en
Feedback
Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1

Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1

Open in Telegram

This is AradaFm 95.1 Official Telegram Channel አጭር የመልዕክት መቀበያ 8545

Show more
4 221
Subscribers
+324 hours
+107 days
-1430 days
Posts Archive
አርሰናል በቼልሲ ላይ ያለውን የበላይነት አስቀጥሏል ጳጉሜ 01፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሳምንቱ የመጨረሻ እና ተጠባቂ ጨዋታ አርሰናል ቼልሲን 2 ለ 1 አሸንፏል። በጨዋ
አርሰናል በቼልሲ ላይ ያለውን የበላይነት አስቀጥሏል ጳጉሜ 01፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሳምንቱ የመጨረሻ እና ተጠባቂ ጨዋታ አርሰናል ቼልሲን 2 ለ 1 አሸንፏል። በጨዋታው 77ኛ ሰከንድ ላይ ሞርጋን ሮጀርስ ያስቆጠረው ግብ ሰማያዊዎቹን በጊዜ መሪ አድርጓል። በ25ኛው ደቂቃ ላይ ካይ ሀቨርዝ ባስቆጠረው ግብ መድፈኞቹ አቻ ሲሆኑ የመጀመሪያው አጋማሽም በአንድ አቻ ውጤት ተጠናቋል። በሁለተኛው አጋማሽ 50ኛው ደቂቃ ላይ ደግሞ ማርቲን ኦዲጋርድ መድፈኞቹን አሸናፊ ያደረገ ግብ አስቆጥሯል። ከ2021 በኋላ በቼልሲ ያልተሸነፈው አርሰናል ውጤቱን ተከትሎ የበላይነቱን ያስቀጠለበት ሆኗል። በ4ኛው ሳምንት የሊጉ መርሐግብር አርሰናል ከሰንደርላንድ እንዲሁም ቼልሲ ደግሞ ከሀል ሲቲ ጋር ይጫወታሉ። ሀብታሙ ምትኩ

ባርሴሎና ከሜዳው ውጪ ቫሌንሲያን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል በስፓኒሽ ላሊጋ አራተኛ ሳምንት ባርሴሎና 5ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል። የባርሴሎናን የማሸነፍያ ግቦች ላሚን ያማል(2) ፈርሚን ፣
ባርሴሎና ከሜዳው ውጪ ቫሌንሲያን በሰፊ የግብ ልዩነት አሸንፏል በስፓኒሽ ላሊጋ አራተኛ ሳምንት ባርሴሎና 5ለ0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፏል። የባርሴሎናን የማሸነፍያ ግቦች ላሚን ያማል(2) ፈርሚን ፣ ራፊኒሃና ኩንዴ አስቆጥረዋል። ባርሴሎና ሪያል ማድሪድ በአራተኛ ሳምንት በራዮ ቫይካኖ መሸነፉን ተከትሎ ሊጉን በ12 ነጥቦች መምራት ጀምሯል። ራፊኒሃ በአራት ጨዋታ ስድስት ግቦችን አስቆጥሮ በዘጠኝ ቁጥር ቦታ ጥሩ ግዜን እያሳለፈ ይገኛል AradaFm-Sport

