uz
Feedback
Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Kanalga Telegram’da o‘tish

ዜና ከምንጩ

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Addis Maleda - አዲስ ማለዳ analitikasi

Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 31 881 obunachidan iborat bo'lib, Yangiliklar & Media toifasida 7 849-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 067-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 31 881 obunachiga ega bo‘ldi.

11 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 123 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 17.46% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 10.59% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 566 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 3 377 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 14 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
ዜና ከምንጩ

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 12 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Yangiliklar & Media toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

31 881
Obunachilar
-724 soatlar
+247 kunlar
+12330 kunlar
Postlar arxiv
ሦስት ፓርቲዎች በተለያዩ አካባቢዎች “ምርጫው እንዲደገም” ሲጠይቁ፣ ሁለት ፓርቲዎች ደግሞ አጠቃላይ “ምርጫውን ዕውቅና” ነፈጉ ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) በኢትዮጵያ ከተካሄደው 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ጋር ተያይዞ የተለያዩ የፖለቲካ ፓርቲዎች ተቃውሞና ቅሬታቸው እየበረታ የመጣ ሲሆን ሦሰት ፓርቲዎች በተለያዩ ስፍራዎች “ምርጫው እንዲደገም” ሲጠይቁ ሁለቱ ደግሞ “ሙሉ እውቅና በመንፈግ” አጥብቀው አወገዙ። ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲ (ጎጎት)፣ የነፃነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) እንዲሁም የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትሕ ፓርቲ (ኢዜማ) በተለያዩ አካባቢዎች ምርጫው እንዲደገም ሲጠይቁ፤ በሌላ በኩል ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት እና የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) አጠቃላይ የምርጫውን ሂደት ዕውቅና መንፈጋቸውን በተናጠል ባወጧቸው መግለጫዎች አስታውቀዋል። ጎጎት ለጉራጌ አንድነት እና ፍትሕ ፓርቲ(ጎጎት) በዛሬው ዕለት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ በተወዳደረባቸው በጉራጌ እና በምሥራቅ ጉራጌ ዞኖች ምርጫው በድጋሚ እንዲካሄድ በይፋ ጠይቋል። ፓርቲው በምርጫ ዕለት “ከሕግ ያፈነገጡ በርካታ ተግባራት መፈጸማቸውን” የገለጸ ሲሆን በእነዚህ አካባቢዎች የሚገኙ የምርጫ ጣቢያዎች በገዢው ፓርቲ “ቁጥጥር ሥር ወድቀው” እንደነበረ በመጥቀስ፣  መታወቂያ የሌላቸውና ጣታቸው ላይ ምልክት ያልተደረገባቸው መራጮች በተደጋጋሚ ድምጽ ሲሰጡ ተስተውሏል ብሏል። በተጨማሪም የድምጽ መስጫ ሳጥንን መገልበጥ እና ምልክት በተደረገበት ወረቀት ድምጽ የመስጠት “ሕገ ወጥ ሂደቶች” መፈማቸውን ፓርቲው ማረጋገጡን ይፋ አድርጓል። ፓርቲው  እነዚህን የምርጫ ሕግ ጥሰቶች ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ማቅረቡንና ጉዳዩ በገለልተኛ አካል ታይቶ ውሳኔ እንዲሰጥበት መጠየቁን ገልጧል። ምርጫ ቦርድ በበኩሉ ከተለያዩ ፓርቲዎች ቅሬታ መቀበሉንና