ኢቅራ የሰለፊያ ዳዕዋ ና ቂራት👇👇👇
Open in Telegram
اقرأ بسم ربك الذى خلق የዚ ቻናል አላማ የሉጋ ኪታቦች የተለያዩ ዱሩሶች መሳጭ የሆኑ ቲላዋዎች ኹጥባ ሌላሌላም አስተማሪ የሆኑ ትምህርቶች ይለቀቃል ላሎት አስተያየት 👇👇👇 @ibnu_zeynu
Show more273
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
🇵🇸ሩቅ አይደለም!!
💫ነብዩ ኢብራሂምﷺ እጅ እና እግራቸው ጠፍረው እሳት ውስጥ የወረወሯቸው ሰዎች በዝያች ቅፅበት አላህ አላጠፋቸውም።
💫ፊርዓውን "እኔ ጌታችሁ ነኝ" እያለ ያልተቀበሉት ሰዎች ሰውነታቸው ቆራርጦ ሰቅሎ እየገደለ ሲያሰቃያቸው በዝያች ቅፅበት አላህ አላጠፋውም።
💫አላህ ከሰማይ መልእክት እያወረደላቸው "ጌታችሁ አላህ ነው, ተገዙት" ያሉ ነብያቶች የገደሉ ሙጅሪሞች አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
💫"ጌታችን አላህ ነው, በእሱም አምነናል።" በማለታቸው ብቻ ጎድጓድ ቆፍረው እሳት አንድደው ያቃጠሏቸው “አስሀብ አል_ኡኽዱድ” አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
💫ለዓለማት እዝነት ተደርገው የተላኩት ውዱ ነብይﷺ ጀርባ ላይ ፈርስ እየጣሉ፣ በተደጋጋሚም የግድያ ሙከራ ያደረጉ ሙጅሪሞች አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
💫አላህ ከፈጠረው ሁሉ በላጭና ክቡር የሆኑት ነብዩﷺን ጦር ሜዳ ላይ ገጥመው ጭንቅላታቸው እስኪደማ የተዋጉዋቸው ሙጅሪሞች አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
💫ቀራሚጣዎች ጀናዛ የያዙ አስመስለው ሰይፋቸው በከፈን ሸፍነው ወደ ኻረም ካስገቡ በኋላ በአንድ ጀምበር ብቻ ከሶስት ሺህ (3000) በላይ ሑጃጆች ገድለው፣ የዘምዘም ውሃ በሑጃጆች ጀናዛ ደፍነው፣ የተከበረው የካዕባ ሽፋን በጣጥሰው፣ መሪያቸው ከፍታ ላይ ቆሞ “የዛሬው ንግስና ለማን ነው?” እያለ ሲፎክር፣ “ጠይረል አባቢል የት አሉ? ሂጃራ ሚን ሲጂል የት አለች?” እያለ ሲፎክር፣ ሱረቱል ቁረይሽ እየቀራ “ከፍራቻ ሰላም ሰጣቸው ይላል ከእኛ ፍራቻ ግን ሰላም አልሰጣቸውም” እያለ ሲያላግጥ፣ ሀጀረል አስወድን ቀምተው ወደ ሀገራቸው ወስደው ሲጫወቱበት አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
لا إله إلا الله
በዚች ምድር ላይ ምን ግፍ አልተፈፀመም??
ታድያ እነዝያ ሁሉ በዳዮች አሁን የት ነው ያሉት⁉️
ወዴት ነው የሄዱት⁉️
ወላሂ ሁላቸውም ወደ ሰሩት ነገር ሄደዋል!!
ምክንያቱም፦
ከጌታህ ሊያመልጥ የሚችል የለም!!
እናም ወዳጄ……
የቁድስን ክብር አዋርደው፣ የሙስሊሞች ሀገር ቀምተው፣ ሴቶችና ህፃናት ጨፍጭፈው; እንዲሁ የሚተዉ ይመስልሀል!?
ወላሂ አይተዋቸውም‼️
=> ቅጣታቸው የበለጠ አሳማሚ እንዲሆን አመፃቸው እንዲበዛ፣
=> አላህ የያዘላቸው ቀጠሮ እስከ ሚደርስ
እና
=> አላህ የፈለገው ጥበብ እስኪሟላ ያቆያቸዋል እንጂ
ሁሉም የጀሀነም ሙኩቶች ናቸው ወደዝያው በቅርብ ይነዳሉ።
ቅርብ ነው, ሩቅ እንዳይመስልህ!!
Repost from 🇸🇦ሐምዱ ቋንጤ🇵🇸
🇵🇸ሩቅ አይደለም!!
