en
Feedback
Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Open in Telegram

ዜና ከምንጩ

Show more

📈 Analytical overview of Telegram channel Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Channel Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) in the Amharic language segment is an active participant. Currently, the community unites 32 978 subscribers, ranking 7 600 in the News & Media category and 1 041 in the Ethiopia region.

📊 Audience metrics and dynamics

Since its creation on невідомо, the project has demonstrated rapid growth, gathering an audience of 32 978 subscribers.

According to the latest data from 28 August, 2026, the channel demonstrates stable activity. Although there has been a change in the number of participants by 542 over the last 30 days and by -11 over the last 24 hours, overall reach remains high.

  • Verification status: Not verified
  • Engagement rate (ER): The average audience engagement rate is 14.39%. Within the first 24 hours after publication, content typically collects 9.96% reactions from the total number of subscribers.
  • Post reach: On average, each post receives 4 745 views. Within the first day, a publication typically gains 3 284 views.
  • Reactions and interaction: The audience actively supports content: the average number of reactions per post is 9.

📝 Description and content policy

The author describes the resource as a platform for expressing subjective opinions:
ዜና ከምንጩ

Thanks to the high frequency of updates (latest data received on 29 August, 2026), the channel maintains relevance and a high level of publication reach. Analytics show that the audience actively interacts with content, making it an important point of influence in the News & Media category.

32 978
Subscribers
-1124 hours
+467 days
+54230 days
Posts Archive
ሩሲያ ወደ ውጭ የምትልከው ነዳጅ እስከ መስከረም መጨረሻ ታግዶ እንዲቆይ ወሰነች ቅዳሜ፣ ነሐሴ 23 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) ሩሲያ የአገር ውስጥ የነዳጅ ገበያን ለማረጋጋት በሚል ወደ ውጭ በምትልከው ነዳጅ ላይ የጣለችው እገዳ  እ.አ.አ መስከረም 30 ቀን 2026 ድረስ ማራዘሟን ዛሬ ቅዳሜ ይፋ አደረገች። የአውሮፓን ህብረት ፕሬዝዳንት በቅርቡ ከሩሲያ የሚገባው ነዳጅ መቅረቱ፣ አህጉሩን ከባድ ዋጋ እያስከፈለው መሆኑን ተናግረው ነበር። የሩሲያ መንግሥት ይህንን አስመልክቶ ባወጣው ይፋዊ መግለጫ፤ የእገዳ ውሳኔው ለከባድ ተሽከርካሪዎች የሚውለው ዲዝል በተጨማሪ የማሪን ነዳጅ እና የጋዝ ምርቶችን በሙሉ  ያካትታል። ውሳኔውን በተመለከተ በሰጠው ማብራሪያም “እርምጃው የተወሰደው የአገር ውስጥ የነዳጅ ገበያን ለማረጋጋት እና የዋጋ ንረትን ለመግታት ታስቦ ነው” ብሏል። ሮይተርስ ኢንዱስትሪ ላይ የሚሰሩ ምንጮችን እማኝ አድርጎ እንደዘገበው፤ ሩሲያ እገዳውን እንድታራዝም ያስገደዳት በዩክሬን ድሮን  በሚደርሱ ጥቃቶች ምክንያት በርካታ የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካዎቿ አገልግሎት ማቋረጣቸውን ተከተሎ በአገር ውስጥ የታየውን የነዳጅ እጥረት ለመቅረፍ በማለም ነው። ሩሲያ ከዚህ ውሳኔዋ አስቀድሞ ወደውጵ በሚላከው ነዳጅ ላይ፣ በአውሮፓውያኑ  ከሐምሌ አንድ እስከ ሐምሌ 25 ባለው ጊዜ ውስጥ እገዳ ጥላ የነበረ ቢሆንም እስከ ነሐሴ 25 ቀን አራዝማው ነበር። አሁን ደግሞ እገዳው ለተጨማሪ አንድ ወር እንዲራዘም ወስናለች። ከዚህ በተጨማሪም ሩሲያ አምራች ባልሆኑ ኩባንያዎች የሚደረግ የዲዝል እና የሞተር ቤንዚን እስከ ጥር  2027 እንዲሁም የጄት ነዳጅ 2026  ድረስ ታግዶ እንዲቆይ ማድረጓ የሚታወስ ነው። ከአሜሪካ ቀጥሎ በዓለም ሁለተኛዋ ትልቋ የዲዝል ላኪ የሆነችው ሩሲያ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በሚሳኤል እና በድሮን ጥቃቶች ሳቢያ የማጣሪያ አቅሟ በመቀነሱ ምክንያት ወደ ውጭ የምትልከው የነዳጅ መጠን በከፍተኛ ሁኔታ እየቀነሰ ነው ተብሏል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

