ar
Feedback
"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

الذهاب إلى القناة على Telegram

🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ልጅ🤗

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

تُعد قناة "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 (@orthodoxtewahdoc) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 25 380 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 987 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 1 323 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 25 380 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 19 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار -75، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 3.71‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 2.62‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 943 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 665 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 14.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ...

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 20 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

25 380
المشتركون
+124 ساعات
+447 أيام
-7530 أيام
أرشيف المشاركات
✝የጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አዳኝነትእና የቅዱሳንመላእክት አዳኝነት 👉 2011 የተሰጠ ቢሆንም ከቅዱሳን መላእክት ጋር የተያያዘ ስለሆነ ይደመጥ ዲ/ዮርዳኖስ አበበ ""ከቅዱሳን ሕይወት ተማሩ ብለን እንለምናችኋለን!!"" " ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::        አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/ https://t.me/zikirekdusn

*_<<የትሩፋት ሥራ ጀምር>>_* ጨክነህ ቆርጠህ የትሩፋትን ሥራ ጀምር፡፡ በትሩፋት አጠገብ እየተጠራጠርህ አትኑር፡፡ ክብር ይግባውና እግዚአብሔር ከማመን ተስፋ ወጥተህ በልብህ እንኳ አትጠራጠር፡፡ ትሩፋትህ ረብህ ጥቅም የሌለው እንዳይሆን የትሩፋት ሥራ ክቡድ አይምሰልህ፡፡ መሐሪ እግዚአብሔር ለለመኑት ሰዎች ጸጋውን ፈጽሞ እንዲሰጣቸው እመን እንጂ ስጦታው እንደየሥራችን አይደለም፡፡ በትጋታችን፣ በማመናችንና በመሻታችን መጠን ነው እንጂ እንደ ሃይማኖትህ ይደረግልህ ብሏልና፡፡ የትሩፋት ሥራም ይህች ናት፣ አንዱ መተምተሚያ አዘጋጅቶ መሐል ራሱን ይተመትመዋል፡፡ በየጊዜው በሚጸልየው ጸሎት እንዳያፍር ትቀርበኛለች ብሎ ያዝናል፡፡ አንዱ አብዝቶ ይሰግዳል፣ ልጸልይ ያለውን ይጸልያል፣ ስለ ጸሎቱ ፈንታ ብዙ ያለቅሳል፣ በልቅሶው ረብህ ጥቅም ያገኝበታል፡፡ አንዱ የልቡና ሥራ የምትሆን ትሩፋትን በመዘከር ይጋደላል፣ ወደ ተወሰነለት ጸጋ ይደርሳል፣ አንዱ ምግብ ነስቶ ሰውነቱን በረኃብ ያስጨንቃታል ጸሎቱን መፈጸም የማይቻለው እስኪሆን ድረስ፣ አንዱ ተናዶ እየመላለሰ ዳዊት ይጸልያል። በመድገም ዘወትር ጸሎትን ገንዘብ ያደርጋታል፣ አንዱ መጽሐፍ ለመመልከት፣ ለመድገም ጽሙድ ሆኖ ይኖራል፣ አንዱ ከአምላክ በተገኙ መጻሕፍት ያለውን ትርጓሜ ምሥጢር ያስበዋል፣ ያስተውለዋል፣ ይመረምረዋል። ወደ ሥራው ይሳባል፤ አንዱ የዐቢይ ምዕራፉን መለያ አይቶ ምሥጢሩን ያደንቃል፣ ዝምታ ይሰለጥንበታል፡፡ በልማድ መጽሐፍ ከመመልከት በልማድ ከመድገም ይከለከላል፡፡ አንዱ ደግሞ ሁሉንም አንድ አድርጎ ይሠራቸዋል፡፡ በዚህም ይሰለቻል፡፡ ዓለማዊ ሥራ ይሠራል፣ ለሐኬት ጽሙድ ሆኖ ይኖራል። አንዱ መጽሐፍ ከመመልከት ጥቂት ምሥጢር ያገኛል፡፡ በዚህም ትዕቢት ያድርበታል፡፡ በሰው መዘበት ያድርበታል፤ ይበድላል፡፡ አንዱ የልማድ ምክንያት ይሰለጥንበታል፣ አንዱም ይህን ሁሉ ድል ይነሣል፤ ከዚህ ሁሉ ይጠበቃል፡፡ ዕንቁ ክርስቶስን ገንዘብ እስኪያደርገው ወደኋላ አይመለስም፡፡ ደስ ብሎህ እግዚአብሔር ያዘዘውን የትሩፋት ሥራ ጀምር፡፡ (ምክር ወተግሣጽ ዘማር ይስሐቅ💙🦋

