ar
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

الذهاب إلى القناة على Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

إظهار المزيد
2 303
المشتركون
-424 ساعات
-117 أيام
-1230 أيام
أرشيف المشاركات
https://youtu.be/ucEXVNwBa5sራሳችንን እንድናጠፋ የሚገፋፋንን ክፉ መንፈስ በዚህ መንገድ አሸንፉ!! ትዝታው ሳሙኤል ዘንድሮም ብሶበታል ያሳዝናል!! 100% እጅግ የምታተርፉበት ተግሳጽ!!

ወላጆች ልጆቻሁን እባካችሁን ጠብቁ በተለይ አዳማና አዲስ አበባ ተጠንቀቁ!! የሰው ዋጋ ከዶሮ ዋጋ በታች ሆኗል እጅግ ያሳዝናል!! https://youtu.be/_iyCz1i6BHU

የደንቃራ መተት እጅግ ከባዱ ጉዳይ ማወቅና መጠንቀቅ ያለባችሁ ነገሮች!! በሽታን በመናፍስት እገዛ ማዘዋወርና አደገኛው ጉዳይ!! https://youtu.be/jDwLC-ZfKP4

አመቺሳና መዘዙ ይሄንን በደንብ አዳምጡ! https://youtu.be/WA82kbp8Bnc?si=PRbN-sd47NikkGWA

5ቱ ስማቸው ታርካቸውና ዘራቸው የጠፋ ትውልድ እጅግ ወሳኝ መልዕክት!! ቴዲ አፍሮ ለጀግናዋ ሯጭ መሰረት ደፋር ምን ሰጣት!! https://youtu.be/Otnu3Zz4T2I

መምህር ተስፋዬ በአዲስ አመት የገጠመው እጅግ አስደንጋጭ ጉዳይ! 5ቱ ምልክቶች መናፍስት ውስጣችን ለመኖራቸው!! በአዲሱ አመት እጅግ መጠንቀቅ ያለብን ነገሮች! https://youtu.be/-Om6Bi-lRx8

ዐውደ ዓመት ለባርኮ ባርኮ ዐውደ ዓመት ንዒ ማርያም ለምሕረት ወሣህል። እዛኝ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረድኤት አትለየን። ቸር ዐውደ ዓመት ታድርግልን። ሰላሙን ያድለን። አሜን።
ዐውደ ዓመት ለባርኮ ባርኮ ዐውደ ዓመት ንዒ ማርያም ለምሕረት ወሣህል። እዛኝ እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በረድኤት አትለየን። ቸር ዐውደ ዓመት ታድርግልን። ሰላሙን ያድለን። አሜን።

መምህር ግርማ ከማህበሩ የቀረበላቸው የማታለያና የወጥመድ ጥያቄዎች!! ዲያቆን ሄኖክ የገለጠው ጴንጤዎች ማዳመጥ ያለባቸው!! የተሳሳቱ ሰዎችን አይታችሁ አትለፉ! https://youtu.be/hoDahm-AOrw

"ለሰጣችሁ ሁሉ...." ​"እግዚአብሔር አምላክ አዲሱን ዘመን የነፍሳችሁ መታደሻ፣ የውስጥ ማንነታችሁ መጠናከሪያ ያድርግላችሁ። ከመንፈሳዊ ድካም፣ ከህሊና እረፍት ማጣትና ከዓለም ውጣ ውረድ ሰውሮ፣ በቃሉና በሰላሙ የጸና ልብ ይስጣችሁ። ከአምላካችሁ ጋር ያላችሁ ግንኙነት በየቀኑ እየታደሰ የሚሄድበት፣ መንፈሳዊ ጉዞአችሁ የጠራና ወደ ከፍታ የሚያደግበት፣ ቤታችሁና እጃችሁም ለበጎ ነገር ሁልጊዜ የተባረከ ይሁን!" መልካም ሌሊት ይሁንላችሁ

በመጽሐፈ መነኰሳት እንዲህ ያለ ታሪክ ተጽፏል የእስክድስ አባትና እናት ፍልስፍና ይማር ብለው ወደ አቴና ሰደዱት። ፍጹም ትምህርት ተማረ። አባቱ በሚሞትበት ጊዜ «ወንድ ለምደሽ፣ ባል ወደሽ ልጄን በሰው ሀገር እንዳታስቀሪው» አላት። ሦስት ዓመት ተጠብቃለች። መምህሩ «ሴቶች መጠበቃቸው እስከ ሦስት ቀን ድረስ ነው። ከዚያ በኋላ ግን ቦታ ከተመቻቸው፣ ሰው ከተለያቸው ጽናት የላቸውም፤ ይህን ሳትፈትን ይደረጋል አይደረግም አትበል» አለው። በፍልስፍና የሰበሰበውን ገንዘብ ይዞ ሒዶ ከወንዝ ዳር ሰፈረ። በዚያ አካባቢ የአባቱ ባሪያ ውኃ ልትቀዳ መጣች። «ጌታሽ አለ?» አላት። «አትገዳደረኝ ሙቷል፤ እንዴውም አንተን ይመስል ነበር» አለችው። «ከእመቤትሽ አገናኝኝ» አላት። «አይሆንም ትጣላኛለች እንዲህ ያለ ነገር አታውቅምና» አለችው። «ብዙ ወርቅ እሰጥሻለሁ» አላት። ብትነግራት ራሷን ገመሰቻት። ወደእሱ ሒዳም «አይሆንም አለችኝ» አለችው ከቅጽር ተጠግቶ ሰፈረና በገና ይደረድር ጀመረ። በገናው ከእንጒርጉሮው እንጒርጉሮው ከበገናው ተስማምቶ ሲሰማ ሰምታ፦ «ይህ ሰው መልከ መልካም ነውን?» አለቻት «አዎን! እኔማ ያጨዋውትሽ ብዬ ነበር አይሆንም አልሽኝ እንጂ» አለቻት «ግባ በዪው» አለቻት። ሲገባ ልቡናዋ በፍርቅር ተታሎ ተነሥታ ተገናኘችው። በልተው ጠጥተው ተኙ። እግሩን ወደራሷ ራሱን ወደእግሯ አድርጎ ተኛ። "እንዲህ ሆኘ (ተዘቅዝቄ) የወጣሁበት ነው" ሲል። ሆዷን ይስመዋል "ዘጠኝ ወር ከአምስት ቀን የኖርሁበት ነው" ሲል ጡቷን ይስማል። "ሦስት ዓመት ከመንፈቅ ያደግሁብህ" ሲል። ሌሊቱን ሙሉ እሷ በፍትወት ሥጋዊ እሱ በፍትወት መንፈሳዊ ሲናደዱ አድረዋል። አላስችላት ሲል «አንተ ሰው የመጣህበትን አታደርግምን? ልትዘብትብኝ ነው የመጣህን» አለችው «እናቴ አላወቅሽኝም እኔማ ልጅሽ እስክንድስ ነኝ» አላት። «እስካሁን የተጠበቅሁትን በልጄ ላፈርስ? ሌላም ቢሆን እንዲህ ነው።» ብላ ታንቃ ሞተች። «ኦ አፍ ዘአቅተልከ እመከ ይደልወከ አርምሞ - አንተ እናትህን ያስገደልህ አፍ ሆይ ዝምታ ይገባሃል።» ብሎ አርምሞ ይዟል። ዛሬም በዘመናችን በንግግራችን የሰበርናቸው፣ ያለ አግባብ የወጋናቸው ግለሰቦች ብዙ ናቸው። ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን እየጣሱ፣ መሠረተ ሃይማኖትን እየገረሰሱ፣ በዐደባባይ ነውርን ለሚገሡ ወገኖች ግን አርምሞ (ዝምታ) ረብ የለውም። «በቀሲስ ገትነት አይተነው»

በአመቺሳ የተወለዱት 4ቱ ልጆች የገጠማቸው እጅግ የሚያሳዝን ህይወት!! ጸጉራችሁን ረጅምና ራስታ የሚታደርጉ እባካችሁን ተጠንቀቁ!! https://youtu.be/vM_-MWzYz5k

