en
Feedback
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

Open in Telegram

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

Channel ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍ (@moamediamoresh) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 11 497 subscribers, ranking 17 044 in the News & Media category and 2 912 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 11 497 subscribers.

According to the latest data from 01 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by -156 over the last 30 days and by 5 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 8.95%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 6.57% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 1 029 views. Within the first day, a publication typically gains 756 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 4.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 02 August, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

11 497
Subscribers
+524 hours
-427 days
-15630 days
Posts Archive
የጦርነት ጭጋግ ያጠላበት ሰሜን አምሓራ ፀለምት ወረዳ በድርቅ ተመታ‼️ በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ ያለው የክረምት ሁኔታ ከላይ በምስል የተያያዘውን ይመስላል፣ ምንም ዝናብ የለም። የፓስፍክ ው
+2
የጦርነት ጭጋግ ያጠላበት ሰሜን አምሓራ ፀለምት ወረዳ በድርቅ ተመታ‼️ በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ ያለው የክረምት ሁኔታ ከላይ በምስል የተያያዘውን ይመስላል፣ ምንም ዝናብ የለም። የፓስፍክ ውቂያኖስ ሙቀት ባልተለመደ ሁነታ በመጨመሩ ምክንያት በሰሜን፣ በመካከለኛና  ምስራቅ አከባቢ የዘንድሮው የክረምት ዝናብ አጭር መሆኑና ክረምቱም ቶሎ እንደሚወጣ የኢትዮጵያ ሜትሮዎሎጂ ማስታወቁ አይዘነጋም።

ህወሓት በኦህዴድ ምክክር ኮሚሽን መንጋ ውስጥ ወኪል አሳትፎ አዲስ አበባ ገብቷል‼️ እነ አጅሬው አስመራም ሱዳንም መቀሌም አዲስ አበባም ናቸው። ብዙ ሰው አዲስ አበባ መገኘታቸው ግራ ሊያጋባው ይችላል
ህወሓት በኦህዴድ ምክክር ኮሚሽን መንጋ ውስጥ ወኪል አሳትፎ አዲስ አበባ ገብቷል‼️ እነ አጅሬው አስመራም ሱዳንም መቀሌም አዲስ አበባም ናቸው። ብዙ ሰው አዲስ አበባ መገኘታቸው ግራ ሊያጋባው ይችላል። አስመራም ሱዳንም ያሉት ለጦርነቱ ነው። ለካስ ለምክክር ኮምሽኑም በርካታ ሰው ልከዋል። እኔ በምክክር ኮምሽኑ እየተሳተፈ የመሰለኝ ከእነ ደብረፅዮን ጋር የጥቅምና ስልጣን ብቻ ልዩነት ያለው የእነ ጌታቸውና ፃድቃን ቡድን ነበር። ትናንት ሳጣራ ግን እነ ደብረፅዮንም ለካ ተሳታፊ ልከዋል። በተለያየ አደረጃጀት፣ በተለያየ መንገድ! ጭራሽ "ግብአተ መሬቱን እንፈፅማለን" የሚሉትን የብልፅግናን አላማ ደግፈው ነው በምክክሩም እየጮሁ ያሉት። የኦሮሞ ብሔርተኞችን ደግፈው በአዲስ አበባ፣ በቋንቋና ሌላው ላይ እጅ እያቀሳሰሩ እንደሚውሉ አንድ ተሳታፊ አጫውቶኛል። ከአገዛዙና ከውሃብያ ቀጥሎ ጠርዝ ይዘው፣ አገርና አማራን እየወቀሱ ይውላሉ። እኔ እስከ ትናንት ድረስ ለጊዜው ከእነ ደብረፅዮን ያፈነገጠው ኃይል መሰሎኝ ነበር ምክክር ምናምን ላይ የተሳተፈው። እነ አጅሬውም "ሁሉም አይቅርብን" ብለው ወኪሎቻቸውን ልከዋል። ሲፈልጉ ደግሞ ተቃውመው መግለጫም ያወጣሉ። ኮምሽኑ "ትግራይን አሳተፍኩ" ማለት ፈልጓል። እነሱም የሆነ መድረክ እንዲያመልጣቸው አይፈልጉም። እናም በተለያየ መንገድ "አሳትፉን" እያሉ እየጠየቁ መጥተዋል። በተለያዩ አደረጃጀቶች ስም በምክክር ኮምሽኑ እየተሳተፉ ይገኛሉ። በምክክርኮሚሽን ተሳተፋችሁ ብሎ ንፁሃንን ያስር ይገድል የነበረ፣ ት/ቤት አስተማራችሁ ብሎ መምህራንን አንበርክኮ የሚነዳ የሚገድልም ፋኖ ነኝ ባይን ባሰብኩ ጊዜ በ2ቱ ኃይላት ሰርጎገብ እንደተወረርን እገነዘባለሁ።

