3 209
订阅者
+224 小时
+167 天
+5030 天
帖子存档
3 209
ሜስታወሻ:- ውድ ወላጆች የተማሪዎች ውጤት ካርድ የሚሰጠው ከሰኞ ሰኔ 29 ቀን 2018 ጀምሮ መሆኑን እየገለጽን ካርድ ለመውሰድ ስትመጡ የሰኔ ወር የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ደረሰኝ መያዝ እንዳለባችሁ ልንገልጽ እንወዳለን። በተጨማሪም የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ረቡዕ ሐምሌ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የሚጀመር መሆኑን ልናስገነዝብ እንወዳለን።
ሳዌአ አስተዳደር
3 209
✨እንኳን ደስ ያለን ሳውዝ ዌስት አካዳሚ (58 ቅርንጫፍ) የ2018 የ8ኛ ክፍል በከተማ አቀፍ ፈተና 100% አሳልፏል!!
ይህ ውጤት እንዲመዘገብ ከፍተኛ ሚና ሲጫወቱ ለነበሩ የት/ቤታችን ባለድርሻ አካላትን ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ ልንል እንወዳለን !!✨
3 209
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት ይፋ ይሆናል፡፡
(ሰኔ 22/2018 ዓ.ም) የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና ውጤት ዛሬ ከሰዓት የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የአጠቃላይ ካውንስል አባላት በማለፊያ ነጥቡ ላይ ውይይት ካደረጉ በሃላ ይፋ ይደረጋል።
የ2018 ዓ.ም የ8ኛ ክፍል መልቀቂያ ከተማ አቀፍ ፈተና በአጭር ጊዜ ታርሞ ይፋ መደረጉ ተማሪዎች ለቀጣዩ የትምህርት አመት ከወዲሁ በቂ ዝግጅት እንዲያደርጉ የሚያስችል ሲሆን የ2018 የትምህርት ዘመን የ8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ሰኔ 11 እና 12 /2018 ዓ.ም በከተማ አስተዳደሩ በሚገኙ 201 የመፈተኛ ጣቢያዎች ለተከታታይ ሁለት ቀናት ለ 85,737 ተማሪዎች መሰጠቱ ይታወሳል፡፡
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
3 209
ለሳዌአ 58 ተማሪዎች ወላጆች /ህጋዊ አሳዳጊዎች በሙሉ:- የ2018ዓ.ም የትምህርት አገልግሎት ክፍያ ከፍላችሁ ያላጠናቀቃችሁ የዓመቱ የት/ት ጊዜ እየተጠናቀቀ ስለሆነ ውዝፍ ክፍያ እና የሰኔ ወር ክፍያ ያለባችሁ እስከ ነገ ሰኞ ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ከፍላችሁ እንድታጠናቅቁ በጥብቅ እናሳስባለን፤
ሳዌአ አስተዳደር
3 209
ማስታወሻ:- የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተናን
በተመለከተ፤
የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ሐሙስ ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ለሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት እስከ 1:30 ተጠቃላችሁ በትምህርት ቤታችን በሳዌአ 58 እንድትገኙ እናሳስባለን።
ወላጆችም በተጠቀሰው ሰዓት ተማሪዎች እንዲገኙና ከሰዓት ከ10 ሰዓት ጀምሮ እንድትረከቡ በትህትና እንጠይቃለን።
በተጨማሪም በቀጣዩ ቀን ዓርብ ፈተናው ከረፋዱ 5:00 ሰዓት አካባቢ እንደሚጠናቀቅ ልናስታውስ እንወዳለን።
የሳዌአ 58 አስተዳደር
3 209
አስቸኳይ ማስታወቂያ ከሳዌአ 58 አስተዳደር
ጉዳዩ፡ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍሎች የኦረንቴሽን (ቅድመ-ፈተና ገለጻ) ቀንን ይመለከታል፤
ከሰኞ ሰኔ 8 - 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈታኞች ስለሚጠበቅባቸው ኃላፊነትና ግዴታዎች በፈተና ጣቢያው (መጋቢት 28 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት) በፈተና ሰጪ አካላት ገለጻ (Orientation) ይሰጣል።
ስለሆነም ሁሉም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በትምህርት ቤታችን በሳዌአ 58 እንድትገኙ እናሳስባለን።
⏰ የወላጆችና የተማሪዎች የሰዓት መርሃ-ግብር
ክፍል- የኦረንቴሽን ሰዓት- ወላጆች ተማሪዎችን መውሰድ የሚችሉበት ሰዓት
6ኛ ክፍል ጠዋት (በመደበኛ መግቢያ ሰዓት) ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ
8ኛ ክፍል ከረፋዱ 4:30 ሰዓት ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ
ማሳሰቢያ ለወላጆች፦ ፈተናው ከተማ አቀፍ በመሆኑና ተማሪዎች የሚፈተኑበትን ትምህርት ቤት (መጋቢት 28 ት/ቤት) ሕጎችና ደንቦች አስቀድመው ማወቅ ስላለባቸው ተማሪዎች በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙና ወላጆችም ልጆቻችሁን በተባለው ሰዓት እንድትረከቡ በትህትና እንጠይቃለን።
የሳዌአ 58 አስተዳደር
3 209
📢 አስቸኳይ ማስታወቂያ ከሳዌአ 58 አስተዳደር
📌 ጉዳዩ፡ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍሎች የኦረንቴሽን (ቅድመ-ፈተና ገለጻ) ቀንን ይመለከታል
ከሰኞ ሰኔ 8 - 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈታኞች ስለሚጠበቅባቸው ኃላፊነትና ግዴታዎች በፈተና ጣቢያው (መጋቢት 28 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት) በፈተና ሰጪ አካላት ገለጻ (Orientation) ይሰጣል።
ስለሆነም ሁሉም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በትምህርት ቤታችን በሳዌአ 58 እንድትገኙ እናሳስባለን።
⏰ የወላጆችና የተማሪዎች የሰዓት መርሃ-ግብር
ክፍልየኦረንቴሽን ሰዓትወላጆች ተማሪዎችን መውሰድ የሚችሉበት ሰዓት6ኛ ክፍል🌅 ጠዋት (በመደበኛ መግቢያ ሰዓት)⏱️ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ8ኛ ክፍል☀️ ከረፋዱ 4:30 ሰዓት🕒 ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ
⚠️ ማሳሰቢያ ለወላጆች፦ ፈተናው ከተማ አቀፍ በመሆኑና ተማሪዎች የሚፈተኑበትን ትምህርት ቤት (መጋቢት 28 ት/ቤት) ሕጎችና ደንቦች አስቀድመው ማወቅ ስላለባቸው ተማሪዎች በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙና ወላጆችም ልጆቻችሁን በተባለው ሰዓት እንድትረከቡ በትህትና እንጠይቃለን።
የሳዌአ 58 አስተዳደር 🏫
3 209
ማስታወቂያ :-
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍሎች ኦረንቴሽን ቀንን ይመለከታል፤
ከሰኞ ሰኔ 8-12 ቀን 2018 ጀምሮ የሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና በፈተና ቀናት ተፈታኞች ስለሚጠበቅባቸው ሃላፊነትና ግዴታ ፈተና በሚወስዱበት መጋቢት 28 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በፈተና ሰጪ አካላት "ኦረንቴሽን" ስለሚሰጥ ሁሉም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በት/ቤታችን በሳዌአ 58 እንዲገኙ እናስታውቃለን ። በተጨማሪም የ6ኛ ክፍሎች ኦረንቴሽን ጠዋት ሲሆን ወላጆች እንደጨረሱ ከ ረፋዱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ ከት/ቤት ልትወስዷቸው ትችላላችሁ። የ8ኛ ክፍሎች ኦረንቴሽን ከሰዓት 8:00 ሰዓት ስለሆነ ሙሉ ቀን በት/ቤታቸው የሚቆዪ ይሆናል።
ሳዌአ 58 አስተዳደር
3 209
+1
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣
➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡
➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ
⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም።
⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።
3 209
ማሳሰቢያ:- የት/ቤት ዝግ ቀናትን ይመለከታል ፤
1) ሰኞ ግንቦት 24/2018 ብሔራዊ ምርጫ ቀን ስለሆነ ትምህርት ቤት ዝግ ይሆናል፣
2) ከማክሰኞ - ረቡዕ ፣ግንቦት 25 እና 26 ቀን ዓ.ም.2018 የፈተና የቅድመ ዝግጅት ስራ ስለሚሰራ ት/ቤት ለተማሪዎች ዝግ ስለሚሆን ተማሪዎች በቤት በሚቆዩበት ቀናት ወላጆች ትምህርታቸው ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ እንድታግዟቸው ለማሰባሰብ እንወዳለን።
3) በቀጣይ ሐሙስ ግንቦት 27ቀን 2018ዓ.ም መደበኛ ት/ት ይቀጥላል።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