💫ነብዩ ኢብራሂምﷺ እጅ እና እግራቸው ጠፍረው እሳት ውስጥ የወረወሯቸው ሰዎች በዝያች ቅፅበት አላህ አላጠፋቸውም።
💫ፊርዓውን "እኔ ጌታችሁ ነኝ" እያለ ያልተቀበሉት ሰዎች ሰውነታቸው ቆራርጦ ሰቅሎ እየገደለ ሲያሰቃያቸው በዝያች ቅፅበት አላህ አላጠፋውም።
💫አላህ ከሰማይ መልእክት እያወረደላቸው "ጌታችሁ አላህ ነው, ተገዙት" ያሉ ነብያቶች የገደሉ ሙጅሪሞች አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
💫"ጌታችን አላህ ነው, በእሱም አምነናል።" በማለታቸው ብቻ ጎድጓድ ቆፍረው እሳት አንድደው ያቃጠሏቸው “አስሀብ አል_ኡኽዱድ” አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
💫ለዓለማት እዝነት ተደርገው የተላኩት ውዱ ነብይﷺ ጀርባ ላይ ፈርስ እየጣሉ፣ በተደጋጋሚም የግድያ ሙከራ ያደረጉ ሙጅሪሞች አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
💫አላህ ከፈጠረው ሁሉ በላጭና ክቡር የሆኑት ነብዩﷺን ጦር ሜዳ ላይ ገጥመው ጭንቅላታቸው እስኪደማ የተዋጉዋቸው ሙጅሪሞች አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
💫ቀራሚጣዎች ጀናዛ የያዙ አስመስለው ሰይፋቸው በከፈን ሸፍነው ወደ ኻረም ካስገቡ በኋላ በአንድ ጀምበር ብቻ ከሶስት ሺህ (3000) በላይ ሑጃጆች ገድለው፣ የዘምዘም ውሃ በሑጃጆች ጀናዛ ደፍነው፣ የተከበረው የካዕባ ሽፋን በጣጥሰው፣ መሪያቸው ከፍታ ላይ ቆሞ “የዛሬው ንግስና ለማን ነው?” እያለ ሲፎክር፣ “ጠይረል አባቢል የት አሉ? ሂጃራ ሚን ሲጂል የት አለች?” እያለ ሲፎክር፣ ሱረቱል ቁረይሽ እየቀራ “ከፍራቻ ሰላም ሰጣቸው ይላል ከእኛ ፍራቻ ግን ሰላም አልሰጣቸውም” እያለ ሲያላግጥ፣ ሀጀረል አስወድን ቀምተው ወደ ሀገራቸው ወስደው ሲጫወቱበት አላህ በዝያች ቅፅበት አላጠፋቸውም።
لا إله إلا الله
በዚች ምድር ላይ ምን ግፍ አልተፈፀመም??
ታድያ እነዝያ ሁሉ በዳዮች አሁን የት ነው ያሉት⁉️
ወዴት ነው የሄዱት⁉️
ወላሂ ሁላቸውም ወደ ሰሩት ነገር ሄደዋል!!
ምክንያቱም፦
ከጌታህ ሊያመልጥ የሚችል የለም!!
እናም ወዳጄ……
የቁድስን ክብር አዋርደው፣ የሙስሊሞች ሀገር ቀምተው፣ ሴቶችና ህፃናት ጨፍጭፈው; እንዲሁ የሚተዉ ይመስልሀል!?
ወላሂ አይተዋቸውም‼️
=> ቅጣታቸው የበለጠ አሳማሚ እንዲሆን አመፃቸው እንዲበዛ፣
=> አላህ የያዘላቸው ቀጠሮ እስከ ሚደርስ
እና
=> አላህ የፈለገው ጥበብ እስኪሟላ ያቆያቸዋል እንጂ
ሁሉም የጀሀነም ሙኩቶች ናቸው ወደዝያው በቅርብ ይነዳሉ።
ቅርብ ነው, ሩቅ እንዳይመስልህ!!
https://t.me/hamdquante
አትርሳ
~
ሸይኽ ኢብኑ ዑሠይሚን - አላህ ይዘንላቸውና - እንዲህ ይላሉ፦
"ትኩረትህ ሁሉ የራስህ ጉዳይ ላይ፣ ሃሳብህ ሁሉ የራስህ ሃሳብ ላይ ይሁን። ወደሚጠቅህ ነገር ተመልከትና ፈፅመው፡፡ የማይጠቅምህን ተወው። የማይመለከቱህን ነገሮች ማሰስ ከኢስላምህ ውበት ውስጥ አይደለም።"
[ሸርሑ ሪያዲ ሷሊሒን፡ 1/511]
Ibnu Munewor
بسم الله الراحمن الرحيم
🌹 السلام عليكم وراحمة الله وبركاتة🌹
✨እነሆ አስደሳች ዜና ይዘንሎት ቀርበናል✨
የአላህ ሰለም ራህማት በረከት በእናንተ ላይ ይሁን እያልን አል ፈተያት (الفتيات ) የሴቶች የኦላይን ቂራት ሴንተር ይዘንሎት ቀርበናል አላህ በቃሉ እንደሚለው
<< والقد يسرنا القران الذكر فهل من مدكر >>
ቁርአንንም ለመገንዘብ በርግጥ አገራነው ተገንዛቢም አልለን ?
እህቶቼ አላህ ቃሉን አግርቷልን ሰለ እኛ ከዝንጉዎች ሆንን ! በቻልነው እንድንማመር ዘንድም ጥሪ አቀርባለሁ በተጅዊድ መማር ምትፈልጉ በዚ ከታች ባለው ሊንክ በመጫን ወደጉሩፓችን ጎራ ይበሉ ከአላህ በተች ሆናን ልነግዛቹ በአላህ ስም ቃል እንገባለን አላህ ያጠንክራን ያጠንክራቹ ።።።።
👇👇👇👇👇
https://t.me/+lRaHEJMMJmxiM2U0
በውስጥ መስመር ማውራት ለምትፈልጉ
@Elahi6697
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"የውሻ ጩኸት ደመናን አይጎዳም!"
