7 367
Subscribers
+424 hours
+907 days
+34030 days
Posts Archive
7 368
+1
Inbox
ሰላም እንዴት ነህ ወንድሜ ? ከአሰኮ ነው የምጽፍልህ።ወንድሜ እኛ ያለንበት መከራ እናንተ በሚዲያ ከምትሰሙት የከፋ ነው።እናንተ የምትሰሙት ከሚሆንብን ጥቂቱን ነው። ተሰደው በመከራ ውስጥ ካሉት ወንዶቹ ተመርጠው ወደ አከባቢያችሁ ተመለሱ ተብለው ሄደዋል ። ልብ በል መኖሪያ ቤት የለ የት ነው የሚያድሩት!ይኽን ያደረጉት " ጳጳሳቱ ይመጣሉ"መባሉን ተክትሎ ነው ብዙ ስደተኛ መኖሩን ለመደበቅ ሲሉ ነው እንዲህ የሚያደርጉት።የሚያሳዝነው ነገር የወንዶቹ ተመርጠው እንዲመለሱ መደረግ ብቻ ሳይሆን የጳጳሳቱ አለመምጣት ነው።ሊደርሱ ነው ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ነው የቀራቸው ተብለን በጉጉት ስንጠብቅ ብዙም ሳንቆይ ወደ አቦምሳ "ተመለሱ"የሚል ዜና ሰማን።መመለሱን እሺ ይመለሱ ምነው በጸጥታ ምክንያት እንደተመለሱ ተናግረው እኛም ያለንበትት ሰቆቃ ቢያሳውቁ! በ አባቶቻችን አፈርን።ከገዳዮች ባልተናነሰ ነው የጎዱን። ለአቦምሳ ድጋፍ አደረግን ሲሉ ጥቂት እንኳ አያፍሩም?አባት እንዴት የልጆቹን መከራ ይሸፍናል? ከመድኅንዓለም በቀር የሚደርስልን እንደሌለ አሁን ተረዳን ።በዚህ ላይ ከባለሥልጣናቱ ብዙ ዛቻና ማስፈራሪያ እየደረሰብን ነው። ወንድሜ ወዴት እንደምንጮህ ግራ ገብቶናል።
7 368
+1
Inbox
ሰላም እንዴት ነህ ወንድሜ ? ከአሰኮ ነው የምጽፍልህ።ወንድሜ እኛ ያለንበት መከራ እናንተ በሚዲያ ከምትሰሙት የከፋ ነው።እናንተ የምትሰሙት ከሚሆንብን ጥቂቱን ነው። ተሰደው በመከራ ውስጥ ካሉት ወንዶቹ ተመርጠው ወደ አከባቢያችሁ ተመለሱ ተብለው ሄደዋል ። ልብ በል መኖሪያ ቤት የለ የት ነው የሚያድሩት!ይኽን ያደረጉት " ጳጳሳቱ ይመጣሉ"መባሉን ተክትሎ ነው ብዙ ስደተኛ መኖሩን ለመደበቅ ሲሉ ነው እንዲህ የሚያደርጉት።የሚያሳዝነው ነገር የወንዶቹ ተመርጠው እንዲመለሱ መደረግ ብቻ ሳይሆን የጳጳሳቱ አለመምጣት ነው።ሊደርሱ ነው ጥቂት ደቂቃዎች ብቻ ነው የቀራቸው ተብለን በጉጉት ስንጠብቅ ብዙም ሳንቆይ ወደ አቦምሳ "ተመለሱ"የሚል ዜና ሰማን።መመለሱን እሺ ይመለሱ ምነው በጸጥታ ምክንያት እንደተመለሱ ተናግረው እኛም ያለንበትት ሰቆቃ ቢያሳውቁ! በ አባቶቻችን አፈርን።ከገዳዮች ባልተናነሰ ነው የጎዱን። ለአቦምሳ ድጋፍ አደረግን ሲሉ ጥቂት እንኳ አያፍሩም?አባት እንዴት የልጆቹን መከራ ይሸፍናል? ከመድኅንዓለም በቀር የሚደርስልን እንደሌለ አሁን ተረዳን ።በዚህ ላይ ከባለሥልጣናቱ ብዙ ዛቻና ማስፈራሪያ እየደረሰብን ነው። ወንድሜ ወዴት እንደምንጮህ ግራ ገብቶናል።
7 368
Repost from Zemedkun Bekele (ዘመዴ)
