ar
Feedback
"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

"ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

الذهاب إلى القناة على Telegram

🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ልጅ🤗

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒

تُعد قناة "ቤተ ማርያም መንፈሳዊ ሚዲያ💒 (@orthodoxtewahdoc) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 25 489 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 872 في فئة الدين والقيم الروحية والمرتبة 1 363 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 25 489 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 14 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 53، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 10، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 3.79‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 2.81‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 967 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 716 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 13.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
🌹«ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን /አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ።♥ https://t.me/Orthodoxtewahdoc ሐምሌ 3 በ2014 ዓ°ም ተከፈተ። 📌እግዚአብሔር ቢፈቅድ የቅዱሳኑን ታሪክ እንመማርበታለን ብለን ከፈትነው ቅዱስ እግዚአብሔር ይፍቀድልን አሜንለምት @fentanesh21_23 🗯ፈንታነሽ / የእመ ብርሃን ...

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 15 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة الدين والقيم الروحية.

25 489
المشتركون
+1024 ساعات
+157 أيام
+5330 أيام
أرشيف المشاركات
ነገ መስከረም 6 እናታችን የእምነት አርበኛ ቅድስት አርሴማ ናት። ጥበቃዋ አይለየን ከክፉ ነገር ሁሉ ትጠብቀን።🙏❤⛪
ነገ መስከረም 6 እናታችን የእምነት አርበኛ ቅድስት አርሴማ ናት። ጥበቃዋ አይለየን ከክፉ ነገር ሁሉ ትጠብቀን።🙏❤⛪

🌹#እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ወር በገባ በ6 እናታችን ቅድስት አርሴማ ናት🌹 👰"ውበት ሐሰት ነው፤ ደም ግባትም ከንቱ ነው እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርሷ ትመሰገናለች" ምሳሌ 30፥31
🌹#እንኳን አደረሰን አደረሳችሁ ወር በገባ በ6 እናታችን ቅድስት አርሴማ ናት🌹 👰"ውበት ሐሰት ነው፤ ደም ግባትም ከንቱ ነው እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርሷ ትመሰገናለች" ምሳሌ 30፥31። "ቅድስት አርሴማ"እግዚአብሔርን የምትፈራ በቅዱሳን ሰማዕታት ማህበርና በገነት በሮች የሕይወት ፍሬ ያፈራች ሰማዕት ናት። ⛪የምድር ሀብት ጌጥ ብሎም #የንጉሥ ሚስት #ንግሥት መባልን ሁሉ እንቢ ብላ ለምድርም ለሰማይም ንጉሡ ለሆነው ለ #ክርስቶስ የተሞሸረች ስለእርሱም #በነፍሷ መከራን የተቀበለች ብፅዕት ሰማዕት ናት "በብዙ መከራና ስቃይ የእግዚአብሔርን #መንግሥት ልንገባ ይገባናል" እንዳለ መጽሐፍ.ቅዱስ #የሐ.ሥራ. 14፥22) ቅድስት #አርሴማም የመከራውን ሸክም የእሳቱን ዋዕይ #ታገሠች። ስለዚህም መንግሥተ ሰማያትን #ወረሰች። እርሷ ከ #ድንግል ማርያም #በታች ከሴቶች ልጆች #ትበልጣለችና በዚህች ቅድስት ሰማዕት #አርሴማ ጸሎት የሚታመን ብፁዕ ነው። #መታሰቢያዋንም በዕጣንና በመሥዋዕት #የሚያደርግ ብፁዕ ነው። ስለ ቅድስት #አርሴማ እንጀራንና ጽዋ ውኅ #ለድሃ የሚሰጥ ብፁዕ ነው። በዚህ ዓለም በሥጋው መዳንን ዕጥፍ ድርብ ያገኛል። በሚመጣው ዓለም መልካም ዋጋንና #የማያልፍ ሕይወትን ፈጽሞ ያገኛል። #ጌታችን #ኢየሱስ #ክርስቶስ በወንጌል ቃል=> "በነቢይ ስም ነቢይን የሚቀበል የነቢይን #ዋጋ ያገኛል በጻድቅ ስም ጻድቅን የሚቀበል የጻዲቁን #ዋጋ ያገኛል፤ በስሜና በደቀመዝሙሬ ስም ከታናናሾች ለአንዱ ቀዝቃዛ ጽዋ ውኅ ያጠጣ እውነት እላችኃለሁ #በሰማያት ዋጋውን አያጣም" ብሏልና። (ማቴ 10፥40-42)። የእናታችን ቅድስት አርሴማ ባረከቷ ይዳርብን ። አሜን። #አርሴማ አርሴማ ቅድስት ሰማዕት ሞገስ አግኝተሻል #በክርስቶስ ፊትhttps://t.me/Orthodoxtewahdoc

🛐#ማርያም መግደላዊት 🌹 📍☞ወር በገባ በ6 ቀን የምትታሰው የመድኃኔዓለምን ትንሳኤ ቀድማ ያየች የተመረጠች የቅድስ ማርያም መግደላዊት ወርሐዊ መታሰቢያዋ ነው☞ማርያም መግደላዊት አስቀድሞ ጌታ 7 አጋንንትን ያወጣለት ደግ እናት ናት፡፡ ከዚያ ጀምራ ጌታን ተከተለች፡፡ ☞እነዚህም ክፍ አጋንንት መንፈሰ ትዕቢት፤ መንፈሰ ጽርፈት(ስድብ)፤መንፈሰ ቅንዓት፤ መንፈሰ ትውዝፍት(ምንዝር ጌጥ የማድረግ) መንፈሰ ዝሙት፤ መንፈሰ ሐሜትና መንፈሰ ሐሰት ነበሩባት፡፡ ☞ከሁሉ ሐዋርያቶችም እንኳን በፊት ለመጀመሪያ ጊዜ ትንሳኤውን የገለጠላት እጅግ ዕድለኛ ሴት ነች፡፡ ☞---ከሣምንቱ በፊተኛው ቀን መግደላዊት ማርያም ገና ጨለማ ሳለ ማልዳ ወደ መቃብሩ መጣች ድንጋዩም ከመቃብሩ ተፈንቅሎ አየች -- ማርያም ግን እያለቀሰች ከመቃብሩ በስተውጭ ቆማ ነበር ስታላቅስም ወደ መቃብሩ ዝቅ ብላ ተመለከተች ሁለት መላእክት ነጭ ልብስ ለብሰው የኢየሱስ ሥጋ ተኝቶበት በነበረው አንዱ በራስጌ ሌላው በግርጌ ተቀምጠው አየች -- ኢየሱስም ቆሞ አየች እነሱም አንቺ ሴት ስለምን ታለቅሻለሽ?አሉት፡፡ አርሷም ጌታዬን ወስደውታል ወዴት እንዳኖሩት አላውቅም አለቻቸው፡፡ ይህን ብላ ወደ ኃላ ዘወር ስትል ኢየሱስ ቆሞ አየችው ኢየሱስም እንደሆነ አላወቀችም አንቺ ሴት ሰለምን ታለቅሻለሽ ማንንስ ትፈልጊያለሽ አላት፡፡ ☞እርሷም የአትክልት ጠባቂ መስሎት ጌታ ሆይ አንተ ወስደኽው እንደ ሆነህ ወዴት እንዳኖርኸው ንገረኝ እኔም ወስጄ ሽቱ እቀባው ዘንድ አለቸው፡፡ ☞ኢየሱስም ማርያም አላት፡፡ እርሷም ዘወር ብላ በዕብራይስጥ ረቢኑ አለቸው ትርጓሜውም መምህር ሆይ ማለት ነው፡፡ ኢየሱስም ገና ወደ አባቴ አላረግሀምና አትንኪኝ ነገር ግን ወደ ወንድሞቼ ሄደሽ እኔ ወደ አባቴና ወደ አባታችሁ ወደ አምላኬ አምላካችሁ ዐርጋለሁ ብሏል ብለሽ ንገሪያቸው አላት፡፡ ☞መግደላዊት ማርያም መጥታ ጌታ እንዳየች ይህን እንዳላት ለደቀ መዛምርቱ ነገረቻቸው፡፡(ዮሐ 20 1-8) ☞ከጌታ ዕርገት በኃላ በጽርሐ ጽዮን መንፈስ ቅዱስን ከሐዋርያት ጋር ተቀብላ ወንጌልን ሰብካለች፡፡ ]ብዙ ሴቶችም ወደ ሃይማኖት መልሳለች፡፡ ☞ማርያም መግደላዊት ቁጥሯ ከ36 ቅዱሳን እንስት ወገን ነው፡፡ ☞ይቺ ሴት ስለ ክርስቶስ እየመሰከረች ስታስተምር ስድብና ግርፋት ደርሶባት ከዚያም ከብዙ ተጋድሎ በኃላ በዚህ በነሐሴ 6ቀን ተጋድሎዋን ፈጽማ በሰማዕትነት አርፋለች፡፡ ☞(መድብለ ታሪክ) ☞የቅድስት መግደላዊት ማርያም የጸሎቷ በረከቷ አይለየን፡፡ ☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ

26//ከእንጨት ለቃሚዋ ቤት የገባህ ኤልያስ ሆይ ለአንተ ጭኖች ሰላም እላለሁ።በሚሰማ የበረከት ቃል ገንዘቧን በባረክህ ግዜ ጎዶሎ የነበረው የማሰሮ ዘይት ሞላ ተጨመረም እፍኝ ሙሉው ዱቄትም እጥፍ ድርብ ሆነ ። *ሰላም ለአብራኪከ* 27፣ ዝናብን ለመስጠት ፀሎት በጀመርህ ጊዜ የራስህ መደገፊያ ለሆኑት ጉልበቶችህ ሰላምታ ይገባል ። የባረካ ልጅ የሄኖክ ጓደኛ የቀርሜሎስ ሰው ኤልያስ ሆይ ለነፍሴ ንስሓ ፋሲካን አድርግበት ዘንድ አባቴ የማማለድ አዳራሽህ ያለው የት ነው። *ሰላም ለአእጋሪከ* 28፣ በይሁዳ ምድር እስከ ምትገኝዋ እስከ ምድረ ኮሬብ ድረስ ለአርባ ቀን ያክል ያለማቋረጥ ለተጓዙ እግሮችህ ሰላምታ ይገባል ።ኤልያስ ሆይ የዘመኔን ጉድለት ንገረኝ። በፀሎትህም ነጭ የሆነ የበረዱን ዘመን ጠብቅ ለትውልድ ሁሉ ተስፋቸው የሀገሩ ፍሬ ነውና። *ሰላም ለሰኮናከ* 29 ፣ በሰረገላ ከተጫነው ከንጉሱ ከአካዓብ ይልቅ አሯሯጡ ፈጣን ለሆነ ለተረከዝህ ሰላምታ ይገባል። ኤልያስ ሆይ የሞት ሰረገላ ፈጥኖ በከበበኝ ግዜ እኔ ወደ ንስሀ ቤት በመግባት እቀድመው ዘንድ አዳኝ የሆነ የእውቀት ሀይልን አስታጥቀኝ። *ሰላም ለመከየድከ* 30 .ወዲያና ወዲህ ሆኖ በተከፈለ ጊዜ ዮርዳኖስን ለረገጠው ጫማህ ሰላምታ ይገባል። አዲስ የሆነ የወልድ ማረግ መንገድን የረገጥህ ኤልያስ ሆይ በሌለበት ቦታ የሚነድድ እሳት ፈረስን አገኘህ፣ለዕርገትህ ጊዜም ነፋስን ጠቀስኸው። *ሰላም ለአፃብኢከ* 31 ዐሥር ለሆኑ ደናግል ጣቶችህ ሰላምታ ይገባል፣ዳግመኛም ለመብራት ጥፍሮቻቸው ሰላምታ ይገባል ። የመርዓዊ የክርስቶስ ወዳጅ ኤልያስ ሆይ ዐሥሩን ቃላት መፈጸም የተሳነኝ እኔን እንደ ወዳጁ ዮሐንስ በፍቅርህ ግምጃ ካጌጡት ጋር ጨምረኝ *ሰላም ለቆምከ ወለመልክእከ* 32 ለቁመትህ፣የተሰወረውን ለሚመለከት ለድንግሉ ለእስክንድር ዓይን ግልጽ ለሆነው ለመልክህም ሰላምታ ይገባል። የሰማዕታት መጨረሻ ጴጥሮስ ኤልያስ ሆይ በእውነት ተቆጣኝ፣ከዳግመኛም ሞት ታድነኝ ዘንድም በይቅርታ ዝለፈኝ። *፫አመት ወ፮ አውራሃ* *ሰልስተ አመተ ወ ስድስቱ አውርሃ* 33 ሦስት አመት ከስድስት ወር ወደ በረሃ ሸሸህ በውስጧ ኖርህ።ኤልያስ ሆይ ለጌታህ መሸሽ መሪ የሆንኸውም አንተ ነህ ኢሳያስ በብሩህ ደመና ተጭኖ ወደ ምድረ ግብፅ ይወርዳል እያለ ተናግሯልና። ስልሳውን የሰበታት ሱባዔ መፈጸምን ከፈፀምህ ብኃላ የክርስቶስን መምጣት ለሚቀድመው አመጣጥህ ሰላምታ ይገባል። ኤልያስ ሆይ የበድንህ ማረፊያ እነሆ ጌታህ በተሰቀለበት ፣ደሙን፣ባፈሰሰበት፣ዮሴፍም በድኑን በሳማበት በፍጥሞ ነው። *ሰላም ለምፅአትከ* 35. ራሱን አዳኝ ክርስቶስ ነኝ ለሚለው አውሬ ሰውነትህን ለመስጠትህ ሰላምታ ይገባል።የበጎች መዳኛ ኤልያስ ሆይ የርሃብ ተኩላዎችና ጽኑዕ ደዌ በግህ እኔን ከጉልምስና መንጋዬ እንዳይነጥቁኝ ጠባቂ ሁነኝ። *ሰላም ለመጥዎትከ* 36. እንደ ደቀ መዝሙሩ እንደ ዮሀንስ ቃል በአራት ቀን እኩሌታ በሁለት ቀን ለሚሆን ትንሳዔህ ሰላምታ ይገባል። መጥምቁ ዮሐንስ ስለጌታችን ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ከእኔ. በፊት የነበረው ከእኔ ብኃላ ይመጣል ብሏልና።ቅን የሆንህ ኤልያስ ሆይ በእውነትም ይገባኃል። *ካህን ወነብይ ወሰማዕት* 37. ካሕንና፣ነብይ በሁለተኛው ጥሪት ሰማእት የምትሆን በታቦሩም ጉባኤም ከሐዋርያት ጋር ሐዋርያ የሆንህ፣የመነኮሳትንም ሕግ መስራች(ሠሪ)የሆንህ ኤልያስ ሆይ በአምስተኛው ሱባኤ በሰላም ምስጋናህን ፈጽሜያለሁና እንደ አስነሳህው እንደ ዮናስ ወዳጅ አድርገኝ *ስብሐት ለአብ* 38 ,ለሄኖክ ስራውን ገናናነቱን ሁሉ ላሳየው ለአብ ምስጋና ይገባል ከሀዋርያት ጋር በአንድነት ክብሩን ያይ ዘንድ ኤልያስን ለመረጠው ለወልድ ምስጋና ይገባል ለእዝራ የእሳት ጽዋን ላጠጣው ለመንፈስ ቅዱስ ምስጋና ይገባል የኤልያስ መልክአ በዚህ ተፈጸመ :: ዳግመኛም ለአገልጋይህ ለእኔ የንስሀ ዘመንን ትሰጠኝ ዘንድ በመልክህ ሰላምታ እማጸንሀለሁ አሜን :: *ኤልያስ እም ኤልሳዕ* 39, ከኤልሳዕ ይልቅ ሌላውን የማታስቀድም ኤልያስ ሆይ ካረግህ በኃላም ባህርን ስትከፍል ተመለከተህ እደዚሁም ሁሉ አንደበቴ ስምህን መጥራት እዳያቆርጥ ዳግመኛም ልቦናዬ አንተን ማስታወስን እዳይረሳ ዘወትር ከእኔ ጋር ሁን አሜን :: አቡነ ዘበሰማያት____ የተለያዮ ትምህርቶች በዝህ ያግኙ https://t.me/+hHIKQgF1DygyOThk