Ethiopia: Drone Strike on Christian Monastery Raises Questions for Abiy Ahmed | Firstpost Africa Firstpost examines the growing fears among Ethiopia's Orthodox Christian community after a deadly drone strike reportedly hit the historic Abbay Giyorgis St. Arsema Unity Monastery in the Amhara region. Reports say the strike killed members of the monastic community and injured several others during a religious gathering. Ethiopian government sources have alleged that Fano fighters were using the monastery as a shelter, while church leaders strongly deny that any armed group was present and insist only priests, nuns and worshippers were targeted. The incident has drawn international condemnation, with the World Council of Churches calling for an independent investigation. It also comes amid broader concerns over attacks... Alyson Le Grange explains why this incident is resonating far beyond Ethiopia, raising questions about the protection of Africa's oldest Christian heritage during war, on Firstpost Africa.

የህወሓት የጦርነት ስትራቴጅው የሚመራው በአስመራ ሰዎች ነው። ራሱን መምራቱ ከእጁ እና ከህዝብ ፍላጎት ወጥቷል። የቀድሞ ህወሓት ቃል አቀባይ እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት የአሁኑ የፋሽስታዊ
የህወሓት የጦርነት ስትራቴጅው የሚመራው በአስመራ ሰዎች ነው። ራሱን መምራቱ ከእጁ እና ከህዝብ ፍላጎት ወጥቷል። የቀድሞ ህወሓት ቃል አቀባይ እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት የአሁኑ የፋሽስታዊ አገዛዙ ደህንነት አማካሪ ጌታቸው ረዳ

"ጽምዶ" ሲባል "አቤት!" የሚል አምሓራ የለም። የሁለትዮሽ "ሻዕቢያ እና ወያኔ" ጥምረት መካከል አምሓራ ስፍራ የለውም። ጌቶቻቸው ሲመቱ የሚጮሁ ተላላኪ ቡችሎች የሉም ማለት ግን አይደለም። አምሓራ
"ጽምዶ" ሲባል "አቤት!" የሚል አምሓራ የለም። የሁለትዮሽ "ሻዕቢያ እና ወያኔ" ጥምረት መካከል አምሓራ ስፍራ የለውም። ጌቶቻቸው ሲመቱ የሚጮሁ ተላላኪ ቡችሎች የሉም ማለት ግን አይደለም። አምሓራ የራሱ የህልውና ትግል እና መራራ ጦርነት ውስጥ ከገባ ዘመናት ባቱ…!

በሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን በዘፈቀደ ታፍነው እየታሰሩ ነው‼️ የሳዑዲ ዓረቢያ ፖሊስ የአገሪቱን ድንበር በሕገወጥ መንገድ አቋርጠው ሊገቡ ሞክረዋል ያላቸውን በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሠረ። የአገሪቱ የጸጥታ ኃይሎች ባለፉት ስድስት ቀናት ባካሄዱት የጸጥታ ቁጥጥር ዘመቻ ካሠሯቸው 1 ሺሕ 418 ሰዎች መካከል፣ 45 በመቶዎቹ ኢትዮጵያዊያን መኾናቸውን የአገሪቱ ጋዜጦች ዘግበዋል። የጸጥታ አካላት በተጠቀሠው ጊዜ ውስጥ በሕገወጥ መንገድ ድንበር ከማቋረጥ፣ ከመኖሪያ ፍቃድ እና ከሠራተኛ ቅጥር በተያያዙ ወንጀሎች በጠቅላላው 14 ሺሕ 154 ሰዎችን አስረናል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ከሳምንት በፊት በተመሳሳይ ድንበር በሕገወጥ መንገድ ሲያቋርጡ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን እንደታሠሩ ተዘግቦ ነበር። በሌላ በኩል፣ በአገሪቱ እስር ቤት የሞት ፍርዳቸውን የሚጠባበቁ እስከ 200 የሚደርሱ ኢትዮጵያዊያን እንደሚገኙ በምስጢር ካነጋገራቸው ፍርደኞች መረዳቱን ቢቢሲ ዘግቧል።

