Federal Law and Justice Institute የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት
Відкрити в Telegram
5 922
Підписники
+424 години
+127 днів
+2930 день
Архів дописів
+5
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች ልዩ ሥልጠና መስጠት ጀመረ
(አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 18/2018 ዓ.ም)
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን አመራሮችና ባለሙያዎች በአራት ዋና ዋና ርዕሶች ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።
በመድረኩ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የፌዴራል ቤቶች ኮርፖሬሽን የሕግ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ከልክሌ፤ ኮርፖሬሽኑ ከተቋቋመበት ዓላማ አንጻር ሥልጠናው በንግድ ሥርዓቱ ዙሪያ ያለውን ግንዛቤ ለማዳበር ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው ገልጸዋል። አክለውም ሰልጣኞች ሥልጠናውን በንቃት በመከታተል ያገኟቸውን እውቀቶች በስራ ገበታቸው ላይ በተግባር ማዋል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።
ይህ የአቅም ማጎልበቻ ሥልጠና ዛሬን ጨምሮ ለ10 የሥራ ቀናት የሚሰጥ ሲሆን፣ በተለይም ዛሬ በተጀመረው ሥልጠና የንግድ ሕግ እና ተዛማጅ የሕግ ማዕቀፎች ላይ በማተኮር ለሚቀጥሉት 3 ቀናት የሚሰጥ ሲሆን ዋና ዓላማውም በአዲሱ የንግድ ሕግ የተሻሻሉና አዲስ የተጨመሩ መሠረታዊ ጉዳዮችን መለየት፣ ስለ ንግድ እና ነጋዴነት አጠቃላይ ጽንሰ-ሐሳብ በቂ ግንዛቤ ማስጨበጥ፣ እንዲሁም የንግድ ማኅበራትን ምንነት፣ ዓላማ፣ ዓይነቶችና መሠረታዊ ባህሪያት (አንድነትና ልዩነት) በግልጽ ማሳወቅ ነው።
በተጨማሪም ተሳታፉፊዎች የንግድ ማኅበራት ምስረታን፣ ሕጋዊነት መስፈርቶችን፣ የአደረጃጀትና አስተዳደር ሥርዓት አሰራርን እንዲረዱ ከማድረጉም በላይ፣ የማኅበራቱ መሪዎች ተግባር፣ ኃላፊነትና ተጠያቂነት ላይ ግልጽ ግንዛቤ በመፍጠር የስብሰባ ሥነ-ሥርዓትና የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶችን በትክክል ለይተው እንዲያውቁ ማስቻል ነው።
===================
ዘገባው:-የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
በተቋማዊ ልህቀት ረገድ ግልጽነትና ተጠያቂነት ያለው አሠራር ለመዘርጋት የአመራርና የአፈጻጸም አቅም የሚገነባ ሲሆን፣ የፊዚካልና የዲጂታል መሠረተ ልማቶችን በማዘመን ስማርት የሥልጠናና የምርምር ማዕከላት ይደራጃሉ። በተጨማሪም ስትራቴጂካዊ ኮሙኒኬሽንና አጋርነትን ማጠናከር የትኩረት አቅጣጫ ተደርጎ ተይዟል።
በሕግና ፍትሕ ጥናትና ምርምር ዘርፍ ኢንስቲትዩቱ ችግር ፈቺ ጥናቶችን ለማሳደግ የውስጥ ተመራማሪዎችን አቅም የሚያጎለብት ሲሆን፣ በዳኝነትና ፍትሕ አካላት አቅም ግንባታ በኩል ደግሞ የቅድመ-ሥራና የሥራ ላይ ሥልጠናዎችን ጥራት በማሻሻል የዲጂታልና የኢ-ለርኒንግ አማራጮች ሰፊ ትኩረት ይሰጣቸዋል። በተመሳሳይ በፍላጎት ላይ የተመሠረቱ የሥልጠና ሞጁሎችን በማዘጋጀት በሀገር አቀፍ ደረጃ የሕግ አሠልጣኞችን ብቃት ለማሳደግ ታቅዷል።
