ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
Kanalga Telegram’da o‘tish
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
Ko'proq ko'rsatish3 293
Obunachilar
-324 soatlar
-197 kunlar
-4130 kunlar
Postlar arxiv
Repost from ምሥራቀ ፀሐይ ጉባኤ ቤት
#የመላእክት-ተልእኮ-በሰው-መዳን ያለው ድርሻ!!!
""""""""""""""""""""""""""""""""""""""""
#እግዚአብሔር መላእክትን ሲፈጥራቸው #ለሦስት ጉዳዮች ነው፦
#አንደኛ፦የባሕርይ ክብሩን በፀጋ እንዲሳተፉ ነው፡፡
#ሁለተኛ፦ሁልጊዜም እርሱን ያለ እረፍት እንዲያመሰገኑ ነው፡፡
#ሦስተኛ ለሰው ልጅና ለፍጥረታት ሁሉ ጥበቃ ነው፡፡
#ዛሬ የመልአኩ የቅ/ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል ከመሆኑም አንጻር የሰውን ልጅ ጠብቆት እናያለን፡፡
#እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ይሁን ብሎ በልዑል ሥልጣኑ እንደፈጠረው በይሁንታ መጠበቅ ይችላል፡፡
"ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና"
ሉቃ1፥37፡፡
#ነገር ግን እግዚአብሔር የባሕርይ ጠብቆቱን መላእክት በጸጋ እንዲሣተፉትና የሰውን ልጅ እንዲጠብቁት አድርጓል፡፡የሰው ልጅ አማኒም ይሁን መናፍቅ ደግም ይሁን ክፉ ጻድቅም ይሁን ኀጥእ በመላእክት ጠብቆት ውስጥ ጸንቶ የሚኖር ነው፡፡የሰው ልጅ አይ እኔ ኦርቶዶክስ ስላልሆንኩ የመላእክት ጠብቆት አያስፈልገኝም ሊል አይችልም፡፡ምክንያቱም የእግዚአብሔር መግቦት በሁሉም ፍጥረት ላይ ስለሆነ ነው፡፡
"በሰማያት ላለ አባታችሁ ልጆች ትሆኑ ዘንድ ጠላቶቻችሁን ውደዱ:የሚረግሟችሁንም መርቁ ለሚጠሏችሁም መልካም አድርጉ: ስለሚያሳድዷችሁም ጸልዩ:እርሱ በክፉዎችና በበጎዎች ላይ ፀሓይን ያወጣልና:በጻድቃንና በኀጢአተኛዎችም ላይ ዝናቡን ያዘንባልና። የሚወዷ፟ችሁን ብትወዱ ምን ዋጋ አላችሁ? ቀራጮችስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?:: ወንድሞቻችሁንም ብቻ እጅ ብትነሡ ምን ብልጫ ታደርጋላችሁ?አሕዛብስ ያንኑ ያደርጉ የለምን?፡፡እንግዲህ የሰማዩ አባታችሁ ፍጹም እንደ ሆነ እናንተ ፍጹማን ሁኑ"
ማቴ. 5:45-48
#እግዚአብሔር ለፍጡራን የሚያደርጋቸው መግቦታቱ በሙሉ የሚከናወኑ በመላእክት ተልእኮ ነው፦
ዝናሙ፣ደመናው፣ጠሉ፣ፀሐይ፣ጨረቃ፣ከዋክብት፣ነፋሳት፣መባርቅት፣ነጎድጓት...እነዚህ ሁሉ የሚመግቡን በመላእክት ተልእኮና ሥልጣን ነው፡፡ስለዚህ ዓለም በእኒዚህ መግቦት እስካለ ድረስ መላእክትን አይጠብቁኝም ማለት እኔ ከእግዚአብሔር ጠብቆትና መግቦት እልፍም ሲል በእራሴ ዓለምነት ነው የምኖር ያሰኛል፡፡
"መላእክተ ገጽንም የሚያመሰግኑ መላእክትንም በእሳት አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም በጨለማና በብርሃን አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም በውርጭና በበረድ አካል ላይ የተሾሙ መላእክትንም፡፡በውኃ ላይ በመብረቅና በነጐድጓድ ላይ የተሾሙ መላእክትንም በነፋሳት ላይ የተሾሙ መላእከተን በቁርና በውርጭ በመጾውና በክረምት በበጋና በጸደይ በምድርና በሰማይ ባሉ ነፋሳት ሁሉ ላይ የተሾሙ መላእክትን በወንዙ ሁሉ በብርሃንና በጨለማ እግዚአብሔር በባሕርይ እውቀቱ ባዘጋጃቸው በምሽትና በመንጋት ላይ የተሾሙ መላእክትን ፈጥሮአልና። የፍጥረትን ነገር ሁሉ ጻፍ ብሎ ነገረው።
