የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር - Ministry of Women and Social Affairs
Open in Telegram
ይህ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር ይፋዊ የቴሌግራም ገጽ ነው!! ስለ ሴቶችና ማሕበራዊ ጉዳዮች ሚኒስቴር ተጨማሪ መረጃዎችን ለማግኘት ተከታዮቹን ገፆቻችንን ይጎብኙ Follow ministry of Women and Social Affairs pages for more information ***** ድረ ገጽ፦ https://www.mowsa.gov.et/ ፌስቡክ፡- https://www.facebook.com/Ethio
Show more1 600
Subscribers
No data24 hours
-47 days
+630 days
Data loading in progress...
Similar Channels
Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
September '26
September '26
+8
in 0 channels
August '26
+48
in 0 channels
Get PRO
July '26
+41
in 0 channels
Get PRO
June '26
+48
in 0 channels
Get PRO
May '26
+48
in 0 channels
Get PRO
April '26
+49
in 0 channels
Get PRO
March '26
+90
in 0 channels
Get PRO
February '26
+65
in 0 channels
Get PRO
January '26
+47
in 0 channels
Get PRO
December '25
+62
in 0 channels
Get PRO
November '25
+82
in 0 channels
Get PRO
October '25
+63
in 0 channels
Get PRO
September '25
+70
in 0 channels
Get PRO
August '25
+53
in 0 channels
Get PRO
July '25
+97
in 0 channels
Get PRO
June '25
+60
in 0 channels
Get PRO
May '25
+57
in 0 channels
Get PRO
April '25
+99
in 0 channels
Get PRO
March '25
+70
in 0 channels
Get PRO
February '25
+86
in 1 channels
Get PRO
January '25
+68
in 0 channels
Get PRO
December '24
+115
in 0 channels
Get PRO
November '24
+86
in 0 channels
Get PRO
October '24
+112
in 0 channels
Get PRO
September '24
+43
in 0 channels
Get PRO
August '24
+117
in 0 channels
Get PRO
July '24
+71
in 0 channels
Get PRO
June '24
+59
in 0 channels
Get PRO
May '24
+435
in 0 channels
| Date | Subscriber Growth | Mentions | Channels | |
| 09 September | +1 | |||
| 08 September | +1 | |||
| 07 September | +1 | |||
| 06 September | 0 | |||
| 05 September | 0 | |||
| 04 September | +1 | |||
| 03 September | +1 | |||
| 02 September | +1 | |||
| 01 September | +2 |
Channel Posts
ሚኒስቴሩ የኀብር ቀንን አስመልክቶ ለተቋሙ ሰራተኞችና ለተለያዩ የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ማዕድ አጋራ
