en
Feedback
ABG Lebu branch (G9 2018)

ABG Lebu branch (G9 2018)

Open in Telegram
1 478
Subscribers
-124 hours
+157 days
+4830 days
Posts Archive
ለአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቀቶቜ ለቡ ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀት ወላጆቜ በሙሉ፩ በቅድሚያ ዹኹበሹ ሰላምታቜን እያቀሚብን በመቀጠል ዚሚኚተሉትን ማስታወቂያ በትኩሚት እንድትኚታተሉ እናሳስባለን ። ᅵ
ለአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቀቶቜ ለቡ  ሁለተኛ ደሹጃ ትምህርት ቀት ወላጆቜ በሙሉ፩ በቅድሚያ ዹኹበሹ ሰላምታቜን እያቀሚብን በመቀጠል ዚሚኚተሉትን ማስታወቂያ በትኩሚት እንድትኚታተሉ እናሳስባለን ። 👉ዚነባር ተማሪዎቜ ምዝገባ ኹ9-15/11/2018ዓ.ም (ኹሐምሌ 9-15 ብቻ)መሆኑን አውቃቜሁ በተጠቀሰው ጊዜ እንድታስመዘግቡ ይሁን፡፡ ኚቅዳሜ እና እሁድ ውጪ 👉ለምዝገባ ስትመጡ በአሀዱ ዚባንክ ቁጥር 0000582310901 በተማሪዎቜ ID Number እና ሙሉ ስም ዹተጠቀሰውን ዚመስኚሚም ወርና ዚመመዝገቢያ ብር በመክፈል ደሹሰኝ መያዝ ፣ዚተማሪዎቜ ሁለት ጉርድ ፎቶ ግራፍ ፣ዚፍይዳ ካርድ ኮፒ፣ዚተማሪዎቜ ሪፓርት ካርድ ኮፒ እና ዚተማሪዎቜን ትክክለኛ ዚትውልድ ቀን እና ስም በፎርሙ ላይ መሙላት ያስፈልጋል ። 👉ዚ11ኛ -12ኛ ክፍል ዚክሚምት ትምህርት መርሃ ግብር ኹሐምሌ 6/2018 እስኚ ነሐሮ 29/2018 ዚሚሰጥ ሲሆን ሁሉም ተማሪ መገኘት ግዎታው ነው።(በክሚምት ትምህርት መርሃ ግብር ያልተሳተፈ ተማሪ በበጋ እንደማይቀጥል እንዲታወቅ) ክፍያ ለ 2ወር ዚአንድ ወር ዹመደበኛ ትምህርት ክፍያ -4750 ብር ብቻ ቀድሞ ሰኞ መኹፈል ይኖርበታል። 👉ዚ12ኛ ክፍል አስፈታኝ በመሆናቜን ለአንድ ሳምንት ትምህርቱ ዹሚሰጠው ፈለገ ነዋይ ት/ቀት ይሆናል። 👉ወደ 9 ኛ ክፍል ዚተዘዋወራቜሁ ተማሪዎቜ ዹ8ኛ ክፍል ዚሚኒስትሪ ካርድ ዋናው ስላልመጣ ዚውጀታቜሁን ኮፒ(ፕሪንት) ይዛቜሁ እንድትቀርቡ። 👉ዚመመዝገቢያ ሰዓት ጥዋት ኹ2:30 እስኚ 6:00 ኚሰዓት ኹ7:00 እስኚ 10:00 መሆኑን እንገልፃለን ። 👉ዝውውር ዚሞላቜሁ ወላጆቜ ኹ9/11/2018 ጀምሮ ትምህርት ቀት በመምጣት መሹጃ እንድትወስዱ ይሁን።መሚጃ ለመውሰድ ስትመጡ ዚተማሪ ፎቶ ግራፍ እንድታመጡ ይሁን።                 á‰µ/ቀቱ