~
በነብያችን ﷺ ላይ የሚሳለቅ እራሱን እንጂ እሳቸውን ምንም ሊያደርጋቸው አይችልም። የላካቸው አምላክ "መወሳትህን/ዝናህን ከፍ አደረግንልህ" ብሏቸዋል። ይሄው የዝናቸው ከፍ ማለትም ነው ዛሬ በርካታ ውሾችን እያስጮኻቸው ያለው። ትላንትም የዛሬዎቹ ውሾች አያቶች የመልእክተኛውን ክብር ሊያንቋሽሹ ሞክረው ነበር። አላህ ግን እራሱ ለመልእክተኛው ﷺ ተከላካይ ይሆንና መልእክተኛው ግን ነገሩን ንቀው እንዲተውት እንዲህ ይጠቁማቸዋል፡-
(فَٱصۡدَعۡ بِمَا تُؤۡمَرُ وَأَعۡرِضۡ عَنِ ٱلۡمُشۡرِكِینَ إِنَّا كَفَیۡنَـٰكَ ٱلۡمُسۡتَهۡزِءِینَ ٱلَّذِینَ یَجۡعَلُونَ مَعَ ٱللَّهِ إِلَـٰهًا ءَاخَرَۚ فَسَوۡفَ یَعۡلَمُونَ وَلَقَدۡ نَعۡلَمُ أَنَّكَ یَضِیقُ صَدۡرُكَ بِمَا یَقُولُونَ فَسَبِّحۡ بِحَمۡدِ رَبِّكَ وَكُن مِّنَ ٱلسَّـٰجِدِینَ وَٱعۡبُدۡ رَبَّكَ حَتَّىٰ یَأۡتِیَكَ ٱلۡیَقِینُ)
"የታዘዝክበትንም ነገር በይፋ ግለፅ፤ አጋሪዎችንም ተዋቸው። እኛ ተሳላቂዎችን ሁሉ በቅተነሃል። (እነሱም) እነዚያ ከአላህ ጋር ሌላ አምላክን ያደረጉ ናቸው፤ በርግጥም (የስራቸውን ዋጋ) ወደፊት ያውቃሉ። አንተም በሚሉት ነገር ልብህ የሚጠብ መሆኑን በርግጥም እናውቃለን። ጌታህንም ከማመስገን ጋር አጥራው፤ ከሰጋጆቹም ሁን። እውነቱም (ሞት) እስከሚመጣህ ድረስ ጌታህን አምልክ።" [አልሒጅር፡ 94-99]
ስለዚህ ተሳላቂዎቹ ውሾች ቢሳለቁም የነብያችን ﷺ ዝና የበለጠ ይገንናል። የውሾቹ ስም ይከስማል። ውሻ ደግሞ ምን ታሪክ አለውና?! እስኪ የነብያችንና የትላንት ጠላቶቻቸውን ዝና አወዳድሩ። ሲጀመር መወዳደር ይችላሉ? በጭራሽ! “የሰማይና የመሬት ያክል ነው” ብንል እንኳ በትክክል አይገልፀውም።
ግን የነብያችንን ﷺ ክብር ለማጉደፍ ተፍ ተፍ የሚሉ ሰዎች አላማቸው ምን ይሆን? መልሱ ግልፅ ነው።
1. አንዳንዶቹ በነብዩ ﷺ እውቅና ሂሳብ እውቅና መሸመት የሚፈልጉ ናቸው። “አንዳንዶች ታዋቂዎችን በመተቸት ታዋቂ መሆን ይፈልጋሉ” ሲባል አልሰማችሁም?
2. ሌሎቹ ደግሞ የኢስላም ውበቱና ሁለንተናዊነቱ የሚያስቀናቸው፤ ከፍተኛ ግስጋሴው የሚያስበረግጋቸው ናቸው። ስለሆነም ሙሐመድን ﷺ ሲያንቋሽሹ የኢስላም ውበቱ የሚደበዝዝ፣ ግስጋሴው የሚገታ ይመስላቸዋል። እውነታው ግን ተቃራኒው ነው። ኢስላም ዛሬ ጠላቶቹን እንቅልፍ በሚነሳ መልኩ በከፍተኛ ፍጥነት እየገሰገሰ ነው። ስለዚህ ውሾቹ አመል ሆኖባቸው ይጮሃሉ እንጂ የኢስላምን ግስጋሴ ሊገቱት አይችሉም!! ውሾቹ ይጮሃሉ፣ ዋው! ዋው!....። ግመሉ ግን ጉዞውን ቀጥሏል። ውሻ ግመልን ማስቆም ከቻለች ትሞክር።
ባይሆን ከኛ አንድ ነገር ይጠበቃል። ከሃዲዎችን የነብያችንን ﷺ ስም ለመዘለፍ ያበቃቸው ለነብዩ አስተምሮ ያላቸው ጥላቻ መሆኑ ይታወቃል። አዎ የነቢዩ ﷺ ሱና እጅጉን ያስቆጫቸዋል!! እውነቱ ይህ ከሆነ ከሃዲዎችን የበለጠ ለማስቆጨት የሚጓጓ፤ ለሙሐመድ ﷺ እውነተኛ ወዳጅነቱን ማንፀባረቅ የሚፈልግ፣ ብሎም የአላህን ውዴታ ማትረፍ የሚሻ የበለጠ ወደ መልእክተኛው ሱና ይቅረብ፤ ትእዛዛቸውንም ይፈፅም፤ ከከለከሉትም ይራቅ። ይህን የሚያደርግ ጠላቱን የበለጠ ያስቆጫል። የአላህንና የመልክተኛውንም ﷺ ውዴታ ያፍሳል። ያ ሱብሓላህ! የአላህና የመልክተኛውን ውዴታ ያገኘ ምን የቀረበት ነገር አለ?! ያ ወሃ፞ቡ አንተ ወፍቀን! ኣሚን
(ኢብኑ ሙነወር፣ መስከረም 08/2005)
የቴሌግራም ቻናል
https://t.me/IbnuMunewor
السلام عليكم وراحمة الله وبركاتة
