en
Feedback
Eotc Task Force

Eotc Task Force

Open in Telegram

ወቅታዊ ጉዳይ

Show more
7 269
Subscribers
-1324 hours
-277 days
-6230 days

Data loading in progress...

Similar Channels
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+26
in 7 channels
August '26
+193
in 7 channels
Get PRO
July '26
+550
in 12 channels
Get PRO
June '26
+6 031
in 26 channels
Get PRO
May '26
+89
in 3 channels
Get PRO
April '26
+88
in 3 channels
Get PRO
March '26
+506
in 1 channels
Get PRO
February '26
+5
in 0 channels
Get PRO
January '26
+15
in 1 channels
Get PRO
December '25
+78
in 4 channels
Get PRO
November '25
+519
in 2 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
08 September0
07 September0
06 September+2
05 September+3
04 September+1
03 September+14
02 September+4
01 September+2
Channel Posts
ዓመቱ በሙሉ በማውራት አለቀ። አሁንም ማውራት ከዚያም ማውራት ማውራት... ነጥብ ያለው ተግባር ካልተፈጸመበት ዓመቱ በሙሉ በፍሬ የተሞላ አይሆንም። ከማውራት ዓመት ወደ መልካም የወሬ ዓመት ልንል ትንሽ ቀርቶናል።

2
"ጥቋቁር(ጀርመኖች)ናዚዎች በኢትዮጵያ ምድር" የጀርመን ክርስትና” አቀንቃኞች የዘር ሕጎችን በእምነታቸው ውስጥ ከፍ አድርጎ መደገፍ ከእግዚአብሔር የተጣለባቸው የመገለጥ አደራ እንደሆነ ይሰማቸዋል። በ
"ጥቋቁር(ጀርመኖች)ናዚዎች በኢትዮጵያ ምድር" የጀርመን ክርስትና” አቀንቃኞች የዘር ሕጎችን በእምነታቸው ውስጥ ከፍ አድርጎ መደገፍ ከእግዚአብሔር የተጣለባቸው የመገለጥ አደራ እንደሆነ ይሰማቸዋል። በጀርመን ክርስትና ቸርች 10 ነጥቦች ያለው መመሪያ ሲያሳትሙ ማዕከል ያደረገው ዘረኝነትን ነበር። ሰባተኛው ነጥብ እንዲህ ይል ነበር፡- “እግዚአብሔር ዝርያን፣ አገርን፣ ብሔራዊ ሕጎችን እንድንጠብቅ አደራ ሰጥቶናል። . .ስለዚህ የዝርያ መቀላቀልን አጥብቀን መቃወም አለብን።”  እንዲሁም ነጥብ ዘጠኝ፡- “አይሁድ ለዝርያችን ጥራት ከፍተኛ አደጋ ሆነው ይገኛሉ። ተልዕኳችን እንግዳና ባዕድ የሆነ ደም ወደ ዘራችን እንዳይገባ መጠንቀቅና መጠበቅ ግዴታችን ነው። መዳቀል ደማችንን የመበከል እድል ስለሚፈጥር የአይሁድን የጀርመን ዜግነት የሚፈቅድ ሕግን እንቃወማለን። በጀርመንና በተለይ በአይሁድ መካከል የሚደረግ ጋብቻ ፈጽሞ ሊከለከል ይገባል” ይላል፡፡  በ1933 በታተመው The Handbook of the German Christians በሚል  የጀርመን ክርስትናን አቋም በሚገልጥ ዐረፍተ ነገር ላይም “የጀርመን ዜጋ ከሌላ ጋር መጋባት ከእግዚአብሔር ፈቃድ የሚቃረን ነው” ሲል ያውጃል። የጀርመን ክርስትና” ዘረኝነት ራሱን የሚገልጠው በዋናነት በጸረ-ሴማዊነት (ሴማዊነትን በመጥላት) ነው። ስለዚህ በዶክትሪናቸው ውስጥ ጸረ-ሴማዊነት ተደጋግሞ ይንጸባረቅ ነበር።
