en
Feedback
Federal Law and Justice Institute የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት

Federal Law and Justice Institute የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት

Open in Telegram

Bridging the gap-between Law and Practice!

Show more
5 797
Subscribers
+324 hours
+187 days
+3930 days
Posts Archive
ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ ስልጠናው ረዳት ዳኞች የባለጉዳዮችን ሚስጥር በመጠበቅ ውዝግቦችን ወደተሻለ መፍትሄ የሚያደርሱበትን ክህሎት የሚያስጨብጥ በመሆኑ፣ ለስራቸው ውጤታማነት የጎላ እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸው፤ ሰልጣኞች ንቁ ተሳትፎና የጋራ መማማር እንዲያደርጉ አሳስበዋል። የማስማማት አፈጻጸሙ ከ17 ወደ 1,464 መዛግብት አድጓል። የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጌታው ለገሰ በበኩላቸው፣ በፍርድ ቤቱ የማስማማት ስራ በተጀመረበት ወቅት አፈጻጸሙ 17 መዛግብት ብቻ የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 1,464 ማደጉን ጠቁመዋል። ይህም በፍርድ ቤቱ በኩል ውጤታማና ተስፋ ሰጪ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የሚያሳይ ማረጋገጫ ነው ብለዋል። በህግና በተሞክሮ ላይ የተመሰረተ ስልጠና ይህ የአስማሚነት ክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና በአሰልጣኝ አቶ ኃይሉ ቡራዩ እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን፣ ስልጠናው የተዘጋጀው፦በአዋጅ ቁጥር 1234/2013፣ በፍርድ ቤት መር አስማሚነት መመሪያ ቁጥር 9/2015 እና ከአሰልጣኙ የረጅም ጊዜ የስራ ልምድና ተሞክሮ በመነሳት በተዘጋጀ የማስማማት ስልጠና ማንዋል ላይ ተመስርቶ መሆኑ ተገልጿል። ================== ምንጭ፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

ምክትል ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም፣ ስልጠናው ረዳት ዳኞች የባለጉዳዮችን ሚስጥር በመጠበቅ ውዝግቦችን ወደተሻለ መፍትሄ የሚያደርሱበትን ክህሎት የሚያስጨብጥ በመሆኑ፣ ለስራቸው ውጤታማነት የጎላ እገዛ እንደሚያደርግ ገልጸው፤ ሰልጣኞች ንቁ ተሳትፎና የጋራ መማማር እንዲያደርጉ አሳስበዋል። የማስማማት አፈጻጸሙ ከ17 ወደ 1,464 መዛግብት አድጓል። የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጌታው ለገሰ በበኩላቸው፣ በፍርድ ቤቱ የማስማማት ስራ በተጀመረበት ወቅት አፈጻጸሙ 17 መዛግብት ብቻ የነበረ ቢሆንም፣ በአሁኑ ወቅት ወደ 1,464 ማደጉን ጠቁመዋል። ይህም በፍርድ ቤቱ በኩል ውጤታማና ተስፋ ሰጪ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን የሚያሳይ ማረጋገጫ ነው ብለዋል። በህግና በተሞክሮ ላይ የተመሰረተ ስልጠና ይህ የአስማሚነት ክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና በአሰልጣኝ አቶ ኃይሉ ቡራዩ እየተሰጠ የሚገኝ ሲሆን፣ ስልጠናው የተዘጋጀው፦በአዋጅ ቁጥር 1234/2013፣ በፍርድ ቤት መር አስማሚነት መመሪያ ቁጥር 9/2015 እና ከአሰልጣኙ የረጅም ጊዜ የስራ ልምድና ተሞክሮ በመነሳት በተዘጋጀ የማስማማት ስልጠና ማንዋል ላይ ተመስርቶ መሆኑ ተገልጿል። ================== ምንጭ፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

