1 790
Subscribers
-124 hours
+127 days
+4430 days
Posts Archive
ADRA Ethiopia ፕሮጀክት ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር ላለፉት አመታት ሲተገብር የቆየውን የVQEP/Green Energy TVET Project Phase II ፕሮጀክት አጠናቆ የማጠቃለያ መድረክ አካሄደ::
ፕሮጀክቱ ባለፉት አመታት በአስተዳደራችን ለመጀመርያ ጊዜ ከ130 በላይ ወጣቶችን አዲስና ተፈላጊ በሆነ የሙያ ዘርፍ(Solar PV Installation & Maintenance) ላይ አሰልጥኖ ወደ ስራ እንዲገቡ ያደረገ ፕሮጀክት መሆኑን ያስታወሱት የስራና ክህሎት ቢሮ ሀላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ሲሆኑ ፕሮጀክቱ በስልጥናው ዘርፍ ለፈጠረው አቅም ፣በከተማና በገጠር ላከናወነው የስራ እድል ፈጠራ እንዲሁም የSolar ኢነርጂን ተደራሽ በማድረግ የGreen TVTን በተግባር እንድናሳይ ላከናወናቸው ተግባራት በቢሮውና በአስተዳደሩ ስም ምስጋና እቅርበዋል::
ADRA Ethiopia በሀገሪቱ ብዙ ቦታዎች ላይ ይንቀሳቀስ የነበረ ቢሆንም ድሬዳዋን ተደራሽ ያደረገው በዚህ ፕሮጀክት መሆኑን ያስተወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ ከዚህ በፊት ያልነበሩ እንቅስቃሴዎችና ብዙ በረከቶችንም ወደ ተቋማች ይዞልን የመጣ ፕሮጀክት ነው ያሉ ሲሆን በGreen Energy ላይ ግንባር ቀደም ሆነን እንድንሰራ ፈር የቀደደልን ልዩ ፕሮጀክት ነውም ብለዋል::
የኮሌጁ ዲን አክለውም ፕሮጀክቱ ያስቀመጠውን ግብ በመምታት ረገድ ጥሩ የሚባል አፈፃፀም እንደነበረው አስታውሰው ፕሮጀክት የራሱ የጊዜ ገደብ ያለው በመሆኑ ዛሬ ማጠቃለያ ብናደርግም በቀጣይ በጋራ የምንሰራቸው በርካታ ስራዎች በመኖራቸው እንደ ተቋም ደስተኞች ነንም ብለዋል::
የADRA Ethiopia ፕሮጀክት በ120 ሀገሮች ውስጥ ቢሮ ከፍቶ የሚቅሳቀስ ግብረ ሰናይ ድርጅት እንደሆነ ያስታወሱት የፕሮጀክቱ ዋና ዳይሬክቶር ዶ/ር ዘሪሁን አዋኖ በበኩላቸው ፕሮጀክቱ ላለፉት 43 አመታትም በተለያዩ የሀገሪቷ ክፍሎች ላይ ሰው ተኮር ስራዎችን እየሰራ የሚገኝ ፕሮጀክት መሆኑን ገልፀው በውቢቷ ድሬዳዋ በነበረው የፕሮጀክቱ ሂደትና የተመዘገበው ውጤት እጅግ የሚያኮራና የአስተዳደሩንም ሆነ የኮሌጁን አመራሮች ቁርጠኝነት የተመለከቱበት እንደነበርም ገልፀዋል::
በማጠቃለያ መድረክ ላይ የADRA Ethiopia ፕሮጀክት ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ያከናወናቸውን ቁልፍ ተግባራትና ያስመዘገባቸው አመርቂ ውጤቶች በፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ሀብታሙ በየነ አማካኝነት ለባለድርሻ አካላት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን በተጨማሪም በፕሮጀክቱ ሂደት ላይ በኮሌጁ ጥናት በማድረግ የመጣውን ለውጥ የሚገመግም ሰነድም በመድረኩ ቀርቦ ገለፃ ተደርጎበታል::
ADRA Ethiopia ከጀርመን የልማት ትብብር ተቋም(BMZ) እና በADRA Germany በተገኘ የገንዘብ ድጋፍ ከጥቅምት 2015 ዓ.ም ጀምሮ በድሬዳዋ አስተዳደር ከኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ እና ከሌሎች ቁልፍ ባለ ድርሻ አካላት በመተባበር ሲተገበር የነበረው የVQEP/Green Energy TVET Project Phase II ፕሮጀክት በርካታ ስኬቶችን በማስመዝገብ በዛሬ እለት ፍፃሜውን አድርጏል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ግንቦት 20/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+1
እንኳን አደረሳችሁ!!
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል አድሃ(አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የፍቅር፣ የደስታ እና የመተሳሰብ እንዲሆንላችሁ ከወዲሁ እመኛለሁ::
አቶ ታደለ አሰፋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን
#ኢድ_ሙባረክ!!
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የአምራች ኢንዱስትሪውን ፍላጎት ለመለየት የተዘጋጀ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ለባለድርሻ አካላት ቀርቦ ውይይት ተካሄደ::
አምራች ኢንዱስትሪው የሚጠይቀውን ብቁና የሰለጠን የሰው ሀይል በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ አሰልጥኖ ለማቅረብ ታሳቢ ያደረገ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት በተቋም ደረጃ የተጠና ሲሆን ወጣቶች ጊዜው የሚጠይቀውን የአጫጭር ስልጠና ምርጫቸው ከማድረጋቸው ጋር ተያይዞ የአምራች ኢንዱስትሪውን የሙያ ፍላጎት መሰረት ያደረገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም ለመቅረፅ የጥናት ቡድኑ ከኢንዱስትሪ አድቫይዘሪግ ቦርድ አባላት ጋር በቅንጅት መስራቱም ተገልፇል::
በEASE ፕሮጀክት ትግበራ ትኩረት ተደርጎባቸው ከሚከናወኑ ተግባራት መካከል ለኢንዱስትሪው ግብዓት የሚሆኑ ብቁ ባለሙያዎችን የማፍራቱን ሂደትን መደገፍ ዋነኛው መሆኑ የተገለፅ ሲሆን የፕሮጀክቱ ባለሙያዎች ከትምህርትና ስልጠና ዘርፉ ጋር በመቀናጀት ባዘጋጁት የኢንዱስትሪውን ፍላጎት መሰረት ያደርገ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራም ላይ አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል ሲያደርግም ቆይቷል::
በፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ መሰረት ውጤታማነታቸው ታምኖበት የተለዩ የአጫጭር ስልጠና ፕሮግራሞችን የጥናት ቡድኑ በዝርዝር ያቀረበ ሲሆን በተጨማሪም ለስልጠና ፕሮግራሞቹ እየተዘጋጁ ሚገኙት ማሰልጠኛ ሞጁሎች ላይም ለባለድርሻ አካላት ገለፃ አድርገዋል::
በመድረኩ በቀረቡት አጠቃላይ ሰነዶች መነሻነት ውይይት የተካሄደ ሲሆን ተሳታፊዎች በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የበቃ የሰው ሀይል ከማሟላት አኳያ በጥናቱ ያልተዳሰሱና ሊካተቱ ይገባል ያሏቸውን ጉዳዮች ለጥናት ቡድኑ አመላክተዋል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ግንቦት 18/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
+9
ለኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን በInnovative Pedagogy ላይ ያተኮረ ስልጠና እየተሰጠ ይገኛል::
ለኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን የተሰጠ የሚገኘው የInnovative Pedagogy ስልጠና በፌደራል ስራና ክህሎት ሚኒስቴር አዘጋጅነት ከፌደራል TVET ኢንስቲትዩት በመጡ የዘርፉ ባለሞያዎች እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን የስልጠናው ዋና ዓላማም የተለመደውን የማሰልጠኛ ስነ-ዘዴ ለማሻሻልና ጊዜው የደረሰበትን ዲጂታል ቴክኖሎጂን በመጠቀም ትምህርትና ስልጠናውን ለማዘመን ያለም ስልጠና እንደሆነም ተገልፇል::
ይህ በኮሌጁ ለ5 ቀናት የሚቆየው ስልጠናም ባለፉት 15 ቀናት አሰልጣኝ መምህራኑ በOnline ሲከታተሉት የነበረውን የ Innovative Pedagogy ስልጠና በተግባር የሚሰለጥኑበት እንደሆነው ተመላክቷል::
ስልጠናው በሀገሪቱ በሚገኙና የEASE ፕሮጀክት በሚተገበባቸው 24 ፖሊቴክኒኮች ላይ ለሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን አየተሰጠ እንደሚገኝም ተገልፇል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ግንቦት 11/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
ሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድርን አስመልክቶ በኮሌጁ ምልከታ ተካሄደ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በካይዘን ፅንሰ-ሃሳብ መነሻነት እያከናወናቸው የሚገኙ ዘርፈ ብዙ ተግባራትና ወቅታዊ አፈፃፀም ላይ ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በዛሬው እለት ግምገማ ተካሂዷል::
የሀገር አቀፍ የካይዘን ውድድር አካል በሆነውና ከፌደራል በመጡ ባለሙያዎች በተካሄደው ምዘና በኮሌጁ የስራ ቦታን ምቹ ከማድረግ ፤ ብክነትን ከመቀነስ፤ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና ፍጥነትን ከማሻሻል አኳያ በተቀመጡ መመዘኛዎች የተከናወኑ ተግባራትንም ገምግሟል::
የምልከታ ቡድኑ በኮሌጁ የካይዘን ትግበራ አጠቃላይ የአፈፃፀም ሪፖርትን የተመለከት ሲሆን ከ8ቱ የውጤት አመላካች አኳያ የተገኙ ውጤቶችን በሪፖርቱ ተመልክተዋል::
በማስቀጠል ቡድኑ በተቋሙ የሚገኙ የስራ ክፍሎችና የስልጠና ወርክሾፖች ላይ የተከናወኑ የካይዘን ትግበራዎችን ከመመልከት በተጨማሪ የካይዘን ትግበራው ውጤታማነትና የተገኘውን ለውጥ የሚያመላክቱ ሰነዶችን በዝርዝር የገመገመ ሲሆን በኮሌጁ በትግበራ ወቅት የተገኙ ምርጥ ተሞክሮችንም መመልከት ችሏል::
"ዛሬን እናሻሽል፤ ብክነትን እንቀንስ፤ ጥራትና ፍጥነትን እንጨምር፤ ነገን እንገንባ"!!
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሚያዚያ 30/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) እና የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ (Civil Servant Data Verification) ምንነትና አስፈላጊነት
========================
ኢትዮጵያ የመንግሥት ሠራተኞችን መረጃ በማዕከላዊ ዲጂታል ሥርዓት ለማስተዳደር ያላትን ፍላጎት ለማሳካት እና ቀደም ሲል የነበረውን ችግር በዘላቂነት መቅረፍ በሚያስችል መልኩ የሰው ሀይል መረጃን ወደ ዘመናዊ የሰው ኃይል አስተዳደር ስርዓት ለመሸጋገር በርካታ እርምጃዎችን እየወሰደች ነው።
እንደ ሀገር እየተወሰዱ ካሉ እርምጃዎች መካከል አንዱ የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) ተግባራዊ ማድረግ ሲሆን ይህንኑ መሰረት በማድረግም የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና የኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት በጋራ በመሆን የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ቬሪፊኬሽን ስራ ተጀምሯል።
የተቀናጀ የሲቪል ሰርቪስ መረጃ አያያዝ ስርዓትን (ICSMIS) እና የመንግስት ሰራተኞች መረጃ ቬሪቪኬሽን ስራዎች የሚከተሉትን ዋና ዋና ነጥቦች በውስጣቸው ይይዛሉ:-
1. የICSMIS ፍቺ እና አላማ
ይህ ስርዓት በመንግሥት ተቋማት ውስጥ ያሉ ሠራተኞችን ብዛት፣ የሥራ መደብ፣ ዕድሜ፣ ትምህርት ደረጃ፣ ደመወዝ እና ሌሎች መረጃዎች በማዕከላዊ መረጃ ቋት ለማስተዳደር የተዘጋጀ አገር አቀፍ የመረጃ ስብስብ ነው። በአብዛኛው የሚመራው በPublic Service and HR Directorate ወይም በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ነው።
2. የመረጃ ማረጋገጫ (Verification) አስፈላጊነት
ከዚህ ቀደም የሠራተኛ ፋይሎች በተቋማት ተበትነው ስለነበር፣ ትክክለኛ ማዕከላዊ መረጃ ቋት አልነበረም። ስለዚህ የሚከተሉትን ለማስፈጸም የሲቪል ሰርቪስ ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ አስፈለገ፦
· ትክክለኛ የመንግሥት ሠራተኞች ዳታቤዝ መፍጠር
· የደመወዝ ክፍያ ሥርዓት ማሻሻል
· የሰው ኃይል እቅድ ማውጣት
· ዘመናዊ የሰው ኃይል አስተዳደር መሠረት መጣል
· ተደጋሚ ወይም ክፍት የሥራ መደቦችን ለይቶ ለወደፊት ዕቅድ መረጃ ማግኘት
3. የፌዴራል ሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን ሚና
ኮሚሽኑ ከአንድ ክፍለ ዘመን በላይ በተለያዩ ሕጎች መሠረት የተቋማትን አደረጃጀት እና የሰው ኃይል አስተዳደር በበላይነት ሲያስተዳድር ቆይቷል። ኮሚሽኑ የሲቪል ሰርቪስን የሰው ኃይል መረጃ ሥርዓት በወጥነት እና በዘመናዊነት ተግባራዊ ለማድረግና ማዕከላዊ የመረጃ ምንጭ ሆኖ ለማገልገል ይሠራል።
4. ያጋጠመ ተግዳሮት
ኮሚሽኑ በቴክኖሎጂ የተደገፈ ዘመናዊ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥ ሥርዓት ሳዘረጋ በመቅረቱ፣ ከአገልግሎት ጥራትና ቅልጥፍና አንጻር ተፈላጊውን ደረጃ ላይ መድረስ አልቻለም።
5. መፍትሔ እና ወቅታዊ እንቅስቃሴ
አሁን ላይ ኮሚሽኑ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን ለማሻሻልና ቀልጣፋ አገልግሎት ለማስገኘት በርካታ የለውጥ ፕሮግራሞችን በመተግበር ላይ ይገኛል። እንዲሁም የመንግሥት አገልግሎት እና አስተዳደር ፖሊሲ ሰነድ አዘጋጅቶ እንዲጸድቅ ተደርጓል።
👉የኢስሚስ (ICSMIS) ትግበራ፣ ችግሮች፣ እና የመረጃ ማረጋገጫ (verification) አስፈላጊነት ዋና ዋና ነጥቦች፦
1. የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ አስፈላጊነት
የአገልግሎት አሰጣጥ ማሻሻያ ግብ ለማሳካት፣ የሲቪል ሰርቪስ የሰው ኃይል መረጃ አያያዝ ሥርዓት በወጥነት እና በዘመናዊነት እንዲተገበር ዲጂታል ቴክኖሎጂ መደገፍ አስፈለገ። ከፖሊሲው ሰባት አምዶች አንዱ ዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ መገንባት ሲሆን፣ ለዚህም የዲጂታል ሲቪል ሰርቪስ ስትራቴጂ ተዘጋጅቶ ወደ ሥራ ገብቷል።
2. የICSMIS ትግበራ ታሪክና ተግዳሮት
· ከ2004 በጀት ዓመት ጀምሮ ሥርዓቱን ማስፋፋት ተጀምሯል።
· ነገር ግን በቂ ክትትልና ተግባራዊነት ባለመኖሩ በወቅቱ ሙሉ በሙሉ ሊተገበር አልቻለም።
· ከ2006 ጀምሮ በፕሮጀክት ጽሕፈት ቤት ደረጃ ተቋቁሞ ሥራዎችን ማከናወን ጀምሯል።
3. እስካሁን ያሉ ሥሪቶች (Versions)
· 1ኛ ሥሪት (1st version ICSMIS) – በአንዳንድ የክልልና የፌዴራል ተቋማት አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
· 2ኛ ሥሪት (2nd version ICSMIS) – በአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር እየተጠቀመ ይገኛል።
· አዲሱ ሥሪት – ብሔራዊ መታወቂያ (ፋይዳ)ን መነሻ በማድረግ በአገር አቀፍ ደረጃ ለመተግበር የቅድመ-ዝግጅት ሥራ እየተከወነ ነው።
4. የመረጃ ማረጋገጫ (Verification) አስፈላጊነት
ሥርዓቱ በአገር አቀፍ ደረጃ ሙሉ በሙሉ ባለመተግበሩ የሚከተሉት ችግሮች ተፈጥረዋል፦
· የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ በአንድ ቦታ ባለመደራጀቱ ለፖሊሲ ጥናት የሚሆን ግብአት ማቅረብ አልተቻለም።
· በሲቪል ሰርቪስ ኮሚሽን እና በገንዘብ ሚኒስቴር መካከል ስለ መንግሥት ሠራተኞች ቁጥር ጉልህ ልዩነት አለ።
ለዚህም መፍትሔ እንዲሆን አገር አቀፍ የመንግሥት ሠራተኞች መረጃ ማረጋገጫ (Civil Servant Data Verification) በመካሄድ ላይ ነው። ግቡም ትክክለኛውን የሠራተኞች ቁጥርና ተጓዳኝ መረጃ በኦንላይን ወደ ICSMIS ማስገባት ነው።
Repost from Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
+2
ለሥራ ፈላጊዎች የወጣ ማስታወቂያ
በተለያዩ የውጭ አገራት የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆን ለምትፈልጉ ዜጎች የኢትዮጵያ መንግስት ከአገራቱ ጋር በፈጠረው ስምምነት እድሉ ተመቻችቷል።
