en
Feedback
🎤ሙስጠፋ (አቡ ዐብዱረህማን)✍

🎤ሙስጠፋ (አቡ ዐብዱረህማን)✍

Open in Telegram

@በእውቀት መስራትና መናገርን የተገጠመ ታድሏል!!!

Show more
1 940
Subscribers
No data24 hours
-57 days
-1730 days

Data loading in progress...

Tags Cloud
No data
Any problems? Please refresh the page or contact our support manager.
Incoming and Outgoing Mentions
---
---
---
---
---
---
Attracting Subscribers
April '25
April '25
+14
in 0 channels
March '25
+35
in 0 channels
Get PRO
February '25
+24
in 0 channels
Get PRO
January '25
+40
in 9 channels
Get PRO
December '24
+48
in 3 channels
Get PRO
November '24
+39
in 1 channels
Get PRO
October '24
+43
in 3 channels
Get PRO
September '24
+178
in 13 channels
Get PRO
August '24
+389
in 31 channels
Get PRO
July '24
+39
in 1 channels
Get PRO
June '24
+32
in 1 channels
Get PRO
May '24
+54
in 4 channels
Get PRO
April '24
+58
in 3 channels
Get PRO
March '24
+132
in 12 channels
Get PRO
February '24
+303
in 30 channels
Get PRO
January '24
+158
in 21 channels
Get PRO
December '23
+92
in 10 channels
Get PRO
November '23
+192
in 25 channels
Get PRO
October '23
+161
in 14 channels
Get PRO
September '23
+186
in 0 channels
Get PRO
August '23
+126
in 0 channels
Get PRO
July '23
+21
in 0 channels
Get PRO
June '23
+26
in 0 channels
Get PRO
May '23
+50
in 0 channels
Get PRO
April '23
+10
in 0 channels
Get PRO
March '23
+11
in 0 channels
Get PRO
February '23
+6
in 0 channels
Get PRO
January '23
+19
in 0 channels
Get PRO
December '22
+44
in 0 channels
Get PRO
November '22
+26
in 0 channels
Get PRO
October '22
+53
in 0 channels
Get PRO
September '22
+29
in 0 channels
Get PRO
August '22
+31
in 0 channels
Get PRO
July '22
+51
in 0 channels
Get PRO
June '22
+149
in 0 channels
Get PRO
May '22
+120
in 0 channels
Get PRO
April '22
+53
in 0 channels
Get PRO
March '22
+159
in 0 channels
Get PRO
February '22
+119
in 0 channels
Get PRO
January '22
+302
in 0 channels
Date
Subscriber Growth
Mentions
Channels
18 April0
17 April0
16 April+1
15 April0
14 April0
13 April+2
12 April+2
11 April0
10 April+2
09 April0
08 April+4
07 April0
06 April0
05 April+1
04 April0
03 April+1
02 April+1
01 April0
Channel Posts
አሁን ቀጥታ ስርጭት ስልጤ ዞን አልቾ ወረዳ ገድራት ቀበሌ አል አቅሳ መስጅድ ሀገር አቀፍ የዳዕዋ ፕሮግራም በሸይኽ አብድልሃሚድ አል ለተሚ https://t.me/medresetulislah

2
