en
Feedback
"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

Open in Telegram

🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ልጅ🤗

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

Channel "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 (@orthodoxtewahdoc) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 25 480 subscribers, ranking 2 898 in the Religion & Spirituality category and 1 362 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 25 480 subscribers.

According to the latest data from 07 September, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 68 over the last 30 days and by 33 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 3.72%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 2.59% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 947 views. Within the first day, a publication typically gains 660 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 13.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ...

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 08 September, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the Religion & Spirituality category.

25 480
Subscribers
+3324 hours
+487 days
+6830 days
Posts Archive
ዛሬ ጳጕሜ 3 ቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱ ነው❤ "ሩፋኤል ማለት ሩፋ ማለት ጤና ፈውስ ፣ መድሃኒት ሲሆን ኤል ማለት ደሞ አምላክ ፣ እግዚአብሔር ማለትነው። አማላጅነቱ አይለየን🙏❤
ዛሬ ጳጕሜ 3 ቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱ ነው❤ "ሩፋኤል ማለት ሩፋ ማለት ጤና ፈውስ ፣ መድሃኒት ሲሆን ኤል ማለት ደሞ አምላክ ፣ እግዚአብሔር ማለትነው። አማላጅነቱ አይለየን🙏❤

ድርሳነ ቅዱስ ሩፋኤል ዘጷጒሜ🤲🌷 ቅዱስ ሩፋኤል ሆይ ፈታሂ ማህፀን ነህና ልጅ አተው በፀበል የሚንከራተቱትን በልጅ ባርክልን። የተወለዱትን በስነ ምግባር አንፅልን አሜን በእውነት🤲🌷 https://t.me/Orthodoxtewahdoc

❗ከዋሸህ አትማል አንዱ ኃጢአት ይበቃል📍 ስንስካር ዘወርኀ ጷጒሜን ፫/3 ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ፀሎት ይማረን በቸርነቱ ለዓዲሱ ዓመት ያድርሰን💗🌷🤲

#ድንግል_ማርያም ሀሳብ ጭንቀታችንን ከስሩ ትንቀልልን በሰላም ለአዲሱ ዓመት ታድርሰን መውጣት መውረዳችንን ትይልን🙏❤
#ድንግል_ማርያም ሀሳብ ጭንቀታችንን ከስሩ ትንቀልልን በሰላም ለአዲሱ ዓመት ታድርሰን መውጣት መውረዳችንን ትይልን🙏❤

✨ 🌼🌼🌼 የንጉሥ ሥልጣን በሥጋ ላይ ነው፤ የካህን ሥልጣን ግን በነፍስ ላይ ነው፡፡ ንጉሥ ይቅር ቢል የገንዘብን ዕዳ ነው፤ ካህን ይቅር ሲል ግን የበደል የኃጢኣት ዕዳን ነው። ንጉሥ ያዝዛል፤ ካ
✨                  🌼🌼🌼 የንጉሥ ሥልጣን በሥጋ ላይ ነው፤ የካህን ሥልጣን ግን በነፍስ ላይ ነው፡፡ ንጉሥ ይቅር ቢል የገንዘብን ዕዳ ነው፤ ካህን ይቅር ሲል ግን የበደል የኃጢኣት ዕዳን ነው። ንጉሥ ያዝዛል፤ ካህን ግን ያስተምራል ይዘክራል፡፡ ንጉሥ ያስገድዳል፤ ካህን ግን ነጻ ፈቃድን ያያል፡፡ ንጉሥ ቁሳዊ የጦር ዕቃ መሣሪያ አለው፤ ካህን ግን ረቂቅ (መንፈሳዊ) የጦር ዕቃ መሣሪያ አለው፡፡ ንጉሥ የጦር ዕቃ መሣሪያውን ቢሰብቅ አንገዛም ብለው ባመፁት (እንዲሁም ከወራሪዎች ሥጋውያን ደማውያን) ላይ ነው፤ ካህን ግን ውጊያው ከጨለማ አበጋዞች ከአጋንንት ጋር ነው፡፡ ስለዚህ ሥልጣነ ክህነት ከሥልጣነ መንግሥት ይበልጣል፡፡ እንዲህም በመኾኑ ንጉሥ አንገቱን ለካህናት እጅ ያጎነብሳል። አባቶች ካህናትን እግዚአብሔር ይጠብቅልን ! [ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ] https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ጷጒሜን 3 ርኅወተ ሰማይ ትባላለች። ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የፀሎት መዝገብ የሚከፍትበት ልዮ ቀን ነው። ጸሎታችንን ያሳርግልን🙏😥
ጷጒሜን 3 ርኅወተ ሰማይ ትባላለች። ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የፀሎት መዝገብ የሚከፍትበት ልዮ ቀን ነው። ጸሎታችንን ያሳርግልን🙏😥

ካህኑ መልከ ጼዴቅ ቸሩ መድኃኔዓለም ከበረከቱ ይክፈለን ፀጋ በረከቱን ያሳድርብን አሜን🤲
ካህኑ መልከ ጼዴቅ ቸሩ መድኃኔዓለም ከበረከቱ ይክፈለን ፀጋ በረከቱን ያሳድርብን አሜን🤲

