uz
Feedback
Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1

Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1

Kanalga Telegram’da o‘tish

This is AradaFm 95.1 Official Telegram Channel አጭር የመልዕክት መቀበያ 8545

Ko'proq ko'rsatish
4 224
Obunachilar
-324 soatlar
+87 kun
-430 kun
Postlar arxiv
የአልቲሜት ቻምፒየንሺፕ ዛሬ ምሽትም ቀጥሎ ይደረጋል መስከረም 02፣ 2019 (አራዳ ኤፍ ኤም) ትናንት ምሽት የጀመረው የመጀመሪያው የአልቲሜት ቻምፒየንሺፕ ዛሬ ምሽትም ቀጥሎ ይደረጋል። ከምሽት 01:
የአልቲሜት ቻምፒየንሺፕ ዛሬ ምሽትም ቀጥሎ ይደረጋል መስከረም 02፣ 2019 (አራዳ ኤፍ ኤም) ትናንት ምሽት የጀመረው የመጀመሪያው የአልቲሜት ቻምፒየንሺፕ ዛሬ ምሽትም ቀጥሎ ይደረጋል። ከምሽት 01:10 ጀምሮ ዘጠኝ የፍፃሜ እንዲሁም አምስት የግማሽ ፍፃሜ ውድድሮች ይደረጋሉ። ኢትዮጵያዊያን እንስት አትሌቶች በሁለት የፍፃሜ ወድድሮች ላይ የሚሳተፉ ሲሆን 02:36 በሚጀምረው 1500 ሜትር አራት አትሌቶቻችን ተሳታፊ ናቸው። ብርቄ ኃየሎም ፣ ሀረገወይን ካላዩ ፣ ሳሮን በርሔ ፣ እንዲሁም ፍረወይኒ ኃይሉ የ150 ሺህ ዶላሩ አሸናፊ ለመሆን ከሌሎች 8 አትሌቶች ጋር በርቀቱ ይፋለማሉ። በ800 ሜትር ፍፃሜ ደግሞ ትናንት ምሽት ማጣሪያውን ያለፈችው ንግስት ጌታቸው ከ03:18 ጀምሮ ውድድሯን ታደርጋለች። ሀብታሙ ምትኩ AradaFM_Sport

የወርልድ አትሌቲክስ አልቲሜት ሻምፒዮንሺፕ ዛሬ ይጀምራል መስከረም 01፣ 2019 (አራደ ኤፍ ኤም) የመጀመሪያው የወርልድ አትሌቲክስ አልቲሜት ሻምፒዮንሺፕ ዛሬ ከምሽት 02:00 ጀምሮ መካሄድ ይጀምራ
የወርልድ አትሌቲክስ አልቲሜት ሻምፒዮንሺፕ ዛሬ ይጀምራል መስከረም 01፣ 2019 (አራደ ኤፍ ኤም) የመጀመሪያው የወርልድ አትሌቲክስ አልቲሜት ሻምፒዮንሺፕ ዛሬ ከምሽት 02:00 ጀምሮ መካሄድ ይጀምራል። ሻምፕዮናው በሀንጋሪ ዋና ከተማ ቡዳፔስት ናሽናል አትሌቲክስ ሴንተር ከዛሬ ጀምሮ ለሶስት ተከታታይ ቀናቶች ይካሄዳል። ውድድሩ አትሌቶችን ከፍተኛ ገንዘብ ተሸላሚ የሚያደርግ ሲሆን በ28 የውድድር አይነቶች 10 ሚልዮን ዶላር ለሽልማት ብቻ አዘጋጅቷል። አሸናፊዎች 150 ሺህ ዶላር የሚሸለሙ ሲሆን ሁለተኛ 75 ሺህ ዶላር ሶስተኛ ደግሞ 40 ሺህ ዶላር ተሸላሚዎች ይሆናሉ። በዚህ ሻምፒዮና ላይ 12 ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች ሲሳተፉ በወንዶች 5000 ሜትር ቢኒያም መሃሪ እና አዲሱ ይሁኔ በሴቶች 800 ሜትር ደግሞ ንግስት ጌታቸው ይወዳደራሉ። በሴቶች 1500 ሜትር ፍረወይኒ ሃይሉ ፣ ሳሮን በርሄ ፣ ብርቄ ሀየሎም እና ሀረገወይን ካላዩ እንዲሁም በሴቶች 5000 ሜትር ልቅና አምባው ፣ አለሽኝ ባወቅ ፣ ፋንታየ በላይነህ ፣ ሰናይት ጌታቸው ፣ፍረወይኒ ሃይሉ እና ሂሩት መሸሻ ተወዳዳሪዎች ናቸው። ዛሬ ምሽት ኢትዮጵያዊያን አትሌቶች የሚሳተፉባቸው የወንዶች 5 ሺህ ሜትር ፍፃሜ 03:36 ጀምሮ እንዲሁም የሴቶች 800 ሜትር ግማሽ ፍፃሜ ደግሞ ከ04:07 ጀምሮ ይደረጋሉ። ሀብታሙ ምትኩ AradaFm_Sport

