uk
Feedback
Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Відкрити в Telegram

ዜና ከምንጩ

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу Addis Maleda - አዲስ ማለዳ

Канал Addis Maleda - አዲስ ማለዳ (@addismaleda) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 32 026 підписників, посідаючи 7 758 місце в категорії Новини і ЗМІ та 1 057 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 32 026 підписників.

За останніми даними від 02 липня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 177, а за останні 24 години на 29, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 14.03%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 9.30% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 4 494 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 980 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 9.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
ዜና ከምንጩ

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 03 липня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Новини і ЗМІ.

32 026
Підписники
+2924 години
+587 днів
+17730 день
Архів дописів
በኮንጎ ለተከሰተው ኢቦላ የህክምና ሙከራ መጀመሩን የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ ዓርብ፣ ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የዓለም ጤና ድርጅት በዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ የመቶዎችን  ሕይወት እየቀጠፈ የሚገኘው አደገኛውን የኢቦላ ወረርሽኝ መንስኤ የሆነውን የቫይረስ ዓይነት ለመዋጋት የሚስችል የሕክምና ሙከራዎች መጀመሩን አስታወቀ፡፡ የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም(ዶ/ር) እንደገለጹት የመጀመሪያው ታካሚ በዚሁ አዲስ የህክምና ሙከራ ውስጥ መካተቱን እና ለህክምና ምዝገባው በኮንጎ መጀመሩን አስታውቀዋል። ይህ ሙከራ የተጀመረው “ቡንዲቡግዮ ቫይረስ” ለተባለው እና በሀገሪቱ ለተቀሰቀሰው የኢቦላ ዝርያ እስካሁን የተፈቀደ እና የተረጋገጠ ምንም ዓይነት ፈቃድ ያገኝ  ክትባት ወይም መድኃኒት የሉትም ብሏል። እንደ ድርጅቱ መረጃ ከሆነ በኮንጎ ብቻ ከ1,400 በላይ በበሽታው የተጠቁ ግለሰቦች ያለ ሲሆን 438 ሰዎች ሕይወታቸው አልፏል፡፡ አሁን ያለው ሙከራ በዓለም ጤና ድርጅት በገንዘብ የሚደገፍ ሲሆን፣ በኮንጎ ብሔራዊ የባዮሜዲካል ምርምር ተቋም እና በቤልጂየም የትሮፒካል ሕክምና ተቋም እንዲሁም በዩናይትድ ኪንግደም የኦክስፎርድ ዩኒቨርሲቲ ሳይንቲስቶች ትብብር እየተካሄደ ይገኛል ተብሏል፡፡ ድርጅቱ በዋና መስሪያ ቤቱ ጄኔቫ በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ዋና ዳይሬክተሩ ቴድሮስ እንደገለጹት፣ የመጀመሪያው ታካሚ መመዝገቡን ተከትሎ የሁለቱ የሕክምና መድኃኒቶች ክሊኒካዊ ሙከራ በይፋ መጀመሩን ገልጸዋል። “ምንም እንኳን ፈቃድ ያገኙ ሕክምናዎች ባይኖሩም፣ ሰዎች ከዚህ በሽታ እያገገሙ ነው፡፡ ነገር ግን በእርግጥ ደህንነታቸው የተረጋገጡና እና ውጤታማ የሆኑ የሕክምና መሳሪያዎች ቢኖሩ ብዙ ተጨማሪ ሕይወቶችን ማዳን እንችል ነበር” ሲሉ የድርጅቱ ዳይሬክተር ተናግረዋል። በኮንጎ እና በዩጋንዳ የተነሳው የኢቦላ ወረርሽኝ የጀመረው በግንቦት ወር ላይ ሲሆን የዓለም ጤና ድርጅት ለሕዝብ ጤና ድንገተኛ አደጋ ነው ብሎታል፡፡ የኢቦላ በሽታ የሚከሰተው የሰውነትን በሽታ የመከላከያ ሥርዓትን እና የአካል ክፍሎችን በሚያጠቃ ቫይረስ ነው። ቫይረሱ በመደበኛነት እንስሳትን በተለይም ፍራፍሬ የሚበሉ የሌሊት ወፎችን የሚያጠቃ ቢሆንም በሰዎች መካከል ወረርሽኝ ሊፈጠር የሚችለው ሰዎች የተጠቁ እንስሳትን ሲይዙ እንደሆነ የድርጅቱ መረጃ ያሳያል። የበሽታው ተላላፊነት ደግሞ ብዙውን ጊዜ በሰዎች ላይ የበሽታ ምልክቶች ከታዩባቸው በኋላ ብቻ ነው፡፡ እንዲሁም የበሽታው ምልክቶቹ ለመታየት ከሁለት እስከ 21 ቀናት ይወስዳል። በተጨማሪም ምልክቶቹ በድንገት የሚታዩ ሲሆን እንደ ጉንፋን ወይም ወባና ትኩሳት፣ ራስ ምታት እና የድካም ስሜት በመሰማት የሚጀምር ነው። አሁን ወደ ስድስት ገደማ የኢቦላ ዝርያዎች ያሉ ሲሆን ለእያንዳንዱ የኢቦላ ዝርያ በተናጠል ክትባቶች መዘጋጀት ያለባቸው ቢሆንም ከእነዚህ ውስጥ ሦስቱ ብቻ ወረርሽኝ ያስከትላሉ። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

