en
Feedback
ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።

Open in Telegram

📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623

Show more
3 275
Subscribers
-324 hours
-237 days
-5630 days
Posts Archive
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሐቲ ድንግል 4ኛ ግዜ ታትማለች በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ። እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዎች በDh
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሐቲ ድንግል 4ኛ ግዜ ታትማለች በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ። እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዎች በDhl እና በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት መጽሐፍትን እንልካለን ይዘዙን። አድራሻ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ። t.me/GhionBookStore1623

#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሐቲ ድንግል 4ኛ ግዜ ታትማለች በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ። እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዎች በDh
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሐቲ ድንግል 4ኛ ግዜ ታትማለች በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ። እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዎች በDhl እና በኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት መጽሐፍትን እንልካለን ይዘዙን። አድራሻ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ። t.me/GhionBookStore1623

#ዜና_መጽሐፍ #ርእስ፦ ሐተታ ዘቅዱስ አትናቴዎስ- ተስእሎተ አንትያኮስ #ይዘት፦ ቅዱስ አትናቴዎስ በዘመኑ የተለያዩ መጻሕፍትን አዘጋጅቷል፡፡ ከሥራዎቹ አንዱ አንትያኮስ የሚባል መኰንን ለጠየቀው ጥያቄ
#ዜና_መጽሐፍ #ርእስ፦ ሐተታ ዘቅዱስ አትናቴዎስ- ተስእሎተ አንትያኮስ #ይዘት፦ ቅዱስ አትናቴዎስ በዘመኑ የተለያዩ መጻሕፍትን አዘጋጅቷል፡፡ ከሥራዎቹ አንዱ አንትያኮስ የሚባል መኰንን ለጠየቀው ጥያቄ መልስ የሰጠበት ይህ “ተስእሎቶ አንትያኮስ" የተባለ መጽሐፍ ነው፡፡ የመኰንኑ ጥያቄና የሊቁ መልስ በሁለት ክፍል የተከፈለ ነው፡፡ የመጀመሪያው ክፍል ሰባ ስምንት ጥያቄዎችንና መልሶቻቸውን የያዘ ሲሆን የሁለተኛው ክፍል ደግሞ አርባ ጥያቄዎችንና መልሶቻቸውን ይዟል፡፡ መጽሐፉ በድምሩ በሊቁ የተመለሱ የ118 ጥያቄዎች መልሶችን ይዟል ፡፡ በእነዚህ ጥያቄዎች ውስጥ ሥነ ፍጥረት፣ ነገረ መለኮት፣ ሥርየተ ኃጢአት፣ ልዩ ልዩ የምግባር ሥራዎችና ሌሎችም ጥያቄዎች ተካተውበታል፡፡ አብዛኞቹ በዚያ ዘመን የነበሩ መናፍቃን ኑፋቄዎች ለመሆናቸው የጥያቄዎች መንፈስ ያስረዳል። #የገጽ_ብዛት፦ 180 #የሽፋን_ዋጋው፦ 290 ብር ___   ያልደረሳችሁ እያለቀ ስለሆ የተዎሰነ ቅጅዎች አለን ከግዮን ቅናሽ ጋር እንጠብቅዎታለን - ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ።

በግዮን መጻሕፍት ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ።እንዲሁም በመላው አለም ለምትኖሩ ውድ አንባቢዮቻችን በተለያዩ አማራጮች መጽሐፍትን እንልካለን ይዘዙን። አድራሻ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ። t.me/GhionBookStore1623

በግዮን መጻሕፍት ነባር እና አዳዲስ መጽሐፍትን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ለማግኘት ቻናሉን Join ያድርጉ።አድራሻ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ። t.me/GhionBookStore1623

