en
Feedback
swa 58 primary

swa 58 primary

Open in Telegram

Materials platform for swa 58

Show more
3 270
Subscribers
+424 hours
+57 days
-530 days
Posts Archive
photo content

photo content

ለሳዌአ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች ጉዳዩ:- የ2019 የት/ዘመን ቅድመ-ዝግጅት ማስታወሻ ፤ የማክበር ሰላምታችንን እያቀረብን ለትምህርት ቤት ዝግጅት እንዲያመቻችሁ የሚከተሉትን ጉዳዮች ልናስታውስ ወደድን፦ 1. የትምህርት ዘመን እና የክፍል ሰዓት • ትምህርት የሚጀመርበት ቀን፦ ሁሉም ቅድመ ዝግጅቶች ተጠናቀው መደበኛ ትምህርት ሰኞ መስከረም 04 ቀን 2019 ዓ.ም. ይጀምራል። • የክፍል ምደባ ማስታወቂያ፦ የተማሪዎች የክፍል ምደባ በትምህርት ቤቱ የውስጥ ማስታወቂያ ሰሌዳ ላይ ይለጠፋል። • ከጠዋት 2:00 ሰዓት ከሰልፍ ስነ-ስርዓት በፊት ተማሪዎች ት/ቤት ግቢ እንድታደርሷቸው እና ትምህርት ለሙሉ ቀን እስከ 9:00 ሰዓት ስለሆነ በጊዜ እንድትወስዷቸው ይሁን። 2. የስነ-ስርዓት፣ የፀጉር እና የአለባበስ መመሪያዎች:- እነዚህን ቅድመ ሁኔታዎች ያላሟሉ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ቤት ግቢ የማይገቡ መሆኑን አስተዳደሩ በጥብቅ ያሳስባል፦ • ለወንድ ተማሪዎች፦ የራስ ፀጉራቸውን ሁልጊዜም እኩል የሆነ አጭር ቁርጥ (Clean Cut) መሆን አለበት። የተለየ ፋሽን ወይም ረጅም ፀጉር ማሳደግ የተከለከለ ነው። • ለሴት ተማሪዎች፦ የራስ ፀጉራቸውን ንጹህ አድርገው በተገቢው ሁኔታ ሹሩባ መሥራት ይኖርባቸዋል። ፀጉርን ሳይሰሩ መምጣት፣ ሰው ሰራሽ ፀጉር (ኤክስቴንሽን) መጠቀም ወይም የተለያዩ ደማቅ የፀጉር ማስያዣዎችን ማድረግ አይፈቀድም። • ጌጣጌጥ እና ሜካፕ፦ ማንኛውንም አይነት የፊት ሜካፕ፣ የጥፍር ቀለም፣ ጉትቻ፣ የአንገት ሀብል፣ ቀለበት ወይም የእጅ አንባር ማድረግ ሙሉ በሙሉ የተከለከለ ነው። • የደንብ ልብስ (ዩኒፎርም)፦ ተማሪዎች በየቀኑ ሙሉ፣ ንጹህ እና ያልተቀደደ የትምህርት ቤቱን ደንብ ልብስ መልበስ አለባቸው። ከደንብ ልብስ ውጪ የሆኑ ሲቪል ልብሶችን ደርቦ መምጣት አይቻልም። 3. የምግብ አቅርቦት እና የጤና ጥበቃ መመሪያዎች • የግል እቃዎች አቅርቦት፦ ተማሪዎች የዕለት ምሳቸውን በምሳ ዕቃ (Lunchbox) እና በቂ የውሃ ኮዳቸውን ይዘው መምጣት አለባቸው። • ስም መጻፍ፦ በማንኛውም መልኩ እንዳይጠፉ የተማሪው ሙሉ ስም እና ክፍል በምሳ ዕቃቸው፣ በውሃ ኮዳቸው ፣ በቦርሳቸው እና  በመጽሃፋቸው ላይ በግልጽ መጻፍ አለበት። • ምግብ አለመቀያየር (Strict No-Sharing)፦ ለተማሪዎች ጤና፣ ንጽህና እና ከአለርጂ ለመጠበቅ ሲባል ተማሪዎች እርስ በእርሳቸው ምግብ፣ መክሰስ፣ ወይምውሃ  መለዋወጥ እና መጋራት የተከለከለ ነው። • የተከለከሉ ምግቦች፦ በጣም የተቀነባበሩ ፓኬት ምግቦችን፣ ሰው ሰራሽ ማጣፈጫ የበዛባቸውን ጣፋጮች እና ጋዝ ያላቸውን ለስላሳ መጠጦች (ሶዳ) ይዞ መምጣት የተከለከለ ሲሆን፤ በቤት ውስጥ የተዘጋጁ ጤናማ ምግቦች ይመረጣሉ። 4. የመማርያ ደብተር ብዛት:- ከ1-2ኛ ክፍሎች ብዛት 7፣ ከ3-6ኛ ክፍሎች ብዛት 8፣ ከ7-8ኛ ክፍሎች ብዛት 11፤ መልካም የዝግጅት እና የአዲስ ዓመት በዓል እንዲሆንልን ከወዲሁ እንመኛለን!! የሳዌአ አስተዳደር