photo content

እስራኤል የኢራንን የድርድር ተወካዮች ለመግደል አቅዳ እንደነበር ተዘገበ ዓርብ፣ ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) አሜሪካና ኢራን በሁለቱ አገራት መካከል የነበረውን ውጥረት ለማርገብ በድርድር ላይ በነበሩበት ወቅት፣ እስራኤል የኢራንን ከፍተኛ የድርድር ተወካዮች ለመግደል እቅድ እንደነበራት የአሜሪካ ባለሥልጣናት ማመናቸውን ኒውዮርክ ታይምስ ዘግቧል። ስማቸው እንዳይገለጽ ያልፈፈቀዱ የአሜሪካ ባለሥልጣናት እንደተናገሩት፣ የእስራኤል ዋና ኢላማዎች የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራቺ እና የኢራን ፓርላማ አፈ-ጉባኤ እንዲሁም ዋና የድርድር ተወካይ መሐመድ ባገር ጋሊባፍ ነበሩ። አንድ የአሜሪካ ባለሥልጣን ለዋሽንግተን ፖስት በሰጡት ደግሞ አስተያየት፤ “እነዚህን ሰዎች ከገደላችኋቸው፣ በድርድር መንገድ መፍትሔ የሚፈልጉትን ወገኖች እያስወገዳችሁ ነው” ብለዋል። ዘ ኒው ዮርክ ታይምስ በበኩሉ፣ አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ያሉ አጋር አገራትን በመጠቀም ይህንን አደጋ ለኢራን ለማሳወቅ ጥረት ማድረጓን ባለሥልጣናትን ዋቢ አድርጎ መዘገቡን አልጀዚራ በዘገባው አሰፍሯል። በተጨማሪም እስራኤል በቀጣናው የሚካሄዱ የሰላም ድርድሮችን ለማሰናከል በሚል፣ የድርድር ተወካዮችን ኢላማ ያደረገችበት ታሪክ እንዳላት ሪፖርቶቹ ያመለክታሉ። ለዚህም ማሳያ በጥቅምት ወር በኳታር ዋና ከተማ ዶሃ የሐማስ ባለሥልጣናት የተኩስ አቁም ሀሳብ በሚመረምሩበት ወቅት፣ በቡድኑ መሪዎች ላይ የተፈጸመውን ጥቃት አስታውሰዋል፡፡ እስካሁን ድረስ እስራኤል በእነዚህ ሪፖርቶች ላይ ይፋዊ ምላሽ አልሰጠችም፤ የተጠቀሱት መረጃዎችም ስማቸው እንዳይገለጽ ከጠየቁ የአሜሪካ ባለሥልጣናት የተገኙ መሆናቸው ተጠቁሟል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

