ru
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Открыть в Telegram
1 077
Подписчики
+524 часа
+107 дней
+530 день
Архив постов
የ2017 በጀት አመት ቅድመ ሞዴልና ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ድጋፍ አሠጣጥ ዙሪያ ከቴ/ሙ/ስ ኤጀንሲ ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽ ባለሙያዎች፣ ከሲኦሲ፣ ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስና ከአንድ ማዕከል ባለሙያዎችና አመራሮች ጋር ውይይት ተደረገ፤ በውይይቱ ላይም ተሳታፊዎች የተለያያዩ ሃሳቦችን ያነሱ ሲሆን የሚሰጠው ድጋፍና በኢንተርፕራይዞች በኩል ያለው ፍላጎት ያለመጣጣም፤ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ያለመስራትና ብድር ተወስዶ በጊዜው ተመላሽ ያለመሆን እና በአፈጻጸም ሂደት ያስተዋሏቸውን ነገሮች አንስተዋል፡፡ በቢሮው የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ከዚህ በፊት የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ በዋናነት ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በማድረግ ሂደት ተዋናይ የሆኑ ተቋማት ወደ አንድ መምጣታቸው መልካም ዕድል ፈጥሯል በዚህም ቅንጅታዊ ሥራዎችን እንድንሰራ እና ከዚህ በፊት አላሰራ ብለው የቆዩ አሰራሮችንና አደረጃጀቶችን በማሻሻል ላይ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እደሆነ ገልጸዋል፡፡ በተያያዘም በቢሮው የሚገኙ ከድጋፉ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ኤጀንሲዎችና ዳይሬክቶሬቶች መግባባት የፈጠሩ ሲሆን በተጨማሪም መንግስታዊ  ያልሆኑ ደጋፊ ተቋማት ስለ ፕሮጀክቶቻቸው ሃሳብ ለኢንተርፕራይዞች በሚሰጡት ድጋፎች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የ2017 በጀት አመት ቅድመ ሞዴልና ሞዴል ኢንተርፕራይዞን ድጋፍ አሠጣጥ ዙሪያ ከቴ/ሙ/ስ ኤጀንሲ ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽ ባለሙያዎች፣ ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስና ከአንድ ማዕከል ባለሙያዎችና አመራሮች ጋር ውይይት ተደረገ፤ በውይይቱ ላይም ተሳታፊዎች የተለያያዩ ሃሳቦችን ያነሱ ሲሆን የሚሰጠው ድጋፍና በኢንተርፕራይዞች በኩል ያለው ፍላጎት ያለመጣጣም፤ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ያለመስራትና ብድር ተወስዶ በጊዜው ተመላሽ ያለመሆን እና በአፈጻጸም ሂደት ያስተዋሏቸውን ነገሮች አንስተዋል፡፡ በቢሮው የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ከዚህ በፊት የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ በዋናነት ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በማድረግ ሂደት ተዋናይ የሆኑ ተቋማት ወደ አንድ መምጣታቸው መልካም ዕድል ፈጥሯል በዚህም ቅንጅታዊ ሥራዎችን እንድንሰራ እና ከዚህ በፊት አላሰራ ብለው የቆዩ አሰራሮችንና አደረጃጀቶችን በማሻሻል ላይ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እደሆነ ገልጸዋል፡፡ በተያያዘም በቢሮው የሚገኙ ከድጋፉ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ኤጀንሲዎችና ዳይሬክቶሬቶች መግባባት የፈጠሩ ሲሆን በተጨማሪም መንግስታዊ  ያልሆኑ ደጋፊ ተቋማት ስለ ፕሮጀክቶቻቸው ሃሳብ ለኢንተርፕራይዞች በሚሰጡት ድጋፎች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