496
3
"የትናንት ለዘብተኝንትና አድርባይነት ዛሬ በቅሎ ሞት አሳጭዶናል። የዛሬ እንቅልፍና ስንፍና ነገ ባዶ ያስቀረናል።" ንዋይ ካሳሁን
483
4
የመከራውን  ጥልቃት የማይረዳ ሕዝብ ሁሌም የጥቃት ዒላማ እንደሆነ ነው የሚቀጥለው።ትግል ቢጀምር እንኳ፦ 👉ለምን  እንደሚታገል በአግባቡ አይረዳም 👉ትግሉ በሐሰተኞች ተጠልፎ የ እንጀራ መብያ ይሆናል፣እንደ አንድ የሥራ መስክ ይቆጠራል 👉  የገዳዮች አገልጋይ ይሆናል
1 134
5
👆ይኽን ጽሑፍ ትኩረት ሰጥተን እናንብበው
733
6
ክራውስ የጀርመን ክርስትናን ለማስተዋወቅ ባደረገው ጥረት ጥቃቱ በብሉይ ኪዳን ብቻ ሳይገደብ “ኢየሱስም ቢሆን” [አምላካችን ክብር ምስጋና ይድረሰውና] አለ፡- “ኢየሱስም ቢሆን ሊገለጽና ሊቀርብ የሚገባው ከብሔራዊ ሶሻሊስት ፓርቲ ፍላጎት አንፃር ነው” አለ።  የኒዮርክ ታይምስ ጋዜጣ ክራዑስ “ወደ ጀግናው አርያናዊው ኢየሱስ መመለስ አለብን፣ ጀርመኖች ኢየሱስን ተዋጊ መሪ አድርገው መሳል ይገባቸዋል” ብሎ መናገሩን ጽፏል።  በንግግሮቹ “የጀርመን ክርስትና” አራማጆች የሞቀ ጭብጨባ ይለግሱት ነበር።  ክርስትና ዘረኞች ለክፉ ዓላማቸው መጠቀሚያ ሊያደርጉት ሲሞክሩ ምን ሊመስል እንደሚችል የክራዑስ ገለጻ አሳይቷል።  የተመረጡት አዳዲሶቹ “የጀርመን ክርስትና” መሪዎች አርያን ያልሆኑ ዝርያዎችን ከየመሥሪያ ቤቶች የማስወገዱን አሠራር በቤተ ክርስቲያንም ተገበሩት።  የመጀመሪያው የአርያን አንቀጽ “ዝርያው አርያን ያልሆነ ወይንም አርያን ካልሆነ ሰው ጋር የተጋባ ሰው ካህን አይባልም”  ይላል። ከዚያም ስዋስቲካን አንግበው የናዚን ፍላጎት የሚያስፈጽሙ “የጀርመን ክርስቲያኖች” የፕሮቴስታንት ቸርች ውስጥ ተልእኮ ይዘው በመግባት የናዚ ርእዮት መምህራን ሆነው በመስቀሉ ጀርባ ተደብቅው በክርስቶስ ፈንታ ለሂትለር ታማኝ ስለ መሆንና ለጀርመን ዝርያ ልዩነት ስለ መቆም፣ ዘረኝነትንና ጥላቻን አበክረው እንዲሰብኩ ይደረጉ ነበር። የጀርመን ብሔራዊ ሶሻሊስት ፓርቲን ክርስትናን የማጥፋት እቅድ ፊት ለፊት ቆመው የሚዋጉ አያሌ ጀርመናዊ ክርስቲያኖች ነበሩ። የጀርመን ፓስተሮችና ክርስቲያኖች ቡድን በአንድነት ሆነው በዘርና በብሔር ላይ ያተኮረውን “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ ተቃውመዋል። ከእነዚህ ተቃዋሚዎች መካከል አንዱ ዲይትሪች ቦንሆፈር ነው። የናዚን ሥርዓት የተቃወሙ ብዙዎች ሰዎች ቢኖሩም ቦንሆፈር የተቃውሞው ምልክት ሆኖ ወጣ። ቦንሆፈር የአርያን አንቀጽን የሚቀበል ክርስቲያን ሁሉ ከእውነተኛ ክርስትና የተለየና የሐሰት ክርስትና የሚከተል መሆኑን በኃይልና በቁጣ ያስተምር ነበር። በእንዲህ ዓይነት ጊዜ እውነተኛውን ክርስትና ለመጠበቅ ሲባል መሰደድና ከእነዚህ መናፍቃን መለየት እንደሚገባም በአጽንኦት አስተምሯል።    ለአርያን አንቀጽ መታወጅን ምላሽ የፓስተሮች የአደጋ ጊዜ ሊግ (Pastor’s Emergency League) ተመሠረተ።  የንቅናቄው መሪ የነበረ ፓስተር ማርቲን ኒሞለር (Martin Niemoller) የጀርመን ቤተ ክርስቲያንን ናዚፊኬሽን ይቃወም ነበር። ከዚህ ንቅናቄ ውስጥ የኮንፌሲንግ ቸርች ተወለደ። ቢያንስ ግማሽ ያህሉ የጀርመን ቸርች የናዚን መስመር የማስገባት (Gleichschaltung) ዶክትሪን ተቃውመዋል። ሰነዱ ሲነበብ የተቃውሞው መንፈስ በቃላቶቹ ግልጽ ይሆናል።  