ጥብቅ ማሳሰቢያ ✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝✝ ዹ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ዚማገናኚሪያ መርሃ-ግብር ዹሚጀምሹው ሰኞ ሐምሌ 6/18 በመሆኑ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ ኚወዲሁ እናሳስባለን። 👉 አለመማር አይፈቀድም 👉11ኛ ክፍሎቜ ዚምትማሩበትን ዚት/ዘርፍ በመምሚጥ (ማ/ሳይንስ ወይም ተ/ሳይንስ) በማለት እስኚ ሐሙስ ጠዋት 4:00 ድሚስ ተ/ሳይንስ በ0918334286 ለመ/ር ታዘብ ማ/ሳይንስ በ 0918820157 ለመ/ር ይብዛወርቅ እንድትልኩ እናሳስባለን። 👉ትምህርቱ ዚሚሰጥበትን ቊታ እና ዚክፍያ ሁኔታዎቜ ቀጣይ እናሳውቃለን። ት/ቀቱ

ዚአቡነ ጎርጎሪዮስ ሁ/ደ/ት/ቀት 👉በቀን 27/8/2018ዓ/ም ኚት/ቀቱ ዚአመቱን ማጠቃለያ መርሐ-ግብር በወይራ ቅርንጫፍ በደማቅ ሁኔታ አሳልፈናል። 👉ኚ23/10/18 እስኚ 10/10/18 ድሚስ ለቡ ቅርንጫፍ ት/ቀት 12ኛ ክፍል ተማሪዎቜን በማስፈተን ላይ ዹሚገኝ በመሆኑ ካርድ ያልወሰዳቜሁ ተማሪዎቜ እና ወላጆቜ በአፀደ ህጻናት ግቢ ብቻ በመጠቀም ኹሰኞ ጀምሮ አገልግሎት ማግኘት ትቜላላቜሁ ። 👉እለቱ ዚሚያሳዩ ፎቶዎቜ በጥቂቱ...

ሰላም ውድ ወላጆቜ /አሳዳጊዎቜ/ እንዎት ዋላቜሁ ዚትምህርት ቀትታቜን ዹ 12 ክፍል ተማሪዎቜ ሀገር አቀፍ ፈተና ስለሆኑ እና ትምህርት ቀቻቜን ዹመፈተኛ ጣቢያ ስለሆነ ዚውጀት መግለጫ ካርድ ዹሚሰጠው ቅዳሜ 27/10/2018 ዓ.ም በወይራ ቅርንጫፍ ትምህርት ቀት በመሆኑ ኚወዲሁ እንድትዘጋጁ በትህትና እናሳውቃለን ።

መሹጃ ✝✝✝✝✝✝✝✝ 👉ኚነገ 23/10/2018 ዓ.ም -10/11/2018 ዓ.ም ዹ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና በት/ቀታቜን ዚሚሰጥ ሲሆን በተጠቀሱት ቀናት ምንም አይነት አገልግሎት በቅርንጫፍ ት/ቀቱ ዚማይሰጥ መሆኑን እናሳውቃለን። 👉 ዚተማሪዎቜ ዚውጀት መግለጫ ካርድ ቅዳሜ ሰኔ 27/2018 ወይራ ቅርንጫፍ ግቢ ኹ3:00 ጀምሮ ዚሚሰጥ ይሆናል።

ሐምሌ 1 በዚህ ሊንክ ይመዝገቡ https:/esdros.com/a/new.admission/

አዲስ ተመዝጋቢዎቜ በበዹነ መሚብ ብቻ ያመልክቱ።አመለኚቱ ማለት ተመዘገቡ ማለት አይደለም።

ሁሉም ዚአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቀቶቜ ወላጆቜ ጉዳዩ፡- ዚእህትና ወንድም እንዲሁም ዚተማሪዎቜ ዝውውር ማመልኚቻ ጊዜ ማራዘምን ይመለኚታል። እንደሚታወቀው፣ በትምህርት ቀታቜን ዚሚካሄደው ዚእህትና ወንድም እንዲሁም ዚተማሪዎቜ ዝውውር ዚማመልኚት ሂደት ቀደም ሲል በተወሰነው ጊዜ ውስጥ እንዲጠናቀቅ ታቅዶ ነበር። ሆኖም ግን ሁሉም ወላጆቜ በበቂ ሁኔታ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማስቻል እና በብዙ ወላጆቜ በቀሹበው ጥያቄ መሠሚት፣ ዚእህትና ወንድም ምዝገባ እና ዚተማሪዎቜ ዝውውር ማመልኚቻ ጊዜ እስኚ 18/10/2018 ዓ.ም ምሜት ድሚስ እንዲራዘም ተወስኗል። በመሆኑም እስካሁን ምዝገባቜሁን ያላጠናቀቃቜሁ ወላጆቜ በተጠቀሰው ዹጊዜ ገደብ ውስጥ ሂደቱን እንድታጠናቅቁ በአክብሮት እናሳስባለን። ኹተጠቀሰው ዚመጚሚሻ ቀንና ሰዓት በኋላ ዚሚቀርቡ ማንኛውም ጥያቄዎቜ እንደማይስተናገዱ በአክብሮት እናሳውቃለን። [ለውድ ርዕሰ መምህራን በሙሉ ኹላይ ዹተላለፈውን መልዕክት ባላቜሁ አማራጭ ሁሉ በአስ቞ኳይ እንዲያውቁት አድርጉ። መልካም ቀን።

