fa
Feedback
Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

Ethio-Italy Polytechnic College (Dire Dawa)

رفتن به کانال در Telegram
1 739
مشترکین
+224 ساعت
+17 روز
-430 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ አመራርና ሰራተኞች በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች ዘንድ የሚፆመውን የአብይ ፆም ምክንያት በማድረግ በቅድስት ስላሴ ቤተክርስትያን ተገኝተው ከቅዳሴ ለሚወጡ ምእመናን ማዕድ የማጋራት መርሃ-ግብር አካሂደዋል።

ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር ይሆንላችሁ ዘንድ ከወዲሁ መልካም ምኞቴን መግለፅ እወዳለሁ። አ
ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አልፈጥር በዓል አደረሳችሁ እያልኩ በዓሉ የሰላም፣ የጤና፣ የፍቅር ይሆንላችሁ ዘንድ ከወዲሁ መልካም ምኞቴን መግለፅ እወዳለሁ። አቶ ታደለ አሰፋ የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ዲን     #ኢድ_ሙባረክ!!

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በተቋሙ ስራ ሂደቶች ክፍሎች ላይ ሲያካሂድ የቆየውን የ2018 በጀት አመት የመጀመሪያ ስድስት ወር የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብር አጠናቀቀ:: የ2018 የመጀመርያ ግማሽ አመት የድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብሩ በድጋፍና ክትትል ቡድኑ አማካኝነት ባለፉት ሳምንታት ሲካሄድ የቆየ ሲሆን በዚህም አጠቃላይ በኮሌጁ የሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶችና ስራ ክፍሎችን ተደራሽ በማድረግ በስኬት ማጠናቀቅ ተችሏል:: በድጋፍና ክትትል መርሃ-ግብሩ ወቅት በኮሌጁ የሚገኙ ዋና ስራ ሂደቶች፣ ደጋፊ ስራ ሂደቶች፣ የትምህርትና ስልጠና ክፍሎችን ጨምሮ አጠቃላይ የስራ ክፍሎችን ተደራሽ ማድረግ የተቻለ ሲሆን በድጋፍና ክትትል ቼክሊስት መሰረት የተለዩ ጠንካራ ጎኖችን ለማስቀጠል እንዲሁም የተስተዋሉ ውስነቶችንም ለማሻሻል የሚያግዝ ግብረ-መልስ ለስራ ሂደቶችና ክፍሎች ተሰጥቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 9/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የታላቁ ረመዳን ወር ፆምን ምክንያት በማድረግ የኮሌጁ ሰራተኞችና ባለድርሻ አካላት የተካፈሉበት የኢፍጣር መርሃ-ግብር በተቋሙ አካሄደ::  ይህን መሰል የኢፍጣር መርሃ-ግብር እንደ ተቋም ብሎም እንደ ሀገር አብሮነት እና እንድነት የሚፀባረቁበት ልዩ ትዕይንት መሆኑን የተገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አክለውም ይህን መደጋገፍና በህብረት መቆምን በሁሉም መስኮች ላይ ጠብቆ ማስቀጠል ይገባል ያሉ ሲሆን ይህን ልዩ የኢፍጣር መርሀ-ግብር ላዘጋጁ እንዲሁም ለተሳተፉ የኮሌጁ ማህበረሰብና አጋር አካላት ምስጋና አቅርበዋል።  በኢፍጣር መርሃ-ግብሩ ላይ የስራና ክህሎት ቢሮ አመራሮች እንዲሁም የኮሌጃችን አመራርና ሰራተኞችን ጨምሮ ሰልጣኝ ተማሪዎችም የተሳተፉበት የአብሮነት መርሃ-ግብርም ነበር ። የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 8/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ ከአራቱም ክላስተሮች ለተወጣጡ ወጣቶች ሲሰጥ የቆየው የክህሎት ስልጠና ተጠናቀቀ:: ስልጠናውን የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ ከኮሌጁ ጋር በመተባበር ከአራቱም የገጠር ክላስተሮች ለተወጣጡ 20 ለሚሆኑ ሰልጣኞች በህይወት ክህሎት፣ በመሰረታዊ ቢዝነስ አያያዝ እንዲሁ በካይዘን ስልጠናዎች የተሰጡ ሲሆን ሰልጣኞችም ላለፉት ሳምንታት በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭር ስልጠና ማዕቀፍ የተሰጣቸው ስልጠና በአግባቡ ተከታትለው ማጠናቀቅም ችለዋል:: በስልጠናው ማጠናቀቂያ ላይ ለሰልጣኞች መልዕክት ያስተላለፉት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ ይህ ስልጠና ወጣቶቹ ከዚህ በፊት በኮሌጁ የወሰዱትን የMarketing based sanitation concrete slab training በአግባቡ ስራ ላይ እንዲያውሉ የሚያግዛቸው መሆኑን ገልፀው ወጣቶች እዚህ ያገኟቸውን ክህሎቶች በየአካባቢያቸው የሚስተዋሉትን መሰረታዊ ችግሮች በመቅረፍ የሚፈጠርላቸውን የስራ እድል በእግባቡ መጠቀም ይገባቸዋልም ብለዋል:: በአስተዳደሩ የጤና ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ የሆኑት አቶ ዩሱፍ ሰኢድ በበኩላቸው መሰል ስልጠናዎችን ለአስተዳደሩ ወጣቶች አዘጋጅተው ወደ ኮሌጁ ሲመጡ ምንግዜም ፈጣን ምላሽ ከኮሌጁ እንደሚያገኙ አስታውሰው ለዚህ ስልጠና መሳካት ጉልህ ሚና ለተወጡ የኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን እና አመራሮችም ምስጋና ያቀረቡ ሲሆን ለወጣቶቹም የቀጣይ የስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል:: በመድረኩ ማጠቃለያም ስልጠናውን ተከታትለው ላጠናቀቁ ወጣቶች የምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ መጋቢት 3/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በኮሌጃችን የሚስተዋለውን ከፍተኛ የውሃ እጥረት አስመልክቶ ይህን ችግር በዘላቂነት ለመቅረፍ በተቋማችን ለረጅም ጊዜያት ተዘግቶ የቆየውን የከርሰምድር ውሃ አገልግሎት ላይ ለማዋል ሲደረግ የቆየው ከፍተኛ ጥረት የተሳካ ሲሆን በተጨማሪም የከርሰምድር ውሃውን በሶላር ፓምፕ እንዲሰራ የማድረጉ ስራም ውጤታማ ሆኖ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል::

በድሬዳዋ የነበረኝ ቆይታ ቅኝት

የድሬ የኮሪደር ልማት ምቹ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች፣ የተሻሻለ የአካባቢ ውበትን እና ጥራታቸውን የጠበቁ የማህበረሰብ መሰብሰቢያ ስፍራዎች በድሬ እውን እንዲሆኑ አስችሏል። በኮሪደሩ ለከተማዋ ነዋሪዎች
+9
የድሬ የኮሪደር ልማት ምቹ የህዝብ መዝናኛ ቦታዎች፣ የተሻሻለ የአካባቢ ውበትን እና ጥራታቸውን የጠበቁ የማህበረሰብ መሰብሰቢያ ስፍራዎች በድሬ እውን እንዲሆኑ አስችሏል። በኮሪደሩ ለከተማዋ ነዋሪዎች ገቢ ለማስገኘት የሚያስችሉ የኤሌክትሪክ መኪና ቻርጂንግ ስቴሽን፣ ሱቆች፣ ካፍቴሪያዎች እንዲሁም ደረጃቸውን የጠበቁ የፓርኪንግ ቦታዎች እንዲካተቱበት ተደርጓል።

ኢፍጣር በድሬደዋ የረመዳን ኢፍጣር ከድሬደዋ ነዋሪዎች ጋር። Iftar in Dire Dawa Breaking bread with the local community during Ramadan. #PMOEthiopia