ኩፋ.2፥6-7::
"ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ዑርኤል በመብረቅ በነጐድጓድ የተሾመ ነው።በሰው ቁስል የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሩፋኤል ነው፡፡ ዲያብሎስን የሚበቀለው አጋንንትንም የሚበቀላቸው ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ራጉኤል ነው።ለሰው ባደረገው በጎነት ላይ ለሕዝቡ ታዛዥ ነውና ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ሚካኤል ነው።በባቦች ላይ በገነትም ባሉ ጻድቃን ላይ በኪሩቤልም ላይ የተሾመ ከከበሩ ከመላእክት አንዱ ገብርኤል ነው።
ሄኖ.6:2-7::
"አንዱም አንዱም በየወገናቸው እንዳሉ አንዱም አንዱ በየዘመናቸውና በየሥልጣናቸው አንዱም አንዱም በየመውጫቸውና በየስማቸው ከኔ ጋራ ያለ መሪያቸው የሚሆን የከበረ መልአኩ ዑርኤል ባሳየኝ በየወራታቸውም ጸንተው እንዲኖሩ የሚናገር መጽሐፍ ይህ ነው።
ሄኖ.21:2::
#ስለዚህ መላእክት ለሰው ልጅ በሁለተናው የሚጠብቁት ናቸው፦
ከእሳት ሲገባ አብረው ገብተው አድነውታል፡፡ከአንበሳ አፍ አድነውታል፡፡ባሕር ከፍለውለታል፡፡ከጠላት ጋር ተዋግውለታል፡፡ትንቢት ተናግረውለታል፡፡ራዕዮችን ሕልሞችን ተርጉመውለታል፡፡የክርስቶስን ሰው መሆን አብሥረውታል፡፡የክርስቶስን ልደት አብሥረውታል፡፡በጎል አብረውት አመስገነዋል፡፡በሥደት አብረው ተሰደዋል፡፡ሚጠቱን ነግረውታል፡፡በገዳም አገልገለውታል፡፡ትንሳኤውን እርገቱን አብሥረውታል፡፡ዳግም ምጽአቱን ነግረውታል፡፡ከእስርቤት አውጥተውታል፡፡ከሰይፍ አድነውታል፡፡
አጠቃላይ መላእክት ለሰው ልጅ ለደስታውም ለመከራውም በዓለ ወጎች ናቸው፡፡ስለዚህ ሰው ከመላእክት ጠብቆት መራቅ ፈጽሞ አይችለም፡፡
"ሁሉ መዳንን ይወርሱ ዘንድ ስላላቸው ለማገዝ የሚላኩ የሚያገለግሉም መናፍስት አይደሉምን??"
ዕብ.1:14::
"ከነዚህ ከታናናሾቹ አንዱን እንዳትንቁ ተጠንቀቁ፡፡ መላእክታቸው በሰማያት ዘወትር በሰማያት ያለውን የአባቴን ፊት ያያሉ እላችኋለሁና"
ማቴ.18:10፡፡
"በዚያም ዘመን ስለሕዝብህ ልጆች የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሣል:ሕዝብም ከሆነ ዠምሮ እስከዚያ ዘመን ድረስ እንደ እርሱ ያለ ያልሆነ የመከራ ዘመን ይሆናል:በዚያም ዘመን በመጽሐፉ ተጽፎ የተገኘው ሕዝብህ ሁሉ እያንዳንዱ ይድናል"
ትን.ዳን.12:1::
"እንሆም:የጌታ መልአክ ቀረበ በቤትም ውስጥ ብርሃን በራ:ጴጥሮስንም ጐድኑን መቶ፟ አነቃውና ፦ ፈጥነህ ተነሣ አለው።ሰንሰለቶቹም ከእጁ ወደቁ። መልአኩም፦ታጠቅና ጫማህን አግባ አለው፡ እንዲሁም አደረገ"
ሐዋ.12:7-8::
#የክርስቶስ ሰው መሆን መጸነስ፣መወለድ፡መሠደድ፡መጠመቅ ማስተማር፣ሕግ መሥራት፣መሰቀል፣መሞት፣መቀበር፡መነሳት ማረግ፣ዳግም፡መምጣት ለሰው ልጅ እንደሆነ ሁሉ የመላእክትም ጥበቃ ለሁሉም ፍጥረት ነው፡፡
ስለዚህ ከመላእክት ጠብቆት ፈጽሞ መውጣት አይቻልምና የመላእክት በዓል ማክበር ለክርስትና ብቻ ሳይሆን ለሰው ልጅ በሙሉ ነው፡፡
✞ ቅዱስ ገብር እንደ ሠለስቱ ደቂቅ እኛንም ከሦስት ነገር ይጠበቀን፦
☞ ዳያብሎስ!!! ☞ ስስእት!!!
☞ ኃጢአት!!! ☞ ፍቀረ ንዋይ!!!
☞ ፍዳ ሞት!!! ☞ ትእቢት!!!
❖እናመልከው ዘንድ ለፈጠረን እግዚአብሔር ምስጋና ይግባው እንላለን!!!
