cookie

We use cookies to improve your browsing experience. By clicking «Accept all», you agree to the use of cookies.

avatar

"Ke slfoch elocution"

@sunna

Show more
The country is not specifiedThe language is not specifiedThe category is not specified
Advertising posts
179
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days

Data loading in progress...

Subscriber growth rate

Data loading in progress...

Repost from ISLAM IS UNIVERSITY
<<የእብድ ገላጋይ ድንጋይ ያቀብላል>> ✍ አሚር ሰይድ ‼️ራዕይ በተግባር የሚቀረፅ ህልም እንጂ በአእምሮ ብቻ የምናስበዉ መዳረሻ አይደለም፡፡ አንድ ልጅ እናቱ ጋር ይኖራል ከዛም እንቁላል ይሰርቃል እናቱ ዝም አለችዉ ከዛ በሂደት የሌላ ሰዉ ዶሮ ይሰርቃል ከዛም ሌባ ሲባል እናቱም ስትቆጦ ልጁም"" እናቴ ምነዉ በእንቁላሉ በቀጣሽኝ ዶሮ ባልሰረኩ "" አላት.. ምን ለማለት ፈልጌ ነዉ ሞጣ ላይ ባደረጉት ድረጊት ስላልተቀጡ አሁንም በእነሱ አልፈረድም የእኛ ዝምታ ጥግ ደረሰ የእነሱ ጥጋብ ሞልቶ ፈሰሰ ችግሩ ከራሳችን ነው ጠንካራ ሁኖ ማሳየት አቃተን ተጠራቅመን የአገሪቱ ከግማሽ በላይ ነን እያሉ ወሬ ስም ብቻ ...የአሁን ዘመን ሙስሊም እሰዉ ቤት የሄደ እንግዳ ይመስል መሽለጥለጥ ማሽቃበጥ ይወዳል፡፡ የሀይማኖት መሪ ተብየዎች በተለያየ ጊዜ ሙስሊሞች ሲገደሉ ሲፈናቀሉ ለሙስሊሙ ከመድረስ ድምፅ ከማሰማት ይልቅ ከመንግስት ሹመኛ ጋር ፎቶ መነሳት ይቀላቸዋል፡፡ጠና ቢል ቢሰሩ ሰላማዊ ሰልፍ ወይ በየመስጊዱ ተቃዉሞ ከዛ ቆፍጠን ያለ የአቋም መግለጫ አንብቦ ይበተናል ሙስሊሙ ቁጣዉን በሰልፍ በመስጊድ ባነር አሰርቶ ፎቶ ተነስቶ በሚዲያ ይለቃል ከዛ ይረሳል በዛዉ ተድበስቦሶ ያልፋል፡፡ ከመንግስት ጎን ይለጠፉና የእብድ ገላጋይ ዲንጋይ ያቀብላል ነዉና ነገሩ መንግስት የጠቀሙ መስለዉ ሙስሊሙን ግን እንዲጎዳ ያደርጋሉ፡፡ ☞በሂደት የ ጎንደርን መስጅድ ለመገንባት እና ወንድሞቻችንን ለማቋቋም ተብሎ ገንዘብ ይሰበሰባል ....ዲኑን እየተጫወቱበት ያሉ የሴት ሊቀመንበር ሙነሺዶች ስለ ጎንደር ጥቃት ነሺዳ አዘጋጅተዉ ለአንድ ቀን ይለቀሳል....ከዛ በቲሸርትና በባነር የጎንደር ሙስሊሞች ህመም የኔም ህመም ነዉ ይባላል....ከዛስ .....