es
Feedback
ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

Ir al canal en Telegram

የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍

El canal ሞዐ ሚዲያ- Moaa Media…✍ (@moamediamoresh) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 11 496 suscriptores, ocupando la posición 17 044 en la categoría Noticias y medios y el puesto 2 912 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 11 496 suscriptores.

Según los últimos datos del 01 agosto, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de -156, y en las últimas 24 horas de 5, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 8.95%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 6.57% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 1 029 visualizaciones. En el primer día suele acumular 756 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 4.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
የቤተ-አምሓራ ነፃ ህዝብ፣ የትግል ልሳን ነን፣ ይከተሉን፣ "ነፃ ሀሳብ ለነፃነት" መርኸ መስመራችን ነው!

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 02 agosto, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Noticias y medios.

11 496
Suscriptores
+524 horas
-427 días
-15630 días
Archivo de publicaciones
+1

አዲሱ የአምሓራ ትውልድ በፍጥነት መንቃት አለበት‼️
+1
አዲሱ የአምሓራ ትውልድ በፍጥነት መንቃት አለበት‼️

በህወሓት እና አገዛዙ መካከል በሰሜን አማራ ወልቃት ግንባር ግዛት ልዩ ስሙ ሸረሪና በተባለ ቦታ የተጀመረው ውጊያ መቆሙን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ማንነታቸው ያልተገለጸ የመረጃ ምንጮች ዋቢ አድርጎ
በህወሓት እና አገዛዙ መካከል በሰሜን አማራ ወልቃት ግንባር ግዛት ልዩ ስሙ ሸረሪና በተባለ ቦታ የተጀመረው ውጊያ መቆሙን የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ማንነታቸው ያልተገለጸ የመረጃ ምንጮች ዋቢ አድርጎ ዘገበ። ከኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር አቅራቢያ በሚገኘው ሰሜን አማራ ግዛት ሸረሪና የተባለ ቦታ ውጊያ የተቀሰቀሰው ትላንት ቅዳሜ ከማለዳው 12 ሰዓት ገደማ እንደሆነ አንድ ስማቸው ያልተገለጸ የህወሓት አባል መናገራቸውን የዜና ወኪሉ ዘግቧል። በከባድ የጦር መሣሪያ እና በድሮን ጭምር የተደረገው ውጊያው ከ23 ሰዓታት ገደማ በኋላ እንደቆመ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ዋቢ ያደረጋቸው የመረጃ ምንጭ ተናግረዋል። በግጭቱ ምን ያክል ሰዎች እንደተገደሉ ወይም እንደቆሰሉ መረጃ ከመስጠት ተቆጥበዋል። ስማቸው እንዳይገለጽ የጠየቁ ሌላ የጸጥታ የመረጃ ምንጭ በእርግጥም ውጊያው እንደቆመ ለፈረንሳይ ዜና አገልግሎት ተናግረዋል። ይሁንና ከህወሓት በኩል የቀረበው መረጃ ትክክለኛ መሆኑን በገለልተኝነት እንዳላረጋገጠ የፈረንሳይ ዜና አገልግሎት በዘገባው ጠቁሟል። በኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በተሰረዘው ህወሓት የሚመራው የትግራይ ክልላዊ መንግሥት ትላንት ቅዳሜ ባወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ፌድራል መንግሥት ከማለዳ ጀምሮ በሸረሪና በኩል ውጊያ ጀምሯል በማለት ወንጅሎ ነበር። አገዛዙ ግን ስለ ጉዳዩ በይፋ የሰጠው ማብራሪያም ሆነ ምላሽ የለም። ይሁንና የመስኖ እና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትሩ አብርሀም በላይ በተረጋገጠ የፌስቡክ ገጻቸው ባሠፈሩት ጽሁፍ ህወሓትን በሸረሪና በኩል ጦርነት በመክፈት ወንጅለዋል። በኦህዴድ አገዛዝ ሰራዊትና በህወሓት መካከል ሐምሌ 25 ቀን 2018 ውጊያ መቀስቀሱ የተሰማው በአዲስ አበባና በመቐለ በሚገኙ ባለሥልጣናት መካከል ያለው ውጥረት በኃይል በተባባሰበት ወቅት ነው።