#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚ
#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚነት ያለው መጽሐፍ ይህ መጽሐፍ መሆኑ በስፋት የተነገረለት ነው፡፡ እስከ ዛሬ ወደ እኛ ባለመምጣቱ የቀረብንን ይኸው ዛሬ መጽሐፉ ተተርጉሞ በመቅረቡ አንድ ጉድለት ተሸፍኗል፡፡ መጽሐፉ የክርስትና ሕይወትን ምንነት በአግባቡ ለመረዳትና ለመኖር በሚሹ ዘንድ ሁሉ የሚፈለግና የሚጠቅም መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ እግዚአብሔር አምላካቸውን በገዳማዊ ሕይወት ለሚያገለግሉ ጠቀሜታው እጅግ የጎላ ነው፡፡"             ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ይህ ለረጅም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረውና ግሩም የሆነ መጽሐፍ አሁን በድጋሚ ታትሞ  ለገበያ ቀርቧል። በግዮን መጻሕፍት መደብርም ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።

#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚ
#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት "ዮሐንስ ዘሰዋስው በምሥራቁ ቤተ ክርስቲያን ዘንድ በእጅጉ ተወዳጅና ከፍተኛ ተጽእኖ ፈጣሪ የሆነ መጽሐፍ ነው፡፡ እንዲያውም በገዳማዊ ሕይወት ውስጥ ከወንጌል ቀጥሎ ተጠቃሹና ተሰሚነት ያለው መጽሐፍ ይህ መጽሐፍ መሆኑ በስፋት የተነገረለት ነው፡፡ እስከ ዛሬ ወደ እኛ ባለመምጣቱ የቀረብንን ይኸው ዛሬ መጽሐፉ ተተርጉሞ በመቅረቡ አንድ ጉድለት ተሸፍኗል፡፡ መጽሐፉ የክርስትና ሕይወትን ምንነት በአግባቡ ለመረዳትና ለመኖር በሚሹ ዘንድ ሁሉ የሚፈለግና የሚጠቅም መሆኑ ግልጽ ነው፡፡ ይህ እንዳለ ሆኖ በተለይ ደግሞ እግዚአብሔር አምላካቸውን በገዳማዊ ሕይወት ለሚያገለግሉ ጠቀሜታው እጅግ የጎላ ነው፡፡"             ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ ይህ ለረጅም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረውና ግሩም የሆነ መጽሐፍ አሁን በድጋሚ ታትሞ ለገበያ ቀርቧል። በግዮን መጻሕፍት መደብርም ታገኙታላችሁ።