ከዛማ ዝም ዝም ነዋ ሌላ ምን ይፈጠራል፡፡ ሙስሊሙ ልቡ በዱንያና በሴት ፍቅር ታዉሯል አዉርቶ ይቀራል ከዛ እነሱ እንደ ስለት በአመት አንዴ የሚፈልጉትን አጀንዳ ያስፈፅማሉ፡፡ ☞የሚገርመዉ አሁን ድረስ ብሄርን ከእስልምና የሚያስበልጥ መኖሩ ነዉ ...የዛሬ 2 አመት በፊት በፁሁፍ ስለአማራ ክልል ሙስሊም ፅፌ የአማራ ክልል የሚኖሩ ሙስሊሞች ተችተዉኝ ከቻናል ፁሁፉን ለመሰረዝ ተገድጄ አጥፍቸዋለሁ ..የዛን ጊዜ የተናገርኩት በሁለት አመቱ በጎንደር ሙስሊሞች ላይ ደረሰ ...ምን ዋጋ አለዉ በፊት ነበር እንጂ መጥኖ መደቆስ አሁን ምን ያደርጋል ድስት ጥዶ ማልቀስ እናም እኛ ሙስሊሞች የምናየዉ የዛሬን እና የነገን ብቻ ነዉ እንጂ ከትናንት ወዳ ምን ነበር? ከነገ ወዳስ የዛሬ አመትስ ምን ይፈጠራል?ብለን ማሰብ ስለማንችል እነሱ ግን ለወደፊት 50 ወይ 60 አመት ፕላን አዉጥተዉ ሲንቀሳቀሱ በእነሱ ወጥመድ እንወድቃለን፡፡ ስለ ኢትዮጲያ የምንሰማዉ የ13 ወር ፀጋ ነገር ግን የምናየዉ የ13 ወር ለሙስሊም ጥላቻ ነዉ፡፡ ☞ግን የጎንደር ሙስሊሞች በረመዳኑ በጥይት ያስፈጠሯቸዉ በአደባይይ ኢፍጣር ላይ የታቀደ ነበር ..ግን በቀብሩ ጀመሩት እንጂ ..ግን ይሄ የአደባባይ ኢፍጣር እኔ ብዙም አልተዋጠልኝ ጉዳቱ ግን አንደ ጎንደር ያሉ ሙስሊሞችን ዋጋ አስከፍሏል፡፡ እኛ ሙስሊሞች የምንዋረደዉ በሱና በኸይር ስራ መሸቀዳደም ትተን ከሌሎች ሀይማኖት ተከታዮች ጋር ፉክክር ስንገባ ነዉ ዉድቀታችን መታወቅ አለበት፡፡ አሏህ በተከበረ ቅዱስ ቁርአኑ በዱንያ እነሱ እንደሚደሰቱ ግን በአኼራ እንደሚቀጡ ነግሮናል እነሱ በስኳር መንፈስ መንገዱን አደባባዩን እንደፈለጉ ሲጠቀሙበት እኛ ሙስሊሞች እነሱ ጋር ምን አፎካከረን?? የነብዩ ሱና ይበልጣል ወይስ ከአነሱ ጋር ፉክክር?? ☞በደሴ በነበረዉ ኢፍጣር አይቻለሁ ሴቶች እንደ ኢድ ልብስ ለብሰዉ ተኳኩለዉ ፊታቸዉን በቡርሽ ቦርሸዉ ነበር የመጡት እናም በዛን ጊዜ ታዳ በዛ የአይን ዚና የእጅ ዚና የአፍ ዚና ወዘተ ወንጀል መሰራቱ ይቀራል ወይ?? በአደባባይ ኢፍጣር ወንድ ሴት ፊት ለፊት እየሆነ ሲያፈጥሩ አይተናል ይሄ የነብዩ ሱና ነዉ ወይ?? ☞የኢፍጣሩ ብር ከተለያዩ ባንኮች እስፓንሰር ተደርጓል ..በወለድ የሚሰሩ ባንኮች ለዚህ ኢፍጣር ሰጥተዋል ...ግን ይበቃል ወይ?? ይሄ ጥያቄዉ ለአሊሞቻችን ነዉ ☞ በተለይ ሴቶች በTik tok በfb youtube ለመልቀቅ ነበር አመጣጣቸዉ...