🔷  ልብ እንደ ድስት ነው በያዘው ነገር ይንተከተካል ። قال يحيى بن معاذ – رحمه الله – : "  القلوب كالقدور تغلي بما فيها ، وألسنتها مغارفها ، فانظر إلى الرجل حين يتكلم فإن لسانه يغترف لك بما في قلبه ، حلو وحامض ، وعذب وأجاج ، وغير ذلك ، ويبين لك طعم قلبه اغتراف لسانه ، أي كما تطعم بلسانك طعم ما في القدور من الطعام فتدرك العلم بحقيقته ، كذلك تطعم ما في قلب الرجل من لسانه ، فتذوق ما في قلبه من لسانه ، كما تذوق ما في القدر بلسانك ".            الجواب الكافي   ص ( 159 ) 🔹 የሕያ ኢብኑ ሙዓዝ የተባለ ሊቅ ስለ አንድ ሰው ልብ ሲናገር እንዲህ ይላል : – " ልብ እንደ ድስት ነው በያዘው ነገር ይንተከተካል ። ምላስ ጭልፋው ነው ። አንድን ሰው ሲናገር አዳምጠው ምላሱ ልቡ ውስጥ ካለው እየጨለፈ ነው ።     ጣፋጭ,  የተበላሽ , ለዛ ያለው,  ጨዋማ ( ጎምዛዛ ) የመሳሰሉት,  የልቡን ቃና ምላሱ ይገልፅልሀል ። በምላስህ ቀምሰህ ድስት ውስጥ ያለውን ምግብ ቃና እንደምታውቀው ሁሉ በሰውየው ልብ ያለውን ደግሞ በምላሱ ታውቀዋለህ ። በልቡ ያለውን በምላሱ ትቀምሰዋለህ ። በድስት ያለውን በምላስህ እንደምትቀምሰው ሁሉ " ። !!!!!      🔹 እዚህ ጋር ልብ ማለት ያለብን የሕያ እየተናገረ ያለው አንድ ሰው ስለሚናገረው ነገር ነው ። የሚናገረው በልቡ ካለው ስለሆነ ነው ታውቀዋለህ የሚለው እንጂ በአንድ ሰው ልብ ውስጥ ያለውን ከአላህ ውጪ የሚያውቅ የለም ። የሕያ ግን ልብ ውስጥ ካለው ምላስ ግልፅ ያደረገውን ነው ታውቀዋለህ እያለ ያለው ይህም ቢሆን ሁሌ ልክ ይሆናል ማለት አይደለም ። ልክ ዓማር ኢብኑ ያሲር ልቡ በኢማን ተሞልቶ በምላሱ የኩፍር ቃል እንደተናገረው ሁሉ ። እንደነዚህ አይነቶቹ ክስተቶች በጣም ጥቂት ( ናዲር ) ስለሆኑና በአብዛኛው ሰው በልቡ ያለውን ስለሚናገር ነውና መልእክቱን በተዛባ መልኩ እንዳንረዳው ። https://t.me/bahruteka
447
3
https://t.me/Abdul_halim_ibnu_shayk?livestream
434
4
በስልጤ ዞን አልቾዊሪሮ ወረዳ በገድራት ቀበሌ ልዩ ልዪ ስሙ ጮል ተብሎ በሚጠራ መንደር አል አቅሳ መስጂድ።።። ከቦዦባር እና ከጠረጋ ለምትመጡ  ከጠረጋ ወደ ቃዋቆቶ በሚያስኬደዉ ፒስታ መንገድ ኩተሬ ደርሳቹ ወደ ቂልጦ በሚየስኬደዉ መንገድ ላይ ከሾሞ ወደ ግራር ትምህርት ቤት በምያስኬደዉ መንገድ ተሻግሮ ከወራቤ ለምትመጡ ወንድሞች ከወራቤ ኩተሬ ደርሳቹ ወደ ቅልጦ በምያስኬደዉ መንገድ ከሾሞ ወደ ግራር ትምህርት ቤት በምያስኬደዉ መንገድ ተሻግሮ።።።ልዪ ስሙ ጮል ይባላል
351
5
🕌  🕌 ልዩ የዳዕዋና ኮርስ ፕሮግራም       በአላህ ፈቃድ የዲን ትምህርት ድግስ ከዛሬ ጥር 9/5/2017 የጁመዓ ኹጥባና ሰላት ጀምሮ  ለተከታታይ 3 ቀናቶች ተዘጋጅቷል :: ቀናቶቹ በታላላቅ የሀገራችን  መሻይኾችና ኡስታዞች  የኮርስና የሙሃደራ ፕሮግራሞች ይደምቃሉ:: ➡️  ቦታ      በአሊቾ ዊሪሮ ወረዳ በገደራት ቀበሌ ልዪ ስሙ ጮል በተሰኘችው መንደር በአል-አቅሳ መስጂድና መድረሳ ተሰናድቶ ይጠብቃችኋል:: የፕሮግራሙ አዘጋጅ :-      የገደራት ቀበሌ አል-አቅሷ መስጂድ እና መድረሳ ማህበረሰብ እና የአካባቢው ተወላጆች ■ በዝግጅቱ ላይ ከሚገኙ ውድና ብርቅዬ መሻይኾች መካከል: ↪️  አሸይኽ ዐብዱልሐሚድ ቢን ያሲን አለተሚይ(ከለተሞ) بعنوان :-  وقفات مع سورة نوح ልዪ ቆይታ ከሱረቱ ኑህ ጋር ↪️  አሸይኽ ሙሐመድ ሀያት (ከወሎ ሐራ) دورة مكثفة في المنهج ልዩ ኮርስ በሚንሃጅ ዙሪያ 🕌 አሸይኽ ሁሰይን ከረም  (ከወሎ ሐራ) بعنوان:-الإعتصام بحبل الله ርእስ:-በአላህ ገመድ መተሳሰር ↪️   አሸይኽ ሙሐመድ ጀማል (ከኮምቦልቻ) بعنوان:-خطر البدع وأهلها في الإسلام የቢድዐ እና የቢድዐ ባለቤቶች አደጋ በእስልምና ላይ ↪️ አሸይክ ሙባረክ አልወልቂጢይ (ከወልቂጤ) بعنوان :- مجمع الشرك    የሺርክ መናሀሪያዎች  ↪️ አሸይኽ ሁሰይን  ሙሐመድ አስልጢይ  (ከአዲስ አበባ) بعنوان :- الصبر في الدعوة إلى الله    ሰብር ወደ አላህ በመጣራት ላይ ↪️ አሸይኽ መህቡብ (ከሳንኩራ)        بعنوان :- كن على بصيرة في ديك    የቻሌ የንበሪ (በስልጢኛ ቋንቋ) ↪️ አሸይኽ አወል (ከዳሎቻ) إن هذا الدين أمانة عظيمة      ዲኒ እኮ የሮሬን አማነ (በስልጥኛ ቋንቋ) 🛜   አሸይኽ አቡ ዘር (ከሱኡዲ አረቢያ) በቀጥታ ስርጭት 📜ጣፋጭ የግጥም ስንኞች በወንድማችን ኢብኑ ኑሪ ተዘጋጅተዋል በስልጥኛ በአማርኛ በአረብኛ ይደመጣሉ:: 🕌እንዲሁም በርካታ ውድና ተናፋቂ ሰለፍይ ኡስታዞች የሚታደሙበት ደማቅ ፕሮግራም ነው ። ማሳሰቢያ:-ሁላችሁም ማንነታችሁን የሚገልፅ መታወቂያ እና የማታ ልብስ እንዳትዘንጉ:: 👌የሀቅ ወዳጆች ሁሉ በአክብሮት ተጋብዛችኋል እንዳትቀሩብን‼️ 📲+251913890385 📲+251716270733 📲+251938306021 https://t.me/YeIslam_brhan_ye_ewket_maed
328
6
🟢ብልጣብልጦች አይሸዉዱን إعلم - رحمك الله- ለኢስላም የሚሰሩ የሚመስሉ ሙናፊቆች ፣ ለሱነህ ታጋይ የሚመስሉ ሙብተዲዖች ፣ ሰለፊይ መሳይ ህዝቢዮች ይኖራሉ:: በውስጣቸው ያዘሉትን አዝለው ገፅታቸውን የሚያሳምሩት ስልጣን ለመቆናጠጥ ፣ ወይም ገንዘብ ለመሰብሰብ ፣ አሊያም ሴቶችን ለማደን ፣ ወይም ሌላ ድብቅ ሴራ ቋጥረው ሊሆን ይችላል:: 👉ብልጣብልጦች ስላሸበረቁና ውርውር በማለታቸው ለላመታለል በአላህ ታግዞ መጠንቀቅ !! ከሰለፎች ንግግሮች መካከል : "لستُ بالخِبِّ ولا الخِبُّ يخدعني"  " አታላይ (ብልጣብልጥ) አይደለሁም ብልጣብልጥም አይሸውደኝም::" ከአላህ ንግግሮች ውስጥ: ﴿أَمْ حَسِبَ الَّذِينَ فِي قُلُوبِهِمْ مَرَضٌ أَنْ لَنْ يُخْرِجَ اللَّهُ أَضْغَانَهُمْ (٢٩) وَلَوْ نَشَاءُ لأرَيْنَاكَهُمْ فَلَعَرَفْتَهُمْ بِسِيمَاهُمْ وَلَتَعْرِفَنَّهُمْ فِي لَحْنِ الْقَوْلِ وَاللَّهُ يَعْلَمُ أَعْمَالَكُمْ (٣٠) (እነዚያ በልቦቻቸው ውስጥ በሽታ ያለባቸው አላህ (በውስጣቸው የቋጠሩትን) ተንኮል አያወጣው መሰላቸውን? ። ብንፈልግ እነርሱን ባመላከትንህና በምልክታቸውም በእርግጥ ባወቅሃቸው ነበር፡፡ በእርግጥ በንግግር መንጋደድ  ታውቃቸዋለህ፡፡ አላህም ሥራዎቻችሁን ያውቃል፡፡)  ( إِنَّ فِي ذَلِكَ لآيَاتٍ لِلْمُتَوَسِّمِينَ) ﴿٧٥ الحجر) (በዚህ ውስጥ በጥልቀት ለሚመለከቱ በእርግጥ መገምገሚያዎች አሉበት፡፡) 👉ሸረኞችን በምልክታቸው ማወቅና መጠንቀቅ የነቢዩ (ﷺ) እና የሰለፎች ፈለግ ነው :: ✍  ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊየህ) http://t.me/Abuhemewiya
303
7
በወርቅ የሚፃፍ ንግግር ! የህያ ኢብኑ ሙዓዝ ረሂመሁሏህ እንዲህ ይላል « القُلوب كالقُدور في الصُّدور تَغلي بما فيها، ومغارِفُها ألسِنَتُها، فانتظِر ال
በወርቅ የሚፃፍ ንግግር ! የህያ ኢብኑ ሙዓዝ ረሂመሁሏህ እንዲህ ይላል « القُلوب كالقُدور في الصُّدور تَغلي بما فيها، ومغارِفُها ألسِنَتُها، فانتظِر الرجُل حتى يتكلَّم، فإنَّ لسانَهُ يغتَرِفُ مِن قلبه، مِن بين حُلوٍ وحامِض، وعذب وأجاج يخبرك عن طعم قلبه اغتراف لسانه ” ልቦች በደረት ውስጥ እንደ ድስት ነች በውስጡ ባለው ነገር ይፍለቀለቃል መጨለፊያው ምላስ ነው አንድን ሰው እስኪናገር ጠብቀው ምላሱ ከልቡ ይጨልፍልሃል ከጣፋጩም ከጎምዛዛውም ጣፋጭ የሆነውንም ከመርጋጋው ስለ ልቡ ጠዓም በምላስ መጨለፊያው ታውቃልህ“ ኢብኑል ቀይምም የሚከተለውን ይላል ፦ በድስት ውስጥ ያለን ነገር በምላስህ ቀመሰህ ሁኔታውን እንደምታውቀው ልክ እንደዚሁ ሰውን በምላሱ ትቀምሰዋልህ በድስት ውስጥ ያለውን በምላስህ እንደምትቀምሰው " ። وَأَيْسَرُ حَرَكَاتِ الْجَوَارِحِ حَرَكَةُ اللِّسَانِ وَهِيَ أَضَرُّهَا عَلَى الْعَبْدِ. ኢብኑልቀይም ረሂመሁሏህ እንዳለው ከአካል ቀላሉ እንቅስቃሴ የምላስ እንቅስቃሴ ነው እሷ ማለት በጣም ባሪያውን የምትጎዳ ነች ። join #telegram ቻናል https://t.me/abuabdurahmen
264
8
🔴 بشرى للسلفيين. 🎙 الشيخ محمد امان الجامي رحمه الله.