#የመላእክት-ተልእኮ-በሰው-መዳን ያለው ድርሻ!!! """""""""""""""""""""""""""""""""""""""" #እግዚአብሔር መላእክትን ሲፈጥራቸው #ለሦስት ጉዳዮች ነው፦ #አንደኛ፦የባሕርይ ክብሩን በፀጋ እንዲሳተፉ ነው፡፡ #ሁለተኛ፦ሁልጊዜም እርሱን ያለ እረፍት እንዲያመሰገኑ ነው፡፡ #ሦስተኛ ለሰው ልጅና ለፍጥረታት ሁሉ ጥበቃ ነው፡፡ #ዛሬ የመልአኩ የቅ/ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል ከመሆኑም አንጻር የሰውን ልጅ ጠብቆት እናያለን፡፡ #እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ይሁን ብሎ በልዑል ሥልጣኑ እንደፈጠረው በይሁንታ መጠበቅ ይችላል፡፡ "ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና" ሉቃ1፥37፡፡ #ነገር ግን እግዚአብሔር የባሕርይ ጠብቆቱን መላእክት በጸጋ እንዲሣተፉትና የሰውን ልጅ እንዲጠብቁት አድርጓል፡፡የሰው ልጅ አማኒም ይሁን መናፍቅ ደግም ይሁን ክፉ ጻድቅም ይሁን ኀጥእ በመላእክት ጠብቆት ውስጥ ጸንቶ የሚኖር ነው፡፡የሰው ልጅ አይ እኔ ኦርቶዶክስ ስላልሆንኩ የመላእክት ጠብቆት አያስፈልገኝም ሊል አይችልም፡፡ምክንያቱም የእግዚአብሔር መግቦት በሁሉም ፍጥረት ላይ ስለሆነ ነው፡፡ "በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ:የሚረግሟችሁንም መርቁ ለሚጠሏችሁም መልካም አድርጉ: ስለሚያሳድዷችሁም ጸልዩ:እርሱ በክፉዎችና በበጎዎች ላይ ፀሓይን ያወጣልና:በጻድቃንና በኀጢአተኛዎችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና። የሚወዷ፟ችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?:: ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ?አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?፡፡እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ" ማቴ. 5:45-48 #እግዚአብሔር ለፍጡራን የሚያደርጋቸው መግቦታቱ በሙሉ የሚከናወኑ በመላእክት ተልእኮ ነው፦ ዝናሙ፣ደመናው፣ጠሉ፣ፀሐይ፣ጨረቃ፣ከዋክብት፣ነፋሳት፣መባርቅት፣ነጎድጓት...እነዚህ ሁሉ የሚመግቡን በመላእክት ተልእኮና ሥልጣን ነው፡፡ስለዚህ ዓለም በእኒዚህ መግቦት እስካለ ድረስ መላእክትን አይጠብቁኝም ማለት እኔ ከእግዚአብሔር ጠብቆትና መግቦት እልፍም ሲል በእራሴ ዓለምነት ነው የምኖር ያሰኛል፡፡ "መላእክተ ገጽንም የሚያመሰግኑ መላእክትንም በእሳት አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም በጨለማና በብርሃን አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም በውርጭና በበረድ አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም፡፡በውኃ ላይ በመብረቅና በነጐድጓድ ላይ የተሾሙ መላእክትንም በነፋሳት ላይ የተሾሙ መላእከተን በቁርና በውርጭ በመጾውና በክረምት በበጋና በጸደይ በምድርና በሰማይ ባሉ ነፋሳት ሁሉ ላይ የተሾሙ መላእክትን በወንዙ ሁሉ በብርሃንና በጨለማ እግዚአብሔር በባሕርይ እውቀቱ ባዘጋጃቸው በምሽትና በመንጋት ላይ የተሾሙ መላእክትን ፈጥሮአልና። የፍጥረትን ነገር ሁሉ ጻፍ ብሎ ነገረው። ኩፋ.2፥6-7:: "ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ዑርኤል በመብረቅ በነጐድጓድ የተሾመ ነው።በሰው ቁስል የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሩፋኤል ነው፡፡ ዲያብሎስን የሚበቀለው አጋንንትንም የሚበቀላቸው ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ራጉኤል ነው።ለሰው ባደረገው በጎነት ላይ ለሕዝቡ ታዛዥ ነውና ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሚካኤል ነው።በባቦች ላይ በገነትም ባሉ ጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ገብርኤል ነው። ሄኖ.6:2-7:: "አንዱም አንዱም በየወገናቸው እንዳሉ አንዱም አንዱ በየዘመናቸውና በየሥልጣናቸው አንዱም አንዱም በየመውጫቸውና በየስማቸው ከኔ ጋራ ያለ መሪያቸው የሚሆን የከበረ መልአኩ ዑርኤል ባሳየኝ በየወራታቸውም ጸንተው እንዲኖሩ የሚናገር መጽሐፍ ይህ ነው። ሄኖ.21:2:: #ስለዚህ መላእክት ለሰው ልጅ በሁለተናው የሚጠብቁት ናቸው፦ ከእሳት ሲገባ አብረው ገብተው አድነውታል፡፡ከአንበሳ አፍ አድነውታል፡፡ባሕር ከፍለውለታል፡፡ከጠላት ጋር ተዋግውለታል፡፡ትንቢት ተናግረውለታል፡፡ራዕዮችን ሕልሞችን ተርጉመውለታል፡፡የክርስቶስን ሰው መሆን አብሥረውታል፡፡የክርስቶስን ልደት አብሥረውታል፡፡በጎል አብረውት አመስገነዋል፡፡በሥደት አብረው ተሰደዋል፡፡ሚጠቱን ነግረውታል፡፡በገዳም አገልገለውታል፡፡ትንሳኤውን እርገቱን አብሥረውታል፡፡ዳግም ምጽአቱን ነግረውታል፡፡ከእስርቤት አውጥተውታል፡፡ከሰይፍ አድነውታል፡፡ አጠቃላይ መላእክት ለሰው ልጅ ለደስታውም ለመከራውም በዓለ ወጎች ናቸው፡፡ስለዚህ ሰው ከመላእክት ጠብቆት መራቅ ፈጽሞ አይችለም፡፡ "ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን??" ዕብ.1:14:: "ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፡፡ መላእክታቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና" ማቴ.18:10፡፡ "በዚያም ዘመን ስለሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል:ሕዝብም ከሆነ ዠምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል:በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል" ትን.ዳን.12:1:: "እንሆም:የጌታ መልአክ ቀረበ በቤትም ውስጥ ብርሃን በራ:ጴጥሮስንም ጐድኑን መቶ፟ አነቃውና ፦ ፈጥነህ ተነሣ አለው።ሰንሰለቶቹም ከእጁ ወደቁ። መልአኩም፦ታጠቅና ጫማህን አግባ አለው፡ እንዲሁም አደረገ" ሐዋ.12:7-8:: #የክርስቶስ ሰው መሆን መጸነስ፣መወለድ፡መሠደድ፡መጠመቅ ማስተማር፣ሕግ መሥራት፣መሰቀል፣መሞት፣መቀበር፡መነሳት ማረግ፣ዳግም፡መምጣት ለሰው ልጅ እንደሆነ ሁሉ የመላእክትም ጥበቃ ለሁሉም ፍጥረት ነው፡፡ ስለዚህ ከመላእክት ጠብቆት ፈጽሞ መውጣት አይቻልምና የመላእክት በዓል ማክበር ለክርስትና ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ በሙሉ ነው፡፡ ✞ ቅዱስ ገብር እንደ ሠለስቱ ደቂቅ እኛንም ከሦስት ነገር ይጠበቀን፦ ☞ ዳያብሎስ!!! ☞ ስስእት!!! ☞ ኃጢአት!!! ☞ ፍቀረ ንዋይ!!! ☞ ፍዳ ሞት!!! ☞ ትእቢት!!! ❖እናመልከው ዘንድ ለፈጠረን እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው እንላለን!!!              ❖አ.ዘ.ያዕቆብ፡፡             © ጌዴዎን ዘለዓለም፡፡