photo content

የኖርድስትሪም የሩሲያ ነዳጅ መተላለፊያ ፍንዳታ በዩክሬን የመንግስት አካላት ትዕዛዝ መፈጸሙን የጀርመን አቃቤ ህግ አስታወቀ ዓርብ፣ ሰኔ 26 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) ሩሲያ ለአውሮፓ ሀገራት ጀረመን የነዳጅ ማስተላለፊያ መስመር የሆነውን ኖርድ ስትሪም የፈነዳው በዩክሬን መንግስት እና ትዕዛዝ ነው የተባለ ሲሆን ዩክሬን ከአውሮፓ ሀገራት የምትገኘውን ድጋፍ እና ግንኙነት አደጋ ላይ መጣሉም ተገለጸ። የጀርመን መንግስት የፌደራል አቃቢ ህግ ሲሆን ማን ፈጸመው የሚለው ለብዙ ጊዜ ሲያከራክር የቆየ ነበር። ጀርመን ሊዮፓርድ ሁለት የተባለ ውድ የሆነ እና የመዋጋት አቅሙ ከፍተኛ የሆነ ታንክ ለዩክሬን ድጋፍ ስታደርግ የቆች ሀገር ናት፡፡ እ.አ.አ መስከረም 2022 በባልቲክ ባህር ስር የሚገኙትን እና ሩሲያን ከአውሮፓ ጋር የሚያገናኙትን የኖርድስትሪም አንድ እና ሁለት የጋዝ ማስተላለፊያ ቧንቧዎች ላይ የተፈጸመው የጥፋት እርምጃ በዩክሬን የመንግስት አካላት ቀጥተኛ ትዕዛዝ የተቀነባበረ መሆኑን የጀርመን የፌዴራል አቃቤ ህግ ይፋ አድርጓል። አቃቤ ህጉ በሀገሪቱ የግላዊነት ህግ ምክንያት ሰርሂ ኬ የተባለ እና የቀድሞ የዩክሬን ጦር መኮንን ላይ የጦር ወንጀል ክስ መመስረቱ ታውቋል። የክሱ ሰነድ በሃምበርግ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የቀረበ ሲሆን ተከሳሹ እና ሌሎች የዩክሬን ወታደራዊ አባላት የጥፋት ድርጊቱን የፈጸሙት “በዩክሬን የመንግስት አካላት በተሰጠ ትዕዛዝ” ነው ተብሏል። እንደ ጀርመን ድምጽ ዘገባ ከሆነ የመርማሪዎች ገለጻ የሚያመለክተው የዚህ ምስጢራዊ ዘመቻ ዋነኛ ዓላማ የሩሲያ ጋዝ ወደ አውሮፓ የሚጓጓዝበትን መስመር ሙሉ በሙሉ እና ዳግም በማያገግም ሁኔታ በማቋረጥ፣ ክሬምሊን በዩክሬን ላይ ለከፈተው ሙሉ ጥቃት የሚጠቀምበትን የገቢ ምንጭ ማድረቅ ነው ተብሏል። በጥቃቱ ምክንያት ከአራቱ የናፍጣ ማስተላለፈፊያ መስመሮች ውስጥ ሦስቱ ክፉኛ የተጎዱ ሲሆን፣ ከፍተኛ መጠን ያለው የሚቴን ጋዝ ወደ ከባቢ አየር እንዲለቀቅ ምክንያት ሆኗል ሲል ክሱን አሰምቷል። የጀርመኑ አቃቢ ህግ እንዳለው ከሆነ ፍንዳታው የተከሰተው ዩክሬን ጠላቂ ባለሙያዎችን፣ የመርከብ ካፕቴን እና የፈንጂ ባለሙያን ያካተተ ቡድን በመምራት በሀሰተኛ ሰነድ የተከራዩትን ጀልባ በመጠቀም ከጀርመን ሮስቶክ ወደ ዴንማርክ አቅራቢያ ወደምትገኘው ቦርንሆልም ደሴት በመጓዝ ነው። ቦርንሆለም ደሴት ከደረሱ በኋላ የወታደራዊ ደረጃ ያላቸውን አደገኛ እና በከፍተኛ ደረጃ የመፈንዳት አቅም ያላቸውን ፈንጂዎች ከቧንቧዎቹ ጋር በማያያዝ በጊዜ ቆጣሪ አማካይነት አፈንድተዋቸዋል ሲል አስታውቋል። ተከሳሹ ባለፈው የአውሮፓውያን ዓመት በጣሊያን በቁጥጥር ስር ውሎ ወደ ጀርመን ተላልፎ የተሰጠ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት በሃምቡርግ እስር ቤት ይገኛል ተብሏል። ተከሳሹ እና ጠበቃው የቀረበውን ወንጀል ሙሉ በሙሉ ያስተባበሉ ሲሆን፣ የዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በበኩላቸው ስለ ክሱ ዝርዝር መረጃ በይፋ እንዳልደረሳቸውና የሁለቱ ሀገራት የሚመለከታቸው አካላት ተነጋግረው ዝርዝሩን ካወቁ በኋላ ምላሽ እንደሚሰጡ አስታውቀዋል። ይህ የጀርመን አቃቤ ህግ ውሳኔ ጀርመን ለዩክሬን እያደረገች ያለውን ከፍተኛ ወታደራዊ ድጋፍ ተከትሎ በሁለቱ ሀገራት ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ላይ ጥንቃቄ የሚሻ መናጋት ሊፈጥር እንደሚችል እየተነገረ ይገኛል። ይህን ተከትሎ፣ የነዳጅ እጦቱ ግርፋት የደረሰባቸው የአውሮፓ ሀገራት ዜጎች ለዩክሬን የሚደረገውን ድጋፍ በመንቀፍ መንግስታቸው ላይ ተጽዕኖ በማሳደር ኪቭ ያለባትን ችግር በራሷ እንድትፈታ የሚያደርግ እንቅሳቃሴ ሊኖር ይችላል ተብሏል። ምስል _ ከ ሮይተርስ ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

photo content

“በሕዝብ ፍቃድ ያልተመሠረተ አገዛዝ ይሸነፋል” አንዷለም አራጌ ዕውቁ ፖለቲከኛ አንዷለም አራጌ “ብዕር እና ባሩድ” የተሰኘ መጽሐፍ ባለፈው ሳምንት ለንባብ አብቅቷል። መጽሐፉ፣ የሰላማዊና የሃይል አመጻን፤ የ1966 አብዮትና የ2010 ፖለቲካ ለውጥ በበርካታ ማንጸሪያዎች ይፈትሻል። አዲስ ማለዳ፤ በወቅታዊ ዝግጅቷ፣ መጽሐፉን መነሻ በማድረግ ዘለግ ያለ ቆይታን ከፖለቲከኛው ጋር አድርጋለች። የቆይታው አስኳል መጽሐፉ ቢሆንም ቅሉ፣ ወቅታዊ ፖለቲካዊ አጀንዳዎችም በቃለምልልሱ ተዳስሰዋል። ሙሉውን ቃለምልልስ ከስር በተቀመጠው ሊንክ ያገኙታል። https://youtu.be/pGAd0me0geM