Yididiya Tewodros, a Grade 8 student from SWA 58, achieved second place in the Nifas Silk Kifle Ketema City Level Examination Results. On this occasion, he was awarded a certificate and a prize of 4,000 birr by the KK Education Secretariat. Congrats!!✨

photo content
+1

የቀን ማስተካከያ:- የመጽሐፍት ሽያጭ መጀመሪያ ቀን ወደ ሰኞ ነሐሴ 18፣ 2018 መቀየሩን ከይቅርታ ጋር እናስታውቃለን። ከመፅሐፍት ሽያጭ ክፍል

ውድ የሳዌአ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች  የተወሰኑ የአንደኛ ደረጃ መፅሀፍት ለሽያጭ ስለመጡ ከላፍቶ ሁለተኛ ደረጃ ከአርብ ነሀሴ 15፣ 2018 ዓ.ም ጀምሮ መግዛት እንደምትችሉ ለማሳወቅ እንወዳለን::                   የትምህርት ቤቱ አስተዳደር

ጥብቅ ማሳሰቢያ ለወላጆች ህጋዊ አሳዳጊዎች:- ከሁሉ አስቀድመን የከበረ ሰላምታችንን እያቀረብን ለ2019 ዓ.ም. የትምህርት  ዘመን የተማሪዎች  ምዝገባ  ተጀምሯል። ምዝገባው የሚጠናቀቀው ሀምሌ 10 ቀን 2019 ነው። በመሆኑም  ምዝገባችሁን እንድትፈፅሙ እያሳሰብን ከተጠቀሠው የምዝገባ ጊዜ በኋላ  የሚመጣ ነባር ተመዝጋቢ በራሱ ፈቃድ ትምህርት ቤቱን እንደለቀቀ ተቆጥሮ ቦታው በሌላ ተመዝጋቢ እንደሚያዝ በአፅኖት እናሳስባለን። ከዚህ በተጨማሪ በተለያዩ  ምክኒያቶች በ2019 ዓም  የትምህርት ዘመን በትምህርት ቤቱ የማትቀጥሉ ተማሪዎች  እስከ ሐምሌ 10 ቀን 2019 ድረስ ባለው የጊዜ ገደብ ውስጥ ክሊራንስ አውጥታችሁ መሸኛችሁንና አስፈላጊውን ደክመት እንድትወስዱ በጥብቅ እናሳስባለን።

ለሳዌአ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች የማክበር ሰላምታችንን እያቀረብን የ2019 ዓ/ም የትምህርት ዘመን ምዝገባ ሐምሌ 1/2018 ዓ/ም ይጀመራል፡፡ ለምዝገባ የሚያስፈልጉ ቅድመ ሁኔታዎች፡- 1) የ2018ዓ/ም ውጤት ካርድ፣ 2) የምዝገባ እና የመስከረም ወር 2019 ዓ/ም ወርሃዊ ክፍያ የተፈጸመበት ደረሰኝ፣ 3) አንድ 2x3 ጉርድ ፎቶ ግራፍ፣ 4) የተማሪው የፋይዳ መታወቂያ/ቁጥር ይዛችሁ እንድትቀርቡ በትህትና እናሳስባለን፡፡ ጥራት ላለው ትምህርት እንተጋለን!