የ2017 በጀት አመት ቅድመ ሞዴልና ሞዴል ኢንተርፕራይዞን ድጋፍ አሠጣጥ ዙሪያ ከቴ/ሙ/ስ ኤጀንሲ ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽ ባለሙያዎች፣ ከድሬ ማይክሮ ፋይናንስና ከአንድ ማዕከል ባለሙያዎችና አመራሮች ጋር ውይይት ተደረገ፤ በውይይቱ ላይም ተሳታፊዎች የተለያያዩ ሃሳቦችን ያነሱ ሲሆን የሚሰጠው ድጋፍና በኢንተርፕራይዞች በኩል ያለው ፍላጎት ያለመጣጣም፤ የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ያለመስራትና ብድር ተወስዶ በጊዜው ተመላሽ ያለመሆን እና በአፈጻጸም ሂደት ያስተዋሏቸውን ነገሮች አንስተዋል፡፡ በቢሮው የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም ከዚህ በፊት የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ በዋናነት ለኢንተርፕራይዞች ድጋፍ በማድረግ ሂደት ተዋናይ የሆኑ ተቋማት ወደ አንድ መምጣታቸው መልካም ዕድል ፈጥሯል በዚህም ቅንጅታዊ ሥራዎችን እንድንሰራ እና ከዚህ በፊት አላሰራ ብለው የቆዩ አሰራሮችንና አደረጃጀቶችን በማሻሻል ላይ ቢሮው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እደሆነ ገልጸዋል፡፡ በተያያዘም በቢሮው የሚገኙ ከድጋፉ ጋር በቀጥታ ግንኙነት ያላቸው ኤጀንሲዎችና ዳይሬክቶሬቶች መግባባት የፈጠሩ ሲሆን በተጨማሪም መንግስታዊ  ያልሆኑ ደጋፊ ተቋማት ስለ ፕሮጀክቶቻቸው ሃሳብ ለኢንተርፕራይዞች በሚሰጡት ድጋፎች ዙሪያ ገለጻ አድርገዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ 5ኛ አመት የምስረታ በአል "የሀሳብ ልዕልና ለሁለንተናዊ ብልፅግና" በሚል መሪ ቃል በተለያዩ ሁነቶች እየተከበረ ይገኛ። በዛሬው ዕለትም በአሉን ምክንያት በማድረግ የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አደን፣በክቡር አቶ ገዛኸኝ ታዲዮስ የፓርቲ ጽ/ቤት ልዩ ረዳት እና በክቡር አቶ ኑረዲን አብደላ የግብርና ቢሮ ኃላፊ የተመራ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት መርሀ ግብር አካሂዷል፡፡። የልኡክ ቡድኑን የመሩት እና በጉብኝቱ ላይ ማጠቃለያ የሰጡት የድሬዳዋ አስተዳደር ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ክብርት ወ/ሮ ፈቲያ አደን የመሰክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም ኮሌጁ ያለበትን ደረጃ በበቂ ሁኔታ መረዳት እንደቻሉ እንዲሁም ከትምህርትና ስልጠና ባሻገር ከኢንዱስትሪዎች ጋር ኮሌጁ ያለው ትስስር አመርቂ ውጤት እያስመዘገባ እንዳለ መረዳት ችለናል ይህን ተሞክሮ ደግሞ ለሌሎች ተቋማት ማስፋት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ልኡክ ቡድኑን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በባለፉት ግዜያት በኮሌጁ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተለይም የትምህርትና ስልጠና፣የኢንተርፕራይዝ ድጋፍ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ልማትና የኢንዱስትሪዎችን የተለዋጭ ምርት ማምረት ላይ ኮሌጁ ያለውን ተሞክሮ ትኩረት በማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ አብራርተዋል። በመስክ የስራ ጉብኝቱ ላይ ከተለያዩ ሴክተር ተቋማትና ከወረዳዎች የተውጣጡ የፓርቲ አባላት እንዲሁም የመንግስት ሰራተኞች ከብልፅግና ፓርቲ አመራሮች ጋር በጋራ በመሆን በኮሌጁ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን ተዘዋውረው ጎብኝተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 10/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content

በ ኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ሀላፊ እና የድሬዳዋ ከተማ የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ አብዲ ሙክታር የተመራ ልኡክ ቡድን እንዲሁም ከሁሉም ክልልሎች የተውጣጡ የንግ
+8
በ ኢትዮጵያ ኢንተርፕራይዝ ልማት ዋና ሀላፊ እና የድሬዳዋ ከተማ የንግድ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊ ክቡር አቶ አብዲ ሙክታር የተመራ ልኡክ ቡድን እንዲሁም ከሁሉም ክልልሎች የተውጣጡ የንግድ ኢንዱስትሪ ና ኢንቨስትመንት ቢሮ ሀላፊዎችና ከሁሉም ክልሎች እና ከተማ አሰተዳደሮች የተውጣጡ የስራ ክህሎት ቢሮ ሀላፊዎችና ም/ ሀላፊዎች በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ በመስክ ምልከታው ወቅት የተሳተፉ እንግዶች እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በኮሌጁ ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውም የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት መአከል ግንባታ በከፍተኛ ፍጥነት ተከናውኖ ለሚፈለገው አላማ መዋል እንዲችል እየታየ ያለው ርብርብ በጣም አስደማሚ ነው :: በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ ትምህርት ክፍሎች ያላቸው አቅም ከሌሎች ኮሌጆች አንጻር ከድሬዳዋ አልፎ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍሎች የሚበቃ ነው ያሉ ሲሆን በተጨማሪም ለኢንዱስትሪዎችና በኢንተርፕራይዞች በኮሌጁ በኩል እየተደረገ ያለዉ ድጋፍ ኢትዮጵያ በኢንደስትሪው ዘርፍ ለምታደርገው እንቅስቃሴ የቡኩሉን ድርሻ መወጣቱ ለሌሎች ክልሎችና ከተማ አስተዳደሮች መነሳሳትን የሚፈጥር ነው። በኮሌጁ ያለውን አቅም በተገቢው መንገድ በጋራ እየተጠቀምን ሀገራችንን በጋራ የምናለማ ይሆናል ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ ለወጣቶች በተከታታይ ስድስት ዙር ሲደረግ የነበረው የአቻ ለአቻ ውይይት ተጠናቀቀ፤      ወጣቶቹ  በየወሩ የአቻ ለአቻ  ውይይት  በማድረግ  በየጊዜው ያገኙትን ዕውቀት  የገጠማቸውን ችግሮች  ለይተው የተወያዩበት መድረክ  ሲሆን ይህ  ለስድስተኛ ጊዜ የተዘጋጀ እና የመጨረሻው  ውይይት የተደረገ ሲሆን የስራ ላይ ልምምዱን ሲያጠናቅቁ  በተቀጠሩበት ወይም በሚቀጠሩበት ድርጅቶች በሰለጠኑት ሞያ መሰረት የሚያገለግሉ ይሆናል፡፡      በአስተዳደሩ የፕሮግራሙ ሁለተኛ ዙር ትግበራ ከ1700 በላይ ሰልጣኞች ተመዝግበው 1500 በላይ የሚሆኑት የህይወት ክህሎት ሰልጠና ወስደው 972 የሚሆኑ ወጣቶች ተግባራዊ የሥራ ላይ ልምምድን የተቀላቀሉ ሲሆን በተለያዩ በአስተዳደሩ የሚገኙ ኢንደስትሪዎች ላይ ስድስት ወራት የሚፈጀውን ውጤታማ ቆይታ እያደረጉ ሲገኝ ከዚሁ ጎን ለጎን የአቻ ለአቻ ውይይቶችን በየወሩ ሲወያዩ ቆይተዋል፡፡      በዚህም ውይይት ላይ ተሳታፊ የሆኑ ወጣቶች በአጠቃላይ በፕሮግራሙ ተጠቃሚነታቸው በአመለካከት፣ በክህሎት እንዲሁም በዕውቀት ከዚህ በፊት ከነበሩበት የተሻለ ነገሮችን የመረዳትና የማድረግ አቅም ማዳበራቸውን የተናገሩ ሲሆን በተለይ እርስ በዕርስ በመነጋገር ችግሮችን የፈቱበትና የተሻለ ዕውቀት የቀሰሙበት እንደነበር ተናግረዋል፡፡ በስድስተኛው ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ማጠቃለያ የፕሮግራሙ ተጠቃሚ ወጣቶች ከፕሮግራሙ አስተባባሪዎች ጋር የጋራ መድረክ የተዘጋጀ ሲሆን በቀጣይ ትኩረት ማድረግ በሚገባቸው ነገሮች ላይ  መግባባት የፈጠሩበት ሆኗል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 7/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

የቴክኖሎጂ እሴት ሰንሰለት ትንተና እና ሰነድ ዝግጅት ላይ ያኮረ ስልጠና ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች ተሰጠ፡፡ በድሬዳዋ አስተዳደር በሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከጥቃቅን፣ አነስተኛና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች በአዲሱ ዕሳቤ መሠረት ለኢንተርፕራረ አጫጭር የእሴት ሰንሰለት እንዲሰጥ ከሥራና ክህሎት ሚንስቴር በተላለፈው መመሪያ መሠረት የተሰጠ ነው። የዚህ ስልጠና ዋነኛው ዓላማ በሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ በ2017 ዓ.ም በተያዘው ዕቅድ መሰረት በአስተዳደሩ የሚገኙትን የዘርፉን እሴት ሰንሰለት ለማዘጋጀት በቅድሚያ በንዑስ ዘርፍ ተሰማርተው ለሚገኙ የጥቃቅን፤ አነስተኛና ከፍተኛ ኢንተርፕራይዞች በአዲሱ እሳቤ መሰረት ለኢንተርፕራይዞቹ  በተመረጡ በስድስት ንዑስ ዘርፎች የእሴት ሰንሰለት ስልጠና እንዲሰጣቸው ተደርጓል፡፡ በመሆኑም ኢንተርፕራይዞቻችን በቀጣይ በሽግግር ወቅት እስከ ኤክስፖርት ስታንደርድ ሊያደርሳቸው የሚችል የዘርፉ የቴክኖሎጂ ክፍተቶች የሚለዩበትና የምርት/የአገልግሎት ችግሮቻቸውን  ሊፈታ የሚችል ቴክኖሎጂ በቀጣይ ጊዜያቶች በተቋም የሚሰራበትና የሚሸጋገርበትን እድል የሚፈጥር ይሆናል ፡፡ በዚሁም መሰረት በቀጣይ ለነዚህ ለተመረጡት ንዑስ ዘርፎች ከዘርፍ መ/ቤት፤ ከዩኒቨርሲቲና ከተቋሞቻችን በተመረጡ ባለሞያዎች/ኤክስፐርቶች የእሴት ሰንሰለቱ ትንተና የሚሰራ ይሆናል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 6/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+5

"ሀገራዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት!" የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አመራሮችና ሠራተኞች 19ኛውን የኢትዮጵያ ብሔር ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን አከበሩ። በዓሉ በፓናል ውይይት የተከበረ ሲሆን፣ የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በመድረኩ ላይ ባደረጉት ንግግር የዘንድሮው የብሔር ብሔረሰቦች ቀን "ሀገራዊ መግባባት ለህብረ-ብሔራዊ አንድነት" በሚል መሪ ቃል የሚከበር መሆኑን አውስተው፣ ሀገራዊ መግባባትን ለማጽናት ሕገ መንግሥቱን መሠረት በማድረግ ጥያቄዎችን በሰላማዊ አግባብ የሚያስተናግድ ሥርዓት መገንባትና የተጀመረው ሀገራዊ ምክክር ከዳር ደርሶ አንድነታችንን እንዲያጠናክር ቀዳሚ የመንግሥት ትኩረት እንደሆነ ተናግረዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 6/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት የተለያየ ዘርፍ ስር ለሚገኙ ኢንተርፕራይዞች አሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ በማዘጋጀት በሙያ ደህንነትና ጤንነት ላይ ስልጠና ተሰጠ። በቢሮው የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በዋናነት የሰራተኛውን ደህንነትና ጤና የማስጠበቅ ስራዎች ትኩረት የተሰጣቸው ሲሆኑ ይህም የኢንተርፕራይዞቹን ምርታማነት በማሳደግ የስራ ቦታቸውን ሰላም በማረጋገጥ ረገድ የሚያስገኘው ውጤት ቀላል አይደለም። በዚህም በየኢንተርፕራዞቹ የሙያ ደህንነትና ጤንነት ሳይንሳዊ በሆነ መንገድ አንዲደራጅና እንዲጠበቅ ድጋፍ በማድረግ ለኢንተርፕራይዞቹ አሰሪና ሰራተኞች በቀጣይ ስለሚያከናውኗቸው ስራዎች በማስገንዘብ  በተለይ የሙያ ደህንነቱና ጤናው የተጠበቀ የስራ አካባቢን በመፍጠር የስራ ቦታቸውን ሰላም እና ደህንነት በማስጠበቁ ረገድ ያለው ሚና ከፍ ያለ መሆኑን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ መሐመድ ኢብራሂም ተናግረዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 5/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+3

የኢንተርፕራይዞች ውጤታማነት እና ቀጣይነትን ለማረጋገጥ በጥናት ላይ የተመሠረቱ ስራዎችን ከባለድርሻ ተቋማት ጋር በቅንጅት መስራት ወሳኝ ሚና እንዳለው ተገለጸ። የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት በ2017 ዓ.ም ለኢንተርፕራይዞች በሚደረገው የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ድጋፍ ዙሪያ የተዘጋጀ የዳሰሳ ጥናት በኮሌጆች ተዘጋጅቶ ውይይት ተካሄደ። ዳይሬክቶሬቱ በተለያዩ ዘርፎች ለተደራጁ ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት ድጋፍ አስተማማኝነትን ለማረጋገጥና ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ለመስራት በሚያስችል መልኩ ሰነድ ቀርቦ በተለያዩ ጉዳዮች  ዙሪያ የሚመለከታቸው የተቋማት ተወካዮች በተገኙበት የጋራ ስምምነትና መግባባት የተፈጠረበት ውይይት ማካሄድ ተችሏል፡፡ በውይይቱ ላይ የቢሮው ምክትል ኃላፊ እና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ እንደተናገሩት የዛሬ መድረክ ዋና ዓላማ በአስተዳደሩ በተለያዩ ዘርፍ የሥራ ዕድል የተፈጠረላቸው ዜጎችን በቅንጅት ከባለድርሻ አካላት ጋር የሚከናወኑ ተግባራት በጋራ በማከናወን ኢንተርፕራይዞችን የሚጠቅሙና የሚያሳድጉ ስራዎችን ለመስራትና በዚህም ምርትና ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እንደሆነ ተናግረዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 5/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7