#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሁኑ ጊዜ ‹‹ሃይማኖት እንጂ ሥርዓት አያድንም! በሚል ፈሊጥ እምነቱን ፍጻሜ የሚሰጠውና በሥራ የሚያስተረገመው ሥርዓትና ቀኖና በምን አለበት» አዘናጊ ብሂል ፈተና ሲገጥመው ይታያ
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት አሁኑ ጊዜ ‹‹ሃይማኖት እንጂ ሥርዓት አያድንም! በሚል ፈሊጥ እምነቱን ፍጻሜ የሚሰጠውና በሥራ የሚያስተረገመው ሥርዓትና ቀኖና በምን አለበት» አዘናጊ ብሂል ፈተና ሲገጥመው ይታያል፡፡ እውነታው እንዲህ እንዳልሆነና በእንዴት ያሉ ደጋግ አበው፣ በመቼ ጊዜና ቦታ፣ በምን ምክንያትና ምን ዐላማን ለማሳካት እንደ ተጻፈ በዚህ መጽሐፍ እንረዳለን፡፡ መጽሐፉ ብሔራውያን ምንጮች ከውጭ ቅጂዎች በማስተናበር የተጻፈ በመሆኑ የቤተ ክርስቲያናችንን ያልተፋለሰና ያልተቋረጠ የእምነትና የሥርዓተ አምልኮ ጥንታዊነት በውስጥም በአፍአም ማስረጃ ያረጋግጥልናል። እያንዳንዱ ጉባኤ የተደረገበትን፣ የእያንዳንዱን ጉባኤ አናቅጽ ይዘት፣ የድንጋጌያቸውን ምክንያት፣ በጉባኤያቱ የነበሩ ተሳታፊዎችን ማንነትና ከጉባኤው በኋላ የነበረውን የአፈጻጸም ሁኔታ፣ በጉባኤው ሂደትና አፈጻጸም ያጋጠመውን ፈተና፣ የጉባኤያቱ ዓይነት፣ ያነጋገሩትን ጭብጦች፡ ያላስማሙትን ቁልፍ ቃላትና ሌሎችም ተያያዥ ሃይማኖታውያንና ታሪካውያን ሁነቶች መጥኖ አቅርቧል፡፡ እንደዚህ ያለ ታሪክንና ዐውድን ያገናዘበ አቀራረብ፡- ቃለ ሃይማኖትንና ሥርዓትን ቀዳምያኑ ሠሪዎች (ሐጋጊዎች) ባፀደቁበት ዐውድና በእኛ የዛሬ መረዳት መካከል የሚኖረውን ክፍተት በመሙላት ረገድ ዐቢይ ድርሻ ይኖረዋል፡፡ የምንጩ ልሳነ ብዙኅ መሆን የቲዎሎጂ መምህራንና ተማሪዎች ከአብነቶቹ ያላቸውን ተዋሥኦ ያዳብራል፡፡ የወንድማችን የዲያቆን አዶንያስ ብርሃነ ‹የቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች» መጽሐፍ ለዚህ ተዋሥኦና ጥናት ብዙ ርቀት የሚያስጉዝ ስንቅ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ ከኢየሩሳሌሙ የሐዋርያት ጉባኤ እስከ ቊስጥንጥንያ የነበሩትን ጉባኤያት በግሩም አቀራረብ ቃኝቶ በመልካም ትርጓሜ አቅርቦልናል፡፡ መልካም ንባብ! በአማን ነጸረ ደብተራና የሕግ ባለሙያ በግዮን መጻሕፍት ታገኙታላችሁ።

#የተባረከች_አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች #የተባረከች_ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች #የተባረከ_ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል #የተባረከች_ምላስ የአምላ
#የተባረከች_አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች #የተባረከች_ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች #የተባረከ_ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል #የተባረከች_ምላስ የአምላኳን ስጋና ደምን ትቀበላለች #የተባረከ_አንደበት ላይ እግዚሐብሔር ይመስገን የሚል ቃል አይጠፋበትም #የተባረከች_አንገት የአምልኮ ደም የፈሰሰበትን ቅዱስ መስቀል ትሸከማለች #የተባረከች_ልብ ኢየሱስን እስከ እናቱ አንግሳ በፍቅር ትሞላለች #የተባረከች_እጅ የቀረበላትን ምግብ በአምልኮ ስም ትባርካለች #የተባረከች_እግር ጠዋትና ማታ የአምላኳን መቅደስ ትረግጣለች "እኔ እግዚሐብኤር አምላካቹ ነኝና ሰውነታችሁን ቀድሱ ቅዱስም ሁኑ እኔ ቅዱስ ነኝና" ዘሌ. 11፥44 #አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ

"መናፍቃንን እንደ መዶሻ የቀጠቀጣቸው ፣ እንደ ሰም ያቀለጣቸው ፣ እንደ እሳት ያቃጠላቸው ፣ እንደ ገለባ ያበጠራቸው።" መጽሐፍ በድጋሚ ለ17 ተኛ ጊዜ ታተመ። "መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፩" ይህን መጽሐፍ
"መናፍቃንን እንደ መዶሻ የቀጠቀጣቸው ፣ እንደ ሰም ያቀለጣቸው ፣ እንደ እሳት ያቃጠላቸው ፣ እንደ ገለባ ያበጠራቸው።" መጽሐፍ በድጋሚ ለ17 ተኛ ጊዜ ታተመ። "መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፩" ይህን መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ። ለበለጠ መረጃ 0912198891 0913083816

"መናፍቃንን እንደ መዶሻ የቀጠቀጣቸው ፣ እንደ ሰም ያቀለጣቸው ፣ እንደ እሳት ያቃጠላቸው ፣ እንደ ገለባ ያበጠራቸው።" መጽሐፍ በድጋሚ ለ17 ተኛ ጊዜ ታተመ። "መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፩" ይህን መጽሐፍ
"መናፍቃንን እንደ መዶሻ የቀጠቀጣቸው ፣ እንደ ሰም ያቀለጣቸው ፣ እንደ እሳት ያቃጠላቸው ፣ እንደ ገለባ ያበጠራቸው።" መጽሐፍ በድጋሚ ለ17 ተኛ ጊዜ ታተመ። "መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፩" ይህን መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ። ለበለጠ መረጃ 0912198881 0913083816