ያልተነበበው ሰነድ ይነበብ!‼️
+1
ያልተነበበው ሰነድ ይነበብ!‼️

"አብይ አህመድ TPLFን ከደመሰሰ በኋላ አምሓራውን ወደ ማጥቃት ይዞራል… ስለዚህ ከTPLF ጋር መተባበር ግዳችን ነው" የሚል ትንተና … የልሂቅ ነው? እና አሁን እየጨፈጨፈን ያለው ለምን ይሆን? ባልተባበርንበት 7 ዓመታት ጭፍጨፋ እና መፈናቀል ቀርቶልን ነበርዴ? ባለመተባበር፣ በመተባበርም፣ ከዐምሓራ ጠላቶች ኢላማነት አታመልጥም። ይልቅ፣ ህዝባዊ ቅቡልነትህን ጠብቀህ የውስጥ አንድነት እና ክንድህን አፈርጥም! ዋስትናህ የማዶ አጋር ሳይሆን የራስህ ህዝብ እምቅ ጉልበት እና መስመራዊ ሰልፍ ነው።

የጦርነት ጭጋግ ያጠላበት ሰሜን አምሓራ ፀለምት ወረዳ በድርቅ ተመታ‼️ በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ ያለው የክረምት ሁኔታ ከላይ በምስል የተያያዘውን ይመስላል፣ ምንም ዝናብ የለም። የፓስፍክ ው
+2
የጦርነት ጭጋግ ያጠላበት ሰሜን አምሓራ ፀለምት ወረዳ በድርቅ ተመታ‼️ በሰሜን ጎንደር ዞን ጠለምት ወረዳ ያለው የክረምት ሁኔታ ከላይ በምስል የተያያዘውን ይመስላል፣ ምንም ዝናብ የለም። የፓስፍክ ውቂያኖስ ሙቀት ባልተለመደ ሁነታ በመጨመሩ ምክንያት በሰሜን፣ በመካከለኛና  ምስራቅ አከባቢ የዘንድሮው የክረምት ዝናብ አጭር መሆኑና ክረምቱም ቶሎ እንደሚወጣ የኢትዮጵያ ሜትሮዎሎጂ ማስታወቁ አይዘነጋም።

ህወሓት በኦህዴድ ምክክር ኮሚሽን መንጋ ውስጥ ወኪል አሳትፎ አዲስ አበባ ገብቷል‼️ እነ አጅሬው አስመራም ሱዳንም መቀሌም አዲስ አበባም ናቸው። ብዙ ሰው አዲስ አበባ መገኘታቸው ግራ ሊያጋባው ይችላል
ህወሓት በኦህዴድ ምክክር ኮሚሽን መንጋ ውስጥ ወኪል አሳትፎ አዲስ አበባ ገብቷል‼️ እነ አጅሬው አስመራም ሱዳንም መቀሌም አዲስ አበባም ናቸው። ብዙ ሰው አዲስ አበባ መገኘታቸው ግራ ሊያጋባው ይችላል። አስመራም ሱዳንም ያሉት ለጦርነቱ ነው። ለካስ ለምክክር ኮምሽኑም በርካታ ሰው ልከዋል። እኔ በምክክር ኮምሽኑ እየተሳተፈ የመሰለኝ ከእነ ደብረፅዮን ጋር የጥቅምና ስልጣን ብቻ ልዩነት ያለው የእነ ጌታቸውና ፃድቃን ቡድን ነበር። ትናንት ሳጣራ ግን እነ ደብረፅዮንም ለካ ተሳታፊ ልከዋል። በተለያየ አደረጃጀት፣ በተለያየ መንገድ! ጭራሽ "ግብአተ መሬቱን እንፈፅማለን" የሚሉትን የብልፅግናን አላማ ደግፈው ነው በምክክሩም እየጮሁ ያሉት። የኦሮሞ ብሔርተኞችን ደግፈው በአዲስ አበባ፣ በቋንቋና ሌላው ላይ እጅ እያቀሳሰሩ እንደሚውሉ አንድ ተሳታፊ አጫውቶኛል። ከአገዛዙና ከውሃብያ ቀጥሎ ጠርዝ ይዘው፣ አገርና አማራን እየወቀሱ ይውላሉ። እኔ እስከ ትናንት ድረስ ለጊዜው ከእነ ደብረፅዮን ያፈነገጠው ኃይል መሰሎኝ ነበር ምክክር ምናምን ላይ የተሳተፈው። እነ አጅሬውም "ሁሉም አይቅርብን" ብለው ወኪሎቻቸውን ልከዋል። ሲፈልጉ ደግሞ ተቃውመው መግለጫም ያወጣሉ። ኮምሽኑ "ትግራይን አሳተፍኩ" ማለት ፈልጓል። እነሱም የሆነ መድረክ እንዲያመልጣቸው አይፈልጉም። እናም በተለያየ መንገድ "አሳትፉን" እያሉ እየጠየቁ መጥተዋል። በተለያዩ አደረጃጀቶች ስም በምክክር ኮምሽኑ እየተሳተፉ ይገኛሉ። በምክክርኮሚሽን ተሳተፋችሁ ብሎ ንፁሃንን ያስር ይገድል የነበረ፣ ት/ቤት አስተማራችሁ ብሎ መምህራንን አንበርክኮ የሚነዳ የሚገድልም ፋኖ ነኝ ባይን ባሰብኩ ጊዜ በ2ቱ ኃይላት ሰርጎገብ እንደተወረርን እገነዘባለሁ።