ጉዳዩን ለመመርመር የሕግ ባለሙያዎች ጉባዔ ማቋቋሙን  እንዲሁም 120 የምርጫ ክልሎች ላይ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን በትናንትናው ዕለት በሰጠው መግለጫ ማስታወቁ ይታወሳል። ከጎጎት አስቀድሞ ነእፓ ደግሞ፣ “በአማራ ክልል ዳግም መካሄድ” አለበት ሲል፣ ኢዜማ በተመሳሳይ በተለያዩ የምርጫ ክልሎች “እንዲደገም” መጠየቁ አይዘነጋም። ኦፌኮ እና ትብብሩ ደግሞ “ምርጫው የፖለቲካ ድራማ ነው” በማለት ዕውቅና እንደነፈጉት አዲስ ማለዳ ከመግለጫዎቻቸው ለመረዳት ችላለች። ሂደቱን ሙሉ በሙሉ ውድቅ ያደረገው  ኦፌኮ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ “አምባገነናዊነትን ሕጋዊ ለማድረግ የተወጠነ የፖለቲካ ድራማ” ሲል ኮንኖታል። ፓርቲው ባወጣው መግለጫ፣ በሀገሪቱ ሰፋፊ ክልሎች አውዳሚ ጦርነት እየተካሄደና የፖለቲካ ምህዳሩ በተዘጋበት ሁኔታ በግድ የተጫነ ምርጫ ሰላምና ዴሞክራሲን አያመጣም ሲል ተችቷል። ኦፌኮ የምርጫ አስፈጻሚዎችን አድሏዊነት፣ የመራጮችን መታፈንና የምርጫ ታዛቢዎችን ሚና የነቀፈ ሲሆን፣ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ታዛቢዎች ያወጡትን ሪፖርት “የምርጫ ዕለት ቱሪዝም” ሲል አጣጥ፣ ፈርጆታል። ፓርቲው ብቸኛው መፍትሔ ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ውይይትና ድርድር መሆኑን በመጥቀስ፣ ለአጠቃላይ የምርጫው ሂደት ዕውቅና እንደማይሰጥ አስታውቋል። በተመሳሳይ መልኩ አጠቃላይ ምርጫውን የነቀፈው ትብብር ለኢትዮጵያ አንድነት፣ ሂደቱ ካለፉት አምባገንናዊ የጥርነፋ ባህሪያት ያልተላቀቀና “ከጨረባ ምርጫ” የማይለይ መሆኑ ገሃድ የወጣ ሲል ባለፈው ሳምንት ማስታወቁ አይዘነጋም። ትብብሩ ለአዲስ ማለዳ በላከው መግለጫ “የምርጫው ውጤት ምንም ቢሆን የትኛውም ዕጩ በትብብሩ ስም ምክር ቤት እንዳይገባና ቢገባም ፍጹም ተቀባይነት የሌለው መሆኑን” በጥብቅ ማሳሰቡ ይታወቃል። ትብብሩ ወደ ምርጫው የገባው የመንግስትን “የነውር ገመና በተጨባጭ ለማጋለጥ በማለም” እንደነበር ጠቅሶ፣ መንግስት የሕዝብን ድምጽ እስከሚያከብር ድረስ ሕዝብን ያሳተፈ ሰላማዊ ትግል እንደሚያደርግም ጭምር ገልፆ ነበር። እንዲሁም በተለይ ሁለቱ ፓርቲዎች(ኦፌኮና ትብብር) ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብና የዲፕሎማቲክ ተልዕኮዎች መንግስት ሸብረክ ብሎ ከፖለቲካ ኃይሎች ጋር እስከሚደራደር ድረስ ለሂደቱ ምንም ዓይነት ዕውቅና ከመስጠት እንዲቆጠቡ አጥብቀው አሳስበዋል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በምክክሩ ላይ “የማይካተቱ አጀንዳዎች” ወደ ክልሎች ይመለሳሉ አለ ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከሕዝብ የተሰበሰቡ የአጀንዳ ግብዓቶችን የመለየት ሥራ እያከናወነ መሆኑን በመግለጽ፣ በሀገራዊ ምክክሩ መድረክ ሊካተቱ የማይችሉ አካባቢያዊ ጉዳዮች ምላሽ እንዲያገኙ ወደ ክልሎችና ወደሚመለከታቸው አስፈጻሚ አካላት እንደሚመለሱ አስታወቀ። ኮሚሽኑ ይህንን የገለጸው በትናንትናው ዕለት ረቂቅ አጀንዳዎችን ለፖለቲካ ፓርቲዎች አቅርቦ ግብዓት በሚሰበስብበት ወቅት ነው። ኮሚሽኑ እንደተናገረው ከሆነ፣ ከአንደኛው ዙር የአጀንዳ ማሰባሰብ ሂደት በርካታ ጥያቄዎችና ግብዓቶች የተገኙ ቢሆንም፣ ሁሉም ጉዳዮች ለሀገራዊ ምክክር የሚቀርቡ አይደሉም። በመሆኑም የተሰበሰቡት አጀንዳዎች በሁለት ዋና ዋና ዘርፎች ተከፍለው እንዲታዩ ተደርጓል። የመጀመሪያው ዘርፍ ወደ ክልሎችና ወደ አስፈጻሚ አካላት የሚመለሱ አጀንዳዎች ናቸው። እነዚህም በነባር የሕግና የፖሊሲ ማዕቀፎች ምላሽ ሊያገኙ የሚችሉ፣ ነገር ግን በተለያዩ ምክንያቶች ሳይፈጸሙ የቆዩ የሕዝብ ጥያቄዎችና “የሕዝብ እሮሮዎች” ናቸው። እነዚህ አጀንዳዎች የሕዝብ ድምፅ በመሆናቸው መጥፋት የለባቸውም ያለው ኮሚሽኑ፤ ጉዳዩ በቀጥታ ወደሚመለከታቸው የክልል መንግሥታትና የፌዴራል አስፈጻሚ አካላት ተመልሰው መፍትሔ እንዲያገኙ እንደሚደረግ አስታውቋል። ሁለተኛው ደግሞ ለሀገራዊ ምክክሩ መስፈርቱን የሚያሟሉ አጀንዳዎች ናቸው። እነዚህ አጀንዳዎች በኮሚሽኑ መቋቋሚያ አዋጅ ላይ በተቀመጡት መስፈርቶች ተመዝነው የሚለዩ ሲሆን፤ እንደ ሕገ መንግሥት ማሻሻያ፣ የፖለቲካ ሥርዓት ለውጥ እና መሠረታዊ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ጉዳዮችን