ብዙ ሰዉ የሄደዉ ማለት ይቻላል ብዙዉ ኢንተርኔት ላይ ተጥዶ tik tok እና fb ላይ ነበር ☞ ከፍጥሪያዉ ቡሀላ አንዳንድ ጀመአዎች በተለይ የአህባሽ አቂዳ የሚከተሉ ለብቻቸዉ ተገንጥለዉ ወንድ ከሴት ተቀላቅለዉ መንዙማ ከፍተዉ ሲጨፍሩ አይቻለሁ ... ይሄ ሁሉ ማስረጃ በስልኬ video አለኝ ግን ሁሉም በሚዲያ ግልፅ ማድረግ አግባብ አይደለም፡፡ ✔መዉሊድ የተጀመረዉ ቀስ በቀስ ነዉ ወደ ሰዉ ልብ የሰረፀዉ ..የኛም ህዝብ ይሄ የአደባባይ ኢፍጣር በአመት አንዴ በሆነ ቁጥር የሚመጣዉ ትዉልድ ሱና ነዉ ብሎ እንዳይዘዉ☺️ ያሰጋል እናም አላህ ካደረሰኝ ለሚመጣዉ አመት ረመዳን ከአደባባይ ኢፍጣር ተብየ አዲስ የመጣ አንድነትን ለማሳየት ተብሎ ብዙ መዘዝ ይዞ ለሚመጣ እኔ አልሳተፍም...መታወቅ ያለበት ይሄ የራሴ ብቻ አመለካከት ነዉ፡፡ ☞ በፊት ከዛሬ 3 አመት በፊት ጀምሬ ሙነሺዶች የያዙት አቋም ከባድ ነዉ ነቢይ እያሉ ሌላ ነዉ እቅዳቸዉ እል ነበር...በዚህ የተነሳ ብዙ ሰዉ ይወቅሰኝ ነበር...ይሄዉ ዛሬ አሊም የሚሰማ ጠፍቶ ፈተዋዉም ደአዋዉም ከሙነሺዶች ሆነ ...እኔ የሚገርመኝ በተለያዩ tv ቻናሎች ስለኢስላም ሀይማኖት ሲባል እነሱ ይቀርባሉ ..ግን የክርስቲያን ዘማሪዎች ክርስትናን ወክለዉ ቀርበዉ አያቁም እነሱ አምላክ ነዉ ብለዉ ለያዙት ጥርት ያለ ስራ እየሰሩ ነዉ በtv program ወሬ የለም...የኛ ሙነሺዶች ግን በተለያየ Tv ቀርበዉ ሲበጠረቁ እያየን ነዉ ...ነሺዳና ሙዚቃ መለየት የማንችልበት ዘመን ደርሰናል...አሁንም ስለጎንደር ሙስሊሞች ነሺዳ አዉጥተዉ አንድ ደቂቃ አስለቅሰዉ ያስረሱናል፡፡ ራዕይ በተግባር የሚቀረፅ ህልም እንጂ በአእምሮ ብቻ የምናስበዉ መዳረሻ አይደለም፡፡ ብቻ ከባድ ነዉ ብዙ ማለት ይቻል ነበር መፃፍ ሳልፈልግ ጊዜ አስገድዶኝ ነዉ ..ትናንት ዛሬም ጎንደር ደዉየ ነበር የሚሰማዉ ወላሂ በጣም ከባድ የሚያስለቅስ ነዉ😔 ... ዛሬ የረመዳን 27 ለይል ነዉ ሌላ ማድረግ ቢያቅተን ሳንተኛ በዱአ እንገዛቸዉ ...አላህ ይሰማን ይሆናል ኢንሻ አሏህ በዱአ የጎንደር ሙስሊሞችን እንዳንረሳ አዉፍ በሉኝ በችኮላ በ30 ደቂቃ ዉስጥ ያለዝግጅት የተፃፈ ነዉ....አደራ አደራ ለጎንደር ሙስሊሞች ዱአ እንድናደርግ https://t.me/IslamisUniverstiy_public_group
Show all...
የጎዳና ላይ የኢፍጣር ፕሮግራም በሸሪዓ ሚዛን በሸይኽ ሙሐመድ ሐያት አቡ መንሱር( حفظه الله تعالى ) الحمدلله وحده لاشريك له والصلاة والسلام على من لانبي بعده أما بعد فانظروا ياأهل السنة والجماعة أخطاروأضرار التفطير والإفطار على الشوارع(طريق الناس) ዝርጋታ) እናንተ የሱና የአንድነት ባለቤቶች ሆይ በሰዎች መንገድ(ጉዳና)ላይ የማፍጠር ማስፈጠርን ጉዳትና አደገኝነት ተመልከቱ (١)ضررمن يمر بها من ركاب السيارات والمشاة ጉዳት (1) በዚያ የሚያልፈውን ተሳፋሪና እግረኛ ማስቸገሩ لأن السيارات قد تحجز من صلاة العصر الى المغرب ምክንያቱም ከ ዐስር እስከ መግሪብ ሶላት ድረስ መኪናዎች ስለሚታገዱ وفي الحديث لاضررولاضرار رواه أحمد وابن ماجه وله طرق أخرى يقوى بعضه بعضا በሐድሥ አውቆም ሆነ ተዘናግቶ መጉዳት አይቻልም የሚል አለ (٢)جلب الرياء والسمعة قال تعالى(وماأمرواإلا ليعبدواالله مخلصين له الدين ----البينة ጉዳት (2) ይሉልኝናን ይስሙልኝን ማካበት (መላመድ ነው) ነው ጌታችን ደግሞ እንድህ ይላል (ሰዎችና አጋንንቶች) አምልኮን ለሱ (ለአሏህ) ጥርት አድርገው ሊያመልኩት እንጂ አልታዘዙም። (٣)كثرة التصوير بلاحاجة ولافائدةبل يجعلون القسوس في جنبك وقد أخذ أوعلق صليبه فيصورونك مع القسوس ጉዳት (3) ያለ አስገዳጅና ያ ጉዳይ ፎቶ ቀረፃ መብዛቱ ነው እንደውም እንደውም ቄሱ መስቀሉን ጨብጦ ወይም ጨንጠልጥሎ ከጎንህ ያደርጉትና ሊቀርፁህ ይችላሉ (٤)احضار المسيحيين في أمر الدين لأن الإفطار من أمور الدين الذي ترتب عليه الثوابالجسيم ጉዳት (4)ነሳራዎችን በኃይማኖት ጉዳይ ማቅረብ አለበት ምክንያቱም ማስፈጠር ታላቅ ምንዳን የሚያስገኝ ነገር ስለሆነ فاإذاشارك المسيحييون في هذا الطعام يقل ثواب المفطرين ነሷራዎች እዚህ ምግብ የቀረቡ ጊዜ የአስፈጣሪዎቹ ምንዳ ያንሳል فاإن قلت كيف يقل ثوابهم أقول قال رسول الله صلى الله عليه وسلم (من فطر صائما كان له مثل أجره غير أنه لاينقص من أجر الصائم) رواه الترمذي وغيره مثلا إذافطرت عشرة من المسلمين فكأنك صمت عشرة أيام أو حصل لك أجور عشرة ለምሳሌ አስር ሙሊሞች ብታስፈጥር የአስር ሰው አጅር አለህ ከነዚያ አምስቶቹ ነሷራ ከሆኑ ግን የአምስት ሰው ቀነሱ فاإذاكان الخمسة من المسيحيين فقد فطرت خمسة من المسلمين فقط فحصل لك أجور الخمسة فهذا هوقلة الثواب والأجور እንዴት ምንዳቸው ያንስባቸዋል ካልከኝ መልእክተኛﷺእንድህ ብለዋል ፆመኛን ያስፈጠረ የፆመኛውን አይነት ምንዳ ከፆመኛው ምንዳ ሳይጎድል ለአስፈጣሪዉም አለው። (٥) وفيه دعوة إلى دين اشتراكي لأنهم إذاكان عيدهم وطقوسهم سيقولون احضروا في عيدنا وطقوسنا نستضيفكم كمااستضفتموناويقولون أجيبوادعوتنا كمااستجبنادعوتكم ጉዳት (5)በውስጡ ወደ የጋራ ኃይማኖት መጣራት አካቷል ለምን ብትሉ እነሱም(ቄሶቹ)የራሳቸው በዓል ሲሆን ኑቶሎ እናንተ እንዳስተናገዳቹህን እኛም በባዓላችን እናስተናግዳቹህ ይላሉ فاإن حضرت في عيدهم وطقوسهم فقد تعاونت على كفرهم ومعصيتهم وقال تعالى )ولاتعاونوا على الإثم والعدوان) المائدة ከበዓላቸው ከተጣድክ በክህደታቸው በወንጀላቸው ላይ ተባበርክ ማለት ነው። وإن لم تحضرها يقولون هذا رجل لايحب الوحدة لايأكل ولايشرب معنا አልጣድም ብለህ ከቀረህ ይህ ሰው አንድነትን አይደግፍም ከኛጋ አይበላም አይጠጣም ይላሉ (٦)التشبه بالنصارى لأنه مأخوذ منهم كما قيل وقال صلى الله عليه وسلم( من تشبه بقوم فهو منهم) رواه أبوداود ጉዳት(6)በነሷራ መሳሰል አለበት እንደተባለው ከሆነ ከነሱ የተያዘ ስለሆነ (٧)إختلاط الرجال بالنساء وهذا حرام كما يعلم ጉዳት (7) ሴትና ወንደ መቀላቀል አለበት ይህ ደግሞ እንደሚታወቀው እርም ነው። (٨) الظهور على الشوارع نوع من أنواع المظاهرات كما يعرف من يعرف تخطيطهم ጉዳት (8) በጎዳናዎች ላይ መብለጭለጩ ከሰልፍ አይነቶች አንዱ ነው ከኢስቲራቴጃቸው የሚያውቅ እንደማይውቀው ولا يصدر ِهذالعمل إلا من الذين لايرون الولاء والبراء في الدين وهم الإخوان المسلمون بلا شك ይህ ተግባር ከነዚያ በኃማኖት ላይ ወላእና በራእ ከሌላቸው አካቶች ከኢኽዋኖች እንጂ ከሌላ አይመነጭም ይህ ነው ለኔ ግልፅ የሆነልኝ والله أعلم .وصلى الله وسلم على النبي الأمين وعلى أله وصحبه ومن تبعهم بإحسان إلى يوم الدين ١٤٤٢هجرية ዐረበኛ በ ሸይኽ ሙሀመድ ሀያት አቡ መንሱር (ከሀራ ከተማ) አማረኛ አቡ ሙአዝ ሀሰን ኢድሪስ በግርድፍ አማረኛ የዛሬ አመት የተለጠፈ👆👆👆‼️ t.me/abumuazhusenedris t.me/abumuazhusenedris
Show all...
አቡ ሙዓዝ(ሀሰን ኢድሪስ)