❖አ.ዘ.ያዕቆብ፡፡
© ጌዴዎን ዘለዓለም፡፡
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት
አሁኑ ጊዜ ‹‹ሃይማኖት እንጂ ሥርዓት አያድንም! በሚል ፈሊጥ እምነቱን ፍጻሜ የሚሰጠውና በሥራ የሚያስተረገመው ሥርዓትና ቀኖና በምን አለበት» አዘናጊ ብሂል ፈተና ሲገጥመው ይታያል፡፡ እውነታው እንዲህ እንዳልሆነና በእንዴት ያሉ ደጋግ አበው፣ በመቼ ጊዜና ቦታ፣ በምን ምክንያትና ምን ዐላማን ለማሳካት እንደ ተጻፈ በዚህ መጽሐፍ እንረዳለን፡፡ መጽሐፉ ብሔራውያን ምንጮች ከውጭ ቅጂዎች በማስተናበር የተጻፈ በመሆኑ የቤተ ክርስቲያናችንን ያልተፋለሰና ያልተቋረጠ የእምነትና የሥርዓተ አምልኮ ጥንታዊነት በውስጥም በአፍአም ማስረጃ ያረጋግጥልናል። እያንዳንዱ ጉባኤ የተደረገበትን፣ የእያንዳንዱን ጉባኤ አናቅጽ ይዘት፣ የድንጋጌያቸውን ምክንያት፣ በጉባኤያቱ የነበሩ ተሳታፊዎችን ማንነትና ከጉባኤው በኋላ የነበረውን የአፈጻጸም ሁኔታ፣ በጉባኤው ሂደትና አፈጻጸም ያጋጠመውን ፈተና፣ የጉባኤያቱ ዓይነት፣ ያነጋገሩትን ጭብጦች፡ ያላስማሙትን ቁልፍ ቃላትና ሌሎችም ተያያዥ ሃይማኖታውያንና ታሪካውያን ሁነቶች መጥኖ አቅርቧል፡፡ እንደዚህ ያለ ታሪክንና ዐውድን ያገናዘበ አቀራረብ፡- ቃለ ሃይማኖትንና ሥርዓትን ቀዳምያኑ ሠሪዎች (ሐጋጊዎች) ባፀደቁበት ዐውድና በእኛ የዛሬ መረዳት መካከል የሚኖረውን ክፍተት በመሙላት ረገድ ዐቢይ ድርሻ ይኖረዋል፡፡ የምንጩ ልሳነ ብዙኅ መሆን የቲዎሎጂ መምህራንና ተማሪዎች ከአብነቶቹ ያላቸውን ተዋሥኦ ያዳብራል፡፡ የወንድማችን የዲያቆን አዶንያስ ብርሃነ ‹የቤተ ክርስቲያን ጉባኤዎች» መጽሐፍ ለዚህ ተዋሥኦና ጥናት ብዙ ርቀት የሚያስጉዝ ስንቅ እንደሆነ ይሰማኛል፡፡ ከኢየሩሳሌሙ የሐዋርያት ጉባኤ እስከ ቊስጥንጥንያ የነበሩትን ጉባኤያት በግሩም አቀራረብ ቃኝቶ በመልካም ትርጓሜ አቅርቦልናል፡፡ መልካም ንባብ!
በአማን ነጸረ
ደብተራና የሕግ ባለሙያ
በግዮን መጻሕፍት ታገኙታላችሁ።
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
#የተባረከች_አይን የእግዚሐብሔርን ቃል በማንበብ ትጠመዳለች
#የተባረከች_ጆሮ የንስሀ መዝሙር በመስማት እራሷን ታንጻለች
#የተባረከ_ጉሮሮ ላይ የተቀደሰ ውሀ ይንቆረቆርበታል
#የተባረከች_ምላስ የአምላኳን ስጋና ደምን ትቀበላለች
#የተባረከ_አንደበት ላይ እግዚሐብሔር ይመስገን የሚል ቃል አይጠፋበትም
#የተባረከች_አንገት የአምልኮ ደም የፈሰሰበትን ቅዱስ መስቀል ትሸከማለች
#የተባረከች_ልብ ኢየሱስን እስከ እናቱ አንግሳ በፍቅር ትሞላለች
#የተባረከች_እጅ የቀረበላትን ምግብ በአምልኮ ስም ትባርካለች
#የተባረከች_እግር ጠዋትና ማታ የአምላኳን መቅደስ ትረግጣለች
"እኔ እግዚሐብኤር አምላካቹ ነኝና ሰውነታችሁን ቀድሱ ቅዱስም ሁኑ እኔ ቅዱስ ነኝና" ዘሌ. 11፥44
#አቡነ_ሺኖዳ_ሣልሳዊ
"መናፍቃንን እንደ መዶሻ የቀጠቀጣቸው ፣ እንደ ሰም ያቀለጣቸው ፣ እንደ እሳት ያቃጠላቸው ፣ እንደ ገለባ ያበጠራቸው።" መጽሐፍ በድጋሚ ለ17 ተኛ ጊዜ ታተመ።
"መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፩" ይህን መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
ለበለጠ መረጃ
0912198891
0913083816
"መናፍቃንን እንደ መዶሻ የቀጠቀጣቸው ፣ እንደ ሰም ያቀለጣቸው ፣ እንደ እሳት ያቃጠላቸው ፣ እንደ ገለባ ያበጠራቸው።" መጽሐፍ በድጋሚ ለ17 ተኛ ጊዜ ታተመ።
"መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፩" ይህን መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
ለበለጠ መረጃ
0912198881
0913083816
"መናፍቃንን እንደ መዶሻ የቀጠቀጣቸው ፣ እንደ ሰም ያቀለጣቸው ፣ እንደ እሳት ያቃጠላቸው ፣ እንደ ገለባ ያበጠራቸው።" መጽሐፍ በድጋሚ ለ17 ተኛ ጊዜ ታተመ።
"መድሎተ ጽድቅ ቅጽ ፩" ይህን መጽሐፍ በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
ለበለጠ መረጃ
0912198881
0913083816
ቃና ዘገሊላ መጽሐፍ ለ11ኛ ጊዜ ታተመ።
"የዮሐንስ ወንጌል ምዕራፍ ሁለትን የመጀመሪያ አንቀጽ መነሻ ያደረገችውና በሰርግ ቤቱ ስም ቃና ዘገሊላ በማለት የተሰየመ ይህ መጽሐፍ፥ እንደ ሰርግ ቤቱ ስድስት ጋኖች በስድስት ምዕራፎች የተከፈለ ነው። ሁለት ወይም ሦስት እንስራ ይይዝ እንደነበሩት እንደ ቃና ጋኖችም እነዚህ ምዕራፎች እያንዳንዳቸው ሦስት ወይም አራት የንዑስ ርዕስ እንስራን የያዙ ናቸው፡፡ ...