አንድ ድሀ ሰው ነበረ.. ሶስት ብርቱካኖችን ይገዛል.. ሊበላ አንደኛውን ብርቱካን ሲቆርጠው የተበላሸ ነው.. ሁለተኛውንም ሲቆርጠው የተበላሸ ነው.. ሶስተኛውን ከመቁረጡ በፊት ግን መብራቱን አጠፋና
አንድ ድሀ ሰው ነበረ.. ሶስት ብርቱካኖችን ይገዛል.. ሊበላ አንደኛውን ብርቱካን ሲቆርጠው የተበላሸ ነው.. ሁለተኛውንም ሲቆርጠው የተበላሸ ነው.. ሶስተኛውን ከመቁረጡ በፊት ግን መብራቱን አጠፋና ቆርጦ በላው። 💠 አንዳዴ ለመኖር ሲባል አይተን እንዳላየን ሰምተን እንዳልሰማን መሆን አለብን። መልካም ቀን ይሁንልን🥰❤️

☦መልክዓ ቅዱስ ሩፋኤል📗 "ቅዱስ ሩፋኤል በእለተ ቀኑ ልጅ አተው በየፀበሉ የሚንከራተቱትን ልጅ ያስታቅፍልን በልጅ ይባርክልን አሜን።🙏 https://t.me/Orthodoxtewahdoc

✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥ ✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚          ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥ 📗ስንክሳር ዘወርኃ ሰኔ ፲፫።13/ https://t.me/Orthodoxtewahdoc 🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊

❝"የኔ ሴት ..ችግርን በፈገግታ መጋፈጥ ህመምን በውስጥ መደበቅ ያለ ማንም እርዳታ መበርታት ከቻልሽ እመንኝ ኣንች ማንም ልገምታት የማይችል ጠንካራዋ ሴት ነሽ።🤌🏿💦
❝"የኔ ሴት ..ችግርን በፈገግታ መጋፈጥ ህመምን በውስጥ መደበቅ ያለ ማንም እርዳታ መበርታት ከቻልሽ እመንኝ ኣንች ማንም ልገምታት የማይችል ጠንካራዋ ሴት ነሽ።🤌🏿💦

❝"የኔ ሴት ..ችግርን በፈገግታ መጋፈጥ ህመምን በውስጥ መደበቅ ያለ ማንም እርዳታ መበርታት ከቻልሽ እመንኝ ኣንች ማንም ልገምታት የማይችል ጠንካራዋ ሴት ነሽ።🤌🏿💦

ስለ መልአከ ምክሩ ቅዱስ ሚካኤል ፀበለ ፃድቅ ቅመሱ በቃልኪዳኑ የከርሞ ሰው ይበለን ከቁጥር አያጉድለን።🙏❤
ስለ መልአከ ምክሩ ቅዱስ ሚካኤል ፀበለ ፃድቅ ቅመሱ በቃልኪዳኑ የከርሞ ሰው ይበለን ከቁጥር አያጉድለን።🙏❤

ጊዜ ሊመለስ የማይችል ሀብት ነው። በህይወት ውስጥ እጅግ ውድ ሀብት ነው፣ ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ብዙ ጊዜ በቀላል ነገሮች እና በከንቱ ነገሮች እናባክነዋለን። አስታውሱ! የጠፋ ገንዘብ መልሶ ማግኘት
ጊዜ ሊመለስ የማይችል ሀብት ነው። በህይወት ውስጥ እጅግ ውድ ሀብት ነው፣ ግን በሚያሳዝን ሁኔታ ብዙ ጊዜ በቀላል ነገሮች እና በከንቱ ነገሮች እናባክነዋለን። አስታውሱ! የጠፋ ገንዘብ መልሶ ማግኘት ይቻላል፣ የጠፉ ነገሮች ሊመለሱ ይችላሉ፣ ነገር ግን ያለፈ ጊዜ ተመልሶ አይመጣም። ስለዚህ እያንዳንዱን ቀን በዓላማ አሳልፉት። በደምብ የታሰበበት ውሳኔዎችን ያድርጉ፣ ሕይወትህን የሚያሻሽሉ፣ ህልሞችህን ወደ እውነታ የሚያቀርቡ እና ለሌሎችም ጠቃሚ በሆኑ ነገሮች ላይ ጉልበትህን አፍስሰው። ጊዜን በመጠቀም ላይ ያለህ ሀሳብ፣ ፍላጎት እና ስትራቴጂ የስኬት ቁልፎች መንገድ ከፋች ናቸው። ጊዜን በዓላማ ይጠቀሙበት፣ ምክንያቱም ይህ የህይወትን እውነተኛ ዋጋ የሚያስተምር ስጦታ ነው። Amari La