#update የዕንቁ ሴት ንቁ ሴት 9ኛው ዙር የዕውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ተካሄደ በዛሬው ዕለት በተካሄደው በዚህ ዝግጅት ላይ በሥራቸው ስኬታማ በመሆን ለሌሎች ሴቶች ምሳሌ መሆን ለቻሉ ሴቶች የ
+1
#update የዕንቁ ሴት ንቁ ሴት 9ኛው ዙር የዕውቅናና የሽልማት መርሃ ግብር ተካሄደ በዛሬው ዕለት በተካሄደው በዚህ ዝግጅት ላይ በሥራቸው ስኬታማ በመሆን ለሌሎች ሴቶች ምሳሌ መሆን ለቻሉ ሴቶች የዕውቅና ሰርተፍኬት እና የምስጋና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል ዘንድሮ በተደረገው የእውቅና ሽልማት አምባሳደር ሙሉ ሰሎሞን፣የቻለ ማሞ፣መካነ ሰላም መሐመድ እና ቲና ተረፈ፣መስከረም አሰግድ፣ሰናይት በዙ፣ ፍሬህይወት ታምሩ፣ ፅላት ገዝሙ እና ገነት ከበደ (አቢሲያኒያ) እውቅና አግኝተዋል ሲስተር ዘቢደር ዘውዴ በዚህ ሽልማት የበላይ ጠባቂ ሲሆኑ  የሽልማት መርሀ ግብሩ ላይ በርካታ የኪነ ጥበብ ባለሙያዎች የተሸላሚ ቤተሰቦች እና አጋር አካላት ተገኝተውበታል ዕንቁ ኤቨንትስና ሳሜሎስ ሚዲያና ኮሚኒኬሽን በጋራ ያዘጋጁት "ዕንቁ ሴት - ንቁ ሴት" የዕውቅና ሽልማት ለሚገባቸው ጠንካራ ሴቶች ማበርከቱን ወደፊትም በተጠናከረ መልኩ እንደሚቀጥል የሽልማቱ  ሀሣብ አመንጪ እና  መሥራች አቶ ሳሙኤል ገረመው  ተናግረዋል የእውቅና ሥነ-ሥርዓቱንና የሚድያ ማስተባበሩን እንዲሁም  የሕይወት ታሪክ የማጠናከር ዝግጅቶች ደግሞ በተወዳጅ ሚድያ ተከናውኗል "ዕንቁ ሴት- ንቁ ሴት" ሽልማት ከዚህ ቀደም ለ8 ጊዜ ያህል የተካሄደ ሲሆን  ደራሲት የዝና ወርቁ ፣ ደራሲት ሜሪ ጃዕፋር፣ ደራሲት ውዳላት ገዳሙ፣  አርቲስት መቅደስ ጸጋዬ ፣ በረከት ወርቁ(በረከት ገበሬዋ)፣ ዲዛይነር ሳራ መሐመድ፣ ሜንቶር ፍጹም ኪዳነማርያም፣ ጨምሮ ከ 20 በላይ ለሆኑ ተምሳሌት ሴቶች የዕውቅና ሽልማት እንደተበረከተላቸው ይታወሳል ሰናይት በየነ

ማንችስተር ዩናይትድ 96ኛው ደቂቃ ላይ በተቆጠረበት ግብ ነጥብ ጥሏል ጳጉሜ 01፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ ከኤቨ
ማንችስተር ዩናይትድ 96ኛው ደቂቃ ላይ በተቆጠረበት ግብ ነጥብ ጥሏል ጳጉሜ 01፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የሶስተኛ ሳምንት የዕለቱ ቀዳሚ ጨዋታ ማንችስተር ዩናይትድ ከኤቨርተን 2 ለ 2 ተለያይተዋል። ብርያን ኤምቡኤሞ በ47ኛው ደቂቃ ያስቆጠረው ግብ ቀያይ ሰይጣኖቹን እስከ 82ኛው ደቂቃ ድረስ መሪ አድርጓቸው ነበር። በ83ኛው ደቂቃ ግን ቲሪክ ጆርጅ በጠንካራ ምት ግብ አስቆጥር የጨዋታውን ውጤት ወደ አቻ ቀይሮታል። ከዚህ ግብ መቆጠር 5 ደቂቃዎች በኋላ ግን ተቀይሮ የገባው ቤንጃሚን ሴስኮ ማንችስተር ዩናይትድን ዳግም መሪ ያደረገ ግብ አስቆጥሯል። ነገር ግን በ90+6ኛው ደቂቃ ላይ በኤቨርተን በኩል ተቀይሮ የገባው ሜይትላንድ ኒልስ ክለቡን አቻ አድርጓል። በአራተኛው ሳምንት ማንችስተር ዩናይትድ ከማንችስተር ሲቲ እንዲሁም ኤቨርተን ከቶተንሀም ሆትስፐርስ ይጫወታሉ። ሀብታሙ ምትኩ AradaFm_Sport

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታን በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 በቀጥታ ስርጭት ይከታተሉ አርሰናል ከቼልሲ በፒች ስፖርት የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtub
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታን በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 በቀጥታ ስርጭት ይከታተሉ አርሰናል ከቼልሲ በፒች ስፖርት የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm  Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