"…ከበሻሻ ጀምሮ ክርስቲያን ኦርቶዶክስን በማሳረድ የተካነው፣ እስከዛሬም የሚያሳርደው፣ የሚያፈናቅል፣ የሚዘርፍ የሚያወድመው የዳግማዊ ግራኝ የአቢይ አሕመድን የአረመኔ ሰይፉን እሳት ስለት ጥይቱን ተራ በተራ ቁጭ ብላችሁ ተጎልታችሁ የመታረጃ ቀናችሁን የምትጠብቁ፣ ስትታረዱም የዶሮን ያህል እንኳ ለመፈንፈራገጥ እንቅስቃሴ የማታደርጉ እንደወለጋ ልጆች በከንቱ በብላሽ አንሞትም ብላችሁ የማትንቀሳቀሱ ውዝፍ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክሳውያን ተዋሕዶ ልጆች ሆይ…
• እንደምን አደራችሁ…?
7 368
በአርሲ ሀገረ ስብከት ከአሰኮና ከመርቲ ተፈናቅለው በአቦምሳ ከተማ በትንሣኤ ብርሃን መድኅንዓለም ቤተ ክርስቲያን ለተሰበሰቡ ክርስቲያኖች ጉብኝትና ድጋፍ ተደረገ
7 368
የአርሲ ሀገረ ስብከት ሚዲያ ደግሞ EOTC በዋሸው ላይ ሌላ ወጨት በመጨመር እርዳታው አሰኮ ኦርቶዶክሳውያን ጭምር ተደርጓል " እያለ ነው። የአሰኮ ኦርቶዶክሳውያን ሆይ እናንተስ ምላሻችሁ ምንድን ነው?
7 368
Repost from ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)
ጳጳሳቱ አሰኮ ሳይደርሱ ተመለሱ
የቤተክህነቱ ልዑካን ጳጳሳት ጉዞ የጀመሩት አሰኮ ወረዳ የተጎዱትን ምእመናን ለማየት ነበር። ነገር ግን አሰኮ ወረዳ ሊደርሱ ትንሽ ኪሎ ሜትር ሲደርሱ ተደሎ "የጸጥታ ችግር አለና ተመለሱ" ተባሉ።
ወደ ኋላ ዞረው ተመለሱ በዚኽ ጊዜ ነው ወደ አቦምሳ ጎራ ብለው የያዙትንም እዛው አራግፈው እግሬ እውጭኝ ብለው የተመለሱት።
እነርሱ እንደተመለሱ አሰኮ የጸጥታ አካላት ተከትለው ገቡ።
ይኽንን መተንተን የእኛ ጉዳይ ነው። ጳጳሳቱ ከመጡ ሕዝቡ ወጥቶ እንደ ልቡ ሊናገር ነው። ችግሩን ሊዘረዝር ነው። ስለዚኽ ለጳጳሳቱ ደውለው ተመለሱ የሚለው ራሱ የመንግሥት አካል ነው። ስለዚኽ ገዳዩ ራሱ መንግሥት መኾኑን ያሳያል።
ንዋይ ካሳሁን
7 368
በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የተመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ አርሲ-አቦምሳ ወረዳ ተገኝቶ ምዕመናንን አጽናና ጊዜያዊ እርዳታም አበረከተ።
ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በአርሲ ዞን አንዳንድ ወረዳዎች የተከሰተውን ችግር ተከትሎ
በብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁና በብፁዕ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊው የሚመራ የቤተክርስቲያናችን ልዑክ በሥፍራው በመገኘት ተጎጂዎችን እንዲያጽናና ጊዜያዊ ርዳታም እንዲያደርግ ያስተላለፈውን ውሳኔ ተከትሎ ዛሬ ማለዳ ወደ አርሲ ዞን አቦምሳ ወረዳ በመጓዝ ጉዳት የደረሰባቸውን ወገኖች አጽናንቷል፤ ጊዜያዊ እርዳታም አበርክቷል።
በአቦምሳ ወረዳ የትንሣኤ ብርሃን ደብረ ገነት መድኃኔዓለም ቤተክርስቲያን በመገኘት ተጎጂ ኦርቶዶክሳዊያንን ያጽናኑት
ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ፣የደቡብ ምዕራብ ሸዋና የሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ቅድስት ቤተክርስቲያን በበኦርቶዶክሳዊያን ልጆቿ ላይ በደረሰው ጉዳት እጅግ በጣም ማዘኗን ገልጸው እግዚአብሔር አምላክ ለሞቱት ወገኖቻችን መንግስተሰማያትን እንዲያወርስልን፣ለቤተሰቦቻቸው መጽናናት እንዲያድልልን የዘወትር ጸሎታችን ነው።በርቱ፣ጠንክሩ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን ብለዋል።
አያይዘውም ቋሚ ሲኖዶስ በአካል ተገኝቶ እናንተን ለማጽናናትና ጊዜያዊ ድጋፍ ለማድረግ በመካከላችሁ ተገኝተናል ያሉት ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ችግሩን ከመሰረቱ ለመፍታትና የተቃጠለውን ቤተክርስቲያን ለመሥራት የሚያስቼል አቢይ ኮሚቴ በጠቅላይ ቤተክህነት ተሰይሞ ወደ ሥራ ገብቷል ብለዋል።
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ባስተላለፉት አባታዊ መልዕክት ቅድስት ቤተክርስቲያን በተከሰተው ችግር ጥልቅ ኃዘን የተሰማት መሆኑን ገልጸው ምዕመናን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ፣በፈተና ሁሉ እንዲታገሱ አደራ ካሉ በኋላ እግዚአብሔር አምላክ ኃዘንተኞችን እንዲያጽናና ከዳግም ኃዘን እንዲሰውርልን ዘወትር እንጸልያለን በማለት ቃለ ምዕዳንና ቃለ ቡራኬ ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ብፁዕ ጠቅላይ ሥራ አስኪያጁ ለተፈናቀሉ ወገኖች የተዘጋጀውን ርዳታ ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ለብፁዕ አቡነ ኤልሳዕ አስረክበዋል።በዚሁ ጊዜ የአቦምሳ ከተማ የሀገር ሽማግሌዎችና አባ ገዳዎች ብፁዓን አባቶችን እንኳን ደህና መጣችሁልን በማለት በሀገሩ ባህል መሰረት የሰንጋ ስጦታ ካበረከቱ በኋላ የደረሰውን ጉዳት በመኮነን ሕዝቡ በስምምነት፣በአንድነትና በመቻል የኖረና ወደፊትም የሚኖር ሕዝበብ መሆኑን ጠቅሰው የተፈጠረውን ችግር ሃይማኖታዊ መልክ ለማስያዝ የሚደረገው ጥረት ተገቢነት የሌለው ነው ብለዋል።ለብፁዓን አባቶች የተበረከተው የሰንጋ ስጦታም ለተፈናቀሉ ወገኖች እንዲደርስ ተደርጎ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።
መረጃው የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ነው።
7 368
እስከመቼ እውነትን ደብቃችሁ ታስፈጁናላችሁ? እርዳታውን ይዛችሁ የወጣችሁት በአሰኮ ላሉት ተፈናቃዮች ነው መንግሥት ድራማ ሠርቶባችሁ እዚያ እንዳትደርሱ አደረጋችሁ። ይኽን እውነታ ለምንድን ነው የምትደብቁት?