ነገ ¹³ፈታሄ ማህጸን ቅዱስ ሩፋኤል ወቶ ከመቅረት ከድገተኛ አደጋ ከዲያብሎስ ፈተና ከመከራ ስጋ ወነፍስ ይጠብቀን አሜን!!!🙏♥

❤ቅዱስ ሩፋኤል🌹 ✳ትርጉሙ እንዲህ ነው ፣ በልሳነ ዕብራይስጥ ሩፋ ማለት ጤና ፣ ፈውስ ፣ መድሃኒት ሲሆን ኤል ማለት ደሞ አምላክ ፣ እግዚአብሔር ማለትነው። ♨አምጻኤ ዓለማት እግዚአ መላዕክት እግዚአብሔር በነገደ መላዕክት አለቆች ይኾኑ ሰብዓቱን ሹሟል ። ቅዱስ ሩፋኤልን ከሊቃነ ነገደ መላዕክት ቅዱስ ሚካኤልና ቅዱስ ገብርኤል በመቀጠል በማዕርግ ሶስተኛ ኾኖ የተሾመው ሊቀመላዕክት ነው ፣ ዮሃንስ ወንጌላዊ ቀደም ብሎ ተናግረዋል እንዲህ ይላል ርኢኩ ሰብዓተ መላዕክተ እለ ይቀውሙ ቅድመ እግዚአብሔር ራእ 8:21 ቅዱስ ሩፋኤል የሴቶችን ማህጸን ይፈታ ዘንድ ሥልጣን ተሰጥቶታል ። መላኩ ሩፋኤል በ 23 ነገደ መላዕክት መናብርት ተብለው የሚጠሩት የተሾመው ብርሃናዊ መላክ ነው ። የነገድ ስማቸውን እንዲህ ነው ፣ አጋእዝት ፣ ሓይላት ፣ ሥልጣናት ፣ ሊቃናትና መናብርት ፣ መኳንንትና አርባብና ፣ ኪሩቤልና ሱራፌል አዕላፍም ፣ ድርገታትም ተብለው ይታወቃሉ ። አለቆቻቸውም ዓስር ናቸው ። እሊኽም ፣ ቅዱስ ሚካኤል ፣ ቅዱስ ገብርኤል ፣ ቅዱስ ሩፋኤል ፣ ቅዱስ ፋኑኤል ፣ ቅዱስ ራጉኤል ፣ ቅዱስ ኡራኤል ፣ ቅዱስ ሱርያል ፣ ቅዱስ ሰዳክያል ፣ ቅዱስ ሰላትያል ፣ ቅዱስ አናንኤል ናቸው ። እሊኽ ነገደ መላዕክትም ለዘለዓለም በሰማያት ሕያዋን ኹነው ይኖሩ ዘንድ እግዚአብሔር ወሰናቸው ። ነገር ግን እግዚአብሔር ግን በጠራቸው ግዜ ፈቃዱን ለመፈጸም እሊኽ መላዕክት እስከ ጽርሃ አርያም ይወጣሉ ። በላካችውም ግዜ የፍጥረተ ሁሉ ወሰን እስከኾነችው ጨላማይቱ የባርባሮስ ሥፍራ ድረስ ይወርዳሉ ። ተመልሰውም ብቻውን የነበረው ያለና የሚኖር በአገዛዝ ላይም ሁሉ ሥልጣን ያለው እርሱን ከማመስገን በቀር በሽታም ሞትም ቢሆን ሓዘንም ቢሆን ወደሌለባቸው ቦታቸው ይገባሉ ። እግዚአብሔር ከሊቃነ መላዕክት ሩፋኤል ሠራዊት መርጦ በመንበሩ ዙርያ አቆማቸው ፣ ከእሳት ወርቅ የተሰራ ጽናዎችምና የሚያንጸባርቅ የብርሃን አክሊል አንጓቸው ብርሃን የሆነ ዘንግንም ሰጣቸው ። መልኩ መብረቅ የሆነ የክህነት ልብስን አለበሳቸው ። ከማዕጠንታቸውም ምስጋና የተሞላ መዓዛውም ደስ የሚያሰኝ ዕጣን ይወጣል ፣ እግዚአብሔርም በማዕጠንታችሁ የቅዱሳን ሁሉ ጸሎት ወደኔ ይቀርብ ዘንድ ይደረግላችሁ አላቸው ። አዎ ወደ ፈጣሪያቸውን እግዚአብሔርም ሳያቋርጡ ዘወትር ስለሰው ልጆች ይለምናሉ ፣ በሰማያት የሚኖር የአብም ገጽ ዘወትር ያያሉ ፣ ንስሐ ስለሚገባው አንድ ሓጥእም በእግዚአብሔር መላዕክት ታላቅ ደስታ ይደረጋል ፣ እግዚአብሔር ቅዱሳን መላዕክት ሁሉ ስለዚህ ነገር ፈጥራችኋል ። አዎ ከእግዚአብሔር በስተቀር የመላዕክትን ተፈጥሮ የሚያውቅ ማንም ማንም የለም ። ኩፋሌ 2:7 ቅዱስ ሩፋኤል ቅዱሳን ጻድቃን በገድላቸውም የሚረዳቸው ፣ የምያጽናናቸው ፣ የሚደግፋቸው እርሱ ነው ፣ ፈታሄ ማህጸን ፣ ዐቃቤ ሆህት ፣ ሰዳዴ አጋንንት ፣ ከሣቴ ዕውራን ፣ ፈዋሴ ዱያን ተብሎ በመሆኑ ይታወቃል ። ሄኖክ 6:3 ዘፍ 3:24 🌹❤️የቅዱስ ሩፋኤል በረከት ፣ የዕልፊ አዕላፍ ነገደ መላዕክት ረድኤት ፣ አማላጅነት ፣ የእግዚአብሄር በጎ ቸርነትና ምህረት ዛሬም ዘወትርም ከኛ ጋር ይሁን 🙏አሜን አሜን አሜን🙏🙏🙏 ወስብሃት ለእግዚአብሄር ። ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር አሜን 💓💖❤️💙💜💚💖❤️💙 https://t.me/Orthodoxtewahdoc