ውድና የተከበራቹ የቻናሌ ቤተሰቦች እነሆ ዛሬ አስደናቂ የመርከዝ ኢብኑ አባስ የተማሪዋች ምረቃ በቀጥታ አሁን እየተላለፈ ነው
بسم الله الراحمن الرحيم
مدرسة سلسبيل(التبيان) لتحفيظ القران الكريم
✨ታላቅ የሀፍላ ( የምረቃ) ፕሮግራም
መድረሰቱል ሰልሰቢል የሂፍዝና ተርቢየ
ማእከል የፊታችን እሁድ ቋግቄ 5/2015
በሰልሰቢል መስጂድ ከጠዋቱ 2:30
ጀምሮ ያካሂዳል
✨በእለቱም
👉የሰላሳ ጁዝ ሂፍዝ ውድድር
👉ኹጥባ
👉ነድዋ
👉ኺዋር
✨በቁርአን ላይ አስደናቂ ትእይንት እንዲሁም ሌሎችም አስደናቂ ፕሮግራሞች ስላሉ ተጋብዘዋል
👂 ልብ ይበሉ ለሴቶች በቂ ቦታ ተዘጋጅታል
👉ያስተውል አይደል መቅራት ማርፈድ ሁሉ ያስቆጫል
🕌ቦታ ሰልሰቢቢል መስጅ 🕌
ይ🀄ላ🀄ሉን👇👇 share👇
┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓
@IbnuZynu
@IbnuZynu
┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛
Repost from ባህሩ ተካ - Bahiru Teka
🚫 የግብረ – ሶዶማዊነት አደጋ
ግብረ ሶዶማዊነት ማለት የወንድ ለወንድ ፆታዊ ግንኙነት ማለት ሲሆን ይህ ተግባር አላህ እርም ያደረገው ፍፁም የተወገዘ በነብዩላሂ ሉጥ ህዝቦች ላይ መቅሰፍት እንዲወርድ ያደረገ ተግባር ነው ። አላህ የሉጥ ህዝቦችን ያጠፋበት ሁኔታ እንዲ ብሎ ይነግረናል : –
« فَلَمَّا جَاءَ أَمْرُنَا جَعَلْنَا عَالِيَهَا سَافِلَهَا وَأَمْطَرْنَا عَلَيْهَا حِجَارَةً مِّن سِجِّيلٍ مَّنضُودٍ »
هود ( 82 )
" ትዕዛዛችንም በመጣ ጊዜ (ከተማይቱን) ላይዋን ከታችዋ አደረግን (ገለበጥናት) ፡፡ ተከታታይም የሆነን የሸክላ ድንጋይ በርሷ ላይ አዘነብን ፡፡"
« مُّسَوَّمَةً عِندَ رَبِّكَ ۖ وَمَا هِيَ مِنَ الظَّالِمِينَ بِبَعِيدٍ »
هود ( 83 )
" ከጌታህ ዘንድ ምልክት የተደረገባት ስትሆን (አዘነብናት) ፡፡ እርሷም ከበደለኞቹ ሩቅ አይደለችም ፡፡"
የአላህ መልእክተኛ – ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም –
" የሉጥ ህዝቦችን ተግባር ሲፈፅም ያገኛችሁት ፈፃሚውም የተፈፀመበትም ግደሉዋቸው " ብለዋል ።
ኢስላም ግብረሶዶማዊነትን በጣም ከትላልቅ አላህ ከታመፀባቸው ወንጀሎች ተርታ ይመድበዋል ። ይህ ተግባር ምእራባዊያን የዲሞክራሲ መብት ነው በሚል የእነርሱ ሸይጧናዊ አስተሳሰብ የሰው ልጆች ከአላህ ትእዛዝ አፈንግጠው የሸይጧን አምላኪና ታዛዥ እንዲሆኑ ለማድረግ የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም ። የምእራባዊያን ትልቁ ትኩረት እስልምናን መዋጋት ሲሆን ይህን እውን ለማድረግ የእስልምናን አስተምሮዎችን ለመናድ ሙከራ ማድረጉን ተያይዘውታል ።
በሁሉም ጤነኛ አመለካከት ባለውና ከሰማይ የወረደ ኪታብ አለኝ በሚል እምነት የተወገዘና ንፁህ ልቦና የማይቀበለው ተግባር ስለሆነ ሀገራችን ላይ ሶሞኑን እየተወሰደ ያለው እርምጃ እሰየው የሚያሰኝ ሲሆን የትኛውም እምነት አለኝ የሚልና ጤነኛ ትውልድ እንዲተካ የሚፈልግ እንዲሁም ሀገርና ህዝብ ከአላህ ከሚመጣው መቅሰፍት ሰላም እንዲሆን የሚመኝ ሊደግፈው የሚገባ ነው ።
እንደሚታወቀው ምእራባዊያን የራሳቸውን ደመ ነፍሳዊ ፍላጎትና አይዲዮሎጂ በአፍሪካ ሀገሮች ላይ በሀይል ለመጫን በኢኮኖሚና በማእቀብ ያስፈራራሉ ።