መሹጃ 👉ኚ9-11ኛ ክፍል ያላቜሁ ተማሪዎቜ ✝ዹፈተና ወሚቀት ሐሙስ 18/10/18 ኚጠዋቱ 2:30-5:00ዚሚሰጥ ይሆናል። 👉 ለፈተና ሲመጡ ዚትምህርት ቀት ዚደንብ ልብስ ብቻ መልበስ ይኖርባ቞ዋል። 👉ምንም አይነት ኀሌትሮኒክስ፣ኚት/ ቁሳቁስ ውጪ ይዞ መምጣት አይፈቀድም። 👉 በእለቱ ውጀታ቞ውን ኚመምህራኖቻ቞ው 100% ማሚጋገጥ ይኖርባ቞ዋል(ቜግሮቜ ካሉ በእለቱ ማስተካኚል ይጠበቅባ቞ዋል) 👉 ዹ11ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ኚወዲሁ ዹማ/ሳይንስ እና ዹተ/ሳይንስ ምርጫ በመኖሩ ቀድማቜሁ ኚልጆቜ ጋር ውይይት በማድሚግ እንድትወስኑ። 👉ዚ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ዚክሚምት መደበኛ ትምህርት እንዳለ ኚመንግስት ለማወቅ ቜለናል ለዚህ ዝግጅት ኚወዲሁ እንዲደሚግ እናሳስባለን ። 👉በቀጣይ ሰርተፍኬት ዚሚሰጥበትን፣ምዝገባ ዚሚኚናወንበት እና ዚክሚምት መርሃ-ግብር ተግባር ዚምናሳውቅ ይሆናል። ት/ቀቱ

ውድ ዚአቡነ ጎርጎሪዮስ ት/ቀት ተማሪዎቜ ፊ ኚቀተ መጜሐፍት ዚተዋሳቜሁትን መጜሐፍት ፈተና ማጠቃለያ እለት ማለትም እስኚ 16/2018ዓ.ም ድሚስ ለቀተ መጜሐፍት ተጠሪ መ/ር እንድታስሚክቡ እናሳስባለን። 👉 12ኛ ክፍል ተማሪዎቜ ለሙኚራ ፈተና ስትመጡ ዚተዋሳቜሁት መጜሐፍት፣ዚተርም እና ዚት/ማላቂያ መርሃ-ግብር ክፍያ አጠናቃቜሁ እና አድሚሜን ካርድ ተይዞ መቅሚብ ይኖርበታል።

ውድ ወላጆቜ ኹነገ 10/2018 ዓ.ም ጀምሮ ዹሁለተኛ መንፈቀ ዓመት ዚማጠቃለያ ፈተና ይሰጣል። በመሆኑም ተማሪዎቜ ኚጠዋት 5:00ላይ ፈተና ዚሚጚርሱ ይሆናሉ። 👉በወላጅ፣ በእግር ዚሚሄዱ ተማሪዎቜን በተባለው ሰዓት እንዲወስዱ እያሳወቅንፀኚወይራ አኚባቢ ውጪ ዚሚመጡ ዚተማሪዎቜ ሰርቢስ ኹአንደኛ ደሹጃ ተማሪዎቜ ጋር በጋራ ዚሚስተናገዱ ኹሆነ ኹ1-8ኛ ትምህርት ሙሉ ቀን በመሆኑ እና ዹ6ኛ እና 8ኛ ሚኒስትሪ ፈተና በመኖሩ እስኚ 9:30ት/ቀት ቅጥር ግቢ መቆዚተት ዚሚቜሉ ይሆናል። 👉ቀተ መጜሐፍት ቀትም እስኚ 9:30 አገልግሎት ይሰጣ቞ዋል።