ያካተቱ ናቸው። በእነዚህ አጀንዳዎች ላይ በቅርቡ በሚደረገው ጉባኤ ከአራት ሺህ በላይ ተሳታፊዎችን ያካተተ ምክክር እንደሚደረግ ተገልጿል። የኢትዮጵያ ሀገራዊ ምክክር ዋና ኮሚሽነር ፕሮፌሰር መስፍን አርዕያ(ፕሮፌሰር) እንደገለጹት፤ አጀንዳዎቹን ወደ ክልል መላክ ያስፈለገው በኮሚሽኑ ሕግ መሠረት የተሻለና ፈጣን መፍትሔ እንዲያገኙ ለማድረግ ነው። ዋና ኮሚሽነሩ፣ “አንዳንድ አጀንዳዎች እዚያው በየክልላቸው ማለቅ የሚገባቸው፣ አንዳንዶቹ አካባቢያዊ ናቸው፤ አንዳንዶቹ ደግሞ በሁለት ክልሎች መካከል ውይይት የሚያስፈልጋቸው ናቸው” ካሉ በኋላ፣ እነዚህ ጉዳዮች ሀገራዊ የሚያሰኛቸውን መመዘኛ በሕጉ መሠረት ማሟላት የማይችሉ መሆናቸውን አስረድተዋል። ፕሮፌሰር መስፍን አክለውም፣ አጀንዳዎችን የመመለስ ሂደት የምክክር መድረኩ ትኩረት ሊሰጣቸው በሚገቡ ዋና ዋና ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ብቻ እንዲያተኩር ለማስቻል እንደሆነ አስገንዝበዋል። ወደ ክልል የሚመለሱ ጉዳዮች ይጣላሉ ማለት እንዳልሆነ የገለጹት ዋና ኮሚሽነሩ፣ “አጀንዳዎች በክብር ወደመጡበት ይመለሱ እንጂ ምንም ይሁን ምን የሚጣል አጀንዳ የለም” ሲሉ አረጋግጠዋል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

በእነክርስቲያን ታደለ የክስ መዝገብ ፍርድ ቤቱ ለዋናው ብይን መደበኛ ቀጠሮ ባይሰጥም፤ ማረሚያ ቤቱ ግን ለሰኔ 16 ተቀጠረ ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በእነክርስቲያን ታደለ የክስ መዝገብ ላይ “ክሳቸውን ይከላከሉ ወይስ በነፃ ይሰናበቱ?” የሚለውን ዋና ብይን ለመስጠት መደበኛ ቀጠሮ ለመቁረጥ ፈቃደኛ ሳይሆን መቅረቱን የተከሳሾቹ ጠበቃ ሰለሞን ገዛኸኝ ለአዲስ ማለዳ ገለጹ። ፍርድ ቤቱ ለብይኑ መደበኛ ቀን ባይቆርጥም፣ ተከሳሾቹ በማረሚያ ቤት እየተፈጸመብን ነው ስላሉት የሰብዓዊ መብት ጥሰት ግን የማረሚያ ቤቱ ኃላፊ ማብራሪያ ይዘው እንዲቀርቡ ለሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል። ጠበቃ ሰለሞን ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም ስለነበረው የችሎት ውሎ እንደተናገሩት፣ ተከሳሾቹ “ፍርድ ቤቱ ለብይኑ ለምንድነው ቀጠሮ የማይሰጠን?” ሲሉ ላቀረቡት ጥያቄ፣ ችሎቱ ሲመልስ “ጉዳዩ ሊያልቅ የተወሰነ ነገር ስለሆነ የቀረው ይሄ ነው የሚባል ቀን አልወስንም” ማለቱን ገልጸዋል። በመሆኑም ጉዳዩ ሊጠናቀቅ የተቃረበ በመሆኑ፣ ፍርድ ቤቱ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱን ለመስማት በሰየመው በዚሁ “በሰኔ 16 ቀን ላይ ዋናው ብይን ሊገለጽ ይችላል፤ ካልሆነ ግን ከዛ በኋላ ባሉት ቀናት ልናሰማ እንችላለን” የሚል ውሳኔ ማስተላለፉን ጠበቃው ጠቅሰዋል። በዕለቱ ተከሳሾቹ “ጉዳዩን የሚከታተሉ የሚዲያ አካላት እና ቤተሰቦቻችን ቀኑን ቀድመው ማወቅና መስማት ስላለባቸው መደበኛ ቀጠሮ ሊሰጠን ይገባል” የሚል ጠንከር ያለ ጥያቄ ቢያነሱም፣ ችሎቱ ግን ተጨማሪ ቀጠሮ ለመስጠት ፈቃደኛ ሳይሆን “በሰኔ 16 ወይም ከዚያ በኋላ ብይኑን እናሰማለን” በማለት የዕለቱን ችሎት ማጠናቀቁ ታውቋል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ለነዳጅ ተሽከሪካሪዎች የሚሰጠው ሰሌዳ ዋጋ እስከ 56 ሺህ ብር እንደሚያስከፍል አስታወቀ ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ መስጠት የጀመረ ሲሆን፣ ለነዳጅ ተሽከርካሪዎች የሚሰጠው ሰሌዳ ዋጋ እስከ 56 ሺህ ብር መሆኑን ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። ባለሥልጣኑ እንደገለጸው፣ ይህ የወጣው ዋጋ አዲሱ የቴክኖሎጂ ሰሌዳ የሚሰጠውን የረዥም ጊዜ አስተማማኝ ጥቅም ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው። አዲሱ የሰሌዳ አሰጣጥ አገልግሎት በዛሬው ዕለት በባለሥልጣኑ 11 ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በይፋ የተጀመረ ሲሆን፣ በቅድሚያ ሰሌዳ ለማውጣት ተመዝግበው በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ ከአንድ ሺህ በላይ ደንበኞች እየተሰጠ ይገኛል። በቀጣይም የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር በሚያወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ሌሎች ተሽከርካሪዎችም ደረጃ በደረጃ አዲሱን ሰሌዳ እንዲወስዱ ይደረጋል። ይህ አዲስ ሰሌዳ ከተሽከርካሪዎች ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የደኅንነትና የሥርቆት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እንዲያስችል ተደርጎ ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። አሁን ላይ በሥራ ላይ የዋለው ሰሌዳ ከቻይና ተመርቶ የገባ ቢሆንም፣ ለአመራረት ቀላል በመሆኑ በቀጣይ በአገር ውስጥ ተመርቶ ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱም ተመልክቷል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

የአዲስ አበባ አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ለነዳጅ ተሽከሪካሪዎች የሚሰጠው ሰሌዳ ዋጋ እስከ 56 ሺህ ብር እንደሚያስከፍል አስታወቀ ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር አሽከርካሪና ተሽከርካሪ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን አዲስ የተሽከርካሪ ሰሌዳ መስጠት የጀመረ ሲሆን፣ ለነዳጅ ተሽከርካሪዎች የሚሰጠው ሰሌዳ ዋጋ እስከ 56 ሺህ ብር መሆኑን ዛሬ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቋል። ባለሥልጣኑ እንደገለጸው፣ ይህ የወጣው ዋጋ አዲሱ የቴክኖሎጂ ሰሌዳ የሚሰጠውን የረዥም ጊዜ አስተማማኝ ጥቅም ከግምት ውስጥ ያስገባ ነው። አዲሱ የሰሌዳ አሰጣጥ አገልግሎት በዛሬው ዕለት በባለሥልጣኑ 11 ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶች በይፋ የተጀመረ ሲሆን፣ በቅድሚያ ሰሌዳ ለማውጣት ተመዝግበው በመጠባበቅ ላይ ለሚገኙ ከአንድ ሺህ በላይ ደንበኞች እየተሰጠ ይገኛል። በቀጣይም የትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር በሚያወጣው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት ሌሎች ተሽከርካሪዎችም ደረጃ በደረጃ አዲሱን ሰሌዳ እንዲወስዱ ይደረጋል። ይህ አዲስ ሰሌዳ ከተሽከርካሪዎች ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የደኅንነትና የሥርቆት ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት እንዲያስችል ተደርጎ ከዘመናዊ ቴክኖሎጂ ጋር የተሳሰረ መሆኑ ተገልጿል። አሁን ላይ በሥራ ላይ የዋለው ሰሌዳ ከቻይና ተመርቶ የገባ ቢሆንም፣ ለአመራረት ቀላል በመሆኑ በቀጣይ በአገር ውስጥ ተመርቶ ተደራሽ ለማድረግ መታቀዱም ተመልክቷል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

ለቀጣዩ በጀት ዓመት የማዳበሪያ ድጎማ 100 ቢሊዮን ብር መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታወቀ ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የገንዘብ ሚኒስቴር ለ2019 ዓ.ም ለማዳበሪያ ድጎማ እንዲውል የታሰበው በጀት 100 ቢሊዮን ብር አድርጎ ለህዝብ እንደራሴዎች አቅረበ። ሚኒስቴሩ ለ2019 በጀት ዓመት 2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ አድርጎ ረቂቁን ያቀረበ ሲሆን በበጀት ዓመቱ የፌደራል መንግስት ከሀገር ውስጥ ገቢ ምንጮች እና ከውጭ ሀገር እርዳታ 1.8 ትሪሊዮን ገቢ ለመሰበስብ እቅድ መያዙን ተናግሯል። የገንዘብ ሚኒስትሩ አህመድ ሽዴ በዛሬው ዕለት በቀጣዩ የሐምሌ ወር ላይ የሚጀምረውን የበጀት ዓመት ዝርዝር እና መጠን የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው 5ተኛ ዓመት የሥራ ዘመን 25ተኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ቀርበው አብራርተዋል፡፡ ከማዳበሪያ በተጨማሪ ለነዳጅ ድጎማ እንዲውል የታሰበው በጀት 20 ቢሊዮን ብር እንደሆነ የገለጹት ሚኒስትሩ የኢትዮጵያ ነዳጅ አቅራቢ ድርጅት ካፒታልን ለማሳደግ 116.4 ቢሊዮን ብር ከመንግስት ግምጃ ቤት የተመደበ መሆኑን ለፓርላማው አስረድተዋል ። ከዚሁ በተጨማሪም ለልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም ማስፋፊያ የሚያስፈልገውን በጀት ከግምት ውስጥ በማስገባት የካፒታል ወጪዎች በዋናነት የነባር ፕሮጀክቶችን ለማስፈፀም የሚያስፈልገውን ወጪ እንዲያካትት መደረጉን ተገልጿል። የክልሎችን የበጀት ድጋፍ በተመለከተ በ2018 የተደረገውን የክልል ሰራተኞች እና ተሿሚዎች የደመወዝ ጭማሪ ማስተካከያ ዓመታዊ ወጪን በ2018 ከጸደቀው የክልሎች የጥቅል በጀት ድጋፍ ጋር በመደመር ለ2019 በጀት ዓመት እስከ አምስት በመቶ ጭማሪ እንዲኖረው ተደርጓል ብለዋል። ሚኒስትሩ አክለውም በአጠቃላይ የ2019 የመንግስት ወጪ ፖሊሲ የፊስካል ቁመናን ማጠናከር እና የማክሮ ኢኮኖሚ መዛባትን በሚያስተካክል መልኩ የተዘጋጀ ነው ብለዋል ። የ2019 የፌደራል መንግስት ረቂቅ በጀት የተመጠነ የበጀት ጉድለት እንዲኖረው ተደርጎ የተዘጋጀ በጀት ነው ያሉ ሲሆን ይህም ከ ሀገር ውስጥ እና ዉጭ በሚገኝ ገንዘብ እንደሚሸፈን አንስተዋል። የ2019 የፌደራል መንግስት ረቂቅ በጀት የተመጠነ የበጀት ጉድለት እንዲኖረው ተደርጎ የተዘጋጀ በጀት ነው ያሉ ሲሆን ይህም ከ ሀገር ውስጥ እና ዉጭ በሚገኝ ገንዘብ እንደሚሸፈን አንስተዋል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

አሜሪካ በኢራን ላይ በከባድ ቦንቦች የታገዘ ድብደባ ማድረሷን ተከትሎ ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥ ሙሉ ለሙሉ መዝጋቷን አስታወቀች ሐሙስ፣ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ ማለዳ) በአሜሪካ እና በኢራን መካከል ያለው ወታደራዊ ግጭት በከፍተኛ ሁኔታ ማገርሸቱን ተከትሎ፣ የኢራን ወታደራዊ ዕዝ የዓለም የነዳጅ አቅርቦት ቁልፍ መተላለፊያ በሆነው የሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ የነዳጅ ጫኝ መርከቦችንና የንግድ ትራፊክን ሙሉ በሙሉ መዝጋቱን አስታወቀ። ኢራን ይህን አስቸኳይ እርምጃ የወሰደችው የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግዝ አሜሪካ በኢራን ቁልፍ ተቋማት ላይ ጠንካራ የአየር ድብደባ ማድረሷን በይፋ ከገለጹ በኋላ ሲሆን አሁን ላይ ምንም ዓይነት መርከብ ቦታው ማለፍ አይችልም ብላለች። የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ትራምፕ ኢራን ስምምነቱን የማትቀበል ከሆነ በነገው ዕለት አይታው የማታውቀው ጥቃት እንፈፅማለን ሲሉ ዝተዋል። የአሜሪካ መከላከያ ሚኒስትር ፒት ሄግዝ በፍሎሪዳ ከሚገኘው የአሜሪካ ማዕከላዊ ዕዝ ዋና መሥሪያ ቤት በሰጡት መግለጫ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ያስተላለፉትን ትዕዛዝ መሠረት በማድረግ የአሜሪካ ጦር በኢራን ውስጥ በሚገኙ ቁልፍ ወታደራዊ እና የስትራቴጂክ ተቋማት ላይ የቦምብ ድብደባ አካሂደናል ሲሉ አስታውቀዋል። ሚኒስትሩ ይህንን እርምጃ “ኢራን በቀጣናው በምታሳየው መተናኮስ እና በሰላም ድርድሩ ላይ በወሰደችው ግትር አቋም” ምክንያት የመጣ መሆኑን በመግለፅ ጥቃቱ በተሳካ ሁኔታ መከናወኑንና የኢራንን ወታደራዊ አቅም ለማዳከም የታለመ ነው ሲሉ ተናግረዋል። ይህንን የአሜሪካን ድብደባ ተከትሎ የኢራን ኻታም አል-አንቢያ የተሰኘው ከፍተኛ ጥምር ጦር እዝ አስቸኳይ መግለጫ ያወጣ ሲሆን የሆርሙዝ ወሽመጥ ለማንኛውም ዓይነት የባህር ላይ ትራፊክ በተለይም ለነዳጅ ጫኝ እና ለንግድ መርከቦች ሙሉ በሙሉ ዝግ መሆኑን አስታውቋል። እዙ አክሎም ትዕዛዙን ጥሶ ለመሻገር በሚሞክር በማንኛውም መርከብ ላይ ጦሩ ወታደራዊ እርምጃ ይወስዳል ሲል አስጠንቅቋል። የኢራን መንግስታዊ ሚዲያዎች በሆርሙዝ አቅራቢያ በነበሩ የአሜሪካ የጦር መርከቦች ላይ የ ሚሳኤልና የድሮን ጥቃት መሰንዘሩን የዘገቡ ቢሆንም የአሜሪካ ወታደራዊ ባለሥልጣናት ግን የተመታ መርከብ የለም በማለት አስተባብለዋል። አሁን ላይ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለፍጆታ የሚውለው የድንጋይ ከሰልና የነዳጅ አቅርቦት አንድ አምስተኛው የሚሻገርበት የሆርሙዝ ወሽመጥ መዘጋት በዓለም የነዳጅ ገበያ ላይ ወዲያውኑ ከፍተኛ ጭማሪ አስከትሏል ሲል ለሮይተርስ ዘግቧል። እንደ አዲስ የተከሰተው ይህ ወታደራዊ ግጭት ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ በሁለቱ ወገኖች መካከል ተደርሶ የነበረውን ደካማ የተኩስ አቁም ስምምነት ሙሉ በሙሉ ያፈረሰ ሲሆን የመካከለኛው ምስራቅ ቀጣና በሙሉ ወደ ከፋ የጦርነት ቀውስ ሊከተው እንደሚችል ዓለም አቀፍ ተንታኞች ስጋታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

በአፋር ክልል በራህሌ ወረዳ  የተከሰተውን ሰደድ እሳት መቆጣጠር አስቸጋሪ ሁኖብኛል አለ ሐሙስ፣ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ ማለዳ) በአፋር ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት፣በኪልበቲ ረሱ ዞን ራህሌ ወረዳ በሚገኝ ጥብቅ ደን ውስጥ ድንገተኛ የሰደድ እሳት መከሰቱን አሰታውቆ መቆጣጠር አስቻጋሪ ሁኖብኛል ሲል አስታወቀ። እሳቱ የተከሰተው ትላንት በትላንትናው ዕለት ዕኩለ ቀን ላይ ሲሆን በወረዳው ሃሌጉቢ ቀበሌ፣ ልዩ ስሙ አፋዓዶና ዔሊ ገረብ በተባለ ስፍራ መሆኑን የክልሉ መረጃ ያመላክታል። አደጋው እንደተከሰተ የአካባቢው ማህበረሰብ እና የወረዳው አመራሮች በጋራ በመሆን እሳቱን ለመቆጣጠር ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆኑን አንስቷል። ክልሉ አክሎም እስካሁን ባለው ሂደት በሰው ሕይወት፣ በእንስሳትና በንብረት ላይ የደረሰ ጉዳት የሌም ያለ ቢሆንም እሳቱን ሙሉ በሙሉ በቁጥጥር ስር ማዋል ግን አዳጋች ነው ብሏል። ለእሳቱ መባባስና በቁጥጥር ስር አለመዋል እንደ ምክንያት ያነሳው የአካባቢው ጥቅጥቅ ያለና ጥብቅ የደን ሽፋን  በመሆኑ፤ ከፍተኛ የሙቀት እና ደረቅ የአየር ሁኔታበመኖሩ መሆኑን አንስቷል። ክልሉ በተጨማሪም መልክዓ ምድሩ ተራራማና አስቸጋሪ በመሆኑ የእሳት አደጋ መከላከያ ተሽከርካሪዎች ወደ ስፍራው መድረስ አለመቻላቸው  ለመቆጣጠር አዳጋች መሆኑን ባወጣው መግለጫ አንስቷል። እነዚህ ተግዳሮቶች እሳቱ ወደ ሌሎች አጎራባች አካባቢዎች እንዳይዛመት ለመከላከል እየተደረገ ያለውን ጥረት በእጅጉ ፈታኝ አድርገውታል ያለ ሲሆን ለመቆጣጠር የሚደረገው ጥረት በቂም አለመሆኑን አንስቷል። የሰደድ እሳቱን ለመቆጣጠር በራህሌ ወረዳ ብቻ የሚደረገው ጥረት በቂ  አይደለም ያለ ሲሆን የጎረቤት ወረዳዎች ማለትም የኮነባ፣ አብዓላ፣ ዔረብቲ፣ ወሰማ እና የአፍዴራ ሕዝብ እንዲሁም ሌሎች የክልሉ የሕብረተሰብ ክፍሎች በጋራ በመረባረብና በቅንጅት በመስራት አደጋውን እንዲከላከሉ እና እግዛ እንድያደርጉለት ጥሪ ቀርቧል። አደጋውን ለመቀልበስ የሚያስችል የተቀናጀ የሰው ኃይል ድጋፍ አሁንም ወሳኝ በመሆኑ ሁሉም አካላት በኃላፊነት ሊንቀሳቀሱ ይገባል ያለ ሲሆን በአካባቢው ያለውን ከፍተኛ የሙቀት መጠን ከግምት በማስገባት በደን ውስጥ በሚፈጠሩ የተፈጥሮ ግጭቶች የእሳት አደጋ ሊቀሰቀስ ስለሚችል ከፍተኛ ጥንቃቄ እንዲደረግ አሳስቧል። ክልሉ አክሎም በስፋት እየተከናወነ ካለው የንብ ማነብ ተግባር ጋር ተያይዞ የእሳት አደጋ ሊከሰት ስለሚችል አርሶና አርብቶ አደሩ እሳትን በሚጠቀምበት ወቅት ጥንቃቄ በተሞላበት መንገድ እንዲንቀሳቀስ የሚመለከተው ቢሮ በአጽንኦት ማሳሰቢያ ሰጥቷል። በተለያዩ አካባቢዎችም የደን ቃጠሎ በሚከሰቱበት ወቅት ለመቆጣጠር አዳጋች መሆናቸውንም ይህ የመጀመሪያው አይደለም። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

ኦፌኮ 7ኛውን ጠቅላላ ምርጫ “አምባገነናዊነትን ሕጋዊ ለማድረግ የተወጠነ የፖለቲካ ድራማ” ሲል ኮነነ   ሐሙስ፣ ሰኔ 04 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)   የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. የተካሄደውን 7ኛ ጠቅላላ ምርጫ አስመልክቶ በትናንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ፤ ሂደቱ ለኢትዮጵያ ዘላቂ ሰላምን፣ መረጋጋትንና ዴሞክራሲያዊ አስተዳደርን እንደማያመጣ በጽኑ እንደሚያምን አስታወቀ።   ፓርቲው በተደጋጋሚ በግልጽ ማሳሰቡን ባስታወሰበት በዚሁ መግለጫው፤ ሰፋፊ የሀገሪቱ ክልሎች ውስጥ አውዳሚ የእርስ በእርስ ጦርነት እየተካሄደ ባለበት፣ ሰፊ የፖለቲካ ጭቆና በነገሰበት እና የፖለቲካ ምህዳሩ በተዘጋበት ሀገር ላይ በግድ የተጫነ የምርጫ ሂደት የዴሞክራሲ ምዕራፍ ሳይሆን “አምባገነናዊነትን ሕጋዊ ለማድረግ የተወጠነ የፖለቲካ ድራማ” መሆኑን አስገንዝቧል።   