🔴 بشرى للسلفيين. 🎙 الشيخ محمد امان الجامي رحمه الله.
3 224
9
https://t.me/YeIslam_brhan_ye_ewket_maed?videochat
598
10
🔹በሙኻሊፎች ላይ ምላሽ መስጠት ሰለፎች ዘንድ ትኩረት የሚሰጠው አካሄድ ነው ። ከዚህ የሚፈራው የስሜት ባልተቤት ወይም በእውቀቱ ደካማ የሆነ ቢሆን እንጂ ሌላ አይደለም ። https://t.me/bah
🔹በሙኻሊፎች ላይ ምላሽ መስጠት ሰለፎች ዘንድ ትኩረት የሚሰጠው አካሄድ ነው ። ከዚህ የሚፈራው የስሜት ባልተቤት ወይም በእውቀቱ ደካማ የሆነ ቢሆን እንጂ ሌላ አይደለም ። https://t.me/bahruteka
622
11
https://t.me/alislaahwomenonlineders?videochat
563
12
https://t.me/medresetulislah?livestream
639
13
🟢የተምዪዕ በሽታ እንዲህ ይጀምራል 🎤ከአሸይኽ ሙሀመድ አማን አልጃሚይ ፈትዋ 👉ጥፋት እና ጥፋተኛን እያዩ ኢንካር ከማድረግ (ከማስተካከል) ይልቅ ምክንያት መደርደር :: 👉የእነ አህመድ ኣደም እና ያሲን ኑር የተመዪዕ ስልት ነች:: 👉የሀገራችን ተመዩዕ በሽታ:: 👉ሰለፊይ ዑለማዎች አጥማሚዎችን እንዲህ አጋልጠው ኡማውን  በአላህ ፈቃድ ታድገዋል :: 👉የሙመይዓዎችን ፍልስፍና ትተህ በነቢዩ (ﷺ) ሀዲስ ስራ:: " مَنْ رَأَى مِنْكُمْ مُنْكَرًا فَلْيُغَيِّرْهُ بِيَدِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِلِسَانِهِ، فَإِنْ لَمْ يَسْتَطِعْ فَبِقَلْبِهِ، وَذَلِكَ أَضْعَفُ الْإِيمَانِ ". أخرجه مسلم في "صحيحه"، كتاب : الإيمان باب النهي عن المنكر من الإيمان (1/ 50) رقم (49). https://t.me/FATTAWAS
781
14
🟡ሀቅ እና ወርቅ ከሸይኹልኢስላም ኢብኑ ተይሚየህ ወርቃማ ንግግሮች قال ابن تيمية 《…فَالْحَقُّ كَالذَّهَبِ ‌الْخَالِصِ، كُلَّمَا امْتُحِنَ ازْدَادَ جَوْدَةً، وَالْبَاطِلُ كَالْمَغْشُوشِ الْمُضِيءِ، إِذَا امْتُحِنَ ظَهَرَ فَسَادُهُ.》 አላህ የወደዳት ወርቃማዋ እውነት ስትፈተን በሳት ዝቃጩን አራግፋ ኮረፉን አረፋ ጨለማውን ገፋ ጠላት አሸንፋ በተሻለ ሴራ አስመሳይ ሲጣራ ጥራቷን ጨምራ እዩ ስታበራ ሀቅን እንደወርቁ ልባሞች እወቁ ከባጢልም ራቁ https://t.me/Abuhemewiya
727
15
👉 ወንድማዊ ምክር ለእህቶችና ወንድሞች መለኮታዊ የህይወት መመሪያን መሰረት ያደረገው ኢስላም ለሴት ልጅ ያጎናፀፈውን ክብርና የሰጣት ቦታ የሚታወቅ ነው ። ሴት ልጅ በኢስላም የተከበረች የእናት ፣ የልጅ ፣ የእህትና ሚስትነት ቦታ የያዘች የህብረተ ሰብ አካል ነች ። ይህ ክብሯ ተጠብቆ የሚቆየው አላህ ባዘዛት ቦታ ስትገኝና ከከለከላት ቦታ ስትርቅ ነው ። ከተከለከለችው ነገር ውስጥ አንዱ ከባዳ ወንድ ጋር መቀላቀልን ነው ። በተቃራኒው ሴት ልጅ ቤቷ ላይ መሆን እንዳለባትና የመሀይማን አይነት መገላለጥ እንዳትገላለጥ አዟል ። የመሀይማን አይነት መገላለጥ የሚለውን ከፊል የኢስላም ሊቃውንቶች ጎዳና ላይ ወጥቶ ከባዳ ወንዶች ጋር