ቦንሆፈር የጀርመን አዋጅን “የደቀ መዛሙርትነት ዋጋ” (The Cost of Discipleship) በሚለው መጽሐፉ ውስጥ ሲገልጸው “ቤተ ክርስቲያን እንደ ብሉይ ኪዳን እስራኤል ብሔራዊ አንድነት ልትፈጥር የተሠራች ሳትሆን ከፖለቲካና አገር አጥር ውጭ የሆነች የአማኞች አንድነት ናት” ብሏል፡፡   በመጨረሻም ቦንሆፈርና ሌሎች ናዚን የተቃወሙ ሕይወታቸውን በመሥዋዕትነት ከፍለዋል።ከ1933-1945 ናዚዎች የፈጠሩት “የጀርመን ክርስትና” በአንድ በኩል፣ ነባሩ ፕሮቴስታንት ክርስትና (ኮንፌሲንግ ቸርች) ደግሞ በሌላ በኩል ያደረጉት ትግል ከባድና መራር ነበር፡፡ በ1945 ጀርመን በጦርነት ስትሸነፍ ፋሺዝም ፈጥሮት የነበረው “የጀርመን ክርስትናም” አብሮ ተሸነፈ፡፡ ኮንፌሲንግ ቸርች ደግሞ አሸናፊ ሆነ። ለኑፋቄው ንቅናቄ የሕጋዊነት ሽፋንና ሁለገብ ድጋፍ ሲሰጥ የነበረው የናዚ ፓርቲ ሲወድቅ አጋፋሪዎቹ አፋቸው ተዘጋ፣ ተበተኑም።  “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ እምነት በመንግሥታት ተስፋ ሰጭነት፣ በዘረኝነትና በብሔርተኝነት ጉዳይ ሲታወር ምን እንደሚከተል ጥሩ ማስተማሪያ ሆኖ  አልፏል። ይህን የኑፋቄ ጠባሳ የጀርመን ክርስቲያኖች የሚዘክሩት የክህደት ሁሉ ቁንጮ አድርገው ነው። “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ ክርስቲያኑን ከድባቴ በመቀስቀስ ከፍተኛ ሚና ተጫውቷል። የአገራችን አሁናዊ ሁኔታ በጀርመን ከተፈጸመው አንጻር ሲቃኝ ምን ይመስላል?  አሁን በአገራችን ያለው ሁኔታ በጀርመን አገር በናዚ ፓርቲ የተደረገውን የሚመስል ሆኖ ይታያል፡፡ አሁን በአገራችን በበተለይም ደግሞ ሁሉም የፓለቲካ ፓርቲና ነጻ አውጪ የራሱን ክርስትና እየፈጠረ ነው። የኦፒዲኦ እና የህወሀት በኦሮሚያና በትግራይ ቤተ ክህነት አቀንቃኞች ዝንባሌ ውስጥ ልዩ ኑፋቄ ተወልዷል። ክርስትናውን ለዘረኛ ፖለቲካ መገልገያነት የማመቻቸት ግብ ይዞ በመነሣት፣ የናዚ ጀርመን የፈጠረውን “የጀርመን ክርስትና” ዓይነት የብሔር ክርስትና (የኦሮሞ፣ የትግሬ፣ የሲዳማ ወዘተ) በሚል ለንዑስ ፖለቲካ-ወለድ ማንነት የሚመች ኑፋቄያዊ “ክርስትና” ለመፍጠር እየተሠራ ነው፡፡ ኦርቶዶክስን ለየብሔረሰቡ ፖለቲካ ለማስማማት ጥረት እየተደረገ ነው። መምህር ፋንታሁን ዋቄ
715
7
👆ከላይኛው የቀጠለ👇 ከቤተ ክርስቲያን የአይሁድ ዝርያ ያላቸውን ክርስቲያኖች የማግለሉ ሂደት ከናዚ እርምጃ ጋር እየተናበበ እርምጃ በእርምጃ እየተጠናከረ ሄደ። በ1935 ናዚ በኑረንበርግ አዋጁ አይሁድነትን የተለየ ዝርያ ተብሎ እንዲታወቅ አሳወጀ። ከኑረንበርጉ ሕግ በኋላ ብዙ “የጀርመን ክርስቲያኖች” የተጠመቁ አይሁዶች የሚያመልኩበት ቦታ የተለየ እንዲሆን መጠየቅ ጀመሩ።  የኑረንበርጉ ሕግ አይሁዶች በሕግ ከጀርመን ማኅበረሰብ የተገለሉ አደረጋቸው፡፡ በቤተ ክርስቲያን ውስጥም ተግባራዊ መደረግ ጀመረ።   ከ1935ቱ የኑረንበርግ ሕግ በኋላ “የጀርመን ክርስትናን” ለተፈለገው አዲስ ንቅናቄያቸው እንዲስማማ አድርገው የራሳቸው ኢየሱስ ለመሣል ሞከሩ።  ለዚህም “ኢየሱስ የአይሁድ ደም የለውም፣ ኢየሱስ አርያን (ጀርመናዊ) ነው” ብለው ደመደሙ። ንቅናቄው ትምህርቱ ተቀባይነት ያገኝ ዘንድ “ኢየሱስ በገሊላ ከሚኖሩ አርያን ጎሣ የተወለደ ነው” እያሉ እንደ ኢማኑኤል ሂንሪሽ (Emanuel Hirsch) እና ሁስተን እስቲዋርት (Houston Stewart) ያሉ ምሁራን ማስተጋባት ጀመሩ፡፡ የጀርመን ክርስትና የነገረ ክርስቶስ ማዕከሉን “ኢየሱስ ሴማዊ አይደለም” በማለት ብቻ ሳይገደብ “ኢየሱስ ዋናው ጸረ-ሴማዊ ነው” በሚል እሳቤ ላይ አደረገ።  