📕#ተአምር_ዘአቡነ_ዘርዓ_ብሩክ🌹 📘☞•••ወር በገባ በ13 ታስበው የሚውሉ አባታችን ዘርዐ ቡሩክ ያደረገው ታአምር ይህ ነው ስሟ ፋሲካዊት በምትባል ሴትዮ ቤት እግዚአብሔር ዳግመኛ ታላላቅ ተአምራት አደረገ፡፡ ያቺም መልካም ሴት ሁል ጊዜ የዘርዐ ብሩክ መታሰቢያውን ታደረግ ነበር አሱንም ከመውደዷ የተነሳ ተገዛችለት ለቃሉም ታዙችለት፡፡ ☞በአንድ ወር ለመታሰቢያው የሚሆን የማኀበሯ ተራ በደረሰ ጊዜ ትደክም ጀመር ብዙ ቀን ሰትጥር ስትግር ሰይጣን ቀንቶባት የመታሰቢያውን የወይን ጠጅ አጠፋባት፡፡ ☞ይህ ሁሉ የደረሰብኝ ሰለ ኃጢአቴና ሰለ በደሌ ነው ብላ ብዙ ምሾ እያወጣቸ ፈጽማ አለቀሰች፡፡ ☞እግዚአብሔርም የለቅሶዋን ጽናትና ኅዘኗን አይቶ በሰይጣን ቅናት የጠፋባትን ያን ወይን ጠጅ የቃናን ውሃ ለውጦ የጣመ እንዳደረገው ያን ቦዶ እንስራ ወደ ወይን ለወጠው ፈጽሞም ጣፈጠ፡፡ ☞በዚያ በጻድቁ አባቷ ዘርዐ ብሩክ ጸሎት ያ የወይን ጠጅ ተለውጦ እንዳ ጣፈጠ ያቺ ሴት አይታ እግዚአብሔርን አመሰገነች፡፡ እናቱ ድንግል ማርያምንም አመሰገነች በጸሎቱና በአማላጅነቱ ተአምራትን መንክራትን ያየረገላት ቅዱስና ብፁዕ የሚሆን አባታችን ዘርዐ ቡሩክ እጅግ ወደደችው፡፡ ☞የጣፈጠው ያ የወይን ጠጅም በክቡር የሚካኤል በዓል ቀን ዳግመኛ አለቀባት የነበሩ ብዙ ማኀበርተኞችም እጅግ አዘኑ የወይን ጠጅ ትበደራቸው ዘንድ በየሀገሩ ዞረች የምትሰጣቸው የወይን ጠጅ ባጣች ጊዜ ከዚያ ከሚጣፍጠው የወይን ጠጅ የቀረ(የተረፈ)አንድ ማድጋ ቅራሪ አመጣችላቸው በቀዱት ጊዜ አተላ ሆነ፡፡ ☞ያዚ ሴትም እጅግ አዘነች ማኀበርተኞችም ሁሉ እንደ አርሷ አዘኑ ዳግመኛ ቀዱት ንጹህና ጣፈጭ ሆነው አገኙት እጅግ ተደነቀች ማኀበርተኞችም እንደ እርሷ አደነቁ፡፡ ☞ይህ ሁሉ ተአምር የተደረገ በጻዱቁ አባታችን ዘርዐ ብሩክ ጸሎትና ልመና ነው፡፡ ☞መታሰቢያውን ለምናደርግ ስሙን ለምንጠራ እንደ እርሷ ተአምራትን ያድርግልን ለዘለአለሙ አሜን፡፡ ☞(ገድለ ዘርዐ ቡሩክ) ☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ ☞https://t.me/Orthodoxtewahdoc

