1 095
Subscribers
+424 hours
+267 days
+2530 days
Posts Archive
ለጥንቃቄ!
ካናዳን ጨምሮ በተለያዩ የአውሮፓ ሀገራት ለሥራ ዜጎችን እንልካለን፡፡ ለዚህም ከሚመለከታቸው አካላት ፍቃድ አግኝተናል በሚል በተለያዩ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ህገ-ወጥ ማስታወቂያዎችን በማሰራጫት ህብረተሰቡን ላላስፈላጊ ወጪና እንግልት እየዳረጉ በመሆኑ መሰል የማጭበርበር ተግባር እየፈፀሙ የሚገኙ አካላትን በህግ ተጠያቂ ለማድረግ ሚኒስቴር መስሪያ ቤታችን በትኩረት እየሰራ ይገኛል፡፡
በውጭ ሀገር ስራ ስምሪቱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ወደ አውሮፓና አሜሪካ ዜጎችን ለሥራ ለማሰማራት ለየትኛውም አካል የሰጠው ውክልና የሌለ መሆኑን እየገለጽን ዜጎቻችን በስምሪቱ ተጠቃሚ ለመሆን ህጋዊ አማራጮችን ብቻ በመጠቀም ካላስፈላጊ ወጪ፣ እንግልትና ሌሎች አስከፊ አደጋዎች ራሳቸውን እንዲጠብቁ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡
የሁለትየሽ ስምምነት በተፈረመባቸው መዳረሻ ሀገራት የሥራ ዕድል ማግኘት ከፈለጉ የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ (lmis.gov.et) በመጠቀም የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት ላይ በመመዝገብ ደህንነቱ የተረጋገጠ የውጭ ሀገር ሥራ ስምሪት ተጠቃሚ ይሁኑ፡፡
Repost from Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት ከተጀመረበት ጊዜ አንስቶ በተከናወነው የፕሮጀክቱ አፈፃፀም ዙሪያ
ከባለድርሻ አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።
በመድረኩ የADRA ኢትዮጵያ ፕሮጀክት አጠቃላይ አፈፃፀም በፕሮጀክቱ ተወካይ በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በመጀመሪያ ዙር ስልጠና ላይ የታዩትን ጠንካራ ጎኖች እንዲሁም ያጋጠሙ ተግዳሮቶች ጭምር በሪፖርቱ ተመላክቷል።
በዚህም በመጀመርያ ዙር የፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት ያጋጠሙ ተግዳሮቶች በቀጣይ ለሚሰጠው ስልጠና እንቅፋት እንዳይሆኑ ከወዲሁ ለማስተካከል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመምከር የመፍትሄ አቅጣጫዋችን ማስቀመጥ ተችሏል።
መድረኩ ቀጥሎም እንደ አገር አዲስ የሆነው የሶላር ቴክኒሺያን እና ኤክስፐርት የስራ መዘርዝር 'JOB BOX ' ሰነድ ከሲቪል ሰርቪስ በመጣ ባለሙያ የቀረበ ሲሆን ሰነዱንም የሚመለከታቸው ተቋማት ሁኔታውን በደንብ ገምግመው ግብረመልስ ተሰቶበታል።
በቀጣይም የተሰራው የJOB BOX ሰነድ እንዲፀድቅና የሶላር ፒቪ ተጠቃሚ ተቋማት የሶላር ኤክስፐርት/ ቴክኒሺያን በመቅጠር የሶላር ዘርፍ ላይ ያለውን ከፍተኛ ክፍተት መሙላት እንደሚጠበቅባቸው የተገለፀ ሲሆን ይህም በADRA ፕሮጀክት የሰለጠኑ ባለሞያዎችም ከሚከፈትላቸው የስራ እድልም ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደላድል ይፈጥራልም ተብሏል።
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 13/2017 ዓ.ም
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በአገልግሎት ዘርፍ ላይ ከተሰማሩ ትምህርት ቤቶችና ሆቴሎች ለተወጣጡ አሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት በስራ ሁኔታ እና በሙያ ደህንነትና ጤንነት ላይ ስልጠና ሰጠ።
በዚህም ስልጠና በዋናነት መሰረታዊ የሥራ ሁኔታ በአሰሪና ሰራተኛው መሃል ያሉ ጠቅላላ ግንኙነቶች የሰራተኛውን የቅጥር ሁኔታ፣ የስራ ሰዓት እና የሰራተኛውን ጥቅማጥቅም የሚመለከቱ ጉዳዮች በአሰሪና ሰራተኛ አዋጁ 1156/2011 ላይ በተደነገገው መሠረት ከላይ የተጠቀሱት ነጥቦች ህግና ስርዓታቸው ተከብሮ የአሰሪና ሰራተኛው ግንኙነት ጤናማ የሚሆንበትና ሰላማዊ የስራ ከባቢ እንዲኖረው ግንዛቤ የሚፈጥርላቸው ሆኗል፡፡