በንቅናቄው ውስጥ የሚሳተፉት ብዙዎች የሂትለር ርእዮት ፕሮፓጋንዳ አባት የሆነውን የዮሴፍ ጎቤልስን (Joseph Goebbels) “ኢየሱስ የመጀመሪያው የአይሁድ ጠላት ነው” የሚለውን ጥሪ የተቀበሉ ነበሩ።  ዘረኝነትን ከእምነታቸው ጋር ለማስማማት ሲባል “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ አይሁዳዊ የሆነውን የመጽሐፍና የአስተምህሮ ይዘት ሁሉ ከክርስትናቸው ለማጽዳት ሞከሩ። ከዚህ የተነሣም አንዳንዶቹ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትን ኢቀኖናዊ ናቸው ብለው ሲክዱ  ሌሎቹ ደግሞ የብሉይ ኪዳንን ቀኖናዊት ሳይክዱ ጸረ-ሴማዊነታቸውን እንዲደግፍላቸው በማድረግ በራሳቸው መንገድ አመሰቃቅለው ይጽፉትና ይተረጉሙት ነበር። ሌሎች ደግሞ ጸረ-ሴማዊ አቋማቸውን ለማጠናከር ብሉይ ኪዳንን የሚጠቅስ ጌታ ለአይሁድ እውቅና የሰጠባቸውን የሐዲስ ኪዳንን ጥቅስ ሁሉ እያስወገዱ ወንጌልን እንደ አዲስ ጽፈዋል።        ሴማዊነትን መጥላትንና መጸየፍን ሁሉንም ጀርመናዊ በአንድነት የሚያሰባስብ የጋራ አጀንዳ አደረጉት፡፡ ኦቶ ብሮክልሸን (Otto Brokelschen) ይህን “የጀርመን ክርስቲያን” አቋም እንዲህ ሲል ይገልጸዋል፡- “የጀርመን ብሔራዊ የክርስቲያኖች አንድነት ለጀርመን ቤተ ክርስቲያን ባዕድ ናቸው ተብለው የሚታመንባቸውን ማንኛውንም ትምህርትና የአይሁድ የሚመስሉትን ነገሮች ሁሉ ከቤተ ክርስቲያን ጠራርጎ ማጽዳት አንድነትን የሚፈጥር ድል አድርገው ወስደውት ነበር።”  ጀርመናዊ አንድነት መፍጠር በሚል ስም ማንኛውንም ዶግማና አስተምህሮ ሙሉ በሙሉ ተካደ።    “የጀርመን ክርስቲያኖች” በአይሁድ ላይ ሉተር የነበረውን ጥላቻ በሁሉም ክርስቲያኖች ላይ እንዲኖር እጅግ ከመናፈቃቸው የተነሳ በ1940 ሉተርን ጠቅሰው እንዲህ ሲሉ በእምነት መጻሕፍት ደረጃ አቅጣጫ ይሰጡ ነበር፡- “የአይሁድን ምኩራቦች በያሉበት አቃጥሏቸው፣ በእሳት ለማቃጠል አስቸጋሪ የሆኑትን ደግሞ ቆሻሻ ከምሩባቸው።”  ያለዚህ ረዥም ታሪካዊ መሠረት “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ መቆምም መኖርም አይችልም ይሉ ነበር።    በሌላ በኩል ሂትለር የጥላቻና ዘር የማጥፋት ዝንባሌ መነሻው የፐሮትስታንት መሥራች የሉተር አስተምህሮና ድርጊቶች ነበሩ። ሉተር በዘመኑ ለሕዝቡ አቅጣጫ ሲሰጥ “አይሁዶችና ውሸቶቻቸው /"On the Jews and Their Lies" በሚል ርዕስ በ1543 እ.አ አ ጸረ አይሁድና  እና ጸረ ሴመቲክ ጽሑፍ ጽፏል።  ሉተር በጽሑፉ አንዲህ ይላል “የአይሁድ ትምህርት ቤቶቻቸው፥ ምኩራቦቻቸውና የንግድብ ቦታቸው በእሣት መቃጠል አለበት”፥ የፈሎት መጽሐፍቶቻቸው መውደም ይገባቸዋል፥ ቤቶቻቸውና ያለቸው ሀብት ሁሉ መወረስ አለበት። ሉተር ለአይሁድ ምንም አይነት ሐዘኔታ፥ የሕግ ከለላና ርኅራኄ ማድረግ አይገባም። እነዚህ መርዞች አካባቢውን ሁሉ ስለበከሉት  ("these poisonous en”venomed worms" ) ተጭነው ወደ አስገዳጅ የጉልበት ሥራ ስፍራ መታቀብ ወይንም ለዘላለም ከዚህ አገር ተጠርገው መባረር አለባቸው።    