#አቡነ ዮሐንስ ዘደብረ ቢዘን ማለት⁉ ♨☞ወር በገባ በ13 የአቡነ ዮሐንስ (ዘደብረ ቢዘን)ወርሐዊ መታሰቢያ በዓል ነው እኚህ ጻድቅ ኢትዮጵያዊ ሲሆኑ በጥቅምት 14 ቀን ተወለዱ ሀገራቸው ትግራይ አድዋ አውራጃ አህሳአ ልዩ ቀበሌ እንዳ መንደር ይባላል። ☞አቡነ ዮሐንስ የአቡነ ፊልጶስ ዘደብረ ቢዘን ደቀመዝሙር ሲሆኑ፣አቡነ ፊልጶስ ሲያርፉ በሳቸው ተተክው ደብረ ቢዘን ገዳምን በአበምኔትነት አስተዳድረዋል። ☞እንደ ነቢየ እግዚአብሔር ደመናን ዝናም እንዳይሰጥ የለጎሙ የከለከሉ ስለሆኑ "ለጓሜ ደመና" በመባል ይታወቃሉ። ነቢዩ ኤልሳዕ በመንፈስ ቅዱስ ሁሉን እንደሚያውቅ ሁሉ አቡነ ዮሐንስም ሰው በልቡ የሚያስበውን ያውቁ ነበር። ☞አቡነ ዮሐንስ በተወለዱበት ሀገር ትግራይ በአህሳአ በስማቸው የተገደመ ''እንዳ አቡነ ዮሐንስ ገዳም" ፣ዛሬ ደብር ነው። አቡነ ዮሐንስ በመነኮሱበትና ባገለገሉበት በደብረ ቢዘን ገዳም በኅዳር 13 ቀን አርፈው ተቀብረዋል። ☞""አቡነ ዮሐንስ ዘአስገዶም"" በመባልም ይጠራሉ። ☞በስማቸው የተሰሩ 5 አብያ ተክርስቲያናት አሉ አምላካችን እግዚአብሔር ስለ ጻድቁ ስለ አቡነ ዮሐንስ ዘደብረ ቢዘን ብሎ ከዘመኑ መቅሰፍትና ጥፋት ይሠውረን፡፡ ☞(ገድለ አበው ቅዱሳን ዘደብረ ቢዘን) https://t.me/Orthodoxtewahdoc

ልቤ ለመዳን ይሻልና ለዘለአለሚዊነትህ ከከንቱ ሞት ኀጢአት ያድነኝ ዘንድ እማፀንህ አለውለመንግሥትህ ፍፃሜ የሌለው ቃልህና አካልህ በመልክዕና በቁመት እጅግ የከበረ የምትደነቅ የብርሃናት መገኛ እግዚአብሔር አብ ሆይ ከአቅም በላይ በኾነና ለመይወሰን አካለ አቅም ህና ዳግመኛም ግርማ *ራእዩ ለሚያስደንቅ መልክዕህ ሰላምታ ይገባል* አንተ እውነተኛ አምላክ ሥትሆን ኹሉን በፈቃድህ የፈፀምህ የኹሉ ፈጣሪ እግዚአብሔር አብ ሆይ ኹሉን ማድረግ የሚቻልህ ሁሉን ለአንተ የቀረበ በአንተም ዘንድ አለና በእውነተኛይቱ መንገድ መርተህ ህግን *አስተምረኝ። እግዚአብሔር አብ ሆይ በለሊትና ቀኑን ሙሉ* *ምስጋና ይገባሀል።* እግዚአብሔር ዓብ ሆይ በክረምት እና በበጋ አውራኀ ልክ ምስጋና ይገባል ። እግዚአብሔር አብ ሆይ በማይታየውም ኹሉ ዘንድ ምስጋና ይገባል አለም ሳይፈጠር አስቀድሞ የነበረና የአለ የሚኖርም ምስጋናህን እነሆ ሰማይ ይናገራል አቤቱ እግዚአብሔር አብ ሆይ ከሥጋና ነፍስ መከራ እኔ _ን ጠብቀኝ ብርሀንህንም አብራልኝ ለዘላለሙ አሜን ። *አባታችን ሆይ* https://t.me/Orthodoxtewahdoc