በተጨማሪ የሥራ ቦታዎች ምቹ፣ ጤናማና ከአደጋ የተጠበቁ እንዲሆኑ በማስቻል ምርታማነትን ከማረጋገጥ አኳያ ከሙያ ደህንነት እና ጤንነት አጠባበቅ አንፃር ስልጠና የተሰጠ ሲሆን በዚህም ለግንዛቤ ያክል የአሠሪና ሠራተኛ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 ላይ በተመለከተው መሰረት የሙያ ደህንነትና ጤንነትን በተመለከተ አሠሪዎች፡-
🔑 ሠራተኞች የሚሰሩት ሥራ ሊያስከትልባቸው ስለሚችለው አደጋ እንዲሁም በጤንነት ላይ የሚደርስ ጉዳትን ለማስወገድ ስለሚያስፈልገው ጥንቃቄ ተገቢውን እርምጃ ይወስዳሉ፣
🔑 የአደጋ ተከላካይ ሠራተኛ ይመድባሉ፤ የሙያ ደኅንነትና ጤንነት ኮሚቴ ያቋቁማሉ፣
🔑 ለሠራተኞች የአደጋ መከላከያ መሣሪያ ልብስና ሌሎች ቁሳቁሶችን ያቀርባሉ፤ ስለአጠቃቀሙም መመሪያ ይሰጣሉ፣
🔑 በሥራ ምክንያት የሚመጡ በሽታዎችንና አደጋዎችን ይመዘግባሉ፤ ለሥራ ሁኔታዎች መቆጣጠሪያ አገልግሎት ያሳውቃሉ፣
🔑 እንደሥራው ጠባይ አዲስ ለሚቀጠሩ ሠራተኞች በራሳቸው ወጪ የጤና ምርመራ እንዲካሄድላቸው ያደርጋሉ፣
🔑 በአደገኛ ሥራ ላይ የሚሰሩ ሠራተኞች እንደአስፈላጊነቱ የጤና ምርመራ እንዲያገኙ ያደርጋሉ፣
🔑 ሆኖም ይህ ምርመራ ኢትዮጵያ ያፀደቀችው የዓለም አቀፍ ስምምነት ካላስገደደ በስተቀር የኤች.አይ.ቪ/ ኤድስ ምርመራን አይጨምርም፤
🔑 የድርጅቱ የሥራ ቦታና ግቢ በሠራተኞች ደኅንነትና ጤንነት ላይ አደጋ የማያስከትል መሆኑን ያረጋግጣሉ፣
🔑 በድርጅቱ ልዩ ልዩ የሥራ ሂደት በሚገኙ ፊዚካላዊ፣ ኬሚካላዊ፣ ባዮሎጂካዊ፣ ኢርጎኖሚካዊና ሥነ ልቦናዊ ምንጮችና ምክንያቶች ሳቢያ በሠራተኞች ደኅንነትና ጤንነት ላይ ጉዳት እንዳይደርስ ተገቢውን ጥንቃቄ የማድረግ ግዴታ አለባቸው፡፡
በመሆኑም የሠራተኞችን የሙያ ደህንነትና ጤንነት በማረጋገጥ ጤናማ አምራች ዜጋ ለመፍጠር በትኩረት እየተሰራ መሆኑን የገለፁት በቢሮው የአሠሪና ሠራተኛ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ኢብራሂም ይህ ስልጠና በብዙ መልኩ አሠሪና ሠራተኛው አዋጁ ባስቀመጠው የሙያ ደህንነትና ጤንነት መብትና ግዴታቸውን ተረድተው የሚያከብሩበትንና የሚያስከብሩበትን ብሎም የጋራ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በመውሰዳቸው በቀጣይ ደህንነትና ጤንነቱ የተጠበቀ ሙያተኛና ምርታማ የሆኑ ተቋማትን መፍጠር ያስችላቸዋል ብለዋል ፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 12/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+5
የኢንተርፕሩነርሺፕና የንግድ ሥራ ክህሎት ስልጠና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛ ስልጠናቸውን ለሚያጠናቅቁ ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው እለት መሰጠት ተጀመረ፡፡
ሰልጣኝ ተማሪዎች በኮሌጅ ውስጥ የነበራቸውን ትምህርታቸውና ስልጠና አጠናቀው ሲወጡ የግላቸውን ስራ ፈጥረው ራሳቸውን፣ ቤተሰባቸውንና ብሎም አገራቸውን እንዲጠቅሙ ከመደበኛው ስልጠና በዘለለ የኢንተርፕሩነርሺፕና የንግድ ሥራ ክህሎት ስልጠና መስጠት አስፈላጊ ነው፡፡ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ሰልጣኝ ተማሪዎች ከቅጥር ይልቅ ስራ ፈጣሪ እንዲሆኑ ማስቻል ዋና አላማቸው ስለሆነ ሁሉም አካላት ለዚህ ስራ ተረባርቦ መስራት እንደሚገባ በስልጠና ወቅት ተገልጿል፡፡
በዛሬው እለት እየተሰጠ የሚገኘው የኢንተርፕሩነርሺፕና የንግድ ሥራ ክህሎት ስልጠና በኢንተርፕርነርሺፕ ልማት ኢንስቲትዩት (EDI) እና በኮሌጁ የተዘጋጀ ነው። የስልጠናውም ለ4 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ እንደሆነ በስልጠናው ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+2
TVT Harmonized ሰነድ ላይ ትኩረት ያደረገ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሚገኙ የትምህርት ክፍል ተጠሪዎችና ለስልጠና አስተባባሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ተጀመረ፡፡
የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመምራትና ትግበራውንም ወጥነት ባለው መልኩ በጥራት ለመፈጸም ቅንጅታዊ ስራዎች የሚመሩበት ሰነድ በ2016 ዓ.ም መዘጋጀቱ የሚታወስ ሲሆን ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች፣የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች የስልጠና አስተባባሪዎች እንዲሁም መምህራን በትምህርትና ስልጠናው ውስጥ ያላቸውን ድርሻ ላስገንዘብ አላማውን ያደረገ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እንደሆነም በስልጠናው ወቅት ማወቅ ተችሏል፡፡
የTVT Harmonized ሰነድ ላይ ትኩረቱን ያደረገው ስልጠና በቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲው የሰልጣኝ ልማትና የአሰልጣኝ ልማት ዳይሬክቶሬቶች በቅንጅት ተካሂዷል፡፡ስልጠናውም እስከ ህዳር 13/2017 ዓ.ም ድረስ የሚቆይ ይሆናል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር12/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+5
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ቢሮ አዘጋጅነት ለጥቃቅንና አነስተኛ፣ መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች ስለሚሰጠው የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ድጋፍ ላይ ያተኮረ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር ተከናወነ፡፡
በውይይት መድረኩ ላይ የተገኙትና ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ እንዳሉት የ2016 ዓ.ም አፈፃፀምን መነሻ በማድረግና የተለዩ ችግሮችን በመለየት በ2017 በጀት ዓመት የተሸለ አፈጻጸም እንዲኖረን ባለድርሻ አካላት ተባብረን በጋራ ልንሰራ ይገባናል ብለዋል፡፡
አያይዘውም የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ስራ በኮሌጆች ብቻ ተፈጻሚ የሚሆን ሳይሆን ባለድርሻ አካላት በጋራ በመሆን በሚከውኑት ተግባር ነው ለውጥ የሚመጣው ስለዚህም በዘንድሮ አመት በተሰራ የኢንተርፕራይዞች የፍላጎት ዳሰሳና ጥናት ላይ መሰረት በማድረግ ልንሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ኢንተርፕራይዞችም ከተለመደው አሰራር በመውጣት የሚደረግላቸውን ድጋፍ በመቀበል ውጤት ለማስመዝገብ ተግተው ሊሰሩ ይገባል ብለዋል፡፡
በመጨረሻም የ2016 ዓ.ም የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አፈፃፀም ላይ፣ የ2017 ዓ.ም በተሰራ የዳሰሳ ጥናት እና በቀጣይ ስለሚደረግላቸው ድጋፍ እና የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የሙያ ብቃት ምዘናን በተመለከተ አጠቃላይ ገለጻ በአቶ ዘየደ ተክሌ የቀረበ ሲሆን በቀረበው ሪፖርት ላይ ባለድርሻ አካላት ውይይት በማድረግ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 11/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመምራትና ትግበራውንም በጥራት ለመፈጸም ቅንጅታዊ ስራዎች የሚመሩበት ሰነድ መዘጋጀቱ ተገለጸ፤
ቴ/ሙ/ት/ስ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና፣ የሰለጠነ የሰው ሃይል መንዳት፣ ስራ ፈጣሪነትን እና ፈጠራን ማጎልበት፣ አለምአቀፍ ተወዳዳሪነትን በማጎልበት እና ማህበረሰባዊ ተሳትፎን በማስተዋወቅ ላይ ትልቅ ዋጋ አለው፤ ዘርፉ እንደ ስትራቴጂ ቀጣይ ዕድገቱን እና ልማቱን ለማረጋገጥ በልህቀት፣ በአካታችነት እና በትብብር መርሆዎች በመመራት በጋራ መስራትን ትኩረት ይሰጣል።