ወደ ቻናሉ⬇ መግባት⬇ ከፈለጉ http://t.me/abumuazhusenedris አሰተያየትና⬇ጥያቄዎች ⬇ካለዎት

https://t.me/abumuazhusen_bot

ይጠቀሙበት!!!

#እውነት_ጌታ_ሞቷል!!? <====================> ጌታ ፍጥረታትን በችሎታው ፈጥሮ፡ ከሊቅ እስከ ደቂቅ በውበት ሰድሮ፡ ሰውም ሆነ አጋንንት ሲመጣ ወደ አለም፡ ለአንድ አላማ ነው ሌላ ነገር የለም፡ ===================== ይህ በእንድህ እንዳለ ከፊሎች አምፀው፡ እንጨትን በመጥረብ አምላክን ቀርፀው፡ ከክብር ሰውነት ከአስተሳሰብ ልቀት፡ ወደታች ወረዱ ለዘላለም ውድቀት፡ ከጌታ ትዕዛዝ ውጭ እጂግ በጣም ዘቅጠው፡ በሸይጧን መረብ ውስጥ በመግባት ተንጠው፡ ========================== ጌታችን ተወግሯል ተሰቅሏል ይላሉ፡ በየ ጎዳናው ላይ ደፍረው ያወራሉ፡ እንጨት ተሸክመው ምንጣፍን በማንጠፍ፡ በጭብጨባ ድምቀት እውነትን ለማጠፍ፡ ወላሒ ይገርማል የሚሰሩት ስራ፡ የእምነት መርሃቸው ሁሉም ነው ፈጠራ፡ ========================= በእጁ ፎቶ ሰርቶ ጌታ ነው ይልሃል፡ የጌታ እናት ብሎም ያመላክትሃል፡ ወሏሒ ስራቸው ይዘገንንሃል፡ የጌታህን ምስል ፎቶ አንተ ከሰራህ፡ በአምላክ ላይ ደፍረህ ቅጥፈትን ካወራህ፡ አንተ ማን ነህና ማንነህ ብየ ልጥራህ!? ======================= ጌታህ አቅም አጥቶ ሰው ከደበደበው፡? ምራቅ እየተፋ አይሁድ ከሰደበው፡? ቀጥቅጠው ሲያበቁ ከንጨት ከሰቀሉት፡? በቃ ጌታ አይደለም ምንድን ነው ምትሉት፡!! ግን እስኪ ልጠይቅ መልስ ሰጪ ባገኝ፡ አሏህ በችሮታው ሙስሊም ካደረገኝ፡ ======================= #ጥያቄዬ!!? ያኔ ጌታ ሙቶ ከመሬት ሲቀበር፡ እስኪነሳ ድረስ አለም እንደት ነበር፡? እንደት ነበር ሰማይ፤ መውደቁ ይቅርና አልተንቀጠቀጠም!? መደርመስ ቀርቶበት ምድር አልተናጠም? መበተኑ ቀርቶ ተራራ አልሰመጠም? <~~~~> #ታዲያ_!! ፈጣሪ በፍጡር ሲሰቀል ተወግሮ፡ አለምን ያለ አምላክ ማን አስቆመው ደፍሮ? ፍጥረታቱን ጥሎ ጌታ ሞትን ሲቀምስ፡ ሰማይና ምድር ሳይተረማመስ!? <<{==================}>> ጁሙዓ ቀን ሞቶ እሁድ እስኪነሳ፡ እንዴት ነበር አለም እፅዋት እንሰሳ፡ በየብስ ላይ ኗሪው የባህሩ ውስጥ አሳ፡ ግን እንዴት ነበሩ ጌታን የገደሉት? እግር እጁን ጠፍንገው አስረው የሰቀሉት? <~~~~~~> #እውነት_ጌታ_ሞቷል!? የአለም ፈጣሪ በሰዎች ተመቷል? ተወግሮ ተሰቅሎ እጂግ ተሰቃይቷል?? እስኪ መልስ ስጡን እውነት ጌታ ሞቷል??<<{=======================}>> #ኑረዲን_አል_አረቢ #ደሴ_ከጦሳ_ሰማይ_ስር!! <<{======================}>> http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi http://t.me/nuredinal_arebi <{=====================}>
Show all...
شـبـاب السـلـــفــــيــــيــن