በሌላ በኩል በሕግና ፍትሕ መረጃና ሪፎርም ዘርፍ ዘመናዊና ሀገር አቀፍ የሕግና ፍትሕ መረጃ ማዕከል በማልማት የመረጃ ክምችትን ለማሳደግ እንደሚሰራ የተጠቆመ ሲሆን ኢንስቲትዩቱ የሕግ ትምህርት ሪፎርምን ጨምሮ የጋራ ሪፎርም ፕሮግራሞችን እንደሚተገብርና ለሥራዎቹ አስፈላጊ የሆነ ስትራቴጂካዊ ሀብት እንደሚያሰባስብም ተገልጿል።
በውይይቱ ማጠቃለያ ላይ የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች አስፈላጊውን ግብረ-መልስና ተጨማሪ አስተያየት የሰጡ ሲሆን፣ የቀጣይ በጀት ዓመት ዋና ዋና የትኩረት አቅጣጫዎች ከተቀመጡ በኋላ መድረኩ ተጠናቋል።
===================
ዘገባው:-የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት
+9
የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በ4 ዋና ዋና መስኮች ላይ በማተኮር የ2019 ረቂቅ ዕቅድ ላይ ተወያየ
(አዳማ፤ ነሐሴ 16/2018 ዓ.ም)የፌዴራል የሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት በ2019 በጀት ዓመት በትኩረት በሚተገብራቸው አራት ስትራቴጂካዊ መስኮች እና 24 ዓላማዎች ላይ ያተኮረ ረቂቅ ዕቅድ ከአመራሮቹ ጋር ገመገመ።
በአዳማ ከተማ በተካሄደው በዚህ የውይይት መድረክ፣ የኢንስቲትዩቱ የዕቅድና በጀት ዝግጅት ቡድን መሪ አቶ ዳንኤል ዋቅጋሪ ባቀረቡት ረቂቅ ዕቅድ መሠረት፣ ተቋሙ በቀጣዩ በጀት ዓመት አደረጃጀቱንና የአገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን የሚያስችሉ በርካታ ተግባራትን ለማከናወን አቅዷል።
የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የ5 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ተቋማዊ ግምገማና ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄደ
(አዳማ፤ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም) የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለቀጣይ አምስት ዓመታት (ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ) የሚያገለግለውን ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ረቂቅ እና የተቋማዊ ሁኔታዎች ግምገማ ሪፖርት በአዳማ ከተማ ካኖፒ ሆቴል ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ።
በመድረኩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ ዋና ዳይሬክተር ክቡር አምባሳደር ደግፌ ቡላ እንደገለጹት፤ ኢንስቲትዩቱ በአዋጅ ቁጥር 1369/2017 መሠረት በነፃነትና በገለልተኝነት የሕግና ፍትሕ የልህቀት ማዕከል ሆኖ እንዲሠራ እንደገና መዋቀሩን አብራርተዋል። ተቋሙ ተጠሪነቱ ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ሆኖ በ7 አባላት ባሉት ቦርድ እንደሚመራና በዋናነትም፡-የጥናትና ምርምር ሥራዎችን ማከናወን፣የአቅም ግንባታና ሥልጠና መስጠት፣የሕግና ፍትሕ መረጃ ማዕከል ሆኖ ማገልገል፣የሕግና ፍትሕ ተቋማት የሪፎርም ሥራዎችን ማስተባበርና መደገፍ የሚሉ ዋና ዋና ተግባራትን እያከናወነ ይገኛል።ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም የቀረበው የ5 ዓመት ስትራቴጂክ ዕቅድ በውጭ ኮንሰልታንት ተዘጋጅቶ፣ የተቋሙ አመራሮችና ባለሙያዎች በቅርበት የተሳተፉበት፣ በተቋም ደረጃ በርካታ ውይይቶች ተደርገውበት እንዲሁም በኢንስቲትዩቱ ቦርድ ከተገመገመ በኋላ ለባለድርሻ አካላት እንዲቀርብ መደረጉን ገልጸዋል።