አማራን ማጥፋትን የፖለቲካ እስትንፋሱና የኅልውናው መሠረት አድርጎ የተፈጠረውን፣ በዚያው ዓላማ የኖረውንና ወደፊትም በዚያው የጥፋት መንገድ የሚቀጥለውን ፋሽስት ወያኔን የአማራ የኅልውና ተጋድሎ አጋር አድርገው ለማቅረብ የሚደረገው አሳፋሪና ወንጀለኛ ሙከራ ዝም ተብሎ ወደማይታለፍበት ደረጃ ላይ ደርሷል። በየማኅበራዊ ሜዲያው እየወጡ ፋሽስት ወያኔን እንደ አማራ ‘ትግል’ አጋር እንድንቆጥርላቸው ላንቃቸው እስኪሰነጠቅ ድረስ ሲለፋደዱ የሚሰሙት አብዛኛዎቹ የፋሽስት ወያኔ ነውረኛ ድርጅት የሆነው የብአዴን ጠረናቸው ሳይለቅ፣ በአማራ የኅልውና ተጋድሎ ላይ ተጣብቀው የተቀመጡ አለቅቶች ናቸው። እነዚህ ፋሽስት ወያኔን ለአማራ ሕዝብ ሊሸጡለት የሚሞክሩት በአማራ ሕዝብ የኅልውና ተጋድሎ ላይ የተጣበቁ የብአዴን አለቅቶች ፋሽስት ወያኔ ከተፈጠረ ጀምሮ ከኀምሳ ዓመታት በላይ በአማራ ሕዝብ ላይ በቀጥታ ሲፈጽምና በወኪሎቹ ሲያስፈጽም የኖረውን ፍጅት፣ የዘር ማጥፋት፣ እልቂት፣ መከራ፣ ግፍ፣ ማፈናቀልና ተቆጥሮ የማያልቅ ታሪካዊ በደል ዳግም በመካድ፣ በአማራ ሕዝብ ደም፣ መስዋዕትነት፣ ክብርና ታሪካዊ ትውስታ ላይ ግልጽ ክህደትና ከባድ የፖለቲካ ወንጀል እየፈጸሙ ነው። ፋሽስት ወያኔ ትናንትናም ሆነ ዛሬ ጦር የሚሰብቀውና የሰበቀው አማራን ለማጥፋት እና አጽመ ርስቱ የሆኑትን ወልቃይትን፣ ጠገዴን፣ ጠለምንት፣ ሁመራን፣ ኮረምን፣ አላማጣ፣ ዋጃ፣ መሆኒ እና በወረራ የያዛቸውን የራያ አካባቢዎች ለመውረር እና ታላቋን ትግራይ ለመመስረት ብቻ ነው። ፋሽስት ወያኔ ከዚህ ውጭ የሚዋጋበት ምክንያት የለውም! በአሁኑ ወቅት አማራ የሚያስፈልገው የአማራ አላማ ያለው እና በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚገዛ አታጋይ ድርጅት እንጂ እንደ ፋሽስት ወያኔ አይነት አማራን ማጥፋትን የፖለቲካ እስትንፋሱና የኅልውናው መሠረት ያደረገ የትግል ‘አጋር’ አይደለም። ባጭሩ እንደ ቱትሲ የዘር ማጥፋት ጦርነት የታወጀበት የአማራ ሕዝብ እንደ ሁቱዎቹ ኢንተርሃሞዮች ከኾነበት የዐቢይ አሕመድ የኦሮሙማው አረመኔ አገዛዝ የዘር ማጥፋት ጦርነት ለመትረፍ ያለው ብቸኛ አማራጭ እንደ ቱትሲዎቹ አላማ እና ዲሲፕሊን ያለው የአርበኞች ድርጅት ማቋቋምና እንደ ፖል ካጋሜ አይነት ጀግና የአርበኛ መሪ መፍጠር እንጂ ሲያጠፋው ለኖረውና ሊያጠፋው ጦር ከሚሰብቀው ፋሽስት ወያኔ ጋር አንሰላ መጋፈፍ አይደለም። የአማራ ሕዝብ እንደ ቱትሲዎቹ አላማ እና ዲሲፕሊን ያለው የአርበኞች ድርጅት ማቋቋምና ከራሱ በላይ የኾነ አላማ ያለው አታጋይ መሪ ካገኘ የፋሽስት ወያኔና መሰል ጸረ አማራ እና ጸረ ኢትዮጵያ ድርጅቶች አጋር አያስፈልገውም።

