en
Feedback
ሪሳለቱል ሂጃብمعرفة الحجاب☀️

ሪሳለቱል ሂጃብمعرفة الحجاب☀️

Open in Telegram

ስለ ሂጃብ እና መስፈርቶቹ ማወቅ ያለብን አስተማሪ ትምህርቶች የምንለቅበት ቻናል ነው ሀሳብ እና አስተያየት ካላቹ 👇 @Risaletulhijab_bot ኒቃቤን ስወዳት Join and Share 👇 @Risaletulhijab

Show more
8 235
Subscribers
-424 hours
-487 days
-14130 days
Posts Archive
የሁለቱን ዒዶች ስርኣት የሚመለከቱ ጥቂት ነጥቦች ከማስረጃዎቻቸው ጋር —————ክፍል 2 የተክቢራ አደራረግንና የዒድ ሶላት አሰጋገድን ያካተተ ክፍል 1 ለማግኘት ⤵️ https://t.me/IbnShifa/5118 ሴቶች የዒድ ሶላት ወደ ሚሰገድበት ቦታ ሲወጡ… »-» ሴቶች ሲወጡ ማንኛውም አይነት ማራኪ ሽታ ያለውን ነገር መቀባትና ጌጣ ጌጥ ያለውን ልብስ ለብሰው መውጣት ሀራም ይሆንባቸዋል። ኢብኑ ተይሚያ (ረሂመሁላህ) የሴቶችን ወደ ዒድ ቦታ መውጣት በተመለከተ ሲናገሩ እንዲህ ይላሉ:- “ሴቶች የዒድ ቦታ ላይ ማንኛውም አይነት ሽታ ያለውን ነገር ሳይጠቀሙ፣ የጌጣ ጌጥና የዝነኞችን ልብስ ሳይለብሱ ቢወጡ ችግር የለውም። ምክንያቱም ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋልና:- ምንም አይነት ሽታ ያለውን ነገር ሳይጠቀሙ ይውጡ…።” [ተውዲሁል አህካም ሸርህ ቡሉግ…] ይህ በሴቶች ላይ የተቀመጠ መስፈርት ነው። ይህን መስፈርት ስሜቴንና ሸይጧንን አሸንፌ ማሟላት አልችልም የምትል ሴት ከቤቷ ትቀመጥ!። ወደ ዒድ ቦታዎች እየወጣች ለጌታቸው ሊሰግዱና ጌታቸውን አላህን ሊያወድሱ የወጡ ወንዶችን ወንጀል ውስጥ እየጣለች ለራሷም ወንጀል ሸምታ ከመግባት ልትቆጠብ ይገባል!!። ሽቶ ተቀብተውና ተጋግጠው የሚወጡ እህቶች አላህን ሊፈሩት ይገባል!!። በደስታ ቀን አላህን ከማመፅ ሊቆጠቡ ይገባል። እህቴ ሆይ! በደስታ ቀን አላህን ካመፅሽ በዱኒያና ነገ በጭንቁ ቀን ጭንቀት እንዳይጨምርልሽና ስቃይሽን እንዳያበረታው ልትፈሪና ልትጠነቀቂ ይገባል!! እህቴ ወደ ዒድ ቦታ መውጣት ከፈለግሽ ሽቶና ዲዮድራንት… መሰል ነገሮችን ከመቀባት ርቀሽ፣ የሰውነት ቅርፅሽን የሚያሳዩ የተጣበቁና የተጋጌጡ ልብሶችን አሽቀንጥረሽ ጥለሽ ሰፋፊ ሸሪዓዊ አለባበስ ለብሰሽ ድምፅሽን አጥፍተሽ ወጥተሽ አምላክሽን አላህን አወድሰሽና አልቀሽ ለእርሱም ሰግደሽ ተመለሺ። ይህን ማድረግ ካልቻልሽ ግን አላህን ፈርተሽ ቤትሽ ይስፋሽ!!። »-» ወደ ዒድ ቦታ ሲኬድ ድምፅን ከፍ አድርጎ ተክቢራ ማለት ተደንግጓል። አምላካችን አላህ እንዲህ ብሏል:- وَلِتُكْمِلُوا الْعِدَّةَ وَلِتُكَبِّرُوا اللَّهَ عَلَىٰ مَا هَدَاكُمْ وَلَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ «ቁጥሮችንም