በዚህም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ሪፎርም ካደረገባቸው የሰነድ ስራዎች ውስጥ የዘርፉ የተቀናጀ አሰራር ለማምጣት የሚያስችል ሰነድ ላይ በድሬዳዋ አስተዳደር ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት ጋር የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ውይይት በኤጀንሲው የሰልጣኝ ልማትና የአሰልጣኝ ልማት ዳይሬክቶሬቶች በቅንጅት ተካሄደ፡፡
በመሆኑም TVT Harmonized ሰነድ ላይ እንዴት ወደ ስራ መግባት እንደሚቻል ከዲፓርትመንት ተጠሪዎች እና ከስራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ግንዛቤ በመፍጠር ወደ ስራ የሚገባባቸው ዋናዋና ጉዳዮች ላይ በመወያየት የሁለት ወራት ዕቅድ ማዘጋጀት ተችሏል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 11/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የቴ/ሙ/ት/ስ ዘርፍን ውጤታማ በሆነ መልኩ ለመምራትና ትግበራውንም በጥራት ለመፈጸም ቅንጅታዊ ስራዎች የሚመሩበት ሰነድ መዘጋጀቱ ተገለጸ፤
ቴ/ሙ/ት/ስ ለሀገራችን ኢኮኖሚያዊ ብልጽግና፣ የሰለጠነ የሰው ሃይል መንዳት፣ ስራ ፈጣሪነትን እና ፈጠራን ማጎልበት፣ አለምአቀፍ ተወዳዳሪነትን በማጎልበት እና ማህበረሰባዊ ተሳትፎን በማስተዋወቅ ላይ ትልቅ ዋጋ አለው፤ ዘርፉ እንደ ስትራቴጂ ቀጣይ ዕድገቱን እና ልማቱን ለማረጋገጥ በልህቀት፣ በአካታችነት እና በትብብር መርሆዎች በመመራት በጋራ መስራትን ትኩረት ይሰጣል።
በዚህም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ ሪፎርም ካደረገባቸው የሰነድ ስራዎች ውስጥ የዘርፉ የተቀናጀ አሰራር ለማምጣት የሚያስችል ሰነድ ላይ ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት የግንዛቤ ማስጨበጫ እና ውይይት በኤጀንሲው የሰልጣኝ ልማትና የሰልጣኝ ልማት ዳይሬክቶሬቶች በቅንጅት ተካሄደ፡፡
በመሆኑም TVT Harmonized ሰነድ ላይ እንዴት ወደ ስራ መግባት እንደሚቻል ከዲፓርትመንት ተጠሪዎች እና ከስራ ክፍል ኃላፊዎች ጋር ግንዛቤ በመፍጠር ወደ ስራ የሚገባባቸው ዋናዋና ጉዳዮች ላይ በመወያየት የሁለት ወራት ዕቅድ ማዘጋጀት ተችሏል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 11/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የ2017 በጀት አመት ቅድመ ሞዴልና ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ አሠጣጥ ዙሪያ ከቴ/ሙ/ስ ኤጀንሲ ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽ ባለሙያዎች፣ ከሲኦሲ፣ ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስና ከአንድ ማዕከል ባለሙያዎችና አመራሮች ጋር ውይይት ተደረገ፤
በውይይቱ ላይም ተሳታፊዎች የተለያያዩ ሃሳቦችን ያነሱ ሲሆን የሚሰጠው ድጋፍና በኢንተርፕራይዞች በኩል ያለው ፍላጎት ያለመጣጣም፤ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ያለመስራትና ብድር ተወስዶ በጊዜው ተመላሽ ያለመሆን እና በአፈጻጸም ሂደት ያስተዋሏቸውን ነገሮች አንስተዋል፡፡
በቢሮው የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ከዚህ በፊት የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ በዋናነት ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በማድረግ ሂደት ተዋናይ የሆኑ ተቋማት ወደ አንድ መምጣታቸው መልካም ዕድል ፈጥሯል በዚህም ቅንጅታዊ ሥራዎችን እንድንሰራ እና ከዚህ በፊት አላሰራ ብለው የቆዩ አሰራሮችንና አደረጃጀቶችን በማሻሻል ላይ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እደሆነ ገልጸዋል፡፡