እንዲሁም በአይሁዳውያን ላይ አልቂት እንዲታወጅ ጥሪሳያቀርብ “እንዚህን በጅምላ መርዞ አለመጨረሳችን የእኛ ስህተት ነው/  "[W]e are at fault in not slaying them" ይላል . ይህ ጽሑፍ  ከ500 ዓመታት በኋላ ለተነሳው ሂትለርና ሌሎች የጸረ አይሁድና ጸረ ሱሜቲክ ንቅናቄዎችን መሠረት ሆኗል።  ሂትለር በተነሳበት ዘመን መጽሐፉ በአስተሳሰቡ ደጋፊዎችና በፓርቲው  ዘንድ በብዛት ተሰራጭቶ ይነበብ ነበር።  በ2ኛው ዓለም ጦርነት መጽሐፉ በሰልፈኞች እጅ ተይዞ ይታይ ነበር፥ ምናልባተም ለአይሁድ እልቂት ዋና ሞተር የሆነው የዚህ የሉተር አስተምህሮ እንደሆነ ይታመናል።   ለተጨማሪ ጥናትና ንባብ ---  “የጀርመን ክርስትና” ኑፋቄያዊ ንቅናቄ ለናዚ ፓርቲ የፕሮቴስታንት ቸርችን ሰብሮ “ናዚያዊ ፕሮቴስታት” በመፍጠር የራሱ ዓላማ ማስፈጸሚያ ማድረጉ መንገዱን ቀላል አደረገለት። በዚህ ሂደት ራሳቸው ቸርቾቹ ወንጌላውያንና መምህራን ከናዚ ፕሮፓጋንዲስቶች ባልተናነሰ አገልጋይ ሆነው ተገኙ። ስለዚህ ለናዚዎች ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት ከመታገል ይልቅ በመቀየር (ውስጧ ገብቶ በመቆጣጠርና ሪፎርም በማድረግ) መጠቀሙ ትርፋማነቱ ልቆ ተገኘ።  በዚህ ስሌት መሠረትነት ሂትለር የቻንሰለርነት ሥልጣኑን ባገኘ በሰባት ወር ውስጥ ሐምሌ 23፣ 1933 በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ምርጫ እንዲካሄድ ጥሪ አደረገ። ምርጫው የተፈለገው ለናዚ ፓርቲ ምቹ የሆነች ጀርመናዊት የሬይክ ቸርች (Reichskirche - Reich Church) ለመመሥረት ነበር። በጥንቃቄ በታቀደ ስልት ምርጫው ለሂትለር ግብ እንዲያገለግል ተደርጎ ተከናወነ። የቦንሆፈር ግለ ታሪክ ጸሐፊ ኤሪክ ሜታክሳስ (Eric Metaxas) የሂትለርን የቸርች ምርጫ እንደሚከተለው ያጠቃልለዋል፡- “በምርጫው ሂደት ላይ ምንም አይነት አሉታዊ ተጽእኖ ለማሳደር የሚሞክር ሁሉ በጀርመን ክርስትና ንቅናቄ “በአገር ክህደት” ይከሰሳል። ትርጉም ያለው ተቃውሞ እንዳይደራጅ የምርጫ ጥሪው በተላለፈበት ቀን እና በምርጫው ዕለት መካከል የነበረው ጊዜ አንድ ሳምንት ብቻ ነበር።”  በሂትለር በተመረጡ ሰዎች አማካይነት ከ28ቱ የፕሮቴስታንት አህጉረ ስብከቶች ከሦስቱ በስተቀር ሁሉም ቸርቾች ከምርጫው በኋላ በናዚ ርእዮትና መርሆዎች መስመር ገቡ።    እዚህ ላይ በአገራችን “ሃይማኖቶቹ ሁሉ ከኦሮሙማ በታች ናቸው”   በሚል የብልጽግና መንግሥት አሠራር የኦሮሞ፥ የትግራይ ወዘተ የዘር ሲኖዶስ ለመፍጠር ብያኔ ተሰጥቶ ሰው እስኪጨፈጨፍለት የደረሰ ተመሳሳይ ጉዞ መኖሩና ማስታወስ ለማገናዘብ ይጠቅማል።  የሂትለር እቅድ እንደታሰበው ተሳካ። የጀርመን ቸርቾች የተዋረዳዊ መዋቅራት አመራር አዲስ በተመረጠው “የጀርመን ክርስትና” መሪዎች እጅ ወደቀ። ከዚያም ዋና ሥራቸው የናዚን ርእዮተ ዓለም ማስተማር ሆነ። የተለያዩ ሰልፎችና ንግግሮችም ይደረጉ ጀመር፡፡ ከራውስ የተባለ ተናጋሪ “በክርስትና ውስጥ ያለው የአይሁድ ተጽእኖ ተቀባይነት የለውም”፣ “ብሉይ ኪዳን፣ ሐዋርያ ጳውሎስ፣ የመስቀል ምልክት ሁሉ በናዚ ርእዮት መሠረት ተቀባይነት የላቸውም”  ሲል ሃያ በሺህ ሰዎች ፊት በአደባባይ ተናገረ። ይቀጥላል..