"መናፍቃንን እንደ መዶሻ የቀጠቀጣቸው ፣ እንደ ሰም ያቀለጣቸው ፣ እንደ እሳት ያቃጠላቸው ፣ እንደ ገለባ ያበጠራቸው።" መጽሐፍ በድጋሚ ለ17 ተኛ ጊዜ ታተመ። "መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፩" ይህን መጽሐፍ
"መናፍቃንን እንደ መዶሻ የቀጠቀጣቸው ፣ እንደ ሰም ያቀለጣቸው ፣ እንደ እሳት ያቃጠላቸው ፣ እንደ ገለባ ያበጠራቸው።" መጽሐፍ በድጋሚ ለ17 ተኛ ጊዜ ታተመ። "መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፩" ይህን መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ። ለበለጠ መረጃ 0912198881 0913083816

ቃና ዘገሊላ መጽሐፍ ለ11ኛ ጊዜ ታተመ። "የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ሁለትን የመጀመሪያ አንቀጽ መነሻ ያደረገችውና በሰርግ ቤቱ ስም ቃና ዘገሊላ በማለት የተሰየመ ይህ መጽሐፍ፥ እንደ ሰርግ ቤቱ ስድስ
ቃና ዘገሊላ መጽሐፍ ለ11ኛ ጊዜ ታተመ። "የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ሁለትን የመጀመሪያ አንቀጽ መነሻ ያደረገችውና በሰርግ ቤቱ ስም ቃና ዘገሊላ በማለት የተሰየመ ይህ መጽሐፍ፥ እንደ ሰርግ ቤቱ ስድስት ጋኖች በስድስት ምዕራፎች የተከፈለ ነው። ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዝ እንደነበሩት እንደ ቃና ጋኖችም እነዚህ ምዕራፎች እያንዳንዳቸው ሦስት ወይም አራት የንዑስ ርዕስ እንስራን የያዙ ናቸው፡፡ ... "ይህ መጽሐፍ በስድስቱ ጋኖች /ምዕራፎች/ ውስጥ በቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት ትርጓሜ መነሻነት በሰርግ ቤቱ ውስጥ ጥቂት እንድንቆይ ለማድረግ ይተጋል፡፡ .…. "እንኪያስ እኛም በኄኖክ መሪነት በቃና ዘገሊላ ሰርግ ቤት ውስጥ እንድንመላለስ፣ ከጌታችንና ከሐዋርያቱ ጋር ወደ ሰርግ ቤቱ እንድንገባ፣ ወደ ጓዳ ዘልቀን የወይኑን ማለቅ አስበን እንድንጨነቅ፣ እመቤታችን ስታማልድ ልጇም ሲማለድ እንድናይ፣ ከአገልጋዮቹ ጋር ውኃ ልንቀዳ ወንዝ እንድንወርድ፣ አብረን ውኃውን እስከአፉ ሞልተን ጌታችን የሚያደርገውን እንድንመለከት፣ ከታዳሚዎች ጋር ወይን የሆነውን ውኃ ቀምሰን እንድናደንቅ፣ መልካሙ የወይን ጠጅ ምነው እስካሁን ቆየ? ብለን ከአሳዳሪው ጋር አብረን እንድንቆጭ፣ ከዚያም ከሐዋርያቱ ጋር በስሙ አምነን ከሰርግ ቤቱ እንድንወጣ፣ ከምድራዊው ሰርግ ቤት ወጥተንም ወደ የቤታችን ሳንገባ ወደ ሌላ ሰማያዊ ሰርግ እንድንታደም ይህን ግሩም መጽሐፍ እናንብብ፡፡... ____ በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፎቶችን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኛላችሁ። ለበለጠ መረጃ በ0912198891/0913083816 ይደውሉ።

