💙..ነጠብጣብ ✨🧩
Open in Telegram
✨ትዝታማ አለሽ የለኝም ብትይኝ እኔም አላምንሽም በህይወት መንገድ ላይ ተራምደሽ ሳታልፊ ዛሬ ላይ አልቆምሽም፨ ህይወት ያለ ታሪክ ቀን ያለ ጨለማ መች ቶሎ ይመሻል ሰዉ ስለሆንሽ ብቻ ለሰዉ ምታወጊዉ ቅፅበት ይኖርሻል፨ ትዝታ አለሽ?አዉጊኝ ትዝታ አለኝ!ላዉጋሽ ..እንዲህ ብናወራስ...ቅፅበታት እናዉጋ.. የልብ ንግግሮችም አይታጡም..ግቡ💙 ለአስተያየታችሁ @AnchinayehuGebrie
Show more2 612
Subscribers
+124 hours
+47 days
+5630 days
Posts Archive
2 612
ታስሬ ነበር💔
©Adhanom Mitiku
የሚያዉቁኝ ሰዎች ሁሉ "ታስሮ ስላልጠየቅነው ነው የተቀየረብን" ይላሉ::
እውነታቸውን ነው ተቀይሬያለሁ....... ተቀይሜያቸው ግን አይመስለኝም
ህይወቴ ውክብክብ ያለ ነበር ። የጓደኞቼ ብዛት የትየለሌ የሚባል አይነት ነው። ስልክ ሳወራ ነው የምውለው ።
ሁሉም የማወራው ስልክ አንገብጋቢ፣ አስፈላጊ ይመስለኝ ነበር ....
የሚሰማኝን የምነገራቸው፣ የሚሰማቸውን የሚነግሩኝ ፣
ተባበሩኝ የምላቸው ፣
ተባበረኝ የሚሉኝ ፣
ቀልድ የምናወራ፣
በርታ በርታ የምንባባል፣
አጀንዳዎችን የምንተነትን ፣ የማባብላቸው ፣
ያልፋል የሚሉኝ ሰዎች ጋ ስደዋወል የምውል ሰው ነበርኩ ።
እቅድ በየቀኑ አወጣለሁ......
ሼልፌ ላይ ማንበብ ያለብኝ መፅሀፎች፣
ጀምሬ የተውኩት ስዕል፣
የሆነ ቀን ይጠቅመኛል ብዬ ያኖርኳቸው ዶክመንቶች፣
እስክገዛው ድረስ 'አንገብጋቢ ነው' ያልኩት ከገዛሁት ሳምንት በኃላ ችላ ያልኩት እቃ....
ቤቴ ብዙ ነገሩ ለመስራት ባዘጋጀኋቸው፣ ጀምሬ በተውኳቸው እና እንዳሉኝ በዘነጋውት ነገሮች ተሞልቷል....
ከምሰራው የምሞክረው ይበልጣል ፣ ከምተገብረው የማቅደው ይበዛል፣
ጥሩ ሰው ለመባል የምጥረው ጥሩ ከማደረገው ይበልጣል.....
እፊቴ ለሚያብራራ ሰው ሳይገባኝ አንገቴን የምነቀንቀው፣ ስለማከብረው ብቻ ሲቀልድ የውሸት የምስቀው ይበዛል.....
ታሪኩን ለሚነግረኝ ሰው መወገን ግዴታ ይመስለኛል!!!
ውሎዬ ሁሉ perform በማድረግ የታጀበ ነበር !!
ደንገት ባልሰራሁት ወንጀል ተጠርጥሬ ዘብጥያ ወረድኩ ።
እስር የመጀመርያዬ ነበር…. ፖሊሶቹ ሲወስዱኝ እንደሚረሸን ሰው ነው ልቤ ላይ የተሰማኝ ፍርሃት .....
እስርቤት የመጀመርያ ሶስት ሳምንት ጠያቂዎቼ በዙ። ቀን ሲጨምር ስድስት ሰዎች ብቻ ቀሩ..... ቀን ሲጨምር አምስት ሰዎች ብቻ ፀኑ
ሶስት ቤተሰቤ ሁለት ጓደኞቼ ።
እውነት ነው ህይወት አይሞላም ቅድሚያ የሚሰጡት ብዙ ጉዳይ አላቸው ።
በሆነ በተከለለ አጥር ውስጥ ከድብርት ጋ ተያየን...
ከድብርቴ ስወጣ እርግት ስል ታውቆኛል ።
ከ 11 ወር በኋላ ተፈታሁ።
ስፈታ ከዚ በፊት የኖርኩበት መንገድ ተቀይሯል። ዋናዬን ለየሁ!
ጨለማው ውስጥ ያገኘሁት እኔ ያሳዝን ነበር….
ሰነፍ ነበር ጠንካራ አልነበረም….
የዋህ ነበር ስሜቱን ዋጥ ማድረግ …. የተሰማውን አለመናገር አይችልም ነበር ።
ንፁህነቴ ተረጋግጦ ከእስር ስወጣ የድሮ ማንነቴ ሞቶ ነበር።
ከእስር ስወጣ አንድም የተቀየመኩት ያለ አይመስለኝም …የድሮ እራሴን ከመታዘብ ውጪ።
ከእስር ስወጣ ስገባ የነበርኩትን እኔን ትቼው ነው የወጣሁት
እራስን እንደመቀየም አይነት ከባድ ስሜት ያለ አይመስለኝም !!
ካልገመቱት እውነታ ጋ እንደመፋጠጥ አሳዛኝ ነገር የለም!
ጭንቅላት ውስጥ የፈጠሩትን አለም እንደማጣት አይነት ህመም የለም !
አክብደው የሚያዩትን ነገር ተራ ሆኖ እንደማግኘት ግራ የሚያጋባ ነገር የለም!
አውቀዋለሁ ያሉትን ነገር አለማወቅ አይነት አስፈሪ ነገር የለም !
እስርቤት ብቻዬን ስቆዝም በመታሰሬ አዝኜ መስሏቸው ነበር። መጀመርያ ሰሞን ነበር ባልሰራሁት መታሰሬ ያሳዘነኝ….ስቆይ ያስደነገጠኝ የመጣሁትን መንገድ ስመለከት ነው ።
የኖርኩትን ህይወት ሰከንድ ሳይቀር መዝግበዉ እንደሰጡኝ አይነት ነው ራሴን አገላብጬ ያየሁት ....
የማይረባ ማንነታችንን እርቃኑን ለመጀመርያ ግዜ ማየት እንዴት ያሳዝናል!!
ከእስር ስወጣ ሌላ ሰው ሆኜ ነበር ።
ከዚህ ሁሉ በኃላ …… ከመታሰሬ በፊት የነበረውን እኔን
ዋስ ሆኖ ማስፈታት ማን ይቻለዋል ?!!
2 612
Repost from Dildiy - (ድልድይ)
😵💫
✨ የዓመቱን የመጨረሻ እሁድ እንዴት ለማሳለፍ አቅዳችኋል?
ፍልስፍና፣ በተለይም የሩቅ ምስራቅና ዐፍሪካዊ ነጽሮተ ዓለም የስራዎቹ ማጠንጠኛ በማድረግ የምታውቁት ደራሲና ገጣሚ O' Pulto (ኦታም ፑልቶ) በ 92ተኛው የአውደ ፋጎስ መርሃግብር ላይ እንገናኝ ብሏችኋል...
በሙያ Landscape Architect (የመልክዓ ምድር ነዳፊ) የሆነው ደራሲው በዚህ ዕለት ሁለት አዳዲስ መፃሕፍቱን ያስተዋውቃል...
🤩 “ዑቡንቱ ዕና ፑልቶ” እና “የፕሌቶ ኃጢአት”
መፃሕፍቱ ለማስተዋወቅ የሚሞክሩት ዐብሮኛዊ ፍልስፍና መልክዐምድርን እንደ ቅኔ ያያል... ቅኔ ደግሞ የተለያዩ ነበባዎችንና ትርጓሜዎችን ይፈቅዳል...
እናም ይጠይቃል....
❓ የቤተክርስቲያን ሥነ-ዕነጻ እንደመንፈሳዊ ጉዞ ካርታ ሊነበብ ይችላል?
❓ የግል መንፈሳዊ ጉዞን ብቻ ሳይሆን የሰው ዘርን የሥልጣኔ ጉዞ ዕምርታዎችንስ ሊያሳይ ይችላል?
ዝግጅቱ - የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናትን ክበባዊ የቦታ አወቃቀሮችን እንደግላዊ የመንፈሳዊ ንቃት ካርታ፣ እንደ ሰው ዘር ሥልጣኔያዊ ዕመርታ ደረጃዎች እያሰናኘ ያቀርባል... በዐፍሪቃዊው ፍልስፍና ውስጥ የሚኖረውን መሠረታዊ ቦታም ባጭሩ ያስቃኛል...
🔔 በነገራችን ላይ...
መድረኩ በዐፍሪቃ ዕጣፈንታ ቅኔያዊ ቅኝት፣ እና በፍልስፍናዊ ዕንስልስላት አማካኝነት በቅርቡ የሚጀመረውን ዐለምዐቀፍ የዐፍርቃ ፍልስፍናዊ ንቅናቄ በጋራ እንድንጀምረውና እንድንመራው ጭምር ይጋብዛል...
በተለይ ደግሞ - ለወጣት ጸሐፍት፣ ስክሪን ራይተርስ፣ የፊልም ባለሙያዎች፣ የባህል አዋቂዎች፣ እና የቴክኖሎጂ ሰዎች ለዓመታት የሚዘልቁ ልዩ ዕድሎችን ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተዋውቃል...
🔑 በቦታው ተገኝታችሁ የውይይቱና የዕድሎቹ ተሳታፊ ሁኑ።
📩 ይህን መልዕክት ለወዳጅዎ ያጋሩዋቸው
____
🗓️ ቀን - ዕሁድ - ጳጉሜ 01/2018
⏰ ሰዓት - ከቀኑ 8:00 ሰዓት
📍 ቦታ - ወመዘክር
____
የደራሲውን ስራዎች ለመከታተል ይህን አዲስ ገጽ ይቀላቀሉ ⬇️
https://t.me/OPultoSinkneh
2 612
Repost from ቢራቢሮ🦋.......(ሰadi)
ስወድ አስቸጋሪ ነኝ! ያለኝን ሁሉ ነገር ሰጥቼ እንደሰጠሁት እንዲሰጡኝ እጠብቃለሁ።
በአጋጣሚ ህይወቴ ውስጥ የገባ ሰው የኔ ሰው ሆኖ ይመዘገባል....ያኔ ሀላፊነቱ እንዳለብኝ ይሰማኛል።
በየእለቱ ፍቅርን የምሰብ፥ በየእርምጃዬ ለመኖር ምሞክር ብሆንም በልኩ ይሁን ማለትን ከመንገዴ ተምሪያለሁ።
መኖር ቆንጆ ነገር ነው! ከሌሎች ጋር ተዋዶና ተሳስቦ መኖር ደሞ ይበልጥ ውብና ተወዳጅ ያደርገዋል።
ከምንሰጠው ብዙ ፍቅር ጋር ለምንወዳቸው ነፃነትና ለፍላጎታቸው መተውንም መስጠት ይጠበቅብናል።
ውዶቻችንን ለፍላጎታቸው መተው፥ ለውሳኔና ፍቃዳቸው አሳልፈን መስጠትም ከፍቅር ነው!
መኖር ቀለሙ ብዙ ነው፥ ልከኛ መልኩ ግን ፍቅር ነው❤
ተዛዘኑ ተዋደዱ ለብዙ ልቦች ትተርፋላችሁ🥰
ለልቤ መውደድን የለገስኩ ነኝ. . .🌼
መልካም ቅዳሜ በፍቅር ዋሉ🥰🥰💃
2 612
✨#ጓደኝነትን_የት_ነው_የምታውቂው ...?#❸
✨ ጓደኝነትን የት ነው የምታውቂው? አልኳት
ፀጉሯን ወደ ኋላ ሰብሰብ አድርጋ በሙሉ ትኩረቷ ከዘመተችበት ኑድልስ ላይ ቀና ሳትል የስልኳን lock wallpaper ከጎኑ ነካ አድርጋ አሳየችኝ
ሁለታችንም የ Korea series ወዳጆች በመሆናችን ከቢሯችን አጠገብ ኑድልስ ቤት መከፈቱን እንዳየን ባልተራዘመ ቀጠሮ መምጣታችን ነው።
ከአንድ ሳምንት በፊት ነው ያወኳት...ሥራ ቀይሬ የገባሁበት አዲስ ቢሮ ውስጥ ነው የተግባባነው...ቦታዬ ከእርሷ አጠገብ በመሆኑ የማስለመድ ድርሻውን የወሰደችው እርሷ ነበረች።ደስ ትላለች...መናገር ያለባትን ታውቃለች...እርጋታዋ ሌላ ውበቷ ነው...ከቢሮ ወጥተን በረንዳ ላይ እንደቆምን በትልቁ የተጻፈ "ቻኖሊ ኑድልስ" የሚል ባነር ትኩረታችንን ሳበው...ተያየን...አሁን ከቤቱ ጥግ ላይ ካሉ ወንበሮች ተሰይመናል።
ስልኳ ላይ የሚታየው ስብስብ ምስሎች በመሆኑ አልገባኝም? አልኳት
"ጓደኛ የለኝም "
ለምን ?
"ክበቤ ውስጥ ሰው የለም... እኔና አምላኬ ከዛ እዚህ የምታያቸውና ሌሎች የለመድኳቸው የምወዳቸው ድርጊቶች ናቸው።"
እንዴት? ማለት ብፈልግም ተውኩት የማይመለከተኝን የምጠይቅ ሰው አይደለሁም።
አእምሮዬ ውስጥ የሸዊት ንግግር አስተጋባ "
በቃ እስከፈቀደችልሽ ተጓዥ ...እስከነገረችሽ ድረስ ብቻ ስሚ...ውትወታሽ ችለሽ የማታጽናኚውን ነገር ያሰማሻል!!"እኔም ወደ ምግቤ አቀረቀርኩ "ይልቅ ግን አንድ የምወደውን የጓደኝነት ታሪክ ልንገርሽ" አለችኝ ከንፈሯን በናብኪን እየጠራረገች... በደስታ!! በይሁዳ ምድር...እስራኤል ነው። እርሱ ደግሞ የንጉሥ ተወዳጅ ልጅ ለአባቱ ዙፋን ተጠባባቂ ባለተስፋ የተመሰገነ ልዑል ነው። ሃገሪቷ ውጥረት ውስጥ ናት።ፍልስጤማውያንና እስራኤል ተፋጠዋል...ይልቁንም ደግሞ አስፈሪው የፍልስጤም ጦረኛ ጎልያድ የሚገጥመኝ እያለ ይፎክራል ....አልተገኘም ! ከዛ በፊት... በንጉሥ መተዳደር የእስራኤል ወግ ባይሆንም በዙሪያቸው ካሉ ሕዝቦች አይተዋልና በእነርሱ ዘንድ ፈራጅ የነበረውን ነብይ ሳሙኤልን ካልሾምክልን ብለው አስጨነቁቱ...ሳኦል ተሾመላቸው አህያ ነጋዴ ነበር.....!! የሳኦል ዘመን እያከተመለት መሆኑን ሲያውቅ ነብዩ ንጉሥ ፍለጋ ከእሴይ ቤት ተገኘ።የእሴይ ልጆች መጡ ቅብኣ ዘይቱ ግን ቀስ ቀስ አላለም...ግራ ተጋብቶ ጠየቀው የቀረ ልጅ የለህም?...ከእረኝነት ተፈልጎ መጣ።ገና ከሩቁ ዘይቱ ተንተከተከ....ንጉሱን ጨምሮ ድፍን ይሁዳ የምትንቀጠቀጥለት ታላቁ ነብይ ሳሙኤል ከዛ ትንሽ ብላቴና ፊት ዝቅ አለ... በእስራኤል ፊት ሲንጎራደድ የነበረው ታላቁ ጦረኛ ጎልያድ ለጦር ያይደለ ስንቅ ለማድረስ በመጣ ታናሽ እረኛ ወንጭፍ ተገደለ።ሴቶች ከበሯቸውን ይዘው "ሳኦል ሺህ ገደለ ዳዊት እልፍ" አሉ....የሳኦል ልብ በቅናት ነደደች...የንግሥና ዘመኑ እያበቃ ቢሆንም በአንድ እረኛ ብላቴና መተካት እንቢ አለ....ይገድለው ዘንድ ያሉትን መንገዶች ሁሉ ሞከረ.... በዚህ ሁሉ መኃል ግን የአንድ ሰው ልብ በተለየ ዳዊትን ወደደች ።ምናልባትም መጥላት ቢፈልግ የተሻለ ምክንያት ያለው ደግሞ እርሱ ነበር። ለዮናታን በቀጣይ መንገስ ዳዊት ስጋት ነው።የሆነው ግን በተቃራኒው ነበር ጎልያድን አሸንፎ ሲመጣ የለበሰውን ካባ አውልቆ እርሱንና ልብሱን ሰይፉንም ቀስቱንም መታጠቂያውንም ሸለመው። አየሽ አንዳንድ መውደድ ከዝምድና እና ከስልጣን ይልቅ ለምታከብሪው ነገር ያጋድላል። "አባቱ ሊገድለው መሻቱን አውቆ ከዛ አካባቢ እንዲሸሽ ሸኘው።ስንብታቸው ላይ በጋራ ቤታቸው ለዘላለም ቃል ኪዳን ገቡ። በእነርሱ ታሪክ ውስጥ ተደጋግሞ የተጠቀሰው ቃል ምን እንደሆነ ታውቂያለሽ?" እንደነፍሱ ወደደው !! አልኳት "በትክክል!! "ፊቷ በራ ጦርነቱ ቀጥሎ ንጉሡ ሳኦልና ልጁ ዮናታን በተራራ ወደቁ።ዳዊት ማቅ ለብሶ አመድ ነስንሶ አዘነ....በመዝሙሩ ተቀኘላቸው።
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ²⁵ ኃያላንም በሰልፍ ውስጥ እንዴት ወደቁ! ዮናታንም በኮረብቶችህ ላይ ወድቆአል። ²⁶ ወንድሜ ዮናታን ሆይ፥ እኔ ስለ አንተ እጨነቃለሁ፤ በእኔ ዘንድ ውድህ እጅግ የተለየ ነበረ...ዓመታት አልፈው የተቀባው ዳዊት ነገሠ።እስራኤል ያደረገውን ሁሉ አይታለችና ተገዛችለት።የተደላደለ ዙፋኑ ላይ ተቀምጦ አገልጋዮቹን ጠየቀ "ቸርነትን አደርግለት ዘንድ ከዮናታን ቤት ማን አለ ?" አንድ አገልጋይ ቀርቦ "እግሩ ሽባ የሆነ አንድ የዮናታን ልጅ አለ አለው።" የዮናታን ልጅ ሜምፊቦስቴ ወደ ዳዊት መጣ።
"ዳዊትም፦ ስለ አባትህ ስለ ዮናታን ቸርነት ፈጽሜ አደርግልሃለሁና አትፍራ፤ የአባትህንም የሳኦልን ምድር ሁሉ እመልስልሃለሁ፥ አንተም ሁልጊዜ ከገበታዬ እንጀራ ትበላለህ አለው።""አየሽ ጓደኝነት አብሮ መብላት መጠጣትን መገናኘትን ይዘላል።አለመኖር እስካያቆመው ይሻገራል።ጓደኝነት ብዙ መልክ ማሰሪያው ደግሞ ፍቅር ነው።" በመስማማት ራሴን አወዛወዝኩ። "በይ ረፍዷል ተነሺ ወደ ቢሮ እንመለስ..."ተያይዘን ወጣን። ✍️𝓮𝓶𝓾𝔂𝓮𝓮 https://t.me/yeesua_queen
2 612
Repost from ቢራቢሮ🦋.......(ሰadi)
ገጣሚ ዘውድ አክሊል አንድ ኢንተርቪው ለይ ፍቅር ማምለጫ ነው ሲል ሰማሁት.... ዋሻ ነው መሳሳት ምንችለበት ዋሻ!
ሁልጊዜ ጠባሳችንን ሸፍነን አንችልም አውልቀን የምናሳይበት ቦታ ነው ፍቅር!
ማነሳችንን፥ ሚያነክስ እጅ እግራችንን፥ ሚያነክስ ህሊና እና ልባችንን ምንገልጥበት ቦታ ነው እያለ ይቀጥላል...
አዎ በምንወዳቸው ሰወች ውስጥ ምንም መሆን ሳይጠበቅብን... ከነ ምንምነታችን ቀናትን እንሻገራለን።
መኖር ቀለሙ ብዙ አይደል በተለያዩ የህይወት መልኮች ለይ ያመላልሰናል። ታዲያ በእዚህ ምልልሶች ማንዝለው የኛ ሰወች ትከሻ አብሮን ስላለ ነው።
ለብቻ ሊሻገሩት ገደል የሆነ በጋራ ይቀላልና የእናንተን ሰወች አደራ!
እየመነዘርን ምንኖረው የተሰጠንን ፍቅር ነው...ምንሰጠው አያሳጣን❤️
መልካም ቅዳሜ በፍቅር ዋሉ🥰
2 612
Repost from N/a
እንደምን አለሽ አበባዬ..?
እንዴት ሆኖልሽ ሌቱ ነጋ?
በረዶ ሲጥል - ባደረ ክረምት
ጠራራ ፀሀይ - ባዘለ በጋ?
እንዴት ቢሆን ነው - የአንድ ዕለት አዳር
ወዝሽን ወስዶ - ወና ያደረገሽ - ከዳር እስከ ዳር?
.
መልከኛ ነበርሽ..
ዛሬ እንደ ትናንት - ፈፅሞ አታምሪም
በወጠውለግሽ
ባጣሽው ሁሉ - አታማርሪም?
.
ብላት ምን አለች?
.
እንዳሳለፍኩት - ጠራራ ፀሀይ - ማማር አይጠልቅም
ተራ ጠብቆ እንደወረደው - በረዶ ዝናብ አይፈራረቅም
መልክ ሲቀይር - ተመልካች ካለ ውበት አያልቅም።
.
ትናንት ካየሽው - የፈካ ገላ - የተካከለ
ጠጋ ብትዪ..
በጠባሳዬ ተፅፎ 'ሚታይ - ውብ ታሪክ አለ።
.
ከትናንት ጋር
ትናንቴም ቢቀር - ዛሬን አተረፍኩ
አመስጋኝ ነኝ - ስላልተቀጠፍኩ።
ከውጣ ውረድ - ከግርግሩ - ታልፎ ሲታረፍ
ሚዛን ያነሳል...
ከህይወት ካጡት - በህይወት መትረፍ።
2 612
🎶🎶🎶
✨ከምኔው ከምኔው ከምኔው ነውሳ፤
ልበ ቢስ የሆንኩት በአንተው የተነሳ።
ከምኔው ከምኔው ከምኔው ደግሞ ፤
እንዳልተው ያረገኝ ናፍቆትህ አዳክሞ፨
....🦋
እንዳልተው
ወይ ከኔ አካል ጎሏል ወይ ካንተው🪽
https://t.me/yeesua_queen
2 612
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
" ተማሪዎች ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው ውጤታቸው ማየት ይችላሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽባቸው አድራሻዎች ይፋ ሆነዋል።
በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም ከምሽቱ 1፡00 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን (Link) በመጠቀም ማየት የሚችሉ መሆኑን የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።
በተያያዘም ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26/2018 ዓ/ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል የሚችሉ መሆኑን አገልግሎቱ ገልጿል።
ውጤት የሚገለጽባቸው ማስፈንጠሪያዎች፡-
- በድረ ገጽ ፡ https://result.eaes.et
- ቴሌግራም፡ https://result.eaes.et/telegram
- አጭር የጽሑፍ መልዕክት፡ https://result.eaes.et/sms
ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ/ም
@tikvahethiopia
2 612
Repost from Dildiy - (ድልድይ)
➡️
.
.
.
በጦርነት ምድር ቀድሞ የሚሞተው እውነት ወይም ህይወት አይደለም፤ 'የእርሱ ህመም እንደኔ ህመም ያለ ነው፣ የእርሷ ስቃይ እንደኔ ዓይነት ስቃይ ነው' የሚለው እውቅና እንጂ...
እያንዳንዱ ጥይት ኢላማውን ሁለት ጊዜ ይመታል - አንዴ አካልን ቀስፎ፣ ደግሞም የአካሉን ባለቤት ውብ ነገዎችን ገድሎ...
ጦርነት - ባልተፈፀመ ኑረት የደም ቀለምነት ክፉ ታሪክ የሚፃፍበት የመከራ ደብተር ነው...
ጦርነት 'ድል ላደረጉ' ህያዋን የክብር አክሊል ሲጭንላቸው፣ የሞቱትን ተስፋና ነገ ግን ከመሬት ስር ይደብቃል... የውጊያ ሜዳ ነግ ሳይወለድ የሚቀበርበት መቃብር ነው... ጦርነት አንድን ህይወት ብቻ አይቀስፍም፣ ከዚያ ህይወት ሊያብብ የሚችለውን የነገውን ትውልድ ጭምር እንጂ...
በጦርነት ውስጥ ጎልቶ የሚሰማው ድምፅ የቦምብ ፍንዳታ አይደለም፣ ወጥቶ የቀረ ክፋያቸውን በሚጠብቁ አፍቃሪዎች ጎጆ ውስጥ የሚረበው ጭጭታ እንጂ...
ጦርነት ሲያበቃ የመሳሪያዎች አፍ ይዘጋል፣ ድምፃቸውም ይፀጥታል፣ በህፃናት ልብ ውስጥ ያለው ጩኸት ገደል ማሚቶ ግን ለዘላለም ይኖራል...
በጦርነት አንድም የሚያሸንፍ ህዝብ የለም፣ የአንዳንዶች 'ድል' ከሌሎቹ ኪሳራ አንፃር ኁልቆ አልባ ከመሆኑ ውጪ...
ምድር መቼም ቢሆን ደም እንድንረጫት ጠይቃን አታውቅም፣ ደም የሚጠማው የሰው ልጅ አእምሮ ብቻ ነው...
ጦርነት የሌላው ሰው ሞት ለኔ ህይወት ይሆናል ብሎ እራስን የሚያታልሉበት ቅዠት ነው...
ጦርነት የሌላው አካል መቁሰል፣ ለኛ ፈውስ እንደሚሆን የምናስብበት የውሸት ተስፋ ነው...
ጦርነት ማለት...
[ብቻ ይደክማል...]
____
@bridgethoughts
2 612
Repost from Thoughts
አስጠኚ ይፈልጋሉ?
እኛ ጋር ብቁ አስጠኚዎች የእናንተን ፍቃድ ብቻ ይጠብቃሉ። ከእናንተ የሚጠበቀው በተጠቀሱት ስልኮች መደወል ብቻ ነው። ከሚፈልጉት አስጠኚ ጋር እናገናኛችኋለን።
☑️Group: https://t.me/grandtutorss
💬Account: @grandtutors1
🗣️ Phone number: 0980806056
2 612
🕋☪ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች ቤተሰቦቻችን በሙሉ፤ የነቢዩ መሐመድ (ሰ.ዐ.ወ)
የልደት በዓል (መውሊድ)እንኳን አደረሳችሁ! እያልን በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣የጤና እና የበረከት እንዲሆንልዎ ከልብ እንመኛለን!🕋🌙
https://t.me/yeesua_queen
2 612
Repost from N/a
የተመኘውን - ሳልከለክለው
የወደደውን - እንቢ ሳልለው
የታሰረውን - ሰንሰለት - ሰብሮ
ያሻውን ሁሉ - እንዲይዝ በሮ
ሁሉን ፈቅጄ - ልቤን ፈተንኩት
ወረተኛ ነው - ይኸው ታዘብኩት...
.
ሳቅ ከከበበው - ደስታ ካለበት - አያሰኘዉም
የሚሰብረውን እስካላገኘ - እረፍት የለዉም።
2 612
የተመኘውን - ሳልከለክለው
የወደደውን - እንቢ ሳልለው
የታሰረውን - ሰንሰለት - ሰብሮ
ያሻውን ሁሉ - እንዲይዝ በሮ
ሁሉን ፈቅጄ - ልቤን ፈተንኩት
ወረተኛ ነው - ይኸው ታዘብኩት...
.
ሳቅ ከከበበው - ደስታ ካለበት - አያሰኘዉም
የሚሰብረውን እስካላገኘ - እረፍት የለዉም።