🌻ጳጉሜ -1 🌻 ዘመንሽ ይባረክ የተሰኘ የህብረት ሙዚቃ አንድነትን ገላጭ ህብረትን ጠቋሚ ነው፡፡ ይህ የሙዚቃ ሥራ ከወጣ ሰባት አመታትን ተቆጥሯል፡፡ አዲሱን ዓመት አቀባብሎ የማለፍንና የቀደመውን
🌻ጳጉሜ -1 🌻 ዘመንሽ ይባረክ የተሰኘ የህብረት ሙዚቃ አንድነትን ገላጭ ህብረትን ጠቋሚ ነው፡፡ ይህ የሙዚቃ ሥራ ከወጣ ሰባት አመታትን ተቆጥሯል፡፡ አዲሱን ዓመት አቀባብሎ የማለፍንና የቀደመውን በጎ ዘመን የማስታወስ ታላቅ የበዓል መንፈስ ይጋብዛል። አራቱ ድምፃውያን በህብረት በመቀንቀን የማህበረሰብን ትስስር፣ አብሮነትንና ሀገራዊ አንድነትን በሙዚቃዊ ቋንቋ ገልጸውልናል። ሥራው ያለፈው ዘመን የተደረጉ መልካም ነገሮችን እያሰቡ ማመስገንንና መጪውን አዲስ ዘመን በደስታና በተስፋ መቀበልን ትኩረት ያደርጋል። በግጥሞቹና በዜማው አካሄድ የበዓሉን ድምቀት፣ የተፈጥሮን መታደስና የሰዎችን የደስታ ስሜት በጥሩ ሁኔታ ያንፀባርቃል። "በምድርሽ ሲጠባ መስከረም ብርቅ ሆኖ የዓመቱ ጅማሬ ዘመንሽ ይባረክ ዘላለም፤ ሰላም ሁኚ ኢትዮጵያ ሀገሬ" በሙዚቃው ውስጥ በጉልህ የሚታየው ሌላው ዋና ሀሳብ የሀገር ፍቅር፣ የህዝቦች አንድነትና የወንድማማችነት እሴት ነው። ከተለያዩ አቅጣጫዎች ተውጣጥተው የተሰባሰቡት ድምፃውያን በአንድነት በማቀንቀናቸው የኢትዮጵያን ባህላዊ ብዝሃነትና የማህበረሰቡን ትስስር አጉልተውታል። "አጊጠሽ ስታምሪ በእለተ እንቁጣጣሽ አምናለሁ እማማ ከልጅሽ መልስ አለሽ" ይህም በዓላት የደስታ ጊዜያት ብቻ ሳይሆኑ፣ ህዝቦች ተቀራርበው አብሮነታቸውንና ፍቅራቸውን የሚያጠናክሩበት አጋጣሚ መሆናቸውን ያስገነዝባል። የሙዚቃውን ሀሳብ በጆሯችንና በምስለ-ህሊናችን ስናስበው የኢትዮጵያን ተፈጥሯዊ ውበትና ባህላዊ ሀብቶች በስፋት ያሳየናል። ተመስገን ኡካሬ ተጨማሪ ለማንበብ https://www.facebook.com/100083001655534/posts/pfbid02vgD8EBP94vYXCCyFHotM4L8hN9vDaUAY2QJ8WaDYZmwDsXf69YYqHRjwSZfwM4Sel/?mibextid=wwXIfr @Arada_Fm

በአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች መርሐግብር ጳጉሜ 01 ፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) 🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 10:00 ኤቨርተን ከ ማንችስተር ዩናይትድ 12:3
በአውሮፓ ታላላቅ ሊጎች ዛሬ የሚደረጉ ጨዋታዎች መርሐግብር ጳጉሜ 01 ፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) 🏴󠁧󠁢󠁥󠁮󠁧󠁿 የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ 10:00 ኤቨርተን ከ ማንችስተር ዩናይትድ 12:30 አርሰናል ከ ቼልሲ 🇪🇸 የስፔን ላሊጋ 11:15 ቫሌንስያ ከ ባርሴሎና 01:30 አላቬስ ከ ኦሳሱና 01:30 ማላጋ ከ ሌቫንቴ 04:00 እስፓኞል ከ ሲቪያ 🇮🇹 የጣልያን ሴሪ ኤ 10:00 ፍሮሲኖኔ ከ ቬኔዝያ 10:00 ፓርማ ከ ሞንዣ 01:00 ቦሎኛ ከ ሳሱኦሎ 03:45 ጁቬንትስ ከ ኤሲ ሚላን 🇩🇪 የጀርመን ቡንደስሊጋ 10:30 ሀምቡርግ ከ ሜይንዝ 12:30 ፍራንክፈርት ከ ኦግስበርግ 🇫🇷 የፈረንሳይ ሊግ አንድ 10:00 ትሮይስ ከ ስትራስቡርግ 12:15 ኦንዤ ከ ሬንስ 03:45 ማርሴ ከ ፓሪስ ሀብታሙ ምትኩ

የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታን በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 በቀጥታ ስርጭት ይከታተሉ ኤቨርተን ከማንቸስተር ዩናይትድ በጌም ኦን የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www
የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታን በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 በቀጥታ ስርጭት ይከታተሉ ኤቨርተን ከማንቸስተር ዩናይትድ በጌም ኦን የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm  Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