በማንችስተር ዩናይትድ ሲፈለግ የነበረው ተጫዋች አዲስ ውል ፈርሟል መስከረም 01፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኒውካስትል ዩናይትዱ የግራ መስመር ተከላካይ ሌዊስ ሀል በክለቡ አዲስ የውል ማራዘሚያ ፈ
በማንችስተር ዩናይትድ ሲፈለግ የነበረው ተጫዋች አዲስ ውል ፈርሟል መስከረም 01፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኒውካስትል ዩናይትዱ የግራ መስመር ተከላካይ ሌዊስ ሀል በክለቡ አዲስ የውል ማራዘሚያ ፈርሟል።። የ22 ዓመቱ ተጫዋች እስከ 2029 የሚያቆየው ውል የነበረው ቢሆንም በአዲሱ ውሉ እስከ 2031 በሴንት ጀምስ ፓርክ ለመቆየት ተስማምቷል። በ2023 ከቼልሲ ኒውካስትል ዩናይትድን የተቀላቀለው ሀል በ106 ጨዋታዎች ላይ ለክለቡ ተጫውቷል። ሀል በክረምቱ በማንችስተር ዩናይትድ በጥብቅ ሲፈልጉ ከነበሩ ተጫዋቾች መካከል አንዱ እንደነበር ይታወሳል። ሀብታሙ ምትኩ AradaFm_Sport

አርብ መስከረም 01/2019 ዓ.ም አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት! መልካም ቀን ! @Arada_Fm
አርብ መስከረም 01/2019 ዓ.ም አራዳ ኤፍኤም 95.1 ፤ ውለው የሚያመሹበት! መልካም ቀን ! @Arada_Fm

ከ600 በላይ እስረኞች በይቅርታና ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር ተለቀቁ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በሀይል ለመናድ ሞክረዋል በሚል ታስረው የነበሩ ግለሰቦች እንዲፈቱ
ከ600 በላይ እስረኞች በይቅርታና ክሳቸው ተቋርጦ ከእስር ተለቀቁ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን በሀይል ለመናድ ሞክረዋል በሚል ታስረው የነበሩ ግለሰቦች እንዲፈቱ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን ከመንግስት ጋር ላለፉት 5 ወራት ጥረት ሲያደርግ መቆየቱን አስታውቋል። በፍርድ ቤት ውሳኔ ታሰረው የነበሩት በይቅርታ፣ በክስ ሂደት ላይ የነበሩት ደግሞ ክሱ እንዲቋረጥ ተደርጎ ከ600 በላይ እስረኞች በዛሬው እለት እንዲፈቱ መደረጉን የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽነር ብርሃኑ አዴሎ ገልጸዋል። ይህ ቁጥር ክልሎች በየራሳቸው ከሚፈቷቸው ውጭ መሆኑ የተገለጸ ሲሆን፣ የተፈቱት እስረኞች ከአማራና ከኦሮሚያ ክልል በፌደራል ደረጃ የታሰሩ እንደነበሩም ተነግሯል። በይቅርታ ከመፍታትና ክስ ከማቋረጥ በተጨማሪም በህግ የታገዱ መብቶቻቸው እንዲመለሱ መደረጉ ተገልጿል። በተመሳሳይ መዝገብ የሚገኙ 28 የሚሆኑ እስረኞች የይቅርታ ጥያቄ ባለማቅረባቸው ከእስር አለመፈታታቸውን ኢሰመኮ አስታውቋል። የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm  Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