የኢሕአፓ አመራርና አባል ተጨማሪ ምስክር እንዲያቀርቡ ለቀጣይ ሳምንት ሐሙስ ቀጠሮ ተሰጣቸው ዓርብ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) ተጠርጣሪዎቹ ተጨማሪ ምስክር እንዲያቀርቡ በማለት የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለነሐሴ  28 ቀጠሮ መስጠቱን ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ተናገሩ። በሽብር ወንጀል የተጠረጠሩት፤ የኢሕአፓ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊው  ይስሐቅ ወልዳይ፣ የፓርቲው አባል አበበ አካሉ እንዲሁም ጠበቃ አበራ ንጉሥ በዛሬው ዕለት  በከፍተኛ ፍርድ ቤት ቀርበው እንደነበር ጠበቃቸው ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። የከፍተኛ  ፍርድ ቤት ዛሬ ባስቻለው ችሎት ተከሳሾቹ  የፌደራል ፖሊስ የምርመራ መዝገቡን ማጠናቀቁን እና የቴክኒክና የፎረንሲክ መረጃዎች በቂ ስለሆኑ የፌደራል ፖሊስም መረጃዎችን ወደ ማጠናቀቁ  እንደደረሠ አሰረድቷል። ነገር ግን ተከሳሾቹ ያቀረቧቸው ምስክሮች በቁጥር ሁለት ብቻ  በመሆናቸው ፍርድ ቤቱ ለመጨረሻ ጊዜ በሚል ለቀጣይ ሳምንት ሐሙስ ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ቀጠሮ እንደተሠጣቸው ጠበቃ ሰለሞን አስረድተዋል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች የሚገባው የውሃ መጠን 20 በመቶ እንደቀነሰ አስታወቀ ዓርብ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የኤትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ወደ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች በዋናነትም ወደህዳሴው ግድብ እና ጊቤ ሦስት የሚገባው የውሃ መጠን 20 በመቶ በኤልኒኖ ምክንያት እንደቀነሰ በመግለጽ በቀጣይ ዓመት ገቢ ማስገባት አለብኝ ብሎ ያቀደው በዚህ ዓመት ካተረፈው በታች መሆኑን ገለጸ።   ይህ ስጋት በኃይል ማመንጨት አቅም ላይ የሚያደርሰውን ተጽዕኖ ለመቀነስ ሌሎች የኃይል ማመንጫዎች ላይ መስራት እና የዳታ ማይኒንግ ላይ የሚጠቀሙትን በመቀነስ እርምጃ እየተወሰደ እንደሆነ ተገልጿል። ተቋሙ ይህንን ያለው በዛሬው ዕለት የተጠናቀቀውን የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈጻጸም እና የወደፊት እቅዶችን በተመለከተ ጋዜጣዊ መግለጫ በሰጠበት ወቅት ነው። የተቋሙ ዋና ስራ አስፈጻሚ አሸብር ባልቻ ከፍተኛው የውሃ ፍሰት የሚገባው በሐምሌ እና በነሐሴ እንደሆነ ገልጸው በተወሰነ ደረጃ መስከረም እና ጥቅምት ላይ ይገባል ያሉ ሲሆን በተለይም በህዳሴ ግድብ አካባቢ ከፍተኛው ጎርፍ የሚገባው በነሐሴ ወር ላይ እንደሆነ አመልክተዋል፡፡ ሆኖም ግን ባለፋት ወራት ከሰኔ ጀምሮ እየቀነሰ መምጣቱን አንስተዋል። አክለውም ባለፉት ወራት ከተለያዩ የሜትሮሎጂ ትንበያዎች እንደ ኢጋድ፣ እንዲሁም ከውሃ እና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከፍተኛ  አማካሪ ባለሙያዎች ጋር በተደረገ የጋራ ክትትል የውሃ ፍሰቱ እየቀነሰ መምጣቱን አረጋግጠናል ብለዋል። "ባደረግነው ክትትል (ሞኒተሪንግ)የሚገባው ውሃ በትንሹ 20 በመቶ የቀነሰ ስለሆነ፣ እሱ በቀነሰበት ሁኔታ እንግዲህ ተጨማሪ ከፍ አድርገን ማቀድ አንችልም። ገበያችን በዋናነት የሚመሰረተው ከምናመነጨው ኢነርጂ አንጻር ነው።" ብለዋል በተጨማሪም የውሃው መጠን በወረደ ቁጥር የኃይል ማምረት አቅም አብሮ እንደሚቀንስ የገለጹ ሲሆን አንዳንድ ቦታ ላይ የውሃው መጠን ከፍታ በወረደ ቁጥር የማመንጨት አቅሙም እንደሚወርድ አንስተዋል። አክለውም የኃይል ማመንጨቱ ከውሃ ጋር የተያያዘ መሆኑን ተናግረዋል። ለአብነትም በጊቤ 3 ግድብ የውሃው ሙሊት ዝቅ በሚልበት ወቅት እስከ 50 ሜጋዋት በዩኒቱ  እንዲያጡ እንደሚያደርግ ጠቅሰዋል። ይህን ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት የ2019 የገቢ እቅድ እና የኤክስፖርት መጠን የተቀረጸ መሆኑ ተጠቅሷል። ወደ ውጪ የሚላክን ኃይል በተመለከተ ደግሞ በሰጡት ማብራሪያ፣ በዋናነት፤ ለኬንያ እና ለጂቡቲ የኃይል ሽያጭ ይደረጋል ያሉ ሲሆን፣ በሱዳን ባጋጠመው ጦርነት እና የኃይል ማሰራጫ መስመሮች መበላሸት ምክንያት ወደ እዚያ የሚላከው ኃይል እንደተቋረጠ አንስተዋል።  ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚው ኤፍሬም ወልደኪዳን በበኩላቸው፤ ኢልኒኖ ያደረሰው ተጽዕኖ ቀላል የሚባል እንዳልሆነ ጠቅሰው፣ በታሪክ ከፍተኛ የሚባለውን የውሃ መቀነስ እንዳጋጠመ ተናግረዋል። አክለውም ይህ የውሃ መቀነስ ያጋጠመው በዋናነት ከ65 በመቶ በላይ ኃይል የሚያመነጩት የህዳሴ ግድብ ላይ እና ጊቤ ሶስት ላይ መሆኑን ገልጸዋል፡፡   በዚህም ምክንያት የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች የሚጠቀሙትን ኃይል እየቀነሱ እንደሆነ እና ወደፊትም እየቀነሱ እንደሚሄዱ አንስተዋል። በተጨማሪም ተቋሙ በተያዘው በጀት ዓመት 313.8 ቢሊዮን ብር እንደሚያስፈልገው የገለጸ ሲሆን በጀቱም በብድር እና በልማት ድርጅቶች እንደሚሸፈን አስታውቋል። በተጠናቀቀው  የበጀት ዓመት የተፈቀደለት አጠቃለይ በጀት 251 ቢሊዮን ብር የነበረ ሲሆን 152.8 ቢሊዮን ብር ወጪ አድርጓል፡፡ ይህም ያልተጠቀመው በጀት የእዳ ሽግሽግ ባለመደረጉ፣ የካፒታል ፕሮጀክቶች በተፈለገው መልኩ ባለመሄዳቸው  ጋር እንደሚያያዝ ገልጿል። በተያዘው የበጀት ዓመት ካባለፈው የተሸጋገረ ገንዘብ እንዳለው አስታውቋል። ተቋሙ በተጠናቀቀው  የ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት 124.2 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ገቢ በማግኘት 39.5 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ ማግኘቱን አስታወቀ። ዋና ስራ አስፈፃሚው በበጀት ዓመቱ  ካሉት 21 የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች 9730 ሜጋ ዋት ኤሌክትሪክ ማመንጨት  ተችሏል ያሉ ሲሆን እንደ አጠቃላይ አፈፃፀሙ 91.9 በመቶ እንደሆነ ተናግረዋል። በተጀመረው የ2019 የበጀት ዓመት ደግሞ 50 ሜጋ ዋት ለመጨመር ማቀዱን አስታውቋል። አጠቃላይ ከተገኘው ገቢ ከዳታ ማይኒነግ የተገኘው 50 ቢሊዮን ብር ሲሆን ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የተገኘው ደግሞ 45 ቢሊዮን ብር ነው። ይሁን እንጂ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት 56 በመቶውን ኃይል የሚያቀርብ ሲሆን ለዳታ ማይኒንግ ደግሞ 32 በመቶው ነው። ቀሪዎቹ ደግሞ ለኢትዮ-ጅቡቲና ለከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች የሚቀርቡ ናቸው፡፡ ዋና ሥራ አስፈጻሚው የገቢው ልዩነት የመጣበትን ሲያስረዱም፤ ዳታ ማይኒንግ የሚሰሩት በውጭ ምንዛሬ እየሚከፍል በመሆኑ ነው ብለዋል። እንዲሁም በአጠቃላይ ከ476 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ መገኘቱን አስታውቋል። ተቋሙ በ2018ዓ.ም አጠቃላይ ሀብቱ ከ900 ቢሊዮን ብር በላይ የሲሆን የተከፈለ የካፒታል መጠኑ 585 ቢሊዮን ብር ነው። በተጨማሪም የካፒታል መጠኑን እስከ 1.3 ትሪሊዮን ብር ለማሳደግ እንደተፈቀደለት አስታውቋል። ከዚህ ቀደም የነበረበትን የሀገር ውስጥ እዳ ሙሉ ለሙሉ  መንግስት መውሰዱ እና  ባለፈው ዓመት ታሪፍ  ጭማሪ በማድረጋቸው ለዚህ አፈፃፀማቸው ጉልህ አስተዋፅኦ እንዳደረገ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ተናግረዋል። የህዳሴ ግድብ  ተጠናቅቆ ወደ ኃይል ማመንጨት መግባቱ አጠቃላይ 97 በመቶ ሀገሪቱ ከውኃ ኃይል የምታመነጭ ሲሆን 51 በመቶ የሚሆነውን ሸፍኗል ተብሏል። ምንም እንኳ ሀገሪቱ አብዛኛውን ኃይል ከውሃ  የምታገኝ በመሆኑ በቀጣይ ኤልኒኖ ይዞት የመጣውን ተፅእኖ ለመቀነስ ሲባል ወደሌሎች የኃይል ማመንጫ አይነቶች ላይ በትኩረት ለመስራት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አስታውቋል። ተቋሙ የፕሮጀክቶች አፈጻጸምን በተመለከተ በአማራ ክልል እክል እንደገጠመውም አልሸሸገም። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

