HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
الذهاب إلى القناة على Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
إظهار المزيد2 260
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+177 أيام
+1930 أيام
أرشيف المشاركات
የደብተራውን ጉድ የዘረገፈ አስገራሚ ተዓምር ይኼንን ጉድ ተመልከቱ! የዘመኑ መንፈስና እኛ ያልገቡን ከባባድ ምስጥሮች! ቤተክርስቲያን የማያስገቡ 3ቱ ኃጢአቶች! https://youtu.be/vSBsoP4W764
እባካችሁ ይኼንን ምልክት ካያችሁ የሙጬ ዘሪጋ አጋንንት ውስጣችን አድፍጧልና ንቁበት!! የካህኑ እጅግ አሳፋርና አስነዋሪ ተግባር ይማረን!! https://youtu.be/vsB1hZPdTmw?si=UJ08KR2GdxeWJNHo
ኦርቶዶክሳዊያን ከእንቅልፋችሁ ንቁ ከዚህ በኋላ ዝምታ ይበቃል!! የአቡነ ጴጥሮስ ጥብቅ መልዕክትና ማስጠንቀቂያ! የታፈነው ቅዱስ ሲኖዶስና የገዳዮቻችን ንግግር! https://youtu.be/A0965Vi6MU0
የቅርብ ጓደኞቼ በመተት የለምጽ በሽተኛ አደረጉኝ ይኼን ጉድ ተመልከቱ!! የአንጋፋዋ አርትስት እጅግ አሳዛኝ ንግግር!! መግባባትና በሰላም መኖር ለከበዳችሁ!! https://youtu.be/IniRafYtAwg
አቤቱ ጌታ ሆይ ተመልከተን ይቅርም በለን በእውነት! በዚህ ሁሉ የሚያሳዝነው የአባቶችና የሊቃነ ጳጳስት ዝምታ ነው።
ከዚህ በላይ ምን የሚያሳዝን ነገር አለ! ሰው በዘሩ በሃይማኖቱ ተለይቶ መገደል እስከመቼ ድረስ። አቤቱ ጌታ ሆይ ማረን ይቅር በለን በእውነት። ይኼ እጅግ ያሳዝናል።
የአርሲ ገዳዮችና ጨፍጫፊዎች ታውቀዋል ይኼንን ጉድ አዳምጡ እባካችሁ!! ራስን መከላከል በክርስትና ኃጢአት አይደለም!! ጳጳስ አይሳሳትም አያጠፉም ያለው ማነው? https://youtu.be/dKwKSRpzanY
ውድ ኦርቶዶክሳዊያን ይኼንን የዩቱብ ቻናል በደንብ ሰብስክብራይብና ላይክ በማድረግ ለብዙ ኦርቶዶክሳዊያን በተለይም ደግሞ ለኦሮሚኛ ቋንቋ ተናጋሪዎች አዳርሱ! https://youtu.be/e9iekjkiEeI?si=rxLWPQ0_fWgg0vqj
ይኼንን መዝሙረ ዳዊት ጸልያችሁ ቀናችሁን ከጀመራችሁ እመኑኝ ታሸንፋላችሁ!! መናፍስት አብረውን እንዴት ይወለዳሉ የብዙዎች ጥያቄ!! የአርሲ ወገኖቻችን ደም!! https://youtu.be/NYHjkOweL8M
"ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ ነው የመጣው " - ቅዱስነታቸው
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያኗ እና በምዕመኖቿ ላይ የደረሰውን ጥቃት በማስመልከት አባታዊ የሀዘን መልእክት አስተላልፈዋል።
ቅዱስነታቸው "በአርሲ ሀገረ ስብከት በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤ እና በሙኔሳ ወረዳዎች በመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንና በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ ስለደረሰው አሰቃቂ ጥቃት የሰማነው በተሰበረ ልብ ነው" ብለዋል።
"የእምነት ነፃነት ተደፍሮ መቶ ዓመታት ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በተቃጠለበት፣ እንዲሁም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን በተዘረፈበት በዚህ ክፉ ቀን፤ በርካታ ምእመናን በግፍ መሰዋታቸውና በመቶዎች የሚቆጠሩ ወገኖቻችን ከቀዬአቸው መፈናቀላቸው ቤተ ክርስቲያናችንን በእጅጉ ያሳዘነ ክስተት ነው" ሲሉ ገልጸዋል።
"የሰላም፣ የፍቅርና የታሪክ ማህደር የሆነችው ቤተ ክርስቲያን በምድራዊ መከራ ውስጥ ያሉትን ምእመናን በምታጽናናበት በዚህ ወቅት ራሷ በፈተና ውስጥ ሆና ከመቸገሯም በላይ በአርሲ ምድር በተደጋጋሚ የሚስተዋለው በደልና ግፍ በሁላችንም ልቡና ውስጥ 'እስከ መቼ?' የሚል የቁጭት እና የኀዘን ጥያቄን ፈጥሯል" ብለዋል።
"በመሆኑም ይህ መከራ እያበቃ ሳይሆን እየሰፋ በመምጣቱ የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን አደራ የተጣለባችሁ የጸጥታ አካላትና በየመዋቅሩ ያላችሁ ሓላፊዎች ከምንም በላይ ታሪክ የሚጠይቃችሁ በሥልጣን ዘመናችሁ ለዜጎች ደኅንነት በምትከፍሉት ዋጋ ነውና ይህንን የጥቃት ሰንሰለት በማስቆምና ወንጀለኞችን ለሕግ በማቅረብ ከታሪክ ባለዕዳነት ትድኑ ዘንድ በቤተ ክርስቲያናችን ስም አበክረን እናሳስባለን" ሲሉ አስገንዝበዋል።
ቅዱስነታቸው "በየአካባቢው የምትገኙ ምእመናንና መላው ኢትዮጵያውያንም በወንድማማችነት መንፈስ ተጋግዛችሁ፣ የተፈናቀሉ ወገኖችን በመደገፍና በጸሎት ከቤተክርስቲያናችን ጎን እንድትሆኑ ጥሪያችንን እናቀርባለን" ብለዋል።
"ቤተ ክርስቲያናችን ለሰላም፣ ለይቅርታና ለሰው ልጆች ክብር ሁል ጊዜ የምትቆም መሆኑን በመግለጽ ይህንን የኀዘን ሰዓት አምላካችን በምሕረቱ ያሳልፍልን፣ የሞቱትን ነፍሶቻቸውን በመንግሥቱ ይቀበልልን፣ የተጎዱትንም በቸርነቱ ያጽናናልን" በማለት አባታዊ የኀዘን መልእክታቸውን በእግዚአብሔር ስም አስተለልፈዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ግንቦት 26 ቀን 2018 ዓ/ም
ከንቲባ አዳነች አቤቤ በትውልድ ስፍራቸው ይህ ሁሉ ህዝብ ሲያልቅ ቢያንስ ድርጊቱን ማውገዝ ይጠበቅባቸዋል!
ከትናንት በስቲያ ጀምሮ በኦሮሚያ ክልል ምሥራቅ አርሲ ዞን በአሰኮ ወረዳ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች እና ቤተክርስቲያናት ላይ ተነጣጥሮ በታጣቂዎች ተሰነዘረ መጠነ ሰፊ እና አሰቃቂ የተባለ ጥቃት እስካሁን የ49 ሰዎች ሕይወት ማለፉን፣ ቁጥራቸው ምናልባትም ከ280 በላይ የሆኑ ሰዎች ደግሞ የደረሱበት ባለመታወቁ እና በስልክ ሊገኙ ስላልቻሉ ተገለው ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት እንዳላቸው የአካባቢው ነዋሪዎች በስልክ አሳውቀውኛል።
የሸኔ ታጣቂዎች ጥቃቱን እንደፈፀሙት የሚናገሩት ነዋሪዎቹ ከዚህ በፊትም ከሰባት ግዜ በላይ 'ጠለታ ገብርኤል' በሚባል አካባቢ ጥቃት አድርሰው እንደነበር ተናግረዋል።
የአሁኑን ለየት የሚያደርገው ታጣቂዎቹ ከመርቲ ወረዳ፣ ከፈንታሌ እና ከከረዩ እንዲሁም ከኢቱ አካባቢ የነበሩ ሁሉ ተሰባስበው በግምት ሶስት ሺህ ሆነው አሰኮ ወረዳና አካባቢው በመምጣት ቢዮ ቀበሌ፣ ጠለታ ገብርኤል፣ ኩፍቴና መዳህኒአለም እና አካባቢውን በአሁኑ ሰዓት ሙሉ በሙሉ አቃጥለዋል የሚሉት በለቅሶ እና በድንጋጤ በመጯጯህ የሚናገሩት ነዋሪዎች ናቸው።
በእሬቻ ሚካኤል፣ በሱንቴ ማርያም፣ በሌንጫ ኦዳ፣ በኳስ ድሬ፣ በአርባ ቀላ፣ በወራንቡስ እና በተለያዩ ቦታዎች አሁን ድረስ ጥቃቱ ተስፋፍቶ ይገኛል የሚሉት ነዋሪዎቹ እስካሁን አንድም የመንግስት ሀይል ወደ ስፍራው እንዳልገባ እና ታጣቂዎቹ አካባቢው ላይ ከበባ በማድረግ ሰው እንኳን እንዳያመልጥ አድርገው ጭፍጨፋ እየፈፀሙ መሆናቸውን ተናግረዋል።
ይህ አካባቢ የከንቲባ አዳነች ትውልድ ስፍራ ነው፣ ምናልባትም ከሟቾቹ መሀል አንዳንዶቹን ሊያውቁ ወይም አብረው ተምረው፣ ሰርተው ይሆናል። ታድያ ሌላው አለም ላይ እንደምናየው በፍጥነት የጥቃቱ ቦታ ላይ ሄዶ ህዝብን ማረጋጋት እና ማፅናናት በአካባቢው በቀጠለው ጥቃት ምክንያት አልተቻለም እንበልና... በትውልድ ስፍራቸው እንዲህ አይነት ዘግናኝ ጥቃት ሲፈፀም 'ነፍስ ይማር' ለማለት እና ድርጊቱን ለማውገዝ ምነው ተሳናቸው? ሌሎች ባለስልጣናት እና የፀጥታ አካላትስ?