7 368
አርሲ አሰኮ
በከፍተኛ መሳሪያ ታጅበው ወደ አሰኮ ሲጓዙ የነበሩ ጳጳሳት አሰኮ ሊደርሱ ሲሉ ከከፍተኛ ባለሥልጣናት ተደውሎባቸው "ከፊታችሁ ችግር አለ"እንዲመለሱ ተደርገዋል።ልክ እነርሱ እንደተመለሱ ደግሞ ፌዴራል ፖሊስ ያለምንም ኮሽታ አሰኮ ገብቷል።ይኽ ሆን ተብሎ የተሠራ ሴራ ነው
በስፋት እመለስበታለሁ።
7 368
ቤተ ክርስቲያን ስደት ላይ ነች፡፡
ይኸንን ሲቃ፣ ይኸንን መከራ፣ ይኸንን እውነት በፕሮፓጋንዳ እና በሐሰት ልትሸፍነው አትችልም፡፡
ሐቁ እየወጣ፣ ለዓለም እየተገለጠ ይሄዳል፡፡ ወይ ችግሩን ከሥሩ ትፈታለህ ወይም ሀገርህን ይዘህ ገደል ትገባለህ፡፡ ከዚህ የተነሣ ነው የኦርቶዶክሳውያን ግድያ የኦርቶዶክሳውያን ብቻ ጥያቄ የማይሆነው፡፡ ሀገሩን የሚፈልግ ሁሉ ኢፍትሐዊነትን፣ ግፍን፣ ዘግናኝና ክብ ጭፍጨፋን የማስቆም ግዴታ አለበት፡፡
ይኸው ነው፡፡
አረጋ አባተ
7 368
"በኦርቶዶክሳውያን ላይ ግፍን ማውገዝ ፖለቲካ አይደለም"
"ኢትዮጵያ በኦርቶዶክሳውያን ደም አትበለጽግም"
"ለመታረድ የሚያዘጋጀን ሰባኪ ከሚያርዱን ለይተን አናይም"
7 368
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
ጥቃቱ በአርሲ ብቻ ተወስኖ ይቀራል?
https://t.me/Eyo21e
7 368
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
ክፍል 2
ክርስትናን ከምሥራቅ ኢትዮጵያ ለማጥፋትና ኢስላማዊ ቀጠና ለመፍጠር ዒላማ የተደረጉ ክርስቲያኖች የሚበዙባቸው አከባቢዎች እነ ማን ናቸው?
https://t.me/Eyo21e
7 368
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
አርሲ ላይ እየሆነ ያለው እልቂት መነሻው ምንድን ነው? የመጨረሻ ግቡስ ምንድን ነው?
https://t.me/Eyo21e
7 368
ሥርዐታዊ ቁማር በኦርቶዶክስ ላይ
"በአሰኮ የተፈጠረውን ችግር በአንድነትና በመቀናጀ መንገድ በመመከት የተረጋጋ ሰላም ለማረጋገጥ በቁርጠኝነት እየተሡራ ነው"እያሉን ነው እነ ኢብራሂም ከድር።እዚህ ላይ ጥያቄ እናንሳ፦
1) የታረደው የተሰደደው ፣ቤተ ክርስቲያን የተቃጠለበት ኦርቶዶክሱ ሆኖ ሳለ ሙስሊሞችን መሰብሰብ ለምን አስፈለገ?
2) እዚህ ስብሰባ ሳይ አንድም ኦርቶዶክስ ያልተገኘው ለምንድን ነው?
3) ኢስላማዊት ኦሮሚያን ለማዋለድ ለወሀቢያው ስንቅና ትጥቅ የምታቀርቡት እናንተው ሆናችሁ ሳላችሁ እንዴት ነው ሰላምን የምታረጋግጡት?
አስረግጠን እንነግራችኋለን የፈለጋችሁትን ያክል የውሸት ፕሮፓጋንዳ ብናሰራጩ እልቂታችንን መሸፋፈን አትችሉም።Dghugaan Jira Kanaadha
7 368
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
+2
ቤተ ክህነቱ የኦርቶዶክሳውያን እልቂት የቤተ ክርስቲያን ውድመት ባያሳስበውም የቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአርሲ ኦርቶዶክሳውያንን በተመለከተ ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ጥያቄያቸውን አቅርበዋል
https://t.me/Eyo21e