በኔፓል የጎርፍ አደጋ ከ540 በላይ ሰዎችን ህይወት ቀጥፎ ተጨማሪ የጎርፍ ሥጋት መደቀኑ ተሰማ ዓርብ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) በኔፓል እና በቻይና  ድንበር  ቲቤት ላይ በተከሰተው ከፍተኛ እና ድንገተኛ የጎርፍ አደጋ የሞቱት ሰዎች ቁጥር ቢያንስ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ 547 ደረሰ፡፡ ከሞቱት በተጨማሪ፤ ከአንድ ሺህ ሰዎች በላይ የጠፉ ሲሆን የነፍስ አድን ቡድኖች በጭቃና ፍርስራሽ የተሸፈኑ ቦታዎችን መቆፈራቸውን የቀጠሉ ቢሆንም በቻይና በኩል ነፍስ አድኖቹ ደህንነቱ ወደተጠበቀ ቦታ እንዲሄዱ አሳሰባለች። ረቡዕ ዕለት በሂማላያ ተራራማ አካባቢ በተከሰተ ከፍተኛ የበረዶ ግግር ተደርምሶ የተነሳው የጎርፍ እና ጭቃ ጎርፍ፣ በወንዞች መስመር ላይ ያሉ መንደሮችን፣ የውሃና ኤሌክትሪክ ማመንጫዎችን እና የመሰረተ ልማት አውታሮችን ከጥቅም ውጪ አድርጓቸዋል፡፡   ቻይና አሉ የሚባሉ መሃንዲሶቿ በቡድን ሁነው ጎርፉን መቋቋም የሚችል ንድፍ (3ዲ) ሰርተው፤ ግንባታ እንዲጀመር አሳስባለች። ይህ ቡድን  በከፍተኛ አመራሮች የሚመራም ይሆናል ተብሏል። የኔፓል ባለሥልጣናት  የሟቾች ቁጥር ከ500 በላይ እንደሚደርስ የገለጹ ሲሆን በከ1,000 በላይ ሰዎች የት እንደደረሱ አልታወቀም። በርካታ የውጭ ሀገር ቱሪስቶችም ከእነርሱ ውስጥ ይገኙበታል፡፡ በአደጋው ምክንያት በተፈጠሩ የመሬት መንሸራተት ሳቢያ ወንዞች ተዘጋግተው የተፈጠሩ ሰው ሰራሽ ሐይቆች የሞሉ ሲሆን  የመፍሰስ አደጋ በመደቀናቸው አዲስ የጎርፍ ማዕበል እንዳይከሰት ስጋት ፈጥሯል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል። በሌላ በኩል ደግሞ ለሦስት ሰዓት ያህል ፍለጋው ቁሞ የነበረ ሲሆን የቻይና ባለስልጣናት  በቲቤት በኩል የሚገኙ የነፍስ አድን ቡድኖችን ጊዜያዊ ደኀንነቱ ወደተጠበቀ ቦታ እንዲያፈገፍጉ ትዛዝ አስተላልፈዋል። የኔፓል ጦር እና ፖሊስ፤ ሄሊኮፕተሮችን እና ከባድ ማሽነሪዎችን በመጠቀም የተዘጋጉ መንገዶችን ለመክፈት እና ሰዎችን ለማዳን እየሰሩ ነው። በተለይም በ'ትሪሹሊ በተሰኘች የውሃ ኤሌክትሪክ ማመንጫ ዋሻ ውስጥ ተቀርቅረው የነበሩ ከ300 በላይ ሰራተኞችን ማዳን የተቻለ ሲሆን የቀሩትን የማውጣት ስራ በከፍተኛ ጥንቃቄ ቀጥሏል። ህንድ እና ቻይና የድንበር አካባቢዎቻቸውን በከፍተኛ ጥንቃቄ ላይ ያደረጉ ሲሆን፣ ህንድ በጋንዳክ ወንዝ ተፋሰስ አቅራቢያ የሚገኙ በሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎቿን ከቀያቸው እያስወጣች ነው። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ለስድስት ወራት ታግዶ የቆየውን የሮይተርስ ዘጋቢዎች ፈቃድ አደሰ ዓርብ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙኃን ባለሥልጣን ከዓለም አቀፉ የዜና ተቋም ሮይተርስ የሥራ ኃላፊዎች ጋር ከተወያየ በኋላ፣ ላለፉት ስድስት ወራት ታግዶ የቆየውን የሦስት ቋሚ የዜና ወኪሎቹን የዘገባ ፈቃድ ማደሱን አስታወቀ። የባለሥልጣኑ ዋና ዳይሬክተር ኃይማኖት ዘለቀ ከሮይተርስ ኤክስክዩቲቭ ኤዲተር ኒክ ታተር እና የአፍሪካ ኤዲተር ሲልቪያ አሎይሲ ጋር ባካሄዱት ውይይት፤ ተቋሙ ባለፉት ሰባት ወራት ካሰራጫቸው ዘገባዎች መካከል የተወሰኑት የኢትዮጵያን ሕግ፣ የመገናኛ ብዙኃን አዋጅን እና ብሔራዊ ጥቅም የሚጻረሩ እንዲሁም የጋዜጠኝነት ሙያዊ ሥነ-ምግባርን ያልተከተሉ እንደነበሩ የሚዲያ ሞኒተሪንግ ውጤቶችን በማስደገፍ ማስረዳታቸውን የባለስልጣኑ መረጃ ያመላክታል፡፡ ዋና ዳይሬክተሯ አክለውም፣ ሮይተርስ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ያሰራጫቸው አንዳንዶቹ ዘገባዎች በሚዛናዊነት፣ በትክክለኝነት እና በተአማኒነት በኩል ክፍተት የነበረባቸውና ወደ አንድ ወገን ያደሉ እንደነበሩ ገልጸው፣ ለተስተዋሉት የሕግና የሙያ ሥነ-ምግባር ጥሰቶች አስፈላጊው እርማት ሊደረግላቸው እንደሚገባ አፅንኦት ሰጥተዋል። በውይይቱ ላይ የሮይተርስ ኃላፊዎች በበኩላቸው፣ የዜና ወኪሉ ገለልተኛ ሚዲያ መሆኑን ገልጸው ዘገባዎችን ሚዛናዊ፣ በተጨባጭ መረጃ ላይ የተመሠረቱ እና ከአድልዎ የጸዱ ለማድረግ ጥብቅ የኤዲቶሪያል መመሪያዎችን እንደሚከተሉ አስረድተዋል። አያይዘውም አልፎ አልፎ ለተፈጠሩ ስህተቶች ይቅርታ የጠየቁ ሲሆን አስፈላጊውን እርማት እንደሚያደርጉም አረጋግጠዋል። ሮይተርስ ለኢትዮጵያ ከፍተኛ ክብር እንዳለው የገለጹት የሥራ ኃላፊዎቹ፣ ሀገሪቱ ባላት የሕዝብ ቁጥርና የኢኮኖሚ ግዝፈት ልክ ሰፊ ዓለም አቀፍ የሚዲያ ሽፋን ማግኘት አለባት በሚለው አቋማቸው እንደሚጸኑ ተናግረዋል። አክለውም የሀገሪቱን ሕግ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊና ባህላዊ እሴቶች በማክበር ዘገባዎችን እንደሚያቀርቡ እና ጋዜጠኞቻቸውም ብሔራዊ ጥቅምን ተረድተው የሙያ ሥነ-ምግባርን ጠብቀው እንዲሠሩ እንደሚያደርጉ አስታውቀዋል። በውይይቱ ማጠናቀቂያ ላይ ከሕግና የሙያ ሥነ-ምግባር ጋር ተያይዞ ለጊዜው ታግዶ የቆየው የሮይተርስ የኢትዮጵያ የዜና ወኪሎች የዘገባ ፈቃድ እንዲታደስ በባለሥልጣኑ ተወስኗል። በመጨረሻም ባለሥልጣኑ የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የሮይተርስ ቋሚ የዜና ወኪሎች ፈቃድ መታደሱን አውቀው አስፈላጊውን ትብብር እንዲያደርጉላቸው ጥሪ አቅርቧል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