"ይህ መጽሐፍ በስድስቱ ጋኖች /ምዕራፎች/ ውስጥ በቤተ ክርስቲያናችን ሊቃውንት ትርጓሜ መነሻነት በሰርግ ቤቱ ውስጥ ጥቂት እንድንቆይ ለማድረግ ይተጋል፡፡ .….
"እንኪያስ እኛም በኄኖክ መሪነት በቃና ዘገሊላ ሰርግ ቤት ውስጥ እንድንመላለስ፣ ከጌታችንና ከሐዋርያቱ ጋር ወደ ሰርግ ቤቱ እንድንገባ፣ ወደ ጓዳ ዘልቀን የወይኑን ማለቅ አስበን እንድንጨነቅ፣ እመቤታችን ስታማልድ ልጇም ሲማለድ እንድናይ፣ ከአገልጋዮቹ ጋር ውኃ ልንቀዳ ወንዝ እንድንወርድ፣ አብረን ውኃውን እስከአፉ ሞልተን ጌታችን የሚያደርገውን እንድንመለከት፣ ከታዳሚዎች ጋር ወይን የሆነውን ውኃ ቀምሰን እንድናደንቅ፣ መልካሙ የወይን ጠጅ ምነው እስካሁን ቆየ? ብለን ከአሳዳሪው ጋር አብረን እንድንቆጭ፣ ከዚያም ከሐዋርያቱ ጋር በስሙ አምነን ከሰርግ ቤቱ እንድንወጣ፣ ከምድራዊው ሰርግ ቤት ወጥተንም ወደ የቤታችን ሳንገባ ወደ ሌላ ሰማያዊ ሰርግ እንድንታደም ይህን ግሩም መጽሐፍ እናንብብ፡፡...
____
በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፎቶችን ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኛላችሁ።
ለበለጠ መረጃ በ0912198891/0913083816 ይደውሉ።
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
ወዳጄ ሆይ
የትዕቢት መርዝ ተጠራቅሞ አብጦብሃልን? እንኪያስ ወደ #ቅዱስ_ሥጋዉና_ክቡር_ደሙ ቅረብ፤ ስለ ወዳጆቹ ሲል አርአያ ገብርን የነሣ ትሑቱ ጌታም ትሕትናን ያስተምርሃል፡፡
የስግብግብነት ትኩሳት አስቸግሮሃልን? ወደ #ቅዱስ_ሥጋዉና_ክቡር_ደሙ ቅረብ፤ ደግነትንም ትማራለህ፡፡
የምቀኝነት ብርድ አስቸግሮሃልን? እንኪያስ ወደ #ሰማያዊው_መዓድ ቅረብ፤ ምህረት ማድረግንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡
ትዕግሥትን የማጣት እከክ ይዞሃልን? እንኪያስ ወደ #ቅዱስ_ሥጋዉና_ክቡር_ደሙ ቅረብ፤ ራስን መግዛትንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡ በመንፈሳዊ ሕይወትህ ልል ዘሊል ብትሆን ይህን #መንፈሳዊ_መዓድ ተመገብና ብርቱ ትሆናለህ፡፡
ቆሽሸሃልን? እንኪያስ ወደዚሁ መብልና መጠጥ ቅረብ ብዬ እመክርሃለሁ፤ ንጽሕናንም ገንዘብ ታደርጋለህ፡፡”
#ቅዱስ_ቄርሎስ_ዘእስክንድርያ
የትቤ ተዋሕዶ ይዘቶች
ጸሐፊ፦ መ/ር መዝገበ ቃል ገብረ ሕይወት
የገጽ ብዛት፦ 200
ትቤ ተዋሕዶ ፲፮ የሚያህሉ የተዋሕዶ ዓይነቶችን እንደ ዐቢይ ጉዳይ በመያዝ በሌሎች ንኡሳን አርእስቶችና ዝርዝር ይዘቶች ተዋቅሮ የቀረበ መጽሐፍ ነው፡፡ ዐቢይ ይዘቱና የአሳቡ ማእከል ስለ ተዋሕዶ ሆኖ መዘርዝር ነጥቦችን ሳናካትት ዐበይት ይዘቶቹ የሚከተሉት የተዋሕዶ ዓይነቶች ናቸው፦
፩. የህልውና ተዋሕዶ (ያለ አካላት መጠፋፋት የሦስቱ አካላት የአንዱ በአንዱ መኖር)
፪. የፈቃድ ተዋሕዶ (ሦስቱ አካላት በአንድ ልብ አስበው የሚፈቅዱት አንድ ፈቃድ)
፫. የፍቅር ተዋሕዶ (አንዱ አካል አንዱን አካል የሚወድበት ፍቅረ ባሕረይ፣ ፍቅረ ተዋሕዶ፣ ፍቅረ ህልውና)
፬. የሕይወት ተዋሕዶ (የመላእክት በመንፈስ ቅዱስ ሕይወትነት መኖር)
፭. የዐራቱ ባሕርያት ተዋሕዶ (በፍጥረት አካል ውስጥና በየሚኖሩበት ዓለም ጸንቶና ተስማምቶ መኖር)
፮. የሰው ተዋሕዶ ፩ኛ የሥጋ አካል የሆኑት የ፬ቱ ባሕርያት ተዋሕዶ ፪ኛ የነፍስና የሥጋ ተዋሕዶ ፫ኛ ሥጋዊ ተዋሕዶ (ከልደት እስከ ሞት ከፍጥረት ጋር ያለን መስተጋብር) ፬ኛ የመንፈሳዊ ሕይወት የጸጋ ተዋሕዶ