መደባለቅ ብለው ፈስረውታል ። ከእነዚህ ውስጥ ታላቁ ታቢዕይ ሙጃሂድ ይገኝበታል ። ይህ ክልክል የሆነው መቀላቀል በተለያየ መንገድ ሊሆን ይችላል ። ከእነዚህ ውስጥ በተለያዩ አንድ ወንድና ሴት ተለይተው ሊገናኙ በሚችሉባቸው ግሩፖች ላይ መቀላቀል ይገኝበታል ። የዘመናችን ትላልቅ የሱና ዑለሞች ሴቶች ለብቻቸው ግሩፕ መክፈት እንዳለባቸውና ከወንድ ጋር እንዳይቀላቀሉ ይከለክላሉ ። ምናልባት ግዴታ መቀላቀል ካስፈለገ ሴት መሆኗ በማያስታውቅ ስም ትቀላቀል ሀሳብ ስትሰጥም በዛው መልኩ ይሁን ይላሉ ። ይህ ሁሉ የፊትና በሮችን ለመዝጋት ነው ። ምክንያቱም ኢስላም አንድን ነገር እርም ሲያደርግ ወደዛ የሚያዳርሱ መንገዶችንም እርም ያደርጋል ( ይዘጋል) ። ዝሙትን እርም ሲያደርግ ወደዛ የሚያደርሱ መንገዶችንም እርም አደረገ ። ሴት ሸሪዓዊ እውቀት ካላት ለሴቶች ማስተማር ትችላለች ምናልባት ወንዶች ዘንድ የማይገኝ እውቀት ካላት ሸሪዓ ባስቀመጠው መስፈርት ወንዶችን ማስተማር ትችላለች ። ነገር ግን አሁን እያየነው ያለው አይነት ኡሙ እገሌ እያለች ግሩፕ ወይም ቻናል ከፍታ እየፃፈች ወንዶች በተለያየ ቻናልና ግሩፕ ሼር ማድረጋቸው ፊትናን ለማስፋፋት እንደመተባበር ይቆጠራልና ከዚህ ተግባር እህቶችም ወንድሞችም ሊቆጠቡ ይገባል ። እንዲህ አይነት አደባባይ መውጣት በፍፁም ከሰለፍይ እህት የሚጠበቅ አይደለም ። ምክንያቱም እሙ እገሌ ማን ነች ስሟ ማን ነው ስልኳን እንዴት ማግኘት እችላለሁ የሚሉ የፊትና በሮችን ይከፍታል ። ፈተና ይርቁታል እንጂ አያቀርቡትም ስለዚህ እንዲህ አይነት ተግባር ውስጥ የገባችሁ እህቶችና ሼር የምታደርጉ ወንድሞች ከዚህ ተግባራችሁ ተቆጠቡ እላለሁ ። ለስሜታችን የሚከብድ ሊሆን ስለሚችል ጉዳዩን ወደ ዑለሞች ማድረስና መጠየቅ ጥሩ ነው ። አላህ ሐቅን አውቀው ከሚሰሩበትና ባጢልን አውቀው ከሚርቁት ባሮቹ ያድርገን ። https://t.me/bahruteka
568
16
የአዲስ ደርስ ማስታወቂያ ዘወትር ቅዳሜ፣ እሑድ፣ ሰኞ እና ማክሰኞ ከፈጅር ሶላት በኋላ ሲሰጥ የነበረው የአል-አርበዑን አንነወዊ ኪታብ ስላለቀ በቦታው የተተካው 📚 ሪያዱ አስሷሊሒን ሚን ከላሚ ሰዪዲ
የአዲስ ደርስ ማስታወቂያ ዘወትር ቅዳሜ፣ እሑድ፣ ሰኞ እና ማክሰኞ ከፈጅር ሶላት  በኋላ ሲሰጥ የነበረው የአል-አርበዑን አንነወዊ ኪታብ ስላለቀ በቦታው የተተካው 📚 ሪያዱ አስሷሊሒን ሚን ከላሚ ሰዪዲል ሙርሰሊን የኢማም አንነወዊይ ከፊታችን ቅዳሜ ጀምሮ በተለመደው ሰአት የሚቀጥል ይሆናል። 🎙 ትምህርቱ የሚሰጠው  በአቡ ሐመዊያህ ሸምሱ ጉልታ (ሐፊዘሁላህ) 🕌  አልኢስላሕ መድረሳ የአልኢስላሕ መድረሳ👇👇👇   የተለያዩ ደርሶችን በቀጥታ ስርጭት ለመከታተል እና የሚለቀቁ ደርሶች ለማግኘት የመድሳውን ቻናል #join በማለት ይቀላቀሉ። https://t.me/medresetulislah
473
17