በቅርቡ የኡጋንዳ ህገመንግስት የዚህ አይነት ተግባር የሚፈፅምን ከሞት እስከ እድሜ ልክ እስራት በሚደርስ ቅጣት ለመቅጣት ህግ በማፅደቃቸው ምክንያት የተለያየ የማእቀብ ጫና እየደረሰበት ነው ። ይሁን እንጂ መንግስቱም ይሁን ህዝቡ የማይበገር አቋም በመያዝ ለሌሎች አስተማሪ የሚሆን ስራ ሰርተዋል ።
ምእራባዊያን ማንኛውም ሰው ፆታውን ወደ ፈለገበት መቀየር ይችላል ። አንድ ሰው በተፈጠረበት ፆታ የመቆየት ግዴታ የለበትም የሚል ህግ አውጥተው ለህፃናት በየትምህርት ቤቱ እንዲህ አይነቱን ዝቅጠት እንዲማሩ አድርገዋል !!!!! ። የእነዚህ የምእራባዊያን እንሰሳዊ አስተምሮ ህዝቦቻቸው ከዚህ በላይ እኛ ሰው ሆነን ተፈጥረን ሰው ሆነን የመቆየት ግዴታ የለብንም የሚል የአእምሮ ጨለማ ዝቅጥት ውስጥ ከተዋቸው ሶሞኑን አንዱ አሜሪካ ላይ ብዙ ሺህ ዶላር በመክፈል ራሱን ወደ ውሻነት መቀየሩንም ተቀብለው እንደጀብድ ያወሩት ይዘዋል ‼።
ሙስሊሞች ባጠቃላይ በምእራቡ አለም የምትኖሩ በተለይ ራሳችሁንና ልጆቻችሁን የዚህ ተግባር ፀያፍነትና የሚያስከትለው ሁለንተናዊ አደጋ በማስተማርና ግንዛቤ በማስጨበጥ ከጥፋት መጠበቅ ግድ ይላል ።
የምእራባዊያን የመለኮታዊው መመሪያ የመዋጋት ጥረት በብዙ መልኩ የተለያየ እስራቴጄ በተለያየ ጊዜ በመንደፍ ባጀት መድበው የሰው ሀይል አዘጋጅተው እየቀጠሉበት በመሆኑ ሙስሊሞች ዲናቸውን በማወቅና መመሪያውን በራሳቸው ላይ ተግባራዊ በማድረግ ሊከላከሉት ይገባል ።
አላህ ከምእራባዊያን ሸርና ተንኮል ይጠብቀን ።
https://t.me/bahruteka
📚 ከሰላት በኋላ ዱዐ ማድረግ
🗳حكم الدعاء بعد الصلاة
السؤال: بعض الناس في صلاة الفرض يرفعون أيديهم بعد الدعاء فما رأيكم؟
🎤 በሸኽ ሷሊህ አልዑሰይሚን ረህመቱላሂ አለይሂ
📌ጥያቄ: አንዳንድ ቦታዎች ላይ ከፈርድ ሰላት በኋላ ሰጋጆች ለዱዐ እጃቸውን ያነሳሉ። ይህ እንዴት ይታያል?
الجواب:
الدعاء بعد الصلاة ليس بسنة، لأن الله تعالى قال: فَإِذَا قَضَيْتُمُ الصَّلاةَ فَاذْكُرُوا اللَّهَ [النساء:103] إلا في حالة واحدة وهي صلاة الاستخارة؛ لأن صلاة الاستخارة قال فيها النبي ﷺ:
(إذا هم أحدكم بأمر فليصل ركعتين ثم ليدعو) فجعل الدعاء بعد صلاة الركعتين، أما ما سواها من الصلوات فليس من السنة أن يدعو سواءً رفع يديه أم لم يرفع، وسواءً في الفريضة أو في النافلة؛ لأن الله أمر بذكره بعد انتهاء الصلاة، فقال سبحانه وتعالى:
فَإِذَا قَضَيْتُمُ الصَّلاةَ فَاذْكُرُوا اللَّهَ [النساء:103]، وقال في سورة الجمعة: فَإِذَا قُضِيَتِ الصَّلاةُ فَانْتَشِرُوا فِي الْأَرْضِ وَابْتَغُوا مِنْ فَضْلِ اللَّهِ [الجمعة:10]. وإنما يقال للإنسان: إذا كنت تريد أن تسأل الله شيئاً فادعو الله قبل أن تسلم؛ لوجهين:الوجه الأول: أن هذا هو الذي أمر به الرسول ﷺ، فقال في التشهد: (إذا فرغ فليتخير من الدعاء ما شاء).ثانياً: أنك إذا كنت في الصلاة فإنك تناجي ربك، وإذا سلمت انتهت المناجاة، فهل الأفضل: أن تسأل الله في حال مناجاتك إياه، أو بعد انصرافك من المناجاة؟ الجواب: الأول، تدعو وأنت تناجي ربك.