2018_E_C_2nd_Semester_Grade_9_Grade_11_Revised_Final_Exam_Provision.docx0.67 KB

Sĵ

✔ተማሪዎቜ ፈተና እዚተፈተኑ ባለበት ወቅት ➖ ዹተሹጋጋ መንፈስ መያዝ፣ ➖ ጊዜን በአግባቡ ማስተዳደር ➖ ጥያቄዎቜን በጥንቃቄ ማንበብ እና እርግጠኛ ያልሆኑባ቞ውን ክፍሎቜ ማለፍ ዚተሻለ ውጀት ለማምጣ
✔ተማሪዎቜ ፈተና እዚተፈተኑ ባለበት ወቅት ➖
ዹተሹጋጋ መንፈስ መያዝ፣ ➖ ጊዜን በአግባቡ ማስተዳደር ➖ ጥያቄዎቜን በጥንቃቄ ማንበብ እና እርግጠኛ ያልሆኑባ቞ውን ክፍሎቜ ማለፍ ዚተሻለ ውጀት ለማምጣት ይሚዳል
✅ፈተናውን በአግባቡ ለመወጣት ዚሚኚተሉትን ዋና ዋና ነጥቊቜ ተግባራዊ ማድሚግ ይገባል፡: 👉መመሪያዎቜን በጥንቃቄ ያንብቡ፡ ✅ዹፈተናውን ወሚቀት መመሪያ እና ጥያቄዎቜ ኹመጀመርዎ በፊት በደንብ መሚዳት ስህተቶቜን ይቀንሳል:: 👉ጊዜን በአግባቡ ይመድቡ፡ ✅ለእያንዳንዱ ጥያቄ ዹሚሆን ጊዜ በማስላት በአንድ ኚባድ ጥያቄ ላይ ብዙ ጊዜ አያጥፉ። ጊዜ እንዳይባክን ዚሚያውቋ቞ውን ጥያቄዎቜ አስቀድመው ይስሩ:: 👉አስ቞ጋሪ ጥያቄዎቜን ይለፉ፡ ✅መልሱን ወዲያውኑ ማግኘት ያልቻሉትን ጥያቄ ምልክት በማድሚግ አቆይተው ይመለሱባ቞ው:: 👉መሚጋጋትን ያዳብሩ፡ በፈተና ወቅት ጭንቀት ኚተሰማዎት ጥልቅ ትንፋሜ በመውሰድ አእምሮዎን ያሚጋጉ:: 👉መልሶቜን ይኚልሱ፡ ✅ፈተናውን ኚማስሚኚብዎ በፊት ዚተሰሩትን መልሶቜ በሙሉ በስርዓቱ መፈተሜዎን ያሚጋግጡ::

ዹግዕዝ ሙኚራ ነገ በ9/2018 ዓ.ም ኚሰዓት ዚሚሰጥ በመሆኑ ዝግጅት እንድታደርጉ።

1. ለእህት ወንድም አመልካ቟ቜ (Sibling applicants) ቀጥሎ ያለውን ሊንክ ተጠቅመው ያመልክቱ። 👇👇👇 https://esdros.com/a/admission-request/ 2. ኚቅርንጫፍ ቅርንጫፍ ዝውውር አመልካ቟ቜ (Transfer requesting) ደግሞ ኹዚህ በታቜ ያለውን ሊንክ በመጠቀም ያመልክቱ። 👇👇👇👇👇👇 https://esdros.com/a/transfer-request/

ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም ለሁሉም ዚአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቀቶቜ ባሉበት ጉዳዪ: ዹ2019ዓ.ም ዚአቡነ ጎርጎርስ ት/ቀት ዚነባር ተማሪዎቜ እህት ወንድም ዹሆኑ ዚጀማሪ አመልካ቟ቜ እና ዚነባር ተማሪዎቜ ዝውውር ጥያቄን ይመለኚታል ዹ2019 ዓ.ም ዚነባር ተማሪዎቜ እህት ወንድም ዹሆኑ ዚጀማሪ አመልካ቟ቜም ሆነ ዚነባር ተማሪዎቜ ዝውውር ጥያቄ ዹሚኹናወነው በበይነ መሚብ (online) ነው። ስለሆነም ኹዚህ በታቜ ተያይዞ ዹተላኹውን ሊንክ በመጠቀም እስኚ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ድሚስ ባለው ጊዜ እንድታመለክቱ በእዚገለጜን ኹሰኔ 15 ቀን 2018ዓ.ም በኋላ ሲስተሙ ዝግ ስለሚደሚግ ዚእህት ወንድም አመልካ቟቟ንም ሆነ ዚነባር ተማሪዎቜን ዹዝውውር ጥያቄ ዚማናስተናግድ መሆኑን በአክብሮት ኚወዲሁ ለማሳወቅ እንወዳለን። ማሳሰቢያ፡ 1) በዚህ ዚቅድመ ምዝገባ ሂደት ዚተለዩ ዚነባር እህት ወንድም አመልካ቟ቜ መደበኛ ምዝገባ ዹሚኹናወነው ኚት/ቢሮ ወይም ኚት/ሚኒስ቎ር በሚወርደው ዚምዝገባ ዹጊዜ ሰሌዳ በመሆኑ ማመልኚት ማለት መመዝገብ ማለት አይደለም። ዚነባር ተማሪዎቜ እህትና ወንድም ሆነው በጀማሪ ዹክፍል ደሹጃ ዚሚያመለክቱ ወላጆቜ ዚሚያመለክተው ልጅ ዚነባሩ ተማሪ እህት ወይም ወንድም መሆኑን ዚሚያሳይ ህጋዊ ማስሚጃ በተጠዹቁ ጊዜ ማቅሚብ ዚግድ ይሆናል።

2018_E_C_2nd_Semester_Grade_9_Grade_11_Revised_Final_Exam_Provision.pdf4.14 KB

ውድ ወላጆቜ(አሳዳጊዎቜ ) 👉 ት/ቀታቜን አስፈታኝ እንዲሆን ዚቻልነውን ያክል ጥሚት አድርገን ተማሪዎቻቜን በለመዱት ግቢያ቞ው እንዲፈተኑ ዹተወሰነ ሲሆን :- ት/ቀታቜን 👉 ዚኔትወርክ ዝርጋታ፣30 መፈተኛ ኮንፒውተር፣ፈተናው ዹሚሰጠዉ በጄኔሬተር በመሆኑ ጄኔሬተር ነዳጅ፣ኔትወርክ ስፒድ ማሳደግን እዚሰራ ዹሚገኝ ሲሆን ኚወላጆቜ ጋር ዹሚጠበቅ ላፕቶፕ ቀድሞ በወጣው መስፈርት መሰሚት ዹሚጠቀበቅ ይሆናል። 👉ቀድሞ ሙኚራ ፈተናዎቜ ስለሚሰጡ እና ዚሚጫን ሶፍትዌር በመኖሩ ነገ አርብ ዹመፈተኛ ማ቎ሪያሎቜን ለት/ቀት ማስገባት ይኖርባቹኋል። 👉ኚሰኞ ግንቊት24-26እሮብ ድሚስ ለ3ቀናት ትምህርት እማይኖር መሆኑን መንግስት አሳውቆናል። 👉ቅዳሜ ትምህርት በነበሹው መልኩ ተጠናክሮ ዚሚቀጥል ይሆናል።መደበኛ እና ዚማጠቃለያ ትምህርት ክፍያ አለባቜሁ ወላጆቜ ኚወዲሁ እንድታጠናቅቁ። 👉ኚ9-11ኛ ክፍል ዚማጠቃለያ ፈተና ሰኔ10 ጀምሮ ዚሚሰጥ በመሆኑ ኚወዲሁ ዚተማራቜሁትን በመኚለስ ያሉትን ጊዜያት ትኩሚት እንድትሰጡ እናሳስባለን። ት/ቀቱ

ABG Lebu branch (G9 2018) - Statistics & analytics of Telegram channel @abgslebubg9