ልትሞሉ አላህንም ቅኑን መንገድ ስለመራችሁ ታከብሩትና ታመሰግኑት ዘንድ (ይህን ደነገግንላችሁ)፡፡» አል-በቀረህ 185 ከዐብደላህ ኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ተይዞ፣ የአላህ መልእክተኛ ﷺ በሁለቱ ዒዶች ከፈድል ኢብኑ ዐባስ፣ ከዐብደላህ፣ ከዐባስ፣ ከዐሊይ፣ ከጀዕፈር፣ ከሀሰንና ሁሰይን፣ ከኡሳማ ኢብኑ ዘይድ፣ ከዘይድ ኢብኑ ሃሪሰህ፣ ከአይመን ኢብን ኡሙ አይመን (ረዲየላሁ ዐንሁም) ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ተክቢርና ተህሊል እያሉ ይወጡ ነበር። [በይሀቂይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በኢርዋእ አልገሊል 3/123 ላይ ሶሂህ ነው ብለውታል።] የተክቢራውን አደራረግ በተመለከተ ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጠ ሶሂህ የሆነ ዘገባ የለም። ዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ ግን የሚከተለውን የተክቢራ አይነት ይጠቀም እንደነበር ተረጋግጧል:- “አላሁ አክበር አላሁ አክበር፣ ላ! ኢላሀ ኢለላህ፣ አላሁ አክበር አላሁ አክበር ወ ሊላሂል ሀምድ” [ኢብኑ አቢ ሸይባ በሶሂህ ሰነድ ዘግበውታል።] ዐብደላህ ኢብኑ ዐባስም እንደሚከተለው ይል እንደነበር ተዘግቧል:- “አላሁ አክበር አላሁ አክበር፣ አላሁ አክበር ወ ሊላሂል ሀምድ፣ አላሁ አክበር ወ አጀልሉ፣ አላሁ አክበር ዐላ ማ ሐዳና” [በይሀቂይ ሶሂህ በሆነ ሰነድ ዘግበውታል።] »-» የተክቢራ ጊዜን በተመለከተ የዒደል ፊጥር ተክቢራ የዒዱን ቀን ተሰግዶ እስኪያበቃ ነው። የዒዱል አድሃ ተክቢራ ደግሞ ከዐረፋ ንጋት ሶላት ጀምሮ በተከታታይ አያሙ ተሽሪቅ እስኪጠናቀቅ ድረስ ነው። (የውሙ ዐረፋ ማለት ከዙል ሒጃ 9ኛው ቀን ነው።) ይህ አጠቃላይ ሰለፎች፣ ሶሃባዎች፣ አራቱ መሪዎችና ፉቅሃዎች የተጓዙበት መንገድ ነው። [ሶሂህ ፊቅህ አስ-ሱና አቡ ማሊክ ከማል] »-» አንዳንድ ሰዎች ዒድ ሚሰገድበት ቦታ ሲደርሱ ሱና ብለው ይሰግዳሉ። ይህ ትልቅ ስህተት ነው። ለሁለቱም ዒዶች ከፊታቸውም ሆነ ከኋላቸው ሱና ሶላት የላቸውም። ነገር ግን ነቢዩ ﷺ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ 2ረከዓ ይሰግዱ ነበር። ከአቢ ሰዒድ አል-ኹድሪይ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ የአላህ መልእክተኛ ﷺ ከዒድ በፊት ምንም አይሰግዱም ነበር፣ ወደ ቤታቸው ከተመለሱ በኋላ ሁለት ረከዓ ይሰግዱ ነበር።” [ኢብን ማጀህ 1076 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ ሀሰን ነው ብለውታል።] ለሁለቱም ዒዶች አዛንም ሆነ ኢቃም ማለት የለም። »-» የዒድ ሶላት የአሰጋገድ ሁኔታን በተመለከተ እንደሚከተለው ነው:- የዒድ ሶላት 2ረከዓ ነው። ዑመር ኢብኑል ኸጧብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ ብሏል:- “የተጓዥ (የጉዞ) ሶላት 2ረካዓ ነው። የዒደል አድሃ ሶላትና የዒደል ፊጥር ሶላትም ሁለት ሁለት ረከዓ ነው። እርሱም አጥሮ ሳይሆን ሙሉው ነው 2ረከዓ በነቢያችሁ አንደበት የተደነገገ ነው።” [ነሳኢይ እና ኢማሙ አህመድ የዘገቡት ሲሆን ሀዲሱም ሶሂህ ነው።] » የመጀመሪያውን ረከዓ ልክ እንደሌላው ሶላት  በኢህራም ተክቢራ ይጀምራል። ከዚያ በኋላ ሰባት ጊዜ ተክቢራ ያደርጋል። ሰባቱ ተክቢራ በሚደረግበት ወቅ እጅ ማንሳቱ ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጠ ነገር የለም። ነገር ግን ኢብኑል ቀይም (ረሂመሁላህ) ዐብደላህ ኢብኑ ዑመር የነቢዩን ﷺ ሱንና አጥብቆ የሚከተል ከመሆኑም ጋር በሰባቱም ተክቢራ ጊዜ እጁን ያነሳ ነበር ይላል። ሌላው በየ ተክቢራው መሃል የሚባል ዚክር ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጠ ነገር የለም። ይሁን እንጂ ኢብኑ መስዑድ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ነቢዩ ﷺ በየ ተክቢራው መሃል "አላህን ያወድሱም ያመሰግኑም ነበር” ብሏል። [በይሀቂ የዘገቡት ሲሆን ሰነዱ ሀሰን ነው።] ከሰባቱ ተክቢራዎች በኋላ ፋቲሃ ይቀራል ከዚያም ሱራዎች ይቀራሉ። ተወዳጅ ሱራዎች "ቃፍ፣ ወል ቁርኣኒል መጂድ፣ የሚለውና ኢቅተረበቲ ሰኣቱ… እንዲሁም ሰቢህ እስመ ረቢከል አዕላና ሐል አታከ ሀዲሱል ጋሺየህ…" ሱራዎች ናቸው። [ሙስሊምና ነሳኢይ ሌሎችም ዘግበውታል።] ከዚያም በሁለተኛው ረከዓ ተነስቶ ለመቆም ከሚለው ተክቢራ ውጭ አምስት ተክቢራዎችን ይላል። ከዚያ በኋላ ልክ በመጀመሪያው ረከዓ እንዳደረገው ፋቲሃን እና ሌሎችን ሱራዎች ይቀራል። ከዓኢሻ (ረዲየላሁ ዐንሃ) ተይዞ፣ “የአላህ መልእክተኛ ﷺ በዒደል ፊጥርና በዒደል አድሃ ሶላት በመጀመሪያው ረከዓ ሰባት ተክቢራዎችን በሁለተኛው ረከዓ ደግሞ አምስት ተክቢራዎችን ይሉ ነበር።” ብላለች። [አቡዳውድ የዘገቡት ሲሆን ሀዲሱም ሶሂህ ነው።] በመጨረሻም ከተሸሁድ በኋላ ያሰላምታል። »-» ወደ ዒድ ቦታ ከተጓዙባቸው መንገዶች በተቃራኒ መንገድ መመለስ ሱንና ነው። ከጃቢር ኢብን ዐብደላህ (ረዲየላሁ ዐንሁ) ተይዞ እንዲህ አለ:- “ነቢዩ ﷺ የዒድ ቀን ከሆነ በተቃራኒ መንገድ ይጓዙ ነበር።” [ቡኻሪ ዘግበውታል] አቢ ሁረይራ (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንዲህ አለ:- “ነቢዩ ﷺ ወደ ዒድ መስገጃ ቦታ ከወጡ መጀመሪያ ከወጡበት መንገድ በተቃራኒው ይመለሱ ነበር።” [ኢብን ማጀህ ዘግበውታል] አላህ ዒዳችንን አላህን የምንታዘዝበትና አላህ በሚፈቅደው መልኩ የምንደሰትበት ዒድ ያድርግልን!!