Ethiopia: Drone Strike on Christian Monastery Raises Questions for Abiy Ahmed | Firstpost Africa Firstpost examines the growing fears among Ethiopia's Orthodox Christian community after a deadly drone strike reportedly hit the historic Abbay Giyorgis St. Arsema Unity Monastery in the Amhara region. Reports say the strike killed members of the monastic community and injured several others during a religious gathering. Ethiopian government sources have alleged that Fano fighters were using the monastery as a shelter, while church leaders strongly deny that any armed group was present and insist only priests, nuns and worshippers were targeted. The incident has drawn international condemnation, with the World Council of Churches calling for an independent investigation. It also comes amid broader concerns over attacks... Alyson Le Grange explains why this incident is resonating far beyond Ethiopia, raising questions about the protection of Africa's oldest Christian heritage during war, on Firstpost Africa.

የህወሓት የጦርነት ስትራቴጅው የሚመራው በአስመራ ሰዎች ነው። ራሱን መምራቱ ከእጁ እና ከህዝብ ፍላጎት ወጥቷል። የቀድሞ ህወሓት ቃል አቀባይ እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት የአሁኑ የፋሽስታዊ
የህወሓት የጦርነት ስትራቴጅው የሚመራው በአስመራ ሰዎች ነው። ራሱን መምራቱ ከእጁ እና ከህዝብ ፍላጎት ወጥቷል። የቀድሞ ህወሓት ቃል አቀባይ እና የትግራይ ክልል ጊዜያዊ ፕሬዝዳንት የአሁኑ የፋሽስታዊ አገዛዙ ደህንነት አማካሪ ጌታቸው ረዳ

"ጽምዶ" ሲባል "አቤት!" የሚል አምሓራ የለም። የሁለትዮሽ "ሻዕቢያ እና ወያኔ" ጥምረት መካከል አምሓራ ስፍራ የለውም። ጌቶቻቸው ሲመቱ የሚጮሁ ተላላኪ ቡችሎች የሉም ማለት ግን አይደለም። አምሓራ
"ጽምዶ" ሲባል "አቤት!" የሚል አምሓራ የለም። የሁለትዮሽ "ሻዕቢያ እና ወያኔ" ጥምረት መካከል አምሓራ ስፍራ የለውም። ጌቶቻቸው ሲመቱ የሚጮሁ ተላላኪ ቡችሎች የሉም ማለት ግን አይደለም። አምሓራ የራሱ የህልውና ትግል እና መራራ ጦርነት ውስጥ ከገባ ዘመናት ባቱ…!

በሳዑዲ አረቢያ ኢትዮጵያውያን በዘፈቀደ ታፍነው እየታሰሩ ነው‼️ የሳዑዲ ዓረቢያ ፖሊስ የአገሪቱን ድንበር በሕገወጥ መንገድ አቋርጠው ሊገቡ ሞክረዋል ያላቸውን በብዙ መቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን አሠረ። የአገሪቱ የጸጥታ ኃይሎች ባለፉት ስድስት ቀናት ባካሄዱት የጸጥታ ቁጥጥር ዘመቻ ካሠሯቸው 1 ሺሕ 418 ሰዎች መካከል፣ 45 በመቶዎቹ ኢትዮጵያዊያን መኾናቸውን የአገሪቱ ጋዜጦች ዘግበዋል። የጸጥታ አካላት በተጠቀሠው ጊዜ ውስጥ በሕገወጥ መንገድ ድንበር ከማቋረጥ፣ ከመኖሪያ ፍቃድ እና ከሠራተኛ ቅጥር በተያያዙ ወንጀሎች በጠቅላላው 14 ሺሕ 154 ሰዎችን አስረናል ማለታቸውን ዘገባው ጠቅሷል። ከሳምንት በፊት በተመሳሳይ ድንበር በሕገወጥ መንገድ ሲያቋርጡ በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያዊያን እንደታሠሩ ተዘግቦ ነበር። በሌላ በኩል፣ በአገሪቱ እስር ቤት የሞት ፍርዳቸውን የሚጠባበቁ እስከ 200 የሚደርሱ ኢትዮጵያዊያን እንደሚገኙ በምስጢር ካነጋገራቸው ፍርደኞች መረዳቱን ቢቢሲ ዘግቧል።

አማራን ማጥፋትን የፖለቲካ እስትንፋሱና የኅልውናው መሠረት አድርጎ የተፈጠረውን፣ በዚያው ዓላማ የኖረውንና ወደፊትም በዚያው የጥፋት መንገድ የሚቀጥለውን ፋሽስት ወያኔን የአማራ የኅልውና ተጋድሎ አጋር አድርገው ለማቅረብ የሚደረገው አሳፋሪና ወንጀለኛ ሙከራ ዝም ተብሎ ወደማይታለፍበት ደረጃ ላይ ደርሷል። በየማኅበራዊ ሜዲያው እየወጡ ፋሽስት ወያኔን እንደ አማራ ‘ትግል’ አጋር እንድንቆጥርላቸው ላንቃቸው እስኪሰነጠቅ ድረስ ሲለፋደዱ የሚሰሙት አብዛኛዎቹ የፋሽስት ወያኔ ነውረኛ ድርጅት የሆነው የብአዴን ጠረናቸው ሳይለቅ፣ በአማራ የኅልውና ተጋድሎ ላይ ተጣብቀው የተቀመጡ አለቅቶች ናቸው። እነዚህ ፋሽስት ወያኔን ለአማራ ሕዝብ ሊሸጡለት የሚሞክሩት በአማራ ሕዝብ የኅልውና ተጋድሎ ላይ የተጣበቁ የብአዴን አለቅቶች ፋሽስት ወያኔ ከተፈጠረ ጀምሮ ከኀምሳ ዓመታት በላይ በአማራ ሕዝብ ላይ በቀጥታ ሲፈጽምና በወኪሎቹ ሲያስፈጽም የኖረውን ፍጅት፣ የዘር ማጥፋት፣ እልቂት፣ መከራ፣ ግፍ፣ ማፈናቀልና ተቆጥሮ የማያልቅ ታሪካዊ በደል ዳግም በመካድ፣ በአማራ ሕዝብ ደም፣ መስዋዕትነት፣ ክብርና ታሪካዊ ትውስታ ላይ ግልጽ ክህደትና ከባድ የፖለቲካ ወንጀል እየፈጸሙ ነው። ፋሽስት ወያኔ ትናንትናም ሆነ ዛሬ ጦር የሚሰብቀውና የሰበቀው አማራን ለማጥፋት እና አጽመ ርስቱ የሆኑትን ወልቃይትን፣ ጠገዴን፣ ጠለምንት፣ ሁመራን፣ ኮረምን፣ አላማጣ፣ ዋጃ፣ መሆኒ እና በወረራ የያዛቸውን የራያ አካባቢዎች ለመውረር እና ታላቋን ትግራይ ለመመስረት ብቻ ነው። ፋሽስት ወያኔ ከዚህ ውጭ የሚዋጋበት ምክንያት የለውም! በአሁኑ ወቅት አማራ የሚያስፈልገው የአማራ አላማ ያለው እና በጥብቅ ዲሲፕሊን የሚገዛ አታጋይ ድርጅት እንጂ እንደ ፋሽስት ወያኔ አይነት አማራን ማጥፋትን የፖለቲካ እስትንፋሱና የኅልውናው መሠረት ያደረገ የትግል ‘አጋር’ አይደለም። ባጭሩ እንደ ቱትሲ የዘር ማጥፋት ጦርነት የታወጀበት የአማራ ሕዝብ እንደ ሁቱዎቹ ኢንተርሃሞዮች ከኾነበት የዐቢይ አሕመድ የኦሮሙማው አረመኔ አገዛዝ የዘር ማጥፋት ጦርነት ለመትረፍ ያለው ብቸኛ አማራጭ እንደ ቱትሲዎቹ አላማ እና ዲሲፕሊን ያለው የአርበኞች ድርጅት ማቋቋምና እንደ ፖል ካጋሜ አይነት ጀግና የአርበኛ መሪ መፍጠር እንጂ ሲያጠፋው ለኖረውና ሊያጠፋው ጦር ከሚሰብቀው ፋሽስት ወያኔ ጋር አንሰላ መጋፈፍ አይደለም። የአማራ ሕዝብ እንደ ቱትሲዎቹ አላማ እና ዲሲፕሊን ያለው የአርበኞች ድርጅት ማቋቋምና ከራሱ በላይ የኾነ አላማ ያለው አታጋይ መሪ ካገኘ የፋሽስት ወያኔና መሰል ጸረ አማራ እና ጸረ ኢትዮጵያ ድርጅቶች አጋር አያስፈልገውም።

#USA 🇺🇸 #VISA አሜሪካ ለቪዛ የምትይዘውን ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ዶላር ልታሳድግ ነው። የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የበርካታ አገራት ዜጎች ቪዛ ሲያመለክቱ ያስይዙት የነበረውን ገንዘብ ከ15 ሺህ ዶላር ወደ 20 ሺህ ዶላር (3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) ከፍ በማድረግ ቋሚ ሊያደርግ ነው። መሥሪያ ቤቱ እንደገለፀው መርሃ ግብሩ የቢዝነስ እና የቱሪስት (ቢ1 እና ቢ2) ቪዛ አመልካቾች ላይ ተግባራዊ የሚሆን ነው። ከተፈቀደላቸው ጊዜ በላይ አሜሪካ ውስጥ ከቆዩ ገንዘቡ ተመላሽ እንዳይሆን የሚያደርገው ይህ አሠራር ተግባራዊ ይሆንባቸዋል ከተባሉ አብዛኞቹ ከአፍሪካ ከሆኑ 50 አገራት መካከል ፦ - #ኢትዮጵያ፣ - ጂቡቲ፣ - ናይጄሪያ፣ - ሴኔጋል፣ - ኡጋንዳ፣ - ታንዛኒያ ይገኙበታል። ይህ በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው የተሻሻለው ፕሮግራም፣ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ የሚቆዩ ጎብኝዎችን ለመከላከል ያለመ መሆኑ ተገልጿል። በመርሃ ግብሩ መሠረት አመልካቾች እንደ ኤምባሲው ኦፊሰሮች ውሳኔ ለቪዛ እስከ 20 ሺህ ዶላር (ከ3.1 ሚሊዮን ብር በላይ) የሚደርስ ገንዘብ እንዲያስይዙ ሊጠይቁ ይችላሉ። አሜሪካ ውስጥ ከቪዛ ጊዜያቸው በላይ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ዜጎች ባሏቸው አገራት እና የአገር ውስጥ ሰነዶች ላይ የላላ ቁጥጥር በሚያደርጉ አገራት የቪዛ ማስያዣ የሙከራ መርሃ ግብር ተግባራዊ ማድረግ የጀመረችው ባለፈው ዓመት ነሐሴ ወር ነበር። መርሃ ግብሩ ለአንድ ዓመት የሚቆይ የነበረ ሲሆን የተቀመጠለት ጊዜ መጠናቀቁን ተከትሎ ነው አዲሱ መመሪያ የወጣው። በቀናት ውስጥ ተግባራዊ መሆን ይጀምራል የተባለው ይህ አዲሱ የቪዛ ማስያዣ ገንዘብ ፕሮግራም ቋሚ እንደሚሆንም ተገልጿል። በተጠናቀቀው የሙከራ መርሃ ግብር መሠረት አመልካቾች ከ5 ሺህ ፣ ከ10 ሺህ እስከ 15 ሺህ ዶላር ድረስ እንዲያስይዙ ይጠየቁ የነበረ ሲሆን በአዲሱ ፕሮግራም አነስተኛው 5 ሺህ ዶላር ከዝርዝሩ ወጥቶ፣ ከፍተኛው የማስያዣ ገንዘብ ወደ 20 ሺህ ከፍ ተደርጓል። በአዲሱ መርሃ ግብር ከተካተቱ 50 አገራት መካከል 30ዎቹ የሚገኙት በአፍሪካ ውስጥ ነው።

አምሓራውን ያገለለው ህገ-አራዊት የወያኔ ቅርጫ ክልል… ከዐምሓራው የነጠቀው አዲስ አበባን ሳይሆን ሸዋን ነው። የሸዋን ባለቤትነት በማስመለስ ውስጥ የሸዋ እምብርቷ የነገስታቱ ማዕከል "አዲስ አበባ"
+1
አምሓራውን ያገለለው ህገ-አራዊት የወያኔ ቅርጫ ክልል… ከዐምሓራው የነጠቀው አዲስ አበባን ሳይሆን ሸዋን ነው። የሸዋን ባለቤትነት በማስመለስ ውስጥ የሸዋ እምብርቷ የነገስታቱ ማዕከል "አዲስ አበባ" የዳዊት ከተማ በረራም ነፃ ትወጣለች። አምሓራን ከፖለቲካ ማዕከሉ፣ ከነገስታቱ አንባ ሸዋ ለመግፋት ሲባል… ብዐዴንን ጠፍጥፎ ፈጥሮ ወደ ባህር ዳር የሸኜው የዛኔው የወያኔ ሴረኛ… አሁን ላይ በአምሓራ እርስት ላይ ለመጨፈር እርስቱንም ለመንጠቅ የሚንደረደረውን የኦህዴድ ኦነግ መንጋ… ከወለጋ፣ ባሌ፣ አርሲ፣ ከሀረር እና ብረና ጠርቶ በአዲስ አበባ በማንገስ አጋር አድርጎ ቆይቷል። ያ፣ እንግዳ ቡድን ነው፣ ዛሬ ላይ አዲስ አበባን ለመዋጥ የሚስገበገበው። ወዳጄ… ግጬውን ያማተረው ህወሓት፣ ዋናችንን አስረክቦ እንደፈረጠጠው… አዲስ አበባን የሚያማትረው የጅማ፣ ባሌ እና አርሲ ወራሪ ሸን አስርክቦ ነገሌ የሚገባበትን አደገኛ ጨዋታ ጀምሯል። መጨረሻውን አብረን እናያለን!

በኦህዴድ ብልፅግና የተዋቀረው የፌክ ድራማው ተቋም ውስጥ “ተፅዕኖ ፈጣሪዎች” የተባሉ ግለሰቦች በምክክሩ እንዲሳተፉ በምን መስፈረት ተመረጡ? የሚለው ጥያቄ ከውስጥ መልስ የተሰጠበት ሲሆን… ተፅዕኖ ፈ
በኦህዴድ ብልፅግና የተዋቀረው የፌክ ድራማው ተቋም ውስጥ “ተፅዕኖ ፈጣሪዎች” የተባሉ ግለሰቦች በምክክሩ እንዲሳተፉ በምን መስፈረት ተመረጡ? የሚለው ጥያቄ ከውስጥ መልስ የተሰጠበት ሲሆን… ተፅዕኖ ፈጣሪ የተባሉት ውስጥ 97% የሚሆኑት በብልፅግና ፓርቲ ጥቆማ የተደረገባቸው ናቸው። በክልል ተወካዮች ጉባኤ በክልሎችና በፌደራል ደረጃ በድምሩ 31 በብልፅግና የተጠቆሙ እና የተላኩ “ተጽዕኖ ፈጣሪዎች” እንዲካተቱ ተደርጓል። ይህ ውክልና፤ የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅቶች፣ መምህራን፣ አካል ጉዳተኞች፣ ወጣቶች እና ሴቶች ካገኙት ውክልና የሚበልጥ መሆኑን ያነሱ ቅሬታ አቅራቢዎችም፤ ኮሚሽኑ ይሄን መሰል የአንድ ድርጅት ፍላጎት አስፈፃሚዎች የወረሩት አካሔድን ዳግም እንዲያጤነው ጥቂት በኦህዴድ ማዕበለ ወኪሎች የተወረሩ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል። 

ጦርነት ተከፍቶብናል:-ህወሓት‼️ "የትግራይ ህልውና በብልፅግና መቃብር ላይ ይወሰናል" በሚል ስብሰባ ሲያካሂድ የከረመው ህወሓት በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ተከፍቶብናል ብሏል። ሙሉ የመግለጫው ትርጉም👇
ጦርነት ተከፍቶብናል:-ህወሓት‼️ "የትግራይ ህልውና በብልፅግና መቃብር ላይ ይወሰናል" በሚል ስብሰባ ሲያካሂድ የከረመው ህወሓት በምዕራብ ትግራይ ተኩስ ተከፍቶብናል ብሏል። ሙሉ የመግለጫው ትርጉም👇👇 "የፌደራል መንግሥቱ የትግራይን ሕዝብ ለማጥፋት ሲያካሂድ የቆየውን ሁለንተናዊ ከበባ እና እገዳ፣ በድሮን እና በተላላኪ ታጣቂዎቹ ሲፈጽም የቆየውን ጥቃት ወደ ከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ፣ ዛሬ ሐምሌ 25 ቀን 2018 ዓ.ም. ከማለዳው ጀምሮ በምዕራባዊ ትግራይ ዞን በሸረሪ አቅጣጫ ግልጽ ጦርነት ጀምሯል። የፕሪቶሪያው ስምምነት ከተፈረመ በኋላ እንኳ የትግራይን ሕዝብ ለማንበርከክ እና ለመበታተን ካለው ከፍተኛ ፍላጎት ተነሥቶ የተለያዩ ከበባዎችን፣ እገዳዎችን እና ወታደራዊ ዝግጅቶችን ሲያደርግ ቆይቶ፤ ድጋሚ ትግራይን ለመውረር እና ሕዝቡን ለማጥፋት ተነሳሽነት ወስዶ ጦርነት ከፍቶብናል። ​ስለሆነም በሀገር ውስጥ እና በውጭ የምትኖሩ የትግራይ ሕዝብ፣ ሁላችሁም የትግራይ የጸጥታ ኃይሎች፣ ብሔራዊ ኃይሎች እና የትግራይ ታጋዮች፣ የትግራይ ሲቪል ማኅበራት፣ የትግራይ ሃይማኖት ተቋማት እና ሌሎች የሚመለከታችሁ አካላት በሙሉ ብሔራዊ ህልውናችንን ለማረጋገጥ በሚደረገው ፍትሐዊ ትግል "ለብሔራዊ ጥፋት ፈጽሞ አንበረከክም! ብላችሁ ዛሬም እንደ ትናንቱ ተአምራዊ ታሪክ ለመሥራት እንድትዘጋጁ እያቀረብን፤ የተጀመረውን ድጋሚ ወረራ እና ጥፋት የሚመለከቱ የሁኔታዎች እድገት በየጊዜው በሚመለከታቸው አካላት አስፈላጊው ማብራሪያ እና መግለጫ የሚሰጥበት መሆኑን እናስታውቃለን" ብሏል።