es
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

Ir al canal en Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

Mostrar más
2 263
Suscriptores
+324 horas
+217 días
+1830 días
Archivo de publicaciones
መንግሥት የቤተክርስቲያን መምህራንን በማሰር ላይ ተጠምዷል የአርሲን ጉዳይ አጀንዳ ለማስቀየር ይኼንን ሁሉ ማድረግ ምንም አይጠቅማችሁም። ይኼ እጅግ የሚያሳዝን ተግባር ነው። እግዚአብሔር ያስፈታችሁ!
+1
መንግሥት የቤተክርስቲያን መምህራንን በማሰር ላይ ተጠምዷል የአርሲን ጉዳይ አጀንዳ ለማስቀየር ይኼንን ሁሉ ማድረግ ምንም አይጠቅማችሁም። ይኼ እጅግ የሚያሳዝን ተግባር ነው። እግዚአብሔር ያስፈታችሁ!

ይኼንን ከሚያደርጉ ከሚመክሩ ጓደኞችና ወዳጆች እባካችሁን እራሳችሁን ጠብቁ!! በአጋንንት ተይዘው መያዛቸውን እንኳን የማያውቁ ተሳዳቢዎች!! #እሸቱመለሰ #ጸሎት https://youtu.be/IkmduUVxBmM

4ቱን መንፈሳዊ ኃይሎች ካላወቃችሁ ብዙ ነገር እየጎደላችሁ ነው! ⚠ ለምን ጸሎታችን መልስ አያገኝም? መልሱ ይኸው! መዝሙረ ዳዊት የማይጸልይ ሰው ምን ያጣል? https://youtu.be/jxFofHTF3k8

<<እግዚአብሔር ከእስራታቸው ይፈታቸው ዘንድ ስለታሰሩ ሰዎች እንማልዳለን፤>> [ሥርዓተ ቅዳሴ] የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የነገረ መለኮት መምህር የሆኑት ቀሲስ ዶክተር መዝገቡ ካሳ
<<እግዚአብሔር ከእስራታቸው ይፈታቸው ዘንድ ስለታሰሩ ሰዎች እንማልዳለን፤>> [ሥርዓተ ቅዳሴ] የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርስቲ የነገረ መለኮት መምህር የሆኑት ቀሲስ ዶክተር መዝገቡ ካሳ፥ በእስር ላይ ናቸው። ከአርሲ ጉዳይ ጎን ለጎን ለእኒህ ሊቅም ድምጽ እንሁን።

ልጅ አጣሁ ትዳር መያዝ አልቻልኩም እያላችሁ ከሆነ ይኼንን ልታዳምጡ ይገባል!! የመምህር ተስፋዬ የማንቂያ መልዕክት ለሁላችን!! ስንት ስብከቶች አዳምጣችኋል!! https://youtu.be/5L0B5ERm6CU

የደብተራውን ጉድ የዘረገፈ አስገራሚ ተዓምር ይኼንን ጉድ ተመልከቱ! የዘመኑ መንፈስና እኛ ያልገቡን ከባባድ ምስጥሮች! ቤተክርስቲያን የማያስገቡ 3ቱ ኃጢአቶች! https://youtu.be/vSBsoP4W764

እባካችሁ ይኼንን ምልክት ካያችሁ የሙጬ ዘሪጋ አጋንንት ውስጣችን አድፍጧልና ንቁበት!! የካህኑ እጅግ አሳፋርና አስነዋሪ ተግባር ይማረን!! https://youtu.be/vsB1hZPdTmw?si=UJ08KR2GdxeWJNHo

ኦርቶዶክሳዊያን ከእንቅልፋችሁ ንቁ ከዚህ በኋላ ዝምታ ይበቃል!! የአቡነ ጴጥሮስ ጥብቅ መልዕክትና ማስጠንቀቂያ! የታፈነው ቅዱስ ሲኖዶስና የገዳዮቻችን ንግግር! https://youtu.be/A0965Vi6MU0

የቅርብ ጓደኞቼ በመተት የለምጽ በሽተኛ አደረጉኝ ይኼን ጉድ ተመልከቱ!! የአንጋፋዋ አርትስት እጅግ አሳዛኝ ንግግር!! መግባባትና በሰላም መኖር ለከበዳችሁ!! https://youtu.be/IniRafYtAwg

አቤቱ ጌታ ሆይ ተመልከተን ይቅርም በለን በእውነት! በዚህ ሁሉ የሚያሳዝነው የአባቶችና የሊቃነ ጳጳስት ዝምታ ነው።

ከዚህ በላይ ምን የሚያሳዝን ነገር አለ! ሰው በዘሩ በሃይማኖቱ ተለይቶ መገደል እስከመቼ ድረስ። አቤቱ ጌታ ሆይ ማረን ይቅር በለን በእውነት። ይኼ እጅግ ያሳዝናል።

የአርሲ ገዳዮችና ጨፍጫፊዎች ታውቀዋል ይኼንን ጉድ አዳምጡ እባካችሁ!! ራስን መከላከል በክርስትና ኃጢአት አይደለም!! ጳጳስ አይሳሳትም አያጠፉም ያለው ማነው? https://youtu.be/dKwKSRpzanY

ውድ ኦርቶዶክሳዊያን ይኼንን የዩቱብ ቻናል በደንብ ሰብስክብራይብና ላይክ በማድረግ ለብዙ ኦርቶዶክሳዊያን በተለይም ደግሞ ለኦሮሚኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች አዳርሱ! https://youtu.be/e9iekjkiEeI?si=rxLWPQ0_fWgg0vqj

ይኼንን መዝሙረ ዳዊት ጸልያችሁ ቀናችሁን ከጀመራችሁ እመኑኝ ታሸንፋላችሁ!! መናፍስት አብረውን እንዴት ይወለዳሉ የብዙዎች ጥያቄ!! የአርሲ ወገኖቻችን ደም!! https://youtu.be/NYHjkOweL8M

"ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ ነው የመጣው " - ቅዱስነታቸው ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ የሀዘን መልእክት አስተላልፈዋል። ቅዱስነታቸው "በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው" ብለዋል። "የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው" ሲሉ ገልጸዋል። "የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ 'እስከ መቼ?' የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል" ብለዋል። "በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን" ሲሉ አስገንዝበዋል። ቅዱስነታቸው "በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን" ብለዋል። "ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን" በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታቸውን በእግዚአብሔር ስም አስተለልፈዋል። ቲክቫህ ኢትዮጵያ ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ/ም

ከንቲባ አዳነች አቤቤ በትውልድ ስፍራቸው ይህ ሁሉ ህዝብ ሲያልቅ ቢያንስ ድርጊቱን ማውገዝ ይጠበቅባቸዋል! ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን በአሰኮ ወረዳ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች እና ቤተክርስቲያናት ላይ ተነጣጥሮ በታጣቂዎች ተሰነዘረ መጠነ ሰፊ እና አሰቃቂ የተባለ ጥቃት እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ ቁጥራቸው ምናልባትም ከ280 በላይ የሆኑ ሰዎች ደግሞ የደረሱበት ባለመታወቁ እና በስልክ ሊገኙ ስላልቻሉ ተገለው ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች በስልክ አሳውቀውኛል። የሸኔ ታጣቂዎች ጥቃቱን እንደፈፀሙት የሚናገሩት ነዋሪዎቹ ከዚህ በፊትም ከሰባት ግዜ በላይ 'ጠለታ ገብርኤል' በሚባል አካባቢ ጥቃት አድርሰው እንደነበር ተናግረዋል። የአሁኑን ለየት የሚያደርገው ታጣቂዎቹ ከመርቲ ወረዳ፣ ከፈንታሌ እና ከከረዩ እንዲሁም ከኢቱ አካባቢ የነበሩ ሁሉ ተሰባስበው በግምት ሶስት ሺህ ሆነው አሰኮ ወረዳና አካባቢው በመምጣት ቢዮ ቀበሌ፣ ጠለታ ገብርኤል፣ ኩፍቴና መዳህኒአለም እና አካባቢውን በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ አቃጥለዋል የሚሉት በለቅሶ እና በድንጋጤ በመጯጯህ የሚናገሩት ነዋሪዎች ናቸው። በእሬቻ ሚካኤል፣ በሱንቴ ማርያም፣ በሌንጫ ኦዳ፣ በኳስ ድሬ፣ በአርባ ቀላ፣ በወራንቡስ እና በተለያዩ ቦታዎች አሁን ድረስ ጥቃቱ ተስፋፍቶ ይገኛል የሚሉት ነዋሪዎቹ እስካሁን አንድም የመንግስት ሀይል ወደ ስፍራው እንዳልገባ እና ታጣቂዎቹ አካባቢው ላይ ከበባ በማድረግ ሰው እንኳን እንዳያመልጥ አድርገው ጭፍጨፋ እየፈፀሙ መሆናቸውን ተናግረዋል። ይህ አካባቢ የከንቲባ አዳነች ትውልድ ስፍራ ነው፣ ምናልባትም ከሟቾቹ መሀል አንዳንዶቹን ሊያውቁ ወይም አብረው ተምረው፣ ሰርተው ይሆናል። ታድያ ሌላው አለም ላይ እንደምናየው በፍጥነት የጥቃቱ ቦታ ላይ ሄዶ ህዝብን ማረጋጋት እና ማፅናናት በአካባቢው በቀጠለው ጥቃት ምክንያት አልተቻለም እንበልና... በትውልድ ስፍራቸው እንዲህ አይነት ዘግናኝ ጥቃት ሲፈፀም 'ነፍስ ይማር' ለማለት እና ድርጊቱን ለማውገዝ ምነው ተሳናቸው? ሌሎች ባለስልጣናት እና የፀጥታ አካላትስ? የሀገሪቱ የመከላከያ፣ የፖሊስ፣ የሚሊሻ፣ የአየር ሀይል እና ሌሎች ሀይሎችስ ለሰዓታት ሳይሆን ለቀናት እስካሁኑ ሰዓት ድረስ እየተፈፀመ ያለ ጥቃትን ለመከላከል ለምን አልቻሉም? የዚህ ሀገር ነገር አንዳንዴ ያደክማል... ህዝቡ ድረሱልን ብሎ የሚጮኸው መንግስት ላይ ሳይሆን ሚድያ ላይ፣ ሚድያው መረጃ ለህዝብ ሲያደርስ ተመልሶ በህዝብ እና መንግስት የሚሰደበው እና የሚሳደደው ራሱ ሚድያው። ለማንኛውም ለእኔ ይህን በመፃፌ ቀለል ይለኛል። በለቅሶ፣ በድንጋጤ እና በመጯጯህ ያናገርኳቸው ዜጎች ሁኔታ ግን መቼም ከአዕምሮ የማይፋቅ አሳዛኝ ክስተት ነው። ያሳዝናል፣ ነፍስ ይማር! ምንጭ ዜና መሠረት

ይኼንን ምልክት ካያችሁ ውስጣችን አይነጥላና ዛር አድፍጧልና እባካሁ ንቁ!! ማህጸኗን እንድሸትና ትዳሯ እንድፈርስ ያደረጉ ክፉ መንፈሶች!! https://youtu.be/F7SjPbeOuss