ወዳጄ ሆይ የትዕቢት መርዝ ተጠራቅሞ አብጦብሃልን? እንኪያስ ወደ #ቅዱስ_ሥጋዉና_ክቡር_ደሙ ቅረብ፤ ስለ ወዳጆቹ ሲል አርአያ ገብርን የነሣ ትሑቱ ጌታም ትሕትናን ያስተምርሃል፡፡ የስግብግብነት ትኩሳት
ወዳጄ ሆይ የትዕቢት መርዝ ተጠራቅሞ አብጦብሃልን? እንኪያስ ወደ #ቅዱስ_ሥጋዉና_ክቡር_ደሙ ቅረብ፤ ስለ ወዳጆቹ ሲል አርአያ ገብርን የነሣ ትሑቱ ጌታም ትሕትናን ያስተምርሃል፡፡ የስግብግብነት ትኩሳት አስቸግሮሃልን? ወደ #ቅዱስ_ሥጋዉና_ክቡር_ደሙ ቅረብ፤ ደግነትንም ትማራለህ፡፡ የምቀኝነት ብርድ አስቸግሮሃልን? እንኪያስ ወደ #ሰማያዊው_መዓድ ቅረብ፤ ምህረት ማድረግንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ ትዕግሥትን የማጣት እከክ ይዞሃልን? እንኪያስ ወደ #ቅዱስ_ሥጋዉና_ክቡር_ደሙ ቅረብ፤ ራስን መግዛትንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወትህ ልል ዘሊል ብትሆን ይህን #መንፈሳዊ_መዓድ ተመገብና ብርቱ ትሆናለህ፡፡ ቆሽሸሃልን? እንኪያስ ወደዚሁ መብልና መጠጥ ቅረብ ብዬ እመክርሃለሁ፤ ንጽሕናንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡” #ቅዱስ_ቄርሎስ_ዘእስክንድርያ

የትቤ ተዋሕዶ ይዘቶች ጸሐፊ፦ መ/ር መዝገበ ቃል ገብረ ሕይወት የገጽ ብዛት፦ 200 ትቤ ተዋሕዶ ፲፮ የሚያህሉ የተዋሕዶ ዓይነቶችን እንደ ዐቢይ ጉዳይ በመያዝ በሌሎች ንኡሳን አርእስቶችና ዝርዝር ይዘ
የትቤ ተዋሕዶ ይዘቶች ጸሐፊ፦ መ/ር መዝገበ ቃል ገብረ ሕይወት የገጽ ብዛት፦ 200 ትቤ ተዋሕዶ ፲፮ የሚያህሉ የተዋሕዶ ዓይነቶችን እንደ ዐቢይ ጉዳይ በመያዝ በሌሎች ንኡሳን አርእስቶችና ዝርዝር ይዘቶች ተዋቅሮ የቀረበ መጽሐፍ ነው፡፡ ዐቢይ ይዘቱና የአሳቡ ማእከል ስለ ተዋሕዶ ሆኖ መዘርዝር ነጥቦችን ሳናካትት ዐበይት ይዘቶቹ  የሚከተሉት የተዋሕዶ ዓይነቶች ናቸው፦ ፩. የህልውና ተዋሕዶ (ያለ አካላት መጠፋፋት የሦስቱ አካላት የአንዱ በአንዱ መኖር) ፪. የፈቃድ ተዋሕዶ (ሦስቱ አካላት በአንድ ልብ አስበው የሚፈቅዱት አንድ ፈቃድ) ፫. የፍቅር ተዋሕዶ (አንዱ አካል አንዱን አካል የሚወድበት ፍቅረ ባሕረይ፣ ፍቅረ ተዋሕዶ፣ ፍቅረ ህልውና) ፬. የሕይወት ተዋሕዶ (የመላእክት በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት መኖር) ፭. የዐራቱ ባሕርያት ተዋሕዶ (በፍጥረት አካል ውስጥና በየሚኖሩበት ዓለም ጸንቶና ተስማምቶ መኖር) ፮. የሰው ተዋሕዶ ፩ኛ የሥጋ አካል የሆኑት የ፬ቱ ባሕርያት ተዋሕዶ ፪ኛ የነፍስና የሥጋ ተዋሕዶ ፫ኛ ሥጋዊ ተዋሕዶ (ከልደት እስከ ሞት ከፍጥረት ጋር ያለን መስተጋብር) ፬ኛ የመንፈሳዊ ሕይወት የጸጋ ተዋሕዶ ፯. ፍቅረ እግዚአብሔር የኅድረት ተዋሕዶ ፰. ፍቅረ ቢጽ የፍቅር ተዋሕዶ ፱. የጋብቻ ተዋሕዶ (የሴትና የወንድ) ፲. መንፈሰ ረድኤት ተዋሕዶ (የነቢያት፣ የኦሪት ጻድቃን) ፲፩. የቃልና የትስብእት ተዋሕዶ (ነገረ ሥጋዌ) ፲፪. የጸጋ ተዋሕዶ (በመዓርጋተ ቅድስና የሚገኝ) እኒህ ከላይ ከ፩ እስከ ፲፪ የዘረዘርናቸውና በሰው ተዋሕዶ እስከ ነጥብ ፬ የዘረዘርናቸውን በድምሩ ፲፮ የተዋሕዶ ዓይነቶችን በጥልቀት ይተነትናል፡፡ ጠጠር ያለ ስለሆነ ደጋግመን ማንበብ መልካም ነው፡፡ በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፎችን ያገኛሉ።