📌ምላሽ፦ ከሰላት በኋላ ዱዐ ነብያዊ ሱና አይደለም። አላህም በቁርአኑ
فَإِذَا قَضَيْتُمُ الصَّلاةَ فَاذْكُرُوا اللَّهَ [النساء:103]
«ሰላትን ባጠናቀቃችሁም ግዜ አላህን አስታውሱ» ነው ያለው። ከሰላት በኋላ ዱዐ ሱና የሚሆነው በአንድ አጋጣሚ ብቻ ነው። እሱም ከሰላተል ኢስቲኻራ በኋላ ነው። ሰላተል ኢስቲኻራን አስመልክቶ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋልና « አንዳችሁ በአንድ ጉዳይ በተጨነቀ ግዜ ሁለት ረከዐ ይስገድ ከዛም ዱዐ ያድርግ» አሉ። ዱዐን ከሁለቱ ረከዐ ሰላት በኋላ አዘዙ። ግን ከዚህች ሰላት ውጪ ያለን ሰላት አገባዶ ዱዐ ማስከተል ሱና አይደለም። እጁን አንስቶም ይሁን ሳያነሳ፣ ከፈርድ ሰላት ኋላም ይሁን ከሱና። አላህም ያዘዘን እርሱን በማስታወስ (በዚክር) ነው።
فَإِذَا قَضَيْتُمُ الصَّلاةَ فَاذْكُرُوا اللَّهَ [النساء:103]
«ሰላትን ባገባደዳችሁም ግዜ አላህን አስታውሱ» ብሎ። በሱረቱል ጁሙዐህ ደግሞ
فَإِذَا قُضِيَتِ الصَّلاةُ فَانْتَشِرُوا فِي الْأَرْضِ وَابْتَغُوا مِنْ فَضْلِ اللَّهِ [الجمعة:10]
«ሰላትም በተጠናቀቀች ግዜ በምድር ላይ ተበተኑ: የአላህ ችሮታንም ፈልጉ» ብሏል። ዱዓ ማድረግ የፈለ ሰው ከሶላት ሳይወጣ [ ሳያሰላምት በፊት] ማድረግ ነው ያለበት አንደኛው ነብዩ በዚህ ስላዘሁ ሁለተኛው ደግሞ ወደ አላህ ይበልጥ ቅርብ የምትሆነው ሶላት ዉስጥ በሆንክበት ሰዓት ነው ...
لقاء الباب المفتوح [82] )
للشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله
‼️ ይህ ተግባር አብዛኛው ሰው ጋር የተሰራጨ ልማድ ሲሆን ከሱና ግን መሰረት የሌለው ተግባር ነው በመረጃ እንዳያችሁት ሱናን መከተን ደግሞ ስኬት ነው።
لَّقَدْ كَانَ لَكُمْ فِي رَسُولِ اللَّهِ أُسْوَةٌ حَسَنَةٌ لِّمَن كَانَ يَرْجُو اللَّهَ وَالْيَوْمَ الْآخِرَ وَذَكَرَ اللَّهَ كَثِيرًا
“ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው፣ አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አልላችሁ
Repost from ሁስነል ኹሉቅ ((𝑯𝑼𝑺𝑵𝑬𝑳_𝑲𝑯𝑼𝑳𝑼𝑲))
📚 ከሰላት በኋላ ዱዐ ማድረግ
🗳حكم الدعاء بعد الصلاة
السؤال: بعض الناس في صلاة الفرض يرفعون أيديهم بعد الدعاء فما رأيكم؟
🎤 በሸኽ ሷሊህ አልዑሰይሚን ረህመቱላሂ አለይሂ
📌ጥያቄ: አንዳንድ ቦታዎች ላይ ከፈርድ ሰላት በኋላ ሰጋጆች ለዱዐ እጃቸውን ያነሳሉ። ይህ እንዴት ይታያል?
الجواب:
الدعاء بعد الصلاة ليس بسنة، لأن الله تعالى قال: فَإِذَا قَضَيْتُمُ الصَّلاةَ فَاذْكُرُوا اللَّهَ [النساء:103] إلا في حالة واحدة وهي صلاة الاستخارة؛ لأن صلاة الاستخارة قال فيها النبي ﷺ:
(إذا هم أحدكم بأمر فليصل ركعتين ثم ليدعو) فجعل الدعاء بعد صلاة الركعتين، أما ما سواها من الصلوات فليس من السنة أن يدعو سواءً رفع يديه أم لم يرفع، وسواءً في الفريضة أو في النافلة؛ لأن الله أمر بذكره بعد انتهاء الصلاة، فقال سبحانه وتعالى:
فَإِذَا قَضَيْتُمُ الصَّلاةَ فَاذْكُرُوا اللَّهَ [النساء:103]، وقال في سورة الجمعة: فَإِذَا قُضِيَتِ الصَّلاةُ فَانْتَشِرُوا فِي الْأَرْضِ وَابْتَغُوا مِنْ فَضْلِ اللَّهِ [الجمعة:10]. وإنما يقال للإنسان: إذا كنت تريد أن تسأل الله شيئاً فادعو الله قبل أن تسلم؛ لوجهين:الوجه الأول: أن هذا هو الذي أمر به الرسول ﷺ، فقال في التشهد: (إذا فرغ فليتخير من الدعاء ما شاء).ثانياً: أنك إذا كنت في الصلاة فإنك تناجي ربك، وإذا سلمت انتهت المناجاة، فهل الأفضل: أن تسأل الله في حال مناجاتك إياه، أو بعد انصرافك من المناجاة؟ الجواب: الأول، تدعو وأنت تناجي ربك.