🌙⭐️ عيد مبارك 🌙⭐ 🌷 تقبل الله منا ومنكم صلح الأعمال كل عام وأنتم بالف خير 🌷 አሏህ መልካም ሥራቸውን ከተቀበላቸው፡ ካዘነላቸው፡ ከማራቸው እና ከእሣት ነፃ ካላቸው ሙእሚኖች ያድርገን!!! 🌷አሚን🌷 🕋🕌⭐🌙ኢድ -ሙባረክ⭐🌙 🕋🕌

Part 2 ​3. የሽቶ "GPS" እና የተንቀሳቃሽ እጣን ሱቅ ​አንዳንድ እህታችን ተቀብታው የምትወጣው ሽቶ፣ መንገዱን በሙሉ አውዳው፣ እሷ አልፋ ከሄደች ከግማሽ ሰዓት በኋላ እንኳን "እከሊት በዚህ አልፋለች" ብሎ ለመናገር ያስችላል። መዓዛው አፍንጫን ሰንጥቆ የሰዎችን ትኩረት በግድ ይስባል። ​ማስረጃው ምን ይላል? ከላይ እንደተጠቀሰው ይህ ድርጊት በሸሪዓው እጅግ ከባድ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶበታል። ​"ማንኛዋም ሴት ሽቶ ተቀብታ (መዓዛዋን እንዲያሸቱት አስባ) በወንዶች ስብስብ አጠገብ ካለፈች እርሷ አመንዝራ (ዝሙተኛ) ናት።" (አቡ ዳውድ፣ ቲርሚዚ)
​4. እንደ ጤፍ መቀላቀል (ኢኽቲላጥ) እና የፎቶ ግርግር ​ሶላት እንዳለቀ ዒድ ዒድ የሚሸተው ፆታን ሳይለዩ እንደ ሰርዲን ታሽጎ ፎቶ በመነሳት ይመስል፣ ወንዱና ሴቱ ትከሻ ለትከሻ ይላፋል። "የአጎቴ ልጅ ነው፣ የሰፈሬ ልጅ ነው፣ አብሮ አደጌ ነው" በሚል ሰበብ ከባዳ (አጅነቢ) ወንዶች ጋር መተቃቀፍና መተራመስ የዘመኑ የዒድ "ፋሽን" ሆኗል። ​ማስረጃው ምን ይላል? አጅነቢ (ሊያገቧቸው የሚፈቀዱ) ወንዶችን መጨበጥም ሆነ መነካካት ክልክል ነው። ​ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- "ከእናንተ አንዳችሁ (የማትፈቀድለትን) ሴት ከሚነካ፣ ጭንቅላቱ ላይ በብረት መርፌ ቢወጋ ይሻለዋል።" (ጦበራኒ ዘግበውታል)።
​5. የቲክቶክ ሱስና የዒድ ተክቢራ ​ድሮ ዒድ ሲመጣ ተክቢራ በማድረግ አላህን በማላቅ ነበር ጊዜው የሚያልፈው። አሁን ግን ሶላቱ ቦታ ላይ እንኳን ሳይቀር በጀርባ ተክቢራ እየተባለ፣ ከፊት ለፊት ለቲክቶክ እና ለስናፕቻት ዳንስ እና የተንሻፈፈ የከንፈር ፖዝ ይሰጣል። ዒዱ ዒባዳ (አምልኮ) መሆኑ ቀርቶ የላይክ እና የቪው (View) ማግኛ ፕሮጀክት ሆኗል። ​ማስረጃው ምን ይላል? እስልምና "ሐያእ" (አይነ አፋርነት/ክብርን መጠበቅ) የኢማን (የእምነት) አንዱ አካል መሆኑን ያስተምራል። ​ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) "እያንዳንዱ ሃይማኖት የራሱ የሆነ መለያ አለው፤ የእስልምና መለያ ደግሞ ሐያእ (አይነ-አፋርነት) ነው" ብለዋል (ኢብኑ ማጃህ)። ቪዲዮ እየቀረፁ ራስን ለባዳ ወንዶች ማጋለጥ የዚህን ሐያእ ተቃራኒ ነው። ​6. የዓይን "ራዳር" (እይታን አለመሰብሰብ) ​በዒድ ቀን ሁሉም አምሮና አጊጦ ስለሚወጣ፣ ዓይን አላረፍ ይላል። "ያቺ ምን ለበሰች? የሱ ጫማ ያምራል" እያለ አይን እንደ አውሮፕላን ራዳር 360 ዲግሪ ይዞራል። በዚህ መሃል አይን ባልተፈቀዱ (አጅነቢይ) ሰዎች ላይ አፍጥጦ ይውላል። ​ማስረጃው ምን ይላል? አላህ በሱረቱ-ኑር ለአማኝ ወንዶችም ሆነ ሴቶች እይታቸውን ዝቅ እንዲያደርጉ (አይናቸውን ከሐራም እንዲሰብሩ) በጥብቅ አዟል (24:30-31)። እይታ የሰይጣን መርዛማ ቀስት ነች። ​⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️⭐️ ይቀጥላል