በዚህ የይቅርታ ሂደት የተፈቱ ወገኖች በሀገራዊ ምክክር ምክረ ሐሳቦች ላይ አዎንታዊ ሚና ይጫወታሉ ተብሎ ይታመናል። ካለፈው መንገድ በመማር የወደፊቱን መንገድ የሰላምና የዴሞክራሲ መንገድ ያደርጉታል ተብሎ ተስፋ ተደርጓል። ማኅበረሰቡም እነዚህ ወገኖች በሀገር ሰላምና ልማት የበኩላቸውን አስተዋጽዖ እንዲያደርጉ ማገዝና መምከር አለበት። መነጋገር፣ መከራከርና መፎካከር ሲቻል ግጭትና ጦርነት አዋጪ አይደለም። የብዕርና የሐሳብ ጊዜ እንጂ የጠመንጃ እና የጉልበት ጊዜ አልፏል። የኢትዮጵያ የዘመን መጽሐፍ ካሁን በኋላ የጠመንጃና የጉልበት ታሪክን አይመዘግብም። በታሪካችን ውስጥ በቂ ግጭቶችና ጦርነቶች መኖራቸውን የዘመን መጽሐፋችን አሳይቶናል። ቀጣዩ ምእራፍ አዳዲስ መንዶችን እንጂ አሮጌ አካሄዶችን አይመዘግብም።  ቀጣዩ ዓመት የጉባ ብሥራቶችን የበለጠ ተግባራዊ የምናደርግበት ዘመን ይሆናል። የፖለቲካ ምኅዳሩ ሰፍቶ የተለያዩ ዕሳቤዎችንና አካሄዶችን በብሔራዊ ጥቅም አስተሣሥረን የምንጓዝበት ዓመት ይሆናል። ሁለንተናዊ ሉዓላዊነታችን ይበልጥ የሚከበርበት፣ ኅብረ ብሔራዊ አንድነታችን ይበልጥ የሚጸናበት፣ በሁሉም ዘርፎች የጀመርነው ምርታማነት በዓይነትና በጥራት የሚጨምርበት፣ ሀገራችንም የቀጣናውና የአፍሪካ መሪነቷን ሥር መሠረት የምታስይዝበት፤ የኢትዮጵያ ብልጽግና ትውልድ ተሻጋሪ እንዲሆን ተደርጎ የሚገነባበት ዓመት ይሆናል። ይህ እንዲሳካ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተሳትፎ፣ የልሂቃን ሚና፣ የሃይማኖት አባቶች ጸሎት፣ የጸጥታ ተቋማት ጥንካሬና ቁርጠኝነት፣ የአምራች ኢንዱስትሪው ትጋትና ብርታት፣ የንግዱ ማኅበረሰብ ቅልጥፍናና ለሕዝብ አሳቢነት፣ የገበሬውና የአርሶ አደሩ አይበገሬነት፣ የወጣቶችና ሴቶች ያላሰለሰ ጥረት፣ የሚዲያዎች ሐቀኝነት፣ የዲጂታል ዘርፉ ዘመናዊነት፣ የሲቪል ሰረቫንቱ ንጽሕናና አገልግሎት፣ እጅግ ወሳኞች ናቸው። አዲሱ ዓመት በኢትዮጵያ የዘመን መጽሐፍ ላይ አዲስ ታሪክ፣ አዲስ ሐሳብና አዲስ ሥልጣኔ የምንጽፍበት እንደሚሆን ተስፋ አደርጋለሁ። ይህ እንደሚሆንም አምናለሁ። ፈጣሪም እንደሚረዳን እተማመናለሁ። መልካም አዲስ ዓመት። ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!! ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ! ጳጉሜን 5፣ 2018 ዓ.ም

ዘምዘም ባንክ በእንግሊዝ ለንደን ከተማ በተካሄደው 16ኛው የግሎባል ኢስላሚክ ፋይናንስ አዋርድ ሽልማት ስነ ስርዓት ላይ ሀገራችን ኢትዮጵያን በኩራት የሚያስጠራ ታላቅ ድልን አስመዘገበ! በለንደን የኢ
+2
ዘምዘም ባንክ በእንግሊዝ ለንደን ከተማ በተካሄደው 16ኛው የግሎባል ኢስላሚክ ፋይናንስ አዋርድ ሽልማት ስነ ስርዓት ላይ ሀገራችን ኢትዮጵያን በኩራት የሚያስጠራ ታላቅ ድልን አስመዘገበ! በለንደን የኢትዮጵያ ኤምባሲ ምክትል ሚሲዮን ኃላፊ ክቡር አምባሳደር ላሊሳ ብርሃኑ፣ በ16ኛው ግሎባል ኢስላሚክ ፋይናንስ አዋርድ የሽልማት ስነ ስርዓት ላይ ዘምዘም ባንክን ወክለው በመገኘት ግሎባል ኢስላሚክ ፋይናንስ ሽልማት 2026 የሻምፒዮንሺፕ ሽልማትን በወለድ ነጻ ባንክ ዘርፍ በኩራት ተቀብለዋል። ይህ ታላቅ ክብር ያለው የግሎባል ኢስላሚክ ፋይናንስ ሽልማት 2026 የሻምፒዮንሺፕ ሽልማት ዘምዘም ባንክ በሀገራችን ሸሪዓን መሠረት ያደረገ ፣ሁሉን አቀፍ፣ ፈጠራን ያማከለ እና ዘላቂ የፋይናንስ አገልግሎቶችን ለማስፋፋት ላለው ቁርጠኝነት እንዲሁም በኢትዮጵያ የፋይናንስ ዘርፍ ውስጥ እየተካሄደ ባለው ፈጣን ለውጥ ላበረከተው አስተዋፅኦ የተሰጠ ዓለም አቀፍ እውቅና ነው። ይህን ታላቅ ክብር በዘምዘም ባንክ ስም በመቀበል ላደረጉት ከፍተኛ ድጋፍ ለክቡር አምባሳደር ላሊሳ ብርሃኑ ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን። ለደንበኞቻችን፣ ለባለአክሲዮኖቻችን፣ ለዳይሬክተሮች ቦርድ፣ ለአመራሩ እና ለመላው የዘምዘም ባንክ ሰራተኞች የኩራት ምንጭ ብቻ ሳይሆን ኢትዮጵያ በዓለም አቀፉ የእስላሚከሰ ፋይናንስ ዘርፍ እድገት እያደረገች ያለችውን ከፍተኛ አስተዋጽዖ የሚያሳይ ታላቅ ምስክር ነው። ከዚህ በተጨማሪ ለዚህ ስኬት መሠረት ለሆኑት ደንበኞቻችን፣ ባለአክሲዮኖቻችን፣ የዳይሬክተሮች ቦርዳችን፣ አመራሩ እና መላው የባንኩ ሠራተኞች ላበረከታችሁት የማይተካ ሚና ፣ ቁርጠኝነት እና ያላሰለሰ ጥረት ልባዊ ምስጋናችንን እናቀርባለን #ዘምዘም ባንክ የማይነጥፍ የእድገት ምንጭ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት የዘመን መለወጫን አስመልክተው መልዕክት አስተላልፈዋል። ቅዱስነታቸው ለመላው ኢትዮጵያውያን ወገኖች እንኳን ለአዲሱ ዘመን በሰላም አደረሳችሁ በማለት አባታዊ መልእክት አስተላልፈዋል። ብፁዕነታቸው በመልዕክታቸው አዲሱን ዓመት ባለፈው ዓመት የተከሰቱ መጥፎ ክስተቶችን እና ድርጊቶችን ባለመድገም እና በመተው መቀበል ይገባል ብለዋል። መላው ኢትዮጵያውያን አገራቸውን የጋራ ዕድልና ሃብት አድርገው በመቀበል ልዩነቶችን ጊዜ በመስጠት በውይይት እና በመግባባት በመፍታት በአንድነት እንዲቀጥሉም አባታዊ ጥሪ አቅርበዋል። በመልዕክታቸውም “በይቅርታ መንፈስ፣ በአንድነት ተቃቅፎ ከመቀጠል ውጭ ሌላ የተሻለ ዕድል እንደሌለ በውል ተገንዘቡ፤ ለዚህ ሁላችሁም የበኩላችሁን ልባዊ ጥረት ከማድረግ አትቆጠቡ ብለን ከልብ እንመክራለን” ብለዋል። “ለሁሉም መድኃኒቱ ቀና አዕምሮ በመሆኑም በአዲሱ ዓመት እግዚአብሔር ቅንና በጎ አሳቢ አእምሮ እንዲሰጠን እና በእርሱም ያሉብንን ጉድለቶች አርመንና አስተካክለን ሰላም የሰፈነበትን የመጽናናት ዘመን ማየት እንችል ዘንድ እግዚአብሔርን እንለምን” ሲሉም አባታዊ መልዕክት አስተላልፈዋል። የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

አዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ 21 ጊዜ መድፍ ይተኮሳል ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ነገ መስከረም 1 ቀን 2019 ዓ.ም የሚከበረውን የአዲስ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ 21
አዲስ ዓመት በዓልን ምክንያት በማድረግ 21 ጊዜ መድፍ ይተኮሳል ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ነገ መስከረም 1 ቀን 2019 ዓ.ም የሚከበረውን የአዲስ ዓመት በዓል ምክንያት በማድረግ 21 ጊዜ መድፍ እንደሚተኮስ መከላከያ ሚኒስቴር አስታወቀ። ከንጋቱ 12 ሠአት ላይ 21 ጊዜ መድፍ የሚተኮስ በመሆኑ ነዋሪዎች በጉዳዩ ላይ ተገቢው መረጃ እንዲኖራቸው ሲል የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ አስታውቋል። የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

የምክክር ውጤቶች እስከ መስከረም 10 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባሉ - ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮ
የምክክር ውጤቶች እስከ መስከረም 10 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባሉ - ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገራዊ ምክክር ጉባዔዎች የተገኙ ምክረ ሀሳቦችን ወደ ተግባር ለመለወጥ የሚያስችል ሰነድ ቀርጾ ለሚመለከታቸው አካላት እንደሚያቀርብ አስታውቋል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጉዞ በምክክር ማጠቃለል መቻሉ አዲስ ተስፋ የፈነጠቀ ታላቅ ክንውን መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሂደት ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን በውይይት ፈትተው ወደ የጋራ መግባባት መምጣት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየበት ሂደት ነው ብለዋል። ፕሮፌሰር መስፍን አክለውም፣ በ2018 ዓ.ም የተገኘው ታሪክ ቀያሪ ውጤት ምሉዕ የሚሆነው በአዲሱ ዓመትና በቀጣይ ዘመናት በተግባር ሲረጋገጥ መሆኑን ጠቁመዋል። ኮሚሽኑም በቀሪው የሥራ ጊዜው የምክክሩን ውጤት ዳር ለማድረስ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ተጨማሪ ለማንበብ https://web.facebook.com/share/p/1DfnBVDVE2/ የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

የምክክር ውጤቶች እስከ መስከረም 10 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባሉ - ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮ
የምክክር ውጤቶች እስከ መስከረም 10 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ይቀርባሉ - ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በሀገራዊ ምክክር ጉባዔዎች የተገኙ ምክረ ሀሳቦችን ወደ ተግባር ለመለወጥ የሚያስችል ሰነድ ቀርጾ ለሚመለከታቸው አካላት እንደሚያቀርብ አስታውቋል። የኮሚሽኑ ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን ዓርዓያ ዛሬ በሰጡት መግለጫ በ2018 ዓ.ም የኢትዮጵያ ጉዞ በምክክር ማጠቃለል መቻሉ አዲስ ተስፋ የፈነጠቀ ታላቅ ክንውን መሆኑን ገልጸዋል። ይህ ሂደት ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን በውይይት ፈትተው ወደ የጋራ መግባባት መምጣት እንደሚችሉ በተግባር ያሳየበት ሂደት ነው ብለዋል። ፕሮፌሰር መስፍን አክለውም፣ በ2018 ዓ.ም የተገኘው ታሪክ ቀያሪ ውጤት ምሉዕ የሚሆነው በአዲሱ ዓመትና በቀጣይ ዘመናት በተግባር ሲረጋገጥ መሆኑን ጠቁመዋል። ኮሚሽኑም በቀሪው የሥራ ጊዜው የምክክሩን ውጤት ዳር ለማድረስ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ እንደሚሠራ አረጋግጠዋል። ተጨማሪ ለማንበብ https://web.facebook.com/share/p/1DfnBVDVE2/ የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

የትራምፕ የ5 ሺህ ዶላር ስጦታ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአጋማሽ ዘመን ምርጫው ሪፐብሊካን ፓርቲ ካሸነፈ ለእያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5 ሺህ ዶላ
የትራምፕ የ5 ሺህ ዶላር ስጦታ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በአጋማሽ ዘመን ምርጫው ሪፐብሊካን ፓርቲ ካሸነፈ ለእያንዳንዱ አዋቂ አሜሪካዊ 5 ሺህ ዶላር ይሰጣል አሉ። ትራምፕ ፓርቲያቸው በምርጫው በሁለቱም ምክር ቤቶች ካሸነፈ ስጦታውን እሰጣለሁ ሲሉ ተደምጠዋል። የሪፐብሊካን ፓርቲ ለመጀመሪያ ጊዜ ባካሄደው የፕሬዚዳንታዊ የአጋማሽ ዘመን ጉባኤ ላይ የተናገሩት ዕቅድ ከ1 ትሪሊየን ዶላር በላይ ወጪ የሚያስወጣ መሆኑን ቢቢሲ አስነብቧል። ፕሬዚዳንቱ ስለ ገንዘቡ ምንጭ እና የዕቅዱን አተገባበር ያልገለጹ ሲሆን፥ ይህ ገንዘብ አሜሪካ ውስጥ ብቻ ፈሰስ ይደረጋል ብለዋል። ሃሳቡን ያጣጣሉት ዴሞክራቶች ደግሞ የፕሬዚዳንቱን ዕቅድ “ባዶ ተስፋ” ሲሉት፥ አንዳንድ አባላቱ ደግሞ የመሰል ቃል ሕጋዊነት ላይ ጥያቄ አንስተዋል። ይህ የትራምፕ ዕቅድ በፕሬዚዳንት ቃል የተገባ የመጀመሪያው ሲሆን፥ ዕቅዱ ተግባራዊ ስለመሆን አለመሆኑ ግን አሁንም ጥያቄዎች እየተነሱ ነው። በአሜሪካ 270 ሚሊየን አዋቂዎች እንደሚገኙ ሲታመን ይህ ሃሳብ እውን ቢሆን የትራምፕ አስተዳደር 1 ነጥብ 3 ትሪሊየን ዶላር ወጪ ያወጣል። ይህን መሰሉ ትልቅ ወጪ ደግሞ አሜሪካ በቅርቡ ከኢራን ጋር የገባችበት የመካከለኛው ምስራቅ ጦርነት ካስከተለው ኢኮኖሚያዊ ጫና ጋር ተያይዞ የሀሳቡ ተፈፃሚነት ላይ ጥያቄን አጭሯል። ምናለ ብርሀኑ የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሞጆ የተገነባውን ዘመናዊ የሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፊያ የመጀመሪያ ምዕራፍ መረቁ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሞጆ በ60
+8
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ በሞጆ የተገነባውን ዘመናዊ የሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፊያ የመጀመሪያ ምዕራፍ መረቁ ጳጉሜን 5፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሞጆ በ60 ሄክታር መሬት ላይ የተገነባውን ዘመናዊ የሎጂስቲክስ ማዕከል ማስፋፊያ የመጀመሪያ ምዕራፍ አስመርቀዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት ፅሁፍ ማስፋፊያው ለኢትዮጵያ ብሎም ለአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ስኬት ትልቅ ሚና የሚጫወት እና በዓመት እስከ 1 ሚሊየን ባለ 20 ጫማ ኮንቴነሮች የማስተናገድ አቅም ያላቸው ጣቢያዎችና ዘመናዊ መጋዘኖች ያሉት ነው ብለዋል። ከዚህ በተጨማሪም የደረቅ ብትን ጭነቶችን በሀገር ውስጥ ለማሸግ የሚያስችል እና የውጭ ምንዛሬን ከመቆጠብ ባለፈ ለዜጎች ሰፊ የሥራ ዕድል የሚፈጥር መሆኑንም ገልጸዋል። “የማዕከሉን የአሰራር ፍጥነት ለማሳደግ በሀገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ የተተከለው የባቡር ላይ ክሬን ከባቡር መስመር የሚደረገውን የኮንቴነር ዝውውር በከፍተኛ ፍጥነት ያከናውናል” ብለዋል። ተጨማሪ ለማንበብ https://web.facebook.com/share/p/19ni6P85ma/ የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1 Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical Telegram:-https://t.me/Arada_Fm Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm @Arada_Fm