📌ምላሽ፦ ከሰላት በኋላ ዱዐ ነብያዊ ሱና አይደለም። አላህም በቁርአኑ
فَإِذَا قَضَيْتُمُ الصَّلاةَ فَاذْكُرُوا اللَّهَ [النساء:103]
«ሰላትን ባጠናቀቃችሁም ግዜ አላህን አስታውሱ» ነው ያለው። ከሰላት በኋላ ዱዐ ሱና የሚሆነው በአንድ አጋጣሚ ብቻ ነው። እሱም ከሰላተል ኢስቲኻራ በኋላ ነው። ሰላተል ኢስቲኻራን አስመልክቶ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋልና « አንዳችሁ በአንድ ጉዳይ በተጨነቀ ግዜ ሁለት ረከዐ ይስገድ ከዛም ዱዐ ያድርግ» አሉ። ዱዐን ከሁለቱ ረከዐ ሰላት በኋላ አዘዙ። ግን ከዚህች ሰላት ውጪ ያለን ሰላት አገባዶ ዱዐ ማስከተል ሱና አይደለም። እጁን አንስቶም ይሁን ሳያነሳ፣ ከፈርድ ሰላት ኋላም ይሁን ከሱና። አላህም ያዘዘን እርሱን በማስታወስ (በዚክር) ነው።
فَإِذَا قَضَيْتُمُ الصَّلاةَ فَاذْكُرُوا اللَّهَ [النساء:103]
«ሰላትን ባገባደዳችሁም ግዜ አላህን አስታውሱ» ብሎ። በሱረቱል ጁሙዐህ ደግሞ
فَإِذَا قُضِيَتِ الصَّلاةُ فَانْتَشِرُوا فِي الْأَرْضِ وَابْتَغُوا مِنْ فَضْلِ اللَّهِ [الجمعة:10]
«ሰላትም በተጠናቀቀች ግዜ በምድር ላይ ተበተኑ: የአላህ ችሮታንም ፈልጉ» ብሏል። ዱዓ ማድረግ የፈለ ሰው ከሶላት ሳይወጣ [ ሳያሰላምት በፊት] ማድረግ ነው ያለበት አንደኛው ነብዩ በዚህ ስላዘሁ ሁለተኛው ደግሞ ወደ አላህ ይበልጥ ቅርብ የምትሆነው ሶላት ዉስጥ በሆንክበት ሰዓት ነው ...
لقاء الباب المفتوح [82] )
للشيخ محمد بن صالح العثيمين رحمه الله
‼️ ይህ ተግባር አብዛኛው ሰው ጋር የተሰራጨ ልማድ ሲሆን ከሱና ግን መሰረት የሌለው ተግባር ነው በመረጃ እንዳያችሁት ሱናን መከተን ደግሞ ስኬት ነው።
لَّقَدْ كَانَ لَكُمْ فِي رَسُولِ اللَّهِ أُسْوَةٌ حَسَنَةٌ لِّمَن كَانَ يَرْجُو اللَّهَ وَالْيَوْمَ الْآخِرَ وَذَكَرَ اللَّهَ كَثِيرًا
“ለእናንተ አላህንና የመጨረሻውን ቀን የሚከጅል ለሆነ ሰው፣ አላህንም በብዙ ለሚያወሳ በአላህ መልዕክተኛ መልካም መከተል አልላችሁ
@husnel_khuluk
الله أكبـــــر .. الله أكبـــــر .. لا إله إلا الله ،
الله أكبـــــر .. الله أكبـــــر .. و لله الحمــد
السلام عليكم وراحمة الله وبركاتة
تقبل الله منا ومنكم صالح الأعمال وغفر الله لنا ولكم وكل عام وانتم بخير
و نسأل الله لنا و لكم التوفيق و السداد
اللهم اهدنا و اهد بنا و اجعلنا سببا لمن اهتدى
تكبيرات رائعه بطالب امير زينو حفظه الله وراعة وكثر امثاله
من مدرستة السلسبل حرسها الله
🕋ማራኪ ተክቢራ በመስጅደል ሰልሰቢል
🎙በተማሪ አሚር ዘይኑ አላህ ይጠብቀው
ዐብደላህ ኢብኑ ዑመርና አቡ ሁረይራህ
አሁን ያለንበት የዙል ሂጃ አስርት ቀናት
ላይ ወደ ገበያ ቦታዎች እየወጡ ተክቢራ
ይሉ ነበር ሰዎችም የእነሱን ተክቢራ
(አየሰሙ) አስታውሰው.ይሉ ነበር።
صحيح البخاري م٢/ ٠٢📓👉ምንጭ
الله أكبر
الله أكبر الله أكبر
لا إله إلا الله
الله أكبر الله أكبر
ولله الحمد
ይ🀄ላ🀄ሉን👇👇 share👇
┏━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┓
@IbnuZynu
@IbnuZynu
┗━ 🍃 ━━━━ 🍃 ━┛
{የዙል_ሂጃ አስር ቀናቶች ትሩፋት}
``
➧ ከዱንያ ቀናቶች ሁሉ በላጭ ናቸው።
➩ የአላህ መልዕክተኛ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በሀዲሳቸው እንዲህ ይላሉ፡–
=> "أَفْضَلُ أَيَّامِ الْدُّنْيَا أَيَّامُ الْعَشْرِ، يَعْنِي عَشْرُ ذِي الحْجَّةِ".
"ከዱንያ ቀናቶች ሁሉ በላጭ ቀናቶች አስሩ የዙል ሒጃ ቀናቶች ናቸው።"
➪ በሌላም ሀዲስ እንዲህ በማለት በእነዚህ ቀናቶች የሚሰራ ስራ ያለውን ደረጃ ያስቀምጣሉ።
«ما من أيام العمل الصالح فيهن أحب إلى الله من هذه الأيام العشر،
قالوا ولا الجهاد في سبيل الله؟ قال
ولا الجهاد في سبيل الله، إلاّ رجلا خرج بنفسه وماله فلم يرجع من ذلك بشيء»
«ከእነዚህ ከአስር ቀናቶች የበለጠ መልካም ስራ ወደ አላሁ ሱብሀነሁ ወተዐላ የሚወደድበት ቀን የለም። አሉ
ሰሀቦችም…
በአላህ መንገድ ላይ መታገል (መጋደል) ቢሆንም? ብለው ሲጠይቋቸው…
አው በአላህ መንገድ መታገል ቢሆንም ግን አንድ ሰው ሲቀር አሉ…
እሱም በአላህ መንገድ ለመታገል ነፍሱንም ንብረቱንም ይዞ ወጥቶ እስከ ንብረቱ እዛው የቀረ ሲቀር አሉ»
➩ እናንተ ሙስሊሞች ሆይ!