#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት ዘመናችን ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እጅጉን ፈተና ላይ የወደቀበት, የቤተ ክርስቲያን ሥርዐቷ ባለቤት ያጣበት ጊዜ መሆኑን መናገር ለቀባሪ የማርዳት ያህል ነው፡፡ ነገሩ ሲከፋ ደግሞ
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት ዘመናችን ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እጅጉን ፈተና ላይ የወደቀበት, የቤተ ክርስቲያን ሥርዐቷ ባለቤት ያጣበት ጊዜ መሆኑን መናገር ለቀባሪ የማርዳት ያህል ነው፡፡ ነገሩ ሲከፋ ደግሞ የቤተ ጉባኤና የቤተ ክርስቲያንን የሥርዐት መጻሕፍት ጠቅሶ ማስተማር የሚያሳፍር : የሚመስልበት ደረጃ ላይ ደርስናል። "ጸሐፊ" እና "ሰባኪ" የሚል ስም ተሸክመው ፍትሐ ነገሥትን የመሰሉ የሥርዐት መጻሕፍትን ለመጥቀስ እንኳ ፍላጎት የሌላቸው "አገልጋዮች" እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ ምእመናንን (በተለይም በከተሞችና በውጭ ሀገራት የሚኖሩትን) ለእግዚአብሔር ሥርዐት ግዴለሽ እንዲሆኑ አድርጓል። በውጤቱም ክርስትና ከተግባር ቅድስና ይልቅ ስብከትና ጽሑፍ ብቻ እንዲሆን አስገድዷል። ስለዚህም እንደዚህ ያሉ የሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት በእጅጉ ያስፈልጉናል። ይህ መጽሐፍ ኹሉንም የቤተ ክርስቲያኗን ሥርዐቶች ለማካተት ይዘቱ፤ መጠኑ ባይፈቅድም ወሳኝ የሚባሉትን ነጥቦች በጥያቄና መልስ እያሰናሰለ ይዟል፡፡ ትኩረቱን ደግሞ በተለይ የዘመናችን የሥርዐት ክፍተት የሚታይባቸው የቅዳሴ፤ የቤተ ክርስቲያን ዙሪያና መሰል ጉዳዮች ላይ አድርጓል። ጸሐፊው፦ መምህር አብርሃም ከልጅነታቸው ተምረው በዜማ፤ በቅኔና በመጻሕፍተ ትርጓሜ የበሰለ አእምሮ ከጥሩ ብዕር ጋር ያላቸው ናቸውና ለዚህ የመጀመሪያ የጽሑፍ ሥራቸው መርቀናቸዋል። ቀጥሎም መሰል መጻሕፍትን ከመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የተነሣ ከትበው ያበረክቱልናል የሚል ተስፋ አለን፡፡ ዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።

አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ ወደ ገላትያ ሰዎች የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሐተታ እኛ ዘንድ ከዘወትር ልዩ ቅናሽ ጋር ያገኙታል።
አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ ወደ ገላትያ ሰዎች የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሐተታ እኛ ዘንድ ከዘወትር ልዩ ቅናሽ ጋር ያገኙታል።