፯. ፍቅረ እግዚአብሔር የኅድረት ተዋሕዶ
፰. ፍቅረ ቢጽ የፍቅር ተዋሕዶ
፱. የጋብቻ ተዋሕዶ (የሴትና የወንድ)
፲. መንፈሰ ረድኤት ተዋሕዶ (የነቢያት፣ የኦሪት ጻድቃን)
፲፩. የቃልና የትስብእት ተዋሕዶ (ነገረ ሥጋዌ)
፲፪. የጸጋ ተዋሕዶ (በመዓርጋተ ቅድስና የሚገኝ)
እኒህ ከላይ ከ፩ እስከ ፲፪ የዘረዘርናቸውና በሰው ተዋሕዶ እስከ ነጥብ ፬ የዘረዘርናቸውን በድምሩ ፲፮ የተዋሕዶ ዓይነቶችን በጥልቀት ይተነትናል፡፡ ጠጠር ያለ ስለሆነ ደጋግመን ማንበብ መልካም ነው፡፡
በግዮን መጻሕፍት መደብር ነባር እና አዳዲስ መጽሐፎችን ያገኛሉ።
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት
ዘመናችን ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እጅጉን ፈተና ላይ የወደቀበት, የቤተ ክርስቲያን ሥርዐቷ ባለቤት ያጣበት ጊዜ መሆኑን መናገር ለቀባሪ የማርዳት ያህል ነው፡፡ ነገሩ ሲከፋ ደግሞ የቤተ ጉባኤና የቤተ ክርስቲያንን የሥርዐት መጻሕፍት ጠቅሶ ማስተማር የሚያሳፍር : የሚመስልበት ደረጃ ላይ ደርስናል። "ጸሐፊ" እና "ሰባኪ" የሚል ስም ተሸክመው ፍትሐ ነገሥትን የመሰሉ የሥርዐት መጻሕፍትን ለመጥቀስ እንኳ ፍላጎት የሌላቸው "አገልጋዮች" እጅግ ብዙ ናቸው፡፡ ይህ ደግሞ ምእመናንን (በተለይም በከተሞችና በውጭ ሀገራት የሚኖሩትን) ለእግዚአብሔር ሥርዐት ግዴለሽ እንዲሆኑ አድርጓል። በውጤቱም ክርስትና ከተግባር ቅድስና ይልቅ ስብከትና ጽሑፍ ብቻ እንዲሆን አስገድዷል። ስለዚህም እንደዚህ ያሉ የሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት በእጅጉ ያስፈልጉናል። ይህ መጽሐፍ ኹሉንም የቤተ ክርስቲያኗን ሥርዐቶች ለማካተት ይዘቱ፤ መጠኑ ባይፈቅድም ወሳኝ የሚባሉትን ነጥቦች በጥያቄና መልስ እያሰናሰለ ይዟል፡፡ ትኩረቱን ደግሞ በተለይ የዘመናችን የሥርዐት ክፍተት የሚታይባቸው የቅዳሴ፤ የቤተ ክርስቲያን ዙሪያና መሰል ጉዳዮች ላይ አድርጓል። ጸሐፊው፦ መምህር አብርሃም ከልጅነታቸው ተምረው በዜማ፤ በቅኔና በመጻሕፍተ ትርጓሜ የበሰለ አእምሮ ከጥሩ ብዕር ጋር ያላቸው ናቸውና ለዚህ የመጀመሪያ የጽሑፍ ሥራቸው መርቀናቸዋል። ቀጥሎም መሰል መጻሕፍትን ከመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የተነሣ ከትበው ያበረክቱልናል የሚል ተስፋ አለን፡፡
ዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ
በግዮን መጻሕፍት ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ
ወደ ገላትያ ሰዎች
የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ሐተታ
እኛ ዘንድ ከዘወትር ልዩ ቅናሽ ጋር ያገኙታል።
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት
አሐቲ ድንግል ለ3 ግዜ ታትሞ ወቷል
በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት
አሐቲ ድንግል ለ3 ግዜ ታትሞ ወቷል በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት
አሐቲ ድንግል ለ3 ግዜ ታትሞ ወቷል በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
#ዜና-ድጋሚ-ኅትመት
