Arada FM 95.1 - አራዳ ኤፍኤም 95.1
Открыть в Telegram
4 297
Подписчики
-524 часа
-87 дней
-5830 день
Архив постов
+2
የመንገድ ትራፊክ ደህንነት በጎ ፍቃድ አገልግሎት ተጀመረ
ሰኔ 21፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕዝብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን በዛሬው ዕለት የትራፊክ ደህነት በጎ ፍቃድ አገልግሎትን አስጀምሯል።
ኮሚሽኑ ከአዲስ አበባ ትራፊክ ማኔጅመንት ኤጀንሲ ጋር በመተባበር በክረምት ወቅት የሚከሰተውን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ ያለመ የበጎ ፈቃደኞች ሥራውን በይፋ ማስጀመሩን በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሕዝብ ተሳትፎና በጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ኮሚሽን ኮሚሽነር አቶ ይመር ከበደ ተናግረዋል።
ለክረምቱ በጎ አድራጎት ስራ 10 ሺህ ተሳታፊ እንደሚኖርበት የተገለፀ ሲሆን በሀገራችን እየተከሰተ ያለውን የትራፊክ አደጋ ለአሽከርካሪዎችና ለእግረኞች ተገቢውን ግንዛቤ በመፍጠር ለመቀነስ የታለመ መሆኑን ጠቅሰዋል።
በሆስፒታል የበጎ ፈቃድ ስራ፣ የስፓርት ንቅናቄ፣ የሙያ፣ የቤተመፅሐፍት፣ የመጀመሪያ እርዳታ ስልጠና እና ሌሎች የበጎ ፈቃድ አገልግሎት ዘርፍ ናቸው ተብሏል።
የ2018 ዓ.ም በጎ ፈቃድ አገልግሎት 9.4 ቢሊየን ብር የሚገመት ወጪን ለማዳን ታቅዶ እየተሰራ ነው።
በጎ ፈቃድ አገልግሎት የሕሊና፣ የመተባበር እና ምንም ዓይነት ክፍያን ሳይጠይቁ፣ እንዲሁም ጾታንና ቦታን ሳይለዩ የሚከናወን በጎ ተግባር ስለመሆኑ የኮሚሽኑ ምክትል ኮሚሽነር ወ/ሮ አስራት ንጉሴ ለጣቢያችን ገልፀዋል።
ሰናይት በየነ
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የዓለም ዋንጫ የጥሎ ማለፍ ድልድል
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የኔዜማ የአድማጮች የሙዚቃ ምርጫ ዘውትር እሁድ ከ 3:00-5:00 በአራዳ ኤፍ ኤም 95.1 ይደመጣል፡፡
ለዛሬ የመርጥነው ሙዚቃዎች…
-ድምፃዊ ሄኖክ አበበ (ልዩ ቀን)
-ድምፃዊ ግርም መዝሙር (ልጅነቴ)
-መስፍን በቀለ(ነይ በክረምት)
-ድምፃዊት ኤደን አሸሹም(ፈራ ተባ)
ከተለያዩ ቦታ አድማጮች እየተሳተፋችሁ ለወዳጅ፣ለዘመድ፣ ለፍቅር አጋሮ በቀጥታ መስመር እየገባችሁ መጋበዝ ትችላላችሁ፡፡ ስልኮቻችን 011 5 58 54 31 ወይም 011 5 58 54 32 ይደውሉ፡፡
አዘጋጅ እና አቅራቢ፡ ተመስገን ኡካሬ
ድሬዳዋ ከተማ ከሊጉ ወረደ
ሰኔ 20፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በ ሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ድሬዳዋ ከተማ ከሀድያ ሆሳዕና ጋር 1 ለ 1 ተለያይቷል።
የሀድያ ሆሳዕናን ጎል ብሩክ በየነ ሲያስቆጥር ለድሬዳዋ ከተማ አቤል ነጋሽ ከመረብ አሳርፏል።
ውጤቱን ተከትሎ ድሬዳዋ ከተማ ከሊጉ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል።
ድሬዳዋ ከተማ መቐለ 70 እንደርታ እና አርባምንጭ ከተማን በመከተል ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረደ ሶስተኛው ክለብ ሆኗል።