የሀገሪቱ የመከላከያ፣ የፖሊስ፣ የሚሊሻ፣ የአየር ሀይል እና ሌሎች ሀይሎችስ ለሰዓታት ሳይሆን ለቀናት እስካሁኑ ሰዓት ድረስ እየተፈፀመ ያለ ጥቃትን ለመከላከል ለምን አልቻሉም?
የዚህ ሀገር ነገር አንዳንዴ ያደክማል... ህዝቡ ድረሱልን ብሎ የሚጮኸው መንግስት ላይ ሳይሆን ሚድያ ላይ፣ ሚድያው መረጃ ለህዝብ ሲያደርስ ተመልሶ በህዝብ እና መንግስት የሚሰደበው እና የሚሳደደው ራሱ ሚድያው።
ለማንኛውም ለእኔ ይህን በመፃፌ ቀለል ይለኛል። በለቅሶ፣ በድንጋጤ እና በመጯጯህ ያናገርኳቸው ዜጎች ሁኔታ ግን መቼም ከአዕምሮ የማይፋቅ አሳዛኝ ክስተት ነው።
ያሳዝናል፣ ነፍስ ይማር!
ምንጭ ዜና መሠረት
ይኼንን ምልክት ካያችሁ ውስጣችን አይነጥላና ዛር አድፍጧልና እባካሁ ንቁ!! ማህጸኗን እንድሸትና ትዳሯ እንድፈርስ ያደረጉ ክፉ መንፈሶች!! https://youtu.be/F7SjPbeOuss
ለህልም ጥያቄዎቻችሁ የተሰጠ ኦርቶዶክሳዊ መልስና ፍቺ ክፍል 8 || ከሞተ ሰው ጋር በተደጋጋሚ ጫት እየቃሙ በህልም ማየት!! አውራ ዶሮ ሲያባርራችሁ ካያችሁ! https://youtu.be/2ZCY2yWwYZE
Why Oriental Orthodox Reject Papal Supremacy - Was Peter The First Pope! Did Jesus Create The Papacy https://youtu.be/GSz7MfA1Img
ለህልም ጥያቄዎቻችሁ የተሰጠ ኦርቶዶክሳዊ መልስና ፍቺ ክፍል 7 || የሞቱ ሰዎች በህልም አቅፈውን ስስሙን ማየት!! በህልም ግዙፍ ነገር ስጫነንና መጨነቅ!! https://youtu.be/0Wb9CEWDmFM
ከቤታችን በረከትን የሚያርቁ እነዝህን 3 ነገሮች ከማድረግ እባካችሁን ተቆጠቡ!! ትምህርት አልገባ ካላችሁና በሥራ ከተጀገራችሁ ይኼንን አድርጉ!! https://youtu.be/tcuIye4D6nA
👉 ደብረ ምጥማቅና ጣልያን፡ ጌታችን ክርስቶስ ጥሎት የተነሣውን መግነዝ ለማየት ሚሊዮኖች ለዓመታት ደጅ ይጠናሉ። ከረዥም የኢንተርኔት ምዝገባና ሰልፍ በኋላ 'Shroud of Turin' እየተባለ የሚጠራውን በቱሪን (ጣልያን) የሚገኘውን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተገነዘበትን መግነዝ አይተው ይደሰታሉ። ያ መግነዝ ገባሬ ተአምር መሆኑ አይጠረጠርም።
👉 ግንቦት 21 የምናከብረው በዓል ግን የተለየ ነው። ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ፥ አምላክ ሰው የሆነባት እመቤታችን በግብፅ የታየችበትና ለአምስት ዕለታት ያህል ሕዝብና አሕዛብ የተባረኩበት ቀን ነው። ሚሊዮኖች ከረዥም ዐመት በኋላ ተሰልፈው የሚያዩትን መግነዝ፥ጌታችን በመቃብር ትቶት ተነሥቷል፤ ጥሎትም አርጓል።
👉 ከድንግል ማርያም የነሣውን ሥጋ ግን በመቃብር አልተወውም፤ ጥሎትም አላረገም። ከተዋሐደው ሥጋ ጋር አንድ አካል አንድ ባሕርይ ሆኗልና።
ሰው አምላክ ሆኖ በዘባነ ኪሩቤል ይቀመጥ ዘንድ ምክንያት የሆነች የአምላክ እናት መታየቷ፥ በእርግጥም ዐለም በሰልፍ ከሚያየው መግነዝ ይበልጣል። ከእርሷ የነሣውን ሥጋ ጥሎት አላረገምና። መግነዙ ላይ ከሚታየውም የጌታችን ሥዕል ይልቅ በእርሷ ላይ የተገለጠው መገለጥ ይበልጣል። ምስሉ እ.ኤ.አ. 1968 የነበረውን ሌላ መገለጥ የሚያሳይ ነው።
👉 እንኳን አደረሳችሁ ለግንቦት 21 ለእመቤታችን አመታዊ ክብረ በዓል!
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