#ሰለፍያ_ቀጥተኛ_የሀቅ_መንገድ_ብሎም_አይነኬ_ፅኑ_ተራራ_ነው ለአስተያዬትና እርማት @Nuredin_al_arebi_Bot

ቅንድብ መቀንደብ https://t.me/SadatKemalAbuMeryem/2987
Show all...
♦️ለይለተልቀድር በአይን ትታያለች ‼️ አንዳንዶች እግራቸውን ዘርግተው ወሬያቸውን እየፈጩ ሰማይ ሰማይ ያንጋጥጣሉ፡፡ የሚጠባበቁት ተወርዋሪ ኮከብ ነው፡፡ እሱን ሲያልፍ ሲመለከቱ “አኑረን አክብረን” ብለው በህብረት ይንጫጫሉ፡፡ ይሄ እዚህ ግባ የማይባል ባዶ እምነት ነው፡፡ ለይለተልቀድር አላህ በአንዳንድ ባሮቹ ቀልብ ላይ ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ የመረጋጋት ወይም የመለየት ስሜት ከማሳደሩ ውጭ በአይን የሚታይ ነገር አይደለም፡፡ የሚታየው ምልክቶቿ እንጂ እራሷ አይደለችም። ነገር ግን ሰዎች ሊጠመዱ የሚገባቸውም በዒባዳ፣ በዚክር፣ በሶላት፣ በዱዓእ፣ በቁርኣን እንጂ በወሬ መሆን የለበትም፡፡ ሰዎች የሚጠበቅባቸውን ከተወጡ ለሊቱ ለይለተልቀድር መሆኑን ባያውቁ እንኳን ትሩፋቷን አያጡም፡፡ ለይለተልቀድር እንደሆነ ውስጡ ያደረ ሰው ምን ያድርግ? በተለይ ደግሞ ለሊቱ ለይለተልቀድር እንደሚሆን ውስጣችንን ከተሰማን ይበልጥ ልናተኩርበት የሚገባን ዱዓእ “አልሏሁመ ኢንነከ ዐፉውዉን ቱሒቡልዐፍወ ፈዕፉ ዐኒ” (“ጌታዬ ሆይ! አንተ በርግጥም ይቅር ባይ ነህ፡፡ ይቅር ማለትን ትወዳለህ፡፡ ስለሆነም ከኔ ይቅር በለኝ” የሚለው ነው። 📚[አልባኒ ሶሒሕ ብለውታል] ስለዚህ ዋናው ልናተኩርበት የሚገባን በዱንያም በአኺራም ከአላህ ይቅርታን እንድናገኝ መጣጣር ነው፡፡ ግን ለምን አላህ ለይለተልቀድርን ስውር አደረጋት? ዑለማዎች እንደሚሉት ታላላቅ ትሩፋቶች በሚገኝባቸው የረመዳን የመጨረሻ ለሊቶች ሙስሊሞች በዒባዳህ ይበራቱና ይጠናከሩ ዘንድ ነው አላህ ይቺን ለሊት ስውር ያደረጋት፡፡ እናም ለይለተልቀድርን እንዳታመልጣቸው ሲጣጣሩ ለይተው ቢያውቋት ሊኖራቸው ከሚገባው በበለጠ ይበልጥ በዒባዳህ ላይ ይቆያሉ፣ ይነቃቃሉም፡፡ በዚህም ይበልጥ ይጠቀማሉ፡፡ ለይተው ቢያውቋት ግን እሷ ብቻ ላይ አነጣጥረው ሌሎቹን ለሊቶች ሊዘናጉ ይችሉ ነበር፡፡ እናም መሰወሯ ነብዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዳሉት ለኛ ኸይር ነው፡፡📚[ቡኻሪ] አላህ ይቺን ታላቅ ለሊት ያድለን፡፡ የምንጠቀምባትም ያድርገን፡፡ ኣሚን፡፡ መልካም ሆኖ ካገኙት ሼር ማድረግ እንዳይረሱ፡፡ ሌሎችንም ተጠቃሚ ያድርጉ፡፡ 📝(ኢብኑ ሙነወር...ሰኔ 29/2007 ↷ ⇣🌹⇣↷