****
(ጳጉሜ 4/2018 ዓ.ም) የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር አመራሮችና ባለሙያዎች "ብዝኀነት የኢትዮጵያ ጌጥ!" በሚል መሪ ሃሳብ የኀብር ቀንን በተለያዩ መርሐግብሮች በድምቀት እያከበሩ ይገኛል።
ሚኒስቴሩ የህብር ቀንን እንዲሁም መጪውን አዲስ አመት ምክንያት በማድረግ የተቋሙ ሰራተኞች ከነቤተሰባቸው በዓሉን ተደስተው እንዲያሳልፉ አስፈላጊውን የበዓል መዋያ ድጋፍ አድርጓል።
በተጨማሪም አቃቂ ቃሊቲ ለሚገኘውና ጥቃት የደረሰባቸው ሴቶች ማረፊያና የልማት ማህበር የ200 ሺህ ብር እና የቴምር ድጋፍ ተደርጓል። በተመሳሳይ ለ13 የበጎ አድራጎት ተቋማት የቴምር ድጋፍ አበርክቷል።
በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የክብርት ሚኒስትር አማካሪ ክቡር አቶ ጌታቸው በዳኔ በዕለቱ ባስተላለፉት መልዕክት፤ ብዝሃነት ለሀገር ጥንካሬ እና ለህዝቦች ማህበራዊ ትስስር የጸና ምሰሶ መሆኑን አንስተዋል።
የኅብረ ብሔራዊ አንድነት እሴቶችን ማጠናከር ሀገርን ከማፅናት ባለፈ የነገዋን የበለጸገች ሀገር ዕጣ ፈንታ የሚወስን ቁልፍ ጉዳይ እንደሆነም ገልጸዋል።
ዛሬ ከምንጊዜውም በላይ በህብረት የመቆሙን አስፈላጊነት ተረድተን ለጋራ ቤታችን በጋራ መትጋት ይገባናል ሲሉም አሳስበዋል።
በልዩነታችን አምሮብን፣ በአንድነታችን ጸንተን፣ ለጋራ ብልጽግናችን በህብር መቆምና በየተሰማራንበት መስክ ጠንክረን መስራት ከሁላችንም ይጠበቅብናል ብለዋል።
#ጳጉሜን4 #የኀብርቀን #ብዝኀነትየኢትዮጵያጌጥ #ኢትዮጵያ
| 2 | No text... | 24 |
| 3 | No text... | 20 |
| 4 | በተቀናጀ አሰራር የተጋላጭ ወገኖችን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚያስችል የ“GO-NGO” ፎረም በድጋሚ ለማቋቋም የሚያስችል ምክክር ተካሄደ
****
የሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር መንግስታዊ እና መንግስታዊ ባልሆኑ ተቋማት መካከል የትብብርና ቅንጅት ሥራዎችን ለማጠናከር፣ የ“GO-NGO” ፎረም ዳግም ምሥረታ መድረክ በአዲስ አበባ አካሂዷል።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ሚኒስቴር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሳልፈው አመዲን እንደገለጹት፤ ሴቶች፣ ሕፃናት፣ ወጣቶች፣ አካል ጉዳተኞች፣ አረጋውያን እና ሌሎች ተጋላጭ የማኅበረሰብ ክፍሎችን በባለቤትነትና በተቀናጀ መልኩ ለመደገፍ አሁን ላይ ጠንካራ የትብብር ማዕቀፍ መዘርጋት ወሳኝ ነው።
ቀደም ሲል ተቋቁሞ የነበረው ይህ ፎረም ከተቋማዊ መዋቅር ለውጥ ጋር ተያይዞ ተቋርጦ መቆየቱ ሥራዎች በተበጣጠሰ መልኩ እንዲከናወኑና የሀብት ብክነት እንዲኖር ማድረጉ ተነስቷል።
አሁን ዳግም የተቋቋመው ፎረም ይህንን ክፍተት በመዝጋት የሥራ ድግግሞሽን በማስቀረት፣ ተጠያቂነትን በማጠናከር እና ሀብትን በአግባቡ በማስተባበር ተጨባጭ ውጤት እንደሚያስመዘገብ ታምኖበታል።
ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከተሰጠው ኃላፊነት አንጻር ከሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ላደረገው ትብብር ምስጋና ያቀረበ ሲሆን፤ በቀጣይም ለፎረሙ ስኬታማነት የቴክኒክና የፋይናንስ ድጋፍ ላደረገው ዪኤንውመን(UN WOMEN) እና ለተባበሩ አካላት ሁሉ ልባዊ ምስጋና አቅርቧል።
🇪🇹#MoWSA #GONGOForum #Ethiopia #Inclusion #SocialDevelopment #AddisAbaba
| 19 |
| 5 | No text... | 22 |
| 6 | ጳጉሜን 4- የኀብር ቀን እንኳን አደረሳችሁ!