photo content

በዘይሴ ወረዳ በመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት 10 ሰዎች መሞታቸውን ኢሰመጉ ገለጸ ሐሙስ፣ ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጋሞ ዞን ዘይሴ ወረዳ በመንግሥት ታጣቂ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት የ10 ሰዎች ሕይወት ማለፉን የገለጸው የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ)፤ ድርጊቱን በአስቸኳይ እንዲቆም ጥሪ አቀረበ። ኢሰመጉ ዛሬ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳስታወቀው፤ በዘይሴ ወረዳ በሚገኙ በተለያዩ ቀበሌዎች ውስጥ ከሰኔ 11 እስከ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ድረስ በመንግሥት የታጠቁ ኃይሎች በተፈጸመ ጥቃት የ10 ሰዎች ሕይወት አልፏል። በተጨማሪም በ3 ግለሰቦች ላይ የአካል ጉዳት፣ ጾታዊ ጥቃት፣ የንብረት ዘረፋና ውድመት እንዲሁም የጅምላ እስር መፈጸሙን ድርጅቱ ከአካባቢው ካሰባሰበው መረጃ ለማረጋገጥ መቻሉን ገልጿል። ከአካባቢው በተነሱና ምላሽ ባላገኙ የማኅበረሰብ ጥያቄዎች ሳቢያ እየተባባሰ በመጣው በዚህ ጥቃት ምክንያት፣ በርካታ ነዋሪዎች ሕይወታቸውን ለማዳን ሲሉ መኖሪያ ቤታቸውን ለቀው ለመሰደድ መገደዳቸውን መግለጫው ያስረዳል። ኢሰመጉ ቀደም ሲል በየካቲት ወር 2018 ዓ.ም በተመሳሳይ መልኩ ጥሪ አቅርቦ የነበረ ቢሆንም፣ የሰብዓዊ መብት ጥሰቱ አሁንም ተጠናክሮ መቀጠሉን ገልጿል። ጉዳዩን አስመልክቶ ከአርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ አስተዳደር መረጃ ለማግኘት የተደረገው ጥረት እስካሁን ባይሳካም፣ ወደፊት ተጨማሪ ምርመራዎችን በማድረግና የወረዳውን ምላሽ በማካተት ዝርዝር መረጃዎችን ይፋ የሚያደርግ መሆኑን  አስታውቋል። በመጨረሻም የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ጉባኤ (ኢሰመጉ) የተለያዩ ጥሪዎችን አስተላልፏል። የደቡብ ኢትዮጵያ ክልልና የጋሞ ዞን የጸጥታ አካላት የንጹኃንን ደህንነት የመጠበቅና የሰብዓዊ መብቶችን የማክበር ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ፣ የጸጥታ አካላት በወንጀል የሚፈልጓቸውን ግለሰቦች በቁጥጥር ስር አውለው ፍትህ የማግኘት መብታቸውን እንዲያከብሩ፣ በክልሉ የሚነሱ ጥያቄዎች ሕግን በተከተለና ማኅበረሰቡን ባሳተፈ ሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ፣ በዘይሴ ማኅበረሰብ ላይ እየተፈጸመ ያለው የሰብዓዊ መብት ጥሰት በአስቸኳይ እንዲቆም ተገቢው ትኩረት ተሰጥቶ፣ በአካባቢው በደረሱት ጥሰቶች ላይ አፋጣኝ ማጣራት ተደርጎ ጥፋተኞች ለሕግ እንዲቀረቡ አበክሮ ጠይቋል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