🌹ወር በገባ በ1እና በ6 ቅዱስ ኤልያስ ነው 💖🌹 🛐🌹መልከአ ቅዱስ ኤልያስ እነሆኝ🌹#ኦ ኤልያስ🛐 1.ተአምራትን ላደረገ ለደቀ መዝሙርህ ለኤልሳዕ ከመጠምጠሚያ ጋር መንፈስን በእጥፍ የሰጠኸው ኤልያስ ሆይ የመልክህን ሰላም እናገር ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እንደወለዳቸው በየሀገሩ ቋንቋም እንደተናገሩ እንደ ሀዋርያት በተቀደሰች ረድኤትህ ከጌታህ ጸጋን ስጠኝ። *ሰላም ለትርጓሜ ስምከ* 2. ዘይት ለተባለ ለስምህ ትርጓሜ ሰላምታ ይገባል።መቆረጥን ላልተቆረጠ ጸጉርህም ሰላምታ ይገባል ።ስምህን በመጥራት ኤልሳዕ የዮርዳኖስ ውሃ ከፈለ ፤ክፋትን ሳልሰራ ክፉ ስምን አትስጠኝ። *ሰላም ለርዕስከ ወለ ገጽከ* 3,ለራስህ መልኩ እንደ ጽጌረዳ ለሚያበራው ወደ ብሔረ ሕያዋን በገባ ጊዜ እስክንድር ለተመለከተው ፊትህም ሰላምታ ይገባል።ኤልያስ ሆይ የኩነኔ እና የጭቀትን ወንዝ እሻገርበትም ዘንድ የአንተን መጠምጠሚያህን ስጠኝ። *ሰላም ለቀራንብትከ ወለአይንትከ* 4 //ለቅንድቦችህ በታቦር ደም ግባቱ ያማረ የክርስቶስን ምስጋና ለተመለከቱ አይኖችህ ሰላምታ ይገባል። ከታላቅነቱ የተነሳ የሙሴ ጓደኛ የሐዋርያት አለቃቸው ኤልያስ ሆይ ይቅርታን እንዳደረገው እንደ አብድዪ ይቅርታህን አሳየኝ። እንደ ኢዩብም የኃይል መንፈስን አሳድርብኝ። *ሰላም ለአእዛኒከ* 5. መጀመሪያ በኮሬብ ብኃላም በታቦር ከእግዚአብሔር ዘንድ ነገርን ለሰሙ ጆሮችህ ሰላምታ ይገባል።ኤልያስ ሆይ ምቾትን ሁሉ ትፈጽምልኝ ዘንድ ከድንግል ማርያም ጋር በአንድነት ና። *ሰላም ለመላትሒከ* 6.ቀጭን እንደሆነ የፉጨት ድምፅ ያለ የአብን ቃል በሰማ ግዜ በመጠምጠሚያው ለተሸፈነው ፊትህ ሠላምታ ይገባል።ይዘኑትን ፊት ብሩህ የምታደርግ ኤልያስ ሆይ በጸሎትህ የመካኗ ደመና ማሕፀን በተፈታ ጊዜ በዚያን ወቅት ኀዘኑ ተረሳ። *ሰላም ለአዕናፍከ* 7.የጻድቃን ነፍሶች በየጊዜው የሚያሸቱት ሽታው የአሞራ አበባ ለሆነው ለአፍንጫህ ሰላምታ ይገባል። ከኄኖክና እርሱን ከመሰሉት ጋር በአንድነት የምትኖር ኤልያስ ሆይ ለተወደደው የይቅርታ ደመና አበባው እንዳያልፈኝ አባቴ ለአፍንጫዬ የመዓዛህን በር ክፈት። 8. *ሰላም ለልሳንከ ወለአፍከ* ለከንፈሮችህ በጽሕም ለተከበበ ከዕርሱም የእሳትና የፍም ነጸብራቅ ለሚወጣበት ለአፍህ ሰላምታ ይገባል።የሁዋላና የፊት ነብይ ኤልያስ ሆይ በሄድሁበት መንገድ ዝናም እንዳይመጣብኝ የቀደመው ተአምርህን ፅንዓት ዛሬ አሳየኝ። *ሰላም ለስህን ህብስተ* 9 .በመጀመሪያ በሁለተኛ ጊዜም በተቀደሰው መልአክ እጅ የህይወትን ሕብስት ላላመጠው ለጥርስህ ሰላምታ ይገባል። በየለቱ የማትለወጥ ጉዋደኛ ኤልያስ ሆይ በአንድነታቸው ክርክር እንዳይመጣ የዘወትር ፍቅርን ስጣቸው ። *ሰላም ለልሳንከ* 10. በዕልፍ ሳይሆን በመቶ ወንዶች ዘንድ እንደሚነድድ እሳት ሰይፍ ለሆነው ለአንደበትህ ሰላምታ ይገባል። እስከዘላለሙ የማትተኛ ወፍ ኤልያስ ሆይ በፀሎትህ ዘወትር የሚያሰቃዬኝ የደዌ መንፈስ ከእኔ አስወግድ የአንደበቴ ዛፍ ለስምህ መጠለያ ነውና። *ሰላም ለቃልከ* 11.በሽንገናላና በበደል ነገር ናቡቴን በገደለው ግዜ አክዓብን ላስደነገጠው ለቃልህ ሰላምታ ይገባል። ኤልያስ ሆይ በአምስቱ ሰነፎች ላይ በሩ በሚዘጋበት ግዜ ከሰማያዊ ሙሽራ ቤት ከብልሆቹ ጋር እገባ ዘንድ በደስታ ወደ አንተ አቅርበኝ። *ሰላም ለእስትንፋስከ* *12,,* የሞተ የመበለቷን ልጅ ላስነሣ ለትንፋሽህ የውኃው ምንጭ በጠፋ ጊዜም ለተጠማው ለጉረሮህ ሰላምታ ይገባል ። ለአርባ ቀን ያህል የጾምህ ኤልያስ ሆይ ዛሬ ግን ረኅብና ጽምን አታሳየኝ ።