🌼የአዲስ አመት መዳረሻ🌼 የኔዜማ የአድማጮች የሙዚቃ ምርጫ ዘወትር እሁድ ከ 3:00-5:00 በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 ይደመጣል፡፡ ለዛሬ የመረጥነው ሙዚቃዎች… 🌼ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን-(አበባአ
🌼የአዲስ አመት መዳረሻ🌼 የኔዜማ የአድማጮች የሙዚቃ ምርጫ ዘወትር እሁድ ከ 3:00-5:00 በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 ይደመጣል፡፡ ለዛሬ የመረጥነው ሙዚቃዎች… 🌼ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን-(አበባአየሆይ) 🌼ድምፃዊት ትዕግስት በቀለ(ለእግሩ ውሀ አሙቁለት) 🌼ድምፃዊ አብዱ ኪያር(መልካም አመት በዓል) መልካም ምኞቻችሁን አቀብሉን፣ ይቅርታ እና ምስጋናም አክላችሁ ማድረስ ትችላላችሁ፡፡ ☎️ስልኮቻችን 011 5 58 54 31 ወይም 011 5 58 54 32 ይደውሉ፡፡ አዘጋጅ እና አቅራቢ፡-ተመስገን ኡካሬ የኔ ዜማ ከወዲሁ እንኳን አደረሳችሁ

እሁድ ዻጉሜ 1 /2018 ዓ.ም አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት! መልካም ቀን ! @Arada_Fm
እሁድ ዻጉሜ 1 /2018 ዓ.ም አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት! መልካም ቀን ! @Arada_Fm

ማንቼስተር ሲቲ ሲያሸንፍ ቶተንሃም የመጀመሪያ ነጥቡን አገኘ ነሐሴ 30፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ ኮቨንትሪ ሲቲን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የማንቼ
+1
ማንቼስተር ሲቲ ሲያሸንፍ ቶተንሃም የመጀመሪያ ነጥቡን አገኘ ነሐሴ 30፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ማንቼስተር ሲቲ ኮቨንትሪ ሲቲን 1 ለ 0 በሆነ ውጤት አሸንፏል፡፡ የማንቼስተር ሲቲን የማሸነፊያ ጎል ኧርሊንግ ሃላንድ አስቆጥሯል፡፡ ውጤቱን ተከትሎም ማንቼስተር ሲቲ ለተከታታይ ሦስተኛ ጊዜ አሸንፏል። በሌላ የሊጉ ጨዋታዎች ክሪስታል ፓላስ ፉልሃምን 3 ለ 2 ሲያሸንፍ፣ ሊድስ ከብራይተን እንዲሁም ብሬንትፎርድ ከሰንደርላንድ በተመሳሳይ አንድ አቻ  ተለያይተዋል፡፡ ቶተንሃም ሆትስፐርስ ከኖቲንግሃም ፎረስት ያለምንም ጎል አቻ ተለያይቷል፡፡ የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm  Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

ኢቻ የምግብ ኮምፕሌክስ ምግብን በቫይታሚን እና በማዕድን አበልፅጌ ለህብረተሰቡ እያቀረብኩ ነው አሐ ነሐሴ 30፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ኢቻ የምግብ ኮምፕሌክስ የበለፀገ የስንዴ ዱቄትን በማምረት
+3
ኢቻ የምግብ ኮምፕሌክስ ምግብን በቫይታሚን እና በማዕድን አበልፅጌ ለህብረተሰቡ እያቀረብኩ ነው አሐ ነሐሴ 30፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ኢቻ የምግብ ኮምፕሌክስ የበለፀገ የስንዴ ዱቄትን በማምረት ለሃገር ውስጥና ለውጭ ሀገር ማቅረብ የጀመረበትን 1ኛ ዓመቱን በሸገር ሲቲ ገላን ከተማ ሲጳ አዋሽ ቀበሌ በሚገኘው ፋብሪካ ቅጥር ጊቢ ውስጥ አክብሯልደ የኢቻ ምግብ ኮምፕሌክስ መስራችና ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ያሬድ  ጥላሁን ለሰውነት የሚያስፈልጉ የተለያዩ ንጥረ-ምግቦችን በስንዴ ምርቱ ውስጥ በማካተት እያቀረበ መሆኑን ገልፀዋል። በተለይ ከልጆች አፈጣጠር ጋር ለሚመጡ ችግሮች እናቶች በቫይታሚን እና በማዕድን የበለፀጉ ንጥረ ነገሮችን መጠቀም ስላለባቸው  ፎሊክ አሲድን ጨምሮ እንዲኖርበት ተደርጎ ምርቱ መመረቱንም ጠቁመዋል። ኢቻ የምግብ ኮምፕሌክስ ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ በኢትዮጵያ ብዛት ያለውን የምግብ ፍላጎት ለማሟላት በሸገር ሲቲ ገላን ከተማ የተቋቋመ ሲሆን፣ የምግብ ጥሬ ዕቃዎችን በመጠቀም የምግብ ምርቶችን በማምረት ያከፋፍላል። እንደ ካርቦሃይድሬት ማዕድን እንዲሁም ቫይታሚንን በስንዴ ምርቱ ላይ እንዲካተት በማድረግ ጥራቱን የጠበቀ የስንዴ ዱቄት በማምረት ባልበለፀገ ዱቄት የሚመጣ የጤና ቀውስን ለመቀነስ እየሰራሁ ነው ብሏል። ሰናይት በየነ የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm  Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

