fa
Feedback
ABG Lebu branch (G9 2018)

ABG Lebu branch (G9 2018)

رفتن به کانال در Telegram
1 546
مشترکین
+124 ساعت
+207 روز
+10730 روز
آرشیو پست ها
photo content

photo content
+4

መረጃ ✝✝✝✝✝ ውድ የ2018ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተማሪዎቻችን የቅድመ ግቢ ጉባኤ መዝጊያ መርሃግብር ዛሬ 22/11/18 የአባታችንን የአቡነ ጎርጎሪዮስ 36ኛ ዓመት ዕረፍታቸው መታሰቢያ ምክንያት በማድረግ በቦሌ አቡነ ጎርጎሪዮስ ቤተ ክርስቲያን ሔደን ዘክረናል ፤ለመምህራኖቻቸው፣ለአስተዳደር አካላት እንዲሁም የቀድሞ የለቡ አቡነ ጎርጎሪዮስ ተማሪዎች እለቱን አስመልክቶ ዝክር፣መንፈሳዊ ትምህርት እና በዝማሬ ስናመሰግን ውለናል። 👉ለዚህ መልካም ተግባር ለለፋችሁ፣ ለደከማችሁ ተማሪዎቻችን ዋጋችሁን እግዚብሔር ይክፈላችሁ ።

ስማችሁ የተዘረዘራችሁ ተማሪዎች እስካሁን ትምህርት ያልጀመራችሁ በመሆኑ ከቀን21/11/18 በኃላ ለትምህርት መምጣት እንደማይቻል እናሳውቃለን።
ስማችሁ የተዘረዘራችሁ ተማሪዎች እስካሁን ትምህርት ያልጀመራችሁ በመሆኑ ከቀን21/11/18 በኃላ ለትምህርት መምጣት እንደማይቻል እናሳውቃለን።

ለ12ኛ ክፍል የ2019ዓ.ም ተማሪዎች 👉የክረምት ትምህርት ያልጀመራችሁ ተማሪዎች ከሰኞ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም መጀመር ግዴታ መሆኑን እያሳወቅን ይህን መልዕክት ሳትቀበሉ ላልመጣችሁ ተማሪዎች ት/ቤቱ ሐላፊነት አይመስድም።

ለውድ የአቡነ ጎርጎርዮስ ትምህርት ቤት ነባር የተማሪ ወላጆች በሙሉ። ከሁሉ አስቀድመን የከበረ ሰላምታችን በያላችሁበት ይድረስ። የ2019 ዓ.ም. የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከሐምሌ 6 እስከ 10 ቀን 2018 ዓ.ም. እንዲካሄድ ታቅዶ ቢጀምርም ያልተመዘገቡ ተማሪዎች በመኖራቸው እና ለወላጆች ተጨማሪ ዕድል ለመስጠት ሲባል የምዝገባው ጊዜ ለተጨማሪ ቀናት ተራዝሞ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅት ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ተማሪዎችን የመቀበል ሂደት እየተካሄደ በመሆኑ ያሉትን ክፍት ቦታዎች በትክክል ለመለየት የነባር ተማሪዎች ምዝገባን በአፋጣኝ ማጠናቀቅ አስፈላጊ ሆኗል። ስለሆነም የሁሉም ቅርንጫፎች የነባር ተማሪዎች የመጨረሻ ምዝገባ እስከ ሐምሌ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ የተራዘመ መሆኑን እናሳውቃለን። እባክዎ ልጅዎን እስከ ሰኞ ሐምሌ 20 ቀን 2018ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ብቻ በሚማርበት ቅርንጫፍ ትምህርት ቤት በመቅረብ ምዝገባውን እንዲያጠናቅቁ በአክብሮት እንጠይቃለን። ከተጠቀሰው የመጨረሻ ቀንና ሰዓት በኋላ ያልተመዘገቡ ነባር ተማሪዎች በፈቃዳቸው እንደለቀቁ በመቆጠር በክፍት ቦታው አዲስ አመልካች ተማሪዎችን የምንቀበልበት መሆኑን በጥብቅ እናሳውቃለን። ስለ ትብብርዎ እናመሰግናለን። የዋናው መሥሪያ ቤት የተማሪዎች ምዝገባና ቅበላ ኮሚቴ

photo content

photo content

ከዚህ በላይ ስማችሁ የተዘረዘራችሁ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች የትምህርት ማላቂያ ስትራቴጂ(ከሐምሌ6-እስከ ነሐሴ 29)ላይ እስካሁን በት/ቤት መማር ማስተር ላይ ያልተገኛችሁ በመሆኑ ከሰኞ 20/11/18 ትምህርት ገበታችሁ ላይ ካልተገኛችሁ ት/ቤቱ ሀላፊነት የማይወስድ መሆኑን እናሳውቃለን ።