✨ውድ ወላጆች/ህጋዊ አሳዳጊዎች:- እንኳን ደስ ያለንት/ቤታችን ሳውዝ ዌስት አካዳሚ የ2018 የ6ኛ ክፍል በከተማ አቀፍ ፈተና 100% አሳልፏል!! ይህ ውጤት እንዲመዘገብ ከፍተኛ ሚና ስትጫወቱ ለነበራችሁ የት/ቤታችን ባለድርሻ አካላት በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ ልንል እንወዳለን !!✨

ሜስታወሻ:- ውድ ወላጆች የተማሪዎች ውጤት ካርድ የሚሰጠው ከሰኞ ሰኔ 29 ቀን 2018 ጀምሮ መሆኑን እየገለጽን ካርድ ለመውሰድ ስትመጡ የሰኔ ወር የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ደረሰኝ መያዝ እንዳለባችሁ ልንገልጽ እንወዳለን። በተጨማሪም የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ረቡዕ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀመር መሆኑን ልናስገነዝብ እንወዳለን። ሳዌአ አስተዳደር

✨እንኳን ደስ ያለን ሳውዝ ዌስት አካዳሚ (58 ቅርንጫፍ) የ2018 የ8ኛ ክፍል በከተማ አቀፍ ፈተና 100% አሳልፏል!! ይህ ውጤት እንዲመዘገብ ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ ለነበሩ የት/ቤታችን ባለድርሻ አካላትን ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ ልንል እንወዳለን !!✨

የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይሆናል፡፡ (ሰኔ 22/2018 ዓ.ም) የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይሆናል፡፡ (ሰኔ 22/2018 ዓ.ም) የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ነጥቡ ላይ ውይይት ካደረጉ በሃላ ይፋ ይደረጋል። የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ሲሆን የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 11 እና 12 /2018 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለ 85,737 ተማሪዎች መሰጠቱ ይታወሳል፡፡ ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

ለሳዌአ 58 ተማሪዎች ወላጆች /ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ:- የ2018ዓ.ም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ከፍላችሁ ያላጠናቀቃችሁ የዓመቱ የት/ት ጊዜ እየተጠናቀቀ ስለሆነ ውዝፍ ክፍያ እና የሰኔ ወር ክፍያ ያለባችሁ እስከ ነገ ሰኞ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም.  ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ በጥብቅ እናሳስባለን፤        ሳዌአ አስተዳደር

ማስታወሻ:- የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናን በተመለከተ፤ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ሐሙስ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት እስከ 1:30 ተጠቃላችሁ በትምህርት ቤታችን በሳዌአ 58 እንድትገኙ እናሳስባለን። ወላጆችም በተጠቀሰው ሰዓት ተማሪዎች እንዲገኙና ከሰዓት ከ10 ሰዓት ጀምሮ እንድትረከቡ በትህትና እንጠይቃለን። በተጨማሪም በቀጣዩ ቀን ዓርብ ፈተናው ከረፋዱ 5:00 ሰዓት አካባቢ እንደሚጠናቀቅ ልናስታውስ እንወዳለን። የሳዌአ 58 አስተዳደር