በኢንዶኔዥያ የተቀሰቀሰውን መንግስታዊ ተቃውሞና ሁከት ተከትሎ በከተማዋ የትራንስፖርት አገልግሎት ተስተጎጎለ ዓርብ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) በኢንዶኔዥያ ዋና ከተማ ጃካርታ ተካሂዶ የነበረው ተቃውሞ ወደ ሁከት መቀየሩን ተከትሎ፣ የሀገሪቱ የትራንስፖርት ባለስልጣናት በዛሬው ዕለት አንዳንድ የባቡር እና የአውቶቡስ መስመሮች አገልግሎታቸውን እንዲያቋርጡ ወይም መስመር እንዲቀይሩ ማድረጋቸውን አስታወቁ። በተለያዩ ቡድኖች አስተባባሪነት ትናንት ሐሙስ ጠዋት በፓርላማ ሕንጻ አቅራቢያ የተካሄደው ተቃውሞ፣ ባለፈው ዓመት ለሁለት ሳምንታት ዘልቆ የነበረውንና ለፕሬዝዳንት ፕራቦዎ ሱቢያንቶ አስተዳደር የመጀመሪያው ፈተና የሆነውን ከባድ ጸረ-መንግሥት ተቃውሞ ዓመት ታሳቢ ያደረገ እንደነበር ተገልጿል። ሰልፈኞቹ በመንግሥት ፖሊሲዎች ላይ ያላቸውን ቅሬታ የገለጹ ሲሆን፣ በሙስና በተጠረጠሩ ባለስልጣናት ላይም ጠንካራ እርምጃ እንዲወሰድ ጠይቀዋል። ሰልፉ በዕለቱ ምሽቱን መበተኑ ቢገለጽም፣ ጥቁር ሸሚዝ የለበሱ ግለሰቦች ከሰልፉ በኋላ በጎዳናዎች ላይ በመቆየት የፖሊስ ጣቢያና ሁለት ሞተር ሳይክሎችን በእሳት ማቃጠላቸውን፣ መንገድ መዝጋታቸውን እንዲሁም በፖሊስ ላይ ድንጋይና ዱላ መወርወራቸውን የአካባቢው ሚዲያዎች ዘግበዋል። ፖሊስ በበኩሉ ሁከቱን ለመበተን በአስለቃሽ ጭስ እና በከፍተኛ ጉልበት በሚረጭ ውሃ ምላሽ ሰጥቷል። በአመጹ አካባቢ በርካታ የፍንዳታ ድምፆች የተሰሙ ሲሆን፣ የጃካርታ ፖሊስ እስካሁን በይፋ መግለጫ ባያወጣም የፖሊስ ቃል አቀባይ ቡዲ ሄርማንቶ ለሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን በሰጡት አስተያየት የሁከት ድርጊቶች መከሰታቸውን አረጋግጠዋል። ፖሊስ ሁከት ለማስነሳት ሞክረዋል ያላቸውን 65 ሰዎችን ያሰረ ሲሆን፣ ከአስሪዎቹም ጋር የአየር ሽጉጦች፣ የመገናኛ መሣሪያዎች እና ሞሎቶቭ ኮክቴል ለመሥራት የሚያስችሉ ቁሳቁሶችን መያዙን አስታውቋል። የተቃውሞው መቀስቀስ እ.አ.አ. በ2024 በከፍተኛ ድምፅ ተመርጠው ወደ ሥልጣን የመጡት የቀድሞው ጄኔራል ፕሬዝዳንት ፕራቦዎ ሱቢያንቶ፣ በሕዝብና በባለሃብቶች ዘንድ እየተሸረሸረ የመጣውን እምነት ለመመለስ እየታገሉ ባሉበት አስቸጋሪ ወቅት ላይ የተከሰተ ነው። ቴምፖ በተሰኘው የምርመራ የዜና ድርጅት በቅርቡ በተካሄደ ጥናት የፕራቦዎ የሕዝብ ድጋፍ መጠን ወደ 38 በመቶ ዝቅ ማለቱ ታውቋል። በሁከቱ ምክንያት በዛሬው ዕለት በጃካርታ የመንገደኞች ባቡር እና አውቶቡስ መስመሮች ላይ መስተጓጎል ያጋጠመ ሲሆን፣ በፓርላማው አቅራቢያ ያሉ በርካታ ዋና ዋና ጎዳናዎች መዘጋታቸውን የትራፊክ አስተዳደሩ መግለጹን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡ ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