photo content

የአዲስ አበባ እና  ድሬዳዋ አጀንዳነት ከመንግስት መዋቅር ከሚለው ወጥተው ራሳቸውን የቻሉ አጀንዳ መሆናቸው እንዲሁም  ሙስና አጀንዳ ሁኖ መቅረቡ ጥያቄ ተነሳበት ሐሙስ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የአዲስ አበባ እና የድሬድዋ ጉዳይ ራሱን ችሎ አጀንዳ ከመሆን የመንግስት አወቀቀር በሚለው አጀንዳ ስር  መካተት ነበረባቸው የተባለ ሲሆን ሙስናን ደግሞ ሁሉም የሚጸየፈው እና በመኖሩ የሚስማማ ስለሌለ በምን አግባብ እና ሁኔታ አጀንዳ ሆነ ቀረብ ሲሉ የምክክር ጉባኤ ላይ ሃሳብ የሚያቀርቡ ምሁራን ምክክር ኮሚሽኑን ጠየቁ። ሀገራዊ የምክክር ኮሚሽን በምክክር ጉባኤው ላይ ሙያዊ ማብራሪያ ላይ የሚያቀርቡ ምሁራን ሚናን በተመለከተ በዛሬው ዕለት በስካይላይት ሆቴል በተደረገው የጋራ ውይይት የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ከተሞች አስተዳደራዊ መዋቅር፣ የሙስናና መልካም አስተዳደር አጀንዳ እንዲሁም የወጣቱ ትውልድ ሚና  ተዳሰውበታዋል። በመድረኩ ላይ የተሳተፉ አንድ ባለሙያ በአጀንዳ ቁጥር ሶስት ላይ የተቀመጠው ላይ ትችት ሰንዝረዋል። ይህም ትችት የተነሳው የአዲስ አበባ እና የድሬዳዋ ጉዳይ ራሱን ችሎ በአጀንዳነት መቅረቡን ተከትሎ ነው። እንደ ባለሙያው ገለጻ የከተሞቹ ጉዳይ በሀገሪቱ “የመንግስት መዋቅር ውስጥ ተካትቶ ሊታይ የሚገባው እንጂ እንዴት በተናጠልና ራሱን ችሎ ገለልተኛ አጀንዳ ሊሆን እንደቻለ” ግልጽ እንዳልሆነላቸው ጠንከር ያለ ጥያቄ አንስተዋል። ባለሙያው አክለውም ይህንን ያሉበትን ምክንያት ሲያስረዱ የመንግስት መዋቅር በዋናነት እንደዚህ ዓይነት ጉዳዮችን የሚመለከት በመሆኑ ነው ብለዋል። የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን በበኩሉ የአዲስ አበባ እና ድሬድዋ ጉዳይ ራሱን ችሎ  በአጀንዳነት እንዲቀርብ ብዙ ጊዜ የሚነሱ እና ግፊት የተደረገባቸው ከሆኑ ራሳቸውን ችለው እንዲቆሙ ይደረጋል ሲል ምላሽ ሰጥቷል። ኮሚሽኑ አክሎም አሳማኝ ሃሳብ ያለው እና በአጀንዳ መቅረጹ ሂደት ውስጥ ብዙ ጊዜ ከተወያየበት በኋላ በአጀንዳነት እንደቀረፀው አስታውቋል። ባለሙያው፣ ሙስና ለምን በአጀንዳነት ተካተተ ባይ ናቸው።  የሙስና እና የመልካም አስተዳደር ጉዳይ ላይ የውይይቱ ፍሬ ነገር ምን ሊሆን እንደሚችል ብዥታ እንደተፈጠረባቸው ጠቁመዋል። “የትኛውም የሀገራችን ክፍል ቢመጣ ሙስናን ማንም አይፈልግም፤ ይጸየፋል” ያሉት ባለሙያው እንደ ሀገራዊ መዋቅር ያሉ አጀንዳዎች “ይሄ ይሁን ወይስ ያኛው” ተብሎ አማራጭ የሚቀረብላቸው ሲሆን ሙስና ግን በተቃራኒው የሚቆምለት ሌላ ወገን የሌለው በመሆኑ በውይይቱ ላይ በምን መልኩ ተደርጎ ሊቀርብ እንደታሰበ ማብራሪያ ጠይቀዋል። ሙስና የህግ ማሻሻያ ሁሉ የተጠየቀበት ጉዳይ ነው ያለው ኮሚሽኑ አጀንዳ ሁኖ መቅረቡ አዋጭ ነው ሲል ሞግቷል።  እንዲሁም አሁን ላይ ሙስናን የሚመለከቱ ህግጋት ተፈጻሚነታቸው አነስተኛ እና ያለው ህግም በቂ ባለመሆኑ በአጀንዳነት እንዲቀረጽ ምክንያት ሁኗል ብሏል። ሐምሌ ስምንት በአዲስ ኮንቬንሽን ማዕከል የሚካሄደው የምክክር ጉባኤ 4000 የሚሆኑ ተሳታፊዎች እንደሚገኙበት ይጠበቃል። ይህ በእንዲህ እንዳለ የምክክሩን ሂደት ወቅታዊ እና ሁለንተናዊ ይዘት መዳሰስ ያስፈልጋል ያሉት ሌላው ባለሙያ የማህበራዊ  እና የወጣቶች ጉዳይ አንስተዋል። አሁን ያለው የኢትዮጵያ ወጣት ትውልድ በጦርነትና በግጭት አውድ ውስጥ ያደገ መሆኑን በማስታወስ ይህንን የጦርነት ባህል ወደ ሰላማዊ የውይይት ባህል ለመቀየር ትልቅ የአዕምሮ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ገልጸዋል። አያይዘውም፣ ወጣቱ ትውልድ የችግሮቹና የጉዳቶቹ ቀዳሚ ገፈት ቀማሽ ቢሆንም በጉባኤው ተሳታፊዎች  ዘንድ ያለው ውክልና ግን አነስተኛ ሊሆን ይችላል የሚል ስጋት እንደገባቸው አመልክተዋል። በመሆኑም በምክክሩ ሂደት ውስጥ ወጣቶች የራሳቸውን ተጨባጭ እውነታዎች በራሳቸው አንደበት ማስረዳት እንዲችሉና ውይይቱ በተወሰኑ አካላት ብቻ የበላይነት እንዳይያዝ የወጣቱ ትርጉም ያለው ተሳትፎ ሊረጋገጥ እንደሚገባ  አሳስበዋል። ባለሙያው ይህንን ሊሉ የቻሉት በምክክሩ ላይ የሚሳተፉ ግለሰቦች ወጣቶችን ያላካተተ እንዳይሆን በመስጋት ነው። በዚህ ጉዳይ ላይ ሃሳቡን የሰጠው ምክክሩ ወጣቶችን እና ሁሉንም ማህበረሰብ በአካታችነት ያቀፈ ነው ሲል ለባለሙያዎቹ አረጋግጧል። ይህ የውይይት መድረክ በከተሞች መዋቅርና በሙስና አቀራረብ ላይ ያሉ መሰረታዊ የሃሳብ ማዕቀፍ ከመፍታት ባለፈ የወደፊቷን ሀገር የሚረከበው ወጣት ትውልድ በሰላም ግንባታው ሂደት ውስጥ የበኩሉን ሚና እንዲጫወት ምቹ ሁኔታን ለመፍጠር ያለመ እንደሆነ ተገልጿል። ወጣቱ የሁሉም ገፈት ቀማሽ ሁኖ በቀዳሚነት የሚገኝ በመሆኑ በሰፊው ሊሳተፍ ይገባል ተብሏል። ኮሚሽኑ ለሃሳብ አቅራቢ ምሁራን፣ ምክክር ጉባኤው ላይ የሚሳተፉ ሰዎች ስሜታዊ ሊሆኑ የሚችሉበት ሁኔታ ሰፊ ስለሆነ ሌላ ችግር እንዳይፈጠር ሙያዊ የሆነ ሃሳብ በማቅረብ የማረጋጋት ሃላፊነት አለባቸው ብሏል። ምስል_ ከ ኮሚሽኑ የተወሰደ ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