ለረዳት ዳኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ የአስማሚነት ክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና እየተሰጠ ነው አዲስ አበባ — ሰኔ 19/2018 ዓ.ም የፌደራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከየፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ
+7
ለረዳት ዳኞች ለሁለት ቀናት የሚቆይ የአስማሚነት ክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና እየተሰጠ ነው አዲስ አበባ — ሰኔ 19/2018 ዓ.ም የፌደራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከየፌዴራል  የመጀመሪያ  ደረጃ ፍርድ ቤት ጋር በመተባበር ለረዳት ዳኞች ያዘጋጀው የአስማሚነት ክህሎት ማዳበሪያ ስልጠና በአዲስ አበባ ድሪምላይነር ሆቴል እየተሰጠ ይገኛል። ከሰኔ 19 እስከ 20 ቀን 2018 ዓ.ም የሚቆየው ይህ ስልጠና በዋናነት ረዳት ዳኞች የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን በተመለከተ ያላቸውን ግንዛቤና ክህሎት ለማሳደግ ያለመ ነው። "የፍርድ ቤት መር አስማሚነት ለፍትህ ስርዓቱና ለማህበረሰቡ ሰላም ወሳኝ ነው"  ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ በስልጠናው ላይ በመገኘት የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የፌደራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶክተር ዘካርያስ ኤርኮላ ባስተላለፉት መልዕክት፣ ረዳት ዳኞች የፍርድ ቤት መር አስማሚነትን በመጠቀም አለመግባባቶችን መፍታታቸው በርካታ ጥቅሞች እንዳሉት ገልጸዋል።
"ይህ አሰራር አለመግባባት ውስጥ የገቡ ባለጉዳዮችን ጊዜና ገንዘብ ከመቆጠቡ ባሻገር፣ በፍርድ ቤት የሚከማቹ የመዝገብ ቁጥሮችን ለመቀነስና በማህበረሰቡ መካከል ጤናማ ግንኙነት እንዲኖር ለማድረግ ትልቅ ሚና አለው" ብለዋል።

ለመከላከያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቀቀ አዲስ አበባ ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ላለፉት አራት
ለመከላከያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቀቀ አዲስ አበባ ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ላለፉት አራት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ኢንስቲትዩቱ በበጀት ዓመቱ የፍትሕ አካላት ባለሙያዎችንና አመራሮችን አቅም ለማጎልበት በያዘው ዕቅድ መሠረት የተዘጋጀው ይህ ሥልጠና፥ በዋናነት በጥብቅና እና የክርክር ክህሎት፣ በዳኞች ሥነ-ምግባር፣ ከውል ውጭ ኃላፊነት እንዲሁም በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል። በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ በመገኘት የሥራ መመሪያ የሰጡት የፌዴራል የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ ሲሆኑ "የመከላከያ የዳኝነት አካል የሀገርን ሰላምና ደኅንነት ከማስከበር አንጻር የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው። በመሆኑም ሰልጣኞች ከዚህ መድረክ ያገኟቸውን ዕውቀቶችና ክህሎቶች በተግባር ላይ በማዋል፣ የወታደራዊ ፍትሕ አስተዳደሩ ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ገለልተኛ እና ተዓማኒ እንዲሆን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት ይኖርባቸዋል" ብለዋል። ================== ምንጭ፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

ለመከላከያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቀቀ አዲስ አበባ ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ላለፉት አራት
ለመከላከያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ሲሰጥ የቆየው ሥልጠና ተጠናቀቀ አዲስ አበባ ሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ ወታደራዊ ፍርድ ቤት ዳኞች ላለፉት አራት ተከታታይ ቀናት ሲሰጥ የቆየው የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል። ኢንስቲትዩቱ በበጀት ዓመቱ የፍትሕ አካላት ባለሙያዎችንና አመራሮችን አቅም ለማጎልበት በያዘው ዕቅድ መሠረት የተዘጋጀው ይህ ሥልጠና፥ በዋናነት በጥብቅና እና የክርክር ክህሎት፣ በዳኞች ሥነ-ምግባር፣ ከውል ውጭ ኃላፊነት እንዲሁም በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁጥር 3/2017 ላይ ያተኮረ እንደነበር ተገልጿል። በሥልጠናው ማጠቃለያ ላይ በመገኘት የሥራ መመሪያ የሰጡት የፌዴራል የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ ሲሆኑ "የመከላከያ የዳኝነት አካል የሀገርን ሰላምና ደኅንነት ከማስከበር አንጻር የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው። በመሆኑም ሰልጣኞች ከዚህ መድረክ ያገኟቸውን ዕውቀቶችና ክህሎቶች በተግባር ላይ በማዋል፣ የወታደራዊ ፍትሕ አስተዳደሩ ይበልጥ ቀልጣፋ፣ ገለልተኛ እና ተዓማኒ እንዲሆን የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ማበርከት ይኖርባቸዋል" ብለዋል። ================== ምንጭ፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተከላካይ ጠበቆች ሥልጠና መስጠት ጀመረ አዲስ አበባ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም) የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም
+3
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተከላካይ ጠበቆች ሥልጠና መስጠት ጀመረ አዲስ አበባ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም) የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለመስጠት በያዘው ዕቅድ መሠረት፣ ለፌዴራል ፍርድ ቤቶች ተከላካይ ጠበቆች ወሳኝ በሆኑ ሁለት ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል። ለአራት ተከታታይ ቀናት በሚቆየው በዚህ ሥልጠና ላይ በዋናነት በድንበር ተሻጋሪ ወንጀሎች (Transboundary Crimes) እና በወንጀል ቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁ. 3/2017 ዙሪያ ሰፊ ውይይትና ትምህርት እንደሚሰጥ ታውቋል። በሥልጠናው መክፈቻ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁና የማስጀመሪያ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ፣ የፌዴራል ተከላካይ ጠበቆች አቅም ለሌላቸው ወገኖች በመደገፍና ፍትሕን በማረጋገጥ ረገድ የሚያደርጉት አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን በአጽንኦት ገልጸዋል። አክለውም አሁን የተያዙት የሥልጠና ርዕሶች ወቅታዊ፣ እጅግ አስፈላጊና ለጊዜው የሚመጥኑ መሆናቸውን ገልፀዋል። የሥልጠናውን ዓላማና አስፈላጊነት አስመልክተው ለሰልጣኞች ማብራሪያ የሰጡት የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ክቡር ዳኛ አበበ ሰለሞን በበኩላቸው፣ በቀጣይም ከኢንስቲትዩቱ ጋር ይበልጥ በመቀናጀት መሰል የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠናዎችን ፊት ለፊት (In-person) ብቻ ሳይሆን በበይነ መረብ (Online) ጭምር ተደራሽ ለማድረግ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። ================================= ምንጭ፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ ወታደራዊ ፍትሕ ዳኞች ሥልጠና መስጠት ጀመረ አዲስ አበባ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም ማጎልበ
+6
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ ወታደራዊ ፍትሕ ዳኞች ሥልጠና መስጠት ጀመረ አዲስ አበባ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለመስጠት በያዘው ዕቅድ መሰረት፣ ለመከላከያ ወታደራዊ ፍትሕ ዳኞች በጥብቅና እና የክርክር ክህሎት፣ በዳኞች ሥነ-ምግባር፣ ከውል ውጭ ኃላፊነት እና በቅጣት አወሳሰን መመሪያ ቁ. 3/2017 ላይ ያተኮረ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።   በስልጠናው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ ፣ ከመከላከያ ሰራዊት ጋር መስራት ሀገርን የማገልገል ትልቅ ክብር እንደሚሰጥ ገልጸው፣ ሰልጣኝ ዳኞች ሥልጠናውን በአግባቡ ወስደው ወደ ተግባር እንዲቀይሩት አሳስበዋል። ይህ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለ4 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ይሆናል።    ================================= ምንጭ፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ከተቋሙ አመራሮች በርካታ ጠቃሚ ግብዓቶችና አስተያየቶች የተሰጡ ሲሆን፣ እነዚህን በመጠቀም የ2019–2023 ዓ.ም. ስትራቴጂካዊ ዕቅዱን ይበልጥ የማሻሻል ሥራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ከመግባባት ላይ በመድረስ ተጠናቋል። ”"""""""""""""""""""""'' ምንጭ:- የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለቀጣዩ የ5 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ተቋማዊ ግምገማ አደረገ (አዲስ አበባ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም) የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከ2019 እስከ 2023 ዓ.
+9
የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለቀጣዩ የ5 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ተቋማዊ ግምገማ አደረገ (አዲስ አበባ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም) የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከ2019 እስከ 2023 ዓ.ም. ለሚያከናውናቸው ስትራቴጂካዊ ዕቅዶች ግብዓት የሚሆንና የተቋሙን ወቅታዊ ቁመና በጥልቀት የፈተሸ ሁኔታዊ ትንተና ሪፖርት ለከፍተኛና መካከለኛ አመራሮች ቀርቦ ተገመገመ። ይህ ግምገማ የተካሄደው ተቋሙ በአዋጅ ቁጥር 1369/2017 ተጠሪነቱ ለፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሆኖ ራሱን ችሎ ከተዋቀረ በኋላ ባለው የሽግግርና የእድገት ምዕራፍ ላይ ነው። በአሁኑ ወቅት ያለው የፍትሕ ዘርፍ ሪፎርም፣ የዲጂታል ለውጥ እስትራቴጂ እና የልማት አጋሮች ተሳትፎ መጨመር ለተቋሙ ልዩ ስትራቴጂካዊ ዕድል መፍጠራቸው ተገልጿል። የቀረበው ጥናት የተቋሙን ጥንካሬዎች፣ ድክመቶች፣ ዕድሎችና ስጋቶች (SWOT Analysis) በግልጽ የለየ ሲሆን፤ በተለይም:- ተቋማዊ አደረጃጀትና የአስተዳደር ሥርዓት፣ የሰው ሀብት፣ የደመወዝ፣ ጥቅማጥቅም እና የአገልግሎት ክፍያ ሁኔታዎች፣ የዕቅድ፣ የበጀት፣ የክትትልና ሪፖርት አቀራረብ ሥርዓት፣ የዲጂታላይዜሽንና የቴክኖሎጂ ውህደት፣ እንዲሁም የባለድርሻ አካላት ተሳትፎ ላይ አፅንኦት ሰጥቷል። ሪፖርቱ በሕግና ፍትሕ ምርምር፣ በዳኝነትና ፍትሕ አካላት ሥልጠና፣ በዳታ አስተዳደር እንዲሁም በፍትሕ ማሻሻያ ድጋፍ ዙሪያ የተከናወኑ አፈጻጸሞችን በሚገባ መዝኗል። ከተለያዩ ተሞክሮዎች የተገኙ የንፅፅራዊ ምዘና ግኝቶችን መሠረት በማድረግም፣ በጥናቱ የተለዩትን የልማት ውስንነቶች ለመቅረፍ የሚያስችሉ ቁልፍ ስትራቴጂካዊ ምክረ ሐሳቦች ቀርበዋል።

በቀጣይ በአዳዲስ መረጃዎች እንመጣለን እስከዚው የዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ እያደረጋችሁ በተለቀቁት ዶክመንታሪዎች ደግሞ ተቋሙ ከዬት ተነስቶ የት እንደደረሰ መረጃ ማግኘት ይችላሉ! ሰብስክራይብ ሰብስክራይብ ሰብስክራይብ ሰብስክራይብ ሰብስክራይብ ሰብስክራይብ ሰብስክራይብ ሰብስክራይብ ሰብስክራይብ ሰብስክራይብ https://studio.youtube.com/channel/UCLay285HJaMzVyuBAXLrV9w

የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ የፍትሕ ኃላፊዎች በአመራር ክህሎት ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ አዲስ አበባ | ሰኔ 03 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለመስጠት በያዘው ዕቅድ መሰረት፤ ከሁሉም ዕዞች፣ ኃይሎችና ዋና መምሪያዎች ለተውጣጡ የመከላከያ ፍትሕ ኃላፊዎች ላለፉት 3 ተከታታይ ቀናት በአመራር ክህሎት (Management Skills) በተለይም በውጥረት አያያዝ (Stress Management) እና በዕቅድ ዝግጅት (Planning) ላይ በማተኮር ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል፡፡ በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ በመገኘት ለሰልጣኞች የሥራ መመሪያ የሰጡት የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ደግፌ ቡላ፤ መከላከያ ሰራዊትን መምራት እጅግ ከባድና ታላቅ ኃላፊነት መሆኑን ገልጸው፣ አመራሩ የህግ የበላይነትን ከማረጋገጥ አንፃር የበኩሉን ሚና መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል። አያይዘውም የወታደራዊ አመራር የወጡ ህጎችና መመሪያዎችን ሥነ-ምግባር በጠበቀ መልኩ መተግበርና ማስተግበር እንደሚገባው የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፣ የሰብዓዊ መብትን በማክበር እና በማስከበር ረገድ ሀገራችን ያወጣቻቸውንና ዓለማቀፍ ህጎችን በተገቢው መንገድ መተግበር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በተጨማሪም የህግ ጥሰት በሚኖር ጊዜ ህግን መሰረት በማድረግ ተጠያቂነትን ማስፈንና ፍትሀዊነት እንዲሰፍን ማድረግ እንደሚገባ፣ የመከላከያ አመራርና አባላት ሀገርን ከመጠበቅ ጎን ለጎን የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ማስፈን እንዳለባቸው እንዲሁም የመከላከያ አመራር ቴክኖሎጂን ከመጠቀም አኳያ ራስን ማብቃት እንደሚገባው በጥብቅ አሳስበዋል፡፡ በሌላ በኩል መከላከያ ሰራዊት የሀገር መኩሪያና መከታ መሆኑን የገለፁት የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ፤ ኢንስቲትዩቱ የሰራዊቱን አመራር አቅም በስልጠና ለማጎልበት የጀመረውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል፡፡ የሰራዊቱን ዝግጁነትና የአመራር ብቃት ከፍ የሚያደርገው ይህ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ሲሉ ሀሳባቸውን ቋጭተዋል።

የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ የፍትሕ ኃላፊዎች በአመራር ክህሎት ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ !
+3
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ የፍትሕ ኃላፊዎች በአመራር ክህሎት ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ !

📢 በቅርቡ ይጠብቁ! "ጉዞ ወደ ልህቀት . . .! / Towards Excellence . . .!" የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር፣ በሥልጠና እና በ
📢 በቅርቡ ይጠብቁ! "ጉዞ ወደ ልህቀት . . .! / Towards Excellence . . .!" የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር፣ በሥልጠና እና በተቋማዊ ለውጥ ያሳየውን እድገት የሚያስቃኝ ልዩ የ30 ደቂቃ ዶክመንታሪ እየመጣ ነው! ኢንስቲትዩቱ ከየት ተነስቶ ወደ የት እንደደረሰ፣ ያለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች እና የወደፊት ራዕዩን በሚያሳይ ታሪካዊ ቅኝት ይቀርባል። 🎬 በቅርቡ በይፋ ይለቀቃል! 📌 ይከታተሉን፣ ይጠብቁን፣ ያጋሩ! እስከዚው ድረስ ከስር ባለው ማስፈንጠሪ እየገባችሁ የዩቱብ ቻናላችንን  ሰብስክራይብ አድርጉ! ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ የ12 ደቂቃ መረጃ በውስጡ ስለተጫነ እየገባችሁ ተመልከቱት! https://youtube.com/@federallawandjusticeinstitute?si=gU92LOnAXP_iTHKB #ጉዞ_ወደ_ልህቀት #TowardsExcellence #FederalLawAndJusticeInstitute #FLJI #ዶክመንታሪ #ልህቀት #ፍትሕ #ሕግናፍትሕኢንስቲትዩት

የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ የፍትሕ ኃላፊዎች በማኔጅመንት ስኪል ላይ ስልጠና መስጠት ጀመረ አዲስ አበባ ሰኔ 01 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓ
+4
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ የፍትሕ ኃላፊዎች በማኔጅመንት ስኪል ላይ ስልጠና መስጠት ጀመረ አዲስ አበባ ሰኔ 01 ቀን 2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለመስጠት በያዘው ዕቅድ መሰረት፣ ከሁሉም ዕዞች፣ ኃይሎችና ዋና መምሪያዎች ለተውጣጡ የመከላከያ ፍትሕ ኃላፊዎች በአመራር ክሂሎት (Management Skills) በተለይም በውጥረት አያያዝ (Stress Management) እና በዕቅድ ዝግጅት (Planning) ላይ ያተኮረ ስልጠና መስጠት ጀምሯል። ስልጠናው በሁሉም መስክ ለጋራ ዓላማ እና ግብ በትጋት በመስራት ዘመናዊ ተቋማትን ለመገንባትና ለማሻገር ያለመ ነው። በስልጠናው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ፍትሕ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል አሰፋ ደበሌ ተቋሙ ከሪፎርም ወደ ትራንስፎርሜሽን ራሱን እየለወጠ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ፍትሕን የተከተለ አሰራር ለመተግበር አመራሩ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በመረዳት ስልጠናውን በትኩረት መከታተል እንዳለበት አሳስበዋል። የመከላከያ ፍትሕ ዋና ዳይሬክቶሬት የወንጀል መከላከልና ስልጠና ዳይሬክተር ኮሎኔል ሰለሞን ግርማ በበኩላቸው፣ ለአመራሩ እየተሰጠ ያለው ስልጠና በተቋሙ የፍትሕ ሥርዓትን ለማዘመን አስተዋጽኦው የጎላ እንደሆነና ወደፊትም ቀጣይነት እንደሚኖረው ገልጸዋል። ስልጠናውን እየሰጡ ያሉት የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የተከበሩ ዶክተር ከበደ ገነቲ በበኩላቸው፣ አለም ተለዋዋጭ በመሆኗ በሰራተኞች መካከል ፍትሕን ለማንገስ፣ ኃይልን ለማሰባሰብና አቅጣጫ ለማሳየት ተፅዕኖ ፈጣሪ አመራር ማብቃት ያስፈልጋል ብለዋል። ዛሬ የተጀመረው ይህ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ይሆናል።