ለራሱ የሚጨነቅና ንቃተ ህሊና ያለው ሰው እንዲህ አይነት ብርቅዬ አጋጣሚዎችን በከንቱ አያሳልፍም።
➪ እኛንም አላህ ከሚጠቀሙ ያድርገንና በእነዚህ ቀናቶች ከዚህ በፊት ስናደርገው ከነበረው ለየት ባለ መልኩ ለመስራትና ለመጠቀም ራሳችንን ማነሳሳት አለብን እላለሁ።
➪ አላህን አብዝተን በማውሳት
ተህሊል፣ ተክቢር፣ ተስቢህ እና
ተህሚድ በማድረግ ወደ አሏህ መቃረብ አለብን።
➩ አላህን አብዝተን በመለመን
➪ ሰደቃን በማብዛት
➩ ቁርዐንን አብዝተን በማንበብ
➪ የጀምዐ ሰላትን በመጠባበቅ
➩ ተጨማሪ(ሱና) የሆኑ ሰላቶችን በመስገድ
➪ የቻልነው በመፆም እና አጠቃላይ ኸይር ከተባለ ነገር ሰብስበን ተጠቃሚ ለመሆን ልንተጋ ይገባናል።
➜ ታላቁ አሊም ኢብኑ ዑሰይሚን እንዳሉት
ብዙሃን ሰዎች የሚገርሙ ናቸው። ከረመዷን አሽረል አዋኺር ላይ የቻሉትን ያህል እየታገሉና እየሰሩ ይታያሉ ዙል ሂጃ ላይ ግን ምንም የተለየ ነገር ሲያከናውኑ አይታዩም በማለት ሀዘናቸውን ይገልፃሉ።
➲ ከፊል ኡለሞች ከረመዷን አሽረል አዋኺር የዙል ሂጃ አስር ቀናቶች እንደ ሚያስበልጡስ ስንቶቻችን እናውቃለን?
➽ ምንም እንኳን መስዐላው ዒብኑል ቀይም እንዳስቀመጡት……ቢሆንም
➼ ከለሊቶቻቸው አንፃር የረመዷን አሽረል አዋኺር ሲበልጡ…
➽ ከቀኖቻቸው አንፃር የዙልሂጃ አስር ቀናቶች ይበልጣሉ።
➼ ማለት የፈለኩት ግን…ምን አልባት በቀጣዩ አመት ላንደርስበት እንችላለን
ብዙሃን ለአምናው ደርሰው ለዘንድሮው መድረስ እንደተሳናቸው እኛም እድሉን ሳንጠቀምበት ሊያልፈን አይገባምና በተቻለን እንበራታ የሚል ጥቆማ ለመስጠት ያክል ነው።
በተለይ ደግሞ...‼
አለማችን በፊትና ባህር እየዋኘች ባለችበት በዚህ ወቅት፦
➻ አላህ አስፈሪ የሆነ የፀሀይ ግርዶሽን ያክል ክስተት እና ለብዙሀን ህይወት ጤንነት ማጣት ምክንያት የሆነ ኮሮና የሚባል ወረርሽኝ በሽታ እያሳየ በሚያስፈራራበት ጊዜ እንዲህ አይነት አጋጣሚዎችን ማግኘት ማለት ከእድለኝነትም በላይ እድለኝነት ነው እናም ነቃ ብለን እንጠቀምበት።
➺ በመጨረሻም ለዒደል አድሀ ኡዱህያ ማድረግ የሚፈልግ ሰው የዙል ሂጃ ወር ከገባ ጀምሮ ፀጉሩንም ይሁን ጥፍሩን ከመንካት መቆጠብ አለበት።
ልክ መልዕክተኛው ሰለሏሁ አለይሒ ወሰለም እንዳሉት፡–
"فأراد أحدكم أن يضحي فلا يأخذن من شعره ولا من بشرته ولا من ظفره شيئا"
"ከእናንተ አንዳቹ ኡዱህያ ለማድረግ ከፈለገ ከፀጉሩም ይሁን ከጥፍሩ ምንም ነገር እንዳይነካ"
አሏህ ከተጠቃሚወች ያድርገን አሚን
📝 kelifa [abuubeyda]
https://t.me/AbuImranAselefy]የዱንያ ቀናት ሁሉ ምርጦቹ ቀናት ነገ ሰኞ አንድ ብለው ይጀምራሉ። በነኚህ ቀናት ዉስጥ የሚሰሩ መልካም ሥራዎችን የሚበልጥ ምንም የለም። መልካም መሥራትን እናብዛ። መፆም፣ ሶደቃ መስጠት፣ ቁርኣን መቅራት፣ በጥሩ ማዘዝ፣ ከመጥፎ መከልከል፣ ዝምድናን መቀጠል፣ የታመሙትን መዘየር፣ ችግረኛን መርዳት፣ ወደ አላህ መንገድ መጣራት፣ ....
በአጠቃላይ መልካም የተባለ ሥራ ሁሉ።