photo content

ሩሲያ በኪቭ ላይ በፈጸመችው የሰው አልባ የጦር አውሮፕላን እና የሚሳኤል ጥቃት ቢያንስ 13 ሰዎች ተገደሉ ሐሙስ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) ሩሲያ ሐሙስ ማለዳ በዩክሬን መዲና ኪቭ ላይ በሰነዘረችው ከፍተኛ የድሮን እና የሚሳኤል ጥቃት፤ በትንሹ 13 ሰዎች ሲገደሉ በደርዘን የሚቆጠሩ ደግሞ መቁሰላቸውን የአካባቢው ባለሥልጣናት አስታወቁ። በዋና ከተማዋ በተለያዩ አካባቢዎች ቃጠሎዎች ይስተዋሉ የነበረ ሲሆን፣ የሚሳኤል ጥቃቶች ወይም የተመቱ ሚሳኤሎች ስብርባሪዎች በበርካታ ስፍራዎች በሚገኙ የመኖሪያ ሕንጻዎች እና በማዕከላዊ የኪቭ አደባባይ ላይ በሚገኝ አንድ ሆቴል ላይ አርፈዋል። እንደ ዘ ጋርዲያን ዘገባ፣ የአካባቢው የአደጋ ጊዜ አገልግሎት 86 ሰዎች መቁሰላቸውንና ከእነዚህ ውስጥ 70 የሚሆኑት ሆስፒታል ህክምናቸውን እየተከታተሉ መሆናቸውን የገለጸ ሲሆን፣ በዚህም ምክንያት የሟቾች ቁጥር ከ13ም በላይ ሊያሻቅብ እንደሚችል ተነግሯል። የተሰማሩት ድሮኖች እንዲሁም የክሩዝ እና ባሊስቲክ ሚሳኤሎች ወደ ዋና ከተማዋ ሲተሙና የዩክሬን የአየር መከላከያ ሥርዓት ሊመታቸው ሲሞክር የነበረው ከፍተኛ ፍንዳታ መዲናዋን ለሰዓታት አናውጧታል። የኪቭ ከንቲባ ቪታሊ ክሊትስኮ በቴሌግራም ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት፣ በአንድ አካባቢ የሚገኝ የመኖሪያ ሕንጻ በቀጥታ በመመታቱ ከአንደኛ እስከ ስድስተኛ ወለል(ፎቅ) ያለው አካል ሙሉ በሙሉ ተደርምሷል። በሌላ ስፍራ ደግሞ አፓርታማው በከፊል ከተደረመሰ በኋላ ሰዎች ከፍርስራሹ ስር ወጥተዋል። ሩሲያ በዩክሬን ዋና ከተማ ላይ የሚሳኤል እና የድሮን የተቀናጀ ጥቃቶችን በየጊዜው የምትሰነዝር ሲሆን፣ ሌላ ተመሳሳይ ከፍተኛ ጥቃት ሊሰነዘር እንደሚችል ባለፉት ቀናት ግምቶች ነበሩ። ፕሬዝዳንት ቮሎዲሚር ዘለንስኪ በደብሊን ባደረጉት ጉብኝት ወቅት፣ ረቡዕ ዕለት ለዩክሬናውያን በሰጡት ማስጠንቀቂያ ጥቃቱ በዚያኑ ምሽት ሊከሰት እንደሚችል ገልጸው ነበር። “ሕዝባችን ሁሉ ልዩ ጥንቃቄ እንዲያደርግ፣ ራሳቸውንና ልጆቻቸውን እንዲጠብቁ እና የመጠለያ ቦታዎችን እንዲጠቀሙ እጠይቃለሁ፤ ይህ በጣም ወሳኝ ነው” ብለው ነበር። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