በመድረኩ የተቋሙ አሁናዊ ሁኔታ ጥናትና ግምገማ በአቶ ደሳ ቡልቻ የቀረበ ሲሆን፤ የ5 ዓመቱ ረቂቅ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ደግሞ በለውጥና ስትራቴጂካዊ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር በአቶ አበበ ሹመት አቀራራቢነት ለተሳታፊዎች ቀርቧል።በቀረቡት ሰነዶች ዙሪያ በተሳታፊዎች ሰፊ ውይይት ተካሂዶ ዕቅዱን የሚያዳብሩ አስፈላጊ ግብዓቶች የተሰበሰቡ ሲሆን፤ የምክክር መድረኩን በበላይነት የመሩት የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር የተከበሩ ዶክተር ዘካርያስ ኤርኮላ ናቸው።
===================
ዘገባው:-የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው
+4
የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የ5 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ተቋማዊ ግምገማና ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄደ
+4
የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት የ5 ዓመት ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ተቋማዊ ግምገማና ከባለድርሻ አካላት ጋር አካሄደ
(አዳማ፤ ነሐሴ 15/2018 ዓ.ም) የፌዴራል ሕግና ፍትሕ ኢንስቲትዩት ለቀጣይ አምስት ዓመታት (ከ2019 ዓ.ም ጀምሮ) የሚያገለግለውን ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ረቂቅ እና የተቋማዊ ሁኔታዎች ግምገማ ሪፖርት በአዳማ ከተማ ካኖፒ ሆቴል ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ።
+4
የሕግ ትምህርት ቤቶች ኮንሰርቲዬም ስብሰባ ተካሄደ
አዲስ አበባ፤ ነሐሴ 13 ቀን 2018 ዓ.ም
የፌዴራል የሕግና የፍትሕ ኢንስቲትዩት የሕግ ትምህርት ቤቶች ኮንሰርቲዬም ስብሰባ በአዲስ አበባ ድሪም ላይነር ሆቴል አካሄደ፡፡
በስብሰባው ላይ በመገኘት የእንኳን ደህና መጣችሁና የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢንስቲትዩቱ የጥናትና ምርምር ዘርፍ ተወካይ አቶ ሀይለሚካኤል መላኩ ሲሆኑ፣ ባደረጉት ንግግር የሕግ ትምህርት ቤቶች ኮንሰርቲዬም የሕግ ትምህርት ጥራትን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት ውስጥ የመሪነትና የቅንጅት ድርሻ እንዳለው ገልጸዋል። አክለውም የዚህ ዓይነቱ ስብሰባ በተቋማት መካከል ያለውን አጋርነት ከመጨመር ባሻገር፣ የታቀዱ የሕግ ትምህርት ማሻሻያ ግቦችን በጋራ ለመስራትና ውጤታማ ለማድረግ ትልቅ አስተዋጽኦ እንዳለው አስገንዝበዋል።
የ2018 በጀት ዓመት የሥራ አፈፃፀም ሪፖርትና የቀጣይ 2019 በጀት ዓመት ዕቅድ በኮሚቴው ፀሐፊ አቶ መስፍን እሸቱ የቀረበ ሲሆን በሪፖርቱም በበጀት ዓመቱ የታቀዱ ሥራዎች፣ የተከናወኑ ተግባራት፣ ታቅደው ያልተከናወኑ ተግባራት፣ ያጋጠሙ ችግሮች እና የመፍትሔ ሀሳቦች ተዳሰዋል፡፡
በቀረበው ሪፖርት ላይ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳብና አስተያየቶች ቀርበው ውይይት እየተደረገበት ይገኛል ።
===================
ዘገባው:-የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው !
ኢንስቲትዩቱ የዳኝነት እና የፍትህ ስርዓቱን ለማዘመን የሚያስችሉ ተግባራት እያከናወነ ነው - ኢዜአ አማርኛ
https://www.ena.et/web/amh/w/amh_9412057
+2
ኢንስቲትዩቱ የሕግ ባለሙያዎችን ሙያዊ ዕውቀት ለማጎልበት የበይነ-መረብ ስልጠና ሊሰጥ ነው
ነሐሴ 09/2018 ዓ.ም አዳማ
የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት የዳኞችን እና የዐቃቤያነ-ህግን ሙያዊ ዕውቀትና ክህሎት ለማጎልበት የሚያስችል የበይነ-መረብ (E-learning) ስልጠና እንደሚሰጥ አስታወቀ። ኢንስቲትዩቱ አዲሱን አሰራር ወደ ተግባር ለማስገባት የተዘጋጁ ሞጁሎችን ለፌዴራልና ለክልል የፍትህ ሴክተር አመራሮች ያሳወቀበት የምክክር መድረክ በአዳማ ከተማ አካሂዷል።
የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ዘካሪያስ ኤርኮላ እንደገለፁት፣ ስልጠናው ኢንስቲትዩቱ ከዚህ ቀደም ይከተለው የነበረውን ከገፅ-ለገፅ አሰራር ወደ ቴክኖሎጂ በመቀየር የ'ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030' ግቦችን ለማሳካት ያለመ እንደነበር ተናግረዋል።
ለዚህ መርሃ ግብር ከጠቅላይ ፍርድ ቤት እና ከፍትህ ሚኒስቴር ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ስድስት የዲጂታል ኮርሶች ማለትም የፍርድ ቤት ኬዞች ምዝገባ፣ የፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት፣ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት፣ የክርክር አመራር እንዲሁም የማስረጃ አሰማምና አቀራረብ መዘጋጀታቸውን አብራርተዋል።
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ክብርት ወይዘሮ ለሊሴ ደሳለኝ በበኩላቸው አሰራሩ ዳኞችና የፍትህ አካላት ከስራ ገበታቸው ሳይርቁ ባሉበት ሆነው እንዲሰለጥኑ ያስቻለ በመሆኑ የፍትህ አገልግሎቱን ጥራት፣ ቅልጥፍና እና ተዳራሽነት ለማሳደግ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ማበርከቱን ገልፀዋል።
በመጨረሻም በኢ-ለርኒንግ መርሃ-ግብሩ ለተሳተፉ አካላት የምስክር ወረቀት ተሰጥቶ የመርሃ-ግብሩ ፍፃሜ ሆኗል ።
================
ዘገባው:-የህዝብ ግንኙነትና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክቶሬት ነው !
ኢንስቲትዩቱ የዳኞችና ዐቃቤያነ-ህግን ሙያዊ ዕውቀት ለማጎልበት የበይነ-መረብ ስልጠና ሊሰጥ ነው - ኢዜአ አማርኛ
አዳማ፤ ነሐሴ 09/2018 (ኢዜአ)፦ የፌዴራል ህግና ፍትህ ኢንስቲትዩት የዳኞችና ዐቃቤያነ-ህግን ሙያዊ ዕውቀት ለማጎልበትና ክህሎታቸውን ለማዳበር የሚያስችል የበይነ-መረብ ትምህርትና ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገለፀ።
ኢንስቲትዩቱ የበይነ-መረብ ትምህርትና ስልጠናውን ለማስጀመር የተዘጋጁ ኮርሶችንና ሞጁሎችን በየደረጃው ለሚገኙ የፌዴራልና የክልል የፍትህ ሴክተር አመራሮች እንዲሁም ለባለድርሻ አካላት የማስተዋወቅና ወደ ተግባር ለማስገባት የሚያስችል የምክክር መድረክ በአዳማ በማካሄድ ላይ ይገኛል።
የኢንስቲትዩቱ ምክትል ዋና ዳይሬክተር ዘካሪያስ ኤርኮላ(ዶ/ር) እንደገለፁት፤ ኢንስቲትዩቱ ከገፅ ለገፅ ስልጠና አሰጣጥ ዘዴ በመውጣት በቴክኖሎጂ ወደ ተደገፈ የበይነ መረብ ስልጠና ለመሻገር ነው ብለዋል።
የመደመር መንግሥት የ2030 ዲጂታል ኢትዮጵያ ግቦችን ለማሳካት የኢንስቲትዩቱን የስልጠና አሰጣጥ ሂደትን ወደ ''ኢ-ለርኒንግ'' ለማሻገር ያለመ የበይነ መረብ ስልጠና ማስጀመሪያ ፕሮግራም መሆኑንም ተናግረዋል።
ለዚህም ጠቅላይ ፍርድ ቤትና የፍትህ ሚኒስቴር የህግ ሙያተኞችና ባለድርሻ አካላትን ባሳተፈ መልኩ ስድስት የዲጂታል ኮርሶች ተዘጋጅተዋል ብለዋል።
በመርሃ ግብሩ ዳኞችና የፍትህ አካላት በስራ ቦታ ላይ ሆነው ባላቸው ኮምፒውተር፣ ስማርት ስልኮችና ታብሌቶች ስልጠናውን መውሰድ ይችላሉ ብለዋል።
ይህም ዳኞች ባሉበት ቦታ ሆነው በህግ ላይ ያላቸውን ዕውቀትና ክህሎት እንዲያዳብሩ እንዲሁም አቅማቸውን እንዲገነቡ ያስችላቸዋል ብለዋል።
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት ወይዘሮ ለሊሴ ደሳለኝ በበኩላቸው፣ ኢንስቲትዩቱ ያዘጋጀው የበይነ-መረብ ስልጠና ዳኞችና ዐቃቤያነ-ህግ የህግ ክህሎታቸውን በማዳበር መሰረታዊ አቅማቸውን እንዲገነቡ የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።
የኢንስቲትዩቱ የስልጠና ሂደት በቴክኖሎጂ እንዲደገፍ መደረጉ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ግቦችን ለማሳካት የተጀመረውን ጉዞ የሚያፋጥን ተግባር መሆኑንም ተናግረዋል።
የፍርድ ቤት ኬዞች ምዝገባ፣ የፍትሐብሔር ሥነ-ሥርዓት፣ የወንጀል ሥነ-ሥርዓት፣ የክርክር አመራር፣ እንዲሁም የማስረጃ አሰማምና አቀራረብን ጨምሮ ስድስት ኮርሶች መዘጋጀታቸው ገልጸዋል።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዚዳንት አቶ ቦጋለ ፈይሳ በበኩላቸው፤ የበይነ-መረብ ስልጠናው የዳኞችንና የፍትህ አካላትን ሙያዊ ብቃት ባሉበት ሆነው ለማሳደግ ቁልፍ ሚና እንዳለው ተናግረዋል።
የፍርድ ቤት ዳኞች ስራ የሚበዛባቸው በመሆኑ፣ ከስራ ገበታቸው ሳይርቁ ባሉበት ቦታ ሆነው አቅምና ዕውቀታቸውን እንዲያዳብሩ የሚያስችል መሆኑንም ተናግረዋል።
በተጨማሪም ስልጠናው የፍትህ አገልግሎቱን ጥራት ለማስጠበቅ፣ ቀልጣፋና ውጤታማ ለማድረግ ወሳኝ መሆኑን የገለጹት ፕሬዚዳንቱ፣ በየደረጃው ያሉ የክልሉ ዳኞች የዕድሉ ተጠቃሚ እንዲሆኑ እንደሚሰሩ ተናግረዋል።
የሐረር ክልል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዚዳንት ወይዘሮ አኢሻ ሚኔ ዑመር በበኩላቸው ያለንበት ዘመን የዲጂታላይዜሽንና የመንግስት የትኩረት አቅጣጫ በመሆኑ የበይነ መረብ ትምህርትና ስልጠና ወሳኝ መሆኑን ገልፀዋል።
የበይነ-መረብ ስልጠና መርሃ ግብሩ ዳኞችና የፍትህ አካላት ከወቅቱ ጋር በመራመድ ራሳቸውን በዕውቀትና በክህሎት እንዲያበቁ የሚያስችል መሆኑንም አክለው ገልጸዋል።
ኢንስቲትዩቱ የዳኞችና ዐቃቤያነ-ህግን ሙያዊ ዕውቀት ለማጎልበት የበይነ-መረብ ስልጠና ሊሰጥ ነው - ኢዜአ አማርኛ
https://www.ena.et/web/amh/w/amh_9405232