👉 ራቁት ሆኖ ከመዝፈን በአላህ ላይ ማጋራት ይበልጣል ! ወንጀል በየትኛውም ሀገር በማንም ቢሰራ ወንጀል ነው ። የሆነ ሀገር ስለተሰራ ከወንጀልነት አያወጣውም ። ሪያድ ላይ በሆነ ፕሮግራም ላይ የነበረ አሳዛኝና አስቀያሜ ተግባር ሶሞኑን ሰዎች ሲያወሩ ሰምቼ ምንድነው ብዬ ለማየት ሞከርኩ ። ድርጊቱ በጣም ፀያፍና አላህን የሚያስቆጣ ተግባር ነው ። የካዕባ ምስል ተሰርቷል ለብሰዋል ለማለት የማያስደፍር ዘፋኝ ሴቶች በምእራባዊያን አኳኋል ያብዳሉ ። የዚህ አይነቱ ተግባር ፍፁም ከኢስላም አስተምሮ የራቀ አስቀያሚ ተግባር ነው ። ይህን ክስተት በተለይ የግብፅና የፍልጢን አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች የሳውዲን መሪዮች ለማክፈርና ለመርገም ምቹ አጋጣሚ ሆኖላቸው አየሁ ። በጣም የሚገርመው አንድ የእናቱን ፊት የተዋሰ የሚመስል የግብፅ ጋዜጠኛ ከሱረቱል ق የተወሰኑ አንቀፆችን ቀርቶ አላህ ፊት የቂያማ ቀን ስለመቆምና ስለሚኖረው ጭንቅ ከተናገረ በኋላ ለሳውዲ መሪዮች ጥያቄ ያቀርባል ። ሱብሓነላህ እንዴት የሚገርም ለዲን መቆርቆር ነው በጣም ደስ ይላል ። በዚህ መልኩ ወንጀልን መፀየፍና ማውገዝ ከኢስላም መርሆች ውስጥ ዋነኛው ነው ። ነገር ግን እኔ ለእነዚህ አካላት ጥያቄ አለኝ እነዚህ ወንጀሎች ሳውዲ ውስጥ ሲሰሩ ነው በዚህ መልኩ የምትቆረቆሩትና የምታወግዙት ወይስ ሀገራችሁም ላይ ? ለመሆኑ ከአላህ ውጪ ላለ አካል ለአላህ እንጂ የማይገቡ የአምልኮ አይነቶችን መስጠት አሁን እያወገዛችሁት ካለው ወንጀል እንደሚበልጥ ታውቃላችሁን ? በግብፅ ምድር ላይ የአሕመደል በደዊ ቀብር ከ3 · 5 ሚሊየን ህዝብ በላይ ጠዋፋ ሲያደርግበት ፣ የቀብሩን አፈር በጥብጦ ሲጠጣ ፣ ከአላህ እንጂ የማይጠየቁ እንደ ከጭንቅ አውጡኝ ፣ አፍያ ስጡኝ ፣ ርዝቄን አስፉልኝ ፣ ዘር ስጡኝ ፣ እና የመሳሰሉ ጥያቄዎችን ለአሕመደል በደዊና ለዱሱቂ ፣ ለዘይነብና ለመሳሰሉ ሙታኖች ሲጠይቁ የት ነበራችሁ? የዚህ አይነቱ የቀብር አምልኮ መንግስታችሁ ባጀት መድቦ ሰራዊት አሰልፎ እንደባአል እንዲከበር ሲያደርግ ታወግዛላችሁ ? ወይስ ይህ በናንተ ሀገር ሲሰራ ወንጀል አይደለም ? ቤቱ በመስታወት የሆነ ሰው በሰው ቤት ላይ ድንጋይ አይወረውርምና ተረጋጉ እንላለን ። ሳውዲ ላይ የሚሰራ የትኛውም ወንጀል ከወንጀልነት ሊወጣ አይችልም ። በወንጀልነቱ ይወገዛል ። ነገር ግን መሪዮችን ለማክፈር መንገድ አድርጎ መጠቀም የኸዋሪጆች አካሄድ ነውና ተጠንቀቁ ነው የሚባለው ። የሳውዲ መሪዮች ደማቸው አረንጓዴ ነው አይነኩም ለማለት አይደለም ። ከመሪዮች የሚሰራ ስህተት የሚታረምበት መንገድ መልእክተኛው ነግረውናል ። ሰለፎችም ተግብረው አሳይተውናል ። የመሪዮችን ስህተት በኹጥባ ፣ በሙሓደራ ፣ በጋዜጣ ፣ በመፅሄት ፣ በተለያዩ ሚዲያዎች ማሰራጨት የነብዩና የሶሓቦች መንገድ የሚከተሉ ሰዎች አካሄድ አይደለም ። መጥፎን ነገር ስንለካ በሸሪዓ መለኪያ እንጂ በስሜታችን መሆን የለበትም ። የወንጀሎችን ክብደትና ቅለትም እንደዚሁ ይህን መሰረት አድርገን ነው ሁሉንም በልኩ ማውገዝ ያለብን ። ሳውዲ በሽርክ ጉዳይ አንገት እየቀላች ድግምተኞችንና መተተኞችን አይቀጡ ቅጣት እየቀጣች ከተለያየ ሀገር መውሊድ ለማክበር የተሰበሰቡ ሱፍዮችን እየበተነችና አሰተባባዮችን በቁጥጥር ስር እያዋለች ማየት ያልቻሉት ወይም አይተው አላየንም የሚሉት በሀገራቸው ላይ ከሚሰራው አመፅና ወንጀል ሊወዳደር የማይችል ወንጀል ሳውዲ ላይ ሲሆን መሪዮች ለማክፈር መንገድ አድርጎ መጠቀም በየትኛውም መመዘኛ ተቀባይነት የለውም ። መሪዮች ሲያጠፉ በግል ይመከራሉ ዱዓእ ይደረግላቸዋል ። እንጂ በአደባባይ ከበሮ አይደለቅም ። ምክንያቱም የዚህ አይነቱ ተቃውሞ መሪዮቹ አፀፌታውን እንወስዳለን ብለው የበለጠ ጥፋት