አስቸኳይ ማስታወቂያ ለነባር ተማሪ ወላጆች ውድ ወላጆች የነባር ተማሪዎች ምዝገባ የመጨረሻ ቀን ዛሬ ማለትም በቀን 15/11/2018 ዓ.ም ተጠናቋል። ሆኖም ሐሙስ እና አርብ (ሐምሌ 16,17/2018)ለመጨረሻ ጊዜ በወላጆች ጥያቄ መሰረት በመራዘሙ እንድታስመዘግቡ ስንል በጥብቅ እናሳስባለን ። በተጠቀሰው ቀን ገደብ ያላስመዘገበ ወላጅ እንደለቀቀ በመቁጠር ከሰኞ ሐምሌ 20/2018 ዓ.ም በምትኩ አዲስ ተማሪዎችን የምንቀበል መሆኑን እናሳውቃለን ።           ትምህርት ቤቱ

ከላይየ የተላከው መልዕክት ከወይራ ወደ 9ኛ ክፍል የምትመዘገቡ ተማሪዎችን አይመለከትም።

photo content

👉ወደ የአቡነጎርጎሪዮስ 2ኛ ደረጃ ለቡ ቅርንጫፍ ከተለያዮ ቅርንጫፍ ት/ቤቶች የተዘዋወራችሁ ተማሪዎች ከነበራችሁበት ት/ቤት በቀን 15-16/11/18 ብቻ 👉ክሊራንስ(መሸኛ)፣ከ10-12ኛ ክፍል ውጪ ትራንስክሪፕት፣ ለ9ኛ ክፍል የሚኒስትሪ መልቀቂያ ኮፒ(ፕሪንት)፣ የተማሪ 2ፎቶ ግራፍ በመያዝ በህብረት ባንክ ሒሳብ ቁጥር[4461811632202013]በተማሪው ስምና ቀድሞ በነበረው መለያ ቁጥር ብቻ ክፍለው ት/ቤት ለምዝገባ እንድትመጡ እናሳስባለን።

የነባር ተማሪ ምዝገባ ነገ የመጨረሻ ቀን ነዉ።

ለአቡነ ጎርጎሪዮሰ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለቡ ቅርንጫፍ ከ10ኛ ከፍል ወደ 11ኛ ክፍል እና ከ 11 ክፍል ወደ 12ኛ ክፍል የተዛወራችሁ ተማሪዎች በሙሉ በ 2018 ዓም በክረምት ወራት ማጠናከሪያ ትምህርት በፈለገ ነዋይ ትምህርት ቤት ለ አንድ ሳምንት እየተሰጠ እንደነበር ይታወቃል ። ነገር ግን ከነገ ሰኞ 13/11/2018 ዓም ጀምሮ ትምህርቱ የሚሰጠው በአቡነ ጎርጎሪዮስ ትምህርት ቤት ሰለሆነ ነገ ጠዋት በ 2:00( ሁለት ሰዓት)  እንድትገኙ እናሳስባለን። 👉ማሳሰቢያ: ዩኒፎርም መልበስ ግዴታ ነው ፤ ሞባይል መያዝ የተከለከለ ነው፤የመማሪያ ደብተር መያዝ ይጠበቅባችኋል።መቅረት በፍጹም አይቻልም።

photo content

👉የመመዝገቢያ ሰዓት ጥዋት ከ2:30 እስከ 6:00 ከሰዓት ከ7:00 እስከ 10:00 መሆኑን እንገልፃለን ።

👉የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ከ9-15/11/2018ዓ.ም (ከሐምሌ 9-15 ብቻ)መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሰው ጊዜ እንድታስመዘግቡ ይሁን፡፡ ከቅዳሜ እና እሁድ ውጪ 👉ለምዝገባ ስትመጡ በአሀዱ የባንክ ቁጥር 0000582310901 በተማሪዎች ID Number እና ሙሉ ስም የተጠቀሰውን የመስከረም ወርና የመመዝገቢያ ብር በመክፈል ደረሰኝ መያዝ ፣የተማሪዎች ሁለት ጉርድ ፎቶ ግራፍ  ፣የፍይዳ ካርድ ኮፒ፣የተማሪዎች ሪፓርት ካርድ ኮፒ እና የተማሪዎችን ትክክለኛ የትውልድ ቀን እና ስም በፎርሙ ላይ መሙላት ያስፈልጋል ።

የ2019 ዓ.ም የነባር የተማሪዎች ምዝገባ ነገ ጠዋት 3:00 የሚጀመር ይሆናል። 👉9ኛ ተማሪዎች ነገ የ8ኛ ክፍል የሚመዘገቡ ተማሪዎች የወላጅ የውጤት ፕሪንት ፣ ወይራ የሚማሩ ቅናሽ ያላቸው ተማሪዎች ከሆኑ ከወይራ ቅርንጫፍ መረጃ ይዘው እንዲሁም የተማሪዎቹን ነባር መለያ ቁጥር ያስፈልጋሉ። 👉 ለወይራ ቅርንጫፍ ለምትመጡ ወላጆች ክፍያ በአሐዱ ባንክ በመሆኑ ዳሽን ክፍያ እንዳትፈጽሙ።