Federal Law and Justice Institute የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት
Ir al canal en Telegram
5 957
Suscriptores
Sin datos24 horas
-27 días
+5030 días
Archivo de publicaciones
+9
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ረቂቅ ላይ ከሠራተኞቹ ጋር ተወያየ
(አዲስ አበባ ፤ መስከረም 07/2019 ዓ.ም) የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ረቂቅ ላይ ከተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ጋር ሰፊ ውይይት አካሄደ።
በውይይት መድረኩ ላይ በመገኘት የሥራ አቅጣጫ የሰጡት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ዕቅዱ የተዘጋጀው የ5 ዓመቱን ስትራቴጂክ ዕቅድ መነሻ በማድረግ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሁሉም የተቋሙ የስራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በ2018 በጀት ዓመት የተገኙ ውጤቶችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በ2019 በጀት ዓመት የተሻለ ሥራ እንዲሠሩ አሳስበዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም እያንዳንዱ ሠራተኛ በየዘርፉና በየስራ ክፍሉ በጥልቀት እርስ በርስ መገማገም እንዳለበትና የመገምገሚያ ነጥቦችም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ዕቅዱን ያቀረቡት የለውጥና ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ ሹመት በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ በነደፋቸው አራት ዋና ዋና የትኩረት መስኮች ማለትም በተቋማዊ ልሕቀት፣ በሕግና ፍትሕ ጥናትና ምርምር፣ በዳኝነትና ፍትሕ አካላት አቅም ግንባታ እንዲሁም በሕግና ፍትሕ መረጃና ሪፎርም ላይ ተመስርተው የተዘጋጁ 11 ስትራቴጂያዊ ግቦችንና ዝርዝር ዓላማዎችን አቅርበዋል።
በቀረበው ረቂቅ ዕቅድ ላይ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ለተነሱ ሀሳቦችና አስተያየቶች ከመድረኩ አስፈላጊው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
=================
ዘገባው፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
+8
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ረቂቅ ላይ ከሠራተኞቹ ጋር ተወያየ
(አዲስ አበባ ፤ መስከረም 07/2019 ዓ.ም) የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ረቂቅ ላይ ከተቋሙ አመራሮችና ሠራተኞች ጋር ሰፊ ውይይት አካሄደ።
በውይይት መድረኩ ላይ በመገኘት የሥራ አቅጣጫ የሰጡት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ደግፌ ቡላ ዕቅዱ የተዘጋጀው የ5 ዓመቱን ስትራቴጂክ ዕቅድ መነሻ በማድረግ መሆኑን ጠቅሰው፤ ሁሉም የተቋሙ የስራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በ2018 በጀት ዓመት የተገኙ ውጤቶችን ከግምት ውስጥ በማስገባት በ2019 በጀት ዓመት የተሻለ ሥራ እንዲሠሩ አሳስበዋል።
ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም እያንዳንዱ ሠራተኛ በየዘርፉና በየስራ ክፍሉ በጥልቀት እርስ በርስ መገማገም እንዳለበትና የመገምገሚያ ነጥቦችም መዘጋጀታቸውን ገልጸዋል።
ዕቅዱን ያቀረቡት የለውጥና ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ ሹመት በበኩላቸው ኢንስቲትዩቱ በቀጣይ በነደፋቸው አራት ዋና ዋና የትኩረት መስኮች ማለትም በተቋማዊ ልሕቀት፣ በሕግና ፍትሕ ጥናትና ምርምር፣ በዳኝነትና ፍትሕ አካላት አቅም ግንባታ እንዲሁም በሕግና ፍትሕ መረጃና ሪፎርም ላይ ተመስርተው የተዘጋጁ 11 ስትራቴጂያዊ ግቦችንና ዝርዝር ዓላማዎችን አቅርበዋል።
በቀረበው ረቂቅ ዕቅድ ላይ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት የተደረገበት ሲሆን ለተነሱ ሀሳቦችና አስተያየቶች ከመድረኩ አስፈላጊው ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
=================
ዘገባው፦ የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የሚሰጣቸው የሥልጠና አይነቶች
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የሚሰጣቸው የሥልጠና አይነቶች