ሊመጣ ስለሚችልና መሪና ተመሪ መካከል ያለው መተማመን ጠፍቶ ሀገር ስለሚበጠበጥ ነው ። ከላይ ለመግለፅ እንደሞከርኩት ወንጀል ማንም የትም ቢሰራው ወንጀል ነው ይጠላል ይወገዛል ። ነገር ግን የሚወገዝበት መንገድ ሸሪዓው ባዘዘው መልኩ መሆን አለበት ነው ትልቁ ነጥብ ። በአሁኑ ጊዜ ሰዎች የሆነ ሰው ነፍሰጡር ሴትን ገደለ ፣ እናቱን ተገናኘ ፣ ከእህቱ ወለደ ፣ አስገድዶ ደፈረ ፣ ህፃን አረደ ሲባል ቢሰሙ ይሰቀጥጣቸዋል ይዘገንናቸዋል በጣም ያወግዙታል እንደ ጭራቅ ያዩታል ። ይህ ባልከፋ ነበር ። ከባድ ወንጀል ስለሆነ ሊወገዝ ይገባልና ነገር ግን እገሌ የሚባል ሰው የቀብር አፈር በጥብጦ ጠጣ ፣ ቀብር ጋር ሄዶ ጫማውን አውልቆ ስልኩን ዘግቶ እያለቀሰ የሞተውን ሰው እርዱኝ ድረሱልኝ አለ ፣ ሌላኛው ለጂኒ አርዶ ደሙን ጠጣ ፣ ሌላኛው ልጅ ፍለጋ ጠንቋይ ቤት ሄደ ቢባሉ ምንም አይመስላቸውም ። ‼ ይህ ሊስተካከል ይገባል ሙስሊሞች በሽርክና በቀባባድ ወንጀሎች መካከል ያለውን ልዩነት እንዲያውቁ ማስተማር ያስፈልጋል ። አላህ በሱ ላይ ማጋራትን በፍፁም አልምርም ሲል ከሽርክ ውጪ ያሉ ወንጀሎችን ለሻው ሰው እንደሚምር ነግሮናል ። ሽርክ ስራን በሙሉ አበላሽቶ የዘላለማዊ ጀሀነም ባለቤት ሲያደርግ ከባባድ ወንጀሎች ግን አላህ ለሻው ሰው የሚምር ሲሆን ከቀጣውም በወንጀሉ ልክ ተቀጥቶ ከእሳት እንደሚወጣና የጀነት እንደሚሆን ኢስላም ያረጋግጣል ። ታዲያ ግብፅ ውስጥ ያለው የቀብሮች አምልኮ ሳውዲ ውስጥ ከተሰራው የሴቶች ተራቁቶ መዝፈን ጋር ሲነፃፀር የሰማይና የምድር ያክል ልዩነት አለው ። ነገር ግን ሁሉም ወንጀሎች በመሆናቸው ይወገዛሉ ይሁን እንጂ አይገናኙም ። https://t.me/bahruteka
464
18
🔹 ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም የፊታችን እሁድ ታሕሳስ 6/2017 በእነሞር ወረዳ ጉንችሬ ክ/ከተማ ጉንችሬ ማዞሪያ ዑመር መስጂድ ላይ ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኃል ። ተጋባዥ እንግዶች 1ኛ
🔹  ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም     የፊታችን እሁድ ታሕሳስ 6/2017 በእነሞር ወረዳ ጉንችሬ ክ/ከተማ ጉንችሬ ማዞሪያ ዑመር መስጂድ ላይ ልዩ የዳዕዋ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ ይጠብቃችኃል ።     ተጋባዥ እንግዶች 1ኛ – ሸይኽ ዐ/ሐሚድ 2ኛ – ወንድማችሁ ባሕሩ ተካ 3ኛ – ኡስታዝ ሱደይስ     ፕሮግራሙ የሚጀመረው አላህ ካለ ጠዋት 2 : 30 ይሆናል ።     https://t.me/bahruteka
372
19
🔸حقيقة منهج التمييع من غير إفراط ولا تفريط🔸 للشيخ العلامة المحدث ربيع بن هادي المدخلي-حفظه الله-
543
20