💝🌿ጳጒሜን 3🌿💝 "በዚች ቀን የመላእክት አለቃ የከበረ መልአክ የቅዱስ #_ሩፋኤል የበዓሉ መታሰቢያ ነው ።እርሱም ከመላእክት አለቆች ሦስተኛ የሆነ ነው ። ደግሞም ከእስክንድርያ ውጭ በደሴት የታነፀች ቤተ ክርስቲያኑ በከበረ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ ዘመን በውስጧ ተአምር የተገለጸባት የከበረችበት ነው ። ይህም እንዲህ ነው ሀብታም ሴት ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ መጥታ ሳለ ከእርሷ ጋርም ብዙ ሰው ነበረ ። ከባሏም የወረሰችው ብዙ ገንዘብ አላት በሊቀ ጳጳሳቱ ቤት አንጻር ያለውን ኮረብታ አስቆፈረችው በጥቅምት ወር ዐሥራ ስምንት ቀን እንደጻፍን የወርቅ መዝገብ ተገለጠ ። በዚያም ወርቅ ብዙዎች አብያተ ክርስቲያናትን አነፀ ከእርሳቸውም አንዲቱ የመላእክት አለቃ በሆነ በከበረ መልአክ ሩፋኤል በስሙ የታነፀች ይህች ናት ። ሥራዋንም በፈጸመ ጊዜ እንደዛሬው በዚች ቀን አከበራት ። ብዙ ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈጽማ ተናወጸች ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና ። የሰዎች ብዛትም በከበደው ጊዜ ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሣሣው ። ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔርም በከበረ መልአክ ሩፋኤል ስም ጮኹ ያን ጊዜ ይህ የከበረ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ እንዲህ አለው እግዚአብሔር አዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጽ ጸጥ ብለህ ቁም ። አንበሪውም ጸጥ ብሎ ቆመ አልታወከም በውስጧም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ለሕሙማንም ፈውስ ሆነ ። ይቺም ቤተ ክርስቲያን እስላሞች እስከተነሡበት ዘመን ኖረች ከዚህም በኋላ ሁለተኛ ያ አንበሪ ተናወጸ ደሴቲቱም በላይዋ ከሚኖሩ ብዙ ሕዝብ ጋራ ሠጠመች ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን የዚህም መልአክ በረከቱ ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን። የሰማያት መዛግብትም ከእጄ በታች ተጠብቀው የሚኖሩ እኔ ሩፋኤል ነኝ ። እኔም እግዚአብሔር እንዳዘዘኝ እከፍታቸዋለሁ እዘጋቸዋለሁም ። በምድር ሰው ለባልንጀራው ስለ ስሜ በጎ ነገር ቢያደርግ እኔ በመከራው በችግሩ ረዳዋለሁ ወይም የሹመቴን ነገር የሚጽፍ ወይም ከቅዱሳን ጋራ ስሜን የሚያስብ ወይም በስሜ ለቊርባን የሚሆነውን የሚሰጥ ወይም በበዓሌ ቀን ምጽዋትን የሚሰጥ ይኸውም እግዚአብሔር በሊቃነ መላእክት ክብር የሾመኝና ያከበረኝ ጳጕሚን ሦስት ቀን ነው ። ወደ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት እስከማስገባው በብርሃን ሠረገላ እኔ እሸከመዋለሁ በምድር ላይ ከቶ እንደርሱ ያለ የማይገኝ መዐዛው እጅግ ጣፋጭ በሆነ ሽቱ ነፍሶቻቸው እርሱን በማሽተት ደስ እንዲላቸው አደርጋለሁ ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ መልአክ አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን ። 💚💛❤️ በቅንነት ቴሌግራም ይቀላቀሉ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