🌹ወር በገባ በ13 እግዚአብሔር አብ ነው እንኳን አደረሰን🎋 ♨#መልክዐ እግዚአብሔር አብ 🌹 📗•••ፀጋን የምታድል የመከራና የችግር ጊዜያትንም የምታሶግድ ፍፁም አለማዊ አምላክ እግዚአብሔር አብ ሆይ ልመናውን የማታቋርጥ ነፍሴ አስቀድሞ ነብያትህ ኄኖክንና ዕዝራን ማስተዋልን እንደመላኋቸው ንጉስን ከወታደሮች ጋራ የሚያጸና ይቅርታህ ይርዳኝ ትልሀለች ። ወዳጅህ እስራኤልን አፍህን ክፈት እኔም አመላዋለሁ ያልኽው እግዚአብሄር አብ ሆይ አንተ ርኽረኽ እና ፍፁም አምላክ ነህ ምስጋናህን አቀርብ ዘንድ አንደበቴን አዘጋጃለሁ። በደሴተ ፍጥሞለ ለነበረ ቅዱስ ዮሐንስ ራዕይን የገለፅህ እግዚአብሔር አብሆይ ጉድለት ችልታ በሌለበት አዲስ አንደበት የመፀሐፍት ሚሥጥራትን አንብቢና ተርጉሜ ህግህን ለማስተማር የጀመርሁትን አዲስ ግብር እፈፅም ዘንድ አቤቱ ፀጋህን አድለኝ ። ከዘመናት አስቀድሞ የነበርኽ የዘመናት ባለቤት ዘመናትንም አሳልፍኽ የምትኖር በባሕርይህ ጉድለት የሌለብህ በፈጡራን ሁሉ አንደበት የምትመሰገን እግዚአብሔር አብ ሆይ ዘመናትን በፀጥታ የምታፈራርቅ አንተ ነኽና ፈጽሞ *ለተመሰገነ ዝክረ ስምህ ሰላምታ ይገባል* ከእግዚአብሔር ወልድ እና ከእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስጋርራ ዕሩይ የሆንኽ የብርሃኑ ክበብ ለሚያስደንቅ የራስ ፀጉርህና ምሳሌ የሌለው ምስጋና የሚገባህ *እግዚአብሔር አብ* ሆይ የሦስትነት የአንድነተመቸሀለ ፀሐይ ለአለም ሁሉ ጌጥ ኾኖ ከምዕራብ። እስከ ምሥራቅ ከምድር እስከ ሰማይ ያበርራል የኹላችን መለያ ክብርህ ሰማያትን የመላ ጌትነትህም ፈጽሞ የተመሰገነ *እግዚአብሔር አብ ሆይ* ከኹለቱ እግዚአብሔር ወልድና እግዚአብሔር።መንፈስ ቅዱስ ጋራ ብርሀን በማስገኘቱ ፈፅሞ ለተመሰገነ ገፅህ ሰላምታ ይገባል ።የብርሀናት ፈጣሬ የሆነ ጨለማ ለማይስማማቸው ብሩሀት አይኖችህና ቅንድቦችህ ሰላምታ ይገባል።ኃይልና ምስጋናም ለአንተ ይገባልና አይኖቼ በምተ ኃጢት እንዳያንቀላፋ በብርሀን እረዴኤትህ ንቁሐን። አድርጋቸው የምስጋና ምስዋዕት የምትቀበል እግዚአብሔር አብ ሆይ ሁልጊዜ ፀሎትን ለሚያዳምጡና። የሚያንፀባርቅ እሳትን ለተጎናፀፉ ጉነጮችህ ሰላምታ ይገባል ። አቤቱ ዘወትር እንደ አሽኮኮ የምጨነቅየት የጭንቅ ጨኽቴን ታሰወግድልኝ ዘንድ ኤሎሔ ኤሎሔ እያልሁኝ የምለምንህ ፀሎቴን ተቀበልኝ። በኹሉም ሁሉ ሥፈራ የነበርህና ያለህ የምትኖር ሳን ታው በተባሉ የምትመሰገን በባሕርይኅ ኀል ፈት ሸረት የሌለበረህ እግዚአብሔር አብ ሆይ የሚያስደስት መአዛን። ለተመሉ አፈንጫህዎችና ዳግመኛም የተወለደደ ።. ቃል በሚስባቸው ከንፈሮችህ ሰላምታ ይገባል። አለም ሳይፈጠር አስቀድሞ የነበርህ አዲሱ አለም ከተገለጠ ቡኋላም ለዘላለም የምትኖር ጌታየ ነህ በፍፁም ምስጋና የተሞላህ የዘላለማዊ አምላክ እግዚአብሔር አብ ሆይ በተወደደ አንደበትህና መለኮታውያን ለኾኑ ጥርሶችህ ሰላምታ ይገባል ። በእጅ ምሀል አለምን የያዝህ እግዚአብሔር አብ ሆይ ወዶ ፈቅዶ ለሚናገር አንደበትህና እንደ ነጎድጓድ። ለሚያስተጋባ ድምፀ ቃናህ *ሰላምታ ይገባል ።*በአንተ ዘንድ ህልው የኾነ ኹሉን የማገልጥ መንፈስ ቅዱስ የእየነገዱን ቋንቋ ኹሉ ይግለጥልኝ። ፅድቅንና ይዎሄን.የትህትናም ግብር ሁሉ የምትወድ ጠላት ሳጥናኤልን የጣለውን ትዕቢትን የምትጠላ ገናንነትህን እጅግ የሚያስደንቅ እግዚአብሔር አብ ሆይ የህውሐት እና የጤና እስትንፋስ በኾነ እስትንፋስህ የፀጥታ ደጃፍ ፤ *የሀይልመግለጫ ለሆነ ጉሮሮህ ሰላምታ ይገባል*። እግዚአብሔር አብ ሆይ እርዝመቱ በሚያስደንቅ ዙሪያውም ክብ ለሆነ መጠኑ ለማይታወቅ *ጽህምህ ሰላምታ ይገባል*።