“ጠላቶች በኢትዮጵያ ላይ የሸረቡትን ሴራ ለማክሸፍ የጸጥታ ኃይሉ ዝግጁ ነው” ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ዓርብ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የሀገር ውስጥ እና የውጭ ጠላቶች ተቀናጅተው በኢትዮጵያ ላይ በርካታ ሴራዎችን በማቀድ ላይ እንደሚገኙ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ገለጹ። ኮሚሽነር ጄነራሉ ይህንን የገለጹት የኢትዮጵያ ፖሊስ ኮሚሽነሮች እንዲሁም የሰላምና ጸጥታ ኃላፊዎች በተገኙበት ሀገራዊ የጋራ የጸጥታ መድረክ ላይ ነው። በመድረኩ ላይ እንደተናገሩት፣ 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ በሰላም እንዲጠናቀቅ የጸጥታና አስተዳደር ኃላፊዎች፣ የሚሊሻ ኃይል እና የሀገር መከላከያ ሠራዊት በተቀናጀ መልኩ በሠሩት ሥራ ትልቅ ሀገራዊ ድል ተመዝግቧል። ከ50 ሚሊዮን በላይ ሕዝብ በሰላም ድምፁን እንዲሰጥ የጸጥታ ተቋማት ያከናወኑት ተግባር በሀገር ውስጥም ሆነ በዓለም አቀፍ ደረጃ አርአያ መሆን መቻሉን በመጥቀስ የምርጫውን ሂደት አሞካሽተዋል። አያይዘውም የሀገር ውስጥና የውጭ ጠላቶች እንዲሁም “የውስጥ ባንዳዎች” ሲሉ የጠሯቸው አካላት ተቀናጅተው የኢትዮጵያን ሰላምና ደህንነት ለማናጋት ሴራዎችን በማቀድ ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። ነገር ግን የጸጥታ ኃይሉ እነዚህን አደገኛ እንቅስቃሴዎች ቀድሞ በማክሸፍ የሀገሪቱን ሰላምና ደህንነት ለማስጠበቅ ሙሉ ዝግጅት ማድረጉን አረጋግጠዋል። በመጨረሻም፣ ሀገሪቱ ጀምራዋለች ያሉት የዕድገት ጉዞ የተሳካ እንዲሆንና ሰላም እንዳይናጋ የጸጥታ አካላት ድርሻቸውን ከመወጣታቸውም በላይ፣ እያንዳንዱ የህብረተሰብ ክፍልና ባለድርሻ አካል የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ኮሚሽነር ጄነራል ደመላሽ ገብረሚካኤል ጥሪ አቅርበዋል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