አሞራ ሆነህ መግበኝ እንጂ። *ሰላም ለክሳድከ* *13,,* የቅድስና አስኬማን ለለበሰ ለአንገትህ ሰላምታ ይገባል። ልብሷ የፍየል ሌጦ ለሆነው ለትከሻህ ሰላምታ ይገባል። በምሳሌና በዜና ከታላላቆች ይልቅ ታላቅ የሆንህ ኤልያስ ሆይ ሕይወትህ የመላእክት ነው ። የሀገርህ ጠልም መና ነው አስኬማህም ነውር የለባትም ። *ሰላም ለዘባንከ* *14,,* ለጀርባህ የጉልማሳነትህ ጽሕም ንጉስ ለተጠጋበት በፊትህ ለሚገኘው ለደረትህም ሰላምታ ይገባል ። ሕማም በሌለበት ሀገር የምትኖር ኤልያስ ሆይ ነፋስ በነፈሰ ዝናብም በዘነመ ጊዜ በእቅፍህ አድርገህ ከበጋና ከክረምት መብረቅ ሰውረኝ ። *ሰላም ለአዕዳዊከ* *15,,* በመስቀል ላይ በቀራኒዮ እንደ ተሰቀለ እንደ ኢየሱስ ክርስቶስ ለጸሎት ለተዘረጉ እጆችህ ሰላምታ ይገባል ። ኤልያስ ሆይ ለለመነህ ምግቡን ስጠው። በፊትህ ቢበድልም በደሉን ይቅር በለው። ለሚቀና መገዛቱ ይቀርለት ዘንድ ተወስኗልና። *ሰላም ለመዝራዕትከ* 16, በወይን ግድ እዳለ ቅርንጫፍ የአንጓዎችህ ቦታ ለሆኑ ክንዶችህ ሰላምታ ይገባል። በአለም ፍጻሜ ግዜ የትንሳኤን ተስፋ የምትናገር ኤልያስ ሆይ መጠኑ የአምላክ ትንሳኤ የሆነለት ትንሳኤህን በምናምን በእኛ ላይ በረከትህን ላክ። *ሰላም ለእመትከ* 17,ለክድህ የሚሰጥ ስጋን ለመቀበል ከቁራ አፍ ይልቅ ለሚሰፋው ለመሃል እጅህ ሰላምታ ይገባል። ኤልያስ ሆይ የሳራ ሁለተኛ ከሆነች ከጥበበኛዋ እናትህ ሁለንተናህ በሳት ተከብቦ የተወለድኸው የእዮብ መታሰቢያ በሆነች በመስከረም አንድ ነው። *ሰላም ለአጻቢእከ* 18// አምስት በወዲያ አምስት በወዲህ ሆነው በጥፍር ልብሶች ለተሸለሙ ጣቶችህ ሰላምታ ይገባል። ኤልያስ ሆይ በምድር ነገስታት እና በእየሱስ ክርስቶስ ፊት የነፍስና የስጋ ሞገስን ስጠኝ። አባት ሆይ አንተ የሞገስ ነብይ ነህ። *ሰላም ለገቦከ* 19. ማረፊያን፣አልጋን፣ምንጣፍን ላልፈለገው ጎንህ ሰላምታ ይገባል፤የማትተኛ ዘወትርም የማታንቀላፋ ኤልያስ ሆይ ያለጊዜው ከመሞት ወጥመድ ማለፊያ ሁነኝ። ዘወትርም የምገረፍ አልሁን። *ሰላም ለከርስከ* 20. መብል መጠጥ፣የካህኑ የአሮን ልብስም ለማያስጨንቀው ለሆድህ ሰላምታ ይገባል። ከዕዝራና ከሄኖክ ጋር አንድ የምትሆን ብፁዕ ኤልያስ ሆይ መጽሐፍህ ምስክር እንደሆነ ሀገርህ የተድላና የደስታ ሀገር አይደለችምን? *ሰላም ለልብከ* 21. በመሬት እየኖረ እንደብፁዓን ፃድቃን የላዩን ለሚያስብ ልቦናህ ሰላምታ ይገባል። እንደ አምላክ በቃልህ ሁሉን የቻልህ ኤልያስ ሆይ ሰባ ሁለቱም የአክዓብ ልጆች ሁሉ በቃልህ ታምመው የጠፋ አይደለምን? *ሰላም እብል ለኩልያትከ* 22. በሕይወት የምትኖር የሕያዋን አለቃ ኤልያስ ሆይ መንታ ለሆነው ኩላሊትህ ሰላምታ ይገባል ፤ አባት ሆይ ከሩቁ ሰማይ እሳትን በጠራህ ጊዜ፥ መሥዋዕትህን ፤ከድጋዩ ጋርም እንጨቱን በላ ። ከውኃው ጋርም መሬቱን ላሰ። *እኤምሀ በህሊናዬ* 23 በሕሊናዬ የተቀደሰ ሕሊናህን ሰላም እልሀለሁ።ለውስጣዊ አካልህም ሁሉ ምስጋናን አቀርባለሁ።አሮጌውን የለበስህ አዲሱንም የተጎናጸፍህ ኤልያስ ሆይ ባለሟልነትን ባገኘህ ጊዜ የዝናምን ኃይል አቆምህ ለሶስት ጊዜ ያህልም የሰማይ እሳትን አወረድህ። *ሰላም ለእንብርትከ* 24 ሞት ያልሰረቅህ መቃብርም ያላጠፋህ መዝገብ ኤልያስ ሆይ ለእንብርትህ ሰላምታ ይገባል።የአንደበቴን ሰላም ዕጠብቅ ዘንድ በደልን የሚያስተሰርይ አድርግልኝ በአዲስ ሕዝቦች መካከል እግዚአብሔርን ሽቶ እንደቀባች አንደ ጥበበኛዋ ማርያምም አድርገኝ። *ሰላም በኅቊኤከ* 25//መታጠቂያ ቁርበት ለሆነ ለወገብህ ሰላምታ ይገባል። የመለኮት ቃል ምሳርህም አካዝያስ ዛፍን የቆረጠው ነው።ሰውነትህ ጸጉር ነው።ኑሮህም በገዳም ነው።በምግባርም በስም አንድ የምትሆኑ ኤልያስ እና ዮሐንስ ሆይ ዛሬ በበዓላችሁ ቀን ባርኩን። *ሰላም እብል ለዘዚአከ*

🌹☞ወር በገባ በ6 የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወርሐዊ መታሰቢያው ነው፡፡እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አማኞች፡ኢየሱስ ስንል አምላከ አማልእክት፡ የአማልክት አምላክ ኢየሱስ ስንል እግዚእ ወአጋእዝት፡ - የጌቶች ጌታ ☞ኢየሱስ ስንል ንጉሠ ነገሥት፡ - የነገሥታት ንጉሥ ☞ኢየሱስ ስንል አልፋ ወ ኦሜጋ፡ - መጀመሪያው እና መጨረሻው፣ ፊተኛው ኋለኛው ☞ኢየሱስ ስንል ንጉሠ ሰማይ ወምድር፡ - የሰማይና የምድር ንጉሥ ☞ኢየሱስ ስንል ኤልሻዳይ፡- ኹሉን ቻይ ኢየሱስ ስንል አዶናይ፡ - መድኃኔዓለም ☞ኢየሱስ ስንል ወልደ አብ ወልደ ማርያም፡ - የአብ ልጅ የማርያም ልጅ በተዋሕዶ ልደት የከበረ ☞ኢየሱስ ስንል ፈጣሬ ኩሉ፡ - ኹሉን የፈጠረ ☞ኢየሱስ ስንል እግዚአብሔር ማለታችን ነው፡፡ ስሙን ስንጠራ ይኽ ሁሉ በልባችን ሰሌዳ ታስቦ ነው፡፡ ☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ አበቃቀሉ ለሚያምር ክቡር ለሆነው የራስ ፀጉር ሰላምታ ይገባል፡፡ ☞ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ከፀሐይ ብርሃን ይልቅ እጅግ ለሚያበራው ፊትህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ☞ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ የፍጥረትን ጥሪ ከመስማት ቸል ለማይሉ ጆሮችህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ እጅግ ያማረ የከርቤ መፍሰሻ ለሆኑ ከንፈሮችህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ በታቦር ተራራ ምሥጢረ መለኮትህን ለመግለጽ ተለንቀሳቀሰው አንደበትህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ ቸር ማኅያዊ ለሚሆን ቃልህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ ለሰው ፍቅር ሲል ለተጠማ ጉሮሮህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ☞ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ኅብረታቸው ነጭ ለሆነ የእጅ ጥፍሮችህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ☞ጌታዬ ኢየሱስ ሆይ ምጥቀቱ ለማይ መረመር ዕርገትህ ሰላምታ ይገባል፡፡ ☞(መልክአ ኢየሱስ) ☞ሲራክ ተክለጻዲቅ የተዋህዶ ልጅ ☞ https://t.me/Orthodoxtewahdoc

‹‹‹‹ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፤፤›››› መስከረም 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት +" ቅዱስ ኢሳይያስ ነቢይ "+ +በቤተ ክርስቲያን ታሪክ የኢሳይያስን ያህል ትንቢት የተናገረ ነቢይ አይገኝም:: ከትንቢቱ ብዛትና ከምስጢሩ ጉልህነት የተነሳ: አንድም ደፋር ስለ ነበር 'ልዑለ ቃል' ተብሎ ተጠርቷል:: ቅዱስ ኢሳይያስ የተወለደው ከክርስቶስ ልደት 800 ዓመታት በፊት ሲሆን ለነቢይነት የተመረጠው ገና በወጣትነቱ ነበር:: +ወላጆቹ 'ኢሳይያስ' (መድኃኒት) ያሉት በትምሕርቱ: በትንቢቱ የጸጋ መድኃኒትነት ስላለው ነው:: እርሱ በነቢይነት በተሾመበት ወራት ሊቀ ካህናቱ አዛርያስ: ንጉሡ ደግሞ ዖዝያን ይባሉ ነበር:: በሊቀ ካህናቱና በንጉሡ መካከል በተነሳ ጠብ ንጉሡ የበላይነቱን ለማሳየት ሃብተ ክህነት ሳይኖረው ሊያጥን ወደ ቤተ መቅደስ ገባ:: +ይህንን የተመለከተው ኢሳይያስ ሊገስጸው ሲገባ 'ወዳጄ ነው' በሚል ዝም አለው:: ፈታሒ እግዚአብሔር ግን ዖዝያንን በለምጽ መታው:: የግንባሩን ለምጽ በሻሽ ቢሸፍነው ከሻሹ ላይ ወጣበት:: በእሥራኤል ለምጽ ያለበት እንኩዋን በዙፋን ከተማ ውስጥም መቀመጥ አይችልምና አስወጡት:: በእርሱ ፈንታም ኢዮአታም ነግሷል:: +ኢሳይያስ ደግሞ እግዚአብሔር በሰጠው አንደበት ሙያ አልሠራበትምና ከንፈሩ ላይ ለምጽ ወጣበት:: እርሱንም ወስደው ጨለማ ቤት ዘጉበት:: ሃብተ ትንቢቱንም ተቀማ:: ቅዱሳን ትልቁ ሃብታቸው ንስሃቸው ነውና በዚያው ሆኖ ንስሃ ገባ: ተማለለ: ጾመ: ጸለየ:: +እግዚአብሔርም ንስሃውን ተመለከተለት:: ከዚያም ንጉሡ ዖዝያን በሞተበት ዓመት ኢሳይያስ እግዚአብሔርን በረዥም (ልዑል) ዙፋኑ ላይ ተቀምጦ: ኪሩቤል ተሸክመውት: ሱራፌል (24ቱ ካህናተ ሰማይ) "ቅዱስ: ቅዱስ: ቅዱስ" እያሉ ሲያመሰግኑት ተመለከተ:: (ኢሳ. 6:1) +አበው ሲተረጉሙ "አንተ ያፈርከው ዖዝያን እነሆ ሞተ:: እኔ ግን መንግስቴ የዘለዓለም ነው" ሲለው ነው ይላሉ:: ያን ጊዜ እግዚአብሔር "ወደ ሕዝቤ ማንን እልካለሁ?" አለ:: ኢሳይያስም "ጌታየ! እኔ ከንፈሮቼ የረከሱ አለሁ" አለው:: እግዚአብሔርም ሱራፊን ላከለት:: መልአኩም ፍሕም (እሳት) በጉጠት አምጥቶ ከንፈሩን ቢዳስሰው ነጻ:: ሃብተ ትንቢቱም ተመለሰለት:: ይኸውም የሥጋ ወደሙ ምሳሌ ነው:: +ከዚህች ቀን በኋላ ግን ኢሳይያስ የተለየ ሰው ሆነ:: ማንንም የማይፈራ እውነተኛ የልዑል ወታደር ሆነ:: ከኦዝያን በሁዋላ በየዘመናቸው 4ቱንም ነገሥታት ገሰጸ:: እነዚህም ኢዮአታም: አካዝ: ሕዝቅያስና ምናሴ ናቸው:: +ቅዱስ ሕዝቅያስ በነገሠ በ14ኛው ዓመት የአሦር ንጉሥ ሰናክሬም በጠላትነት ተነሳበት:: ወደ አካባቢውም መጥቶ: ከቦ አስጨነቀው:: ሰናክሬም በጦር እጅግ ኃይለኛ ነበር:: በዚያውም ላይ ጦር የሚመዙ ከ185,000 በላይ ብርቱ ተዋጊዎች ነበሩትና ሕዝቅያስ እንደማይችለው ተረድቶ መልእክተኛ ላከበት:: +ሰናክሬም ግን ሰይጣን ያደረበት ነውና የሕዝቅያስን ልመና ወደ ጐን ብሎ የእሥራኤልን አምላክ: ቅዱስ ስሙንም ተገዳደረ:: ቅዱስ ሕዝቅያስ በዚህ ጊዜ የፈጣሪው ስም ሲቃለል ሰምቷልና ፈጽሞ አዘነ:: +መልእክተኞችን ወደ ነቢዩ ቅዱስ ኢሳይያስ ልኮ እርሱ ወደ ቤተ መቅደስ ገባ:: በእግዚአብሔር ፊት ልብሱን ቀድዶ ማቅ ለበሰ:: ስለ ኢየሩሳሌምና ሕዝቡም ፈጽሞ አለቀሰ:: በዚህ ጊዜ እግዚአብሔር በኢሳይያስ አንደበት እንዲሕ አለ:- "ስለ ባሪያየ ስለ ዳዊት ከተማዋን አድናታለሁ::" +በዚያች ሌሊትም ድንቅ መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ከሰማያት በግርማ ወረደ:: ወደ ሰናክሬም የጦር ሠፈር ደርሶ አንድ ጊዜ የእሳት ሰይፉን መዝዞ ቢያሳያቸው ከአሕዛብ ሠራዊት 185 ሺ ኃያላን እንደ ቅጠል ረገፉ:: (1ነገ. 18:13, 19:1) +ታላቁ ነቢይ ልዑለ ቃል ኢሳይያስ ሐረገ ትንቢትን ያፈስ ነበርና ከተናገራቸው ትንቢቶችም አንዱ "ድንግል ትጸንሳለች: ወንድ ልጅም ትወልዳለች" የሚል ነበር:: (ኢሳ. 7:14) +በወቅቱ የነበሩ አንዳንድ ክፉ መካሪዎች ቀርበው ንጉሡን በውዳሴ ከንቱ ጠለፉት:: "ንጉሥ ሆይ! ሺህ ዓመት ንገሥ:: እንዳንተ ያለ ማንም የለም:: ነቢዩ የተናገረው ትንቢትም እኮ ላንተ ነው:: 'ድንግል' የተባለች ኢየሩሳሌም ስትሆን 'ወልድ-ወንድ ልጅ' የተባልክ ደግሞ አንተ ነህ" አሉት:: +ይሕንን ጠማማ ትርጉም እህ ብሎ የሰማቸው ቅዱስ ሕዝቅያስ አልወቀሳቸውም:: በዚህ ምክንያት እግዚአብሔር ተቆጥቶ ኢሳይያስን ላከው:: ነቢዩም መጥቶ ንጉሡን አለው:- "ትሞታለህ እንጂ አትተርፍምና ቤትህን ሥራ::" +ወዲያውኑ ሕዝቅያስ ታመመ: ደከመ:: ንጉሡ ወደ ፈጣሪ:- "ጌታ ሆይ! እንደ ቸርነትሕ በፊትህ በቅን መንገድ መሔዴን አስብና ይቅር በለኝ" ሲል ተማጸነ:: ይህ ሲሆን ቅዱስ ኢሳይያስ ገና ከንጉሡ አካባቢ አልራቀም ነበርና የእግዚአብሔር ቃል ወደ እርሱ መጣ:: +ሕዝቅያስን በለው:- "ጸሎትህን ሰምቼ: ስለ ባለሟሌ ስለ ዳዊት ብየ ምሬሐለሁ:: በዘመንህም ላይ 15 ዓመታትን ጨምሬልሃለሁ በለው" አለው:: ነቢዩም ወደ ንጉሡ ተመልሶ ይሕንኑ ነግሮ "እስከ 3 ቀን ድረስ ወደ ቤተ መቅደስ ድነህ ትመለሳለህ" አለው:: +ቅዱስ ሕዝቅያስ "ይሕ እንደሚደረግ በምን አውቃለሁ?" አለው:: ኢሳይያስም ፀሐይን ዓለም እያየ 10 መዓርጋትን ወደ ሁዋላ መለሳት:: +ልዑለ ቃል ቅዱስ ኢሳይያስ ለ70 ዘመናት ሕዝቡን አስተምሮ: ነገሥታቱን ገስጾ: 68 ምዕራፎች ያሉትን ሐረገ ትንቢት ጽፎ አረጀ:: በዘመኑ የነበረው ንጉሥ ምናሴ ግን ይባስ ብሎ ጣዖትን አቆመ: ለጣዖትም ሰገደ:: ቅዱሱ ይህንን ሲያደርግ ዝም አላለውም:: በአደባባይ ገሰጸው እንጂ:: +በዚህ የተበሳጨ ምናሴም ሽማግሌውን ነቢይ በእንጨት መጋዝ ለሁለት አሰነጠቀው:: ቅዱስ ኢሳይያስ በዚህ ዓይነት ሞት በጐ ሕይወቱንና ሩጫውን ፈጸመ:: የተናገራቸው ትንቢቶች ግልጽ ስለ ሆኑ 'ደረቅ ሐዲስ' በመባል ይታወቃሉ:: +ቸሩ አምላክ 'ደሃ ተበደለ: ፍርድ ተጉዋደለ' የሚሉ መምሕራን አባቶችን አይንሳን:: ከነቢዩም በረከቱን ይክፈለን:: +መስከረም 6 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት= 1.ቅዱስ ኢሳይያስ ነቢይ (ልዑለ ቃል) 2.ቅድስት ሰብልትንያ ሰማዕት 3.አባ ያዕቆብ ገዳማዊ 4.ቅዱስ አናቲሞስ ኤዺስ ቆዾስ   በ 06 የሚከበሩ ወርኀዊ የቅዱሳን በዓላት 1.ቅድስት ደብረ ቁስቁዋም 2.አባታችን አዳምና እናታችን ሔዋን 3.አባታችን ኖኅና እናታችን ሐይከል 4.ቅዱስ ኤልያስ ነቢይ 5.ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ 6.ቅዱስ ዮሴፍ አረጋዊ 7.ቅድስት ሰሎሜ 8.አባ አርከ ሥሉስ 9.አባ ጽጌ ድንግል 10.ቅድስት አርሴማ ድንግል ++"+ ኑ እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር:: ኃጢአታችሁ እንደ አለላ ብትሆን እንደ አመዳይ ትነጻለች:: እንደ ደምም ብትቀላ እንደ ባዘቶ ትጠራለች:: እሺ ብትሉ: ለእኔም ብትታዘዙ የምድርን በረከት ትበላላችሁ:: እንቢ ብትሉ ግን: ብታምጹም ሰይፍ ይበላቹሃል:: የእግዚአብሔር አፍ ይህንን ተናግሯልና:: +"+ (ኢሳ. 1:18) ‹‹‹‹ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ››››

ዛሬ ማታ ጀምራችሁ ይሄንን አቅዱ✝                           Size 66.5MB Length 1:11:45   በርዕሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ http://t.me/abagebrekidan http://t.me/abagebrekidan

ማብቂያ አብጅለት! በድለውህ ይከሱሃል፤ አቁስለውህ ሸንጎ ፊት ያቆሙሃል፤ ጎድተውህ ተጎጂ ለመሆን ይጥራሉ፣ አሰቃይተውህ ሲያበቁ አዛኝ ተንከባካቢ ለመምሰል ይሞክራሉ። ዝምታህ ሞኝነት፣ ትዕግሥትህም ቂልነት ሊመስላቸው ይችላል። ፈቅደህ በተዋሃደህ ማንነት ቢዘባበቱብህ፣ በየዋህነትህ ምክንያት ጥለው ሊሻገሩህ ቢሞክሩ፣ በዝምታህ ምክንያት ሴራ ቢያሴሩብ እስኪያጠፉህ ግን አትጠብቅም፤ እስኪጫወቱብህ ግን ዝም አትልም። አዎ! ጀግናዬ..! አስመሳይነታቸውን ግታው፣ በደላቸውን አስቁም፤ እያየህ እንዳለየ፣ እያወክ እንዳለወክ ማለፉን ተው። እርምጃ መውሰድህ እራስህን ለመከላከል፣ እራስህን ለማዳን ብቻ አይደለም የእነርሱንም እውነተኛ ማንነት ለማጋለጥ ነው። መብትህን ሲጋፉ፣ ነፃነትህን ሲገፉ፣ አንተነትህን ሲያዋርዱ፣ ማንነትህን ሲያንቋሸሹ፣ ክብርህን ሲያረክሱ፣ ስብዕናህን ሲያሳንሱ ትዕግስትህ መፈተኑ፣ ስሜትህም መነካቱ አይቀርም። ነገር ግን እያንደንዱ ተግባር የእራሱ ገደብና ልኬት አለው። ከቀይ መስመርህ ባሻገር የሚመጣብህን ጫናና በደል የመጋፈጥ፣ የመመለስ የውዴታ ግዴታ አለብህ። ሚዛናዊ መሆንህ ቢያስከብርህ እንጂ አያዋርድህም፣ ቢያስሞግስህ እንጂ አያሳንስህም። እያወቁ አለማወቅም ገደብ አለው፣ በእራስ ማንነት ሲቀለድ ዝም ማለት አንድ ቀን ዋጋ ማስከፈሉ አይቀርም። አዎ! ማብቂያ አብጅለት፤ ለሚደርስብህ የትኛውም አይነት እንግልትና ነቀፋ፣ ለሚወረወርብህ ክብረ ነክ ተግባር ፍፃሜ ስጠው። እራስህን ባታስከብር የሚያከብርህ አይኖርም፣ ለእራሰህ ባታስብ የሚያስብልህ የለም። ዋጋ የምትከፍለው ለእራስህ ብለህ ነው፤ ከወዳጅ መሳይ ተጣቶችህ የምትርቀው ለክብርህ፣ ለደህንነትህ ብለህ ነው። ከአስመሳዮች ተነጠል፣ የሚጠቅሙህ መስለው ዋጋህን ከሚያሳንሱ፣ ጥቅምህን ፈልገው ከተቆራኙህ፣ በወዳጅነት ሰበብ ከሚጫወቱብህ፣ በበግ ለምድ ከተሸፈኑ አታላዮች እራስህን አድን። በየዋህነትህ መጎዳት፣ በቅንነትህ መሰበር ይብቃህ፤ በልበሙሉነት ቀና ብለህ እራስህን ማስከበር፣ ለእራስህም ተገን መሆን ጀምር።

የእናቱን ጡት ያልጠባ፣ ምግብና ውሃ ያልተመገበ፣ ልብሱ ጠጉር የሆነ፣ 60 ነብሮችና 60 አንበሶች የተከተሏቸው፤ ዓይኑን ለተጠማ ወፍ የሰጠ፣ 562 ዓመት በቅድስና የኖሩት ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መ
የእናቱን ጡት ያልጠባ፣ ምግብና ውሃ ያልተመገበ፣ ልብሱ ጠጉር የሆነ፣ 60 ነብሮችና 60 አንበሶች የተከተሏቸው፤ ዓይኑን ለተጠማ ወፍ የሰጠ፣ 562 ዓመት በቅድስና የኖሩት ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ። የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በረከታቸው ይደርብን፤ ጸሎታቸው አይለየን! 🙏 #አሜን

🌷መልክአ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በአማረኛ📚🔊 አቤቱ የብፀዕ አባታችን የአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አምላክ ሆይ፤ ስለክብሩ ጻድቅ ብለህ ከመከራው ሁሉ እኔን አገልጋይህን ሠውረኝ ለጠላትም አሳልፈህ አትስጠኝ ጠብቀኝ እንጂ አትተወኝ እኔ የአንተ ፍጥረት አንተም የኔ ፈጣሪ ነህና ክብር ምስጋና ለአንተ ይገባል ለዘላለሙ አሜን፡፡

•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥ ✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል"📖ምሳ 1፥33☦📚          ✥•••••●◉ ✞ ◉●•••••✥ 📗ስንክሳር ዘወርኃ መስከረም ፭/5 ወለተ ሥላሴ ብላችሁ በጸሎታችሁ አስቡኝ https://t.me/Orthodoxtewahdoc 🌹የያዕቆብ ሌሊት ይሁንልን🕊

ገብረ መንፈስ ቅዱስ አባታችን በረከትህ ይግባ ቤታችን🤲♥️🙏
ገብረ መንፈስ ቅዱስ አባታችን በረከትህ ይግባ ቤታችን🤲♥️🙏

በስሜት ብሰሉ! አንድ በስሜቱ ያልበሰለ ሰው ሁሌም አንድን ከባድ ስራ ለስራት የሚያነቃቃውን ነገር ይፈልጋል፣ አንድ በስሜቱ የበሰለ ሰው ደግሞ ከባዱን ስራ ሺህ ጊዜ ለመስራት ዲሲፕሊን ይፈልጋል። ልዩነታቸው ግልፅ ነው መነቃቃት አንድን ከባድ ስራ ሊያስጨርስ ይችላል ነገር ግን በፍፁም እንደ ዲሲፕሊን ሺህ ከባባድ ስራዎችን ሊያስጨርሰን አይችልም። በስሜት የበሰለ ሰው የስሜቱ ገዢ እንጂ የስሜቱ ተገዢ አይደለም፣ ማድረግ ያለበትን የሚወስኑለት ሁኔታዎች ሳይሆኑ እራሱ ነው፣ እያንዳንዱ ውሳኔው ከስሜት በላይ ወጥነት ባላቸው የማይቋረጡ እንቅስቃሴዎች ስለመቃኘታቸው እርግጠኛ ይሆናል። መነቃቃት አስፈላጊ ነው፣ ሁሌም ከባድ ነገር በመጣ ቁጥር ግን አነቃቂ ነገር መፈለገ ሚዛናዊ እምነት አይደለም። ከውጭ ከሚመጣው ማነቃቂያ በላይ ከውስጥ የሚገፋን የተለየ ስሜት ያስፈልገናል። አስተውሉ፣ ሁሉም ተፅዕኖ ፈጣሪ ሰው ተፅዕኖውን መፍጠር የቻለው በየቀኑ የሚያነቃቃው ነገር ስላለውና ስሜቱ ስለማይረበሽ ይመስላችኋል? እያንዳንዱ ስኬት ላይ የደረሰ ሰው ስኬታማ የሆነው ስሜቱን እየተከተለ ሲደክመው እያረፈ፣ ሲደብረው ስራውን እየዘለለና እራሱን በጊዜያዊ ምቾት እያታለለ ይመስላችኋል? በፍፁም አይደለም። አዎ! በምንም ነገር ላይ ጣሪያ ለመንካት በቅድሚያ በስሜት ብሰሉ፤ የትኛውንም የህይወት ከፍታ ለመቆናጠጥ አስቀድማችሁ እንዴት የስሜታችሁ ገዢ እንደምትሆኑ እወቁ። ለመጣው ሰው ሁሉ እየታዘዛችሁ የምትገነቡት ዲሲፕሊን የለም፣ ላያችሁትና ለሰማችሁት ሁሉ ምላሽ በመስጠት የምታመጡት ለውጥ የለም። ብልህ ሰው የትኛውንም ተግባር ከማከናወኑ በፊት ከአላማው ጋር ስለመሄዱ ይመረምራል፣ በሳል ሰው ለተጠየቀው ጥያቄ የእሺታ መልስ ከመስጠቱ በፊት ጥያቄውን ባይቀበል ስለሚያጣው ነገር በጥልቀት ያጠናል። እናንተ በጭፍኑ መነዳት ስታቆሙ የሚነዳችሁ ሰው አይኖርም፣ እራሳችሁን መግዛት ስትችሉ የሚገዛችሁ ውጫዊም ሆነ ውስጣዊ ስሜት አይኖርም። ህይወታችሁን በሒደት የሚቀይረውን፣ የተሻለ ሰው የሚያደርጋችሁን፣ በራስመተማመናችሁን የሚገነባውን ከባዱን ነገር ሺህ ጊዜ ለማድረግ የሚያስፈልጋችሁ መነቃቃት ሳይሆን እራስን መግዛት ወይም ዲሲፕሊን ነው። አዎ! ጀግናዬ..! በስሜት እንደበሰልክ ለማረጋገጥ ይሔን አንድ ጥያቄ ብቻ መልስ። ጠቃሚ እንደሆነ እያወክ፣ ህይወትህን እንደሚቀይረው እያመንክ ከባድ ስለመሰለህ ብቻ ሳታደርገው የቀረሀው ተግባር ምንድነው? በእርግጥም በስሜት የበሰልክ ከሆንክ ትኩረትህ የተግባሩ ክብደት ወይም ቅለት ሳይሆን የሚያመጣው ለውጥ ይሆናል፣ ስራውን ለመጀመር የምትወስነው ከሚሰማህ ጊዜያዊ ስሜት በመነሳት ሳይሆን በስተመጨረሻ ከምታገኘው ውጤት አንፃር ይሆናል። ቆመህ ህይወት እስክትሰራህ አትጠብቅ፣ ለዓመታት ቀላል ተግባራትን እየደጋገምክ ዋጋቢስ የወረደ ህይወት አትኑር። ደፋርና ስሜቱን የሚገዛ ብርቱ ሰው ካልሆንክ እንዲሁ እያሳበብክና እያለቀስክ ታረጃለህ እንጂ ምንም የምታመጣው ለውጥ አይኖርም። ቆፍጠን ብለህ ተንቀሳቀስ፣ ጥርስህን ነክሰህ ለከባዱ የህይወት ፈተና ተዘጋጅ፣ በጊዜያዊ ብልጭልጭ ነገር አትሸወድ። ራዕይህን እውን የሚደርግልህንና ያመንክበትን አላማ ከዳር የሚያደርስልህን የማይናወጥ ዲሲፕሊን መገንባት ላይ አተኩር።

እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው 🙏 ለእኔ ያደረገው ብዙ ነው እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው ለእኔ ያረገልኝ ብዙ ነው ❤️ እረዳት እርሱ ነው ከሰማያት እግዚአብሔር ጠባቂ የኔን ሕይወት ☦ ብርሃኑን በፊ
እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው 🙏 ለእኔ ያደረገው ብዙ ነው እግዚአብሔር ስራው ድንቅ ነው ለእኔ ያረገልኝ ብዙ ነው ❤️ እረዳት እርሱ ነው ከሰማያት እግዚአብሔር ጠባቂ የኔን ሕይወት ☦ ብርሃኑን በፊቴ የሚያበራ✨ አምላኬ ድንቅ ነው የእርሱ ስራ🙏 በመንገዴ ሁሉ የሚመራኝ ስነሳ ስወድቅም የሚያስበኝ🫀 ማንም አልመጣልኝ ከወገኔ ከሁሉም ይበልጣል እርሱ ለኔ 😍 የእዳዬን ደብዳቤ ውድቅ አድርጎ ሕይወቴን መራልኝ ወደ በጎ ✨ ኧረ እንደ እግዚአብሔር ማን ይሆናል እሱን ለሚፈሩት ይታመናል 💞 አንድ ቀን አስቤ ተጨንቄ ለመኖር አልቻልኩም ተጠንቅቄ❤️‍🩹 ሁሉን ነገር ለእርሱ ትቸዋለሁ በምሕረቱ ጥላ እኖራለሁ 🙏 ዘማሪ ቀሲስ እንዳልካቸው ዳኘው 😍