Federal Law and Justice Institute የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት
Открыть в Telegram
5 767
Подписчики
-324 часа
+117 дней
+3530 день
Архив постов
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ የፍትሕ ኃላፊዎች በአመራር ክህሎት ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ
አዲስ አበባ | ሰኔ 03 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለመስጠት በያዘው ዕቅድ መሰረት፤ ከሁሉም ዕዞች፣ ኃይሎችና ዋና መምሪያዎች ለተውጣጡ የመከላከያ ፍትሕ ኃላፊዎች ላለፉት 3 ተከታታይ ቀናት በአመራር ክህሎት (Management Skills) በተለይም በውጥረት አያያዝ (Stress Management) እና በዕቅድ ዝግጅት (Planning) ላይ በማተኮር ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቋል፡፡
በስልጠናው ማጠቃለያ ላይ በመገኘት ለሰልጣኞች የሥራ መመሪያ የሰጡት የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ደግፌ ቡላ፤ መከላከያ ሰራዊትን መምራት እጅግ ከባድና ታላቅ ኃላፊነት መሆኑን ገልጸው፣ አመራሩ የህግ የበላይነትን ከማረጋገጥ አንፃር የበኩሉን ሚና መወጣት እንዳለበት አሳስበዋል። አያይዘውም የወታደራዊ አመራር የወጡ ህጎችና መመሪያዎችን ሥነ-ምግባር በጠበቀ መልኩ መተግበርና ማስተግበር እንደሚገባው የገለጹት ዋና ዳይሬክተሩ፣ የሰብዓዊ መብትን በማክበር እና በማስከበር ረገድ ሀገራችን ያወጣቻቸውንና ዓለማቀፍ ህጎችን በተገቢው መንገድ መተግበር እንደሚያስፈልግ አስገንዝበዋል። በተጨማሪም የህግ ጥሰት በሚኖር ጊዜ ህግን መሰረት በማድረግ ተጠያቂነትን ማስፈንና ፍትሀዊነት እንዲሰፍን ማድረግ እንደሚገባ፣ የመከላከያ አመራርና አባላት ሀገርን ከመጠበቅ ጎን ለጎን የዜጎችን ሰላምና ደህንነት ማስፈን እንዳለባቸው እንዲሁም የመከላከያ አመራር ቴክኖሎጂን ከመጠቀም አኳያ ራስን ማብቃት እንደሚገባው በጥብቅ አሳስበዋል፡፡
በሌላ በኩል መከላከያ ሰራዊት የሀገር መኩሪያና መከታ መሆኑን የገለፁት የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ፤ ኢንስቲትዩቱ የሰራዊቱን አመራር አቅም በስልጠና ለማጎልበት የጀመረውን ተግባር አጠናክሮ እንደሚቀጥል አብራርተዋል፡፡ የሰራዊቱን ዝግጁነትና የአመራር ብቃት ከፍ የሚያደርገው ይህ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና በቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል ሲሉ ሀሳባቸውን ቋጭተዋል።
+3
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ የፍትሕ ኃላፊዎች በአመራር ክህሎት ላይ ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ !
📢 በቅርቡ ይጠብቁ!
"ጉዞ ወደ ልህቀት . . .! / Towards Excellence . . .!"
የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ከተመሠረተበት ጊዜ ጀምሮ በትምህርት፣ በምርምር፣ በሥልጠና እና በተቋማዊ ለውጥ ያሳየውን እድገት የሚያስቃኝ ልዩ የ30 ደቂቃ ዶክመንታሪ እየመጣ ነው!
ኢንስቲትዩቱ ከየት ተነስቶ ወደ የት እንደደረሰ፣ ያለፋቸውን ፈተናዎች፣ ያስመዘገባቸውን ስኬቶች እና የወደፊት ራዕዩን በሚያሳይ ታሪካዊ ቅኝት ይቀርባል።
🎬 በቅርቡ በይፋ ይለቀቃል!
📌 ይከታተሉን፣ ይጠብቁን፣ ያጋሩ!
እስከዚው ድረስ ከስር ባለው ማስፈንጠሪ እየገባችሁ የዩቱብ ቻናላችንን ሰብስክራይብ አድርጉ!
ከዚህ በተጨማሪ ደግሞ የ12 ደቂቃ መረጃ በውስጡ ስለተጫነ እየገባችሁ ተመልከቱት! https://youtube.com/@federallawandjusticeinstitute?si=gU92LOnAXP_iTHKB
#ጉዞ_ወደ_ልህቀት #TowardsExcellence #FederalLawAndJusticeInstitute #FLJI #ዶክመንታሪ #ልህቀት #ፍትሕ #ሕግናፍትሕኢንስቲትዩት
+4
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለመከላከያ የፍትሕ ኃላፊዎች በማኔጅመንት ስኪል ላይ ስልጠና መስጠት ጀመረ
አዲስ አበባ ሰኔ 01 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በበጀት ዓመቱ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለመስጠት በያዘው ዕቅድ መሰረት፣ ከሁሉም ዕዞች፣ ኃይሎችና ዋና መምሪያዎች ለተውጣጡ የመከላከያ ፍትሕ ኃላፊዎች በአመራር ክሂሎት (Management Skills) በተለይም በውጥረት አያያዝ (Stress Management) እና በዕቅድ ዝግጅት (Planning) ላይ ያተኮረ ስልጠና መስጠት ጀምሯል። ስልጠናው በሁሉም መስክ ለጋራ ዓላማ እና ግብ በትጋት በመስራት ዘመናዊ ተቋማትን ለመገንባትና ለማሻገር ያለመ ነው።
በስልጠናው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት የመከላከያ ፍትሕ ዋና ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ብርጋዲየር ጄኔራል አሰፋ ደበሌ ተቋሙ ከሪፎርም ወደ ትራንስፎርሜሽን ራሱን እየለወጠ ባለበት በዚህ ወቅት፣ ፍትሕን የተከተለ አሰራር ለመተግበር አመራሩ ሀገራዊና አለም አቀፋዊ ሁኔታዎችን በመረዳት ስልጠናውን በትኩረት መከታተል እንዳለበት አሳስበዋል።
የመከላከያ ፍትሕ ዋና ዳይሬክቶሬት የወንጀል መከላከልና ስልጠና ዳይሬክተር ኮሎኔል ሰለሞን ግርማ በበኩላቸው፣ ለአመራሩ እየተሰጠ ያለው ስልጠና በተቋሙ የፍትሕ ሥርዓትን ለማዘመን አስተዋጽኦው የጎላ እንደሆነና ወደፊትም ቀጣይነት እንደሚኖረው ገልጸዋል።
ስልጠናውን እየሰጡ ያሉት የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ መምህርና የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት አባል የተከበሩ ዶክተር ከበደ ገነቲ በበኩላቸው፣ አለም ተለዋዋጭ በመሆኗ በሰራተኞች መካከል ፍትሕን ለማንገስ፣ ኃይልን ለማሰባሰብና አቅጣጫ ለማሳየት ተፅዕኖ ፈጣሪ አመራር ማብቃት ያስፈልጋል ብለዋል።
ዛሬ የተጀመረው ይህ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ለ3 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ይሆናል።
ሕገ-ወጥ ስደትን እና የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የተዘጋጀ ሀገራዊ ሲምፖዚየም ተጠናቀቀ
ሰመራ /ግንቦት 30 ቀን 2018 ዓ.ም
በፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት እና በሰመራ ዩኒቨርሲቲ በጋራ የተዘጋጀው “ህገ-ወጥ ስደት እና የሰዎች ዝውውር ላይ ትኩረቱን በማድረግ ለሁለት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ብሔራዊ ሲምፖዚየም በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።
ይህ ሲምፖዚየም ከ44 የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች የተውጣጡ የህግ ትምህርት ቤት ዲኖችን፣ ምሁራንን፣ የፖሊሲ አውጭዎች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን ከመላው ሀገሪቱ አሰባስቧል።
በማጠቃለያፕሮግራሙ ላይ የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር እና የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባል የተከበሩ ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ ፣ የሰመራ ዩኒቨርሲቲ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የሌሎች ባለድርሻ አካላት ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
ይህ ሲምፖዚየም በቆይታው ከሰው ማዘዋወር እና ከተደራጀ ህገ-ወጥ ስደት፣ ከኢትዮጵያ የፖሊሲ እና የህግ ማዕቀፎች፣ ከስደት አስተዳደር (migration governance)፣ ከሰው ማዘዋወር ጾታዊ ገፅታዎች፣ ለአስገዳጅ ስደት ከሚሰጡ ህጋዊ ምላሾች እና ችግሮችን በመፍታት ረገድ የሚዲያ ሚና ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን የሚዳስሱ ምሁራዊ የምርምር ፅሁፎች ቀርበዋል።
ይህ ሲምፖዚየም በኢትዮጵያ ውስጥ ለሚታዩት ህገ-ወጥ ስደት እና የሰው ማዘዋወር ችግሮች የሚሰጡ ህጋዊ፣ ማህበራዊ እና ተቋማዊ ምላሾችን ለማጠናከር የሚያስችሉ ተግባራዊ ምክረ-ሀሳቦችን በማመላከት ፍጻሜውን ያገኘ ሲሆን ለሲምፖዚየሙ መሳካ አስተዋፅኦ ላበረከቱ አካላት የምስጋና ምስክር ወረቀት ተበርክቶላቸዋል።
=================================
ምንጭ፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
National Symposium Organized to Prevent Illegal Migration and Human Trafficking Concludes
Samara / June 7, 2026 (Ginbot 30, 2018 E.C.) The two-day national symposium focusing on "Illegal Migration and Human Trafficking," jointly organized by the Federal Law and Justice Institute and Samara University, has successfully concluded.
The symposium brought together law school deans from 44 public universities, scholars, policymakers, and other stakeholders from across the country.
The closing program was attended by H.E. Dr. Zekariyas Erkolla, Deputy Director General of the Federal Law and Justice Institute and Member of the House of Peoples’ Representatives, senior leaders of Samara University, and heads of various stakeholder organizations.
During its course, the symposium featured presentations of scholarly research papers covering issues related to human trafficking and organized illegal migration, Ethiopia’s policy and legal frameworks, migration governance, gender dimensions of human trafficking, legal responses to forced migration, and the role of the media in addressing these challenges.
The symposium concluded by outlining practical recommendations to strengthen legal, social, and institutional responses to the challenges of illegal migration and human trafficking in Ethiopia. Certificates of appreciation were also awarded to individuals and entities that contributed to the success of the symposium.
----------------------------------------------------------------------------------
Source: Public Relations and Communication Directorate
National Symposium Held to Combat Illegal Migration and Human Trafficking
Samara / June 06, 2026 (Ginbot 29, 2018 EC)
The Federal Law and Justice Institute, in collaboration with Samara University, hosted a national symposium aimed at curbing the severe challenges of illegal migration and human trafficking.
The symposium commenced with a welcoming speech by Mr. Ali Zeynu Adem, Vice President for Research (DRTTVP), followed by an opening speech from Dr. Abdurahman, Academic Vice President (AVP) of Samara University.
In his keynote speech, H.E. Dr. Zekarias Erkolla, Deputy Director General of the Federal Law and Justice Institute, emphasized the critical need to build strong linkages between academic research and practical law enforcement to effectively dismantle sophisticated, transnational human trafficking networks.
During the event, six research papers focusing on the current state of migration and human trafficking in Ethiopia were presented by various scholars:
· Prem Sam Ponniah (Ph.D.) presented his research titled "Human Trafficking and Irregular Migration in Ethiopia: South Omo–Turkana Transits," highlighting localized vulnerabilities along major transit routes.
· Mr. Abdushukur Nursela provided a comprehensive overview under the title "Addressing Illegal Migration and Human Trafficking: Policy, Legal, and Institutional Frameworks," identifying key areas requiring reform for legislative and law enforcement bodies.
· Mr. Tsalafu Chaka presented a research paper titled "Ethiopia's Implementation of AU Migration Policy Framework across Moyale Border."
· Mr. Solomon Anteneh shared his study with the audience, titled "Gendered Pathways of Migration and Trafficking in Ethiopia."
· A paper tracing the transition from displacement to exploitation, titled "From Forced Migration to Human Trafficking: Risk Factors and Legal Responses," was presented by Mr. Shishigu Abi Adimasu.
· Mr. Muluken Zemene presented a paper evaluating media responsibilities, titled "The Role of Media in Reducing Illegal Migration and Human Trafficking."
Following the presentations, participants raised numerous questions and constructive ideas, which were addressed with detailed explanations and responses from the presenters.
In its conclusion, the symposium underscored that ensuring sustainable prevention of illegal migration and human trafficking requires enacting policy reforms, strengthening legal responses, and significantly improving border control management.
This forum is an annual event hosted rotationally by selected universities incorporating Ethiopian law schools, drawing participation from prominent legal professionals, researchers, and policymakers.
=================================
Source: Public Relations and Communication Directorate
ሕገ-ወጥ ስደትን እና የሰዎች ዝውውርን ለመከላከል የተዘጋጀ ብሔራዊ ሲምፖዚየም ተካሄደ
(ሰመራ ግንቦት 29/2018 ዓ.ም)የፌዴራል የሕግና የፍትሕ ኢንስቲትዩት ከሰመራ ዩንቨርሲቲ ጋር በመተባበር ሕገ-ወጥ ስደትን እና የሰዎች ዝውውር አስከፊ ፈተናዎች ለመፍታት ያለመ ብሔራዊ ሲምፖዚየም በሰመራ ዩኒቨርሲቲ እያካሄደ ነው።
ይህ መድረክ በኢትዮጵያ የሕግ ትምህርት ቤቶችን ባካተተ መልኩ በአመት አንድ ጊዜ በተመረጠ ዩኒቨርሲቲ የሚካሄድ ሲሆን የህግ ባለሙያዎችን፣ ተመራማሪዎችን እና የፖሊሲ አውጭዎችን በአንድ ላይ በማሰባሰብ የሕገ-ወጥ ስደትን ውስብስብ የሚካሄድ ነው።
ሲምፖዚየሙ በቲቪቲና ምርምር ምክትል ፕሬዝዳንት (DRTTVP) በሆኑት በአቶ አሊ ዘይኑ አደም ሞቅ ያለ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት እና በሰመራ ዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት በዶ/ር አብዱራህማን የመክፈቻ ንግግር ተጀምሯል።
የፌደራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ምክትል ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶ/ር ዘካርያስ ኤርኮላ ባስተላለፉት የዕለቱ ቁልፍ መልዕክት ፤ የተቀናጁ ድንበር ተሻጋሪ የሰዎች ዝውውር መረቦችን ለመግታት በሚሰራ የአካዳሚክ ምርምር እና በተግባራዊ የሕግ ማስከበር ሥራ መካከል ጠንካራ ትስስር መፍጠር እንደሚያስፈልግ አጽንኦት ሰጥተዋል።
በትራንዚት ኮሪደሮች ላይ ያተኮረ ትንታኔ በፕሬም ሳም ፖኒያ (Ph.D.) "በኢትዮጵያ ውስጥ የሰዎች ዝውውር እና ሕገ-ወጥ ስደት፦ የደቡብ ኦሞ–ቱርካና ትራንዚቶች" በሚል ርዕስ ያደረጉትን ምርምር ያቀረቡ ሲሆን፤ በዋና ዋና የትራንዚት መስመሮች ላይ ያሉ አካባቢያዊ ተጋላጭነቶችን አመላክተዋል።
አቶ አብዱሹኩር ኑርሰላ በበኩላቸው "ሕገ-ወጥ ስደትን እና የሰዎች ዝውውርን መፍታት፦ ፖሊሲ፣ ሕግ እና ተቋማዊ ማዕቀፎች" በሚል ርዕስ አጠቃላይ ገለጻ ያደረጉ ሲሆን፤ ለሕግ አውጪውና ሕግ አስከባሪው አካል ማሻሻያ የሚያስፈልጋቸውን ቁልፍ ዘርፎችን ለይተዋል።
“ላይ ያተኮረ ነበር፡፡
=================================
ምንጭ፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
Уже доступно! Исследование Telegram 2025 — ключевые инсайты года 