ኦፌኮ በመግለጫው እንዳብራራው፣ ፓርቲውን ጨምሮ እውነተኛ ያላቸው ተቃዋሚ ፓርቲዎች ነፃ፣ ፍትሐዊ እና ታማኝ ምርጫ ለማካሄድ የሚያስፈልጉ መሠረታዊ ቅድመ ሁኔታዎችን ከአንድ ዓመት በላይ በግልጽ ሲጠይቁ ቆይተዋል። ከእነዚህም መካከል፤ ግጭቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ፣ የፖለቲካ እስረኞች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ የተዘጉ የፓርቲ ጽሕፈት ቤቶች እንዲከፈቱ፣ አፋኝ የሚዲያ እና የሲቪል ማኅበረሰብ ሕጎች እንዲሰረዙ፣ እንዲሁም ገለልተኛና በጋራ መግባባት ላይ የተመሠረተ የምርጫ ቦርድና የጸጥታ አካላት እንዲዋቀሩ የሚሉት ይገኙበታል።   ሆኖም መንግሥት እነዚህን ጥሪዎች ወደ ጎን በመተው ምርጫውን ለይስሙላ ለማካሄድ በመወሰኑ፣ ፓርቲው ሕጉን ለማክበር ሲል ብቻ ጥቂት ዕጩዎችን በማቅረብ እጅግ የተገደበና ተምሳሌታዊ ተሳትፎ ማድረጉን ገልጿል።   የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ ምርጫው በዜጎች የመምረጥ መብት ላይ ከፍተኛ ገደብ የጣለ መሆኑን ጠቅሶ፣ በተለይም በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ባለው አውዳሚ ጦርነት ምክንያት ሂደቱ በከፍተኛ ወታደራዊ ጥበቃ ስር ባሉ ዋና ዋና ከተሞች ብቻ የተገደበ እንደነበርና የትግራይ ክልል ደግሞ ሙሉ በሙሉ እንዳልተካተተበት ገልጿል።   ሂደቱ በተከናወነባቸው አካባቢዎችም የምርጫ አስፈጻሚዎች ግልጽ አድሏዊነት፣ በመራጮች ላይ ማስፈራራት እንዲሁም የተቃዋሚ ተወካዮችን ከምርጫ ጣቢያ በኃይል የማስወጣት ሕገ-ወጥ ድርጊቶች መታዘቡን ጠቅሶ ፓርቲው ከስሷል።   የዓለም አቀፍና የሀገር ውስጥ ታዛቢዎችን ተሳትፎ በተመለከተም ኦፌኮ ጠንካራ ትችት ሰንዝሯል፡፡ የአፍሪካ ኅብረትና የኢጋድ ልዑካን አቋም በተመለከተ፤ ከ52,000 በላይ የምርጫ ጣቢያዎች ባሉባት ሀገር 100 የማይሞሉ ታዛቢዎችን በማሰማራት፣ ደህንነታቸው በተጠበቁ 208 (0.4%) ጣቢያዎች ላይ ብቻ በመገኘት ያወጡት የ“ሰላማዊና ግልጽነት” ሪፖርት “የምርጫ ዕለት ቱሪዝም” እንጂ እውነተኛ የታዛቢነት ሚና አይደለም ብሎታል።   የአውሮፓ ኅብረት አቋምን ደግሞ፤ በአካል ታዛቢ ሳይሰማራ፣ በርቀት ሆኖ ምርጫውን በበጎ መመልከቱ የኅብረቱን የዴሞክራሲ እሴቶች የሚጻረርና “የዲፕሎማሲ ማባበያ” ነው ሲል ኮንኖታል።   ኦፌኮ የሀገሪቱ ጥልቅ የፖለቲካ፣ የማኅበራዊና የኢኮኖሚ ስብራት ነፃና ፍትሐዊ ባልሆነ ምርጫ ሊጠገን እንደማይችል በመግለጽ፣ ብቸኛው አዋጭ መንገድ “ሁሉን አቀፍ የፖለቲካ ውይይት” ማካሄድ ብቻ መሆኑን አጽዕኖት ሰጥቷል። ይህ ውይይት በአሁኑ ወቅት ከመንግሥት ጋር በጦርነት ላይ ያሉ ታጣቂ ኃይሎችን ጨምሮ ሁሉንም ባለድርሻ አካላት ያካተተና በድርድር ላይ ለተመሠረተ አዲስ የፖለቲካ ስምምነት ፍኖተ ካርታ መሰረት የሚጥል መሆን እንዳለበት አሳስቧል።   በመጨረሻም ፓርቲው ሦስት አስቸኳይ ጥሪዎችን አስተላልፏል፤ ለኢትዮጵያ መንግሥት፤ የፖለቲካ ልዩነቶችን በወታደራዊ ኃይል የመፍታት ስልት እንደማይሠራ ተገንዝቦ፣ ግጭቶችን በአስቸኳይ እንዲያቆም፣ የፖለቲካ እስረኞችን እንዲፈታና ለሁሉን አቀፍ ውይይት እርምጃ እንዲወስድ፤   ለኢትዮጵያ ሕዝቦች፤  መሠረታዊ ችግሮች በዚህ ምርጫ እንደማይፈቱ በመረዳት፣ ለእውነተኛ ራስን በራስ ማስተዳደር፣ ለፍትሕ እና ለእውነተኛ ሕብረ-ብሔራዊ ፌዴራሊዝም በሚደረገው ሰላማዊ ትግል ላይ እንዲጸኑ፤   ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፤ ሂደቱ ነፃና አካታች እንዳልነበር በመገንዘብ፣ መንግሥት ሐቀኛና ሁሉን አቀፍ ሀገራዊ ውይይት እንዲያካሂድ ትርጉም ያለው ጫና እንዲያሳድር ጥሪ አቅርቧል። በመጨረሻም የኦሮሞ ፌደራላዊ ኮንግረስ (ኦፌኮ) ዴሞክራሲያዊት እና ሰላማዊት ፌዴራል ኢትዮጵያን እውን ለማድረግ ትግሉን በቁርጠኝነት እንደሚቀጥል በመግለጫው ማጠቃለያ አስታውቋል።   ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