የአዲስ ባንክ የምንዛሪ ተመን የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@arad
የአዲስ ባንክ የምንዛሪ ተመን    የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ   Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1   Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical   Telegram:-https://t.me/Arada_Fm    Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital   Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm   @Arada_Fm

የአፍሪካን ትክክለኛ ስፋት ይገልጻል የተባለ አዲስ ካርታ ሊተካ ነው ነሐሴ 30፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ አሁን ያለው የዓለም ካርታ የአፍሪካን የቆዳ ስ
+1
የአፍሪካን ትክክለኛ ስፋት ይገልጻል የተባለ አዲስ ካርታ ሊተካ ነው ነሐሴ 30፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ አሁን ያለው የዓለም ካርታ የአፍሪካን የቆዳ ስፋት ትክክለኛ በሆነ መጠን በሚገልጽ መልኩ አዲስ ካርታ እንዲተካ ውሳኔ አሳለፈ። “ካርታውን ማስተካከል” የሚለው የውሳኔ ሃሳብ በቶጎ አማካይነት የቀረበና በአፍሪካ ህብረት አባል አገራት ድጋፍ የተቸረው ሲሆን፥ ፈረንሳይ እና ብሪታንያን ጨምሮ የ164 አገራት ድጋፍን አግኝቷል። አሜሪካ ውሳኔውን የተቃወመች ብቸኛ አገር ስትሆን፥ ሥድስት አገራት ድምፀ ተአቅቦ አድርገዋል። የተመድ ውሳኔ አስገዳጅነት የሌለው ሲሆን፥ ዓለም ላይ ያሉ ተቋማት አሁን የሚጠቀሙበትን ካርታ እንዲቀይሩ ሊያደርግ ይችላል መባሉን ቢቢሲ አስነብቧል። አሁን ያለውና ዓለማችን የምትጠቀምበት የዓለም ካርታ የ'መርኬተር' ካርታ ተብሎ የሚጠራ ሲሆን፥ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ ጥቅም ላይ የዋለ ነው። ይህ ካርታ ከአፍሪካ በ14 እጥፍ የምታንሰውን ግሪንላንድን በእኩል መጠን አስቀምጧል በሚል ከፍተኛ ትችት ሲቀርብበት ቆይቷል። ተችዎች ይህ መሆኑ በምድር ወገብ አካባቢ የሚገኙ አገራትን የልማት ፍላጎት እና አቅምን አንሶ እንዲታይ የሚያደርግ ነው ይላሉ። የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

የንብ ባንክ የምንዛሪ ተመን የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@arada
የንብ ባንክ የምንዛሪ ተመን የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

የቅዳሜን በአራዳ እንግዳ ባልከው አለሙ ድምፃዊ ባልከው አለሙ ከ1997 ዓ.ም የኢትዮጵያን አይዶል እስከ 2004 ዓ.ም የባላገሩ አይዶል የፅናት ጉዞውን ያሳየ፣በ መምህርነቱ ትውልድን የሚያንጽ፣ እንዲ
የቅዳሜን በአራዳ እንግዳ ባልከው አለሙ ድምፃዊ ባልከው አለሙ ከ1997 ዓ.ም የኢትዮጵያን አይዶል እስከ 2004 ዓ.ም የባላገሩ አይዶል የፅናት ጉዞውን ያሳየ፣በ መምህርነቱ ትውልድን የሚያንጽ፣ እንዲሁም በ'ለፍቅር ብለን'፣ 'የትዝታ ፈረስ' እና 'ዘውዲቱ' የተሰኙ ገሚስ ሙዚቃዎች የአድማጭን ልብ የገዛው ባለብዙ ሀብቱ ድምፃዊ ባልከው አለሙ የት ጠፋ? ምን እየሰራ ነው? የሚለውን ምላሽ እና የሕይወት እና የሙዚቃ ጉዞ አጫውቶናል፡፡