527
8
በኢትዮጵያ ምድር እየተፈጸመ ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል እስከ የዘር ቤተ ክህነትና ዘር ቸርች ምሥረታ የ6ሚሊየን አይሁዶችን ዘር ካጠፋው ከናዚ ጀርመን ፓርቲ የተቀዳ ነው ። '"አጭር ዐለም አቀፋዊ ታሪካዊ ዳሰሳ" 1. የናዚ ፓርቲ በጀርመን አገር የፈጠረው “የጀርመን ክርስትና” አጭር ዳሰሳ 53121933 ዓ.ም. (እ.ጎ.አ.) ለጀርመን ትልቅ የታሪክ እጥፋት ዓመት ነበር። ይኽ ዓመት በአዶልፍ ሂትለር የሚመራው የናዚ ፓርቲ የጀርመንን መንግሥት መቆጣጠር የቻለበት ነበር። ሂትለር ሥልጣን እንደ ያዘ መጀመሪያ ካደረጋቸው ነገሮች አንዱ ጀርመናዊ “ክርስትና” መፍጠር ነበር፡፡  ፓርቲው በሂትለር እየተመራ ወደ ሥልጣን በመጣ በአጭር ጊዜ ውስጥ “ሁሉን ወደ መስመር ማስገባት” ግሌይሽሻልቱንግ - Gleichschaltung (bringing everything into line) የተሰኘ ፖሊሲ አስተዋወቀ። የፖሊሲው ዓላማ የጀርመንን ማኅበረሰቦች ልዩ ልዩ ማንነቶች ሁሉ ከፓርቲው ርእዮተ ዓለም ጋር ስምሙ እንዲሆኑ ማድረግ ነበር፡፡ በሌላ አነጋገር መላውን የጀርመን ማንነት ናዚያዊ (ናዚፋይ) ማድረግ ማለት ነው። የፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያንም ናዚያዊ ከሚደረጉት ክፍሎች መካከል አንዱና ዋነኛው ነበር። ናዚዎች ለዓላማቸው ማስፈጸሚያ ሲሉ የፈጠሩት አዲሱ ሃይማኖት “የጀርመን ክርስትና” ተብሎ ይታወቃል፡ ይህ “የጀርመን ክርስትና” የጀርመንን ዜጋ ከሌሎች የሰው ልጆች ሁሉ ልዩ እንደሆነና እንደሚልቅ ለማሳየት የግድ አዲስ አስተምህሮ በማስፈለጉ የተፈጠረ ነው። ስለዚህም ልዩ የጀርመን ዝርያን (German Volk) ለመስበክ የተመቸ “የጀርመን ክርስትና” የተሰኘ አዲስ ኑፋቄ ተወለደ።  ስለዚህ “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ ለአዲሱ የናዚ ፓርቲ ርእዮት ማለትም የጀርመን ንጹሕ ደምና የላቀ ዘርኝነትን ማዕከል ያደረገ በቀዳማዊው ፕሮቴስታንትም ሆነ በካቶሊክ ዘንድ ተቀባይነት የሌለው ነበር። ምክንያቱም የክርስትና አስተምህሮ ከናዚ የጭካኔና ከጥንካሬ አስፈላጊነት አስተምህሮ ጋር ስለሚጋጭ እርሱን የሚመስል አዲስ “ክርስትና” መፍጠር አስፈለጋቸው፡፡ ይህ የናዚዎች ትርክት (ቴሲስ) የፕሮቴስታንት ቸርቾች የናዚ ርእዮት አቀጣጣይ እንዲሆኑ በታቀደው መሠረት በፍጥነት ተሠራጨ። ይህን የናዚ ቤተ ክርስቲያንን የመጥለፍ ዘመቻ የሚቃወሙ የክርስቲያን ንቅናቄዎች በጀርመን ውስጥ ተፈጠሩ። ይህ ኑፋቄ በፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መከፋፈልን ፈጠረ። ስለዚህ በፕሮቴስታንት ቸርች ውስጥ በአንድ በኩል ራሳቸውን ለናዚ ፓርቲ ተልእኮ አስፈጻሚነት ባዘጋጁት “የጀርመን ክርስትና” እና በሌላ በኩል ደግሞ ክርስትናን ከናዚ መጫወቻነት ለመከላከል በሚታገሉት “ኮንፌሲንግ ቸርች” መካከል ትግል ተጀመረ።ሪቻርድ ኢስቲግማነ-ጋል የተባለ አጥኚ “ቅዱሱ መንግሥት፡ ክርስትና በናዚ አረዳድ - The Holy Reich: Nazi Conceptions of Christianity) በሚለው መጽሐፉ እንደ ገለጸው፣ “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ ግብ የፕሮቴስታንት ክርስትናን በጸረ-ክርስትና በማጥመቅ ከእናት ፕሮቴስታንት አስተምህሮ መለየት ነበር። “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ ልሂቃን ሂትለርን ለማስደሰት ሲጣደፉ ቀደም ሲል ያልነበረ “ለጀርመን ክርስትና” ብቻ ልዩ የሆኑ አዳዲስ ኑፋቄዎችን በአስተምህሮዎቻቸው ማምረት ጀመሩ።  በናዚዎች የተፈጠረው አዲሱ “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ ሲፈጠር አንደኛው መሠረታዊ እሳቤው ዘረኝነትና በዋናነት ደግሞ የሴማዊነት-ጥላቻ (Anti-Semitism) ነበር፡፡ “የጀርመን ክርስትና” አይሁዳዊ ዝርያ ያላቸውን ክርስቲያኖች ሁሉ እያደነ ከቸርችና ከማናቸውም ክህነታዊ ተሳትፎ ሁሉ ያባርራቸው ነበር።  “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ የመጨረሻ ግብ ጀርመን እንደ አገር ከሌሎች የማትጋራው የሆነ የራሷ ዓይነት ብቻ የሆነ “ጀርመናዊ ክርስትና” መፍጠር ነበር። “የጀርመን ክርስትና” ልዩ ኑፋቄ የተፈለገው አዲሱን ጀርመን ለመፍጠር የግድ አስፈላጊ ቅድመ ሁኔታ ነው ተብሎ ስለታመነ ነበር፡፡ አንዳንድ የጀርመን ታሪክ ምሁራን ልዩ-ጎዳና (Sonderweg) የሚለውን ጽንሰ ሀሳብ እጅግ በመለጠጥ የጀርመን ታሪክ ከአጠቃላይ የአውሮፓ አገራት ሁሉ ጎዳና የተለየ ነው ወደሚል ደርሰው ነበር።  “የጀርመን ክርስትና” ማዕከላዊና መሪ የሆነው ዶክትሪናቸው የጀርመን ዝርያ (German Volk) ጉዳይ ነበር። “የጀርመን ክርስትና” አቀንቃኞች መስቀልን ከቤተ ክርስቲያን ማዕከላዊ ትኩረትነት አንስተው የእምነታቸውን ዋና ማዕከል በጀርመን ዘረኝነት ተኩት። ናዚ ፓርቲም፣ “የጀርመን ክርስትናም” ሁለቱም ንቅናቄዎች የተመሠረቱት በዘርና ዘረኝነት ላይ ነበር። ይህንም የነገረ መለኮት ምሁሩ ካርል ባርዝ (Karl Barth) ሲገልጸው “የጀርመን ክርስትና ከመጽሐፍ ቅዱስ ቀጥሎ ሁለተኛው መገለጥ የጀርመን ዝርያ ልዩ ነው ብሎ ማመኑ ነው” ብሏል፡፡   ዘረኝነት” በጀርመን ክርስትና” ውስጥ የሁሉ ጉዳይ ማጠንጠኛና መወሰኛ ሆነ። “የጀርመን ክርስትና” አቀንቃኞች የዘር ሕጎችን በእምነታቸው ውስጥ ከፍ አድርጎ መደገፍ ከእግዚአብሔር የተጣለባቸው የመገለጥ አደራ እንደሆነ ይሰማቸዋል። በጀርመን ክርስትና ቸርች 10 ነጥቦች ያለው መመሪያ ሲያሳትሙ ማዕከል ያደረገው ዘረኝነትን ነበር። ሰባተኛው ነጥብ እንዲህ ይል ነበር፡- “እግዚአብሔር ዝርያን፣ አገርን፣ ብሔራዊ ሕጎችን እንድንጠብቅ አደራ ሰጥቶናል። . .ስለዚህ የዝርያ መቀላቀልን አጥብቀን መቃወም አለብን።”  እንዲሁም ነጥብ ዘጠኝ፡- “አይሁድ ለዝርያችን ጥራት ከፍተኛ አደጋ ሆነው ይገኛሉ። ተልዕኳችን እንግዳና ባዕድ የሆነ ደም ወደ ዘራችን እንዳይገባ መጠንቀቅና መጠበቅ ግዴታችን ነው። መዳቀል ደማችንን የመበከል እድል ስለሚፈጥር የአይሁድን የጀርመን ዜግነት የሚፈቅድ ሕግን እንቃወማለን። በጀርመንና በተለይ በአይሁድ መካከል የሚደረግ ጋብቻ ፈጽሞ ሊከለከል ይገባል” ይላል፡፡  በ1933 በታተመው The Handbook of the German Christians በሚል  የጀርመን ክርስትናን አቋም በሚገልጥ ዐረፍተ ነገር ላይም “የጀርመን ዜጋ ከሌላ ጋር መጋባት ከእግዚአብሔር ፈቃድ የሚቃረን ነው” ሲል ያውጃል።  “የጀርመን ክርስትና” ዘረኝነት ራሱን የሚገልጠው በዋናነት በጸረ-ሴማዊነት (ሴማዊነትን በመጥላት) ነው። ስለዚህ በዶክትሪናቸው ውስጥ ጸረ-ሴማዊነት ተደጋግሞ ይንጸባረቅ ነበር። በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚታየው የጸረ-ሴማዊነት ባህል በአይሁዶች ላይ በሚፈጸም አካላዊ ጥቃት ሳይቀር ይገለጥ ነበር። “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ አራማጆች የጀርመንን ቤተ ክርስቲያን ከአይሁድ ተሳትፎ በማጽዳት የአንድ ዝርያ ቤተ ክርስቲያን በመፍጠር ላይ ተፋጠኑ፡፡ ንቅናቄው “የጀርመንን ክርስትና” ሕይወት ከአይሁድ ተጽእኖ ነጻ ማውጣት በሚቻልበት መንገድ ላይ የምርምር ኢንስቲቲዩት መሠረተ።  “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ  አባሎቻቸውንና ዝርያቸውን በአይሁድ ዝርያ “ከመቆሸሽ” ለመከላከል ከፍተኛ ጥንቃቄ ያደርጉ ነበር። ለዚህም “የጀርመን ክርስትና” ንቅናቄ አባልነትን ለማግኘት ወሳኙ መስፈርት የጀርመን አርያን ዝርያ መሆኑ በመሐላና በምስክርነት መረጋገጥ እንዲሆን አድርጓል።  በ1935 አዲስ የውጊያና የእምነት ንቅናቄ (Combat and Faith Movement) በሚል የሚታወቀው በጀርመን ክርስትና ውስጥ የአባልነት መስፍርት ተመዝጋቢው “እኔ የአርያን ደም አለኝ፣ ሁለቱም ወላጅ እናት አባቴ እና አያቶቼ የአርያን ንጹሕ ደም ያላቸው ናቸው” የሚለውን መመስከርና መፈረምን ያስገድድ ነበር። 
590
9
https://vt.tiktok.com/ZS9S6Gh9m3vdd-uzeLj/
637
10
ዋጋ እያስከፈለን ያለው የገዳዮቻችን ጥንካሬ ሳይሆን የእኛ ስንፍና ነው
792
11
ይኽች ቤተ ክርስቲያን ምን ብትበድል ነው በዚህ ልክ የዙመትንባት? የመነኮሳትን ልብስ ለ Fashion Show🤔+1
ይኽች ቤተ ክርስቲያን ምን ብትበድል ነው በዚህ ልክ የዙመትንባት? የመነኮሳትን ልብስ ለ Fashion Show🤔
911
12
No text...