🟢መጅሊሳችሁን ገምግሙት በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ መጅሊስ የቋቋማችሁ ፣ የምትመሩት ባለስልጣናቱ ፣ አባላቱ ፣ አጋሮቹ እና ደጋፊዎቹ ሁሉ : መጅሊሳችሁ ከሚስተዋሉበት ጥፋቶች ውስጥ:- 1⃣ሰለፊያን ቀብሮ ሱፊያን አክብሮ ለመንገስ የቆረጠ መጅሊስ በተደጋጋሚ የመጅሊሳችሁ መሪዎችና ተቀጣሪዎች የነቢያት ፣ የሰሃቦች እና የዑለማዎች መንገድ የሆነውን የሰለፊያን ደዕዋ ለማጥፋት ቆርጠው መነሳታቸውን በግልፅ አውጀዋል:: ተቋማቸውም በተግባርም የሚችለውን ሁሉ እየጣረ ነው::የተዊሂድ ደእዋ ይከለክላል ፣ ቂርኣት ያግዳል ፣ ሀቅ ተናጋሪ ኢማሞችን እና ኡስታዞችን  ያባርራል እንዳይንቀሳቀሱ ያግዳል:: ይባስ ብሎም ለእስርና እንግልት አሳልፎ ይሰጣል :: በአላህ ይሁንብኝ ባጢል ሀቅን አያጠፋም:: ሱፊያ እና ድምሮቹ ፊርቃዎች ልብ ወለድ  ሲሆኑ ሰለፊያ ግን የአላህ ዲን ነውና የበላዓይነቱ የፀና ነው❗️ ነቢዩ (ﷺ) እንደተናገሩት: ( ... وَتَفْتَرِقُ أُمَّتِي عَلَى ثَلَاثٍ وَسَبْعِينَ مِلَّةً كُلُّهُمْ فِي النَّارِ إِلَّا مِلَّةً وَاحِدَةً ، قَالُوا : وَمَنْ هِيَ يَا رَسُولَ اللَّهِ ؟ قَالَ : مَا أَنَا عَلَيْهِ وَأَصْحَابِي ) (ህዝቦቼ ወደ ሰባ ሶስት መንገዶች ይላያያሉ:: አንዲት መንገድ ብቻ ስትቀር : ሁላቸውም የእሳት ናቸው:: ሰሃቦችም አሉ " ማነች እርሷ ያ ረሱለላህ ?" አሉ : እኔና ባልደረቦቼ ያለንበት መንገድ::) 2⃣መውሊድን አድምቆ አክባሪ መጅሊስ የሺርኮች እና ቢድዓዎች መናኸሪያ የሆነውን መውሊድን በድፍረትና በተደጋጋሚ ደምቆ እንዲከበር የሚሰራ መጅሊስ መሆኑን አሳያችሁ:: ነቢዩ (ﷺ) እንደተናገሩት: (...وشرًّ الأمورِ محدثاتُها وكلَّ بدعةٍ ضلالةٌ  وكلَّ ضلالةٍ في النارِ ) (...የነገሮች ክፉ ፈጠራዎች ናቸው::ሁሏም ቢድዓህ ጥመት ነች ::ሁሏም ጥመት እሳት ውስጥ ታስገባለች::) 3⃣ሁሉም ለስሜቱ የመሰለውን እንዲሰራ የሚፈቅድ መጅሊስ የፈለገ መወሊድ እንዲያወጣ ፣ የፈለገ ጫት እንዲቅም ያልፈለገ ሳይቃወም ሊተው ወዘተ እያለ ሸሪኣ በመደንገግ ከአላህ ጋር የሚፎካከር ደፋር ተቋም ነው:: قوله تعالى: ﴿أَمْ لَهُمْ شُرَكَاءُ شَرَعُوا لَهُمْ مِنَ الدِّينِ مَا لَمْ يَأْذَنْ بِهِ اللَّهُ وَلَوْلا كَلِمَةُ الْفَصْلِ لَقُضِيَ بَيْنَهُمْ وَإِنَّ الظَّالِمِينَ لَهُمْ عَذَابٌ أَلِيمٌ ﴾ 4⃣ በሸሪኣም ሆነ በሀገር ህግ ባልተሰጠው ስልጣን የሚጨቁን አምባገነን መጅሊስ በመሰረቱ መጂሊሳችሁ አንድ ተቋም እንጂ አሚር ወይም መንግስት አልነበረም:: ነገር ግን መስጂዶችን አስገድዶ በቁጥጥሩ እያስገባ ፣ መድረሳዎችን እያዘጋ ፣ የግለሰብ መስጂዶችን ጭምር በጉልበት እያዘዘ ፣ ትእዛዙን አልቀበል ያለን እያሸማቀቀ ፣ ኡስታዞችና ደረሶችን እያስደበደበ ፣ እና እያሳሰረ በግፍ የተሞላ ጥቁር ታሪክ እያስመዘገባላችሁ ነው:: ✍በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ  አጋዦች ፣ አድናቂዎች እና አጋሮች ሆነው ሲያበቁ መሰል የመጅሊሱን ጥፋቶችና ጉዶችን "እኛ አልሰራነውም" የሚሉ አይጠፋም:: በጋራ የገነባችሁት ቤታችሁ መሆኑን አትርሱ:: የሞተው ወንድምሽ የገደለው ባልሽ ሀዘንሽ ቅጥ አጣ ከቤትሽም አልወጣ አላህን ፈርታችሁ ተመለሱ :: በምድር ላይም አታበላሹ:: ከግፈኞች ታሪክ ተማሩ:: ✍  ሸምሱ ጉልታ (አቡ ሀመዊያ) http://t.me/Abuhemewiya
446