በዚህም እስከ ሚያዚያ 26/2018 ዓ.ም ባሉት የሥራ ቀናት በድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ እና በሁሉም የአስተዳደሩ ወረዳ የሥራና ክህሎት ማስተባበሪያዎች በአካል በመቅረብ መመዝገብ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን።
+7
በኢንዱስትሪው ዘርፍ የሚዘጋጁ ኤክስፖዎች ለአገር በቀል አምራቾች የእርስበርስ ትስስርን መፍጠር እንደሚያችሉ ተገልፀ:
"ድሬ ታምርት፤ ኢትዮጵያ ትበልፅግ” በሚል መሪ ቃል ከሚያዝያ 15 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየው አራተኛው የ“ኢትዮጵያ ታምርት” ሀገር አቀፍ ንቅናቄና የኢንዱስትሪ ኤግዚቢሽንን የኢንዱስትሪ ሚኒስትሩ አቶ መላኩ አለበል የአስተዳደሩ ክቡር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሀርና ከአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በዛሬ እልት በደማቅ ሁኔታ ተከፍቷል።
በዛሬው እለት ጅማሮውን ባድረገው ኤግዚቢሽን እና ባዛር ላይ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅም እየተሳተፈ የሚገኝ ሲሆን በዚህም በኮሌጁ የተሰሩና የማህበረሰቡን ችግር ፈቺ የሆኑ ቴክኖሎጂዎችን እንዲሁም ኢንዱስትሪዎች ምርትና ምርታማነታቸውን በይበልጥ እንዲያሳድጉ ለማስቻል የተሰሩ ተኪ ምርቶችንም ይዞ ቀርቧል::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
ሚያዝያ 15/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው በሰላም አደረሳችሁ!!
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለብርሃነ ትንሳሣኤው አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የፍቅር፣ የደስታና የመተሳሰብ በዓል ይሆንላችሁ ዘንድ ከወዲሁ መልካም ምኞቴን እገልፃለሁ።
አቶ ታደለ አሰፋ
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን
+6
ለኢንተርፕራይዞች ስኬትና ዘላቂነት፦ የጀማሪ ኢንተርፕራይዞችን አቅም በመገንባት ውጤታማና ተወዳዳሪ ማድረግ እንደሚገባ ተገለፀ::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የቴክኖሎጂ ሽግግርና እንዱስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት በአስተዳደሩ ከተለያዩ ወረዳዎች ለተወጣጡ የኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠና ሰጠ::
ለኢንተርፕራዝ አንቀሳቃሾች የአቅም ግንባታ ስልጠናውን የሰጡት የኮሌጁ ም/ል ዲን እና የቴ/ሽ/ኢ/ኤ/አ ሀላፊ አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ የስልጠናው ዋና አላማ ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ፣ ተወዳዳሪና ዘላቂነት እንዲኖራቸው ለማስቻል የተዘጋጀ ስልጠና መሆኑን ገልፀው ጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዞች ከትንሽ ተነስተው ትልቅ ቦታ ለመድረስ ያላቸውን ራዕይ አጠናክረው በቁርጠኝነት ሊተጉ እንደሚገባም ተናግረዋል::
በእለቱ ለኢንተርፕራይዝ አንቀሳቃሾች የተሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠናው በዋናነት.....
- የንግድ ስነ-ምግባር..
- የገበያ ጥናት..
- የፋይናንስ አያያዝ..
- የቴክኖሎጂ ሽግግርና ካይዘን..
- የስራ ፈጠራና የንግድ ኢንኩቤሽን እና..
- የደንበኞች አያያዝ ላይ ያተኮረ ስልጠና በሰፊው ግንዛቤ የተሰጠበት መድረክም ነበር::
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ
መጋቢት 30/2018 ዓ.ም
ድሬዳዋ