ደቡብ ኮሪያ የአሜሪካ እና የሰሜን ኮሪያን የኒውክሌር ድርድር እና ዲፕሎማሲያዊ ውይይት ለመጀመር የሚደረገውን ጥረት እንደምትደግፍ ገለጸች ዓርብ፣ ነሐሴ 22 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) ደቡብ ኮሪያ የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ፤ ከሰሜን ኮሪያ ጋር ተቋርጦ የቆየውን ውይይት እንደገና ለማስጀመር የሚያደርጉትን ጥረት በመደገፍ፣ ሁለቱ ወገኖች ለሚያካሂዱት ንግግር አስፈላጊውን ድጋፍ ትሰጣለች ሲል የሀገሪቱ የብሔራዊ ደኀንነት ገለጸ። የብሔራዊ ደኀንነት አማካሪው ዊ ሱንግ ላክ ግንኙነቱን አስመልክቶ ለጋዜጠኞች መግለጫ የሰጡ ሲሆን፣ በዋሽንግተን እና በፒዮንግያንግ መካከል የሚደረገው ውይይት እንደገና መመለስ  በሰሜን ኮሪያ የኒውክለር መሳሪያዎች  ጉዳይ ላይ ተጨባጭ እና ጥርት ያለ እድገት በማምጣት ላይ ማተኮር እንዳለበት አሳስበዋል። እንደ ሮይተርስ ዘገባ ከሆነ አማካሪው የአሜሪካ እና የሰሜን ኮሪያ የኒውክሌር ውይይት ዳግም መጀመር፣ የደቡብ ኮሪያን የደህንነት ዝግጁነት በማያዳክምበት ሁኔታ ላይ ተመርኩዞ መከናወን እንደሌለበትና ሴኡል ከሂደቱ ውጭ እንዳትሆን ጥንቃቄ እንደሚደረግ ገልጸዋል። ይህ አዲሱ የደቡብ ኮሪያ አቋም የተሰማው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከሰሜን ኮሪያ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጋር በኒውክሌር  መርሃ ግብር እና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ዙሪያ ለመወያየት ባላቸው ፍላጎት የተነሳ ከደቡብ ኮሪያ ጋር የሚደረጉ የጋራ ወታደራዊ ልምምዶችን ለመቀነስ መወሰናቸውን ተከትሎ ነው። ይህ በእንዲህ እንዳለ፤ ከጃፓን እና ከአሜሪካ ጋር በመሆን መስከረም ሁለተኛው ሳምንት ላይ የሰሜን ኮሪያን የሚሳኤል እና የኒውክለር ዛቻ ለመቀነስ በሚል ወታደራዊ ልምምድ እንደሚያካሂዱ ሴኡል አስታውቃለች፡፡ ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