አሐቲ ድንግል ለ3 ግዜ ታትሞ ወቷል
በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
#ዜና_መጽሐፍ
"ከኖኅ ጥፋት ውኃ በስተጀርባ" የተሰኘው የዲ/ን ዶ/ር አብነት ተስፋ መጽሐፍ ታተመ።
መጽሐፉ፥ በሰባት ምዕራፍ እና በ480 ገጾች የቀረበ ሲሆን፥ በኦሪት ዘፍጥረት ምእራፍ 6-9 ላይ ባለው በአንድ ወቅት ዓለም በመላው በመቅሰፍት ጎርፍ ስለ ጠፋበት በኖኅ ዘመን ስለ ተፈጠረው ታሪክ የሚያትት ነው። ምንም እንኳን ታሪኩ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አራት ምዕራፎችን የሸፈነ ቢሆንም፥ በአስተውሎት ከተመለከትነው ግን እጅግ ሰፊ ሐሳቦችን ያረገዘ ነው። በተለይ ከዘመናዊ ትምህርት አንጻር ሊታዩ ፣ ሊመረመሩ ፣ ሊተረጎሙ የሚገባቸው ግሩማን ሐሳቦች አሉበት። ስለዚህም ለእነዚህ ሐሳቦች ሐተታ ለመስጠት መጽሐፉ ''ከኖኅ ጥፋት ውኃ በስተጀርባ'' የሥነ ምሕንድስና (Engineering) ፣ የህክምና ጥበብ ፣ የሥነ ምድር ሳይንስ (Geology) ፣ ሥነ ምድራዊ ፊዚክስ (Geophysics) ፣ የእንስሳት ሥነ ምደባ (Animal Taxonomy) , . . . . . በሮች ያንኳኳል። በተጨማሪ በነገረ አበው ውስጥ ዘልቆ የአባቶችን ድንቅ ትንታኔ ያስቃኛል። ለምግባር እና ለትሩፋት የሚሆኑ ድንቅ የምክር ቋጠሯቸውን ከየመጻፎቻቸው እየፈታ ያቋድሳል። በታሪኩ ውስጥ የተገለጡ ዐበይት ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን (ነገረ ክርስቶስ ፣ ምሥጢረ ጥምቀት ፣ ነገረ መንፈስ ቅዱስ ፣ . . .) ይዳስሳል። ከሁሉም ዓይነት ሊቋደሱበት የሚገባ ቡፌ ሆኖ በ480 ገጽ እና በ650 ብር የሽፋን ዋጋ ተሰናድቶ ለአንባቢያን ቀርቦአል።
በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ።
#ዜና_መጽሐፍ
"ከኖኅ ጥፋት ውኃ በስተጀርባ" የተሰኘው የዲ/ን ዶ/ር አብነት ተስፋ መጽሐፍ ታተመ።
መጽሐፉ፥ በሰባት ምዕራፍ እና በ480 ገጾች የቀረበ ሲሆን፥ በኦሪት ዘፍጥረት ምእራፍ 6-9 ላይ ባለው በአንድ ወቅት ዓለም በመላው በመቅሰፍት ጎርፍ ስለ ጠፋበት በኖኅ ዘመን ስለ ተፈጠረው ታሪክ የሚያትት ነው። ምንም እንኳን ታሪኩ መጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አራት ምዕራፎችን የሸፈነ ቢሆንም፥ በአስተውሎት ከተመለከትነው ግን እጅግ ሰፊ ሐሳቦችን ያረገዘ ነው። በተለይ ከዘመናዊ ትምህርት አንጻር ሊታዩ ፣ ሊመረመሩ ፣ ሊተረጎሙ የሚገባቸው ግሩማን ሐሳቦች አሉበት። ስለዚህም ለእነዚህ ሐሳቦች ሐተታ ለመስጠት መጽሐፉ ''ከኖኅ ጥፋት ውኃ በስተጀርባ'' የሥነ ምሕንድስና (Engineering) ፣ የህክምና ጥበብ ፣ የሥነ ምድር ሳይንስ (Geology) ፣ ሥነ ምድራዊ ፊዚክስ (Geophysics) ፣ የእንስሳት ሥነ ምደባ (Animal Taxonomy) , . . . . . በሮች ያንኳኳል። በተጨማሪ በነገረ አበው ውስጥ ዘልቆ የአባቶችን ድንቅ ትንታኔ ያስቃኛል። ለምግባር እና ለትሩፋት የሚሆኑ ድንቅ የምክር ቋጠሯቸውን ከየመጻፎቻቸው እየፈታ ያቋድሳል። በታሪኩ ውስጥ የተገለጡ ዐበይት ሃይማኖታዊ ጉዳዮችን (ነገረ ክርስቶስ ፣ ምሥጢረ ጥምቀት ፣ ነገረ መንፈስ ቅዱስ ፣ . . .) ይዳስሳል። ከሁሉም ዓይነት ሊቋደሱበት የሚገባ ቡፌ ሆኖ በ480 ገጽ እና በ650 ብር የሽፋን ዋጋ ተሰናድቶ ለአንባቢያን ቀርቦአል።
በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
ኅዳር ጽዮን
"ጽዮን" ማለት "ጸወን አምባ፣ መጠጊያ" ማለት ነው:: ጽዮን የሚለው ስም በቁሙ ለቅዱስ ዳዊት ተራራና ለኪዳኑ ጽላት ሲያገለግል በትንቢታዊ ምሥጢሩ ግን ለድንግል ማርያም፣ ለቤተ ክርስቲያንና ለዘለዓለማዊት ርስት ያገለግላል፡፡
ኅዳር ፳፩ ቀን በታቦተ ጽዮን የተፈጸሙ ታላላቅ ተአምራት የሚታሰቡበት ቀን ነው፡፡ በዚህ ቀን ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን የታቦተ ጽዮንን ተአምራት እግዚአብሔር ቃል ቅድስት ድንግል ማርያምን ታቦቱ አድርጎ ከፈጸማቸው ታላላቅ የድኅነት ሥራዎች ጋር በማነጻጸር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በነገረ ድኅነት ውስጥ ያላትን ድርሻ በስፋት ታስተምራለች፡፡
ነቢዩ ሙሴ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጸልዮና ጹሞ ዐሥርቱ ቃላት የተጻፈበትን ጽላት ከእግዚአብሔር የቃል ኪዳኑን ታቦት ‹ታቦተ ጽዮንን› እንደተቀበለ መጽሐፍ ቅዱስ ይገልጻል፡፡
ታቦተ ጽዮን ከማይነቅዝ እንጨት የተቀረጸችበት ምክንያት የእመቤታችን ድንግል ማርያምን ንጽሕና ለማመልከት ነው፡፡ በውስጥም በውጪም በጥሩ ወርቅ የተለበጠች መሆኗ ደግሞ የእመቤታችን ድንግል ማርያም ቅድስናዋንና በሁለት ወገን ድንግል የመሆኗ ምሳሌ ነው፡፡
ንጉሥ ዳዊት የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት ከአቢዳራ ቤት ወደ ጽዮን ከተማ ባስመጣበት ወቅት በታቦቷ ፊት በሙሉ ኃይሉ በደስታ እየዘለለ ለእግዚአብሔር በዝማሬ ምስጋና አቅርቧል፡፡ ‹‹ለንጉሥ ዳዊትም “እግዚአብሔር የአቢዳራ ቤት የነበረውን ሁሉ ስለ እግዚአብሔር ታቦት ባረከ” ብለው ነገሩት፡፡
ዳዊትም ሄዶ የእግዚአብሔርን ታቦት ከአቢዳራ ቤት ወደ ራሱ ከተማ በደስታ አመጣት፡፡ ከእርሱም ጋር የእግዚአብሔርን ታቦት የተሸከሙ ሰባት መሰንቆ የሚመቱ መዘምራን ነበሩ፤ በሬዎችንና በጎችን ይሠዉ ነበር፡፡ ዳዊትም በእግዚአብሔር ፊት በገና ይደረድር ነበር›› እንዲል፤ ነቢዩ ዳዊት በቃል ኪዳኑ ታቦት ፊት የተቀኘው ለሰው ልጆች ሁሉ የመዳናችን ምክንያት የሆነችውን ቅድስት ድንግል ማርያምንና ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሲያመስገን ነው፡፡ (፪ሳሙ.፮፥፲፪-፲፬)
ታቦተ ጽዮን እስራኤል የዮርዳኖስን ባሕር ለመሻገር በተቸገሩ ጊዜ ነቢዩ ኢያሱ እግዚአብሔር አምላክ በነገረው መሠረት ካህናቱ የቃል ኪዳኑን ታቦት ይዘው በሕዝቡ ፊት ወደ ዮርዳኖስ እንዲሄዱ ነገራቸው፤ እነርሱም እንደታዘዙት አደረጉ፤ ታቦቱን የተሸከሙት የካህናቱ እግሮች በውኃው ዳር ሲጠልቁ ከላይ የሚወርደው ውኃ ቆመ፤ የእግዚአብሔርን የቃል ኪዳን ታቦት የተሸከሙ ካህናት በዮርዳኖስ መካከል በደረቅ መሬት ጸንተው ቆመው ነበር፤ ሕዝቡም ሁሉ ዮርዳኖስን ፈጽመው እስኪሻገሩ ድረስ እስራኤል ሁሉ በደረቅ መሬት ተሻገሩ፡፡ (ኢያ. ፫፥፩-፲፯)
እስራኤላውያን በመካከላቸው የቃል ኪዳኑ ታቦት በያዙ ቁጥር በጦርነታቸው ሁል ጊዜ ያሸንፉ ነበሩ፡፡ ነገር ግን ልዑል እግዚአብሔር ሕዝበ እስራኤል ስለበደሉት እንዲሁም የኤሊ ልጆች አፍኒንና ፊንሐስ በደላቸውና ክፋታቸው ስለበዛ ታቦተ ጽዮን ተማርካ ወደ ፍልስጥኤም ሄደች፡፡ በዚያ በአሕዛብ ምድርም ልዩ ልዩ ተአምራትን እያደረገች ፍልስጥኤማውያንን ስለአስጨነቀቻቸው የፍልስጥኤማውያን አለቆች የቃልኪዳኑን ታቦት ልዩ ልዩ ገጸ በረከቶችን አስይዘው ወደመጣችበት በሠረገላ አድርገው በክብር ሸኝተዋታል፡፡ (፩ኛ.ሳሙ. ፭፥፩-፲፭)
ሀገራችን ኢትዮጵያም በንግሥተ ሳባ አማካኝነት ለታቦተ ጽዮን መቀመጫ እንድትሆን የእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኗል፡፡ ይህም እንዲህ ነበር፤ ንግሥተ ሳባ የንጉሥ ሰሎሞንን ጥበብ ለማድነቅ ምድረ እስራኤል ድረስ መጓዟን ተከትሎ ከንጉሡ ቀዳማዊ ምኒልክን ፀነሰች፡፡
ቀዳማዊ ምኒልክ ከአደገ በኋላ አባቱን ሊጠይቅ ሂዶ ወደ ኢትዮጵያ ሲመለስ አብረውት አንድ ሺህ ሁለት መቶ እስራኤላውያን የበኩር ልጆች፣ ሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት በአዛርያስ የሚመሩ ሌዋውያን ካህናትም አብረውት ለጉዞ ተነሡ፡፡ የብሉይ ኪዳን መጻሕፍትንና ሌሎች በርካታ ቁሳቁሶችን ይዘውም ነበር።
ነገር ግን ታቦተ ጽዮንን አዛርያስና ካህናቱ ተማክረው ቀዳማዊ ምኒልክ እንኳን ሳይሰማ በምሥጢር ይዘዋት ሊመጡ ተስማሙ፡፡ ዕቅዳቸውን ለማሳካት በታቦተ ጽዮን አምሳያ ሌላ ታቦት አዘጋጅተው ለመሄድ በሚነሡበት ዕለት ሌሊትም ወደ ቤተ መቅደስ ይዘውት ሄዱ፡፡
ከቤተ መቅደስ ሲደርሱም የእግዚአብሔር ፈቃድ ነበርና የቤተ መቅደሱ በር ተከፍቶ እና ውስጡም በብርሃን ተሞልቶ ታቦተ ጽዮንም ከመንበሯ በመነሣት ከፍ ብላ አገኟት። በዚህም የአምላክን ፈቃድ ተረድተውና እግዚአብሔርን እያመሰገኑ በፍጥነት ይዘዋት ወጡ፡፡ በአምሳያዋ የሠሩትንም ቅርፅ በመንበሩ ላይ አስቀምጠው ሄዱ።
የንጉሡ ወታደሮች በፍጥነት ቢጓዙም ቀዳማዊ ምኒልክ እና አዛርያስ ታቦተ ጽዮንን ይዘው ሲጓዙ እጅግ ፍጣን ስለበር ሊደርሱባቸው አልቻሉም። መጽሐፈ ክብረ ነገሥት ይህንን ሲጠቅስ ‹‹ከመሬት አንድ ክንድ ያህል ከፍ ብለው ይሄዱ ነበር›› በማለት ይገልጸዋል። ባሕረ ኤርትራን ከተሻገሩና ግብፅ ከደረሱ በኋላ ዕረፍትን ባደረጉ ጊዜ አዛርያስ ለቀዳማዊ ምኒልክ ታቦተ ጽዮንን ይዘዋት እንደመጡ ነገረው፡፡
አያይዞም ‹‹አንተም ብትሻ ታቦቷንም ወደ ሀገሯ ልመልሳት ብትል አትችልም፤ አባትህ ሰሎሞንም ሊወስዳት ቢመጣ አይሆንለትም›› አለው። ከቦታ ቦታ ይዣት እንቀሳቀሳለው ቢልም ያለ ፈቃዷ ምንም እንደማያደርግና ሁሉ ነገር በአምላክ መልካም ፈቃድ እንደሚፈጸም ነገረው። ቀዳማዊው ምኒልክም ይህን ሲሰማ ተደሰተ፤ ሕዝቡና ሠራዊቱ በሙሉ ልዑል እግዚአብሔርን አመሰገኑ፤ ከግብፅ ምድር ወጥተው እስከ ኢትዮጵያ በታላቅ እልልታና ሆታ እግዚአብሔርን እያመሰገኑ መጡ።
ኅዳር ፳፩ ቀን አክሱም በደረሱ ጊዜም እናቱ ንግሥተ ሳባ ተቀበለችው፤ ደስታና እልልታውን ተመልክታ ያገኙት ነገር እንዳለ ብትጠይቀው ታቦተ ጽዮንን እንዳመጧት ነገራት፡፡ የእርሷም ደስታ እጥፍ ድርብ ሆነ። ታቦቷንም በርእሰ አድባራት ወገዳማት አክሱም ጽዮን ማርያም ቤተ ክርስቲያን አስቀመጡአት፡፡
ከዚያም ዘመን ጀምሮ በየዓመቱ ኅዳር ፳፩ ቀን ብዙ ምክንያቶች ቢኖሩም በታቦተ ጽዮን የተፈጸሙ ታላላቅ ተአምራትን በማሰብ ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ታከብራለች፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
ምንጭ፤
ክብረ ነገሥት ተርጓሚ ሥርግው ገላው (1994 ዓ.ም)
መዝገበ ታሪክ ቊጥር 1 (መምህር ኅሩይ ኤርምያስ)
Endi mavjud! Telegram Tadqiqoti 2025 — yilning asosiy insaytlari 
