የታክስ ክሊራንስ ማቅረብ የሚኖርባቸው በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመሪያ ደረጃ ብቻ ነበር። አሁን ግን መመሪያው ወደ ታክስ አስተዳደር አዋጅ ከፍ እንዲል ተደርጓል። ማናቸውም ባንክ ይህንን ማረጋገጫ ሳይዝ ትርፉን ወደ ውጭ መላክ እንደሌለበት በአዋጁ ላይ በግልጽ ሰፍሯል። " የቅሬታ ማቅረቢያ፣ የዋስትና እና የስሌት ስህተቶችን የማረም ሥርዓት ፦ " ግብር ከፋዩ በኦዲተሮች የተጣለበትን ግብር በመቃወም ወደ ግብር ይግባኝ ለመሄድ 50 በመቶ፣ ወደ ፍርድ ቤት ለመሄድ ደግሞ 75 በመቶ መያዣ ማስያዝ ነበረበት። ይህም አቤቱታ የማሰማት መብትን ያጣብብ ነበር። አሁን ግን ግብር ከፋዩ 50 በመቶውን ሳያሲዝ፣ በታክስ ባለስልጣኑ በሚሰየም ገለልተኛ ተቋም ጉዳዩን በስምምነት የሚያልቅበት አማራጭ ተፈጥሯል። አሁን ያለው ችግር ምንድን ነው በእኛ የታክስ አስተዳደር ውስጥ ስህተት መሆኑን እያወቀ ኃላፊው ይፈራል። በአንቀጽ ሰማንያ አምስት መሠረት ' ስህተት አለና አርምልኝ ' ተብሎ ሲቀርብለት፣ ብዙ ጊዜ ኦዲተሮቹ ማረም አይፈልጉም። ' እኔ አላረምልህም፤ ከፈለግክ ይግባኝ ሂድ ' ይሉታል። ኃላፊው ጋር ሲሄድ ደግሞ ኃላፊው ይፈራል፤ ' አሁን ይህንን ስህተት አርም ብዬ ኦዲተሩን ያዘዝኩት እንደሆነ ጉቦ በልቶ ነው ብሎ ስሜን ያጠፋኛል ' ብሎ ስለሚፈራ ያቺን አንቀጽ 85 ተግባራዊ አያደርጉም። በሌላ በኩል ደግሞ ግብር ከፋዩ የሕግ ትርጉም ልዩነትን ሁሉ የስሌት ስህተት አስመስሎ በአንቀጽ  85 ለማሳለፍ ይሞክር ነበር። አሁን ግን የታክስ ባለሥልጣኑ የሰራውን ድምር ስህተት መሆኑን ካመነበት ግልጽ በሆነ ድንጋጌና መመሪያ የሚያርምበት ሥርዓት ተቀምጧል። ስህተቱ ከተረጋገጠ አዲስ የታክስ ውሳኔ ማስታወቂያ ይሰጠዋል፤ የይግባኝ ጊዜ መቆጠር የሚጀምረውም ከዚያ በኋላ ይሆናል። የይግባኝ ማቅረቢያ የጊዜ ገደብ (30 ቀናት) በግልጽ ባለመቀመጡ እስከ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ድረስ ክርክር ሲያስነሳ ነበር። አሁን ግን በግልጽ ለተከታታይ 30 ቀናት ብቻ ተደርጓል። " ወደኋላ ተመልሶ ግብር የመጠየቅ ጊዜ ገደብ ፦ " የታክስ ማጭበርበር የፈጸመ ሰው በማናቸውም ጊዜ (ከ25 ዓመት በኋላም ቢሆን) ወደኋላ ተመልሶ ይጠየቅ ነበር። ነገር ግን በሌላ ሕግ ሰነድ ደግሞ መያዝ ያለበት ለ10 ዓመት ብቻ በመሆኑ ግብር ከፋዩ ራሱን መከላከል አይችልም ነበር። አሁን በተሻሻለው ያለማጭበርበር ከሆነ 5 ዓመት፣ የማጭበርበር ድርጊቶችን ፈጽሞ ከተገኘ ደግሞ እስከ 10 ዓመት ብቻ ወደኋላ ተሂዶ ግብር ሊጠየቅ ይችላል። " የደረሰኝ አጠቃቀም እና ጠንከር ያሉ ቅጣቶች ፦ " ደረሰኝ ባልሰጠ ሰው ላይ የነበረው ቅጣት አነስተኛ በመሆኑ ጥፋቱ ገደብ የለሽ ሆኖ ነበር። በተጨማሪም አንድ ሠራተኛ (ለምሳሌ የውኃ አከፋፋይ ሹፌር) መንገድ ላይ ደረሰኝ ሳይሰጥ ቢቀር፣ ስራ አስኪያጁ መከታተል ባይችልም እንኳ አብሮ እስር ቤት ይገባ ነበር። አሁን ግን ደረሰኝ ባልሰጠ ቁጥር የደረሰኙ ብዛት ሳይታይ በእያንዳንዱ ደረሰኝ 100,000 ብር አስተዳደራዊ ቅጣት ይቀጣል። መጀመሪያና ሁለተኛ ጥፋት ላይ በገንዘብ ተቀጥቶ ይታለፋል። በሶስተኛው ግን ወደ እስር ቤት ይሄዳል። ስራ አስኪያጅ ብቻ ሳይሆን የፋይናንስ ኃላፊውና የገንዘብ ቁጥጥር ላይ ያሉ አካላት ሁሉ በጋራ ይጠየቃሉ። ነገር ግን ስራ አስኪያጁ የሚጠየቀው የውስጥ ቁጥጥር ሥርዓት ሳይዘረጋ ሲቀር ብቻ ነው። በጆብ ዲስክሪፕሽን ሰራተኛውን አስገድዶ፣ ማታ ማታ በደረሰኝ መሸጡን የሚያረጋግጥ አሠራር ከዘረጋ ግን አይታሰርም፤ ራሱን የሚከላከልበት መንገድ በሕጉ ግልጽ ሆኗል። በአንድ የግብር ዘመን ውስጥ ለሁለት ጊዜ ያህል አስተዳደራዊ የገንዘብ ቅጣት ከተቀጣ በኋላ ለሶስተኛ ጊዜ ካጠፋ ከ5 እስከ 7 አመት በሚደርስ ጽኑ እስራት ይቀጣል። " የወደፊት ዕቅድ ፦ አማካሪው በሚቀጥሉት ሦሥት አመታት የገቢ ግብር አዋጅ፣ የታክስ አስተዳደር አዋጅ እና የጉምሩክ አዋጅን ሙሉ ለሙሉ መሰረታዊ ለውጥ የማድረግ ስራ እንደሚሰሩም አመላክተዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ አዲስ አበባ ግንቦት 11 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

Repost from N/a
የስራ ማስታወቂያ (Vacancy Announcement) ባለው ክፍት የስራ መደብ ላይ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ የስራ መደብ መረጃ የስራ መደቡ መጠሪያ፦ የቢሮ ሴክሬታሪ (Office Secretary / Administrator) የቅጥር ሁኔታ፦ በቋሚነት (Permanent) ደመወዝ፦ በስምምነት (Negotiable) የስራ ቦታ፦ ቦሌ ብራስ (Bole Brass) ተፈላጊ ችሎታዎች እና መስፈርቶች የቋንቋ ችሎታ፦ የእንግሊዘኛ ቋንቋ ችሎታ እጅግ በጣም ጥሩ የሆነች፤ የስራ ባህሪ፦ ቀልጣፋ፣ ንቁ እና የቢሮ ረዳት እንዲሁም አስተዳዳሪ (Administrator) ሆና ለመስራት ሙሉ ዝግጁነት ያላት፡፡ የትምህርት ደረጃ፦ የተለየ የትምህርት ደረጃ ወይም የተመረቀችበት የትምህርት መስክ አይጠየቅም (ከላይ የተጠቀሱትን ክህሎቶች ማሟላት ብቻ በቂ ነው)፡፡ የስራው ዋና ዋና ኃላፊነቶች የቢሮ ስራዎችን በብቃት እና በጥራት ማደራጀትና ማስተዳደር፡፡ የእንግሊዘኛ ቋንቋን በመጠቀም የሚደረጉ ግንኙነቶችን በፅሁፍም ሆነ በንግግር መምራት፡፡ ቀልጣፋ የቢሮ ረዳት በመሆን የዕለት ተዕለት ስራዎችን ማገዝ፡፡ እንዴት ማመልከት ይቻላል? መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 7 (ሰባት) ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ rootsinafricaplc@gmail.com በመጠቀም ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ @rootsinafrica

የስራ ማስታወቂያ (Vacancy Announcement) ባለው ክፍት የስራ መደብ ላይ መስፈርቱን የሚያሟሉ አመልካቾችን አወዳድሮ በቋሚነት ለመቅጠር ይፈልጋል፡፡ የስራ መደብ መረጃ የስራ መደቡ መጠሪያ፦ የቢሮ ሴክሬታሪ (Office Secretary / Administrator) የቅጥር ሁኔታ፦ በቋሚነት (Permanent) ደመወዝ፦ በስምምነት (Negotiable) የስራ ቦታ፦ ቦሌ ብራስ (Bole Brass) ተፈላጊ ችሎታዎች እና መስፈርቶች የቋንቋ ችሎታ፦ የእንግሊዘኛ ቋንቋ ችሎታ እጅግ በጣም ጥሩ የሆነች፤ የስራ ባህሪ፦ ቀልጣፋ፣ ንቁ እና የቢሮ ረዳት እንዲሁም አስተዳዳሪ (Administrator) ሆና ለመስራት ሙሉ ዝግጁነት ያላት፡፡ የትምህርት ደረጃ፦ የተለየ የትምህርት ደረጃ ወይም የተመረቀችበት የትምህርት መስክ አይጠየቅም (ከላይ የተጠቀሱትን ክህሎቶች ማሟላት ብቻ በቂ ነው)፡፡ የስራው ዋና ዋና ኃላፊነቶች የቢሮ ስራዎችን በብቃት እና በጥራት ማደራጀትና ማስተዳደር፡፡ የእንግሊዘኛ ቋንቋን በመጠቀም የሚደረጉ ግንኙነቶችን በፅሁፍም ሆነ በንግግር መምራት፡፡ ቀልጣፋ የቢሮ ረዳት በመሆን የዕለት ተዕለት ስራዎችን ማገዝ፡፡ እንዴት ማመልከት ይቻላል? መስፈርቱን የምታሟሉ አመልካቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ 7 (ሰባት) ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ rootsinafricaplc@gmail.com በመጠቀም ማመልከት የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