በተያያዘም በቢሮው የሚገኙ ከድጋፉ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ኤጀንሲዎችና ዳይሬክቶሬቶች መግባባት የፈጠሩ ሲሆን በተጨማሪም መንግስታዊ ያልሆኑ ደጋፊ ተቋማት ስለ ፕሮጀክቶቻቸው ሃሳብ ለኢንተርፕራይዞች በሚሰጡት ድጋፎች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የ2017 በጀት አመት ቅድመ ሞዴልና ሞዴል ኢንተርፕራይዞን ድጋፍ አሠጣጥ ዙሪያ ከቴ/ሙ/ስ ኤጀንሲ ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽ ባለሙያዎች፣ ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስና ከአንድ ማዕከል ባለሙያዎችና አመራሮች ጋር ውይይት ተደረገ፤
በውይይቱ ላይም ተሳታፊዎች የተለያያዩ ሃሳቦችን ያነሱ ሲሆን የሚሰጠው ድጋፍና በኢንተርፕራይዞች በኩል ያለው ፍላጎት ያለመጣጣም፤ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ያለመስራትና ብድር ተወስዶ በጊዜው ተመላሽ ያለመሆን እና በአፈጻጸም ሂደት ያስተዋሏቸውን ነገሮች አንስተዋል፡፡
በቢሮው የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ከዚህ በፊት የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ በዋናነት ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በማድረግ ሂደት ተዋናይ የሆኑ ተቋማት ወደ አንድ መምጣታቸው መልካም ዕድል ፈጥሯል በዚህም ቅንጅታዊ ሥራዎችን እንድንሰራ እና ከዚህ በፊት አላሰራ ብለው የቆዩ አሰራሮችንና አደረጃጀቶችን በማሻሻል ላይ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እደሆነ ገልጸዋል፡፡
በተያያዘም በቢሮው የሚገኙ ከድጋፉ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ኤጀንሲዎችና ዳይሬክቶሬቶች መግባባት የፈጠሩ ሲሆን በተጨማሪም መንግስታዊ ያልሆኑ ደጋፊ ተቋማት ስለ ፕሮጀክቶቻቸው ሃሳብ ለኢንተርፕራይዞች በሚሰጡት ድጋፎች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የ2017 በጀት አመት ቅድመ ሞዴልና ሞዴል ኢንተርፕራይዞን ድጋፍ አሠጣጥ ዙሪያ ከቴ/ሙ/ስ ኤጀንሲ ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽ ባለሙያዎች፣ ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስና ከአንድ ማዕከል ባለሙያዎችና አመራሮች ጋር ውይይት ተደረገ፤
በውይይቱ ላይም ተሳታፊዎች የተለያያዩ ሃሳቦችን ያነሱ ሲሆን የሚሰጠው ድጋፍና በኢንተርፕራይዞች በኩል ያለው ፍላጎት ያለመጣጣም፤ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ያለመስራትና ብድር ተወስዶ በጊዜው ተመላሽ ያለመሆን እና በአፈጻጸም ሂደት ያስተዋሏቸውን ነገሮች አንስተዋል፡፡
በቢሮው የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ከዚህ በፊት የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ በዋናነት ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በማድረግ ሂደት ተዋናይ የሆኑ ተቋማት ወደ አንድ መምጣታቸው መልካም ዕድል ፈጥሯል በዚህም ቅንጅታዊ ሥራዎችን እንድንሰራ እና ከዚህ በፊት አላሰራ ብለው የቆዩ አሰራሮችንና አደረጃጀቶችን በማሻሻል ላይ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እደሆነ ገልጸዋል፡፡
በተያያዘም በቢሮው የሚገኙ ከድጋፉ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ኤጀንሲዎችና ዳይሬክቶሬቶች መግባባት የፈጠሩ ሲሆን በተጨማሪም መንግስታዊ ያልሆኑ ደጋፊ ተቋማት ስለ ፕሮጀክቶቻቸው ሃሳብ ለኢንተርፕራይዞች በሚሰጡት ድጋፎች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ህዳር 10/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