photo content

የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ)፤ ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር ከተቋሙ አባልነት መውጣታቸው ፍትህን ያዳክማል ሲል ገለጸ ሐሙስ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) ሥራ አስፈጻሚ ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር በቅርቡ ከተቋሙ አባልነት ለመውጣት ያደረጉትን እንቅስቃሴ አስመልክቶ ያለውን ስጋት አስታወቀ። ድርጊቱ ዓለም አቀፋዊ ፍትህን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ያዳክማል ሲልም አክሏል። በወታደራዊ አገዛዝ የሚተዳደሩት እነዚህ የምዕራብ አፍሪካ አገራት፣ እ.አ.አ በመስከረም 2025 ላይ ግለሰቦችን በጦርነትና በሰብአዊነት ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች የሚከስሰውን ይህንን ፍርድ ቤት ጥለው ለመውጣት መወሰናቸውን ማስታወቃቸው ይታወሳል። ሦስቱ አገራት ባለፈው ዓመት ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ መቀመጫውን በሄግ ያደረገው ፍርድ ቤት “በኢምፔሪያሊስቶች እጅ የሚገኝ የኒዮ ሊበራል ጭቆና መሣሪያ ነው” ሲሉ ወንጅለውታል። የፍርድ ቤቱን መሥራች አገራት የሚወክለው የአይ.ሲ.ሲ አባል አገራት ጉባኤ፣ “ጉዳዩን በከፍተኛ ስጋት ተመልክተነዋል” ማለቱንና አገራቱ ከአባልነት ለመውጣት በመወሰናቸው ማዘኑን ገልጿል። መግለጫው አክሎም፣ ከአይ.ሲ.ሲ የሚወጡ አገራት “የጋራ የፍትህ ጥረትን የማዳከም እና ወንጀለኞች ያለቅጣት እንዲያመልጡ የማድረግ አደጋ ያመጣሉ” ብሏል። ይህ ተቋም እንደ መጨረሻ አማራጭ ፍርድ ቤት ሆኖ የሚሠራ ሲሆን፣ አንድ አገር ከባድ የሆኑ ዓለም አቀፍ ወንጀሎችን የፈጸሙ ግለሰቦችን ለፍርድ ማቅረብ ሳትችል ወይም ፈቃደኛ ሳትሆን በሚቀርብበት ወቅት ጣልቃ በመግባት ክስ ይመሰርታል። በአጠቃላይ 125 አገራት የአይ.ሲ.ሲ አባል ቢሆኑም፣ ቻይና፣ ሕንድ፣ እስራኤል፣ ሩሲያ እና አሜሪካን ጨምሮ በርካታ የዓለም ኃያላን አገራት ተቋሙን አልተቀላቀሉም። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

photo content

የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ)፤ ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር ከተቋሙ አባልነት መውጣታቸው ፍትህን ያዳክማል ሲል ገለጸ ሐሙስ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) የዓለም አቀፉ የወንጀል ፍርድ ቤት (አይ.ሲ.ሲ) ሥራ አስፈጻሚ ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒጀር በቅርቡ ከተቋሙ አባልነት ለመውጣት ያደረጉትን እንቅስቃሴ አስመልክቶ ያለውን ስጋት አስታወቀ። ድርጊቱ ዓለም አቀፋዊ ፍትህን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ያዳክማል ሲልም አክሏል። በወታደራዊ አገዛዝ የሚተዳደሩት እነዚህ የምዕራብ አፍሪካ አገራት፣ እ.አ.አ በመስከረም 2025 ላይ ግለሰቦችን በጦርነትና በሰብአዊነት ላይ በሚፈጸሙ ወንጀሎች የሚከስሰውን ይህንን ፍርድ ቤት ጥለው ለመውጣት መወሰናቸውን ማስታወቃቸው ይታወሳል። ሦስቱ አገራት ባለፈው ዓመት ባወጡት የጋራ መግለጫ፣ መቀመጫውን በሄግ ያደረገው ፍርድ ቤት “በኢምፔሪያሊስቶች እጅ የሚገኝ የኒዮ ሊበራል ጭቆና መሣሪያ ነው” ሲሉ ወንጅለውታል። የፍርድ ቤቱን መሥራች አገራት የሚወክለው የአይ.ሲ.ሲ አባል አገራት ጉባኤ፣ “ጉዳዩን በከፍተኛ ስጋት ተመልክተነዋል” ማለቱንና አገራቱ ከአባልነት ለመውጣት በመወሰናቸው ማዘኑን ገልጿል። መግለጫው አክሎም፣ ከአይ.ሲ.ሲ የሚወጡ አገራት “የጋራ የፍትህ ጥረትን የማዳከም እና ወንጀለኞች ያለቅጣት እንዲያመልጡ የማድረግ አደጋ ያመጣሉ” ብሏል። ይህ ተቋም እንደ መጨረሻ አማራጭ ፍርድ ቤት ሆኖ የሚሠራ ሲሆን፣ አንድ አገር ከባድ የሆኑ ዓለም አቀፍ ወንጀሎችን የፈጸሙ ግለሰቦችን ለፍርድ ማቅረብ ሳትችል ወይም ፈቃደኛ ሳትሆን በሚቀርብበት ወቅት ጣልቃ በመግባት ክስ ይመሰርታል። በአጠቃላይ 125 አገራት የአይ.ሲ.ሲ አባል ቢሆኑም፣ ቻይና፣ ሕንድ፣ እስራኤል፣ ሩሲያ እና አሜሪካን ጨምሮ በርካታ የዓለም ኃያላን አገራት ተቋሙን አልተቀላቀሉም። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

