213
Subscribers
No data24 hours
No data7 days
No data30 days
Posts Archive
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 4/2016 ዓ.ም ይጀምራል፡፡
(ቀን ጥር 30/2016 ዓ.ም)
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሁለተኛ ወሰነ ትምህርት የካቲት 4/2016 ዓ.ም የሚጀምር መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያዎቹን ይጫኑ!
What Sapp: - https://whatsapp.com/channel/0029VaHFiBpA2pLF0lLslK2D
You Tube: https://www.youtube.com/@addisababaeducationbureau9728
TikTok፡- tiktok.com/@aaeducationbureau
Telegram ፡ https://t.me/wwwAddisAbabaeducationbureau
Twitter ፡ https://twitter.com/aacaebc
Face book: https://www.facebook.com/aacityeducationcommunication
Blog: - http://www.aacaebc.wordpress.com/
Website: - aaceb.gov.et
Email;- aacaebc@gmail.com
Instagram: - https://www.instagram.com/aacaeb/
Repost from Yeka Education
#ሞክሼ ፊደላት
☆ ሞክሼ ፊደላት የሚባሉት አንድ አይነት ድምጽ ያላቸው ነገር ግን በቅርጽ እና በስራቸው የተለያዩ ፊደላት የሆኑ ናቸው።
☆ በድሮ ጊዜ ግን አባቶቻችን ሀን ከ ሐ ፣ ጸን ከፀ ፊደሎችን በድምፅ አወጣጥ ይለዩአቸው ነበር።
☆ እኝህ ፊደላት በቁጥር ፱ (9)ሲሆኑ ሀ ፣ ሐ ፣ ኀ ፣ ሠ ፣ ሰ ፣ አ ፣ ዐ ፣ ጸ ፣ ፀ ናቸው።
☆ ሀ➡ሃሌታው "ሀ" ይባላል።
○ ሃሌ ሉያ ብለን ስጽፍ የምንጠቀመው ይህን ፊደል ስለሆነ ሃሌታው "ሀ" ተብሏል።
☆ ሐ➡ሐመሩ "ሐ" ይባላል።
○ ሐመር ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው በዚህ ፊደል ስለሆነ ነው።
☆ ኀ➡ብዙኀን "ኀ" ይባላል
○ ብዙህ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ስለሆነ ነው።
☆ አ➡አልፋው "አ" ይባላል፡፡
○ አልፋ ኦሜጋ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀምበት ስለሆነ ነው።
☆ ዐ➡ዓይኑ "ዐ" ይባላል።
○ ዓይኑ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀምበት ስለሆነ ነው።
☆ ሠ➡ንጉሡ "ሠ" ይባላል።
○ ንጉሥ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይሄን ፊደል ስለሆ ነው
☆ ሰ➡እሳቱ "ሰ" ይባላል።
○ እሳት ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ፊደል ነው።
☆ ጸ➡ ጸሎቱ "ጸ" ይባላል።
○ ጸሎት ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይሄን ፊደል ስለሆነ ነው።
☆ ፀ➡ፀሐዩ "ፀ" ይባላል።
○ ፀሐይ ብለን ስንጽፍ የምንጠቀመው ይህን ፊደል ነው።
እነዚህ ሞክሼ ፊደላት አንዱ በአንዱ ቦታ መግባት የለበትም ምክንያቱም የትርጉም ለውጥ ያመጣሉ።
ለምሳሌ:-
✍ ሠረቀ = ወጣ
ሰረቀ =ሰረቀ
✍ አመት= አገልጋይ
ዓመት= ዘመን
✍ ሰዓለ= ስዕል ሳለ
ሰአለ= ለመነ
✍ መሀረ= አስተማረ
መሐረ= ይቅር አለ
✍ ኀለየ= አመሰገነ
ሐለየ= አሰበ
✅ቻናላችን
👇👇👇
https://t.me/dam76
via👉👉ewentesfa