የቻይናው ፕሬዝዳንት ሰሜን ኮሪያን መጎብኘታቸውን ተከትሎ ሁለቱ ሀገራት ከሉዓላዊነት መከበር እስከ ኢኮኖሚ ትብብር የሚዘልቅ አጋርነታቸውን ለማጠናከር ተስማሙ   ረቡዕ፣ ሰኔ 03 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)   የቻይናው ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ በሰሜን ኮሪያ ፒዮንግያንግ ባደረጉት ጉብኝት፣ ከሀገሪቱ መሪ ኪም ጆንግ ኡን ጋር በመሆን ስልታዊ ትብብራቸውን ይበልጥ ለማሳደግ ቃል ገብተዋል። በፒዮንግያንግ በተካሄደው በዚህ ጉባኤ መሪዎቹ ግንኙነታቸውን ይበልጥ ለማጥበቅ የተስማሙ ሲሆን፣ ሰሜን ኮሪያ ታይዋን፣ የቻይና ጠቅላላ የግዛት አካል መሆኗን በድጋሚ አረጋግጣለች።   የሰሜን ኮሪያ ብሔራዊ የዜና አገልግሎት እንደዘገበው፤ ፕሬዝዳንት ሺ ጂንፒንግ የሁለቱን ሀገራት ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ ቁርጠኛ መሆናቸውን ገልጸዋል። መሪዎቹ ይበልጥ የተቀራረበ ስልታዊ ግንኙነት ለመፍጠር በተስማሙበት ወቅት ኪም ጆንግ ኡን በበኩላቸው፤ ከቻይና ጋር ያለውን ወዳጅነት ማስቀጠል ለሰሜን ኮሪያ  “ከሁሉም በላይ ቅድሚያ የሚሰጠው ስልታዊ ተግባር” መሆኑን ገልጸዋል።   ኪም ጆንግ ኡን ፕሬዝዳንት ሺን “የላቀ የሀገር እንግዳ” በማለት የጠሯቸው ሲሆን፣ ሺ እ.አ.አ. 2026 የመጀመሪያ የውጭ ሀገር ጉዟቸውን ወደ ሰሜን ኮሪያ ማድረጋቸው ለሀገራቸው የተደረገ “ትልቅ ድጋፍ” መሆኑን ተናግረዋል። በተጨማሪም ፒዮንግያንግ ቤጂንግ ለምትከተለው “አንድ ቻይና መርህ” እና ታይዋን የቻይና የማይነጠል አካል ናት ለሚለው አቋም ያላትን ጽኑ ድጋፍ በድጋሚ ገልጻለች።   በሌላ በኩል የቻይናው ብሔራዊ ቴሌቪዥን እንደዘገበው፤ ቻይና በንግድ፣ በግብርና፣ በኮንስትራክሽን እና በቴክኖሎጂ ዘርፎች ጭምር ከሰሜን ኮሪያ ጋር ያላትን ትብብር ለማስፋፋት ፍላጎት እንዳላት ፕሬዝዳንት ሺ አስታውቀዋል።   ይህ የቻይናው ፕሬዝዳንት የሰሜን ኮሪያ ጉብኝት ከሰባት ዓመታት በኋላ የተደረገ የመጀመሪያው ሲሆን፣ የሁለቱን ሀገራት የወዳጅነት ስምምነት 65ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ግንኙነታቸው “አዲስ ታሪካዊ መነሻ” ላይ መድረሱን መሪዎቹ በጋራ አውጀዋል።   ሰሜን ኮሪያ ከሩሲያ ጋር ያላት ወታደራዊና ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት እያደገ ቢመጣም፣ ለህልውናዋ ግን አሁንም በዋናነት በቻይና ላይ ጥገኛ መሆኗን ስለምታውቅ ከቤጂንግ ጋር ያላትን ትስስር ማጠናከር እንደምትፈልግ የፖለቲካ ተንታኞች ያነሳሉ።   ቻይናም በበኩሏ በስትራቴጂካዊ መልኩ ወሳኝ በሆነችው ሰሜን ኮሪያ ላይ ያላትን ተፅዕኖ በድጋሚ ለማረጋገጥ እና ከአሜሪካ ጋር ለምታደርገው ዓለም አቀፋዊ ፉክክር ይህንን ግንኙነት ይበልጥ ተጽዕኖ ለማሳደር እየተጠቀመችበት እንደሆነ ባለሙያዎች ይገመግማሉ።   ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

ኢራን በዮርዳኖስ፣ ኩዌትና ባህሬን በሚገኙ የአሜሪካ የጦር ሰፈሮች ላይ ጥቃት ሰነዘረች     ረቡዕ፣ ሰኔ 03 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)     ኢራን በዮርዳኖስ በሚገኘው የአሜሪካ ጦር ሰፈር እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ ዙሪያ ባሉ ሌሎች 21 ኢላማዎች ላይ ጥቃት ሰነዘረች፡፡ ይህም ትራምፕ በሆርሙዝ ወሽመጥ አካባቢ ጥቃት እንዲሰነዘር ካዘዙ በኋላ መሆኑን ሮይተርስ ዘግቧል፡፡     የኢራን መገናኛ ብዙኃን እንደዘገቡት የኢራን አብዮታዊ ዘብ ኃይሎች አሜሪካ ጥቃት ማድረሷን ተከትሎ በዮርዳኖስ በሚገኝ የአሜሪካ ጦር ሰፈር እና በፋርስ ባህረ ሰላጤ በሚገኙ 21 ሌሎች ኢላማዎች ላይ ረቡዕ ቀን የአጸፋ ጥቃት ሰንዝሯል። ግጭቱ ሁለቱ አገራት እንደ እ.አ.አ  2026 በሚያዝያ ወር ስምምነት ላይ ከደረሱ በኋላ ከተከሰቱት ከፍተኛ ጥቃቶች አንዱ ነው። የኢራን ጥቃት በኩዌት እና በባህሬን ላይ የተፈሙ ጥቃቶችን ያካተተ ሲሆን ይህም የመጣው የአሜሪካ ጦር በኤክስ ገጹ ላይ ባወጣው መግለጫ በወሽመጡ አካባቢ የኢራን የአየር መከላከያ፣ የመሬት ቁጥጥር ጣቢያዎች እና የስለላ ራዳር ቦታዎች ላይ ጥቃት መሰንዘሩን መናገሩን ተከትሎ ነው።     የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ጥቃቱ የተፈጸመው ማክሰኞ ዕለት አንድ የአሜሪካ አፓቼ ሄሊኮፕተር በኢራን ተመትቶ በመውደቁ ምክንያት ነው ብለዋል። ትራምፕ ለኤቢሲ ኒውስ እንደተናገሩት “ምላሹ በጣም ጠንካራ፣ በጣም ኃያል መሆን አለበት፤  የሆነውም እሱ ነው” ብለዋል። የጥቃት መጠኑ መጨመር እ.አ.አ 2026 የካቲት 28 ቀን አንስቶ በአሜሪካ እና በእስራኤል በኢራን ላይ በጋራ በተሰነዘሩ ጥቃቶች  የተጀመረውን ጦርነት ለማስቆም ሊደረስ የሚችለውን ስምምነት ጥርጣሬን ላይ ጥሎታል።     ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA