swa 58 primary
Ir al canal en Telegram
3 193
Suscriptores
+424 horas
+367 días
+4130 días
Archivo de publicaciones
3 193
አስቸኳይ ማስታወቂያ ከሳዌአ 58 አስተዳደር
ጉዳዩ፡ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍሎች የኦረንቴሽን (ቅድመ-ፈተና ገለጻ) ቀንን ይመለከታል፤
ከሰኞ ሰኔ 8 - 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈታኞች ስለሚጠበቅባቸው ኃላፊነትና ግዴታዎች በፈተና ጣቢያው (መጋቢት 28 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት) በፈተና ሰጪ አካላት ገለጻ (Orientation) ይሰጣል።
ስለሆነም ሁሉም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በትምህርት ቤታችን በሳዌአ 58 እንድትገኙ እናሳስባለን።
⏰ የወላጆችና የተማሪዎች የሰዓት መርሃ-ግብር
ክፍል- የኦረንቴሽን ሰዓት- ወላጆች ተማሪዎችን መውሰድ የሚችሉበት ሰዓት
6ኛ ክፍል ጠዋት (በመደበኛ መግቢያ ሰዓት) ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ
8ኛ ክፍል ከረፋዱ 4:30 ሰዓት ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ
ማሳሰቢያ ለወላጆች፦ ፈተናው ከተማ አቀፍ በመሆኑና ተማሪዎች የሚፈተኑበትን ትምህርት ቤት (መጋቢት 28 ት/ቤት) ሕጎችና ደንቦች አስቀድመው ማወቅ ስላለባቸው ተማሪዎች በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙና ወላጆችም ልጆቻችሁን በተባለው ሰዓት እንድትረከቡ በትህትና እንጠይቃለን።
የሳዌአ 58 አስተዳደር
3 193
📢 አስቸኳይ ማስታወቂያ ከሳዌአ 58 አስተዳደር
📌 ጉዳዩ፡ የ6ኛ እና 8ኛ ክፍሎች የኦረንቴሽን (ቅድመ-ፈተና ገለጻ) ቀንን ይመለከታል
ከሰኞ ሰኔ 8 - 12 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና ተፈታኞች ስለሚጠበቅባቸው ኃላፊነትና ግዴታዎች በፈተና ጣቢያው (መጋቢት 28 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት) በፈተና ሰጪ አካላት ገለጻ (Orientation) ይሰጣል።
ስለሆነም ሁሉም የ6ኛ እና የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በትምህርት ቤታችን በሳዌአ 58 እንድትገኙ እናሳስባለን።
⏰ የወላጆችና የተማሪዎች የሰዓት መርሃ-ግብር
ክፍልየኦረንቴሽን ሰዓትወላጆች ተማሪዎችን መውሰድ የሚችሉበት ሰዓት6ኛ ክፍል🌅 ጠዋት (በመደበኛ መግቢያ ሰዓት)⏱️ ከረፋዱ 4:00 ሰዓት ጀምሮ8ኛ ክፍል☀️ ከረፋዱ 4:30 ሰዓት🕒 ከቀኑ 6:00 ሰዓት ጀምሮ
⚠️ ማሳሰቢያ ለወላጆች፦ ፈተናው ከተማ አቀፍ በመሆኑና ተማሪዎች የሚፈተኑበትን ትምህርት ቤት (መጋቢት 28 ት/ቤት) ሕጎችና ደንቦች አስቀድመው ማወቅ ስላለባቸው ተማሪዎች በተጠቀሰው ሰዓት እንዲገኙና ወላጆችም ልጆቻችሁን በተባለው ሰዓት እንድትረከቡ በትህትና እንጠይቃለን።
የሳዌአ 58 አስተዳደር 🏫
3 193
ማስታወቂያ :-
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍሎች ኦረንቴሽን ቀንን ይመለከታል፤
ከሰኞ ሰኔ 8-12 ቀን 2018 ጀምሮ የሚሰጠው ከተማ አቀፍ የማጠቃለያ ፈተና በፈተና ቀናት ተፈታኞች ስለሚጠበቅባቸው ሃላፊነትና ግዴታ ፈተና በሚወስዱበት መጋቢት 28 አንደኛ ደረጃ ት/ቤት በፈተና ሰጪ አካላት "ኦረንቴሽን" ስለሚሰጥ ሁሉም የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ተማሪዎች ነገ ዓርብ ሰኔ 5 ቀን 2018 በተለመደው የተማሪ መግቢያ ሰዓት በት/ቤታችን በሳዌአ 58 እንዲገኙ እናስታውቃለን ። በተጨማሪም የ6ኛ ክፍሎች ኦረንቴሽን ጠዋት ሲሆን ወላጆች እንደጨረሱ ከ ረፋዱ 5:00 ሰዓት ጀምሮ ከት/ቤት ልትወስዷቸው ትችላላችሁ። የ8ኛ ክፍሎች ኦረንቴሽን ከሰዓት 8:00 ሰዓት ስለሆነ ሙሉ ቀን በት/ቤታቸው የሚቆዪ ይሆናል።
ሳዌአ 58 አስተዳደር
3 193
+1
የ6ኛ እና 8ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ መልስ መስጫ ወረቀት አጠቃቀም መመሪያ ለተማሪዎች፣
➊ የተማሪዎች መለያ ቁጥር እና የትምህርት ዓይነት መለያ ቁጥር ለእያንዳንዳቸው በተቀመጠው ሳጥን ውስጥ ከላይ ወደ ታች መፃፍ አለበት፡፡
❷ በተፃፈው መለያ ቁጥር ፊት ለፊት የተፃፈውን ቁጥር የያዘውን ክብ ብቻ መጠቆር አለበት፡፡
➌ ተማሪዎች የመረጡትን መልስ ትይዩ በተሰጠው ክብ ላይ በትክክል ማጥቆር አለባቸው፡፡
❹ ተማሪዎች ያጠቆሩትን መልስ መቀየር ቢፈልጉ መጀመሪያ ያጠቆሩትን ክብ በደንብ ማጥፋት አለባቸው፡፡
❺ በአንድ ረድፍ ከአንድ በላይ ክብ ማጥቆር የተከለከለ ነው፡፡
❻ ለመፃፍ እና ለማጥቆር ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ምንም አይነት ፅሁፍም ሆነ ጭረት ማድረግ የተከለከለ ነው፡፡
❼ ለመፃፍ ከተፈቀደው ቦታ ውጭ ተፅፎ ወይም ትንሽ ጭረት እና ነጥብ ከተገኘ የመልስ መስጫ ወረቀቱ ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት አይኖረውም፡፡
❽ መልስ በሚጠቆርበት ጊዜ እርሳሱ ከተሰጠው የክብ ሳጥን መውጣት የለበትም። ከወጣም በማጥፊያ (Eraser/Rubber) ማጥፋት ይጠበቅባችኋል።
❾ መልስ መስጫ ኮርነር ላይ ያሉትን አራት ጠርዞች መንካትም ፈጽሞ የተከለከለ ነው፡፡
➓ ተፈታኞች የመልስ መስጫ ወረቀታቸውን በንፅህና መያዝ አለባቸው ማለትም እንዳይቆሽሽ፣ እርጥበት እንዳይነካው፤ እንዳይቀደድ እና እንዳይታጠፍ መጠንቀቅና ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ አለባቸው፡፡
⓫ በእስክሪብቶ መፃፍ አይፈቀድም። ስለዚህ እርሳስ፣ ላጲስ እና መቅረጫ አይለያችሁ
⓬ ፈተና ጨረስኩ ብሎ አላስፈላጊ የሆነ ነገር፤ ስዕል ወይም ሌላ ከጀርባም ይሁን ከፊት አይፃፍበትም።
⓭ በጣም የተቀረፀ ሹል እርሳስ በምንጠቀም ወቅት ወረቀቱ እንዳይቀደድ መጠንቀቅ አለብን።
3 193
ማሳሰቢያ:- የት/ቤት ዝግ ቀናትን ይመለከታል ፤
1) ሰኞ ግንቦት 24/2018 ብሔራዊ ምርጫ ቀን ስለሆነ ትምህርት ቤት ዝግ ይሆናል፣
2) ከማክሰኞ - ረቡዕ ፣ግንቦት 25 እና 26 ቀን ዓ.ም.2018 የፈተና የቅድመ ዝግጅት ስራ ስለሚሰራ ት/ቤት ለተማሪዎች ዝግ ስለሚሆን ተማሪዎች በቤት በሚቆዩበት ቀናት ወላጆች ትምህርታቸው ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ እንድታግዟቸው ለማሰባሰብ እንወዳለን።
3) በቀጣይ ሐሙስ ግንቦት 27ቀን 2018ዓ.ም መደበኛ ት/ት ይቀጥላል።
¡Ya disponible! Investigación de Telegram 2025 — los principales insights del año 