"ብዝኀነት የኢትዮጵያ ጌጥ!" | 101 |
| 7 | የሀገር ፅናት - የሰላም ዓምዶች
*****
የሀገር ጸጥታ፣ ሉዓላዊነት እና የሰላም ዋስትና በደማቸው እና በላባቸው የሚከፈሉ ውድ ዋጋዎች ውጤት ናቸው። የሀገርን ሠላም ለመጠበቅና የሉዓላዊነት ዐምድ ሆኖ ለመቆም ከሚደረገው መስዋዕትነት ጀርባ የሴቶች፣ የወጣቶች እና የሰላም እናቶች ሚና ከፍተኛ ነው።
እነዚህ የህብረተሰብ ክፍሎች በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣ በጸጥታ ተቋማት እና በሰላም ማስከበር ዘርፍ እንዲሁም በባህላዊ የሰላም ግንባታ ግንባር ቀደም በመሆን የከፈሉትና እየከፈሉት ያለው መስዋዕትነት ታሪካዊ ቦታ የሚሰጠው ነው።
የመከላከያ ሰራዊቱ እና የጸጥታ ተቋማት የሀገርን ጸጥታ ለማስጠበቅ በሚያደርጉት ጥረት የሴቶችና የወጣቶች ተሳትፎ ከዕለት ወደ ዕለት እያደገ መጥቷል።
ሴት አባላት በመከላከያ ሰራዊት ውስጥ ከሎጀስቲክስ እና ከሰላም ሰጪነት ባለፈ በከፍተኛ የውጊያ ስልጠናዎች፣ በአየር ሃይል፣ በምህንድስና እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች በብቃት እያገለገሉ ይገኛሉ።
ወጣት ሰራዊት አባላት ለሀገር ሉዓላዊነት ያላቸውን ታማኝነት በውጊያ አውደ-ምድር ብቻ ሳይሆን በድንበር ጥበቃ፣ በህግ ማስከበር እና በሰላም እጦት የተጎዱ አካባቢዎችን በመታደግ ረገድ የፊት መስመር ተሰላፊዎች ናቸው። በአህጉራዊና አለም አቀፍ ተልዕኮ ውስጥ አምባሳደሮቿ የሴት ሰራዊት አባላትና መኮንኖች ሚና ልዩ ትኩረት የሚሰጠው ነው።
በጦርነትና ግጭት የተጎዱ አካባቢዎችን ለማረጋጋት በሚደረጉ አለም አቀፍ የሰላም ማስከበር ዘመቻዎች ሴት አባላት ከጸጥታ ጥበቃ ጎን ለጎን ለተጎዱ ህፃናት፣ ሴቶች፣ አካል ጉዳተኞች እና አረጋውያን ርህራሄን ከሰብአዊነት ያዋደደ ድጋፍ በማድረግ፣ ስነ-ልቦናዊ ድጋፍ በመስጠት እና ሰላምን በመገንባት ረገድ ከፍተኛ አድናቆትን አትርፈዋል።
የሀገር የሞራል ጀርባ እና የባህላዊ ሰላም አርበኞች የሆኑት የሀገር ሽማግሌዎችና ተእናቶቻችን ተቋማዊ ከሆኑ የጸጥታ መዋቅሮች ጎን ለጎን፣ ማህበረሰቡን ከታች ጀምሮ በሰላም በማስተሳሰርና የሰላም ድምጽ በመሆን ሀገር እንድትፀና ሚና የማይተካ ነው። ልጆቻቸውን ለሀገር ሰላም፣ ፍቅርና አንድነት እያስተማሩ የሚያሳድጉት የሰላም እናቶች የሀገር የሞራል መሰረትና የሰላም ህይወት ችቦዎች ናቸው።
የሀገር ሰላም ሲረጋገጥ እና ሉዓላዊነቷ ሲጠበቅ የፊት መስመር አርበኞቹ የሆኑት የመከላከያና ጸጥታ አባላት፣ እንዲሁም የማህበረሰቡ መሰረት የሆኑት የሰላም እናቶች የከፈሉት መስዋዕትነት ሁልጊዜም በክብር የሚታወስ ነው። ሰላማችን የሁሉም የህብረተሰብ ክፍሎች የጋራ ድካም ውጤት በመሆኑ፣ ለዚህ የቁርጠኝነት ስራ ልዩ ዕውቅና ሊሰጠው ይገባል። | 195 |
| 8 | No text... | 155 |
| 9 | ጳጉሜ 3- የጽናት ቀን | 141 |
| 10 | የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ለኢትዮጵያ ማንሠራራት!