በኡጋንዳ የኢቦላ ወረርሽኝ ማብቃቱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ ሐሙስ፣ ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) በኡጋንዳ ተከሰቶ የነበረው የቡንዲቡግዮ የኢቦላ ዝርያ ወረርሽኝ መጠናቀቁን፤ በአንጻሩ በአጎራባች ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ የቫይረሱ ስርጭት አሁንም በቁጥጥር ሥር አለመዋሉን የዓለም ጤና ድርጅት ባለሥልጣን አስታወቁ። ለኡጋንዳ የተሰጠው ከበሽታው ነፃ የመሆን ማረጋገጫ፣ የሃገሪቱ መንግሥት እ.አ.አ ሐምሌ 28 ያቀረበውን ጥሪ ተከተሎ የመጣ ሲሆን፣ በኡጋንዳ በወረርሽኙ 20 ሰዎች ሲያዙ የሁለት ሰዎች ሕይወት አልፏል። የዓለም ጤና ድርጅትም ምንም ዓይነት የቫይረሱ መተላለፊያ ሰንሰለት አለመቀረቱን ለማረጋገጥ እስከዚህ ሳምንት ድረስ ሁኔታውን ሲከታተል መቆየቱን ገልጿል። ነገር ግን የዓለም ጤና ድርጅት የአፍሪካ ክልል ድንገተኛ ዝግጅት ዳይሬክተር ዶክተር ማሪ ሮዝሊን ቤሊዛየር በድርጅቱ ቀጣናዊ ስብሰባ ወቅት እንደገለጹት፣ በዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊክ ኮንጎ የተወሰኑ መሻሻሎች ቢኖሩም የበሽታው ስርጭት እየጨመረ ይገኛል። በኮንጎ የተከሰተው ይህ ወረርሽኝ በታሪክ ሁለተኛው ከፍተኛ ገዳይ ሲሆን የመከላከል ጥረቱንም ፈተና ላይ ጥሎታል። በኮንጎ መንግሥት መረጃ መሠረት እስከ ማክሰኞ ድረስ ከ2,700 በላይ ሰዎች ሲሞቱ ከ5,600 በላይ ደግሞ በቫይረሱ ተይዘዋል። የበሽታው የመተላለፍ ሁኔታ አሁንም ከፍተኛ ነው ያሉት ዶክተር ማሪ፤ የስርጭቱን ፍጥነት ማዘገየት ብንችልም አሁንም አቅጣጫውን ሙሉ በሙሉ መቀየር አልቻልንም ብለዋል። አክለውም በተጋላጭ ሰዎች ፍለጋና በምርመራ ሂደት ላይ መሻሻሎች መኖራቸውን ጠቁመው፣ የቡንዲቡግዮ ቫይረስ በፍጥነት ቢስፋፋም እስካሁን ምንም ዓይነት የዝርያ ለውጥ አለማሳየቱን ገልጸዋል። ይህን የምሥራች ቢያበስሩም፣ በኮንጎ በጣም በተጎዱ አካባቢዎች የሕክምና እና የግል መከላከያ መሣሪያዎችን ለማቅረብ ለሚደረገው የሎጀስቲክስ ሥራ አፋጣኝ የ30 ሚሊዮን ዶላር የገንዘብ እጥረት እንዳለ አስጠንቅቀዋል። ያለዚህ አፋጣኝ ኢንቨስትመንት ያገኘነውን ግስጋሴ የማጣት አደጋ ላይ እንወድቃለን ሲሉ ዶክተር ማሪ አሳስበዋል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