🌹#አፄ_ዘርዓ_ያዕቆብ🌹🙏 ☞"ጳጉሜ 3 እንኳን ለጻድቁ አባታች ለንጉስ አጼ ዘርያዕቆብ የዕረፍታቸው መታሰቢያ በሰላም አደረሳችሁ፡፡ፅንሰት አቡነ ፊሊጶስ(ዘደብረ ቢዘን) የተባሉ ቅዱስ አባት ነበሩ በወቅቱ ከግብፅ ከመጡ አባቶች ተከራክረው ረቷቸው፡፡ በዚህ ምክንያት ተሸናፊዎቹ ወደ ባህርዳር ይጥሏቸዋል፡፡ በወቅቱ የንጉሱ ሚስት የነበረችው በዋናተኛ አስፈልጋ ከሐይቁ ውስጥ አሰወጣቻቸው እግራቸውን አጥባ እጣቢው ጠጣችው ወዲያው ከማህፀንሽ ፍሬ ታላቅ ጻድቅ ልጅ ይወጣል ብለው ትንቢት ነገሯት፡ ☞በትንቢታቸው መሠረት ታላቁ ንጉስ አጼ ዘርያዕቆብ ተጸነሱ፡፡ ☞ውልደት☞የተወለዱበት ዘመን 1391ዓ ም ሲሆን የትውልድ ቦታ ቡልጋ ልዩ ስሙ ጥልቅ ይባላል፡፡ ☞መምህር☞አጼ ዘርያዕቆብን በምግባር እና በእውቀት ያስተማሯቸው ከ40 መጽሐፍ በላይ የደረሱት የእመቤታችን ወዳጅ አባ ጊወርጊስ ዘጋስጫ ናቸው፡፡ ☞ድርሰት☞ አጼ ዘርያዕቆብ በርከት ያሉ ድርሰቶችን ደርሰዋል ከእነዚህ መካከል መልክአ ማርያም፤ መልክአ ጊወርጊስ፤ መጽሐፈ ብርሃን፤ መጽሐፈ ስላሴ፤ ተአቅቦ ምስጢር፤ ስብሐት ፍቅሩ፤ መጽሐፈ ምላድ፤ መጽሐፈ ባሕር፤ ዜና አይሁድ ከብዙ በጥቂቱ ተጠቃሾች ናቸው፡፡ ☞ከትርጉም ስራዎቻቸው መካከል ተአምረ ማርያም እንዲሁም ተርጓሜ ወንጌል ይገኙበታል፡፡ ☞ስርአተ ቤተክርስቲያን✞አጼ ዘርያዕቆብ ሲነሱ አብሮ የሚነሳው የሥርአተ ቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ይነሳል በእለተ ሰንበት ከቅዳሴ በኃላ ተአምረ ማርያም እንዲነበብ፤ የአንገት ማህተብ ማድረግን ያወጁ፡ነጠላ መልበስን እና የሳዕታት ፀሎት አስደምረዋል፡፡ ☞ከእመቤታች ያገኙት ክብር እኔ ያልፈቀድኩለት ደጄን አይረግጥም(ፃድቃኔ ማርያምን መሆኗን ልበ በሉ)ደጄ መጥቶ ውዳሴ ማርያምን በሰባት ጊዜያት በመፀለይ ስምህንና ስሜን አንድ አድርጎ የአጼ ዘርያዕቆብ እመቤት የጻድቃኔዋ ማርያም እያለ የተማፀነኝ ለበቁት አባቶች በገሀድ እገለጥላቸዋለሁ ችግራቸውን እፈታላቸዋለሁ፡፡ ላልበቁት ወጣንያን በህለም በራዕይ አነግረቸዋለሁ ብላ ታላቅ ቃል ኪዳን ገብታላቸዋለች፡፡ ☞ከፈጣሪ ያገኙት ክብር☞---ዳግመኛ ከሚያስፈራ ከሚያስደነግጥ ገደል ውስጥ ጨለማ አዩ ብዙ ሰዎች በውስጡ ይወድቃሉ፡፡ አባታች መባ ጽዩን መድኃኒ ዓለምን ጠየቁት እነዚህ ሰዎች እነማን ናቸው አሉ?ንጉስ ዘርያዕቆብን ያሙት ናቸው፡፡ ስለዚህ ነገር ተፈረደባቸው አለው፡፡ ☞ዳግመኛ በነጫጭ ፈረሶች አምሳል ሁለት ደመናዎችን አየ እነዚህ ፈረሶች የማናቸው ብሎ መባ ጽዮን ጠየቁት መድሀኒዓለም አንዱ የአንተ አንዱ የአጼ ዘርያዕቆብ ወደ ሰማያዊት እየሩሳሌም ስትሄዱ የምትቀመጡባቸው ናቸው፡፡ ☞አባታችን መባ ጽዮን እንዲህ አሉ እኔ በደለኛው ሀይማኖቱ የቀና ከእውነተኛ ፈራጅ ከአጼ ዘርያዕቆብ ጋር በምን አስተካከለኝ አለ ☞መድሀኒዓለም አለ በእኔ ፍቅር ልባችሁ ሰለሚቃጠል ነው አለው ይህን ሰምተው ከመድሀኒዓለም ስጦታ የተነሣ መባ ጽዮን አደነቁ፡፡ ☞መስቀል ስለ ጌታችን መስቀል ወደ ኢትያጵያ መምጣት ጋር ተያይዞ አባታቸው አጼ ዳዊት ጀምረው ከዳር ሳያደርሱት ሞቱ፡፡ ከዚያም ልጃቸው አጼ ዘርያዕቆብ መስቀሉን ወደ ኢትዩጵያ እንዲመጣ አድርገዋል፡፡ ☞ከመስቀሉ በአለፈም አጼ ዘርያዕቆብ የብዙ ቅዱሳን አፅም አምጥተዋል ከነዚህ መሀከል የቅድስት ድንግል ማርያም እናት የቅድስት ሀና ማርያም፤ የመጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ አንገት፤ ልቋስ የሰላት የእመቤታች ስዕል፤ ልብሱን ገርፈው ካበቁ በኃላ ሊሳለቁበት ያለበሱት ከለሜዳ፤ ተጠማሁ ባለ ጊዜ ከርቤውን ከሐሞቱ ቀላቅለው መራራ ሐሞት ያጠጡበት ሰፈነጉን እና ሌሎችን አሰመጥተዋል፡፡ ☞እስተዋፅኦ ለቤተክርስቲያን ይሁን ለአለም ትልቅ አስተዋፅኦ አበርከተዋል ግማደ መስቀሉን ለምዕመኑ መማፀኛ ለሀገር መጠበቂያ አድርገዋል፡፡ ☞በተደራጀ ፈረሰኛ እግረኛ ባለ ጦር ፤ባለቀስት ባለሰይፍ ጀሌ የአገር ግምባታ ፖሊስን በማጠናከር አገሮችንና ክፍለ ሀገራትን በሙሉ በአንድ ማዕከላዊ መንግሥት ስርአት አደራጅተዋል፡፡ ☞መካገ ጎለጎታ፤ፃድቃኔ ማርያም በአሞህራ ዳህያ በሚባል ቦታ ደብረ ነጎድጎድ (ዮሐንስ) ቤተክርስቲያን አሰርተዋል፡፡ ☞ደብረ ብርሃን በንግሰና አስተዳድረዋል፡፡ ☞ብርሃን እንዴት ወረደላቸው?አጼ ዘርያዕቆብ ከሚስታቸው እና ከልጃቸው ጋር ሊቆርቡ ወደ ቤተክርስቲያን ገቡ፡፡ በቁርበባንሰዓት የአጼ ዘርየያዕቆብ ሚሰስት በፅዋው ውስጥ ገባ በዚያ ጊዜ ዲየያቁኑ ፀጉራቸውን ቆርጦ በላው እሳቸውን ገፋቸው በዚህ ጊዜ የንጉሱ ልጀ ዲያቆኑን እናቴን እንዴት ትገፋታለህ ብሎ ከቅዳሴ ሲወጣ ጠብቆ ገደለው፡፡ ☞ይህ ጉዳይ የሀገር ሽማግሌዎች ቢያዩት ጉዳዩን ለንጉሱ ልጅ አድልተው የንግስቲቱን ክብር ዝቅ አድርጓል ብለው ለንጉሱ ልጅ ፈረዱ፡፡ ☞ለመጨረሻ ውሳኔ ንጉሡ ጋር ደረሰ ንጉሡም ከእኔ ልጅ እና ከስጋዎ ደሙ ማን ይበልጣል አሏቸው ሸማግሌዎቹም ስጋ ወደሙ አሉ እንግዲያውስ ዲያቆኑ በተገደለበት ቦታ ልጄን ወስዳችሁ ግደሉት ብለው አዘዙ በዚህ ጊዜ በፍርዳቸው ቀናነት ብርሃን ወረደላቸው፡፡ ደብረ ኢባ ትባል የነበረች ከተማ ደብረ ብርሃን ተብላ መጠራት ጀመረች፡፡ ☞በዕለ ዕረፍት በነገሱ በ34 አመታቸው በድንገት በ69 አመታቸው ጳጉሜ 3 1460 ዓ/ም አርፈዋል፡፡ ☞ከቦታወች ሁሉ ይቺን ቦታ መርጠን አክብረናታል በሏት በጣና ሐይቅ ደሴት በታላቅ ቦታ ዳጋ እስጢፋኖሰ አሰከሬናቸው አርፏል፡፡ ☞እግዚአብሔር የመረጣቸው ድንግል ማርያም ያከበረቻቸው የአጼ ዘርአይቆብ የጸሎታቸው በረከት አይለየን፡፡ ☞የጹሁፍ ምንጭ☞(መዝገበ ቅዱሳን፤ መጽሐፈ ጤፋት፤ ምስጢረ ድህነት፤ ድርሳነ መድሀኒዓለም) ☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ ☞ጳጉሜ2-13-2014 በቅንነት ቴሌግራም ይቀላቀሉ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