ኆኅተ ሰማይ ዛሬ ለሊት የሰማይ መስኮት ይከፈትላችሁ የሰማይ ብርሃን ይገለጥላችሁ የበረከት በር ይከፈትላችሁ የዓመቱ ጸሎታችሁ ያርግላችሁ የዓመቱ ስግደታችሁ ያርግላችሁ የዓመቱ ቁርባናችሁ ይስመርላችሁ
+1
ኆኅተ ሰማይ ዛሬ ለሊት የሰማይ መስኮት ይከፈትላችሁ የሰማይ ብርሃን ይገለጥላችሁ የበረከት በር ይከፈትላችሁ የዓመቱ ጸሎታችሁ ያርግላችሁ የዓመቱ ስግደታችሁ ያርግላችሁ የዓመቱ ቁርባናችሁ ይስመርላችሁ ጠላታችሁ ይደምሰስላችሁ አዲስ በረከት ይምጣላችሁ ምሕረት ይውረድላችሁ የምስራች ያሰማችሁ አሜን።

በራስ ወዳድነት ውስጥ የሚያደፍጡ ክፉ መናፍስቶችና ከባድ ፈተናዎቹ!! የቡዳ መንፈስ እጅግ ከባዱ የጥቃት ስልቶች! https://youtu.be/lBVKsY6u34o

ቦክሰኛው ኒቃተ ህሊና እምነትና ሃይማኖት ማደንዘዣ ናቸው አያስፈልጉም! ክርስቶስ ብቻ ሳይሆን አርስቶትልም ለእኔ ሞቶል! የኒቃተ ህሊና የጸረ ክርስቶስ አካሄድ! https://youtu.be/JvPBHH_mS4c

=> ብዙዎቻችን ንስሐን ለሽምግልና፣ ጸሎትን ደግሞ ለችግር ቀን እናስተርፋለን። ነገር ግን ሞት ቀጠሮ የለውም፤ መቃብርም ለሽማግሌዎች ብቻ አልተቆፈረም። "ነገ እመለሳለሁ" አትበል፤ ነገ ያንተ መሆንዋን አታውቅምና። ሰይጣን "ነገ ትሠራለህ" እያለ ዛሬህን ይሰርቅሃል። "አንተ የምትተኛ ንቃ ከሙታንም ተነሣ ክርስቶስም ያበራልሃል።" (ኤፌሶን ፭፥፲፬) => ሥጋህን በቀን ሦስት ጊዜ ለመመገብና ለማስዋብ ትተጋለህ፤ ነፍስህ ግን የእግዚአብሔር ቃልና ቅዱስ ቍርባን ርቧት ከስታለች። ለሚጠፋ ሥጋ ተጨንቀህ ለማይጠፋው ማንነትህ ለምን ቸል ትላለህ? "ሥጋውን አጥግቦ ነፍሱን የሚያስርብ ሰው፣ ለጠላት ዲያብሎስ የተመቸ ግዳይ ይሆናል።" (ማር ይስሐቅ) "ሰው ዓለሙን ሁሉ ቢያተርፍ ነፍሱንም ቢያጐድል ምን ይጠቅመዋል?" (ማቴዎስ ፲፮፥፳፮) => የገዛ ራሳችንን ታላቅ ኃጢአት (ግንድ) ዘንግተን፣ በወንድማችን ላይ ባለችው ጥቃቅን ስህተት (ጉድፍ) ላይ ፈራጅ እንሆናለን። በሰው ላይ በፈረድክ ቁጥር የእግዚአብሔርን የፍርድ ወንበር እየተቀማህ መሆኑን እወቅ። የራስህን በደል የሚመለከት ዐይን ካለህ፣ በሰው ላይ ለመፍረድ ጊዜ አይኖርህም። "እንዳይፈረድባችሁ አትፍረዱ፤ በምትፈርዱበት ፍርድ ይፈረድባችኋልና።" (ማቴዎስ ፯፥፩-፪) => ጸሎት ስትጀምር እንቅልፍ የሚመጣብህ፣ ሐሳብህ የሚበታተነውና የሚሰለችህ ከሆነ ጸሎትህ ሰይጣንን እያቃጠለው መሆኑን እወቅ። ጠላት የሚያዝልህ ከፈጣሪህ ጋር እንዳትነጋገር ነው። "ሌባ የማይዘርፈው ባዶ ቤት ሳይሆን ሀብት ያለበትን ቤት ነው። ሰይጣንም የሚዋጋህ በእጅህ ያለውን ጸጋ ሊሰርቅህ ስለሚተጋ ነውና በጸሎት ንቃ።" (ታላቁ ቅዱስ አንጦንዮስ) "ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ።" (ማቴዎስ ፳፮፥፵፩) => በሰው ፊት ነጭ ነጠላ ለብሰህ መታየትህ፣ መጾምህና መጸለይህ ብቻ ክርስቲያን አያደርግህም። እግዚአብሔር የሚመለከተው በሰው ፊት የማይታየውንና በቂም፣ በምቀኝነት፣ በክፋት የጠቆረውን ልብህን ነው። ልብህ መቅደስ ካልሆነ፣ ሰውነትህ ለጸሎት ቢቆምም ባዶ ቤት ነው። እግዚአብሔር የሚፈልገው ቃላትህን ሳይሆን ልብህን ነው። "ልጄ ሆይ፥ ልብህን ስጠኝ፥ ዓይኖችህም መንገዴን ይውደዱ።" (ምሳሌ ፳፫፥፳፮)