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የዓለም ዋንጫ የምድብ ጨዋታዎች
ሰኔ 20፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ዛሬ ይደረጋሉ።
ሌሊት 11 ሠአት የዓለም ሻምፒዮኗ አርጀንቲና ከዮርዳኖስ ጋር ትጫወታለች።
በሌላ ጨዋታ ኦስትሪያ ከአልጄሪያ ጋር ጥሎ ማለፉን ለመቀላቀል ይጫወታሉ።
ሌሊት 8:30 ሠአት ፖርቹጋል ከኮሎምቢያ ጋር ጨዋታዋን ታደርጋለች።
ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ምርጥ ሦስተኝነትን ለማግኘት ከኡዝቤኪስታን ጋር ትጫወታለች።
6 ሠአት ላይ እንግሊዝ ከፓናማ እንዲሁም ጋና ከክሮሺያ ዛሬ የሚደረጉ ሌሎች ጨዋታዎች ናቸው።
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የአቢሲኒያ ባንክ የምንዛሪ ተመን
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
+3
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ76ኛ ጊዜ ተማሪዎችን አስመረቀ
ሰኔ 20፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ለ76ኛ ዙር ያስተማራቸውን 6 ሺህ 417 ተማሪዎችን አስመርቋል።
ከተመራቂዎቹ መካከል 2 ሺህ 646 ሴቶች ናቸው።
3 ሺህ 542 የመጀመሪያ ዲግሪ እና 2 ሺህ 241 ደግሞ በሁለተኛ ዲግሪ የተመረቁ ሲሆን፤ 377 የሶስተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች ናቸው።
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የተረጋገጡ የጥሎ ማለፍ ድልድሎች
ሰኔ 20፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በዓለም ዋንጫው ሰባት የአፍሪካ አገራት ጥሎ ማለፉን ሲቀላቀሉ የቢየልሳዋ ኡራጋይ ተሰናብታለች።
ግብፅ
ደቡብ አፍሪካ
ኮት ዲቯር
ኬፕ ቨርዴ
ሞሮኮ
ጋና
ሴኔጋል እስከ አሁን ጥሎ ማለፉን መቀላቀላቸውን ያረጋገጡ የአፍሪካ አገራት ናቸው።
የተረጋገጡ መርሐ ግብሮች
ጀርመን ከ ፓራጓይ
ፈረንሳይ ከ ስዊድን
ደቡብ አፍሪካ ከ ካናዳ
አሜሪካ ከ ቦስኒያ
ብራዚል ከ ጃፓን
ኮትዲቯር ከ ኖርዌይ
አርጀንቲና ከ ኬፕቨርዴ
ኔዘርላንድስ ከ ሞሮኮ
ኦስትሪያ ከ ግብጽ
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የንብ ባንክ የምንዛሪ ተመን
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
ሴኔጋል ጥሎ ማለፉን ተቀላቀለች
ሰኔ 20፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በዓለም ዋንጫው የምድብ የመጨረሻ ጨዋታ ሴኔጋል ኢራቅን 5 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፋለች።
የሴኔጋልን ጎሎች ፓፔ ጉዬ ፤ ንዳዬ ፤ እስማኤል ሳር እና ሀቢብ ዲያራ አስቆጥረዋል።
ሴኔጋል ማሸነፏን ተከትሎ ምርጥ ሶስተኛ ሆና ጥሎ ማለፉን ተቀላቅላለች።
በሌላ ጨዋታ ፈረንሳይ ኖርዌይን 4 ለ 1 በሆነ ውጤት አሸንፋለች።
ፈረንሳይ ምድቡን በአንደኝነት ስታጠናቅቅ ኖርዌይ ሁለተኛ ሆና ጨርሳለች።
በሌላ ምድብ ቤልጂየም ኒውዝላንድን 5 ለ 1 ስታሸንፍ ግብፅ ከኢራን አንድ አቻ ተለያይተዋል።
በጥሎ ማለፉ ፈረንሳይ ከስዊድን እንዲሁም ኖርዌይ ከኮትዲቯር ጋር ይጫወታሉ።