በዝናበ እረዴኤትህ ጠልና ከፍታው እጅግ በበዛ የይቅርታህ ደመና የሕይወቴን ጽድቅ እንደ ካህኑ አሮን ፂም አርዝምልኝ። ከመገለጥ ይልቅ የተሰወረን የበልጥ የምትሠውረ እግዚአብሔር አብ ሆይ ዕበየ።ግርማህ ለከበበው አንገትህና ዳግመኛም በአንድነት ለጸኑ *ትከሻዎችህ ሰላምታ ይገባል*።የባህርየ ልጅህ ክርስቶስ እንክርዳዱን ከስንዴኤው ለይቶ በእሳት ሲያቃጥል ብጽላሎተ ረድኤቱ ይሠውረኝ። ጥልቅ ባህር ጥበባት እግዚአብሔር አብ ሆይ ኪሩብ ሊሸከመው ለማይችለው ጀርባህና ዳግመኛም አርባብ የተሰኙ የዋሃን ነገደ መላዕት ላይ *ከብሮ ገንኖ ለሚኖረ ቅዱስ ደረትህ ሰለምታ ይገባል* ።ኪነ ጥበቡ እጅግ የሚያስደንቅ ኃይልህ እኔ ጠቢብ ልጅህን ከስንፍና ይልቅ ጥበብን ያድለኝ። የክብርህን ነገር ለመናገር የሚያስደንቅ በማስተዋል ለመንግሥትም ፍፃሜ የሌለህ እግዚአብሔር አብ ሆይ የፀጋ ብርሀናትን ለሚያፈልቅ ሕፅንህና ዳግመኛም ለመመገብ *ለተዘረጉ የምህረት እጆችህ ሰላምታ ይገባል*። ድዊይ የምትፈውስ እግዚአብሔር አብ ሆይ ለአሸናፊ ድል ለሚያንጎናፅፍ ክንዶችህ እና ከአካልህ ጋር ለተስማሙ ክርኖችህ ሰላምታ ይገባል።የሀጥያቴን ደዌ አውሬ ዲያብለስን በወጋህበት በጦር ወግተህ በአዳኝ ሀይል አድነኝ .። ከእግዚአብሔር አብ ወልድና ከእግዚአብሔር መንፍ ቅዱስ ጋራ በእሳታዊጨ ዙፋንህ ከብረህ ገንነህ የምትኖ አለም ሳይፈጠ አስቀድም በሥልጣነ የባህሪህ የሆቸ እግዚአብሔር አብ ሆይ ለሚያስፈራ አምላካዊ ክንድህ ይህን ። ይህነ ስፊ አለም ለያዘ መሐል *ሰላምታ ይገባል* የፍቅርና የቸርነት መገኛ ሰማያት በምድር በየብስና በባህር ያሉትን ፍጥረታትን ኹሉ የምትመግብ። እግዚአብሔር አብ ሆይ ይህን አለም ለፈጠሩ ጣቶችህና ድንቅ ሥራዎችህን *ለሚያፈጥኑ ጠረፍሮችህ ሰላምታ ይገባል* ከንፎቻቸው ስድስት የኾኑ ኪሩቤልና ሱራፌል አንተን የዘወትር ከባህርይ። ልጅህ እግዚአብሔር ወልድና ከባህርይ ሕይወትህ ለእግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ጋራ የሚያመሰግኑህ እግዚአብሔር አብ ሆይ ልብሱ መብረቀ ስብሐት ለኾነ ጎንህና የመኖሪያ ሥፍራ *ለማይወስነው ሆድህ ሰላምታ ይገባል*። ይቅርታህን ርኀራኄህ ብዙ ነውና በፍጡራን አንደበት ኹሉ የምትመሰገን እግዚአብሔር አብ ሆይ ቅንና የዋህ ልብህና የዘመናትን ፍፃሜ አስቀድሞ ለሚያውቅ ሕሊናህ ሰላምታ ይገባል ክንድህም ለይቅርታ ዘወትር የተዘረጋ ነው ። ።በለይም በታችም ለዘመለአለም ነግሠህ የነበርህና ያለህ የምትኖር ንጉሥ ነገሥት እግዚአብሔር አብ ሀሰይ መልኩ ለሚያስደንቅ ኀንብርትህና ዳግመኛም *ለትጥቁ ደግ ለሚያምር ሀቊህ ሰላምታ ይገባል* አቤቱ ለይልህ አሸናፊ ነው እናአዐፄም አውሬ ዳቢሎስን አሸንፍ ዘንድ የትዕግስትን ትጠረቅ አልብሰኝ የእግዚአብሔር ወልድ የባህርየ አባት እግዚአብሔር አብ ሆይ ክቡድና መለኮታዊ ለኾኑ ጭኖችህ ዳግመኛም *ለጉልበቶችህ ሰላምታ ይገባል* ጠላት ዳቢሎስ ከሰጠህው ስልጣነ ከተባረረ ቡሀላ ትጉሀን ሰማይ ከሆነ ነገደ መላእክት በአንድነት አመሰገኑህ አለምሠ ሳይፈጠር አስቀድሞ የነበርህ ምድርንም የዘረጋህ ሥራህንም በድንቅ በማስተዋል ከመሥራትህ አሰቀድሞ የምትኖር እግዚአብሔር አብ ሆይ ምድር ለሚያንቀጠቅጡ እግሮችህና ከእግርህ *መረገጨም ጋራ ለተረከዝህ ሰላምት ይገባል*። የአባታችን አዳም የህይወቱ መሰረት እግዚአብሔር አብ ሆይ *ጋራ ባይለዩ ለሚኖር አስሩ ጥፍሮችህና ጣቶችህም ሰላምታ ይገባል*