3ቱ እጅግ አደገኛና ግራ የተጋቡ የሴት ደብተራዎች እባካችሁን ተጠንቀቋቸው!! ጸበልና እምነት ክፉ መናፍስትን በጭራሽ አያርቅም!! https://youtu.be/_5SwBtup3z8

"ደብተራ" እና "መሪጌታ" የሚሉት ማዕረጎች ጣዖት ለኾኑባችሁ ኹሉ፦ በጣም ከሚያሰለቹኝና ብዙ ጊዜም መልስ ሰጥቼበት፡ መላልሳችሁ ከምትጠይቁኝ ጥያቄዎች መካከል አንዱ፦ "ለምን መሪጌቶች እና ደብተራዎች የሚለውን ማዕረግ፡ ከጥንቆላ ጋር አያይዘሽ ትጠቀሚያለሽ?" የሚለው ነው። አልሰማችሁም እንዴ?! ራሳቸውን "መሪ ጌታ" እና "ደብተራ" እያሉ የሚጠሩ ናቸው እኮ "ለመስተፋቅር ለሀብት ለሕገ-ጠብቅ" ምናምን እያሉ ጥንቆላን የሚያስተዋውቁት?! ካላመናችሁኝ ቴሌግራም ቻነላቸውን ተመልከቱ! ማዕረጉን ከጥንቆላ ጋር በስም ብቻ ሳይኾን፡ በተግባርም ካያያዙት እኮ ቆዩ! ዓይናችሁ እያየ አይደለም እንዴ? ወይስ የትኛው ፕላኔት ላይ ነው የምትኖሩት? ድርጊታቸውን ማስቆም ከተፈለገ፡ ማንነታቸው እየተጠራ፡ ሰይጣናዊ ሥራቸው መወቀስ አለበት። ምክንያቱም፡ እስካሁን ከነማዕረጋቸው ነው ያሉት። ቤተክርስቲያን ማዕረጋቸውን ልትገፍፋቸው ሲገባ እስካሁን ማንም የነካቸው የለም። ኹሉም፡ ተባብሮ አጥማቂ ማውገዝ ላይ ነው በርትቶ ያለው። ምክንያቱም አውጋዡ ኹሉ በምሥጢር የመሪጌቶቹ ደንበኛ ነው። ሥራቸው በተወቀሰ ቁጥር፡ "የማዕረጋቸው ስም አይጠቀስ፤ ምክንያቱም ማዕረጉ ክቡር ነው" ብለን በተከላከልንላቸው ቁጥር፡ ትውልዱ "መሪጌቶችና ደብተሮች የሚሠሩት ኹሉ ትክክል ነው" ብሎ ወደመቀበል ነው እኮ የሚኼደው?! ይኽ አደጋ እንዴት አይታያችሁም? "መሪጌታነት የቤተክርስቲያን ማዕረግ እስከኾነ ድረስ፡ ጥበባቸውም የቤተክርስቲያን ጥበብ ነው" እያለ ነው እኮ ብዙ ሰው እየተሸወደ ያለው?! ይኽ እንዴት አይገዳችሁም? "እውነተኛው መሪጌታነትና ድብትርና ይኼ አይደለም" ብሎ፡ ጋኔን በሚጎትቱ ላይ በቁጣ የሚዘምት እስካልተነሳና ማዕረጋቸውን ገፍፎ "አቶ" በሚል ስም እንዲጠሩ የሚያደርግ እስካልተነሳ ድረስ፡ "ስለማዕረጉ ክብር ሲባል ሥራቸውን አንግለጥባቸው" የሚለው አባባል፡ ለአጋንንት አሠራር ሽፋን መስጠት ነው እንጂ፡ ሌላ ምንም ጥቅም ሊሰጠን አይችልም። በተጨማሪም " 'መሪጌቶችና ደብተሮች ጥንቆላ ይሠራሉ' እያሉ ማዕረጉን የሚያጥላሉት፡ ለአማራ ብሔር ጥላቻ ያላቸው የሌሎች ብሔር ተወላጆች ናቸው" እያሉ፡ ጉዳዩን ከመንፈሳዊ የአምልኮ ባዕድ ችግር አላቅቀው፡ የብሔር መልክ የሚሰጡትም፡ ራሳቸው መሪጌቶቹና ደብተሮቹ መኾናቸውንም እወቁት። ይኽን የሚሉት፡ ለራሳቸው አጋንንታዊ ተግባር ሽፋን ለመስጠት እንጂ፡ ለማዕረጉ ተቆርቁረው አይደለም! ለማዕረጉ ቢቆረቆሩማ፡ አዋርደው ሌላ ሥራ ባልሠሩበት ነበር። መቼ ነው የምትነቁት ግን? ሰይጣን፡ ባዕድ አምልኮው ሲነካበት፡ "ብሔሬ ተነካ" ማለት የኖረ ስልቱ ነው። እየሰማችሁ ነው? ደግማችሁ አንብቡት! ሰይጣን፡ ባዕድ አምልኮው ሲነካበት፡ "ብሔሬ ተነካ" ማለት የኖረ ስልቱ ነው። - የደቂቀ እስጢፋ ኑፋቄና ወንጀል ሲጋለጥ - "ትግሬነት ተነካ" ይሏችኋል፤ - ጨሌና አቴቴ ሲጋለጥ - "ኦሮሞነት ተነካ" ብለው ይነሱባችኋል፤ - ሥር ማሽ ቅጠል በጣሽ ደብተሮችና መሪጌቶች ሲጋለጡ "አማራነት ተነካ" - ብለው ይዘልሉባችኋል። - ሌላውም ብሔር፡ እንዲሁ፡ የማያስነካው የየራሱ የጎሳ ጨሌ አለው። ከጥንትም ጀምሮ ለክርስትና እምነት እንቅፋት የኾነው እኮ ይኽ ነው! አርጤምስ ስትነካ "ግሪክነት ተነካ" ይላል፤ የመነናውያን ጥንቆላ ሲነካ "አይሁድነቴ ተነካ ይላል"፤ ኮከብ ቆጠራ ሲነካ "ባቢሎንነቴ ተነካ" ይላል። ሐዋርያት የዓለምን ሕዝብ ወደጽዮን ለማምጣት የተቸገሩት እኮ፡ እንዲህ ባለ የብሔር ድንቁርና ምክንያት ነው?! መቼ ነው የምትነቁት ግን? ከሃይማኖት ብሔርንና ማዕረግን ማስበለጥ፡ የባቢሎናውያን እንጂ፡ የጽዮናውያን ምግባር አይደለም። ከዚያ ውስጥ ውጡ!! "አብርሃም ሆይ! ከሀገርህ፥ ከዘመዶችህ፥ ከአባትህም ቤት ተለይተህ ውጣ፤ እኔ ወደማሳይህ ምድር ኺድ" ስትባሉ፡ እስከመቼ ነው "እንቢ" የምትሉት? ወደ ተስፋይቱ ምድር፥ ወደ ጽዮን፥ ወደ ዩቶፕያ፥ ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ለመኼድ፡ ለምንድነው የምታወላውሉት? ምንድነው የከበዳችሁ? እስኪ ግልጽ አድርጉት? በዶ/ር መስክረመ ለቺሳ ተጻፈ