Show all...
Repost from "ኡማ ቲቪ " Tv
ዘካችሁን ለንግድ ባንክ እንዳትሰጡ! ~ ባያያዝኩት ማስታወቂያ ላይ እንደምታዩት ንግድ ባንክ ዘካ እሰበስባለሁ እያለ ነው። ንግድ ባንክ ፈፅሞ ለዚህ ኃላፊነት የሚሆን አይደለም። ማንንም የሸሪዐ ቦርድ አድርጎ ስላቀፈ እንዳትሸወዱ። ዘካ ቀልድ አይደለም። ቀላል ሃላፊነትም አይደለም። ወይ በራሳችሁ ወይም ደግሞ ታማኝነቱን በምታውቁት አካል በኩል ብቻ አውጡ። በነገራችን ላይ የዘካ ገንዘብ ለቁጠባ የሚቀመጥ ሳይሆን ቀጥታ ለሚገባቸው አካላት የሚሰጥ ነው። ©Ibu munawar ሼር አድርጉ ለወዳጅ ዘመድ የቴሌግራም ቻናላችን ከስር በሊንኩ ይቀላቀሉ👇 https://t.me/+UAKV32q7U2HKzEMf
Show all...
«የለይለተል ቀድርን ደረጃ ከሚገልጹ ነገሮች ውስጥ:- 1/ቁርኣን የወረደው (መውረድ የጀመረው) በዚህች ሌሊት መሆኑ 2/ አሏህ ሱብሓነ ወተዓላ ሌሊቷን "ለይለተል ቀድር" (የውሳኔና የተከበረች ሌሊት) ብሎ መሰየሙ 3/ የተከበሩ እና ቅዱስ የሆኑ መላኢኮች በዚህች ሌሊት በብዛትና በተደጋጋሚ የሚወርዱ መሆናቸው 4/ በዚህች ሌሊት የሚሰራ ዒባዳ ከአንድ ሺ ወር (ከ83 ዓመት) ዒባዳ የሚበልጥ መሆኑ 5/ በቀጣዩ አመት ላይ ሊከሰቱ የሚችሉ ነገሮች በሙሉ የሚወሰንባት ሌሊት መሆኗ 6/ አሏህ ሱብሓነ ወተዓላ ይህችን ሌሊት ሰላም ብሎ መሰየሙና ለሙስሊሞች ሰላም የሆነች ሌሊት መሆኗ 7/ አሏህ ሱብሓነ ወተዓላ ይህችን ሌሊት በተመለከተ አንድ ሙሉ የቁርኣን ሱራ ማውረዱና ወዘተ የዚህችን ሌሊት ደረጃ ገላጮ ናቸውና እኛም ዒባዳዎችን በማብዛት ከሌሎች ሌሊቶች ልንለያት ይገባናል👌🏻 اللهم وفقنا ليلة القدر. واعف عنا وعافنا وأصلح شأننا وشأن أمتنا. واغفر لنا ولوالدينا ولمشاينا وأحبابنا. 🔸ያረብ፥ የኡመቱን ቀልብ በሐቅ ላይ አንድ አድርገው ወደ አንተ መንገድ የሚጣሩ ሰዎችንም አግዛቸው ተሳስቶ ከማሳሳትም ጠብቃቸው በለይለተል ቀድርም መልካሙን ሁሉ ክተብልን! መመለሻችንም ጀነት አድርገው ከእሳትም ጠብቀን "ኣሚን"» ✍ ኡስታዝ አሕመድ ኣደም ረመዷን 22/9/1438
Show all...