ዛሬ ዱአ መቅቡል የሚሆንበት ቀን ነው በዱአ በርቱ የፆማችሁ ሁሉ አላህ  ፆማችሁን ይቀበላችሁ

ነገ ማክሰኞ ግንቦት 18 /2018 ዙልሂጃ 9 ነው።ነገ ቀን የፆመ ያለፈውና የሚመጣው አመት ወንጀሉን ይማርለታል። ይሄ ቀን እንዳያመልጠን ለማለት ነው 🥲🤍

ቁርዓን ካንተ የሚፈልገው ትርፍ ጊዜህን ሳይሆን... ሙሉ ህይወትህን ነው! ሙራጃዕ ለማድረግ(ለመከለስ) ስትቀመጥ ሸይጣን ስራ የሚያበዛብህ፣ ስልክህን እንድታይ የሚገፋፋህ እና እንቅልፍ እንቅልፍ የሚልህ ለምን ይመስልሃል? ምክንያቱም አንተ በምድር ላይ ትልቁን እና ውዱን ሀብት በልብህ ውስጥ እየጠበቅክ ስለሆነ ነው! ሸይጣን ያንን ብርሃን ሊያጠፋብህ ይፈልጋል። ዛሬውኑ ወስን! በቀን 1 ጁዝ ይሁን 1 ገጽ፣ ከሙራጃዓህ ጋር ፍጹም አትደራደር። አንተ ለቁርዓን ጊዜ ስትሰጥ፣ አላህ በጊዜህና በህይወትህ ውስጥ በረካን ይሞላዋል። t/meRisaletulhijab

⏰​በዒድ ቀን መታረም ያለባቸው ተግባሮች☪️ part 1 ​1. የሜካፕ ማዕበል እና የ"Face ID" ፈተና (ተበሩጅ) ​በዒድ ጠዋት አንዳንድ እህቶቻችን ፊታቸው ላይ የሚቀቡት የሜካፕ ብዛት የራሳቸው ስልክ እንኳን በ"Face ID" ሊያውቃቸው እስኪቸገር ድረስ ነው። ከንፈር ደም መስሎ፣ ቅንድብ እንደ ቀስተ ደመና ተስሎ ወደ መስገጃው ሜዳ ሲወጣ፣ የዒድ ሶላት ቦታ የሜክአፕ ውድድር ይመስላል። ​ማስረጃው ምን ይላል? እስልምና ሴት ልጅ ለባሏ እና እቤቷ ውስጥ እንድታምር ያበረታታል፤ ነገር ግን ውበቷን አደባባይ ላይ ለባዳ ወንዶች ማሳየት (ተበሩጅ) በጥብቅ ይከለክላል። ​አላህ በሱረቱል አህዛብ (33:33) ላይ እንዲህ ይላል፡- "በቤቶቻችሁም ውስጥ እርጉ፤ እንደ ፊተኛው (የአለማወቅ) ዘመን ጌጣችሁንም አትግለጡ..."
​2. "ሲኪኒ" አባያ እና የሒጃብ ትርጉም ​"ሒጃብ ለብሻለሁ" ለማለት ብቻ ፀጉርን ሸፍኖ፣ ነገር ግን ቀሪውን የሰውነት አካል "እኔን እዩኝ" በሚል ጠባብ ልብስ ማጣበቅ የተለመደ ሆኗል። አባያው ከጠባቡ የተነሳ ለመራመድም ሆነ ሱጁድ ለማድረግ ጂምናስቲክ መስራት ይጠይቃል። ሌላው ደግሞ ቀሚሱ ረጅም ሆኖ ከስር በኩል ግን እስከ ጉልበት ተቀዶ የውስጥ ሱሪን የሚያሳይ የ"ዘመናዊ" አባያ ስታይል ነው። ​ማስረጃው ምን ይላል? ትክክለኛ ሂጃብ ማለት ፀጉርን መሸፈን ብቻ ሳይሆን፡ ሰፊ የሆነ (አካልን የማይገልፅ)፣ የማያሳጭ፣ ጌጠኛ ያልሆነና የካፊሮችን ልብስ የማይመስል መሆን አለበት። ​ነቢዩ (ሰ.ዐ.ወ) ስለ መጨረሻው ዘመን ሲናገሩ፡- "ለብሰው ያለበሱ (ልብሱ ጠባብ ወይም አሳጭ ከመሆኑ የተነሳ ገላቸውን የሚያሳይ)፣ የሚያማልሉና የተዘነበሉ ሴቶች... ጀነት አይገቡም፣ ጠረኗንም አያገኙም" ብለዋል (ሙስሊም ዘግበውታል)። part 2 ይቀጥላል ⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️⤵️ ​