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
መቐለ 70 እንደርታ ከሊጉ ወረደ
ሰኔ 19፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በሲቢኢ የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ 37ኛ ሳምንት መርሐ ግብር ኢትዮጵያ ቡና መቐለ 70 እንደርታን 3 ለ 0 አሸንፏል።
የቡናማዎቹን ጎሎች ቢኒያም ጌታቸው 2x እና ዲቫይን ዋችኩዋ አስቆጥረዋል።
መቐለ 70 እንደርታ መሸነፉን ተከትሎ ከሊጉ ወደ ከፍተኛ ሊግ መውረዱ ተረጋግጧል።
መቐለ 70 እንደርታ አርባምንጭ ከተማን በመከተል ወደ ከፍተኛ ሊግ የወረደ ሁለተኛው ክለብ ሆኗል።
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ ያዘጋጀው የፓናል ውይይት ሊካሄድ ነው
ሰኔ 19፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ሳይንስ አካዳሚ "ሰው ሠራሽ አስተውሎት እና ኪነጥበብ” በሚል ያዘጋጀው አገር አቀፍ የፓናል ውይይት ሊካሄድ ነው።
"ሰው ሠራሽ አስተውሎት ለኪነጥበብ ዕድሉ፣ ተግዳሮቱ እና መፍትሔው" በሚል ርዕስ ያዘጋጀውን አገር አቀፍ የፓናል በአካዳሚው መሰብሰቢያ አዳራሽ ነው የሚያካሂደው።
ይህ በዕውቀትና በመረጃው ዓለም ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ እየፈጠረ በሚገኘው በሰው ሠራሽ አስተውሎት ዙሪያ የተዘጋጀው መድረክ፥ አካዳሚው በዘርፉ ካቀዳቸው ተከታታይ ውይይቶች የመጀመሪያው ነው ተብሏል።
በተለይም ፍላጎት ያላቸው የኪነጥበብ ባለሙያዎች፣ የቴክኖሎጂ ተመራማሪዎችና የኅብረተሰብ ክፍሎች በነፃ እንዲሳተፉ ጥሪ ቀርቧል።
በዶክተር ብርሃኑ በሻህ ሰብሳቢነት በሚመራው በዚህ መድረክ ላይ በርካታ አንጋፋ ምሑራን ጥናታዊ ጽሑፎችን ያቀርባሉ።
ተጨማሪ ለማንበብ https://www.facebook.com/share/p/18oAxiexgo/
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የደራሲ አጋዝ ገብረኢየሱስ ኃይለማርያም መፅሐፍ ነገ ይመረቃል
ሰኔ 19፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የመጀመሪያውን የጉራጊኛ ረጅም ልቦለድ ‘የጫሙት ሽካ’ በመጻፍ የሚታወቁት አንጋፋው ደራሲ አጋዝ ገብረኢየሱስ ኃይለማርያም፣ ‘የሕይወት መንገድ’ የተሰኘውን መፅሐፋቸውን ነገ ሊያስመርቁ ነው።
በብርሃነ ዓለሙ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ ከጠዋቱ 2:30 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ይመረቃል።
ደራሲ አጋዝ ገብረኢየሱስ በጉራጊኛ፣ በአማርኛና በእንግሊዝኛ ቋንቋዎች 16 መጽሐፍትን ለንባብ ያበቁ ሲሆን፥ ለጉራጌ ቋንቋ፣ ባህልና አንድነት ላቅ ያለ አስተዋጽኦ አበርክተዋል።
እንዲሁም የጉራጌ ሕዝብ ራስ አገዝ ልማት ድርጅት (ጉህራልድ) መሥራች በመሆን በማኅበረሰብ ልማት ዘርፍ ጉልህ ሚና ተጫውተዋል።
ለገበያ የሚበቃው ‘የሕይወት መንገድ’ የተሰኘው አዲሱ መጽሐፍ ከተለመዱት የራስ ሕይወት ታሪክ ሥራዎች በተለየ መልኩ፥ ደራሲው ያሳለፉትን የተኖረ ሕይወትና ተሞክሮዎች በማንፀባረቅ ለሌሎች የሚተርፍ ሰፊ መረጃና ዕውቀት ያካተተ መሆኑ ተገልጿል።