አስቸኳይ ማስታወቂያ ከሳዌአ 58 አስተዳደር  ጉዳዩ፡ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍሎች የኦረንቴሽን (ቅድመ-ፈተና ገለጻ) ቀንን ይመለከታል፤   ከሰኞ ሰኔ 8 - 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈታኞች ስለሚጠበቅባቸው ኃላፊነትና ግዴታዎች በፈተና ጣቢያው (መጋቢት 28 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት) በፈተና ሰጪ አካላት ገለጻ (Orientation) ይሰጣል። ስለሆነም ሁሉም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በትምህርት ቤታችን በሳዌአ 58 እንድትገኙ እናሳስባለን።   ⏰  የወላጆችና የተማሪዎች የሰዓት መርሃ-ግብር ክፍል- የኦረንቴሽን ሰዓት- ወላጆች ተማሪዎችን መውሰድ የሚችሉበት ሰዓት 6ኛ ክፍል ጠዋት (በመደበኛ መግቢያ ሰዓት) ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ 8ኛ ክፍል ከረፋዱ 4:30 ሰዓት ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ማሳሰቢያ ለወላጆች፦ ፈተናው ከተማ አቀፍ በመሆኑና ተማሪዎች የሚፈተኑበትን ትምህርት ቤት (መጋቢት 28 ት/ቤት) ሕጎችና ደንቦች አስቀድመው ማወቅ ስላለባቸው ተማሪዎች በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙና ወላጆችም ልጆቻችሁን በተባለው ሰዓት እንድትረከቡ በትህትና እንጠይቃለን። የሳዌአ 58 አስተዳደር

📢 አስቸኳይ ማስታወቂያ ከሳዌአ 58 አስተዳደር 📌 ጉዳዩ፡ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍሎች የኦረንቴሽን (ቅድመ-ፈተና ገለጻ) ቀንን ይመለከታል ከሰኞ ሰኔ 8 - 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈታኞች ስለሚጠበቅባቸው ኃላፊነትና ግዴታዎች በፈተና ጣቢያው (መጋቢት 28 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት) በፈተና ሰጪ አካላት ገለጻ (Orientation) ይሰጣል። ስለሆነም ሁሉም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በትምህርት ቤታችን በሳዌአ 58 እንድትገኙ እናሳስባለን። ⏰ የወላጆችና የተማሪዎች የሰዓት መርሃ-ግብር ክፍልየኦረንቴሽን ሰዓትወላጆች ተማሪዎችን መውሰድ የሚችሉበት ሰዓት6ኛ ክፍል🌅 ጠዋት (በመደበኛ መግቢያ ሰዓት)⏱️ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ8ኛ ክፍል☀️ ከረፋዱ 4:30 ሰዓት🕒 ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ ⚠️ ማሳሰቢያ ለወላጆች፦ ፈተናው ከተማ አቀፍ በመሆኑና ተማሪዎች የሚፈተኑበትን ትምህርት ቤት (መጋቢት 28 ት/ቤት) ሕጎችና ደንቦች አስቀድመው ማወቅ ስላለባቸው ተማሪዎች በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙና ወላጆችም ልጆቻችሁን በተባለው ሰዓት እንድትረከቡ በትህትና እንጠይቃለን። የሳዌአ 58 አስተዳደር 🏫

ማስታወቂያ :- የ6ኛ እና 8ኛ ክፍሎች ኦረንቴሽን ቀንን ይመለከታል፤ ከሰኞ ሰኔ 8-12 ቀን 2018 ጀምሮ የሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና በፈተና ቀናት ተፈታኞች ስለሚጠበቅባቸው ሃላፊነትና ግዴታ ፈተና በሚወስዱበት መጋቢት 28 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በፈተና ሰጪ አካላት "ኦረንቴሽን" ስለሚሰጥ ሁሉም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በት/ቤታችን በሳዌአ 58 እንዲገኙ እናስታውቃለን ። በተጨማሪም የ6ኛ ክፍሎች ኦረንቴሽን ጠዋት ሲሆን ወላጆች እንደጨረሱ ከ ረፋዱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ ከት/ቤት ልትወስዷቸው ትችላላችሁ። የ8ኛ ክፍሎች ኦረንቴሽን ከሰዓት 8:00 ሰዓት ስለሆነ ሙሉ ቀን በት/ቤታቸው የሚቆዪ ይሆናል። ሳዌአ 58 አስተዳደር

የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣ ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ
+1
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች ➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡ ❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡ ➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡ ❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡ ❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡ ❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡ ❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ  በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡ ❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል። ❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡ ➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት  እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡ ⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ ⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም። ⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።

8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ዝግጅት.doc0.25 KB