******
ሀገራችን ኢትዮጵያን ወደ ላቀ የብልጽግና እና የዕድገት ከፍታ ለማሸጋገር ከሚደረጉ ሁለገብ ጥረቶች መካከል የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ምሰሶ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሰውን አቅም ማቀናጀት ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን ሁለንተናዊ ማንሰራራት የሚያረጋግጥ ብሩህ ተስፋ ነው።
የኢትዮጵያ ማንሠራራት ከአካባቢ ጥበቃ እና ከዘላቂ ልማት ጋር በቀጥታ የተያያዘ ነው። ሀገራችን ባለፉት ዓመታት በአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ያስመዘገበቻቸው ድሎች በበጎ ፈቃደኞች ሰራዊት የተገነቡ ናቸው።
በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎች በፈቃደኝነት ተነሳስተው ችግኝ በመትከልና በመንከባከብ የአየር ንብረት ለውጥን ለመቋቋም የሚያደርገው ጥረት የኢትዮጵያን መልክዓ ምድር ከመለወጥም በላይ ለአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ መሰረት ጥሏል።
በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ወጣቶች፣ ሴቶች፣ ታዳጊዎች፣ አዛውንቶች፣ ተቋማት እና ባለሙያዎች ጊዜያቸውን፣ ጉልበታቸውን እና እውቀታቸውን አስተባብረው ችግረኞችን ሲረዱ፣ አቅመ ደካሞችን ሲንከባከቡ እና ማህበራዊ ተቋማትን ሲደግፉ የሚታየው ትዕይንት የኢትዮጵያዊነት እውነተኛ መገለጫ ነው።
በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚከናወኑ የበጎ ፈቃድ ስራዎች ህብረተሰቡን ከድህነት ለማላቀቅ በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከፍተኛ አስተዋጽኦ አላቸው። ለምሳሌ በክረምት ወራት የሚከናወኑ የደም ልገሳ መርሃግብሮች፣ የትምህርት ቤት እድሳት፣ ለችግረኞች የቤቶች ግንባታ ፣ እና የጽዳት ዘመቻዎች የመንግሥት በጀት ብቻ ሳይጠብቁ በህዝብ ተሳትፎ ትላልቅ ሀገራዊ ክፍተቶችን የሚሞሉ ናቸው።
አቅም ያላቸው ዜጎች በዕውቀታቸው እና በጉልበታቸው ለወገን ሲቆሙ፣ ሀብት በቁጠባና በስርዓት እንዲያዝ በማድረግ ረገድ ትልቅ ድርሻ ያበረከታሉ። ይህ ደግሞ ቀጥተኛ ኢኮኖሚያዊ እፎይታን ለተጠቃሚዎችም ለሀገርም በመፍጠር የልማት ጉዞን በእጅጉ እያቀላጠፈ ይገኛል።
በበጎ ፈቃድ አገልግሎት የሚሳተፉ ሴቶች፣ ወጣቶች፣ ታዳጊዎች፣ አዛውንቶችና ተቋማት የስራ ከበሬታን፣ ኃላፊነትን እና የህብረተሰብ ፍላጎትን የመረዳት አቅማቸውን ማዳበር አስችሏቸዋል። የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ባህል እየሆነ፤ ለጋራ ጥቅም በጋራ መቆም የሚችል ትውልድ እየተፈጠረ መምጣቱ የኢትዮጵያ የመንሠራራት ጉዞ እንዲፋጠን፤ ሀገርም በጸና መሰረት ላይ እንድትቆም ጉልህ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል።
| 187 |
| 11 | No text... | 159 |
| 12 | No text... | 160 |
| 13 | ኢትዮጵያ የብልጽግና ትልሞቿን በፅኑ መሠረት እየገነባች ነው-የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
*****
(አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 2/2018 ዓ.ም ) ኢትዮጵያ የብልጽግና ትልሞቿን በፅኑ መሠረት እየገነባች መሆኑን የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት አስታወቀ።