✝️ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! እንኳን ለርኅወተ ሰማይ: ለቅዱስ ሩፋኤል: መልከ ጼዴቅ: ዘርዓ ያዕቆብና ሰራጵዮን ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። ††† ርኅወተ ሰማይ ይህች ዕለት የሰዎች ሁሉ ጸሎት የሚያርግባት: አራተኛው መጋቢ ኮከብ የሚያልፍባት: ለሰው ልጆች ከፈጣሪያቸው ጸጋ በረከት የሚሰጥባት ዕለት ስለሆነች "ርኅወተ ሰማይ-ሰማይ የሚከፈትባት ቀን::" ትባላለች:: አሁን በሰማይ መዘጋት መከፈት ኑሮበት አይደለም:: የሰው ልጆችን ልመና ቅዱሳን መላእክት ያለ ከልካይ የሚያሳርጉበት: አንድም ቅዱስ ሩፋኤል የዓመቱን የጸሎት መዝገብ የሚከፍትበት ቀን ስለሆነ እንዲህ ተባለ እንጂ:: እመቤታችን ድንግል ማርያም ለአጼ ናዖድ እንደ ነገረቻቸው በዚህች ዕለት ሁሉም ቅዱሳን ስለሚታሰቡ: የእግዚአብሔር የምሕረት መዝገቡ ስለሚከፈት: ዕለቷን ክብርት ያሰኛታል:: በቅዱስ ሩፋኤል አበጋዝነት (መሪነት) በዚህች ዕለት ለዓመት የሚበቃ ምሕረት ይገኛል:: ስለዚህም አባቶቻችን በዚህች ሌሊት ሦስት መቶ ስልሳ አምስት አቡነ ዘበሰማያትን ሲጸልዩ ያድራሉ:: በሌላ ወገን ደግሞ የጌታ ዳግም ምጽዓቱ መታሰቢያ እንደ መሆኗ ትልቅ ትኩረትም ይሰጣታል:: ቸሩ ጌታችን ከተከፈተች ገነት ከተነጠፈች ዕረፍት ሁላችንንም ያድርሰን:: ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት ቅዱስ ሩፋኤል በቤተ ክርስቲያን አስተምሕሮ ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት በደረጃው ሦስተኛ ነው:: በመጀመሪያዋ ዕለተ ፍጥረት እግዚአብሔር መቶ ነገደ መላእክትን ፈጥሮ በአሥር ከተማ ሲያኖራቸው የቅዱስ ሩፋኤል ዕድል ፈንታው ራማ ሆነች:: በዚያም "መናብርት" ተብለው ለሚጠሩ አሥሩ ነገድ አለቃ (መሪ) ሆኖ በፈጣሪው ተሹሟል:: በኋላም "መጋብያን" በሚባሉ በሃያ ሦስቱ ነገድ ላይ ሹሞታል:: ይህች ዕለትም በዓለ ሲመቱ ናት:: አንድ ቀን ጌታችን ክርስቶስ በደብረ ዘይት ተቀምጦ ሳለ ሐዋርያቱ ቅዱስ ሩፋኤልን እንዲያስተዋውቃቸው ለመኑት:: ጌታም ሦስቱን ሊቃናት (ሚካኤል: ገብርኤል እና ሩፋኤል) ይመጡ ዘንድ አዘዛቸው:: ቀጥሎም ቅዱስ ሩፋኤልን "ክብርህን ንገራቸው::" አለው:: እርሱም ለጌታ ሰግዶ ለሐዋርያት ብዙ ምሥጢር ነገራቸው:: በተለይ ስሙን ለሚጠሩ: መታሰቢያውን ለሚያከብሩ የሚደረገውን ጸጋ አብራርቶላቸው ዐረገ:: በመጽሐፈ ጦቢት ላይ ተጽፎ እንደምናገኘው ቅዱሱ መልአክ ሰው (አዛርያን) መስሎ: ጦብያን ለትዳር አብቅቶ: ሣራን አስማንድዮስ ከሚባል ሰይጣን አድኖ: የጦቢትን ዓይን አብርቷል:: በገድላተ ቅዱሳን እንደምናየውም ለብዙ ቅዱሳን ረዳታቸው ሆኖ ገድላቸውን አስፈጽሟል:: ታሪክ እንደሚለው ይህች ቀን ለቅዱስ ሩፋኤል ቅዳሴ ቤቱም ናት:: በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በቅዱስ ቴዎፍሎስ ዘእስክንድርያ አማካኝነት ቤቱ ታንጿል:: የሚገርመው ደግሞ የታነጸው በዓሣ አንበሪ ጀርባ: ደሴት ላይ ነው:: በመልአኩ አጋዥነትም ለሦስት መቶ ዓመታት አገልግሏል:: † ቅዱስ ሩፋኤል ¤መስተፍስሒ (ልቡናን ደስ የሚያሰኝ) ¤አቃቤ ሥራይ (ባለ መድኃኒት ፈዋሽ) ¤መዝገበ ጸሎት (የጸሎት መዝገብ መክፈቻ የተሰጠው) ¤ሊቀ መናብርት (በዙፋን ላይ በክብር የሚቀመጡ መላእክት መሪ) ¤ፈታሔ ማኅጸን (የሰውንም ሆነ የእንስሳትን ማኅጸን የሚፈታ) ¤መወልድ (አዋላጅ: ምጥን የሚያቀል) ይባላል:: "ለሰብእ ወለእንስሳ ፈታሔ ማኅጸኖሙ አንተ" እንዲል:: ቅዱስ መልከ ጼዴቅ ካህኑ መልከ ጼዴቅን ቅዱስ ጳውሎስ "የትውልድ ቁጥር የለውም: ለዘመኑም ጥንትና ፍጻሜ የለውም::" ይለዋል:: (ዕብ.7:3) ሐዋርያው ይህንን ያለው ለወልደ እግዚአብሔር ምሳሌ ሲያደርገው እንጂ ትውልዱ ከነገደ ካም ነው:: ወላጆቹም "ሚልኪ እና ሰሊማ" ይባላሉ:: ገና ከእናቱ ማኅጸን የተመረጠው ቅዱሱ "ካህነ ዓለም: ንጉሠ ሳሌም" ይባላል:: የዛሬ አምስት ሺ አምስት መቶ ዓመት አካባቢ ሴም ባኖረበት ቦታ (በደብረ ቀራንዮ) ለዘላለም ይኖራል:: ካህኑ መልከ ጼዴቅ ከሰው ወገን እጅግ ክቡርም ነው:: † አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ሃይማኖቱ የቀና ኢትዮጵያዊው ንጉሥ አፄ ዘርዓ ያዕቆብ በኢትዮጵያ በነገሠባቸው ሠላሳ አራት ዓመታት (ከ1426 እስከ 1460 ዓ/ም) ብዙ በጐ ነገሮችን ሠርቷል:: ላለፉት ሰባ ዓመታት ግን አንዳንድ ጥቃቅን ሰብአዊ ስህተቶችን እየነቀሱ ተሐድሶዎቹ ስሙን ሲያጠፉት ኑረዋል:: ዛሬ ዛሬ ደግሞ የእኛ ቤት ሰዎችም ተቀላቅለዋቸዋል:: እነርሱ ያሉትን ይበሉ እንጂ ለእኛ ግን ዘርዓ ያዕቆብ ማለት:- 1.ጣዖት አምልኮን ከሃገራችን ለማጥፋት ብዙ ሺህ ካህናትን አሰልጥኖ አሰማርቷል:: 2.የኑፋቄ ችግሮችን ለመቅረፍ ጉባኤያትን አዘጋጅቷል:: 3.ከአሥራ አንድ ያላነሱ መጻሕፍትን በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ደርሶ ለአገልግሎት አብቅቷል:: 4.ብዙ መጻሕፍትን ከውጪ አስመጥቶ አስተርጉሟል (በተለይ ተአምረ ማርያምን) 5.ሰው ሁሉ ለእመ ብርሃንና ለመስቀሉ ፍቅር እንዲገዛ ጥረት አድርጓል 6.እመቤታችንን በፍጹም ልቡ ከመውደዱ የተነሳ ዛሬ ድረስ በሃገራችን ድንግል ማርያም "የዘርዓ ያዕቆብ እመቤት" እየተባለች ትጠራለች:: 7.ብዙ አብያተ ክርስቲያናትን አንጾ: ብዙ ሥርዓቶችም በሊቃውንት እንዲሠሩ አድርጐ: ሌሎች ብዙ በጐ ተግባራትንም ፈጽሞ በዚህች ቀን ዐርፏል:: ቤተ ክርስቲያን ስለውለታቸው ዘርዓ ያዕቆብን: እናታቸው ጽዮን ሞገሳን እና አባታቸው ዳዊትን በክብር ታስባለች:: † ቅዱስ ሰራጵዮን ዘሰንዱን ይህ ቅዱስ እጅግ የበዛ ሃብቱን ለነዳያን አካፍሎ: ወደ ሌላ ሃገር ሔዶ ለባርነት ተሽጧል:: በተሸጠበት ሃገርም በጸሎት ተግቶ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሷቸዋል:: ክብሩን ሲያውቁበትም በተመሳሳይ ወደ ሌላ ሃገር ሒዶ አሕዛብን አድኗል:: በፍጻሜው ወደ በርሃ ገብቶ በተጋድሎ ኑሮ በዚህች ቀን ዐርፏል:: ††† አምላከ ቅዱሳን የወዳጆቹን ሁሉ በረከትና ጸጋ ያብዛልን:: ለዓለምም ሰላሙን ይዘዝልን:: ጳጉሜን 3 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ርኅወተ ሰማይ (የሰማይ መከፈት) 2.ቅዱስ ሩፋኤል ሊቀ መላእክት 3.ቅዱስ መልከ ጼዴቅ ካህን 4.አፄ ዘርዓ ያዕቆብ ንጉሥ (የእመቤታችን ወዳጅ) 5.ቅዱስ ሰራጵዮን ዘሰንዱን 6.ቅዱስ አኖሬዎስ 7.ቅዱስ ቴዎፍሎስ 8.አባ ዮሐንስ 9.ቅዱስ ጦቢት 10.ቅዱሳን ጦብያና ሣራ         ወርኀዊ በዓላት (የለም) ††† "እውነት እውነት እላችኋለሁ:: ሰማይ ሲከፈት: የእግዚአብሔርም መላእክት በሰው ልጅ ላይ ሲወጡና ሲወርዱ ታያላችሁ::" (ዮሐ. ፩፥፶፪)          ወስብሐት ለእግዚአብሔር