በምረቃ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ ከመንግሥት፣ ከደራሲያን ማኅበር፣ ከባህልና ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተውጣጡ እንግዶች የሚገኙ ሲሆን፥ ለደራሲውም ልዩ የዕውቅና መርሐ-ግብር እንደሚበረከትላቸው ተወዳጅ ሚዲያ ያደረሰን መረጃ አመላክቷል።
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
+1
የ3 ቢሊየን ብር የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት መልሶ ግንባታ ፕሮጀክት ተፈረመ
ሰኔ 19፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አልፋና ካፒታል ከተሰኙ የኢንጂነሪንግ እና ዕቃ አቅራቢ ተቋማት ጋር የ3 ቢሊየን ብር የመልሶ ግንባታ ፕሮጀክት ስምምነት ተፈራርሟል፡፡
የአገልግሎቱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ጌቱ ገረመው (ኢ/ር) በዚህ ወቅት እንዳሉት÷ ፕሮጀክቱ በከተሞች ያለውን የኤሌክትሪክ አቅርቦት በማሻሻል ደንበኞች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲያገኙ ያስችላል፡፡
ፕሮጀክቱ በተያዘለት የጊዜ ገደብና በተጠበቀው የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቅ በትኩረት መስራት እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል፡፡
በአምቦ፣ ነቀምቴ እና አሶሳ ከተሞች የሚከናወነው ፕሮጀክቱ በከተሞቹ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶችን በማዘመንና በማጠናከር የአገልግሎቱን አስተማማኝነት ለማሳደግ ያስችላል፡፡
በመልሶ ግንባታና የማሻሻያ ፕሮጀክቱ 325 ኪሎ ሜትር የመካከለኛ ቮልቴጅ የኤሌክትሪክ መስመር የማሻሻያ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ተመላክቷል፡፡
ይህም የኔትወርኩን አቅም ከማሳደግ ባለፈ የኃይል መቆራረጥ እና የቴክኒክ ችግሮችን ለመቀነስ እንደሚረዳ ነው የተገለጸው፡፡
በተጨማሪም 235 ትራንስፎርመሮች ላይ የማሻሻያና የመልሶ ግንባታ ሥራ የሚከናወን ሲሆን ÷ ከእነዚህ ውስጥም 70 በአምቦ፣ 121 በነቀምቴ እና 44 በአሶሳ እንደሚከናወን ተጠቁሟል፡፡
በሁለት ዓመት ውስጥ የሚጠናቀቀው ፕሮጀክቱ ከዓለም ባንክ በተገኘ የ3 ቢሊየን ብር ድጋፍ የሚተገበር ነው፡፡
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የአራዳ የሳምንቱ ዓለም አቀፍ ዐበይት ዜናዎች ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች
ሰኔ 19፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በ23ኛው የዓለም ዋንጫ የምድብ የመጨረሻ ጨዋታዎች ምሽት 4:00 ሠአት ጀምሮ ይደረጋሉ።
የምድቡን መሪ ለመለየትና የምርጥ ሦስተኛ ደረጃ ዕድልን ለመጠቀም ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ።
በምድብ 9 ፈረንሳይ በምድቡ የመጨረሻ ጨዋታ ከኖርዌይ ጋር የምትገናኝ ሲሆን፥ ምድቡን በበላይነት ለማጠናቀው ብርቱ ፉክክር ያደርጋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
በሌላኛው ጨዋታ ሴኔጋል ከኢራቅ ጋር የምትገናኝ ሲሆን፥ ምርጥ ሦስተኛ ሆና ጥሎ ማለፉን ለመቀላቀል በበርካታ የጎል ልዩነት ማሸነፍና የሌሎች ምድቦችን ውጤቶች ትጠብቃለች።
ሌሊት 9:00 ሠአት ላይ በምድብ 8 ዩራጓይ ከ ስፔን እንዲሁም ኬፕ ቨርዴ ከ ሳዑዲ አረቢያ ይገናኛሉ።
ስፔን ምድቡን በ4 ነጥብ ስትመራ ዩራጓይ እና ኬፕ ቨርዴ በእኩል 2 ነጥብ ይከተላሉ።
ማለዳ 12:00 ደግሞ በምድብ 7 ግብፅ ከ ኢራን ኒውዝላንድ ከ ቤልጂየም የሚያደርጉት ጨዋታም ተጠባቂ ነው።
ምድቡን ግብፅ በ4 ነጥብ ስትመራ ኢራን እና ቤልጂየም በእኩል 2 ነጥብ ይከተላሉ።
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
+1
‘ዛጎል’ ዘመናዊ የጉዞ መተግበሪያ ተመረቀ
ሰኔ 19፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) የኢትዮጵያን የጉዞ እና የቱሪዝም ዘርፍ በዲጂታል የሚያሻግረውና ሁሉን አቀፍ አገልግሎት የሚሰጠው ‘ዛጎል’ (Zagol Super App) ዘመናዊ የጉዞ መተግበሪያ በይፋ ተመርቋል።
የሀገር ውስጥ እና ዓለም አቀፍ ተጓዦች የአውሮፕላን ጉዞዎችን ጨምሮ ሁሉንም አገልግሎቶች በአንድ ቦታ በኦንላይን በቀላሉ ማግኘት የሚያስችላቸው ‘ዛጎል’ (Zagol Super App) የተሰኘው አዲስ የጉዞ መተግበሪያ በይፋ ስራ መጀመሩን የዛጎል ቴክኖሎጂ ተቋም አስታውቋል።
መተግበሪያው ደንበኞች ካሉበት ቦታ ሆነው ያለምንም እንግልት የጉዞ ፍላጎቶቻቸውን እንዲያሳኩ የሚያስችል ነው ተብሏል።
መተግበሪያው ሁሉንም የጉዞ ፍላጎቶች በአንድ ስር የሚያሟላ “Super App” ሲሆን በሰባት የተለያዩ ቋንቋዎች አገልግሎት እንደሚሰጥ ተገልጿል።
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
በደቡብ አፍሪካ በሌሎች አገራት ላይ ያንዣበበው ስጋት
ሰኔ 19፣ 2018 (አራዳ ኤፍ ኤም) በደቡብ አፍሪካ ስደተኛ ጠል ቡድኖች ከተለያዩ የአፍሪካ አገራት የመጡ ዜጎች እስከ ፈረንጆቹ ሰኔ 30 ቀን ድረስ ለቀው እንዲወጡ ካስቀመጡት ቀነ ገደብ መቃረብ ጋር ተያይዞ ስጋት ተስተውሏል።
“መጤዎች አገራችንን ለቀው ይውጡልን” የሚሉት እነዚህ ቡድኖች በተለያዩ ከተሞች ሰልፎችን ጠርተዋል።
የአገሪቱ ፖሊስም ከዚህ ጋር ተያይዞ ይፈጠራል ያለውን የፀጥታ ችግር ለመቆጣጠር ዝግጅት አድርጌያለሁ ቢልም የሚስተዋለው ድባብ ግን ከተለያዩ አገራት ለመጡ ዜጎች አስጊ መሆኑን መገናኛ ብዙሃን እያስነበቡ ነው።
‘ማርች እና ማርች’ የሚባለው ቡድንም የሌሎች አገራት ዜጎች ቀነ ገደቡን አክብረው ይውጡልን እያለ ነው።
ከዚህ ባለፈም በዕለቱ በመላው ደቡብ አፍሪካ ምንም አይነት የሥራ እንቅስቃሴ እንዳይኖርም ጠይቋል።
ተጨማሪ ለማንበብ https://web.facebook.com/share/p/1AJTM1KxtT/
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የሳምንቱ የሀገር ውስጥ ዐበይት ዜናዎች ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
የንብ ባንክ የምንዛሪ ዋጋ
የአራዳን ገጾች በመወዳጀት ቤተሰብ ይሁኑ
Youtube:https://www.youtube.com/@aradafm95.1
Tiktok:https://www.tiktok.com/@aradafm95.1offical
Telegram:-https://t.me/Arada_Fm
Telegram:-https://t.me/aradaFmdigital
Facebook:-https://web.facebook.com/aradafm
@Arada_Fm
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