photo content

የምርጫውን ውጤት ተከትሎ ሁለት የፖለቲካ ፓርቲዎች ለቦርዱ አቤቱታ ማስገባታቸውን ለአዲስ ማለዳ ገለጹ ሐሙስ ፣ ሰኔ 25 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ) 7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ መጠናቀቁንና ውጤቱ ይፋ መደረጉን ተከትሎ፣ የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ (ነእፓ) እና የመላው የሲዳማ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ (መሲህዴአፓ) በምርጫው አጠቃላይ ሂደትና በምርጫ ቦርድ አሰራር ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ቅሬታ ለአዲስ ማለዳ ገለጹ። ፓርቲዎቹ ምርጫው ነጻና ፍትሃዊ እንዳልነበር በመጥቀስ፣ ቦርዱ ያቀረቡትን አቤቱታ በተገቢው መንገድ አላስተናገደም ሲሉ ወቅሰዋል። የነጻነትና እኩልነት ፓርቲ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የምርጫ አስተባባሪ ሲሳይ ነጋሽ ለአዲስ ማለዳ እንደተናገሩት፣ ምርጫው እንደሚወራው ነጻ፣ ፍትሃዊና ዴሞክራሲያዊ አልነበረም። “ገዢው ፓርቲ የሚፈልገውን ቦታ ለሚፈልገው ፓርቲ አሳልፎ ስለሰጠ፣ ፓርቲያችን ሊያገኝ የሚገባውን ትክክለኛ ውጤት አላገኘም” ብለዋል። ይሁን እንጂ በምርጫው ሂደት ያጋጠሙትን ጥሰቶች በመገምገም ለቀጣይ ትግል ትልቅ ግንዛቤና ልምድ የተጨበጠበት በመሆኑ ሂደቱን እንደ አንድ ስኬት እንደሚቆጥሩት ገልጸዋል። “ፓርቲው ያለውን ቅሬታ በወቅቱ ቢያቀርብም፣ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ከገዢው ፓርቲ ጉያ ባለመውጣቱ ምክንያት ነገሮች ተሸፋፍነው እንዲቀሩ ተደርጓል” ሲሉ ወንጅለዋል። በምርጫው ወቅት ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር በጥምረት ለመሥራት የተደረገው ጥረት ባይሳካም፣ በቀጣይ ፓርቲው ባዘጋጀው ፕሮግራም መሠረት ውይይት በማድረግ አብሮ ለመሥራት ጥሪ ማቅረባቸውን ጠቁመው፣ ነገር ግን አብሮ መሥራት እንደሚወራው ቀላል እንዳልሆነ አክለዋል። ፓርቲው በአጠቃላይ 35 ወንበሮችን ማሸነፉን ተከትሎ በቀጣይ ከተመሠረተው መንግሥት ጋር ስለሚኖረው የሥራ ግንኙነት ሲያብራሩም፣ “በብሔራዊ ጥቅም ላይ አንደራደርም፤ ገዢው ፓርቲ የፖለቲካ ምህዳሩን እንዲያሰፋ እንታገላለን። ያሉ ችግሮች ተቀርፈው ሁሉም የፖለቲካ ፓርቲዎች እኩል መንቀሳቀስ የሚችሉበት ሜዳ እንዲፈጠር እንሠራለን እንጂ ከመንግሥት ጋር አናጨበጭብም” ብለዋል። ሌላኛው ለአዲስ ማለዳ የድህረ ምርጫ አስተያየታቸውን የሰጡት የመላው የሲዳማ ሕዝብ ዴሞክራሲያዊ አንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ተስፋማርያም ጉጃ በበኩላቸው፣ ፓርቲያቸው በምርጫው ወቅት የተፈጸሙ ጥሰቶችን አስመልክቶ በ11 የምርጫ ጣቢያዎች ላይ ቅሬታ ቢያቀርብም ምላሽ ያገኘው በሁለት ጣቢያዎች ላይ ብቻ መሆኑን ተናግረዋል። ፓርቲው ለመጀመሪያ ጊዜ በምርጫው መሳተፉን የገለጹት ሊቀመንበሩ፣ ያገኙት አንድ ወንበር የሲዳማ ሕዝብ ለፓርቲው የሰጠውን እውነተኛ ድምፅና ፍላጎት እንደማያንጸባርቅ ገልጸዋል። አክለውም ምርጫው “አሳታፊ” ለማለት የሚጎድሉት በርካታ ነገሮች እንዳሉ ጠቁመው፣ “ተአማኒ ነበር” ብሎ ማሰብ ግን በፍጹም የማይታሰብ ነው ሲሉ ሂደቱን ነቅፈዋል። ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦ YouTube ➲ t.ly/vSgS Telegram ➲ t.ly/SOXU Facebook ➲ t.ly/flx8 Twitter ➲ t.ly/mxA

photo content