"" ብመክርህም አትሰማኝም ! "" (ኤር. ፴፰፥፲፬) (ነሐሴ 29 - 2018)

ከሽንፈቶች ትልቁ ሽንፈት በሆድ መሸነፍ ነው ። በሆዱ የተሸነፈ ሰው እንኳን ማንነቱን ሀገሩን ለመሸጥ ወደኋላ አይልም ። በሆዱ የተሸነፈ ዜጋ ነፃ ምርኮኛ ነው ። ከነፃነት ሁሉ ትልቁ ነፃነት የሆድ ነ
ከሽንፈቶች ትልቁ ሽንፈት በሆድ መሸነፍ ነው ። በሆዱ የተሸነፈ ሰው እንኳን ማንነቱን ሀገሩን ለመሸጥ ወደኋላ አይልም ። በሆዱ የተሸነፈ ዜጋ ነፃ ምርኮኛ ነው ። ከነፃነት ሁሉ ትልቁ ነፃነት የሆድ ነፃነት ነው ። ባዶ ሆድ አዋራጅ ነው ።

#ጷጒሜን ፪ "የካህናት ቀን!#አባቶቻችንን እኛ ካላከበርን ማን ያከብርልናል ኑሩልን አባቶቻችን🌹 📌ምሥጢረ ክህነት ካህን ማለት ፦ ተክህነ አገለገለ ። ካለው የግዕዝ ቃል የተገኘ ሲሆን ፤ ካህን ማለት የእግዚአብሔር አገልጋይ ፤ የምዕመናን አባት ፤  ጠባቂ ፤ መጋቢ ማለት ነው ።ምሥጢረ ክህነት በብሉይ ኪዳንየክህነት አንዱ መገለጫው መስዋዕት ማቅረብ ሲሆን ፤ ለመጀመሪያ ጊዜ ለዚህ አገልግሎት የተመረጠውና ካህን ተብሎ የተጠራው መልከ ጼዴቅ ነው ። ዘፍ ፥ 14 ፥ 18 ። በኋላም እግዚአብሔር በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት በቤተ መቅደስ እግዚአብሔርን የሚያገለግል ፣ የሕዝቡን ኃጢአት እየተቀበለ ከእግዚአብሔር የሚያስታርቅ ካህን እንዲመርጥ ሙሴን ስላዘዘው ከመልከ ጼዴቅ በኋላ አሮን ተሾመ ። ዘፀ  ፥  ። ዕብ 7 ፥ 1 ። ከአሮን እስከ ዮሐንስ መጥምቅ ደረስ ረጅሙን የብሉይ ኪዳን ዘመን ከአሮን ዘር ብቻ የሚወለዱት ቅብዓ ክህነት እየተቀቡ በካህንነት እያገለገሉ አልፈዋል ። ነገር ግን በዘር ሐረግ ላይ የተመሠረተው ክህነት ለሐዲስ ኪዳኑ ክህነት ምሳሌ ስለነበረ ፍፁምና ዘላቂ አልነበረምና መስዋዕቱም ሆነ የአመራረጡ ሂደት በሌላ ተተካ ።ዘላቂ ያልሆነበትና በሌላ  የተተካበት ምክንያት– ህነቱ በዘር ብቻ የተገደበ ስለነበረ ፤ በሐዲስ ኪዳን ህጉንና ሥርዓቱን አሟልቶ ለተገኘ ለማንኛውም ሕዝብ የተፈቀደ ሆነ ። ክርስቶስ የመጣው ለዓለም ሁሉ ነውና ። – መስዋዕታቸው ፍጹም ድኅነት የማያሰጥ በመሆኑ ፤ በሐዲስ ኪዳን በክርስቶስ ሥጋና ደም ተተካ ። ዮሐ 6 – አገልግሎቱ ለጊዜው ከሥጋ መቅሰፍት ከማዳን ያላለፈ ነበረ ፤ በሐዲስ ኪዳን ግን በምድርም በሰማይም ማሰር በሚችሉ ፣ በነፍስም በስጋም ላይ ሥልጣን ባላቸው ካህናት ተተካ ። ማቴ 18 ፥ 18 ።ምሥጢረ ክህነት በሐዲስ ኪዳንበብሉይ ኪዳን የመጨረሻው ካህን መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ሲሆን ፤ ከእሱ በኋላ የብሉይ ኪዳን ክህነት አልፏል ። ጌታ ችን ወደ ዮርዳኖስ ሄዶ በዮሐንስ እጅ በመጠመቅ ፡ ካህኑ በሚገኝበት ቦታ ቤተ ክርስቲያን ድረስ ሄደን በካህኑ እጅ መጠመቅ እንዳለብን አስተምሮናል ። ማቴ 3 ፥ ጌታችን ሲያስተምር ስለ ካህናት በብዙ ቦታ ተናግሯል ። ሂድና ራስህን ለካህን አሳይ ። ማቴ 8 ፥ 4 ። አንተ ብፁዕ ነህ ፡ የመንግስተ ሰማያትንም መክፈቻ እሰጥሃለሁ…ማቴ 16 ፥ 17 ። እውነት እላችኋለሁ በምድር ያሰራችሁት በሰማይ የታሰረ ፣ በምድር የፈታችሁት በሰማይ የተፈታ ይሆናል ። ማቴ 18 ፥ 18 ። ይህን የተናገረው በመዋዕለ ስብከቱ ሲሆን  ከሙታን ከተነሳ በኋላም ለሐዋርያት አረጋግጦላቸዋል ። ሂዱና በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም አጥምቋቸው ። ማቴ 28 ፥19 ።..እፍ አለባቸውና መንፈስ ቅዱስን ተቀበሉ ። ዮሐ 20 ፥ 22 ። በመጨረሻም ቅዱስ ዼጥሮስን “….ስምዖን ሆይ በጎቼን ጠብቅ ፤ (ለጊዜው አስራ ሁለቱን ሐዋርያት ፡ ለፍጻሜው ወላጆችን) ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ ፤ (ለጊዜው ሰብዓ አርድዕትን ፡ ለፍጻሜው ወጣቶችን) ፣ ግልገሎቼን ጠብቅ (ለጊዜው ሰላሳ ስድስቱ ቅዱሳት አንስትን ፡ ለፍጻሜው ህጻናትን)” በማለት ሐዋርያትን ዸዸሳት ፣ ቅዱስ ዼጥሮስን የመጀመሪያ ሊቀ ዻዻሳት አድርጎ ሾመው ። ዮሐ 21 ፥ 15 ። ከዚህ ጊዜ ጀምሮ ቤተ ክርስቲያን በሊቀ ዸዸስና በዸዸሳት በሚመራ መንፈሳዊ ጉባኤ (ቅዱስ ሲኖዶስ) አማካኝነት እየተመራች አገልግሎቷን ታካሂዳለች ። ቤተ ክርስቲያን የክህነት ደረጃዎች ፤ የሚከተሉት ናቸው1 ሊቀ ዻሳሳት :- ሊቃነ ዸሳሳት “ፓትርያርክ” እየተባለም ይጠራል ። በአንዲት ቤተ ክርስቲያን (በአንድ ሲኖዶስ) ላይ የበላይ ሆኖ የሚሾም የሁሉም አባት ነው ። የሐ ሥ  20 ፥ 28 ። በሕዝብና በካህናት  ከተመረጠ በኋላ በዻሳሳት ይሾማል ። ፍት ነገ 5 ። ረስጣ 2 ። ፓትርያርክ ያወገዘውን ዻዻስ አይፈታውም ። መንፈሳዊ ሥልጣኑ ከሁሉም በላይ ነውና ። ሲኖ 51 ። ፓትርያርክ በመላዋ ቤተ ክርስቲያን በጸሎት ጊዜ ስሙ ይጠራል ።2 ኤዺስ ቆዾስ :- ዻዻስ በአንድ ሀገረ ስብከት አባት ሆኖ የሚሾም ነው ። ሲያገለግል በነበረበት አካባቢ ባሉ ምዕመናን ጥቆማና ድምጽ በርዕሰ ሊቃነ ዻሳሳቱና በሲኖዶስ ፈቃድ ይሾማል ። ፍት ነገ 5 ። አብጥ 2 ። በአንድ ዻዻስ ብቻ አይሾምም ። ፍት ነገ 5 ። ረስ 58 ።ዲድ 34 ። ዻዻስ በሀገረ ስብከቱ በጸሎት ጊዜ ስሙ ይጠራል ። ፍት 5 ። ክፍ 4 ። አዲስ ጽላት ፣ አዲስ ቤተ ክርስቲያን ፣ ይባርካል ። ለቄስ  ለዲያቆን ሥልጣነ ክህነት ይሰጣል ። 1 ጢሞ 5 ፥ 2 ። ፍት ነገ አን 5 ክፍ 4 ።3 ቀሳውስት :- ቅስና የሚቀበሉ ፤ በዲቁና ክህነት በማገልገል ላይ ያሉ ሲሆኑ ፤ በሁለት መንገድ ይሾማሉ ።3.1 በምንኩስና የተወሰነ ያላገባ ጌታን እንዴት እንደሚያገለግል የጌታን ነገር ያስባል ። 1 ቆሮ 7 ፥ 32 ። በማለት ቅዱስ ዻውሎስ እንደተናገረ ፤ በምንኩስና ለመኖር የፈለገ አስቀድሞ ወደ ገዳም ሄዶ የምንኩስናን ሕይወት መማርና አባቶችን እያገለገለ በተግባር ማየት አለበት ። በገዳም የሚሰጠውን አገልግሎት ከፈጸመ በኋላ አበምኔቱ ሲፈቅድለት ሥርዓተ ገዳሙ በሚያዝዘው መሠረት መዓርገ ምንኩስና ይቀበላል (ይመነኩሳል)ከምንከስና በኋላ ለክህነት የሚያበቃውን ትምህርት ተምሮ በየደረጃው ያሉትን የሥልጣነ መዓርጋት። በድንግልና ከመነኮሰና በትም ሕርቱም ሆነ በግብረ ገብነቱ በቂ ሆኖ ከተገኘ እስከ መጨረሻው የቤተ ክርስቲያን መዓርግ  “ጵጵስና” ሊደርስ ይችላል ።3.2 በህግ የተወሰኑ  ዲያቆናት በአንድ ህግ ከተወሰኑ ፤ በኋላ ለቅስና የሚያበቃ ትምህርትና ሥነ ምግባር ካላቸውና በሚያገለግ ሉበት አጥቢያ ሕዝብ ድምጽ ከተደገፉ ፤ ሊቀ ዻዻሱ ብቃታቸውን መዝኖ የቅስና መዓርግ ይሰጣቸዋል ። ፍ ገ 6 ።ሰላሳ ዓመት ያልሆነው ቅስና አይሾምም ። ፍት ነገ 6 ። የቀሳውስት የአገልግሎት ድርሻ አስተምሮ ማጥመቅ ፤ ንስሐ መቀበልና መናዘዝ ፣ (ማሰርና መፍታት) ፤ ቀድሶ ማቁረብ ፤ ማስተማር…. ናቸው ። ካህን የመጀመሪያ ሚስቱ ከሞተችበት ፤ መነኩሴም ምንኩስናውን ከተወው በኋላ የቅስና (የክህነት) ሥራ መሥራት አይፈ ቀድለትም ። ከማኅበረ ምዕመናን ግን አይለይም ።4 ዲያቆናት :- ዲያቆናት ካህናትን የሚራዱና የሚላላኩ ሲሆኑ ፤ በአገልግሎታቸው መሠረት የሚከተሉት ደረጃዎች አሏቸው –  ዲያቆን                          –  መዘምራን –  ንፍቀ ዲያቆን                    –  አጻዌ ኆኅት –  አናጉንስጢስ                    –  ሴቶች ዲያቆናውያት ናቸው ።ዲያቆን:- አስቀድሞ ሃይማኖቱን የተረዳ ፣ በምዕመናን ዘንድ በግብረ ገብነቱ የታወቀና የተመሰከረለት ፣ ለዲቁና አገልግሎት የሚያበቃውን ትምህርት ጠንቅቆ የተማረ ፤ ሆኖ ሲገኝ በአንብሮተ ዕድ (እጅ በመጫን) ይሾማል ። የተለየ ብቃትና ችሎታ ከሌለው በቀር ዕድሜው ከሃያ አምስት ዓመት በታች የሆነ ዲቁና አይሾምም ። ዲያቆን ከመጀመሪያ (ከህግ) ሚስቱ ከተፋታና ሌላ ካገባ ፣ ሃይማኖቱን ለውጦ በመናፍቃን ከተጠመቀ ፣ ከክህነቱ ይሻራል ። ፍት ነ 7 ክ ፍል 5 ።ዲያቆናት መቅደስ ይገባሉ ፤ ነገር ግን መንበር ፣ ታቦት ፣ (ከተለወጠ በኋላ) ሥጋውንና ደሙን በእጃቸው አይነኩም ። ዲያቆናት ለተልእኮ የሚፋጠኑ ፣ በትህትና የሚላላኩ ፣ በኑሯቸው ለሌላው አርአያ መሆን ይገባቸዋል ።ንፍቀ ዲያቆን :- የዲያቆን ረዳት ሲሆን ፤ መንፈሳዊ ሕይወቱ ፣ ግብረ ገብነቱና የሃይማኖቱ ጽናት በሚያገለግልበት አጥቢያ ካህናትና ምዕመናን የተመሠከረለት ። ፍት ነገ 8 ። ንፍቀ ዲያቆን በቃል ብቻ