#USA 🇺🇸 #VISA አሜሪካ ለቪዛ የምትይዘውን ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ዶላር ልታሳድግ ነው። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የበርካታ አገራት ዜጎች ቪዛ ሲያመለክቱ ያስይዙት የነበረውን ገንዘብ ከ15 ሺህ ዶላር ወደ 20 ሺህ ዶላር (3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) ከፍ በማድረግ ቋሚ ሊያደርግ ነው። መሥሪያ ቤቱ እንደገለፀው መርሃ ግብሩ የቢዝነስ እና የቱሪስት (ቢ1 እና ቢ2) ቪዛ አመልካቾች ላይ ተግባራዊ የሚሆን ነው። ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ አሜሪካ ውስጥ ከቆዩ ገንዘቡ ተመላሽ እንዳይሆን የሚያደርገው ይህ አሠራር ተግባራዊ ይሆንባቸዋል ከተባሉ አብዛኞቹ ከአፍሪካ ከሆኑ 50 አገራት መካከል ፦ - #ኢትዮጵያ፣ - ጂቡቲ፣ - ናይጄሪያ፣ - ሴኔጋል፣ - ኡጋንዳ፣ - ታንዛኒያ ይገኙበታል። ይህ በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው የተሻሻለው ፕሮግራም፣ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ የሚቆዩ ጎብኝዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በመርሃ ግብሩ መሠረት አመልካቾች እንደ ኤምባሲው ኦፊሰሮች ውሳኔ ለቪዛ እስከ 20 ሺህ ዶላር (ከ3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) የሚደርስ ገንዘብ እንዲያስይዙ ሊጠይቁ ይችላሉ። አሜሪካ ውስጥ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ዜጎች ባሏቸው አገራት እና የአገር ውስጥ ሰነዶች ላይ የላላ ቁጥጥር በሚያደርጉ አገራት የቪዛ ማስያዣ የሙከራ መርሃ ግብር ተግባራዊ ማድረግ የጀመረችው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ነበር። መርሃ ግብሩ ለአንድ ዓመት የሚቆይ የነበረ ሲሆን የተቀመጠለት ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ ነው አዲሱ መመሪያ የወጣው። በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው ይህ አዲሱ የቪዛ ማስያዣ ገንዘብ ፕሮግራም ቋሚ እንደሚሆንም ተገልጿል። በተጠናቀቀው የሙከራ መርሃ ግብር መሠረት አመልካቾች ከ5 ሺህ ፣ ከ10 ሺህ እስከ 15 ሺህ ዶላር ድረስ እንዲያስይዙ ይጠየቁ የነበረ ሲሆን በአዲሱ ፕሮግራም አነስተኛው 5 ሺህ ዶላር ከዝርዝሩ ወጥቶ፣ ከፍተኛው የማስያዣ ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ከፍ ተደርጓል። በአዲሱ መርሃ ግብር ከተካተቱ 50 አገራት መካከል 30ዎቹ የሚገኙት በአፍሪካ ውስጥ ነው።

አምሓራውን ያገለለው ህገ-አራዊት የወያኔ ቅርጫ ክልል… ከዐምሓራው የነጠቀው አዲስ አበባን ሳይሆን ሸዋን ነው። የሸዋን ባለቤትነት በማስመለስ ውስጥ የሸዋ እምብርቷ የነገስታቱ ማዕከል "አዲስ አበባ"
+1
አምሓራውን ያገለለው ህገ-አራዊት የወያኔ ቅርጫ ክልል… ከዐምሓራው የነጠቀው አዲስ አበባን ሳይሆን ሸዋን ነው። የሸዋን ባለቤትነት በማስመለስ ውስጥ የሸዋ እምብርቷ የነገስታቱ ማዕከል "አዲስ አበባ" የዳዊት ከተማ በረራም ነፃ ትወጣለች። አምሓራን ከፖለቲካ ማዕከሉ፣ ከነገስታቱ አንባ ሸዋ ለመግፋት ሲባል… ብዐዴንን ጠፍጥፎ ፈጥሮ ወደ ባህር ዳር የሸኜው የዛኔው የወያኔ ሴረኛ… አሁን ላይ በአምሓራ እርስት ላይ ለመጨፈር እርስቱንም ለመንጠቅ የሚንደረደረውን የኦህዴድ ኦነግ መንጋ… ከወለጋ፣ ባሌ፣ አርሲ፣ ከሀረር እና ብረና ጠርቶ በአዲስ አበባ በማንገስ አጋር አድርጎ ቆይቷል። ያ፣ እንግዳ ቡድን ነው፣ ዛሬ ላይ አዲስ አበባን ለመዋጥ የሚስገበገበው። ወዳጄ… ግጬውን ያማተረው ህወሓት፣ ዋናችንን አስረክቦ እንደፈረጠጠው… አዲስ አበባን የሚያማትረው የጅማ፣ ባሌ እና አርሲ ወራሪ ሸን አስርክቦ ነገሌ የሚገባበትን አደገኛ ጨዋታ ጀምሯል። መጨረሻውን አብረን እናያለን!

በኦህዴድ ብልፅግና የተዋቀረው የፌክ ድራማው ተቋም ውስጥ “ተፅዕኖ ፈጣሪዎች” የተባሉ ግለሰቦች በምክክሩ እንዲሳተፉ በምን መስፈረት ተመረጡ? የሚለው ጥያቄ ከውስጥ መልስ የተሰጠበት ሲሆን… ተፅዕኖ ፈ
በኦህዴድ ብልፅግና የተዋቀረው የፌክ ድራማው ተቋም ውስጥ “ተፅዕኖ ፈጣሪዎች” የተባሉ ግለሰቦች በምክክሩ እንዲሳተፉ በምን መስፈረት ተመረጡ? የሚለው ጥያቄ ከውስጥ መልስ የተሰጠበት ሲሆን… ተፅዕኖ ፈጣሪ የተባሉት ውስጥ 97% የሚሆኑት በብልፅግና ፓርቲ ጥቆማ የተደረገባቸው ናቸው። በክልል ተወካዮች ጉባኤ በክልሎችና በፌደራል ደረጃ በድምሩ 31 በብልፅግና የተጠቆሙ እና የተላኩ “ተጽዕኖ ፈጣሪዎች” እንዲካተቱ ተደርጓል። ይህ ውክልና፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ መምህራን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች እና ሴቶች ካገኙት ውክልና የሚበልጥ መሆኑን ያነሱ ቅሬታ አቅራቢዎችም፤ ኮሚሽኑ ይሄን መሰል የአንድ ድርጅት ፍላጎት አስፈፃሚዎች የወረሩት አካሔድን ዳግም እንዲያጤነው ጥቂት በኦህዴድ ማዕበለ ወኪሎች የተወረሩ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል። 

ጦርነት ተከፍቶብናል:-ህወሓት‼️ "የትግራይ ህልውና በብልፅግና መቃብር ላይ ይወሰናል" በሚል ስብሰባ ሲያካሂድ የከረመው ህወሓት በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ተከፍቶብናል ብሏል። ሙሉ የመግለጫው ትርጉም👇
ጦርነት ተከፍቶብናል:-ህወሓት‼️ "የትግራይ ህልውና በብልፅግና መቃብር ላይ ይወሰናል" በሚል ስብሰባ ሲያካሂድ የከረመው ህወሓት በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ተከፍቶብናል ብሏል። ሙሉ የመግለጫው ትርጉም👇👇 "የፌደራል መንግሥቱ የትግራይን ሕዝብ ለማጥፋት ሲያካሂድ የቆየውን ሁለንተናዊ ከበባ እና እገዳ፣ በድሮን እና በተላላኪ ታጣቂዎቹ ሲፈጽም የቆየውን ጥቃት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ ዛሬ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳው ጀምሮ በምዕራባዊ ትግራይ ዞን በሸረሪ አቅጣጫ ግልጽ ጦርነት ጀምሯል። የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ በኋላ እንኳ የትግራይን ሕዝብ ለማንበርከክ እና ለመበታተን ካለው ከፍተኛ ፍላጎት ተነሥቶ የተለያዩ ከበባዎችን፣ እገዳዎችን እና ወታደራዊ ዝግጅቶችን ሲያደርግ ቆይቶ፤ ድጋሚ ትግራይን ለመውረር እና ሕዝቡን ለማጥፋት ተነሳሽነት ወስዶ ጦርነት ከፍቶብናል። ​ስለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ የትግራይ ሕዝብ፣ ሁላችሁም የትግራይ የጸጥታ ኃይሎች፣ ብሔራዊ ኃይሎች እና የትግራይ ታጋዮች፣ የትግራይ ሲቪል ማኅበራት፣ የትግራይ ሃይማኖት ተቋማት እና ሌሎች የሚመለከታችሁ አካላት በሙሉ ብሔራዊ ህልውናችንን ለማረጋገጥ በሚደረገው ፍትሐዊ ትግል "ለብሔራዊ ጥፋት ፈጽሞ አንበረከክም! ብላችሁ ዛሬም እንደ ትናንቱ ተአምራዊ ታሪክ ለመሥራት እንድትዘጋጁ እያቀረብን፤ የተጀመረውን ድጋሚ ወረራ እና ጥፋት የሚመለከቱ የሁኔታዎች እድገት በየጊዜው በሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊው ማብራሪያ እና መግለጫ የሚሰጥበት መሆኑን እናስታውቃለን" ብሏል።

የኢትዮጵያዊነት ጠላቶች የምክክር ጉባኤ ባለቤቶችና ተመካካሪዎች እነማናቸው? የሚመከርባቸውስ?
የኢትዮጵያዊነት ጠላቶች የምክክር ጉባኤ ባለቤቶችና ተመካካሪዎች እነማናቸው? የሚመከርባቸውስ?

የአምሓራ ምድር የሆነውን አልፋሽቃን ለመውረር ከመጣው ሱዳን ጋር አሊያንስ ፈጥሮ ወልቃይት ጠገዴን በኃይል በወረራ ለመቆጣጠር የመጣው ኃይል ጋር የሚተባበር አምሓራን ከመክዳት ተነጥሎ አይታይም። የኦህ
የአምሓራ ምድር የሆነውን አልፋሽቃን ለመውረር ከመጣው ሱዳን ጋር አሊያንስ ፈጥሮ ወልቃይት ጠገዴን በኃይል በወረራ ለመቆጣጠር የመጣው ኃይል ጋር የሚተባበር አምሓራን ከመክዳት ተነጥሎ አይታይም። የኦህዴድ መንግስት መቀመጫ አራት ኪሎ እንጅ ወልቃይት አይደለችም።

አሁናዊ መረጃ ሁመራ ኢትዮጲያ ፦ በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ከሌሊት ጀምሮ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑ ተሰማ። እንደ ምንጮች ዘገባ ከሆነ፣ ተኩሱና ከ
አሁናዊ መረጃ ሁመራ ኢትዮጲያ ፦ በወልቃይት ጠገዴ ሰቲት ሁመራ ዞን በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ከሌሊት ጀምሮ በከባድ መሳሪያ የታገዘ ውጊያ እየተካሄደ መሆኑ ተሰማ። እንደ ምንጮች ዘገባ ከሆነ፣ ተኩሱና ከባድ መሳሪያው ድምፅ ከበረከት ወደ ሸረሪ እና ነጭ አፈር ባሉት የድንበር አከባቢዎች አቅጣጫ ነው። ከእኩለ ሌሊት ጀምሮ የተከፈተው ውጊያ በከባድ መሳሪያዎች የተደገፈ እንደሆነ ተጠቅሷል። (ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም)

በሳዑዲ የተመራ "የቀይ ባህር ዘብ" ጥምር መከላከያ ተቋቋመ፣ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ አልተካተቱም‼️ በሳዑዲ ዓረቢያ አስተባባሪነት፣ 14 አገራት በቀይ ባሕር፣ ባብኤል መንደብና የኤደን ባሕረ ሠላጤ የ
በሳዑዲ የተመራ "የቀይ ባህር ዘብ" ጥምር መከላከያ ተቋቋመ፣ ኤርትራ እና ኢትዮጵያ አልተካተቱም‼️ በሳዑዲ ዓረቢያ አስተባባሪነት፣ 14 አገራት በቀይ ባሕር፣ ባብኤል መንደብና የኤደን ባሕረ ሠላጤ የንግድና የኢነርጂ አቅርቦት መስመር ደኅንነትን የሚያስጠበቅ ጥምር የመከላከያ ኃይል አቋቋሙ። ጥምረቱ፣ አባል አገራት መረጃ እንዲለዋወጡ፣ የዘመቻ እቅድ እንዲያወጡና የጋራ የባሕር ላይ ልምምድ እንዲያደርጉ የሚያስችል ነው። ከአፍሪካ፣ ሶማሊያ፣ ጅቡቲ፣ ሱዳን፣ ግብጽ እና ናይጀሪያ የጥምረቱ መስራቾች ኾነዋል።  ከሌሎች መስራቾች መካከል ሳዑዲ ዓረቢያ፣ ኳታር፣ ቱርክ እና ፓኪስታን ይገኙበታል። ፍላጎቱ ያላቸው አገራት ጥምረቱን በማንኛውም ጊዜ መቀላቀል ይችላሉ ተብሏል። ኢትዮጵያ፣ ኤርትራ፣ ኬንያ፣ እና ኢምሬቶች በጥምረቱ መስራችነት ካልተካተቱ የቀጠናው አገራት መካከል ናቸው።

"የትግራይ ሰዎች (ህወሃቶች) ወልቃይት ጠገዴን በአማራ ስም የሚታገሉ ሃይሎች (ፋኖዎች) "ውሰዱት" ብለውን እያለ በፈለግነው መንገድ እንዳንወስድ ያደረገን ከአማራ ሃይሎች ይልቅ የፌዴራል መንግሥት ነው ይላሉ" ፋሽስቱ Abiy Ahmed Ali ራያን በተግባር ለህወሓት እንደሰጡ እናውቃለን በምን አግባብ ሰጡ? ንግግሩ ፋኖን ከህዝብ መነጠያ ሽሩብ ሴራ ነው። የትኛው የፋኖ ክንፍ ለህወሓቶች የአምሓራ እርስቶቹን "ውረሩ እና ያዙ" እንዳላቸው ግን አልጠቀሰም። ያም ሆነ ይህ፣ ሰውየው ትግራይ ጋር ለሚኖረኝ ጦርነት አግዙኝ፣ ህወሓት ጦር የሰበቀብኝ ወልቃትን በመከልከሌ እና በራሱ አስተዳድር ስር እንዲቆይ በማድረጌ ነው የሚል ሾርኔ ነው። አምሓራው እዚህ ጋር ብልጥ መሆን አለበት። ህወሓትም፣ ብልፅግናም አምሓራውን ከጎን በማሰለፍ በመስዋዕቱ አሸናፊ ሆኖ ለመውጣት እየተፎካከሩ እንጅ… ለዐምሓራው ጥቅም አንዳች አያስቡም። ይልቁንስ የመጀመሪያ እና ቀጣይ ረድፍ ጠላት ናቸው። በአምሓራ ውድቀት የሚያተርፉ የዘመን ጉዶች። እናም አምሓራው፣ በ2ቱ ትርምስ መካከል ጠንክሮ የሚወጣበትን ጥብ ያማትር እንጅ… ተቆስቋሽ ችቦ፣፣ መንገድ ጠራጊ ጀብደኛ እንዳይሆን ይጠንቀቅ!