+6
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በ2018 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸምና በስትራቴጂያዊ ዕቅድ ላይ ተወያየ
አዳማ፤ ነሐሴ 28/2018 ዓ.ም የፌዴራል የሕግ እና ፍትሕ ኢንስቲትዩት
የ2018 ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማና የአምስት ዓመት ስትራቴጂያዊ ዕቅድ ላይ ከኢንስቲትዩቱ ሠራተኞች ጋር ውይይት አካሄደ
በመድረኩ ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክትና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ የአስተዳደራዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ጌታቸው መንግሥቴ ሲሆኑ በመልዕክታቸውም ይህ መድረክ ባለፈዉ ዓመት የተሠሩ ሥራዎችን በመገምገም የታዩ ክፍተቶችን በመሙላት የተጀመሩ ጠንካራ ሥራዎችን የበለጠ ለማጠናከር ያለመ ነው ብለዋል።
በ2019 በጀት ዓመት ከእያንዳንዱ የሥራ ክፍልና ሰራተኛ ምን እንደሚጠበቅ የምንወያይበትና እንደተቋም የአሠራር ሥርዓት የምንዘረጋበት መድረክ ነው ብለዋል::
አቶ ጌታቸው አክለውም የኢንስቲትዩቱን የአሠራር ሥርዓት በመገንባት ረገድ የእያንዳንዱ ሠራተኛ አስተዋፅኦ የላቀ መሆኑን በመጥቀስ ይህ ውይይት ያስፈለገበት ዋናው ዓላማም የ2018 ዓ.ም አፈፃፀምን በመገምገም የ5 ዓመቱን ስትራቴጂክ ዕቅድና የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ ዕቅድ ላይ ተወያይቶ ከስምምነት ላይ በመድረስ ወደ ተግባር ለመግባት መሆኑን ገልፀዋል::
የኢንስቲትዩቱ የዕቅድና በጀት ዝግጅት ቡድን መሪ አቶ ዳንኤል ዋቅጋሪ የ2018 ዓ.ም የሥራ አፈፀም ሪፖርት እና የለውጥና ስትራቴጂክ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አበበ ሹመት የኢንስቲትዩቱን የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ረቂቅ ዕቅድ ያቀረቡ ሲሆን በቀረቡት ሰነዶች ላይ የቡድን ውይይት ተደርጎ በርካታ ሀሳቦች ተነስተዋል።
ውይይቱ በነገው ዕለትም የሚቀጥል ይሆናል ።
================
ዘገባው፡- የሕዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
+5
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች ልዩ ሥልጠና መስጠት ጀመረ
(አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም)
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች በአራት ዋና ዋና ርዕሶች ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።
በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የሕግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ከልክሌ፤ ኮርፖሬሽኑ ከተቋቋመበት ዓላማ አንጻር ሥልጠናው በንግድ ሥርዓቱ ዙሪያ ያለውን ግንዛቤ ለማዳበር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። አክለውም ሰልጣኞች ሥልጠናውን በንቃት በመከታተል ያገኟቸውን እውቀቶች በስራ ገበታቸው ላይ በተግባር ማዋል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ይህ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ዛሬን ጨምሮ ለ10 የሥራ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን፣ በተለይም ዛሬ በተጀመረው ሥልጠና የንግድ ሕግ እና ተዛማጅ የሕግ ማዕቀፎች ላይ በማተኮር ለሚቀጥሉት 3 ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ዋና ዓላማውም በአዲሱ የንግድ ሕግ የተሻሻሉና አዲስ የተጨመሩ መሠረታዊ ጉዳዮችን መለየት፣ ስለ ንግድ እና ነጋዴነት አጠቃላይ ጽንሰ-ሐሳብ በቂ ግንዛቤ ማስጨበጥ፣ እንዲሁም የንግድ ማኅበራትን ምንነት፣ ዓላማ፣ ዓይነቶችና መሠረታዊ ባህሪያት (አንድነትና ልዩነት) በግልጽ ማሳወቅ ነው።
በተጨማሪም ተሳታፉፊዎች የንግድ ማኅበራት ምስረታን፣ ሕጋዊነት መስፈርቶችን፣ የአደረጃጀትና አስተዳደር ሥርዓት አሰራርን እንዲረዱ ከማድረጉም በላይ፣ የማኅበራቱ መሪዎች ተግባር፣ ኃላፊነትና ተጠያቂነት ላይ ግልጽ ግንዛቤ በመፍጠር የስብሰባ ሥነ-ሥርዓትና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶችን በትክክል ለይተው እንዲያውቁ ማስቻል ነው።
===================
ዘገባው:-የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