👉 የኢድ ተክቢራ ቃላቶች 🎙 الشيخ أبو منصور محمد حياة الولوي  الأجباري ثم الهروي 🎙 በሸይኽ ሙሐመድ ሀያት አል-ወልውይ አላህ ይጠብቃቸው 💬 ♻️ ♻️ 👇👇👇 https://t.me/SheikMohmmedHyatHara

✍      አንድ ቀን ብቻ ቀርቶታል!!  =>የዐረፋ ቀን የዐረፋ ቀን ማለት፦     ዙል—ሂጃ 9 ሐጅ የሚያደርጉ ሰዎች ዐረፋ ላይ ሚቆሙበት ቀን ነው።ይህም አላህ ካደረሰን የፊታችን ማክሰኞ ይሆናል። ስለዚህ ቀን የአላህ መልዕክተﷺ ሲናገሩ፦ 📚«ما من يوم أكثر من أن يعتق الله فيه عبيدا  من النار من يوم عرفة.»          /رواه مسلم/   «አላህ ከዐረፋ ቀን የበለጠ ባሮቹን ከእሳት ነፃ የሚያወጣበት የሆነ ቀን የለም።» 📚«من صام يوم عرفة؛ غفر له سنة أمامه، وسنة بعده.»        /رواه ابن ماجه واسناده حسن لغيره/   «የዐረፋ ቀን የጾመ ሰው ከፊት ለፊቱ ና ከበስተ ኋላው ያለውን ዓመት ወንጀሉ ይማርለታል።» 📚«صيام يوم عرفة؛ إني أحتسب على الله أن يكفر السنة التي بعده، والسنة التي قبله.»         /رواه ابو داوود والترمذي/   «የዐረፋ ቀን ጾም: አላህ ያለፈውና የሚመጣውን ዓመት ወንጀል እንደ ሚምር እከጅላለሁ።» 📚«من صام يوم عرفة؛ غفر له ذنب سنتين متتابعتين.»    /رواه ابي يعلى ورجاله رجال الصحيح/   «የዐረፋ ቀን የጾመ ሰው ተከታታይ የሆኑ የሁለት ዓመት ወንጀሉን ይማርለታል።»    ሙስሊም ወንድሜ ሆይ! ይህ ሁሉ የተነገረውና የተላለፈው ለሌላ ሰው ሳይሆን ለኔና ለአንተ ነው። አው ያለ ወንጀል አምሽተን ማንጋት ለተሳነን ለእኔና ላንተ!!   እናት አባቶቻችን እህት ወንድሞቻችን እና በቻልነው ያክል ሙስሊሞችን ሁሉ በማስታወስ የዚህ ትልቅ ቀን ቱሩፋት እንጠቀም።       💫በጾም………      💫በዱዐ………     💫በዚክር……ተክቢራን በማብዛት    💫ቁርኣን በመቅራት……… 💫ሰደቃ በማብዛት………   አጠቃላይ ኸይር በተባሉ ነገሮች ሁሉ ለማሳለፍ ከአሁኑ ሽርጣችን ልናጠብቅ ይገባናል።