አገልግሎቱ ለጳጉሜን 2 የማንሰራራት ቀን በማስመልከት ባስተላለፈው መልዕክት፣ ኢትዮጵያ በመደመር መንግሥት ፖሊሲዎች እና ዕቅዶች እየተመራች ለሁለንተናዊ ብልጽግና እየተጋች ትገኛለች ብሏል፡፡
በየዘመን አንጓው ያጋጠሟትን ፈተናዎች በተደመረ አቅም እየተሻገረች፤ ከችግሮች እና ፈተናዎች ዕድሎችን መንጭቃ እያወጣች፤ ነገዋን በጠንካራ መሠረት ላይ እያጸናች መሆኑንም ጠቁሟል፡፡
ለዘመናት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ከአድማስ እስከ አድማስ የሚያውለበልበው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ነገን ታሳቢ አድርጎ እንደ ቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ባሉ መሠረተ ልማቶች እና ሁለንተናዊ ለውጦች ውስጥ እያለፈ ነው፡፡
ነባር እና አዳዲስ የቱሪዝም መዳረሻዎች እየለሙ እና ተደራሽነታቸው እያደገ ነው፡፡ ግብርናችን ከዝናብ ጥገኝነት እየተላቀቀ እና የገጠሩም የከተሜውም የሥራ ዕድል እየሆነ ነው፡፡
የታዳሽ ኃይል አማራጮቻችን ከውኃ፣ ከነፋስ፣ ከፀሐይ፣ ከጂኦተርማል እና ከኑክሊየር ኃይል እንዲሆኑ የመደመር መንግሥት ሌት ተቀን እየሠራ ነው፡፡
ከተሞቿ ጎስቋላ ገጽታቸው እየተቀየረ እና ነገን እየዋጁ፤ መሠረተ ልማቶቿ እየተስፋፉ እና እየተቀናጁ፤ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ አቅሟ እየተጠናከረ፤ የቀጣናው የታዳሽ ኃይል ማዕከልነቷ እያደገ፤ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ ደረጃ ጥቅም ላይ እያዋለች ለመጪው ትውልድ ሁለንተናዊ ብልጽግና እየሠራች ነው፡፡
የኢትዮጵያን ማንሰራራት የሚያበስሩ፤ እመርታዊ ዕድገቷን የሚያፋጥኑ ፅኑ መሠረቶች እየተገነቡ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያንም ሥርዓቱን ለማጽናት እና መሻታቸውን እውን ለማድረግ ያላቸውን ቁርጠኝነት በመንግሥት ጥሪዎች በሚያሳዩዋቸው ተሳትፎዎች እየገለጹ ነው፡፡
| 196 |
| 14 | No text... | 168 |
| 15 | በደብረ ብርሃን ከተማ ሰክሰስ ፕላስ ከሴቶች ወጣቶች ማኅበራዊ ጉዳይ ጋር በመተባበር የ5 ሚሊዮን ብር ዊልቸር ለአካል ጉዳተኞች ድጋፍ አደረገ
*****
በድጋፍ ርክክቡ ላይ የተገኙት የደብረ ብርሃን ከተማ ተቀዳሚ ከንቲባ አቶ በድሉ ውብሸት እንደተናገሩት፣ በከተማው አካል ጉዳተኞች በማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ዘርፎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ የተሰራው ሥራ ውጤታማ ነው ብለዋል።
በተለይም አካል ጉዳተኞች ሰርተው ራሳቸውን እንዲችሉና እንዲለውጡ መስሪያና መሸጫ ቦታ በማመቻቸት፣ የመኖሪያ ቤት በመስጠት፣ ተደራጅተው የመኖሪያ ቤት መስሪያ ቦታ በማቅረብ እንዲሁም በቅርበት ክትትልና ድጋፍ በማድረግ በኩል ብዙዎችን ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን አመልክተዋል።
በዕለቱም ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ፣ የክልሉ ሴቶች ወጣቶች ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ከበጎ አድራጎት ድርጅቱ ጋር በመተባበር የተደረገው ድጋፍ የመንቀሳቀስ ችግር ያለባቸውን ወገኖች ችግር ለመፍታት ከፍተኛ ጥቅም እንዳለው በመጠቆም ምስጋና አቅርበዋል። ድጋፍ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም ፍንጭ ሰጥተዋል።