906
13
አንተስ? አንቺስ?
አንተስ? አንቺስ?
789
14
ኦርቶዶክሳዊነትን ማስቀጠልየምንችለው እንደ ቀደምት አባቶቻችን ኦርቶዶክሳዊ ልቡና፣ኦርቶዶክሳዊ ማያ፣ኦርቶዶክሳዊ መለኪያ፣ኦርቶዶክሳዊ ኅብረት ሲኖረን ብቻ ነው።
1 442
15
ይኽን ስንል በጥላቻ ተነሳስተን የምንጽፍ የሚመስለው አይጠፋም እኮ ።ከነቃህ ንቃ ራስህን አድን።አሊያ ግን ትሰለቀጣለህ።
ይኽን ስንል በጥላቻ ተነሳስተን የምንጽፍ የሚመስለው አይጠፋም እኮ ።ከነቃህ ንቃ ራስህን አድን።አሊያ ግን ትሰለቀጣለህ።
1 463
16
ማያ መለኪያህ ሲበላሽ ሐሰተኛ ፖለቲከኞች እንደ አንሻጉሊት ነው የሚጠቀሙብህ ።ሲነዱህ መነዳት ሲያስጮውህ ዝም ብሎ መጮህ። ኦርቶዶክስ ሆኖ በዚህ ልክ መዝቀጥ ኑፋቄ ነው።
939
17
No text...
974
18
እሄን ማስታወቂያ ሪፖስት አርጉልኝ
919
19
https://www.tiktok.com/@thtna5.28/video/7682508187559365908?_r=1&u_code=dc0igbil8j4d9c&preview_pb=0&sharer_language=en&_d=eig88kle5kb76j&share_item_id=7682508187559365908&source=h5_m&timestamp=1788729040&user_id=6816223619876062214&sec_user_id=MS4wLjABAAAA2b1LA_Nq7OHWEpPPXWpUS_ZELHN6fm4n4GQGFyIQ3itcJJAVcYYP2VQdKQJmxiQ-&social_share_type=0&utm_source=telegram&utm_campaign=client_share&utm_medium=android&share_iid=7681934865550755605&share_link_id=7c4dbdf1-2cd8-4792-b150-2a4c1a6cf7b8&share_app_id=1233&ugbiz_name=MAIN&ug_btm=b8727%2Cb2878&sp_root_share_link_id=7c4dbdf1-2cd8-4792-b150-2a4c1a6cf7b8&link_reflow_popup_iteration_sharer=%7B%22click_empty_to_play%22%3A1%2C%22dynamic_cover%22%3A1%2C%22follow_to_play_duration%22%3A-1.0%2C%22profile_clickable%22%3A1%7D&panel_source_v2=share_panel&share_enter_from=personal_homepage&item_author_type=1&enable_checksum=1&sp_level=1&sp_root_u=dc0igbil8j4d9c&sp_root_d=eig88kle5kb76j
979
20
እውነት ነው ያስብላል የጽዳት ሠራተኛ ሆኖ ለመቀጠር 80ሺ የሚከፍልበት ሀገረ ስብከት ነው።እሱም ቢሆን ዘመድ ሲኖርህ ብቻ ነው።ምን ይኽ ብቻ የ ጧፍ ሰብሳቢ፣የጧፍ ምክትል ሰብሳቢ፣የጧፍ ጸሐፊ እያሉ
እውነት ነው ያስብላል የጽዳት ሠራተኛ ሆኖ ለመቀጠር 80ሺ የሚከፍልበት ሀገረ ስብከት ነው።እሱም ቢሆን ዘመድ ሲኖርህ ብቻ ነው።ምን ይኽ ብቻ የ ጧፍ ሰብሳቢ፣የጧፍ ምክትል ሰብሳቢ፣የጧፍ ጸሐፊ እያሉ ዘመዶቻቸውን ይሰበስባሉ።እነ አቡን ሳዊሮስም ሀገረ ስብከቱን የተቆጣጠሩት ብልሹ አሠራርንለማስወገድ ሳይሆን የእኛ ነው የሚሉትን ለመሰግሰግና ለመዝበበዝ ነው።የመብያ ቤተ ክርስቲያን።
1 022