ሶብር ማለት የፈለከውን ባታገኝም አሏህን ማመስገን ነው ሶብር ማለት የአሏህን እቅድ ምን እንደሆነ ባታውቅም ተማምነህበት መጠበቅ ነው ሶብር ማለት በአንተ ላይ የሚጨክኑ ሰወችን ታጋሽ እና ይቅር ባይ
ሶብር ማለት የፈለከውን ባታገኝም አሏህን ማመስገን ነው ሶብር ማለት የአሏህን እቅድ ምን እንደሆነ ባታውቅም ተማምነህበት መጠበቅ ነው ሶብር ማለት በአንተ ላይ የሚጨክኑ ሰወችን ታጋሽ እና ይቅር ባይ ሆነህ ማሳየት ነው

🔆ቁርአን ከቃኢዳ ጀምሮ እንዲሁም አጫጭር 👉ኪታቦች መቅራት የምትፈልጉ ☑️በቴሌግራም ቀጥታ (live) እና ☑️በኢሞ በቀጥታ (live) በተጅዊድ ከፈተና  ጋር መቅራት የምትፈልጉ በዚህ አናግሩን 👇👇      👉@Umu_asiya65          👆በዚህ ኑ

ኢላሂ...የተከበረውን ቤትህን ለመጠወፍ ባንታደልም፣በሶፋና በመርዋ መካከል ባንሮጥም፣ዐረፋት ላይ ቆመን፣ ሙዝደሊፋ ላይ አድረን፣ ጀመራት ባንወረውርም... እዚሁ ባለንበት ሆነን በውስጣችን ባለው ታላቅ ናፍቆት 'ለበይከ አሏሁመ ለበይክ!' እንላለን። ያረብ! ቤትህን የምንጎበኝበትን ዕድል በቅርቡ አግራልን፣ ልባችንንም በዚያ የተቀደሰ ስፍራ አሳርፈው።

ኢላሂ...የተከበረውን ቤትህን ለመጠወፍ ባንታደልም፣በሶፋና በመርዋ መካከል ባንሮጥም፣ዐረፋት ላይ ቆመን፣ ሙዝደሊፋ ላይ አድረን፣ ጀመራት ባንወረውርም... እዚሁ ባለንበት ሆነን በውስጣችን ባለው ታላቅ ናፍቆት 'ለበይከ አሏሁመ ለበይክ!' እንላለን። ያረብ! ቤትህን የምንጎበኝበትን ዕድል በቅርቡ አግራልን፣ ልባችንንም በዚያ የተቀደሰ ስፍራ አሳርፈው።

#አላሁ አክበር 🌸🌸 አላህ አላህ እዩልኝ ይህን ዉበት😍 አላህዬ እኛንም ወፍቀን ያ ረቢ 🤲🥺
+4
#አላሁ አክበር 🌸🌸 አላህ አላህ እዩልኝ ይህን ዉበት😍 አላህዬ እኛንም ወፍቀን ያ ረቢ 🤲🥺

ጀነት ዉድ ነዉ።     

አሏህዬ...🥰 "ከሁጃጆች መካከል አደለሁም ግን.. ልቤ ከዛ የተቀደሰ ቦታ አርፏል ወፍቀን ያ'ረብ"🤲

°°° ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢠⣶⣦⣀ ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⣾⣿⣿⣿⣷⡄ ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢻⣿⣿⣿⡿ ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢸⢀⢀⢀⢀⢀⢀⣠⡶⠿⠛⠛⠉⠁ ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢸⡆⢀⢀⢀⡴⠚⠉ ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⠈⡇⢀⢠⣿⣿⣷⣶⣶⣶⣶⣶⣶⣤⣤⣤⣤⡄ ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⣷⢀⠉⠉⠉⠙⠛⠛⠛⠛⢛⣿⣿⣿⣿⣿⠃ ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⣿⡀⢀⢀⢀⢀⣀⣴⠶⠟⠋⠉ ⢸⣆⣀⣀⣀⣤⣶⡞⠈⣇⢀⢀⡴⠟⠉ ⠸⠿⠿⠿⠿⠟⠛⠁⢀⢻⣆⣾⡀ ⢀⢀⢀ﷺ⢀⢀⢀⢀⢀⠻⣿⣿⣦⡀ ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⠙⠿⣿⣿ ⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⢀⠈ ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلَائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ ۚ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ { الأحزاب_ 33:56 }
አላህና መላእክቱ በነቢዩ ላይ የአክብሮት እዝነትን ያወርዳሉ፡፡ እናንተ ያመናችሁ ሆይ! በእርሱ ላይ የአክብሮት እዝነትን አውርዱ፡፡ የማክበርንም ሰላምታ ሰላም በሉ፡፡ { የአሕዛብ ምዕራፍ _ 33:56 }
📿 ዘንጊዎች በዘነጉ፣ አሰታዋሾች ባሰታወሱ ቁጥር፣ በረገፈው ቅጠል፣ በፈሰሰው አሸዋ፣ ሰማይን ባደመቁት ክዋክብት፣ ውቂያኖስ በያዘው ጠብታ መጠን የአላህ እዝነትና ሰላም 🤌🏽 በውዱ ነቢያችን ሙሐመድ (ﷺ) ላይ ይሁን! 📿 صَلَّى اللّٰهُ عَلَيهِ وَاٰلِهٖ وَسَلِِّم  ♡ ♡ ♡ ╭┈─────── ೄ🌹ྀ࿐ ˊˎ- ╰┈ በሰለዋት የደመቀና የተባረከ ቀን ይሁንልን !  💐

ያ الله እድሉን ላላገኘነውና ልባችን በናፍቆት ለሚቃጠለው በሙሉ በሚቀጥለው ዓመት በታላቁ ዐረፋ ተራራ ላይ የምንቆም አድርገን 🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲
ያ الله እድሉን ላላገኘነውና ልባችን በናፍቆት ለሚቃጠለው በሙሉ በሚቀጥለው ዓመት በታላቁ ዐረፋ ተራራ ላይ የምንቆም አድርገን 🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲🤲

⚠️ የጥንቃቄ መልእክት! ብሔራዊ ባንክ የፋይዳ መታወቂያን ከባንክ አካውንት ጋር ለማስተሳሰር የሰጠው ጊዜ ማብቃቱን ተከትሎ፣ ሌቦች "ከብሔራዊ ባንክ ነው የምንደውለው፤ ሒሳብዎን ከፋይዳ ጋር ልናስተሳስር ነው፣ የፋይዳ ቁጥርዎንና አካውንትዎን ንገሩን" በማለት ዝርፊያ እየፈፀሙ ይገኛሉ። በመሆኑም በምንም መልኩ በስልክ ተደውሎ የዚህ አይነት ጥያቄ ስትጠየቁ መልስ ባለመስጠት ራሳችሁን ከዘረፋ እንድትጠብቁ እና አካውንታችሁ ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር ያልተያያዘ ከሆነ፣ ወደ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል በመሄድ ብቻ እንድታስተካክሉ ለማስታወስ እንወዳለን።

⚠️ የጥንቃቄ መልእክት! ብሔራዊ ባንክ የፋይዳ መታወቂያን ከባንክ አካውንት ጋር ለማስተሳሰር የሰጠው ጊዜ ማብቃቱን ተከትሎ፣ ሌቦች "ከብሔራዊ ባንክ ነው የምንደውለው፤ ሒሳብዎን ከፋይዳ ጋር ልናስተሳስር ነው፣ የፋይዳ ቁጥርዎንና አካውንትዎን ንገሩን" በማለት ዝርፊያ እየፈፀሙ ይገኛሉ። በመሆኑም በምንም መልኩ በስልክ ተደውሎ የዚህ አይነት ጥያቄ ስትጠየቁ መልስ ባለመስጠት ራሳችሁን ከዘረፋ እንድትጠብቁ እና አካውንታችሁ ከብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ) ጋር ያልተያያዘ ከሆነ፣ ወደ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል በመሄድ ብቻ እንድታስተካክሉ ለማስታወስ እንወዳለን። = የቴሌግራም ቻናል፦ https://t.me/FuadKemal https://t.me/FuadKemal