የሰክሰስ ፕላስ የበጎ አድራጎት ድርጅት ሥራ አስኪያጅ አቶ ፍሬውሁን መንገሻ በበኩላቸው፣ ድርጅቱ ባላፉት ሶስት ዓመታት በኢትዮጵያ በአራቱም አቅጣጫዎች ለአካል ጉዳተኞች ዘርፈ ብዙ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታወቀዋል።
ድርጅቱ በዋናነት በዊልቸር ድጋፍ፣ በገቢ ማስገኛ፣ በትምህርት ዕድልና ስፖንሰርሺፕ በመስጠት ከመንግስት ጋር በመተባበር እየሰራ እንደሚገኝ ጠቁመው፣ በደብረ ብርሃን ከተማ ለሚገኙ አካል ጉዳተኞችም 5 ሚሊዮን ብር ወጪ የሆነበት 100 ዊልቸር ድጋፍ ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።
በአካል ጉዳተኞች ዘርፍ የሚታዩ የተሳሳቱ አመለካከቶችን ለማረም እና ሁለንተናዊ ተሳትፏቸውን ለማረጋገጥ እየተሰራ መሆኑን በሴቶችና ማኅበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር የአካል ጉዳተኞች ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሲሳይ ጥላሁን አስታውሰው፣ ከለውጡ ወዲህ መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ልዩ ትኩረት ተሳትፏቸውን የሚያረጋግጡ ተግባራት እየተከናወኑ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
የአካል ድጋፍ መሳሪያዎች ዋጋቸው ውድ በመሆኑ በራሳቸው ገዝተው መጠቀም ለማይችሉ ወገኖች ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ከፌዴሬሽኑ፣ ከሰርከስ ፕላስ እና ከአማራ ክልል ሴቶችና ማህበረሰብ ጉዳይ ቢሮ ጋር በመተባበር ድጋፍ ማድረግ መቻሉን ገልፀዋል።
የአማራ ክልል ሴቶች ወጣቶች ማኅበራዊ ጉዳይ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ብርቱካን ሲሳይ እንደገለጹት፣ አካል ጉዳተኞች በማህበረሰቡ ዘንድ ባለው የተዛባ አመለካከት፣ የተደራሽነት እጥረት፣ የባለሙያና የተቋማት አሰራር ድክመቶች ምክንያት ለአካላዊ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ችግሮች ተጋልጠው እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
በተለይም የእንቅስቃሴ ጉዳት ያለባቸው በርካታ ዜጎች በሰው ሰራሽ አካል ድጋፍ እጥረት ከቤት መውጣት አቅቷቸው እንደሚቸገሩ ጠቁመዋል።
የሴቶች፣ ወጣቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ቢሮ የአካል ጉዳተኞችን ችግር የሚቀርፉ የፖሊሲ ሀሳቦች ከማመንጨት ባለፈ፣ የተደነገጉ አለም አቀፍ ስምምነቶች በክልሉ ተፈፃሚ እንዲሆኑ እየሰራ እንደሚገኝ በመግለጽ፣ ተቋማዊ አሰራርን በማጠናከር፣ ልዩ አገልግሎቶችን በማስፋፋት፣ አካል ጉዳተኞችን በማብቃት ላይ ትኩረት መደረጉን ተናግረዋል።
ድጋፍ የተደረገላቸው ወገኖች በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን በመግለጽ፣ የተሰጣቸውን ዊልቸር በአግባቡ ተጠቅመው እንደሚንቀሳቀሱ አመልክተዋል።
| 197 |
| 16 | No text... | 183 |
| 17 | No text... | 176 |
| 18 | የፕሬስ መግለጫ
እመርታ ለዘላቂ ከፍታ!
እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ! እመርታ ከአሉበት የከፍታ ደረጃ ወደ ላይኛዉ መስፈንጠር ነው፡፡ ከፍታን በአዝጋሚ ሂደትም ዘመናትን ወስዶ ማሻሻል ይቻላል፤ በዚያ አግባብ የሚመጣ መሻሻል ከታለመዉ ግብ ለመድረስ የትውልዶችን ጥረት የሚጠይቅ ነው፡፡ ኢትዮጵያውያን ግን በቁጭት ለዘመናት ከቆየንበት ኋላ ቀርነት እና ድህነት በአዝጋሚ ጉዞ ለመላቀቅ ስለማይቻል እመርታዊ ለውጥ ማምጣትን ግብ አድርገን ሠርተን ስኬቶችን እያስመዘገብን ነው፡፡ ያለፉት ጥቂት ዓመታት ጥረቶቻችን ውጤቶች የሚያሳዩትም ይህንኑ ነው፡፡
የኢትዮጵያን ጀርባ ያጎበጡ የውጭ ዕዳዎችን ጫና በመቀነስ፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፣ የኢንዱስትሪዎችን የማምረት ዐቅም በማሻሻል፣ የማዕድን ሀብቶች አጠቃቀምን በማላቅ እመርታዊ ለውጦች ተመዝግበዋል፡፡ የመንግሥት አጠቃላይ የማድረግ ዐቅም በእጅጉ ተለውጧል፡፡ ይህንን እመርታዊ ስኬት ማስመዝገብ የተቻለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያዎችን በማድረግ፤ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማሻሻል፤ የዜጎችን ተሳትፎ እና ተጠቃሚነት በማሳደግ፤ የቢዝነስ ሥርዐቱን ቀልጣፋና ግልጽ በማድረግ፤ የኢትዮጵያን የዲፕሎማሲ ዐቅም ከዜጋ ተኮር እና ብሔራዊ ጥቅም አንጻር በመግራት የመደመር መንግሥት ባደረገዉ ሰፊ ጥረት ነው፡፡
ኢትዮጵያ የማዕድን ሀብቶቿን በላቀ የኃላፊነት ስሜት በሕጋዊ አግባብ መጠቀም ጀምራለች፤ ታዳሽ ኃይልን በማምረት ከራስ አልፎ ለቀጠናዉ የኃይል ምንጭ ኾናለች፤ ብዝኃ ዘርፍ ኢኮኖሚን በመተግበር ኹለንተናዊ ዕድገቶችን እያስመዘገበች መጥታለች፤ የኢንዱስትሪ ምርቶችን በዓለም ገበያ ተወዳድራ የመሸጥ ዐቅም ፈጥራለች፡፡ የመንግሥት የልማት ዕቅድ ከቁጥ ቁጥ ወጥቶ ትውልድን ታሳቢ ያደረገ ግብ አስቀምጦ እየተተገበረ ነው፡፡ በ2018 ዓ/ም በሁሉም መስክ ከተስፋ ብርሃን ወደሚጨበጥ ለውጥ የመሸጋገር ሀገራዊ ራዕይን ማሳካት ተችሏል፡፡ ኢትዮጵያን በ2023 ዓ.ም አፍሪካዊት የብለጽግና ተምሳሌት የማድረግ ግብ ተቀምጦ ርብርብ እየተደረገ የስኬቱ ዋዜማ እየተቃረበ ነው፡፡
ኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመደመር መንግሥት በተነደፉ የፖሊሲ ሐሳቦች ኹለንተናዊ ሉዓላዊነትን የማረጋገጥ ጉዞን ጀምራለች፡፡ በገቢ አሰባሰብ ላይ የታየዉ እመርታ አንዱ አብነት ነው፡፡ የግብር እና ታክስ መሠረትን በማስፋት፣ ገቢ የመሰብሰብ ዐቅምን በማሳደግ፤ የግብር ከፋዩን የመንግሥት አገልግሎት እርካታ በመሶብ አንድ ማእከል እና በዲጂታል አገልግሎቶች ከፍ በማድረግ የላቀ አፈጻጸም ማሳየት ተችሏል፡፡ በዚህም የበጀት ጉድለትን በእጅጉ ማጥበብ ተችሏል፡፡
ባለፉት ጥቂት ዓመታት የመንግሥት ፕሮጀክቶችን የመፈጸም ዐቅም በእጅጉ አድጓል፡፡ ፕሮጀክቶች መቼ እንደሚጀመሩ እና በምን ያህል በጀት እንደሚፈጸሙ ብቻ ሳይኾን መቼ ተጠናቅቀው በትክክል አገልግሎት እንደሚሰጡ ጭምር በከፍተኛ የራስ መተማመን የመሠረት ድንጋይ ሲቀመጥ መናገር የሚቻልበት ቁመና ላይ ተደርሷል፡፡
እመርታዊ ስኬቶችን ዕውቅና ለመስጠት፣ በቀጣዮቹም ዓመታት የበለጠ እመርታዊ ስኬቶችን ለማስመዝገብ መዘጋጀት አስፈላጊ በመኾኑ ዛሬ ጳጒሜን 01 ቀንን “የኢትዮጵያ ማንሰራራት!” በሚል መሪ መልእክት እያከበርን ነው፡፡
እንኳን ለእመርታ ቀን አደረሳችሁ፣ አደረሰን!
ጳጒሜን 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የኢፌዴሪ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት
አዲስ አበባ | 145 |
| 19 | No text... | 164 |
| 20 | የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት
"የእመርታ ቀን
አባቶቻችን የኢትዮጵያን ዳር ድንበር በደምና በአጥንታቸው አስከብረው ታላቅ ሀገር አውርሰውናል፤ ዛሬ ደግሞ እውነተኛ ሉዓላዊነትን እያረጋገጥን ያለነው ከልመናና ከጥገኝነት በተላቀቀው አዲሱና ታሪካዊው መንገዳችን ነው! በሚሊዮን በሚቆጠር ዶላር ስንዴ ከማስገባት ተነስተን ዛሬ የአፍሪካ ቀዳሚ ስንዴ አምራች በመሆን የሚሊዮን ዶላሮችን ወጪ ማስቀረት ችለናል።
በ«ሌማት ትሩፋት» የምግብ ዋስትናን በተግባር እያረጋገጥን፣ በ«ኢትዮጵያ ታምርት» ንቅናቄም አዳዲስ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋትና የሥራ ዕድል በመፍጠር ሉዓላዊነታችንን እያረጋገጥን እንገኛለን። ከዚህ ቀደም የማይደፈሩና አይነኬ ይባልላቸው የነበሩ ከባድ የማክሮ-ኢኮኖሚ ሪፎርም ውሳኔዎችን በቁርጠኝነት በመተግበር፤ የሀገራችንን ኢኮኖሚ በፅኑ መሠረት ላይ እየገነባን እንገኛለን።
እነዚህ ሁሉ ታላላቅ ድሎች ኢትዮጵያ በሚያጋጥሟት ውስጣዊና ውጫዊ ፈተናዎች ሸብረክ ሳትል በፅናት መጓዝ መቻሏን የሚያረጋግጡ ህያው ምስክሮች ናቸው፤ ይህ የእመርታ ጉዟችን ለመጪው ዓመት የሰነቀው ተስፋ እጅግ ግዙፍ ነው!" | 170 |