በድሬዳዋ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ አመት የምስረታ በአል "የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛ።
በዛሬው ዕለትም በአሉን ምክንያት በማድረግ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አደን፣በክቡር አቶ ገዛኸኝ ታዲዮስ የፓርቲ ጽ/ቤት ልዩ ረዳት እና በክቡር አቶ ኑረዲን አብደላ የግብርና ቢሮ ኃላፊ የተመራ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት መርሀ ግብር አካሂዷል፡፡።
የልኡክ ቡድኑን የመሩት እና በጉብኝቱ ላይ ማጠቃለያ የሰጡት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አደን የመሰክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም ኮሌጁ ያለበትን ደረጃ በበቂ ሁኔታ መረዳት እንደቻሉ እንዲሁም ከትምህርትና ስልጠና ባሻገር ከኢንዱስትሪዎች ጋር ኮሌጁ ያለው ትስስር አመርቂ ውጤት እያስመዘገባ እንዳለ መረዳት ችለናል ይህን ተሞክሮ ደግሞ ለሌሎች ተቋማት ማስፋት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
ልኡክ ቡድኑን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በባለፉት ግዜያት በኮሌጁ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተለይም የትምህርትና ስልጠና፣የኢንተርፕራይዝ ድጋፍ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ልማትና የኢንዱስትሪዎችን የተለዋጭ ምርት ማምረት ላይ ኮሌጁ ያለውን ተሞክሮ ትኩረት በማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል።
በመስክ የስራ ጉብኝቱ ላይ ከተለያዩ ሴክተር ተቋማትና ከወረዳዎች የተውጣጡ የፓርቲ አባላት እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞች ከብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን በኮሌጁ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+8
በ ኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ሀላፊ እና የድሬዳዋ ከተማ የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ አብዲ ሙክታር የተመራ ልኡክ ቡድን እንዲሁም ከሁሉም ክልልሎች የተውጣጡ የንግድ ኢንዱስትሪ ና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊዎችና ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አሰተዳደሮች የተውጣጡ የስራ ክህሎት ቢሮ ሀላፊዎችና ም/ ሀላፊዎች በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡
በመስክ ምልከታው ወቅት የተሳተፉ እንግዶች እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል እየታየ ያለው ርብርብ በጣም አስደማሚ ነው ::
በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍሎች የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን በተጨማሪም ለኢንዱስትሪዎችና በኢንተርፕራይዞች በኮሌጁ በኩል እየተደረገ ያለዉ ድጋፍ ኢትዮጵያ በኢንደስትሪው ዘርፍ ለምታደርገው እንቅስቃሴ የቡኩሉን ድርሻ መወጣቱ ለሌሎች ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች መነሳሳትን የሚፈጥር ነው። በኮሌጁ ያለውን አቅም በተገቢው መንገድ በጋራ እየተጠቀምን ሀገራችንን በጋራ የምናለማ ይሆናል ብለዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
ህዳር 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
Available now! Telegram Research 2025 — the year's key insights 