አሜሪካ በአውሮፓ የሚገኘው የጦር ኃይሏን ለማንቀሳቀስ ግምገማ እንዲካሄድ አዘዘች ሐሙስ፣ ነሐሴ 21 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የዩናይትድ ስቴትስ መከላከያ ሚኒስቴር በአውሮፓ የሚገኙ ጦር ሰፈሮቹን ለመቀነስ እና አህጉሪቱ ደህንነቷን በራሷ መጠበቅ እንድትችል ለማድረግ ግምገማ ማካሄድ ጀመረ። ሚኒስቴሩ በአውሮፓ የሚገኘውን የጦር ኃይል ስምሪትና  አደረጃጀትን በተመለከተ ቢያንስ አራት የተለያዩ የአማራጭ ዕቅዶችን እስከ ህዳር 2026 እ.አ.አ. ድረስ ለመከላከያ ሚኒስትሩ ፒት ሄግዝ ለማቅረብ እየሰራ መሆኑ ተነግሯል። ይህ እርምጃ አሜሪካ በአውሮፓ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት ወዲህ የነበራትን ወታደራዊ ሚና እና የኔቶን አጋርነት ለመገምገም የሚደረገው ጥረት አካል ነው ተብሏል። ሮይተርስ ምንጮቸ ነገሩኝ ብሎ እንደዘገበው ከሆነ፤ ፔንታጎን ለመከላከያ ሚኒስትሩ በሚያቀርበው ግምገማ ውስጥ የአሜሪካ ጦር በአውሮፓ የሚኖረውን የወደፊት መዋቅር፣ የወታደሮች ቁጥር መቀነስ ወይም የቦታ ለውጥ ለማድረግ ቢያንስ አራት ስትራቴጂካዊ አማራጮችን ያዘጋጃል። በተጨማሪም አጋር ሀገራት የሚገመገሙት የኔቶ የመከላከያ ወጪ ግዴታቸውን፤ ማለትም ከተያዘው የሀገር ውስጥ ጠቅላላ ምርታቸው አምስት በመቶውን በጀት መመደብን የሚመለከተውን በሚያሟሉበት ደረጃ፣ ለአሜሪካ ጦር የሚያቀርቡት የካምፕ፣ የጦር ሰፈርና የአየር ክልል አጠቃቀም ፈቃድ እንዲሁም ከአሜሪካ የውጭ ፖሊሲ ቅደም ተከተሎች ጋር በሚያደርጉት ትብብር መሠረት የሚገመገሙ ይሆናል። አሜሪካ ለአጋር ሀገራት የላከችው መጠይቅ ምላሽ እስከ ነገ ዓርብ ድረስ እንደሚጠናቀቅ የተገለጸ ሲሆን ይህም ግምገማውን ለማፋጠን እንደሚረዳ ተጠቅሷል። የዚህ ግምገማ ዋና ዓላማ አውሮፓውያን ለራሳቸው አህጉር የመከላከያ ደሀንነት ዋናውን ኃላፊነት እንዲወስዱ ለማድረግ እና የአሜሪካን ወታደራዊ ኃይል ለሌሎች ዓለም አቀፋዊ ጉዳዮች ለማመቻቸት ነው። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA